የተባበሩት መንግሥታት የንግድና የልማት ጉባኤ ዘገባ
በዓለም ዙሪያ የውጭ ባለሃብቶች ውረታ እጎአ በ2013 አፍሪቃን ጨምሮ አድጓል ። ግን በአፍሪቃ የእድገቱ መጠን ከሌላው የዓለም ክፍል ጋር ሲነፃጸር ዝቅ ያለ ነው ። የተባበሩት መንግሥታት የንግድና የልማት ጉባኤ በምህፃሩ UNCTAD ትናንት ባወጣው ዘገባ መሠረት በዓለም ዙሪያ የመሰረተ ልማት ግንባታና የኩባንያዎች እንቅስቃሴ በ9 በመቶ አድጓል ።