ታኀሳስ ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፊደራል ፍ/ቤት ከወንጀል ነፃ ናቸው በሚል ያሰናበታቸወን ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ  የክልሉ አስተዳደር እና ፀጥታ ነፃ አይደሉም በሚል ባቀረበው አቤቱታ ጉዳያቸው በክልሉ ካቢኔ መታየት ጀምሯል፡፡ የክልሉ ካቢኔ ባደረገው ውይይት ለሁለት የተከፈለ ሲሆን አንደኛው ወገን እንፍታቸው ሲል ሌላው ወገን ደግሞ በምርጫው  ላይ አሉታዊ ተጽኖ ስለሚያሳርፉ መፈታት የለባቸውም በሚል ሲከራከሩ ከቆዩ …

ታኀሳስ ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በትውልድ ኢትዮጵያዊ እና በዜግነት ፊላንዳዊ የሆኑት ከፍተኛ የእርሻ ሳይንቲስት  ዶ/ር የሺጥላ ደገፉ የክብር ሜዳልያውን የተሸለሙት ባለፈው ቅዳሜ ፣ ፊንላንድ 97ኛ አመት የነጻነት በአሉዋን ባከበረችበት ወቅት ነው። ዶ/ር የሺጥላ  ዕጽዋት ከየትና እንዴት በሽታ እንደሚይዛቸው፤ እንዴትስ በውስጣቸው እንደሚተላለፍና በራሳቸውም እንዴት እንደሚከላከሉ ከ23 ዓመታት ምርምር በሁዋላ  ሂደቱን ለመጀመሪያ ጊዜ በማግኝታችው ነው። …

“ዘ ጋርዲያን” (The Guardian) በተሰኘው ታዋቂ ጋዜጣ እ.አ.አ ነሐሴ 15 ቀን 2006 እንደ ተዘገበው፤ የጀርመን መንግሥትን በመወከል፤ ወ/ሮ ሔይደማሪ ዊዞረክ-ዜዩል (Mrs. Heidemarie Wieczorek-Zeul)፤ የጀርመን የልማት ሚኒስትር፤ ሐገራቸው እ.አ.አ. በ1904 በናሚቢያ ነዋሪዎች (ሔሬሮዎች) ላይ ስለ ፈጸመችው የዘር ማጥፋት ወንጀል ይቅርታ ጠይቀዋል። ለዚህም ወንጀል፤ ናሚቢያውያን (ሔሬሮዎች) ከይቅርታ መጠየቁ በተጨማሪ $4 ቢሊዮን ካሣ እንዲከፈል የጀርመን መንግሥትን መጠየቃቸው ተገልጿል። […]

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህርና በማኅበረ ቅዱሳን የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል ሓላፊ የሆኑት ዲ/ን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ ከጥቂት ወራት በፊት በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣና በማኅበረ ቅዱሳን ድረ ገጽ ላይ በተከታታይ ‹‹የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዘወርት›› በሚል ዐቢይ ርእስ ያቀረቡትን ጥናታዊ ጽሑፋቸውን ተከታትያለኹ፡፡ ዶ/ር መርሻ በተለይም ደግሞ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በዓለም የክርስትና መድረክ የነበራትንና አሁንም ያላትን ልዩ […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

——
   የክፍለ ሀገር ልጅ ነኝ (በአሁኑ አጠራር የ“ክልል” ልጅ ሆኛለሁ)፡፡ የክፍለ ሀገር ልጅ መሆኔም ብዙ ጥቅም አስገኝቶልኛል፡፡ የክፍለ ሀገር ልጅ መሆኔ ቅር የሚያሰኘኝ በአንድ ነገር ብቻ ነው፡፡ ይህም በልጅነቴ የዓለም ዋንጫን በቀጥታ ስርጭት ለማየት አለመታደሌ ነው፡፡ የዚህም ምክንያት ከተማችን በዚያ ዘመን የቴሌቪዥን ስርጭት ያልነበራት መሆኑ ነው፡፡ በዚያ ዘመን በሰፊው የሀረርጌ ክፍለ ሀገር ውስጥ ከሚገኙት ከተሞች መካከል ቴሌቪዥን የነበራቸው ሀረር፣ ድሬ ዳዋ እና ጅጅጋ ብቻ ናቸው (እነዚህኛዎቹ ክፍለ ሀገር አይባሉም ማለት ነው)፡፡ ዛሬ የሳተላይ ዲሽ እንዲህ በየገጠሩ መበተኑ ላይቀር የደርግ መንግሥት ከሳተላት ዲሽ የሚከፈለውን የቀረጥ ክፍያ ከጣሪያ በላይ እየሰቀለ እኛን በመበደሉ የስራውን ይስጠው እላለሁ (ለነገሩ የአሁኑ መንግሥትም ቢሆን ከጭሮ ከተማ በስተቀር ለሌሎቹ የምስራቅ ኢትዮጵያ ከተሞች የቴሌቪዥን አንቴና አልተከለም፡፡ ኮንትሮባንድ ነው ቶሎ ከተፍ ብሎ ከልጓሙ የገላገለን!! እድሜ ለኮንትሮባንድ! እድሜ ለሀርቲሼክ መንገድ! እድሜ ለቶጎጫሌ መንገድ! ቂቂቂቂቂቂ)
    ——
   የዓለም ዋንጫ የሚባል የውድድር ዓይነት መኖሩን ያወቅኩት የማራዶና ስም በየልብሱ ላይ ታትሞ በመውጣቱ ይመስለኛል፡፡ ነገር ግን ከላይ በገለጽኩት ምክንያት በልጅነት ዘመኔ የተካሄዱትን ሁለት የዓለም ዋንጫዎች በቀጥታ ስርጭት ለማየት አልታደልኩም፡፡ እነርሱም የአጣሊያው የዓለም ዋንጫ (1990) እና የአሜሪካው የዓለም ዋንጫ (1994) ናቸው፡፡ (ከዚያ በፊት የነበሩት ሁለት የዓለም ዋንጫዎች እኔ ከተወለድኩ በኋላ የተካሄዱ ቢሆኑም ዕድሜዬ ገና ስለነበረ እንዳለፉኝ አድርጌ አልቆጥራቸውም)፡፡
 
   ይሁን እንጂ ሁለቱንም የዓለም ዋንጫዎች ተከታትያቸኋለሁ፡፡ የቀጥታው ስርጭት ቢያመልጠኝም ጨዋታዎቹን በሁለት ቀናት ልዩነት በቪዲዮ ካሴት እናያቸው ነበር፡፡ ለዚህ የረዳችን የሁል ጊዜ መኩሪያችን የሆነችው ድሬ ዳዋ ናት፡፡ በዚህም መሰረት ዛሬ የተካሄደው ውድድር በድሬ ዳዋ በካሴት ይቀዳና በማግስቱ ወደ ገለምሶ ከች ይላል፡፡ እኛም በሚቀጥለው ቀን ሲቻል ወደ ሀብሮ አውራጃ አኢወማ መዝናኛ ማዕከል፣ ካልተቻለ ደግሞ “ፎቶ ማወርዲ” ከሚባለው ታዋቂ ፎቶ ቤት በመሄድ ጨዋታውን እየተስገበገብን እናየዋለን፡፡ በዚህ ዓይነት በውድድሩ ከተካሄዱት ጨዋታዎች መካከል ቢያንስ ግማሽ ያህል የሚሆኑትን አይቻለሁ፡፡ ድሬ ለዚህ ባለውለታችን ናት፡፡ ማን እንደ ድሬ!! (ቀሽቲ እኮ ናት)፡፡
——–                                          
     በቪዲዮ የምናየውን ጨዋታ ውጤት በቅድሚያ እናውቀዋለን፡፡ በዚያ ላይ ደምሴ ዳምጤ በአደገኛ ምላሱ እያጣፈጠ የሚሰራቸው ዘገባዎች አያመልጡንም፡፡ የአዲስ ዘመንና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦችንም እንከታተላለን፡፡ በ1986 ደግሞ የግል ጋዜጦችም ተጀምረው ስለነበረ እየተሻማን እናነባቸው ነበር፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ ቅድመ-መረጃ በቪዲዮ የተቀዳልንን ጨዋታ ጣዕም አያደፈርስብንም፡፡ እንዲያውም ደምሴ በዘገባው የጠቀሳቸውን ነጥቦች በጨዋታው ውስጥ ለመመልከት ስንል በከፍተኛ ተመስጦ ውስጥ እንገባለን፡፡
  ታዲያ ዘወትር የሚገርመኝ አንድ ነገር አለ፡፡ ያለፉትን አምስት የዓለም ዋንጫዎችን በቀጥታ ስርጭት ነው ያየኋቸው (እግር ኳስን በቀጥታ ማየት የጀመርኩት እንደኛ አቆጣጠር በ1988 በተካሄደው የEuro-96 ወቅት ነው፡፡) ቢሆንም እነዚህ በቀጥታ ስርጭት ያየኋቸው ጨዋታዎች ያኔ በቪዲዮ እየተቀዱ ከሁለት ቀናት በኋላ የምናያቸውን ጨዋታዎች ያህል አይጣፍጡኝም፡፡ ጎሉም ሆነ ጨዋታው፣ ተጫዋቹም ሆነ ቡድኖቹ፣ አሰልጣኙም ሆነ ዳኛው ያኔ በልብ ላይ ይቀራል፡፡ ከዚያ ወዲህ ግን ሁሉም ነገር ተለውጧል፡፡ በተለይም ባለፉት ሁለት የዓለም ዋንጫዎች ካየኋቸው ክስተቶች አንዳቸውም በአዕምሮዬ ውስጥ የሉም፡፡ ውጤቱንም ብትጠይቁኝ ልነግራችሁ አልችልም (እ.ኤ.አ በ2006 በተካሄደው የዓለም ዋንጫ ዚነዲን ዚዳን ካሳየው ጣፋጭ ፉት ቦልና በፍጻሜው ጨዋታ ማቴራዚን በቴስታ ደረቱ ላይ መቶት ከመጣሉ ውጪ ማለቴ ነው)፡፡
በዚህ ጽሑፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁትን የዓለም ዋንጫ አስቃኛችኋለሁ፡፡ የአሜሪካውን የዓለም ዋንጫ በሌላ ጽሐፍ እመጣበታለሁ፡፡
==== 14ኛው የዓለም ዋንጫ በኢጣሊያ (Italy-1990)===
በኢጣሊያ የተካሄደው 14ኛው የዓለም ዋንጫ በእግር ኳስ ኤክስፐርቶች በጣም አሰልቺ የተባለለት ነው፡፡ በያንዳንዱ ውድድር የገቡት ጎሎች በአማካይ ከሁለት አይበልጡም፡፡ ቢሆንም ግን ያኔ ሁሉም ነገር እየጣፈጠን ነው ያየነው፡፡ ለኛ አሰልቺና አስቀያሚ የሆነብን የመጨረሻው ጨዋታ ብቻ ነው፡፡ በዚያ ጨዋታ ዳኛው ብዙ ቢጫና ቀይ ካርዶችን ማሳየታቸው ሳያንሰን አጨቃጫቂ “ሪጎሬ” ሰጥተው የጨዋታውን ስሜት አበላሹብን፡፡
  በዚያ የዓለም ዋንጫ የተካሄዱትን ጨዋታዎች በተመለከተ ዝርዝር ዘገባውን ከኢንተርኔት ስለምታገኙት እዚያ ውስጥ አልገባም፡፡ እኔ እዚህ የማደርገው ከአዕምሮዬ ያልጠፉ ክስተቶችንና ስብዕናዎች ማሳወቅ ነው፡፡
·        አስደሳቹ መጽሐፍ  
በውድድሩ ዋዜማ በጣም ተወዳጅ የሆነ አንድ መጽሐፍ ታትሞ ነበር፡፡ ርዕሱ “እግር ኳስ፤ ፊፋ እና የዓለም ዋንጫ” ይሰኛል፡፡ በአማርኛ ቋንቋ በስፖርት ዙሪያ ከተዘጋጁ መጻሕፍት እንደርሱ የሚማርከኝ የለም፡፡ ያ መጽሐፍ በርካቶቻችን እግር ኳስን እንድንወደው አስተዋጽኦ ያደረገ ይመስለኛል፡፡ በዓለም ዋንጫውን በንቃት እንድንመለከት ያስቻሉን መረጃዎችንም ሰጥቶናል፡፡ ያንን መጽሐፍ ያዘጋጁት የአዲስ ዘመን ጋዜጣ የስፖርት አምድ አዘጋጆች የነበሩት ግርማ ሰይፉ እና ፋንታሁን ሀይሌ ናቸው፡፡
ታዲያ ያ መጽሐፍ በአንድ ነገር አቀዣብሮኛል፡፡ መጽሐፉ በዝርዝር የሚያወሳቸውን እውቅ ተጫዋቾች በዓለም ዋንጫው ላይ የማያቸው መስሎኝ በጉጉት ስጠብቃቸው ነበር፡፡ በተለይም በ13ኛው የዓለም ዋንጫ ወቅት የተጫወቱትን ተጫዋቾች በናፍቆት እየጠበቅኳቸው ነው ውድድሩ የተጀመረው፡፡ ነገር ግን ብዙዎቹ የውሃ ሽታ ሆነው ቀሩ፡፡ ጥቂቶቹ ብቻ (ማራዶና፣ ቡርቻጋ፣ ቫንባስተን፣ ሩድ ጉሌት፣ ካሬካ፣ ጋሪ ሊነከር፤ ጆን ባርነስ፣ ሎታር ማትያስ፣ ሩዲ ቮለር ) በውድድሩ ውስጥ ነበሩ፡፡ የብራዚሉን ፓውሎ ሮቤርቶ ፋልካኦን ደግሞ ለተጫዋችነት ስጠብቀው አሰልጣኝ ሆኖ አገኘሁት፡፡
·        የአጂፕ ኩባኒያ ውለታ፡
ጨዋታው በጣሊያን ሀገር የተካሄደ በመሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ስርጭቱን ለማስተላለፍ ስፖንሰር የሆነው የኢጣሊያ ኩባኒያ የሆነው አንጋፋው ነዳጅ አቅራቢ “አጂፕ” ነው፡፡ ያኔ በየጨዋታው መሀል ሲነገር ከነበረው ማስታወቂያ እንደሰማሁት “አጂፕ” በኢትዮጵያ ውስጥ 120 የማደያ ጣቢያዎች ነበሩት፡፡ እስከ አሁን ድረስ ቢኖር ኖሮ 1200 ጣቢያዎች ሳይኖሩት ይቀራል?  
·        የካሜሩን ጉዞ

በዓለም ዋንጫው እጅግ ከፍተኛ ደስታ የፈጠረልን የካሜሩን አስደናቂ ጀብድ ነው፡፡ አርጀንቲናን፣ ሩማኒያንና ኮሎምቢያን ያሸነፈባቸው ጨዋታዎች ከማንም አዕምሮ ውስጥ አይጠፉም፡፡ ሮጀር ሚላ፣ ኦማም ቢይክ፣ ማካናኪ እና በረኛው ቶማስ ንኮኖ የዘወትር ትዝታዎቻችን ናቸው፡፡ ይሁንና ለዋንጫው በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ያ አስደሳች ቡድን በእንግሊዝ ጉድ ተሰራና ከመንገድ ላይ ቀረብን፡፡
ያ ጨዋታ ከፍተኛ የዳኛ ተጽእኖ የታየበት መሆኑ አሌ አይባልም፡፡ ካሜሩን እንግሊዝን በሁለት ለአንድ እየመራ ወደ መጨረሻው ደረሰ፡፡ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ስምንት ደቂቃ ብቻ ሲቀረው ዳኛው የፍጹም ቅጣት ምት ለእንግሊዝ ሰጡ፡፡ በዚህም እኩል ሆኑ፡፡ በጭማሪው ሰዓትም ዳኛው በድጋሚ ለእንግሊዝ ሪጎሬ ሰጡና አፍሪቃዊያንን የባሰ አሳረሩ፡፡ ተቃጠልን ነው የምላችሁ!! በጣም ሚያሳርረው ደግሞ እነዚያን ሁለት ከይሲ ጎሎች ያስቆጠረው ከላይ የጠቀስኩትን መጽሐፍ አንብቤ በጉጉት ስጠብቃቸው ከነበሩት ተጫዋቾች አንዱ የነበረው እንግሊዛዊው ጋሪ ሊነከር መሆኑ ነው (ጋሪ ሊነከር በሜክሲኮ በተካሄደው 13ኛው የዓለም ዋንጫ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ነው የጨረሰው)፡፡
   ለኳስ እንደዚያ የተናደድኩበት ጊዜ የለም፡፡ ከኔ በላይ ደግሞ ኳስ አፍቃሪው ኢትዮጵያዊ ህዝብ እርር ነው ያለው፡፡ ታዲያ ጨዋታውን በቪዲዮ ማየት እንደጀመርን (“ቪዲዮው ተቀድቶ የሚመጣልን የጨዋታው ውጤት ከታወቀ በኋላ ነው” ያልኳችሁን አትዘንጉ) ማን እንደፈጠረው የማይታወቅ ወሬ በከተማችን ተዛምቶ ነበር፡፡ “ዳኛው ተጽእኖ ያደረገ መሆኑ ስለተረጋገጠ ጨዋታው ይደገማል” የሚል፡፡ ይህ ወሬ እውነት ነው ብለን ስንጠብቅ ከሁለት ቀን በኋላ እንግሊዝ ከጀርመን ጋር ትጫወታለች ተብሎ ተነገረ፡፡ እንደገና እርር!! እንደገና መቃጠል!! ደግነቱ ጀርመንና ጣሊያን እንግሊዝን ቀጥተውልናል፡፡
·        የማይረሱ ጨዋታዎች
የዓለም ዋንጫው የግብ ድርቅ ስላጠቃው “ወዝ የለውም” ይባል እንጂ ዘወትር ከሰው ህሊና የማይጠፉ ምርጥ ጨዋታዎችንም አይተንበታል፡፡ አርጀንቲናና ሩማኒያ፣ ካሜሩንና ኮሎምቢያ፣ ጀርመንና ኮሎምቢያ፣ ኢጣሊያና ቼኮዝሎቫኪያ፣ ብራዚልና ስዊድን፤ አርጀንቲና እና ኢጣሊያ፣ ጀርመንና ሆላንድ፣ አየርላንድና ሩማኒያ በጣም ጥሩ ጨዋታ አሳይተውናል፡፡
·        እጅግ ምርጥ ጨዋታ
ከላይ ከጠቀስኳቸው ጨዋታዎች ይበልጥ ሁሉንም ሰው ቁጭ ብድግ ያደረገው የአርጀንቲናና ብራዚል ጨዋታ ይመስለኛል፡፡ ከምድቡ ሶስቱንም ጨዋታዎች በአሸናፊነት ያጠናቀቀው ብራዚል ካሜሩንን እንኳ ማሸነፍ ባቃተው የአርጀንቲና ቡድን ተረታ፡፡ ለዋንጫ የጠበቅነው ቡድን ስለነበረ ልባችን ነው የተቆረጠው፡፡
·         አስደሳች ተጫዋቾች
 የሩማኒያው ጆርጅ ሃጂ፣ የአርጀንቲናዎቹ ዲየጎ ማራዶና እና ክላውዶ ካኒንጃ፣ የካሜሩኖቹ ሮጀር ሚላ እና ማካናኒ፣ የብራዚሎቹ ካሬካ፣ አሊማው እና ሙለር፣ የኢጣሊያዎቹ ሳልቫቶሬ ሺላቺ እና ሮቤርቶ ባጂዮ፣ የቼኮዝሎቫኪያው ቶማስ ስኩራቪ፣ የስፔኑ ሚሼል፣ የእንግሊዞቹ ጋሪ ሊነከር እና ፖል ጋስኮኝ፣ የእንግሊዙ በረኛ ፒተር ሼልተን፣ የጀርመኖቹ ሎታር ማትያስ እና ሩዲ ቮለር በጣም ምርጥ ተጫዋቾች ነበሩ፡፡  

·        የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች
በዚያ የዓለም ዋንጫ ላይ ካየኋቸው ተጫዋቾች መካከል ኮከብ ነው ብዬ የምመርጠው የኮሎምቢያውን ካርሎስ ቫልዴራማን ነው፤ በለው! በለው! አቤት ጨዋታ! አቤት ታክቲክ! አቤት አብዶ መስራት፣ ወይኔ! ወይኔ! (ወደዳችሁም ጠላችሁም ኳስ ድሮ ቀረ አቦ!)
ቫልዴራማ ኳስ ሲይዝ አስማት በሉት! ሜዳው ጠቦት ይሸከረክርበታል፡፡ በተለይም የጀርመን ተጫዋቾችን እያጥበረበረ ሲያታልላቸው ሁኔታው ሁሉ ነፍስ ግቢ ነፍስ ውጪ ሆኖባቸው ነበር፡፡ የካሜሩን ቡድንም ኮሎምቢያን አሸንፎ ወደ ሩብ ፍጻሜ ለማለፍ የቻለው በረኛው ቀሽም በመሆኑ እንጂ በኮሎምቢያ ቡድን ድክመት አይደለም፡፡ ቫልዴራማ በዚያ ጨዋታም ላይ ኮከብ ሆኖ ነበር የዋለው፡፡ ቫልዴራማ እ.ኤ.አ. በ1987 የላቲን አሜሪካ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ ተመርጦ ነበር (በ1986 ኮከብ የሆነውን ማራዶናን በልጦ ማለት ነው)፡፡
·        ምርጥ ወጣት ተጫዋቾች
በዚያን ጊዜ ለጨዋታው ልጅ እግር ከሆኑት መካከል በጣም ያስደሰቱኝ ሁለት ወጣቶች ናቸው፡፡ አንደኛው የስዊድኑ ቶማስ ብሮሊን ነው፡፡ ቡድኑ ሁሉንም ጨዋታዎች ተሸንፎ ከምድቡ ቢባረርም ብሮሊን በአጨዋወቱ ማንንም ነበር ያስደሰተው፡፡ ደግሞም በብራዚል ላይ አንድ ግብ አስቆጥራል (ብሮሊን በቀጣዩ የዓለም ዋንጫ ሶስተኛ ኮከብ ሆኗል)፡፡
   ሌላኛው የኢጣሊያው ሮቤርቶ ባጅዮ ነው፡፡ ሮቤ ለኢጣሊያ ሁለት ጎሎችን በማስቆጠር አያያዙ አደገኛ መሆኑን አስመሰክሯል፡፡ እነዚህ ሁለት ተጫዋቾች በኢጣሊያው “ሴሪ አ” ተገናኝተው ምርጥ ፉት ቦል አሳይተውናል፡፡
·        የማይረሱ ተጫዋቾች
1.      ሬኔ ሂጉታ፡
የኮሎምቢያ በረኛ ነው፡፡ በሁኔታዎቹ ሁሉ እብድ በሉት፡፡ ኳስ በእግሩ እንጂ በእጁ ለመያዝ ይጠየፋል፡፡ ሲያቀብል በእግር! ሲቀበልም በእግር! በዚያ ሁኔታው ኮሎምቢያ ለሁለተኛው ዙር ማለፉ አስደናቂ ነበር፡፡ የሂጉታን እብደት ያጠናው የካሜሩኑ ሮጀር ሚላ ግን ሳያስበው ጉድ ሰራው፡፡ አቤት የያኔው የአፍሪካ ደስታ! አቤት የሚላ ዳንስ!! (አቤት የደምሴ ዳምጤ አዘጋገብ)!
2.     የአርጀንቲናው በረኛ፡
ስሙን ዘንግቼዋለሁ፡፡ ሁለተኛ በረኛ ሆኖ ነበር ወደ ኢጣሊያ የሄደው፡፡ ነገር ግን ዋናው በረኛ ከሶቪየት ህብረት ጋር በተደረገው ጨዋታ በመጎዳቱ እርሱን ተክቶ ወደ ጨዋታው ገባ፡፡ ከዚያ በኋላ ማን ይቻለው!!? በተለይም ኢጣሊያ በደጋፊዎቿ ፊት ተጫውታ በመለያ ምቶች በአርጀንቲና ስትሸነፍ የበረኛው አስተዋጽኦ ሌላ ነው፡፡ (ያኔ የውድድሩ ኮከብ በረኛ ምርጫ ባይደረግም ከሁሉም የሚበልጠው እርሱ ይመስለኛል)፡፡   
·        ምርጥ ግብ አዳኞች
1.      ቶማስ ስኩራቪ (ቼኮዝሎቫኪያ)፡
በሁለተኛው ዙር በኮስታሪካ ላይ የሰራውን ሀትሪክን ጨምሮ አምስት ጎሎችን ነው ያስቆጠረው፡፡ ሁለቱን ጎሎች ያስቆጠረው ቼኮዝሎቫኪያ አሜሪካን 5-1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ቼኮዝሎቫኪያ አሜሪካን ማሸነፏ ሶሻሊዝም በኢምፔሪያሊዝም ላይ የተጎናጸፈው ድል ተደርጎ ስለተወሰደ የአውራጃችን አኢወማ መሪዎች ከደስታ ብዛት ማበድ ነው የቀራቸው (ትልቋ ሶቪየት ህብረት በአርጀንቲና መሸነፏን ያልሰሙ ይመስል ጉራው ሌላ ነበረ)፡፡
  ፖለቲካው ሌላ ነው፡፡ ቶማስ ስኩራቪ ግን ያለምንም ማጋነን ነፍስ የሆነ ተጫዋች ነበረ፡፡ ጎል ለማግባት የተፈጠረ አጥቂ ነው፡፡ ይሁንና ከዚያ የዓለም ዋንጫ በኋላ በድጋሚ አላየሁትም (እነ ጆርጅ ሃጂንና ካርሎስ ቫልዴራማን ግን በድጋሚ ለማየት ችለናል)፡፡
2.     ሚሼል (ስፔን)
በጣም ጎበዝ አጥቂ ነበር፡፡ በምድብ ማጣሪያው በደቡብ ኮሪያ ላይ ሀትሪክ ሰርቷል፡፡ በቤልጅግም ላይ አንድ ግብ አስቆጥሯል፡፡
3.     ካሬካ  እና ሙለር (ብራዚል)፡
 አቤት ጨዋታ! አቤት ፍጥነት!! አቤት ዳንስ! በህይወቴ ካየኋቸው አስደሳች ተጫዋቾች መካከል ናቸው፡፡ ሁለቱም በጥምረት የሚያጠቁ ሲሆን ብራዚል ያስቆጠረቻቸውን አራት ግቦች ያገቡት እነርሱ ናቸው፡፡
    ካሬካ በስዊዲን  ላይ ሁለት ጎሎችን ካስቆጠረ በኋላ በቢጫ ማሊያው የደነሰው “ሳንባ” ዳንስ መቼም ቢሆን የሚረሳኝ አይሆንም፡፡ አስራ አንድ ቀጥሩ ሙለርም በኮስታሪካና በስኮትላንድ ላይ አንዳንድ ግቦችን አስቆጥሮ ቡድኑን ወደ ሁለተኛው ዙር አሸጋግሮታል፡፡
4.     ሮጀር ሚላ (ካሜሩን)፡
 ዓለም በሙሉ ነበር የተደነቀበት፡፡ በዓለም ዋንጫ በ38 ዓመቱ ተሰልፎ ከአዕምሮ የማይጠፉ ግቦችን ለማስቆጠር የቻለ ሰው እርሱ ብቻ ይመስለኛል (ይህ ሪከርድ ከአራት ዓመት በኋላ በራሱ ተሰብሯል)፡፡ የሚደንቀው ነገር ሮጀር ሚላ ግቦቹን ያገባው ከእረፍት በኋላ ተቀይሮ እየገባ ነው፡፡ በሩማኒያ እና ኮሎምቢያ ላይ ሁለት ሁለት ጎሎችን ካስቆጠረ በኋላ የደነሰው ዳንስ የሁሉም አፍሪቃዊ ትዝታ ነው (ደምሴ ዳምጤ ጨዋታዎቹን ሲዘግባቸው አፍ ያስከፍት ነበር)፡፡ ታዲያ እስከ አሁን ድረስ ያልገባኝ ነገር ሰውዬው ሮጀር ሚላ ሆኖ ቴሌቭዥኑ “ሚለር” (Miller) እያለ የሚጠራው መሆኑ ነው፡፡
5.     ሳልቫቶሬ ሺላቺ (ኢጣሊያ)
አስገራሚ ብቻ ሳይሆን የዘረኝነትን መጋረጃ የደመሰሰ ተጫዋች ነው፡፡ በሲሲሊ ደሴት ላይ ከምትገኘው የፓሌርሞ ከተማ ተወልዶ የሀብታሞቹን የሰሜን ኢጣሊያ ልጆች ለመብለጥ የቻለ ነው፡፡ ከሰሜናዊ ኢጣሊያ ከተሞች (ሚላን፣ ቶሪኖ፣ ሮማ፣ ፍሎሬንስ፣ ቬኒስ፣ ወዘተ…) የተገኙ ሰዎች በነርሱ እይታ “ደሀ” የሚባሉትን የሲሲሊና የሳርዲኒያ ሰዎችን ያለ ልክ ይንቋቸዋል፡፡ በሁሉም ነገር አንደኛ እኛ ነን ይላሉ፡፡ ሺላቺ ግን ሳይወዱት በግድ ወደ ውስጣቸው እንዲመለከቱ አደረጋቸው፡፡
  
  ይህ ተጫዋች ኢጣሊያ ባደረገቻቸው ሰባት ግጥሚያዎች ላይ ስድስት ግብ አስቆጥሯል፡፡ በዚህም የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ በመሆን የወርቅ ጫማ ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል፡፡ ይሁንና ከውድድሩ በኋላ በኢጣሊያ ውስጥ በዘላቂነት ሊጫወት አልቻለም፡፡ ለረጅም ጊዜ ከኢጣሊያ ተሰዶ ለጃፓን ቡድኖች ይጫወት እንደበረ አውቃለሁ፡፡ አሁን ምን ላይ እንደደረሰ አላውቅም፡፡
  
·        የማይረሱ ጎሎች
1.      ከሮጀር ሚላ ጎሎች መካከል በሬኔ ሂጉታ ላይ ያስቆጠራት ሁለተኛዋ ጎል በዓለም የፉትቦል ተመልካቾች ዘንድ ዘወትር የምትታወስ ትመስለኛለች፡፡
2.     የቼኮዝሎቫኪያው ቶማስ ስኩራቪ በኮስታሪካ ላይ ያስቆጠራቸው ሶስት ጎሎችም አይረሱም፡፡
3.     የአርጀንቲናው ክላውዶ ካኒንጃ ብራዚልን ከጨዋታ ውጪ ያደረገችውን ጎል አስቆጥሮ ስንቱን አስለቀሰ?… ወይኔ ብራዚል! እንደዚያ ምርጥ ጨዋታ እየተጫወተ በመንገድ ላይ ቀረብን!
4.     የኮሎምቢያው ፍሬዲ ሪንኮን በጀርመን ላይ ያስቆጠራት ግብ ፈጽሞ አትረሳም፡፡ ያ ጨዋታ ግብ አልባ ሆኖ ወደ መጠናቀቁ ሲቃረብ ጀርመኖች በ88ኛው ደቂቃ ላይ አንድ ጎል አገቡ፡፡ በዚህም ኮሎምቢያ ያለቀለት መሰለ፡፡ ከዓለም ዋንጫ ሊባረር የሚባረርበት ጊዜ ቀረበ፡፡ ነገር ግን ካርሎስ ቫልዴራማ ብልሃቱን አምጥቶ ያገኛትን ኳስ አስተካክሎ ለፍሬዲ ሬንኮን አቀበለ፡፡ ሬንኮንም የአቻነቷን ጎል አስቆጠረ፡፡ ኮሎምቢያም በአንደኛው ዙር ከመባረር ተርፋ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈች፡፡
·        ኮከብ አሰልጣኝ
የጀርመኑ ፍራንዝ ቤከንባወር ኮከብ አሰልጣኝ ሆኖ መመረጡ ትክክል ይመስለኛል፡፡ ቡድኑ አንድም ጨዋታ ሳይሸነፍ ለዋንጫ ደርሶለታልና፡፡ እኛም ጀግናውን ቤከንባወርን በተጫዋችነት ዘመኑ ለማየት ባይቻለንም በአሰልጣኝነቱ በማየታችን እድለኞች ነን፡፡
·       የማይረሳው አሰልጣኝ
የአርጀንቲና አሰልጣኝ ካርሎስ ቢላርዶን ማንም የሚረሳው አይመስለኝም፡፡ ቢላርዶ ከሌሎቹ አሰልጣኞች የሚለይበት ነገር አሰልጣኞች ከሚቀመጡበት ወንበር ላይ በመነሳት ወደ ሜዳው እየሄደ ለተጫዋቾቹ እየጮኸ ምክር ቢጤ የሚለግስ መሆኑ ነው፡፡ ያኔ በተመለከትኳቸው ጨዋታዎች ሁሉ አሰልጣኞች ከወንበራቸው ሲነሱ አላየኋቸውም፡፡ ካርሎስ ቢላርዶ ግን ከተጫዋቾቹ እኩል ነበር የሚንቀሳቀሰው፡፡
በቀጣዮቹ የዓለም ዋንጫዎች ግን ያ ልማድ ተቀየረ፡፡ ሁሉም አሰልጣኝ ከወንበር እየተነሳ የሚመክር በመሆኑ ወንበር ላይ ተቀምጦ ጨዋታውን የሚያይ አሰልጣኝ ጠፋ (እኔ እንደታዘብኩት ከዚያ ወዲህ ካየኋቸው አሰልጣኞች መካከል ጨዋታው ከተጀመረ በኋላ የተለየ እንቅስቃሴ የማያሳዩት የሞሮኮ ቡድንን ለረጅም ጊዜ ሲያሰልጥኑ የነበሩት ሄንሪ ሚሼል እና በ2002 የኮሪያ-ጃፓን የዓለም ዋንጫ ሴኔጋልን ያሰለጠኑት ብሩኖ ሚትሱ ናቸው፡፡ ( ሄንሪ ሚሼል ቁጭ ብሎ ማስቲካውን ያኝካል፤ ጎል ከገባበት ግን ይናደድና ሲጋራውን ያቀጣጥላል፤ ብሩኖ ሚትሱ ደግሞ እጆቻቸውን በማጣመር ይቆሙና ይተክዛሉ)፡፡  
·        የጨዋታው ማስታወሻ
የዓለም ዋንጫው ከተጠናቀቀ በኋላ ብሄራዊ ሎተሪ ውድድሩን አጠቃልሎ የሚዘግብ ፖስተር በማሳተም አስደሰተን፡፡ የፖስተሩ አብዛኛው ክፍል ለሩብ ፍጻሜ የደረሱትን ስምንት ቡድኖችና የውድድሩ ቅመሞች የነበሩትን ምርጥ ተጫዋቾች በፎቶግራፍ ያሳያል፡፡ ከታች ደግሞ በውድድሩ የተከናወኑ ጨዋታዎች ውጤት በሰንጠረዥ ተጠቃልሎ ቀርቧል፡፡ ብሄራዊ ሎተሪ ፖስተሩን በነጻ ለማሰራጨት ያዘጋጀው ይመስለኛል፡፡ ይሁን እንጂ ለማንም ሰው በነጻ ሲሰጥ አላየሁም፡፡ ሁሉም ሰው በብር እየገዛው ነው በቤቱ ሲለጥፈው የነበረው፡፡ ያ ልምድ በቀጣዩ የዓለም ዋንጫም ተደግሟል፡፡ በዚህ ዘመን ያለው አሰራር ግን ሌላ ነው፡፡ የውድድሩን ፕሮግራሞች ለማሳየት በሚል ከጨዋታው በፊት የተዘጋጁ እንጂ የዓለም ዋንጫ ከተጠናቀቀ በኋላ የሚዘጋጅ የማስታወሻ ፖስተር አላየሁም፡፡

Read more ›

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በምዕራቡ ሀገራት የግድግዳ ጡፍ ወይም ግራፊቲ እንደ ተመልካቹ እና ማህበረሰቡ አተረጓጎም ይለያያል። አንዳንዶች ግራፊቲን ከውንብድና ጋር ሲያገናኙ ሌሎች ስሜት የሚገለፅበት አንድ መንገድ እንደሆነ ይናገራሉ። ሐዋሳ ከተማ የሚገኙ የተወሰኑ ወጣቶች የግድግዳ ጡፍን እንደ አንድ የስዕል ጥበብ ነድፈው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ።

ናይጀሪያ በመጪዉ በምታካሂደዉ የምርጫ ፉክክር ለፕሬዝደንትነት የሚወዳደሩት እጩዎች ማንነት ታወቀ። ዋናዉ ተቃዋሚ ፓርቲ የእድገት ኃይሎች ምክር ቤት በምርህፃሩ APC በጡረታ ላይ የሚገኙትን የቀድሞዉ ወታደራዊ መሪ ሜጀር ጀነራል ሙሀማዱ ቡሀሪን እጩ ፕሬዝደንት አድርጎ አቅርቧል።

የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት FAO በያዝነዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2014 ከፍተኛ የሰብል ምርት መገኘቱን አመለከተ። እንደFAO ዘንድሮ ከ2,5 ቢሊዮን ቶን በላይ የሰብል ምርት በመመረቱ በዓለም የምርት ታሪክ አዲስ ሪከርድ ተመዝግቧል።

Image

‪#‎stopbanningofhijab‬

መንግስት በሰኪዩላሪዝም ሽፋን ህዝብን ሀይማኖት አልባ ለማደረግ የጀመረውን እንቅስቃሴ በአስቸኳይ ያቁም!

የኢፌድሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 90(2) የሚደነገገው ትምህርት በማናቸውም ረገድ ከሃይማኖት፣ ከፖለቲካ አመለካከቶች እና ከባህላዊ ተጽእኖዎች ነጻ በሆነ መንገድ መካሄድ እንዳለበት ያስቀምጣል። የዚህን አንቀጽ ቀጥተኛ ትርጓሜ ስንመለከት በትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሰጥ ትምህርት አንድን ሃይማኖት፣ የፖለቲካ ፓርቲ አቋም ወይም የተወሰነ ማህበረሠብን ባህልና እሴት ማንጸባረቅ አይኖርበትም። በተጨማሪም የአንቀጹን ትርጓሜ በምንመለከትበት ወቅት አንቀጹ ”ትምህርት” እንጂ የትምህርት ተቋማት እንደማይል እንገነዘባለን::

ይህም የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና ሀገራችን የብዙ ብሄር ብሄረሰቦችና የተለያዩ ሀይማኖት ተከታዮች በእኩልነት ተቻችለውና ተከባብረው የሚኖሩባት ስለሆነች ሁሉም የሃገሪቷ ዜጎች ትምህርት ላይ እኩል ተጠቃሚ እንደሆኑም ጭምር የሚያረጋግጥልን አንቀጽ ነው::

በአሁን ሰዓት የመንግስት አካላት ይህን አንቀጽ በመጥቀስ ተማሪዎች በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሃይማኖታዊ ቀኖናዎችንና ማንነታቸውን እንዳተገብሩ እየከለከሉ ይገኛሉ፡፡ ይህን የህገ መንግስቱን አንቀጽ በሚቃረን ሁኔታ የትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ ላይ የራሱን ስልጣን በመጠቀም ትምህርት የሚለውን የትምህርት ተቋም የሚል ትርጓሜ ሰጥቶት የግልም ሆነ የጋራ(ስብስብ) ሀይማኖታዊ ቱፊቶችን(አለባበስ፣ አመጋገብ እና ፀሎት) እንዲከለከል አድርጓል::

የአንቀጹን ትክክለኛ ትርጓሜ ስንወስድ ግን በቡድን የሚደረጉ ሃይማኖታዊ ስርዓቶችንም ይሁን በግል እሚፈጸሙትን በምንም አይነት መልኩ ትምህርት ላይ ተጽዕኖ አያሳድር:: ከላይ የተጠቀሱት አንቀጾች ግን በቡድንም ይሁን በግል እሚፈጸሙትን ሃይማኖታዊ ስርዓቶችንም ከዚሁ የህገ መንግስቱ አንቀጽ አያይዘው ትክክለኛ ያልሆነ ትርጓሜ በመስጠት በርካቶችን ከትምህርት ገበታ እያባረሩ ፣ በርካቶችንም እያሰሩ ይገኛሉ፡፡

የሀገራችን Secularism ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን ሁለት አበይት ነጥቦች ማካተት ይኖርበታል፡-

1/ Secularism ከአሁን በፊት በኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ በሰፊው የተስተዋለውን ያልተገባ የሃይማኖቶች ግንኙነት በማረም የአንድን ሃይማኖት የተናጥልና ኢ-ፍትሃዊ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጫና በማስወገድ የሃይማኖቶችን እከኩልነት ማረጋገጥ፣

2/ የSecularism አንፃራዊ ባህርይ በመገንዘብ የመንግስትና የሃይማኖት መነጣጠል የኢትዮጵያን ሃይማኖቶች ባሕርይ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም Secularismን ከምዕራቡ Judeo- Christian ባህል አኳያ ብቻ ማየቱ በኢትዮጵያ ዉስጥ ለሚገኙ ሁሉም ሃይማኖቶች አግባብነት ላይኖረው ስለሚችል ነው፡፡

የኢትዮጳያ መንግሰት Secular መሆኑን ለማረጋገጥ የወጡ የህገ-መንግስት ድንጋጌዎችም ከአጠቃላይ የ Secularism ዕይታ፣ ከሕገ-መንግስቱ አጠቃላለይ መንፈስና ዓላማ አንፃር እንዲሁም የሀገራችንን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ሊተረጎሙ ይገባቸዋል፡፡ በጥቅሉ Secularism ማለት ሀይማት አልባ መንግስት መመስረት እንጂ ሀይማኖት አልባ ህዝብ መፍጠር አይደለም፡፡ ስለዚህ መንግስት ሀይማኖት አልባ ህዝብ ለመፍጠር እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በአስቸኳይ ይቁም!

በተማሪዎች( በተለይ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ) ላይ የተከፈተው ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆምልን እንጠይቃለን፡፡ ተማሪዎች የተነፈጉትን መብት እስኪመለስላቸው ድረስ እኛም ፀንተን እንታገላለን!

የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 90 ይከበር!

በሰኪዩላሪዝም ሽፋን የሚፈፀመው የሂጃብ ገፈፋ በአስቸኳይ ይቁም!!!

አላሁ አክበር!!!


(አፈንዲ ሙተቂ)
——
አሁንም ግን እደግመዋለሁ!! እኔ ህልመኛ ነኝ! ይህ የኔ ህልም በፈጣሪም ሆነ በሰው ልጆች ዘንድ “ብሩክ” ተብሎ የሚወደስ ነው፡፡ ስለህዝቦች ፍቅር፣ ህብረት፣ አንድነትና እኩልነት ማለም የዘወትር ተግባሬ ነው፡፡ መቼም ቢሆን ይህንን ከማድረግ ወደ ኋላ አልልም፡፡ እንኳንስ በደንብ የማውቃቸውን የኤርትራና የኢትዮጵያ ህዝቦችን ይቅርና አምስቱ የምስራቅ አፍሪቃ ሀገራት (ሱዳን፣ ኢትዮጵያ፣ ሶማሊያ፣ ጅቡቲና ኤርትራ) በኮሎኒያሊስቶች የተሰመሩ ድንበሮችን በጣጥሰው በአንድ ግዛት ስር እንዲጠቃለሉ በጽኑ አልማለሁ፡፡ ምን ይሄ ብቻ! ትልቋ እማማ አፍሪቃም አንድ ሀገር እንድትሆን በብርቱ ነው የማልመው፡፡
*****
ኤርትራና ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ ችግሮች በቆሰቆሷቸው አቧራዎች መነሾነት ሁለት ሀገር ሆነዋል፡፡ ፍቺያችን በደም የታጀበ መሆኑ በጣም ያሳዝነናል፡፡ ያስለቅሰናል፡፡ ይህ ማለት ግን “አንድ ላይ የመሆናችን ጉዳይ ለዘልዓለሙ አብቅቶለታል” ማለት አይደለም፡፡ ሰው ሰራሽ ድንበር በኛ መካከል ቢሰመርም ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋና ጂኦግራፊ በአንድ ላይ ያስተሳስረናል፡፡ የህዝቦቻችን የጋራ ታሪካዊ ውቅር መቼም ቢሆን አይፋቅም፡፡ 
  እኛና ኤርትራዊያን በጣም ነው የምንመሳሰለው፡፡ እንዲህ የሚመሳሰሉ ህዝቦች የማታ ማታ ተመልሰው አንድ የሚሆኑበትን ሁኔታ የዓለም ታሪክ አሳይቶናል፡፡ ሁለቱ ጀርመኖች ከአርባ አምስት ዓመታት በኋላ ተዋህደዋል፡፡ ሁለቱ የመኖችም ከሰላሣ ዓመታት በኋላ ሲዋሃዱ አይተናል፡፡ ታዲያ ይህንን እያየን የምን ተስፋ መቁረጥ ነው?
   እኛና ኤርትራዊያን ከመመሳሰልም አልፎ በጣም ነው የምንቀራረበው፡፡ በጣም እንዋደዳለን፡፡ ይህንን በቀላሉ ለመረዳት ኤርትራዊያንና ኢትዮጵያዊያን በዲያስፖራው ክፍለ-ዓለም የሚኖሩበትን ሁኔታ ማስተዋል ይበቃል፡፡ ወደየትኛውም የዓለም ሀገር ሄደን ብናይ ከማንም በላይ ለኤርትራዊያን የሚቀርቡት ኢትዮጵያዊያን ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ ለኢትዮጵያዊያንም ከማንም በላይ የሚቀርቡት ኤርትራዊያን ናቸው፡፡ አምና (በህዳር ወር 2005) የሳዑዲ ዐረቢያ የጸጥታ ሀይሎች በኢትዮጵያዊያን ላይ የወሰዱትን በደልና ግፍ የተቀላቀላበትን ከሀገር የማባረር እርምጃ ከኢትዮጵያዊያን ጎን ቆመው ሲያወግዙ የነበሩት ኤርትራዊያን ብቻ ነበሩ፡፡ ኢትዮጵያዊያን ባካሄዷቸው ሰልፎች ላይ ከኤርትራዊያን በስተቀር የሌላ ሀገር ዜጋ አልተሳፈተም፡፡
  
   የሜዲትራኒያን ባህርን በህገ-ወጥ ጀልባዎች በማቆራረጥ ወደ አውሮጳ ሲከንፉ ባህሩ የሚበላቸው ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ምንዱባንስ እንዴት ይረሳሉ?… ስለነርሱ በምንሰማው መጥፎ ዜና ሁለታችንም አንድ ላይ “እህ!” እያልንና በቁጭት እየተቃጠልን አይደለም እንዴ?… መርዶአቸው በአንድ ላይ እየደረሰን በአንድ ላይ ለቅሶ እየተቀመጥን አይደለም እንዴ?…
በደጉም ቢሆን መመሳሰላችንና መፈቃቀራችን ብዙ የተጻፈለት፣ ብዙ የተነገረለት ነው፡፡ ዛሬም ድረስ ያንን ሳቂታ የቤኒ አምር ወጣት የኛ ልጅ በመሆኑ ነው የምናውቀው፡፡ ዛሬም ድረስ ከኤርትራዊ ጎረቤቶቻችን ጋር ፋሲካና አረፋን በአንድነት እንታደማለን፡፡
*****
  እኛ ኤርትራን የምንፈልጋት ለወደቦቿ ስንል አይደለም፡፡ እኛ ኤርትራን የምንፈልገው ሁለመናዋ ከኛ ጋር ስለሚመሳሰልና አንድ ዓይነት ስለሆንን ነው፡፡ እኛ ኤርትራን የምንፈልገው ከነህዝቧ ነው፡፡ የኤርትራ ህዝብ የኛ ህዝብ ነው፡፡ እኛ ራሳችን የኤርትራ ህዝብ ነን፡፡ ኤርትራም ኢትዮጵያ ናት፤ ኢትዮጵያም ኤርትራ ናት፡፡ ኤርትራ ወደብ ባይኖራት እንኳ ይህ አቋማችን አይቀየርም፡፡ ታሪኳ፣ ባህሏ እና ቋንቋዋ እናንተ ከምታውቁት ተቀይሯል እስካልተባለ ድረስ ስለርሷ ማለማችንን አንተውም፡፡
 
  ህልማችን ጽኑ ነው፡፡ ወደፊት የትግበራ ምዕራፎቹን እያሰፋ የሚሄድ ነው እንጂ በእንጭጩ ተቀጭቶ የሚቀር አይደለም፡፡ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም በአፋቤት ሽንፈት ሲያጋጥማቸው በተስፋ መቁረጥ ስሜት “ቤንዚን አይቆፈርበት፤ አልማዝ አይወጣበት፣ ሰው የለበት! Nothing`” እንዳሉት እኛም ተስፋ ቆርጠን ኤርትራንና ህዝቧን የምናጥላላበት ሁኔታ በፍጹም አይከሰትም፡፡ ቢኢዝኒላህ!! ኢንሻ አላህ!!
   እኛ ስለትልቋ ኤርትራ ማለምን ትተን “አሰብ የኢትዮጵያ ወደብ ናት” ከሚሉት የወደብ ጥማተኞች ጎንም አንሰለፍም፡፡ ፍላጎታችን “የኢኮኖሚ እድገት” በሚባለው የማቴሪያሊስቶች ዝባዝንኬ የሚመራ ባለመሆኑ ለጥቅም ብለን ህልማችንን በመንደር ደረጃ አናሳንሰውም፡፡ ቢኢዝኒላህ!!
   
    የእነዚህን የወደብ ጥማተኞች ቅስም ለመስበር በሚል የፖለቲካ ስሌት ተነሳስተን “የአሰብ ወደብ እጣ ፈንታ የግመሎች ውሃ መጠጫ ኩሬ ከመሆን አያልፍም” የሚል ታሪካዊ ተወቃሽነትን የሚያስከትል ቃልም አይወጣንም፡፡ ቢኢዝኒላህ!!
 
  እኛ ኤርትራዊያንን እንደኛው አድርገን ነው የምናያቸው እንጂ አንዳንድ ብስጩዎች በሚተነፍሷው ወሬዎች ተናደን “የቅኝ-ተገዥነት ስሜት ሰለባዎች ናችሁ” በማለት አንፈርጃቸውም፡፡ በምንም መልኩ ቢሆን ኤርትራዊ ወገናችንን የሚያሳቅቅና የሚያበሳጭ ክፉ ንግግር አንናገርም፤ ክፋታችንንና የውስጥ ጥላቻችንን የሚያሳብቅ ጽሑፍም አንጽፍም፡፡ በውስጣችን ስለኤርትራ መውደም እያሰብን በምላሳችን ብቻ “አንድ ህዝቦች ነን” እያልን የምንሰብክ መናፍቃንም አይደለንም፡፡ እኛ ኤርትራንና ህዝቧን የምንወደው ከልባችን ነው፡፡ ስለነርሱ የምናልመው ህልማችንም ከልባችን ከተወረወረ የፍቅር ፍላጻ የፈነጠቀ ነው፡፡
*****
ህልማችን የቅርብ ሳይሆን የሩቅ ነው! እጅግ በጣም ሩቅ!! ይሁንና ርቀቱን ፈርተን ማለማችንን አንተውም፡፡ ዘወትር ስለውቢቷ ኤርትራና ህዝቧ ማለማችንን እንቀጥላለን!! ከሩቁና መልከ-መልካሙ ህልማችን ጋር ወደፊት!!
—-
አፈንዲ ሙተቂ
ጳጉሜ 4/2006
—-
Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his facebook page. Just click this link

የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እጅግ ደማቅ በመሆነ ሁኔታ እየተካሄደ ነው። የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት አረንጓዴ ፤የአዲስ አበባ ምክር ቤት ቢጫ፤ የክልል ዞን ተወካዮች ቀይ ቲሸርቶችን በመልበስ ለጉባኤው ድምቀት ሰጥተውታል፡፡ ዛሬና ነገ በሚደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ምርጫ ቦርድ በድርጅቱ ደንብ ላይ የኮረም ቁጠር ይጠቀስ የሚል ጥያቄ በመቅረቡ፣ የቀረበው ጥያቄ ከሕግ ውጭ ቢሆንም ( ደርጅቶች የሚተዳደሩበትን ደንብ ምን […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለዛሬ አርብ (03/04/07) የጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል። ጠቅላላ ጉባኤተኛው ወደ አዳራሹ የገባው ፓርቲው ያዘጋጀውን ነጭ ኮፍያ በአንድነት ያደረጉ ሲሆን የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት አረንጓዴ ፤የአዲስ አበባ ምክር ቤት ቢጫ፤ የክልል ዞን ተወካዮች ቀይ ቲሸርቶችን በመልበስ ለጉባኤው ድምቀት ሰጥተውታል፡፡ የጉባኤ ጠሪ ኮሚቴው መድረኩን ተቀብሎ፤ አቶ ብሩ ብርመጂ ንግግር አድርገዋል፡ […]

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የጠራው ጠቅላላ ጉባኤ የተጀመረ ሲሆን ተሳታፊዎች የብሔራዊ ምክር ቤት አባላት አረንጓዴ ፤የአዲስ አበባ ምክር ቤት ቢጫ፤ የክልል ዞን ተወካዮች ቀይ ቲሸርቶችን በመልበስ ለጉባኤው ድምቀት ሰጥተውታል፡፡
Image

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አርብ (03/04/07) ጠቅላላ ጉባኤውን ያደርጋል፡፡ ፓርቲው ከዚህ ቀደም በታህሳስ 19/20/2007 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን አመት ሳይሞላ ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ለምን እንዳስፈለገ የጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ የሆኑትን አቶ አስራት ጣሴን አነጋግረን ነበር፡፡ አቶ አስራት እንዳብራሩት በታህሳስ 2006 ዓ.ም ተካሂዶ በነበረው ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫ ቦርድ ማብራሪያ ጠይቆ ነበር፡፡ አቶ አስራት በተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ማቋቋሚያ አዋጅ 573/2000 መሰረት ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ጉባኤ ሪፖርት ማብራሪያ መጠየቅ እንደሚችል ገልፀው በሀምሌ 25 ቀን 2006 ዓ.ም በፃፈው ባለ ሶስት ገፅ ደብዳቤ ዘጠኝ ማብራሪያ የሚፈልጉ ጥያቄዎችን አቅርቦ ነበር፡፡
Image
አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ሀምሌ 30 ቀን 2006 ዓ.ም ለተጠየቁት ጥያቄዎች ማብራሪያ ላከ፡፡ ከተላከው ማብራሪያ በመነሳት ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 19 ቀን 2007 ዓ.ም ጥያቄዎቹን ወደ 6 ዝቅ አደረገ፡፡ ፓርቲው በበኩሉ ጥቅምት 21 ቀን 2007 ዓ.ም ለተጠየቁት ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጠ፡፡ ከዚያ በመቀጠል ምርጫ ቦርድ ህዳር 10 ቀን 2007 ዓ.ም ሶስት ማብራሪያ ያስፈልጋቸዋል ያላቸውን ጥያቄዎች ያቀረበ ሲሆን ፓርቲውም ህዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም ማብራሪያ ሰጥቶባቸዋል፡፡
Image
ለአሁኑ ጠቅላላ ጉባኤ መጠራት ምክንያት የሆነው ህዳር 19 ቀን 2007 ዓ.ም ወደ አንድ ወርዶ በምርጫ ቦርድ የቀረበው ጥያቄ ነው፤ ፓርቲው የጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊ ቁጥሩን እንዲገልፅ የተጠየቀበት፤ ፓርቲው የጠቅላላ ጉባኤ ቁጥሩ 320 መሆኑን ገለፀለት፡፡ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ይህ ቁጥር ታህሳስ 19 እና 20 ቀን 2006 ዓ.ም በተደረገው ጉባኤ በተሻሻለው በደንብ ባለመካተቱ ተካቶ ይቅረብልኝ ሲል ጠየቀ፡፡ በዚህ ሁኔታ በፓርቲው ደንብ መሰረት የጠቅላላ ጉባኤ ቁጥር መወሰን የሚችለው ራሱ ጉባኤው በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤ መጥራት እንዳስፈለገ አቶ አስራት ጣሴ ገልፀውልናል፡፡
አቶ አስራት በመጨረሻ ባስቀመጡት ሀሳብ ምርጫ ቦርድ ምርጫ ሲደርስ እንዲህ ዓይነት ጥያቄ መጠየቁ እኛን አጣብቂኝ ውስጥ ለመክተት ቢሆንም ህጋዊ መሰረት ግን አልነበረውም ብሏል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ በደንቡ ላይ የጠቅላላ ጉባኤውን ተሳታፊ ቁጥር የወሰነው ብቸኛው ፓርቲ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ብቻ እንደሆነ ታውቋል፡፡
Image
Image

ከአፍሪቃና ከመካከለኛው ምሥራቅ፣ በጀልባ ፤ ባህር አቋርጠው አውሮፓ ለመግባት የሚሞክሩ ስደተኞች ቁጥር በየጊዜው በመናር ላይ ነው። ቁጥራቸው የሚያመዝነው የአፍሪቃ ስደተኞች መሆናቸውም ይነገራል። የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን

(የሰማያዊ ፓርቲ ዘገባ) በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ታፍሰውና ደብደባ ተፈጽሞባቸው ከታሰሩ በኋላ ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹ህገ መንግስቱን በመናድ፣ መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት በማውደም፣ በሁከትና ብጥብጥ›› እና በመሳሰሉት ክሶች ተከሰው እስከ 14 ቀን ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸው የነበሩት የሰማያዊና የሌሎች የ9ኙ ፓርቲዎች አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች በመታወቂያ ዋስ እንዲፈቱ ተወሰነ፡፡ ከእስረኞቹ መካከል ከፍተኛ ድብደባ ደርሶባቸው አዲስ አበባ ፖሊስ (ሶስተኛ) ታስረው የነበሩት ‹‹ህገ መንግስቱን በመናድ›› ክስ 14 ቀን፣ ፖፖላሬ ታስረው የነበሩት ‹‹መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት በማውደም›› 7 ቀን፣ እንዲሁም ቤላ እስር ቤት ታስራ የነበረችው ወይንሸት ንጉሴ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠርና ህዝቡን በመረበሽ›› 7 ቀን፣ እንዲሁም ኮተቤ ታስረው የነበሩት እነ ፍቅረማሪያም በተመሳሳይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር›› 10 ቀን ተቀጥሮባቸው የነበር ቢሆንም ከቀጠሯቸው ቀን ቀድም በመታወቂያ ዋስ እንዲፈቱ ተወስኗል፡፡ በሶስተኛ፣ ፖፖላሬ፣ ቤላና ኮተቤ የነበሩት እስረኞች ከትናንት ጀምሮ በመታወቂያ ዋስ እንዲወጡ ቢወሰንም ፖሊስ አንዳንድ እስረኞችን በተለይ ፖፖላሬና ሶስተኛ ታስረው የነበሩትን ነጥሎ ለማስቀረት ባደረገው ጥረት የመታወቂያ ዋስ አምጥተው እንዲፈቱ የተነገራቸው እስረኞች ‹‹አብረውን የታሰሩት ካልተፈቱ አንወጣም›› በማለታቸው ሳይፈቱ አድረዋል፡፡ ዛሬ ታህሳስ 2/2007 ዓ.ም ደህንነቶች ሶስተኛ ታስረው የነበሩትን መርከቡ ሀይሌ፣ ሳሙኤል አበበ፣ ምኞት መኮንን እና ሜሮን አለማየሁ እንዲሁም ፖፖላሬ ታስረው የነበሩትን ዮናስ ከድርና ተስፋዬ መርኔ ‹‹አብራችሁን ካልሰራችሁ አትወጡም!›› ብለዋቸው እንደነበር ታውቋል፡፡ ሆኖም በመታወቂያ ዋስ እንዲወጡ የተነገራቸው እስረኞች ‹‹እነሱ ካልወጡ እኛም አንወጣም›› በማለታቸው በአራቱም እስር ቤቶች የሚገኙት ሁሉም ታሳሪዎች የመታወቂያ ዋስ አቅርበው እንዲለቀቁ […]

ቅዳሜ ትብብሩ በጠራው ሰልፍ ለማገዝ ወደ ሰማያዊ ቢሮ ሄዶ ነበር። አግዞ ከዚያ ሲመለስ ይታሰራል። የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ የነበረው ወጣት ተስፋሁን አለምነህ ነው። የሰማያዊ አመራር አባላት በሙሉ ሲፈቱ አቶ ተስፋሁን ስለመፈታቱ የደረሰን ምንም አይነት መረጃ የለም። ሌላው ሕወሃቶች በአንድ በኩል የሰማያዊ አባላትን በመፍታታትቸው ምናልባት ልቦኖ መግዛት ጀመረው ይሆን እያሉ አንዳንዶች ማሰብ በጀመሩ ሰዓታት ሳይሞላ […]

Image
– የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ በዚህ ከቀጠለ ወያኔ እድሜ አይኖረውም::
– የያዝነው መስመር አያዋጣም:እስከመቼስ እንዲህ ይቀጥላል?” የሚሉ አመራሮች ተነስተዋል::
– ካድሬዎች ሕዝቡን እየዞሩ በመቀስቀስ ዳግም እንዲያደራጁ እየተደረገ ነው::

Minilik Salsawi

ከምርጫው መምጣት ጋር በተያያዘ የወያኔው ጁንታ በህዝብ እና በተቃዋሚ ሃይሎች ላይ እየወሰደ የሚገኘውን እርምጃ ተከትሎ በወያኔ/ኢሕአዴግ ፓርቲ ውስጥ በአመራሮች ደረጃ የውስጥ መተራመሱ መቀጠሉ ታውቋል::ሕዝቡን ማዋከብ እና ተቃዋሚውን ማሰር እንዲሁም በየጊዜው የሚከሰተው የውጪ ሃይሎች ጫና አደጋ ውስጥ ይከተናል ልንጠነቀቅ ይገባል የያዝነው መስመር አያዋጣም በሚሉ እና በሕወሓት አመራሮች መካከል ከፍተኛ የሆነ ውዝግብ መከሰቱን ለፓርቲው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ገልጸዋል::

የተወሰነን ከመተግበርና ከማስፈጸም ውጪ ምንም አስተያየት መስጠት አትችሉም የሚል የቁጣ ቃላቶች ከአቶ ደብረጽዮን የሚወርድባቸው የአቶ ሃይለማርያም የደቡብ ኢትዮጵያ ፓርቲ አመራሮች በማንኛውም የፓርቲ ስብሰባ ላይ የተባለውን ከመደገፍ ውጪ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ታዘዋል::በኢሕአዲግ ውስጥ እየተከሰተ ያለው የአካሄድ ልዩነት አመራሮቹን ከማተራመሱም በላይ በአሁን ወቅት እየተወሰዱ ያሉት እርምጃዎች ከምርጫ በኋላ ቢሆኑ ይሻላል የሚሉ አስተያየቶችና የምንከተለው መስመር አዋጪነቱ ምን ያህል ነው የሚሉ ጥያቄዎች በከፍተኛ አመራሩ መካከል ልዩነት መፍጠሩ ታውቋል::የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ መስመሩን ለማሳት አዳዲስ የተሳሳቱ መረጃዎች እና የቤት ስራዎች (በተለይ ለዲያስፖራው) እየተዘጋጁ መሆኑን የውስጥ ምንጮቹ ገልጸዋል::

ከአዲስ አበባ የሚደርሱ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ከተማዋ በውጥረት ውስጥ መሆኗ በገሃድ እየታይ ነው የሃገሪቱ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሕዝቡን ካለማስደሰቱም ውጪ ክፍተኛ የሆኑ የቢዝነስ ስራዎች ከቀድሞው በባሰ መልኩ ቀዝቅዘዋል::የገዢው ፓርቲ ተላላኪዎች በተለያዩ ቦታዎች በመዘዋወር ስለላ እያካሄዱ ሲሆን ሕዝቡም ያለውን ሁኔታ በንቃት እየተከታተለ መሆኑ ታውቋል:: የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ እንደጅምሩ ከቀጠለ ለውጥ እንደሚመጣ እና ወያኗም እድሜ እንደማይኖረው በሚነገርበት በአሁን ሰአት የወያኗ ጁንታ በምርጫው ለሚሳተፉ ተቃዋሚዎች ከፓርላማ 15% ወንበር እንዲመቻችላቸው ከምርጫ ቦርድ ጋር እየሰራ ሲሆን ፓርላማ መግባት ያለባቸው ድርጅቶች እና ግለሰቦችን በመለየት እና በማዘጋጀት ላይ መሆኑ ታውቋል::

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የተከሰተውን ውጥረት ተከትሎ ካድሬ የመንግስት ሰራተኞች ውጡና ቀስቅሱ አደራጁ በማለት ፓርቲያቸው መከራ አብዝቶብናል ሲሉ ማማረራቸው ተሰምቷል::ዳግም በየመንደሩ እየዞሩ በማደራጀት እና በመቀስቀስ ላይ የተሰማሩት ካድሬዎች ወጣቶችን በመቀስቀስ በማደራጅት በመመልመል ዙሪያ አዳዲስ ውይይቶች በኢሕአዴግ አመራሮች ትእዛዝ እየተሰጠ መሆኑ ታውቋል::በዚህም መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ በየቀጠናው ካድሬዎቹ የመንግስት ሰራተኞች ስራቸውን እየተዉ ቢሯቸውን ዘግተው ለዚሁ የአደረጃጀት የምልመላ እና ቅስቀሳ ጉዳይ መሰማራታቸው ሲታወቅ መረጃውን ያደረሱኝ ተቃዋሚዎች ወያኔ ያደራጀውን ሃይል
ተጠቅመው የጀመሩትን የለውጥ ትግል ገፍተው መቀጠል አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል::

ዕለቱ 9ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን እና የሕገ-መንግስታችን 20ኛ የልደት በዓል የሚከበርበት ህዳር 29፤ ቦታው ደግሞ ለዚሁ በዓል ተብሎ በፍጥነት እንዲደርስ የተደረገው የአሶሳ ከተማ ስቴድየም ነው፡፡ የኢ.ፌ.ድሪ ጠቅላላ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ የፌደሬሽን እና የሕዝብ ተወካዮችን ምክር ቤቶች አፈ ጉባኤዎች፣የጎረቤት ሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስቴሮች፣ የውጭና የሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች፣ የሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች የባህል ቡድኖች…ብቻ ምን አለፋችሁ ኢትዮጵያ በስቴድየሙ ከትማለች፡፡ በዓሉ ሰፊ፣ ደማቅና ብዙ ሊባልለት የሚገባ ነበር፡ ስለዚህ ሌላው በይደር ይቆየንና ለዛሬ አንድን ለየት ያለ ክስተት መርጨ ላውጋችሁ።   ለበዓሉ ከታቀዱት ትርኢቶች አንዱ፣ ለ26 ቀናት ሀገሪቱን በመዞር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 204 ሚልዮን ብር የሰበሰበው እና ከታላቁ መሪ ለኢትዮጲያ ብሔር ብሔረሰቦች የተበረከተው የህዳሴ ግድብ ዋንጫ፣ ግድቡንም በአሉንም ወደምታስተናግደው የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ዋና ከተማ መግባት ነበር፡፡ ዋንጫው ወደ አሶሳ ስቴድየም እንዲገባ የታሰበውም ለየት ባለ መንገድ ነበር፤ በሄሊኮፕተር ከሰማይ። በእርግጥ ይህ ለየት ያለ አቀራረብ የታሰበለትን በአሉን የማድመቅ ግብ መትቷል ፡፡ ግቡን የመታው ግን አዘጋጆቹ ባሰቡት መንገድ አልነበረም። ታሪኩ እንዲህ ነዉ። አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፡ የሚመራውን ቡድን በመያዝ የስቴድየሙን መሀል ከተቆጣጠረ የቡድኑን 26 ቀን ሀገር አቀፍ ጉዞ በሰፊው መተረክ ከመጀመሩ ነበር ዋንጫውን ያዘው የመከላከያ ሄልኮፕተር በድንገት ከተፍ ያለው፡፡ ሄልኮፕተሩ ወደ ሜዳው መሀል ጉዞውን ቀጥሏል፤ ሰራዊት ፍቅሬም ትረካዉን። ሄሊኮፕተሩ ወደ መሀል እስኪደርስ የተነቃነቀ ሰው አልነበረም፣ ቀጥሎ ምን ሊፈጠር እንደሚችል የገመተ የነበረም አይመስል። ልክ ሄልኮፕተሩ ሜዳው መሀል ደርሶ ከፍታ […]

በዛሬው እለት 2/4/2007 ዓ.ም ከክልል የመጡ የአንድነት አመራሮች እንዲሁም የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ጋዜጠኛ ስለሺ ሀጎስ፤ ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ፤ ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና ታዋቂ ብሎገር እዩኤል ፍሰሀ በዛሬው እለት አንድነት ፓርቲን ተቀላቀሉ ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ከሚባሉት ፓርቲዎች አንዱ አንድነት መሆኑን ጠቅሰው ፓርቲውን በመቀላቀላቸው የተሰማቸውን ደሰታ የላቀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡


ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–

ዕለቱ መስከረም 2/1977 ነበር፡፡ በዚያች ዕለት ደርግ ከአጼ ኃይለሥላሤ መንግሥት ስልጣን የተረከበበት 10ኛው የአብዮት በዓል ይከበር ነበር፡፡ ያ በዓል ከቀደሙት በዓላት ለየት የሚልበት አንድ ነገር ታይቶበታል፡፡ ይህም የስመገናናው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ (ኢሠፓ) ምስረታ በይፋ መታወጅ ነው፡፡ ይህንን ድርብ ደስታ ለማድመቅ ተብሎ የተዘጋጀው ክብረ በዓል በሀገራችን ታሪክ በድጋሚ አልታየም፡፡ ለዚህ በዓል ማክበሪያ በትንሹ አንድ መቶ ሚሊዮን ብር ወጪ ሆኗል (ያ ገንዘብ በአሁኑ ስሌት ሁለት ቢሊዮን ብር ሊሆን ይችላል)፡፡

በዚያን ጊዜ ነው በአስራ ዘጠኝ ሚሊዮን ብር የተሰራው ታላቁ የኢሠፓ የጉባኤ አዳራሽ ተመርቆ የተከፈተው፡፡ ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት ያለው የ“ትግላችን” ሀውልትም በዚህ በዓል ወቅት ነው የተመረቀው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ለበዓሉ የታጨችው አዲስ አበባ በደማቅ መብራቶችና በልዩ ልዩ መፈክሮች ተጥለቅልቃ ነበር፡፡ እንግዶች በሚንቀሳቀሱባቸው ዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ ያሉ አሮጌ ቤቶች በግንብ አጥርና በትላልቅ የጨርቅ ሽፋኖች እንዲከለሉ ተደርገዋል፡፡ የክፍለ ሀገር ዋና ከተሞችና የአውራጃ ከተሞችም በመፈክሮችና በማጭድና መዶሻ ምስሎች አሸብርቀዋል፡፡ በዋና ዋና መንገዶች ላይ ያሉ የንግድ ድርጅቶችና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በሶስት ቀለማት (አረንጓዴ፤ ቢጫ፤ ቀይ) የተዘጋጁ አምፖሎችን እንዲያበሩ ታዘዋል፡፡ በየቀበሌው የተቋቋሙ የኪነት ቡድኖችም ኢሠፓን የሚያወድሱ መዝሙሮችን አፍልቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የነጭና ጥቁር ስርጭቱን ትቶ ወደ ሙሉ የቀለም ስርጭት የተሸጋገረው በዚያች ታሪካዊ ዕለት ነው፡፡

በዚያ ታላቅ ክብረ በዓል ላይ የምስራቅ ጀርመን ኮሚኒስት ፓርቲ ዋና ፀሐፊና የሀገሪቱ መሪ የነበሩትን ጓድ ኤሪኽ ሆኔከርንና የየመን ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ (ደቡብ የመን) መሪ ጓድ ዓሊ ናስር አል-ሐሰንን ጨምሮ በርካታ የሶሻሊስት ሀገራት ልዑካን ተገኝተዋል፡፡ ከአፍሪቃም የዛምቢያው ኬኔት ካውንዳ፤ የዚምባብዌው ሮበርት ሙጋቤና የሞዛምቢኩ ጓድ ሳሞራ ማሼል የበዓሉ ታዳሚ ነበሩ፡፡ ዋናው የበዓሉ አከባበር ስነ-ስርዓት በኢሠፓ ጉባኤ አዳራሽና በአብዮት አደባባይ የተካሄደ ሲሆን በተለይም በአብዮት አደባባይ የተካሄደው ልዩ ትርዒትና ወታደራዊ ሰልፍ በሀገሪቱ ታሪክ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም፡፡
*****
“ኢሠፓ” የሚባለው ዝነኛ ፓርቲ የተመሰረተው ለአምስት ዓመታት የዘለቀ መጠነ ሰፊ ዝግጅት ከተደረገ በኋላ ነው፡፡ ለፓርቲው ምስረታ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን እንዲያቀላጥፍና ህዝቡን በሶሻሊስታዊ ስርዓት እንዲያደራጅ በሚል “የኢትዮጵያ ሰርቶ አደሮች ፓርቲ አደራጅ ኮሚሽን” (ኢሠፓአኮ) የተባለ ከፍተኛ የአስፈጻሚ አካል በመስከረም 1972 ተመስርቶ ነበር፡፡ ይህንን ኮሚሽን ማቋቋሙ ያስፈለገው “የሰርቶ አደሩን ፓርቲ ለመመስረት የሚቻለው ህዝቡን በማንቃትና በማደራጀት በአንድ ማዕከል ዙሪያ ካሰባሰቡ በኋላ ነው ” በሚለው የኮሚኒስቶች ርዕዮተ-ዓለማዊ መርህ መሰረት ነው፡፡ የዚህ ኮሚሽን ተጠሪ በመሆን በየክፍለ ሀገሩ የተመደቡ ወኪሎች የየአካባቢው የበላይ ውሳኔ ሰጪዎች ነበሩ፡፡ የኮሚሽኑን ዓላማ የሚገልጸው “የኢሠፓአኮ ተልዕኮ ይሳካል” የተሰኘ መፈክር በመላው ኢትዮጵያ ተደጋግሞ ይሰማ ነበር፡፡
  ኢሠፓ የተመሰረተው ለአምስት ቀናት በተካሄደ መስራች ጉባዔ ነው፡፡ በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ በድርጅታዊ አሰራር የተዘጋጀ ምርጫ ተደረገ፡፡ ጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያም የፓርቲው ዋና ጸሐፊ ሆነው መመረጣቸውም ተነገረ፡፡ ከርሳቸው ጋርም መቶ ሰማኒያ ሶስት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ተመረጡ፡፡
*****
የኢሠፓ አወቃቀርና አሠራር በሌሎች የሶሻሊስት ሀገራት ከታዩት ኮሚኒስት ፓርቲዎች ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ ፓርቲው የመንግሥት አስፈጻሚ አካላት የበላይ ነው፡፡ የፓርቲውና የአስፈጻሚ አካላቱ ግንኙነት የጎንዮሽ ሳይሆን ከላይ ወደታች የተዘረጋ መዋቅራዊ መልክ ነበረው፡፡ በመሆኑም ኢሠፓ በየትኛውም እርከን ላይ ላሉት አስፈጻሚ አካላት የበላይና አመራር ሰጪ ነው፡፡ ይህ አወቃቀር በሀገር አቀፍ፣ በክፍለ ሀገርና በአውራጃ ደረጃ የተዘረጋ ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የነበሩት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች አመራር የሚቀበሉት ከኢሠፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት ነው፡፡ በክፍለ ሀገርና በአውራጃ ደረጃ ያሉ መስሪያ ቤቶችም ከኢሠፓ ጽ/ቤት ነው አመራር የሚሰጣቸው፡፡ በመሆኑም የአውራጃና የክፍለ ሀገር የኢሠፓ ኮሚቴ አንደኛ ፀሐፊ ሆኖ የተመደበ ሰው በፕሮቶኮልም ሆነ በስልጣኑ ከሌሎች ተሿሚዎች ሁሉ ይበልጣል፡፡
 የኢሠፓ መዋቅር በኢ-መደበኛ ሁኔታ ሁሉንም የመንግሥት መስሪያ ቤቶች አዳርሷል፡፡ በያንዳንዱ የመንግሥት መስሪያ ቤት፣  በማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅቶችና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ “የኢሠፓ መሰረታዊ ድርጅት ጽ/ቤት” የሚባል መምሪያ ነበረ፡፡ የዚህ መሰረታዊ ድርጅት ዓላማ የኢሠፓን ርዕዮተ ዓለም ማስተማርና ከበላይ አካል የመጡ መመሪያዎች ተፈጻሚ መሆናቸውን መቆጣጠር ነው፡፡ ለፓርቲ አባልነት ብቁ የሆኑ ጓዶችን መልምሎ የአባልነት መታወቂያ የሚሰጠውም እርሱ ነው፡፡
ኢሠፓ በፕሮፓጋንዳው ዘርፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር፡፡ የፓርቲው ልሳን “ሠርቶ አደር” የሚባለው ሳምንታዊ ጋዜጣ ነው፡፡  መስከረም ደግሞ የፓርቲው የርዕዮተ ዓለም መጽሔት ነው፡፡ የፓርቲው አባላት በሁለቱ ህትመቶች በወጡ ጽሑፎች ላይ የመወያየት ግዴታ አለባቸው፡፡
 ኢሠፓ የደርግ መንግሥት ከስልጣን እስከተወገደበት ጊዜ ድረስ ቆይቷል፡፡ በስልጣን ላይ በነበረባቸው ሰባት ዓመታት በጠቅላላው ከ100, 000 ያላነሱ አባላትን አፍርቷል፡፡ አባላቱ ከሲቪልም ሆነ ከጦር ሀይሉ ክፍል የተመለመሉ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ የፓርቲ አባል በስራ ቀናት ከካኪ የተሰፋ ሱሪና ኮት የመልበስ ግዴታ አለበት (ይህ መመሪያ የወጣው “የሀገር ውስጥ ምርቶችን ማበረታታት አለብን” በሚል መነሻ ነው፤ ካኪው በቃሊቲ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ነው የሚመረተው)፡፡ 
ከላይ እንደገለጽኩት የኢሠፓ ዋና ፀሐፊ ጓድ መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ነበሩ፡፡ ፓርቲው ምክትል ዋና ፀሐፊ በይፋ ባይሰይምም የጓድ መንግሥቱ ተከታይ ሆነው ሲሰሩ የነበሩት ጓድ ፍቅረ ሥላሤ ወግደረስ ናቸው፡፡ የርዕዮተ-ዓለም መምሪያ ሃላፊው ጓድ ሽመልስ ማዘንጊያ ሲሆኑ ጓድ ብርሃኑ ባይህ የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ነበሩ፡፡ ጓድ ሸዋንዳኝ በለጠ የኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ሃላፊ፤ ጓድ ተካ ቱሉ የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን ሃላፊ፣ ጓድ ደበላ ዲንሳ የማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ፣ ጓድ ሜጀር ጄኔራል ገብረየስ ወልደሃና የወታደራዊ ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ ነበሩ፡፡ ከሁሉም በላይ ስልጣናቸው ገንኖ የነበረው  ግን የድርጅት መምሪያ ሃላፊው ጓድ ለገሠ አስፋው ናቸው፡፡
  *****
ኢሠፓ የምስረታ ጉባኤውን በሚያካሄድበት ወቅት (ጳጉሜ1-ጳጉሜ 5/1976) ሀገሪቱ በከፍተኛ ድርቅ ተጠቅታ ነበር፡፡ ከአምስት ሚሊዮን የማያንሱ ዜጎች በትግራይ፣ በወሎ፣ በጎንደር፣ በኤርትራ፣ በሀረርጌና በባሌ ክፍላተ ሀገር በቸነፈር ተጠብሰው በሞት አፋፍ ላይ ነበሩ፡፡ አንዳንድ የሀገር ተቆርቋሪዎች መንግሥት የፓርቲ ምስረታ ጉባኤውን ለሌላ ጊዜ እንዲያስተላልፍና የ10ኛ አብዮት በዓልን እንዲያስቀር ቢወተውቱም ሰሚ አላገኙም፡፡ የወቅቱ መንግሥት የድርቁ መኖር ከታወቀ በአብዮት በዓል አከባበሩ ላይ ጥላውን ያጠላል በማለት የምዕራብ ሀገራት የዜና አውታሮች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ከልክሎአቸው ነበር፡፡ ይሁንና አንዳንድ ሚዲያዎች የዜና ዘጋቢዎቻቸውንና የቪዲዮ ሪፖርተሮቻቸውን በድብቅ ወደ ሀገር ውስጥ በማስረግ የዓለም ህዝብ አስከፊውን ድርቅ እንዲያየው አድርገዋል፡፡ በነዚያ ሪፖርተሮች የተቀረጹ ምስሎችን የተመለከቱ የዓለም ህዝቦች ለድርቅ የተጋለጠውን ኢትዮጵያዊ ረሀብተኛ ለመታደግ በተንቀሳቅሰዋል (በሰር ቦብ ጊልዶፍ አስተባባሪነት የተሰባሰቡ የዓለማችን እውቅ አርቲስቶች Live Aid የተባለውን የሙዚቃ ዝግጅት ያቀረቡት ያኔ ነው፡፡ አርቲስቶቹ በዝግጅቱ ላይ በጋራ ያዜሙት We are the world የተሰኘው ዜማ ከምንጊዜም ምርጥ ዜማዎች መካከል አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል)፡፡
   የደርግ መንግሥት በህጋዊ መንገድ ፈቅዶላቸው የመጡ ጥቂት የሶሻሊስት ሀገራት ዘጋቢዎች ደግሞ “ድርቅ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ህዝብ እየቀጠፈ ለዚህ በዓል ከፍተኛ በጀት መመደብ አግባብ ነውን?” የሚል ጥያቄ በይፋ በማቅረብ የሀገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣናት አጨናንቀዋል፡፡ በመሆኑም የአብዮት በዓሉ ሲፈጸም መንግሥት በድርቅ የተጎዳውን ህዝብ ለመታደግ መንቀሳቀሱ ግድ ሆኖበታል፡፡ ሆኖም የመንግሥት እርምጃ በጣም የዘገየ በመሆኑ አምስት መቶ ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን በዚያ አስከፊ ድርቅ አልቀዋል፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
መስከረም 2/2007

ከትብብሩ የተሰጠ መግለጫ በአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ትግላችን አይቆምም! የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ባለፈው አንድ ወር ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጸን ስንቀሳቀስ ዋናው አላማችን የስርዓቱን አረመኔያዊነት ለህዝብ በማጋለጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በትግሉ እንዲሳተፍ ማድረግ ነው፡፡ እንደጠበቅነው ገና ከጅምሩ የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ትግላችንን በጭካኔ ለማስቆም ጥሯል፡፡ ህዳር 27/2007 ዓ.ም የመጀመሪውን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራንበት ወቅት ስብሰባውን በኃይል በትኗል፡፡ ትብብራችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያሰጋው ህወሓት/ኢህአዴግ በተለይ የህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአደባባይ አዳር ሰልፍን እንዳይካሄድ የትብብሩን አመራሮችና አባላቶቻችን በማዋከብ፣ በመደብደብና በማሰር ተጠምዶ ሰንብቷል፡፡ በተለይ በትናንትናው ዕለት ሰልፍ በወጣንበት ወቅት ስርዓቱ አመራሮችንን፣ አባላቶቻችንን፣ ተሳታፊዎችንን እንዲሁም አልፎ ተርፎ መንገደኛውን ህዝብ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ አፍሶ አስሯል፡፡ ሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን በየጎዳናው ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ በርካቶችም በየእስር ቤቶቹ ታጉረዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ከ300 በላይ የትብብሩ አመራሮችና አባላት የታሰሩ ሲሆን የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ድርሶባቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቤል ኤፍሬም ራሱን እስኪስት ተደብድቧል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የተገኙ ሴት አመራርና አባላት አንድ አገርን እየመራሁ ነው ከሚል አካል በማይጠበቅ መንገድ በጭካኔ ተደብድዋል፡፡ እነዚህ በጭካኔ የተደበደቡ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ህክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጥበቃ ሰራተኝነት የሚሰሩ የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር ከስራ ሲወጡ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱና እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቀ ሲሆን ይህም አገዛዙ የመጨረሻው የአረመኔነት ደረጃ ላይ እንደደረሰና […]

ታኀሳስ ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ህዳር 27 በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ሲዘጋጁ በፖሊስና በደህንነቶች ቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት የ9 ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት ከእስር የተለቀቁ ሲሆን፣ ብዙዎቹ በእለቱ በደረሰባቸው ድብደባ ከመጎዳታቸውም በተጨማሪ በእስር ቤት ውስጥ የነበራቸው አያያዝ አስከፊ እንደነበር ታውቋል። የሰማያዊ ፓርቲ የአመራር አባል የሆነው ይድነቃቸው ከበደ  ደህንነቶች ወደ እስር ቤት በተደጋጋሚ …

ታኀሳስ ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከህዝብ የተሰባሰበው መረጃ እንደሚያመለክተው ህዝቡ በሙስና በመማረሩ ስራ መስራት በማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ሙስና የሚጠይቁ ሰዎችን ማጋለጥ ህይወትን እስከ ማስከፈል እንደሚደርስም የተሰባሰበው መረጃ ያመለክታል። አንድ አስተያየት ሰጪ እንደተናገሩት ሙስናን ለማጋለጥ ቢፈለግም ፣ ለሚያጋልጡ ሰዎች በቂ የሆነ የህግ ከለላ አያገኙም ሙስናን ለማጋለጥ ስንሄድ  “ጀርባቸው ይጠና ተብለን እንደገና ጉዳቱ ሙስናን …

ታኀሳስ ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የምስራቅ አፍሪካ የሰብአዊ መብት ሊግ የተባለው ተቋም ለኢሳት በላከው መግለጫ በምእራብ ወለጋ በጊምቢ እስር ቤት በተከሰተው ምንነቱ ያልታወቀ በሽታ አቶ ያቆም ኒጋሩ የተባሉ የፖለቲካ እስረኛ አርፈዋል። ሌሎች በበሽታው የተያዙት 60 ዎቹ እስረኞችም ተመሳሳይ እጣ ሊገጥማቸው እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል። ሟቹ አቶ ያእቆብ ባለፈው ሚያዚያና ግንቦት ወር በኦሮምያ ተከስቶ ከነበረው …

ታኀሳስ ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው በቅርቡ በየመን የባህር ዳርቻ ያለቁትን ከ70 በላይ ኢትዮጵያውያንን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ  አደጋው ዜጎች በሀገራቸው ሰርተው መኖር አለመቻላቸውንና ሰርክ የሚለፈፈው የ11 በመቶ እድገት ዜጎችን ከስደትና ከመከራ ሊታደጋቸው እንዳልቻለ የሚያሳይ ነው ብሎአል። አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በዜጎች ሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጾ፣   ስደትና እልቂት ከዚህ የከፋ ጉዳት ከማድረሱ በፊት ህዝቡ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በሰሜን ማሊ ፤ ሰሐራ ምፍረ በዳ ጫፍ ላይ የምትገኘው ጥንታዊቷ ገናና የንግድ ማዕከል ቲምቡክቱ፣ እ ጎ አ በ 2012 ፣ ከአክራሪ ሙስሊሞች እጅ ከወደቀች ወዲህ የከተማይቱ የንግድ እንቅሥቃሴ ከቶውንም ማንሠራራት እንዳልቻለ ነው የሚነገረው።

በዓለማችን የተለያዩ ቦታዎች የእርስ በርስ ግጭት፣ ጦርነት፣ ያለመረጋጋት እና ወረርሽኝ ሰፍኗል። እንዲያም ሆኖ ግን ሊሰናበት ጥቂት ቀናት በቀሩት የጎርጎሪዮሳዊው 2014 ዓም ውስጥ የዓለም ምጣኔ ሀብት ሦስት በመቶ እንዳደገ ተነግሯል። የምጣኔ ሀብቱ ጭንቀት ይልቁንስ ወደ ዩሮ ዞን የንግድ ቃጣና መሸጋገሩ እንደማይቀር ተገልጧል።

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ነገ አርብ (03/04/07) ጠቅላላ ጉባኤውን ያደርጋል፡፡ ፓርቲው ከዚህ ቀደም በታህሳስ 19/20/2007 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን አመት ሳይሞላ ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ለምን እንዳስፈለገ የጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ የሆኑትን አቶ አስራት ጣሴን አነጋግረን ነበር፡፡ አቶ አስራት እንዳብራሩት በታህሳስ 2006 ዓ.ም ተካሂዶ በነበረው ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫ ቦርድ ማብራሪያ ጠይቆ ነበር፡፡ አቶ አስራት […]

Image

መሐሙድ የሱፍ የተወለደው በ1980ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ርእሰ-መዲና ጅጅጋ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውዶሀን ከተማ ነው፡፡ ለቤተሰቡ ሰባተኛ ልጅ ሲሆን፤ አምስት እህቶችእና ሦስት ወንድሞች አሉት፡፡ በጅጅጋ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ መዝለቁቢሳካለትም፤ ከዚህ በላይ ግን ሊቀጥል አልተቻለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያመንግስት የደህንነት ሠራተኞች የ1999ዓ.ም የግንቦት ሃያ በዓል በጅጅጋ ከተማ ስታዲዬም በተከበረበት ዕለት፣ የኦጋዴን ነፃአውጪ ግንባር (ኦብነግ) በሰነዘረው የቦንብ ጥቃት ተሳትፈሃል በሚል ለእስር በመዳረጉነው፡፡ ይህንን ተከትሎምከምድራችን አስከፊ ማሰቃያዎች መካከል ግንባር ቀደም በሆነውና የክልሉ

ነዋሪ “ጄል-አዳብ” (የገሃነም እስር ቤት) እያለ በሚጠራው ማጎሪያ ውስጥ እጅግ በጣም የከፋ ምድራዊ መከራ እንደተቀበለሀዘን በተጫነው ድምፅ ይናገራል፡፡ በሠውነቱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደ ፍም ቀልተው የሚታዩት ጠባሳዎቹም ያሳለፈውንሥቃይ አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ፡፡ ለአራት ወራት ያህል አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው ተቆልፎበት፤ ሃያ አራት ሠዓታትሙሉ እጆቹ በካቴና ተቀፍድደው፣በቀን ከአምስት ጊዜ በላይ ለምርመራ እየተጠራ ያለዕረፍት ከባድ ስቅየት (ቶርቸር)ሲፈፀምበት ቆይቷል:፡ በመጨረሻም ለአንዲትም ቀን የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጥ፣ ለኦብነግ አባላት አንድ ፓኬት ሲጋራሲያቀብል እጀ-ከፈንጅ ተይዟል በሚል ክስ የጅጅጋ ዞን ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን እዛው እስር ቤት ሆኖከኢትዮጵያ ሬዲዮ የዜና እወጃ እና ከቪኦኤ ሶማሊኛ ፕሮግራም ሠምቷል፡፡

ከፍርዱ በኋላም በተመሳሳይ ወንጀል ከተከሰሰ አንድ እስረኛ ጋር በካቴና ተጠፍሮ በቀን አንድ እንጀራ ለሁለት ተካፍሎእንዲበላ እንደ ውሻ እየተወረወረለት 60 ቀናትን አሳልፏል፡፡ መሐሙድ በተለይም በእንቅልፍ ወቅት እርሱ ወይምየሰንሰለት ደባሉ የተገላበጠ እንደሆነ ካቴናው የሚያደርስበትን የመለብለብ ቃጠሎ ሲያስታውስ ዓይኖቹ በእንባ ይሞላሉ፡፡በአሁኑ ወቅት በዝዋይ ማጎሪያ ከባድ ጥበቃ ለሚደረግባቸው ብቻ በተመደበ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ውስጥ አስራ አንድ ሶማሊኛተናጋሪዎችን ጨምሮ በድምሩ ሰላሳ አራት ሰዎች ጋር ከዛሬ ነገ የግፍ ፍርዱ ተፈጻሚ ሊሆንብኝ ይችላል በሚል ሰቀቀንእየባነነ በስጋት ተጠፍንጎ መኖር ከጀመረ እነሆ ሰባት ዓመት ሊደፍን ሦስት ወራት ብቻ ቀርተውታል፡፡

የተዋረደው የፍትሕ ሥርዓት!. . .

ርግጥ ነው ይህ በጨረፍታ ያቀረብኩት አሳዛኝ ታሪክ የመሐሙድ የሱፍ ብቻ አይደለም፡፡ ሌሎች ሰባት ‹‹አባሪዎቹ››ስቃዩንም ሆነ የሞት ፍርዱን ይጋሩታል (በነገራችን ላይ በአንድ መዝገብ የተወነጀሉት እነዚህ ስምንት የሞት ፍርደኞች፡-መሐድ ኢብራሂም፣ አረብ ሰዋኔ ዱልባንቲ፣ ሐሰን መሐመድ ዑስማን፣ ሐሰን መሐመድ ዓሊ፣ ሙክታር መሐመድ ዓብዱላሂ፣ከድር ሽኩር ሙሳ እና ካሚል ዓብዱልናስር እንኳን በጋራ መንግሥት ላይ ሊያሴሩ ቀርቶ እርስ በርስም የተዋወቁት እስር ቤትውስጥ ነው፡፡ ከጅጅጋ ወደ ዝዋይ ‹‹ዘጠነኛ ቤት›› ተዘዋውረው በርካታ ዓመታትን ያሳለፉትም በጭካኔው ወደርእንደማይገኝለት የሚነገረው የክልሉ ፕሬዚዳንት አብዲ

በአደራ እንዲቀመጡ በመተላለፋቸው መሆኑን ነግረውኛል፡፡) እንደ መሐሙድ ሁሉ እነርሱም ፍርድ ቤት ቀርበውአያውቁም፤ ምንም ዓይነት የሰውም ሆነ የሰነድ ማስረጃ አልተቆጠረባቸውም፡፡ እዚህ ጋ የማነሳው አሳዛኝ ገጠመኝከመካከላቸው አንዳቸውም ራዲዮ ስላልነበራቸው የተጣለባቸውን የሞት ፍርድ ውሳኔ የሠሙት፣ ዜናው ከተላለፈ ከበርካታቀናት በኋላ ሬዲዮ ካላቸው እስረኞች መሆኑ

ነው፡፡ ይህ እጅግ አሳፋሪና አስደንጋጭ መንግሥታዊ ውንብድና በደንብ ይብራራ ዘንድ ለተከሳሶቹ ከተሰጣቸው ባለ አንድገፅ የክስ ቻርጅ የሁለቱን ብቻ በአዲስ መስመር እጠቅሳለሁ፡-‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕቢሮ በሶማሌ ክልላዊ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት

ጅጅጋ

የዐ/ሕግ/መ/ቁ 90/2000

ዝዋይ እስር ቤት ያለው

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከሳሽ፡- ዐ/ሕግ

ተከሳሽ፡- ሐሰን መሐመድ ዑስማን (ሐንን መድቤ)

ዕድሜ፡- 21

ሥራ፡- ተማሪ

አድራሻ፡- ጅጅጋ ከተማ፡- 06 ቀበሌ

ወንጀል

በ1996ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ.መ.ሥ.ሥ.ህ.ቁ. 240(3) እና 251(መ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣

የወንጀል ዝርዝር

ተከሳሽ ከመስከረም 1999 ዓ.ም. ጀምሮ እራሱን ኦ.ብ.ነ.ግ. እያለ ከሚጠራው ተቃዋሚና አሸባሪ ድርጅት ጋር በራሱፈቃድ

በዚሁ በጅጅጋ ከተማ ከላይ በተጠቀሰው ዓመተ-ምህረት አባል በመሆን በጫካ በዚሁ አካባቢ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋርበከተማም

ሆነ በጫካ በመገናኘት በኢኮኖሚ ረገድ የሚያስፈልጋቸውን፡- ጫማ፣ ልብስ የመሳሰለውን እዚያው ድረስ ሄዶ በማቀበልአብሮ

ሲንቀሳቀስ በመቆየቱ ተከሶ ቀርቧል፡፡››

ሁለተኛው የክስ ቻርጅ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፡-

‹‹በሶማሌ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ፍትሕ ቢሮ

በሶ/ክ/መ/ ጅጅጋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት

ጅጅጋ

የዐ/ሕ/መ/ቁ 90/2000

ከሳሽ፡- ዐ/ሕግ

ተከሳሽ፡- መሐድ ሼክ ኢብራሂም

ዕድሜ፡- 28

ሥራ፡- የለውም

አድራሻ፡- ጅጅጋ ከተማ፡- ቀበሌ 05

1ኛ ክስ

ወንጀሉ

በ1996 ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ/መ/ህ/ ቁ. 241 እና 251(መ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣

የወንጀሉ ዝርዝር

ተከሳሹ በ1998 ዓ.ም. ወራትና ቀኑ በውል ካልታወቀ ጊዜ ጀምሮ እራሱን ኦ.ብ.ነ.ግ. እያለ ከሚጠራው ተቃዋሚ የፖለቲካ

ድርጅትና አሸባሪ ጋር በራሱ ፈቃድ አባል በመሆን ከዚህ ሕገ-መንግሥቱን ከሚፃረር ድርጅት በቀጥታ ፌዴሬሽኑእንዲከፋፈል፣ ክልሉን

የመገንጠል ዓላማ ለማሳካት ይህንኑ ድርጅት ከዚሁ በጅጅጋ ከተማ ለጊዜው ካልተያዘ ግብረ-አበሩ ጋር በመሆን ይህንኑአሸባሪ ድርጅት

በሚያስፈልገው ማቴሪያል ሁሉ፡- ጫማ፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ፣ መድሃኒት. . . የመሳሰለውን በማቀበሉ፡፡

2ኛ ክስ

ወንጀሉ

በ1996ዓ/ም የወጣውን የኤ.ፌ.ዴ.ሪ የመ/መ/ህ/ ቁ. 36 (ለ) ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፣

የወንጀሉ ዝርዝር

ተከሳሹ ከ1996 ዓ.ም. ጀምሮ የተለያዩ መ/ቤቶች ማለትም፡- የክልሉ ት/ቢሮን፣ የቀብሪ-ደሐር ት/ቢሮን፣ እንዲሁም የMSF

እና የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችን እና የትምህርት ተቋማትን ማህተም በማስመሰል አትሞ እና የኃላፊዎችን ፊርማ ዓይነትአስመስሎ

በማስፈር ሐሰተኛ ሰነድ አዘጋጅቶ በመገኘቱ ተከሶ ቀርቧል፡፡››

(ሁሉም የክስ ቻርጆች ማኅተም እና አንጋው አፈወርቅ ምንተስኖት የተባለ የክልሉ ዐቃቤ ሕግ ፊርማ አላቸው)

እነሆም ያለአንድ ምስክር፣ ያለምንም የሰነድ ማሰረጃ፣ አንድም ቀን ችሎት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃል ሳይጠየቁ እና

ሳይከራከሩ (ያውም የዞን ፍርድ ቤት) በነዚህ በስም በጠቀስኳቸው በስምንቱ ኢትዮጵያውን ላይ የሞት ቅጣትን የመሰለየመጨረሻ

ውሳኔ እንደቀልድ አስተላልፎባቸዋል፡፡ (በነገራችን ላይ ሌሎች 13 የኢትዮጵያ-ሶማሌ ተወላጆችም በተመሳሳይ የሐሰትውንጀላ የዕድሜ

ልክ እስር ተፈርዶባቸው ዝዋይ ይገኛሉ፡፡ የሚገርመው ጉዳይ ደግሞ ም ቢሆኑ መጀመሪያ ተጠርጥረው በተያዙበት ወንጀልአይደለምየተጠየቁት፡፡ ጉዳዩ ጭራሽኑ በምርመራም ወቅት አልተነሳም) መቼም በዚህ መልኩ በተቀናበረ የውሸት ክስ ከ20-27 ዓመት የሚገኙ

ወጣቶችን በሲኦላዊ እሳተ-ነበልባል ስቅየት ውስጥ እንዲያልፉ ከማድረግም በዘለለ፣ ብሩህ ቀናቸውን አጨልሞ ላይመለሱወደመቃብር

የሚሸኝ ቅጣት ሲጣል ከመመልከት የበለጠ የትኛውንም ዜጋ የሕሊና ስቃይ ውስጥ ከትቶ፣ አንገት አስደፍቶ፣ በቁጣ ቀስቅሶ

ወደአደባባይ የሚያወጣ ገፊ-ምክንያት አለ ብዬ አላምንም፡፡

ማነው ተጠያቂው?

በእነዚህ ንፁሃን ኢትዮጵያውያን ላይ ‹በጄል-አደብ› የደረሰባቸው በነውረኝነት የታጀለ ኢ-ፍትሐዊ ፍርድ እና ስቅየት፣

የሥርዓቱን እውነተኛ ማንነት ገሃድ የሚያወጣ ተጨባጭ ተግባር መሆኑ ባይካድም፡ ይህንን አረሜናዊ ድርጊት በፊት-አውራሪነት

የመሩት፡- ኮሎኔል ሞኒ መንገሻ በጊዜው የክልሉ የፀረ-ሽብር ግብረ-ኃይል ዋና ኃላፊ የነበረ አሁን ወደአዲስ አበባ ተቀይሮ‹ሕገ-ወጥ

የሠው ዝውውር ወንጀል መከላከል› ኃላፊ፣ ቢኒያም የተባለ የክልሉ የደህንነት ኃላፊ፣ ሻለቃ ዘገየ በክልሉ የፌዴራል ፖሊስኃላፊ፣

ወልደአራዌ የክልሉ ፖሊስ ም/ኮሚሽነር፤ እንዲሁም ሻለቃ ወንድሜ፣ ሻለቃ በለጠ እና ታሰረ የተባሉ ኃላፊነታቸውንለይተው

የማያስታውሷቸው ግለሰቦች መሆናቸውን ግፉአኖቹ በተሰበረ ልብ፣ ምሬት በሞላው ድምፅ፣ ተስፋ በቆረጠ ስሜትሲተርኩልኝ ዓይኖቼ

ላይ የተቋጠረው የእንባ ከረጢት ገንፍሎ እንዳይፈስ ብርቱ ትግል ማድረጌን አልሸሽግም፡፡

የሆነው ሆኖ እነዚህ የሥርዓቱ ሹማምንት የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጡ፣ የሞት ቅጣት እንዲተላለፍባቸው ባደረጓቸው

ምስኪኖች ላይ የማሰቃያ ጥበቦቻቸውን በሙሉ ከሞከሩባቸው በኋላ፡- ‹‹ሞት እንፈርድባችኋለን!!›› እያሉ ያስፈራሯቸውናይዝቱባቸው

ነበር፤ እነርሱም፡- ‹‹እናንተ ፍርድ ቤት ናችሁ እንዴ?›› ብለው በግርምትና ባለማመን ሲጠይቋቸው፣ ማናአህሎኝነትያሳበጣቸው የፀጥታ

ኃላፊዎች እንዲህ በማለት አስረግጠው መልስ መስጠታቸውን ሰምቻለሁ፡-

‹‹አዎን! ፍርድ ቤት ማለት እኛ ነን!!››

በርግጥ ከዚህ ሁሉ መከራ በኋላ የተላለፈባቸው ውሳኔ፣ ያውም በሞት እንዲቀጡ የሚል መሆኑን ስናስተውል የዛቻውን

መነሾ መረዳቱ አዳጋች አይሆንብንም፡፡ በአናቱም በምርመራ ወቅት ዕድል ፊቷን ያዞረችበትን ተጠርጣሪ እዛው እስረኛ ፊትበሽጉጥ

ግንባሩን በርቅሰው እንደ መናኛ ነገር ሜዳ ላይ ይዘረጉት እንደነበረ የዓይን እማኞች ይመሰክራሉ፡፡

በጥቅሉ ይህ ሁነት በሀገሪቱ አለቅጥ የተንሰራፋውን የፍትሕ እጦት፣ የሠብአዊ መብት ጥሰት፣ ዳኞች ከሕግ ይልቅ ከቤተ-

መንግሥት በሚላክላቸው የፍርድ ውሳኔ ንፁሃኑን ለምድራዊ ስቃይ ከመዳረግም አልፈው ተርፈው በጭካኔሕይወታቸውንም

እንደሚነጠቁ በቂ ማስረጃ ይመስለኛል፡፡

‹‹ጄል-አዳብ››

የክልሉ ኗሪዎች ‹‹ጄል-አዳብ›› (የገሃነም እስር ቤት) እያሉ የሚጠሩት የጅጅጋው ማሰቃያ ቤት ክፍሎች የተሠሩት አራትመቶ

ታሳሪዎችን እንዲይዙ ታስቦ ቢሆንም፣ አብዛኛውን ጊዜ ከአራት ሺህ በላይ ታሳሪዎች እንደሚታጎሩበት አረጋግጫለሁ፡፡ይህም አንድ

ሰው ከአንድ ሰዓት በላይ በእንቅልፍ ማሳለፍ እንዳይችል አድርጎታል፡፡ ምክንያቱም ቦታውን ለተረኛው የመልቀቅ ግዴታአለበትና፡፡

ምናልባት እንቅልፍ ቢጥለው እንኳ ተረኞቹ ቀስቅሰው (ጎትተው) ያስነሱታል፡፡

ከ‹‹ጄል-አዳብ›› በሕይወት ተርፎ የሚወጣ ሰው ዕድለኛ ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዚህ ቦታ ከቤተሰብ ጋር መገናኘት ጭራሽ

አይሞከርም፡፡ ማሰቡ እንኳ እንደ ቅንጦት ነው የሚታየው፡፡ በእስር ቤቱ አጥር ሦስት መቶ ሜትር ክልል ርቀት ዙርያ ውስጥመገኘትም

ለከባድ ስቃይ (አንዳንዴም ለሞት ቅጣት) ይዳርጋል፡፡ በሃያ አራት ሰዓት አንዴ፣ አንድ እንጀራ ለሦስት እየተቃመሱለአምስት ዓመት

በዛ እስር ቤት ያሳለፈ ምስኪን አጋጥሞኛል፡፡ ይህ ወጣት በ2004ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ሦስት ዓይነት ተላላፊ በሽታ(ተቅማጥ፣

ሰውነትን የሚያሳክክና ጉሮሮን አሳብጦ ለአዕምሮ መቃወስ የሚዳርግ) ተከስቶ በቀን እስከ አስራ አራት ሰው ድረስ ይሞትእንደነበር

ያስታውሳል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ሕክምና ብሎ ነገር አልነበረም፡፡ እንዲያውም በግልባጩ የክልሉ አስተዳዳሪዎችጭካኔያቸውን (ኢ-

ሠብአዊነታቸውን) ወለል አድርገው የሚያሳብቁ ድርጊቶች መፈፀማቸውን አላቋረጡም፡፡ ለማሳያ ያህልም እስረኛው ከሌሊቱስድስት

ሰዓት ላይ በአንድ ድምፅ እንዲህ የሚል መፈክር እንዲያሰማ መገደዱን እዚህ ጋ መጠቀስ ይቻላል፡-

‹‹መለስ ዜናዊ ሐኖላዶ!›› (መለስ ዜናዊ ለዘላለም ይኑር!)

‹‹አብዲ ሑመድ ዑመር ሐኖላዶ!››

‹‹ኢትዮጵያ ሐኖላዶ!››

ኦብነግ ሐዳኦዶ!›› (ኦብነግ ይውደም!)ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ቤተሰብ ታሳሪ ልጁ በሕይወት ይኑር ይሙት የሚያውቀውከማጎሪያው በስንት ጊዜ አንዴ የሚፈታ

ሰው ሲገኝ ብቻ የመሆኑ እውነታ ነው፡፡ እናም ድንገት በአንዲት ‹ዕድለኛ› ቀን አንድ ታሳሪ ከ‹‹ጄል-አዳብ›› የተለቀቀእንደሆነ ወሬው

ከመቅጽበት ይዛመትና ለሳምንታት አሊያም ለወራት የእስረኛው ቤት በእንግዶች እስከ አፍ-ገደፉ ጢም ብሎ ይውላል፡፡የተለመደ

ነውና እሱም ያለመታከት የቀረበለትን ጥያቄ በሚከተለው መልኩ ሲመልስ ይከርማል፡-

‹‹ኦ!… እገሌ ከሞተ እኮ ሁለት ዓመት አለፈው›› ፤ “እገሌማ ሲያሳዝን! ካረፈ ገና አንድ ወሩ ነው”፤ “ኦ! እገሌ ለወደፊቱ

እግዜር ይጠብቀው እንጂ እስካሁን በሕይወት ይገኛል…” ወዘተ ወዘተ. . .

አንዳርጋቸው እንዴት ከወያኔ እጅ ሊገባ እንደቻለ ዛሬም ድረስ ግልፅ መረጃ የለም። የተለያዩ መላ ምቶችን እየሰማን፣ እያነበብን ቆይተናል። አንዳርጋቸውን በቅርብ ከሚያውቁት አንዱ እንደመሆኔ እኔም ካለኝ መረጃ በመነሳት የራሴን ግምት መውሰዴ አልቀረም። የኔን ግምት ይፋ ከማድረጌ በፊት ሌሎች የሚሉትን ለመስማት በሚል እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ሳልፅፍ ቆይቼ ነበር። አሳማኝ መረጃ ሳይፃፍ ወይም ሳይገለፅ ጊዜው ስለረዘመ እነሆ! እኔም የግል አስተያየቴን ለማኖር ወሰንኩ… (ቅዳሜ ለንባብ ይበቃል)

በቦረና ዞን ገላን ወረዳ የአንድነት አባላት መታሰራቸውን ከአከባቢው በደረሰን ሪፖርት አረጋግጠናል። የታሳሪዎቹ ስም ዝርዝር አቶ በድሉ መንግስቱ በቦረና ዞን ገላን ወረዳ ሰብሳቢ፣ አቶ ቆንጨሪ ሳፋይ አባል አቶ ንጉሴ ገልገሎ አባል አቶ ብርሃኑ ሳፋይ አባል ሲሆኑ፤ ሰብሳቢው አቶ በድሉ መንግስቱ የታሰሩት የመንግስትን ስም አላግባብ አጥፍተሀል ተብለው ነው። በተያያዘ ዜና በምስራቅ አሩሲ የኦሆዴድ አባል፣ የጢዮ ወረዳ የሲቪል […]

ኢትዮጵያችን ከምትታወቅባቸው ዘርፈ ብዙ ገዥ- ወለድ ችግሮች መካከል ስደት አንዱ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ ዜጎቻችን በሀገራቸው ላይ ሰርተው የመኖር ዋስትና በመነፈጋቸው፤ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው እናስተዳድራችኋለን በሚሉ ገዥዎች በመጨፍለቁ የተሸለ ነፃነትና ኑሮ ፍለጋ እግራቸው በመራቸው መሰደድ የተለመደ ሁኗል፡፡ ገዥው ፓርቲም ከራሱ የስልጣን ቆይታ በስተቀር ሀገራዊ አደጋ እየሆኑ የመጡና የዜጎችን ስነ-ልቡና የሚጎዱ ሁነቶችን እንደማንኛውም ዜጋ አድማጭ ከመሆን በዘለለ ችግሩን […]

የታሰሩ እንዲፈቱ በፖለቲካ ድርጅቶች ላይ የሚደረገው ወከባና ጫና እንዲቆም በመግለጫው ጠይቋል::
http://www.andargachewtsige.com/?p=343

Image

በሰሜን ምሥራቅ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ውስጥ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት ማሕበረሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እደጣለዉና መፍትሄ አልባ እንዳደረገዉ ተገልፆአል። የሲቪሉ ማሕበረሰብ ድርጅቶች አማፅያን የሚያደረሱት ጥቃት ለመከላከል የዓለም አቀፉን ርዳታ ጠይቀዋል።

በ  
የአንድ ዓመት ዕድሜ ያለውን ህፃን ልጇን ተሰድቤበታለሁ፤…

ዛሬ ዛሬ ከረጅም አመታት ጀምሮ በሃገራችን የተነሳው የሴቶች መብት ይከበር የሚለውን ይህዝብ ጥያቄ ለመቃረን እስኪመስል ድረስ ከባለፉትም ጊዜያቶች በባሰ ሁኔታ የሴቶች መብት እየተጣሰ ይገኛል። ከዛም አልፎ ተቆርቋሪ አካል የሌላቸው የሃገራችን ሴቶች ህይወታቸው አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል። ለዚህም በየጊዜው ወደ ተለያዩ አፍሪካና አረብ ሃገራት በተለይም በሱዳን በየመን የሚፈልሰው የኢትዮጵያውያን ሴቶ ች ቁጥር መጨመር ማረጋገጫ ነው። በተለያዩ […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
ብዙዎቻችን በስርቅርቅ ድምጻቸው እናውቃቸዋለን፡፡ እጅግ በተዋጣለት የኦርኬስትራ ቅንብር በመታጀብ የተጫወቷቸው ጥዑም ዜማዎች  በአዕምሮአችን ላይ ተቀርጸዋል፡፡ እኔ ጸሐፊው ሙዚቃቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁበትን አጋጣሚ አላስታውስም፡፡ ሆኖም የነርሱን ዘፈን በምሰማበት ጊዜ ሁሉ ሶስት ነገሮች ይታወሱኛል፡፡
   የመጀመሪያው ከተማችንን (ገለምሶን) ለሁለት ከፍሎ የሚያልፈውን አውራ ጎዳና ተከትለው ከተደረደሩት ሻይ ቤቶች ይንቆርቆር የነበረው የእንስቶቹ ዝማሬ ነው፡፡ በተለይም የሻይ ቤቶቹ ባለቤቶች በበርካታ የህብረተሰብ ክፍል እንደ ህብረ-ዜማ ይዘፈን የነበረውን “መሼና መሼና”ን እየደጋገሙ ማጫወታቸው የየዕለቱ ትዕይንት ሆኖ እንደቆየ አስታውሳለሁ፡፡ ሁለተኛው አይረሴ አጋጣሚ የተከሰተው በትምህርት ቤት ቆይታዬ ነው፡፡ በ1980 የአምስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ከለገዳዲ ሬድዮ ጣቢያ የሚተላለፈውን “የህብረተሰብ ትምህርት በሬድዮ” ለማዳመጥ በሄድንበት አንድ ጠዋት “ተማሪዎች፤ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆነችውን ሱዳንን ታውቋታላችሁ?” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ትምህርት ተሰጠን፡፡ የሬድዮ ትምህርቱን የሚያቀርበው ባለሙያ “ሱዳን፣ በአፍሪቃ ትልቅ ሀገር ናት፤ ስፋቷ ወደ አንድ ሚሊዮን ስኩዌር ማይልስ ይጠጋል፤ ዋና ከተማዋ ካርቱም ነው” እያለ በሚያስተምርበት ጊዜ በየአፍታው እንደመሸጋገሪያ አድርጎ የተጠቀመው እንስቶቹ “ለውነል መንጋ” እያሉ የሚያዜሙትን ተወዳጅ ዘፈን ነበር፡፡ ያንን ዘፈን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት በዚያች ዕለት ነው፤ ከዚያ በኋላ ከጭንቅላቴ ላወጣው አልቻልኩም፡፡
  ሶስተኛው አጋጣሚ በ1984 በአንዲት የማክሰኞ ምሽት ነው የተከሰተው፡፡ በዕለተ ማክሰኞ ሲገበያይ የሚውለው የከተማችን ህዝብ የቀኑን ድካም ለማራገፍ ሲል ምሽት ላይ እራቱን ከበላ በኋላ ሆጃና ሻይ አፍልቶ ለበርጫ መሰየሙ የተለመደ ነገር ነው፡፡ እኔም በዚያች የማክሰኞ ምሽት አብዱልቃዲር ከተባለ ዘመዳችን ሱቅ ሄድኩና ከጥቂት ጓደኞቹ ጋር በርጫውን ሲያስኬድ አኘሁት፡፡ አብዱልቃዲር ለበርጫው ማሟሟቂያ የመረጠው የእንስቶቹን ተወዳጅ ካሴት ነው፡፡ በተለይም ደግሞ “ኡሸ ሰጊራ፣ ኪፋያ ዐለይና” የተሰኘውን ዘፈን ይደጋግመው ነበር፡፡ እኔም የአብዱልቃዲር ሁናቴ አስገርሞኝ ስለእንስቶቹ እንዲያጫውተኝ ጠየቅኩት፡፡ እርሱም የዘፋኞቹን ማንነትና የሙዚቃ ጉዞአቸውን እያዳነቀ ተረከልኝ፡፡ እንግዲህ በዚያች አጋጣሚ ነው ስማቸውን ለመያዝ የበቃሁት፡፡
*****
አዎን! የኢትዮጵያን ሙዚቃ አውቃለሁ የሚል ሰው ሶስቱን የሱዳን ድምጻዊያን በደንብ ነው የሚያውቃቸው፡፡ እነዚህ እንስቶች እህትማማቾች ናቸው፡፡ ትክክለኛ ስማቸውም “ሐያት”፣ “አመል” እና “ሃዲያ” ነው፡፡ በዓለም ዙሪያ በደንብ የሚታወቁት ግን “አል-በላቢል” በተሰኘው የቡድን ስማቸው ነው (በዐረብኛ “አል-ባቢል” ሲባል “ዘማሪ ወፎች” እንደማለት ነው)፡፡ በምስራቅ አፍሪቃ የሙዚቃ ታሪክ የነርሱን ያህል የሚታወቅ የሴት ድምጻዊያን ቡድን የለም፡፡
“አል-በላቢል” በሰሜን ሱዳን በዋዲ-ሃልፋ ከተማ ነው የተወለዱት ነው፡፡ የአፍ-መፍቻ ቋንቋቸው “ኑቢያ” ነው፡፡ ሙዚቃን በዋዲ ሃልፋ ቢጀምሩትም ከእውቅና ማማ ላይ የወጡት ግን በካርቱም ከተማ ነው፡፡ በተለይም እንስቶቹ እ.ኤ.አ ከ1974-እስከ 1982 በነበረው ዘመን በሱዳን ሙዚቃ ላይ ነግሰው ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ያወጧቸው “መሼና”፣ “ሙትዓሉ ዐለይና”፣ “ሸባብ አንኒል”፣ “ዑሸ ሰጊራ”፤ “ለውነል መንጋ”፣ “ሒልዊን ሐለዋ”፣ “ጣኢረል ጀንና” የመሳሰሉት ዘፈኖቻቸው ዘመን ተሻግረው እስከ ዛሬም ድረስ ይደመጣሉ፡፡
  የአል-በላቢል አዕዋፋት ዝና በምድረ-ሱዳን ብቻ አልታቀበም፡፡ ከካይሮ እስከ ሞምባሳ፣ ከበርበራ እስከ ባማኮ (ማሊ) ባሉት የአፍሪቃ ከተሞች የሚኖሩ የሙዚቃ አፍቃሪዎች በስራቸው ተማርከውላቸዋል፡፡ በኢትዮጵያ፣ በግብጽ፣ በሶማሊያ፣ በጅቡቲ፣ በቻድ፣ በኬንያ፣ በናይጄሪያ፣ በአልጄሪያ፣ በማሊና በሌሎችም የአፍሪቃ ሀገራት ሙዚቃዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮጳና በአሜሪካም ተዟዙረዋል፡፡
*****
ሆኖም ሶስቱ እንስት ከ1986 በኋላ የሙዚቃ ስራቸውን በአንድ ላይ ለመቀጠል አልቻሉም፡፡ ትልቋ “ሐያት” እና ሁለተኛዋ ሃዲያ በጋብቻ ምክንያት ሱዳንን በመልቀቃቸው ብዙዎች ያደነቁላቸው የቡድን ስራቸው በመንገድ ላይ ቀረ (ሐያት በአሜሪካ፣ ሐዲያ ደግሞ በባህሬን ይኖሩ ነበር)፡፡ ሆኖም የሱዳን ህዝብ እንዲሁ አልተዋቸውም፡፡ እንስቶቹ በአንድ ላይ ተሰባስበው ስራቸውን እንዲሰሩ በልዩ ልዩ መንገድ ጫና ሲያደርግባቸው ነበር፡፡ እነርሱም ለህዝቡ ውዴታ በመሸነፋቸው በድጋሚ በመሰባሰብ የሙዚቃ ስራቸውን ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
    ታዲያ አል-በላቢል በድጋሚ የቡድን ስራቸውን በጀመሩበት የአውሮጳዊያኑ 1998 አጋማሽ ላይ የለቀቁት “ኩልለ-ኑጁም” የተሰኘው አልበም በዓለም ዙሪያ በእልፍ አዕላፍ ቅጂዎች ነው የተሸጠው፡፡ የሱዳን የሙዚቃ ኤክስፐርቶች በዚያ አልበም የተካተቱትን ስራዎች ከሀገሪቱ የምንጊዜም ተወዳጅ ዜማዎች መካከል ደምረዋል፡፡ በተለይም የአልበሙ መጠሪያ የሆነው “ኩልላ-ኑጁም” የተባለው ዜማ ከሱዳን አልፎ በውጪው ዓለም (በጀርመን) ለሽልማት አብቅቶአቸዋል፡፡ የአውሮጳ ህብረት በበኩሉ ታህሳስ 11/ 2013 ባዘጋጀው ልዩ ዝግጅት እህትማማቾቹ ለሱዳን ሙዚቃ እድገት ላደረጉት አስተዋጽኦ ዓለም አቀፍ ሽልማት ሸልሞአቸዋል፡፡ እንስቶቹ የምታዩትን ፎቶግራፍ የተነሱት ሽልማቱን በተቀበሉበት ወቅት ነው፡፡
*****
አል-በላቢልን በሌላ ቀን እንዘይራቸዋለን፡፡ ለዛሬ ግን በኛ ሀገር በስፋት የሚታወቀውን “መሼና”ን እንገባበዝና እናብቃ፡፡
 መሼና መሼና መሼና
ቢጠሪቀል ሑብቢ መሼና
አዕዛቡ ያ ናር አልጊና
መሼና መሼና መሼና…
(እህትማማቾቹ መሼናን ሲዘፍኑ ለማየት የሚከተለውን ሊንክ ይክፈቱ)፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 4/2007
ገለምሶ-ምስራቅ ኢትዮጵያ
—-
The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia.  You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.