ቤኒሻንጉል ጉሙዝን ለመገንጠል የሽብርተኝነት ድርጊት ፈጽመዋል በሚል የተጠረጠሩ ተከሰሱ Ethiopia formally charges 10 men in attempting to separte Benshangul Gumuz region and disrupt construction of Renissance dam
ተጻፈ በ ታምሩ ጽጌ
-የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለማስተጓጐል ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው ተጠቁሟል በታምሩ…
ተጻፈ በ ታምሩ ጽጌ
-የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ለማስተጓጐል ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው ተጠቁሟል በታምሩ…

የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች (Amara Force) እኛ በውህደቱ የለንበትም ብሏል::
Minilik Salsawi ምንሊክ ሳልሳዊ – ከአስመራ ከተማ የሚገኙ ምንጮቼ በስልክ እንዳስታወኩኝ ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ የግንቦት ሰባት አመራር አባላት የሆኑት አቶ ነእመን ዘለቀ:የአቶ አንዳርጋቸው ወንድም አቶ ብዙአየሁ ጽጌ አቶ አበበ ቦጋለ እና ሌሎች የኢሳት ሪፖርተሮችን አስከትለው አስመራ የገቡ ሲሆን የአርበኞች ግንባር አመራሮች ወደ አስመራ የሚልኩትን ሰው መርጠው ባለመጨረሳቸው እንደዘገዩ ሲጠቆም እስከ እሁድ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል::ዶክተር ብርሃኑ ነጋ መግባታቸውን ለማረጋገጥ ቢሞከርም ሆተሎች ጥብቅ የጸጥታ ክትትል ስለሚደረግባቸው መረጃዎች ለጊዜው እንዲዘገዩ ተደርጓል::
በአስመራ የተለያየ ሆተል ማረፊያ የተዘጋጀላቸው የግንቦት ሰባት አመራሮች የአርበኞች ግንባር አመራሮች እንደገቡ በመጭው አዲስ አመር ጥር መጀመሪያ የውህደት መስራች ጉባያቸውን በማድረግ የአርበኞችና ግንቦት ሰባት ዲሞክራሲያዊ ግንባር ይመሰርታሉ ተብሎ ሲጠበቅ ውህደቱን የአርበኞች ግንቦት ሰባት ደምህት እና ሻእቢያ ሰራዊቶች ሊያጅቡት ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል ሲሉ ምንጮቹ ከአስመራ ገልጸዋል::
እንደ ደምሕት እና ኦነግ እንዲሁም የጋምቤላ ቤንሻንጉል እና አፋር ነጻ አውጪዎች በውህደቱ እንዳይሳተፉ ተደርጓል ያሉት የአስመራ ምንጮች ሻእቢያ የጎሳ ድርጅቶችን ለአላማው ስለሚተቀምባቸው ከአንድነት ሃይሎች ጋር እንዲዋሃዱ አይፈሊግም ሲሉ ተናግረዋል::(በዚህ ጉዳይ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ምንጮቹ አሁን እንዳይጻፍ ጠይቀዋል::)
የአይሮፕላን ወጪያቸውን ሸፍነው አስነራ የደረሱት ነጻ አውጪዎች በሻእቢያ አስመራ ከተማ ውስጥ ሙሉ ወጪያቸው ሲሸፈን የመብራት አገልግሎት እንዳይቋረጥባቸው ጄኔራተር በመትከል እና እንዲሁም የደህንነት እና የጸጥታ ጥበቃ በማድረግ ላይ እንደሆነ ምንጮቹ ሲናገሩ በግንባር ያገኟቸው የግንቦት ሰባት ሰዎች ለጊዜው ዝርዝር ምረጃ ሊሰጡ ፈቃደኞች እንዳልሆኑ ገልጸዋል::
በውህደቱ ዙሪያ በአርማጮ በረሃ ያሉትን የአማራ ፎርስ ሰራዊት አመራሮችን አነጋግሬቸው እንደመለሱልኝ ከሆነ ክታሰሩ አባሎቶቻችን ውጪ በአስመራ ያለንን ሃይል ያስወጣን እና ከሻእቢያ ጋር ያለውን ግንኙነት ዘግተናል ሲሉ የገለጹ ሲሆን ካሁን በፊት ባወጡት መግለጫ ከአስመራ መንግስት ጋር ሆኖ ዪትዮጵያን ህዝብ ነጻነት ማሰብ ስህተት መፍጠር ነው ሲሉ ገልጸው ነበር::በአስመራ በኩል የተዘጋጁትን ነጻ አውጪዎች የተሳካ ቀሪ ዘመን እየተመኘው ቀሪ ዝርዝር ዘገባ ይዤ ለመመለስ ቃል እገባለሁ:: #ምንሊክሳልሳዊ
ባልተለመደ ሁኔታ ዘግይተው የተሰየሙት ዳኞች የጠበቆች የተሻሻለው ክስ ላይ ያላቸውን አስተያት ማቅረባቸውን ሰምተዋል፡፡ የተከሳሽ ጠበቆች ክሱ ላይ የጽሁፍ አስተያየታቸውን ማቅረባቸውን ነገር ግን አቃቤ ህግ ክሱን አለማሻሻሉን በቃል ክርክር ለማቅረብ ቢሞክሩም ፍርድ ቤቱ የቃል ክርክር አስፈላጊ አንዳልሆነ እና መሻሻል አለመሻሻሉን አይቶ አንደሚወስን በማሳወቅ የጠበቆችን የቃል ክርክር ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል፡፡ ከፍርድ ሂደቱ በኋላ አስተያየታቸውን የሰጡት ጠበቃ አምሃ የጽሁፍ ምልልሱ የፍርድ ሂደቱን እያጓተተው በመሆኑ በቃል ማስረዳትን አንደአማራጭ ለመጠቀም ፈልገው አንዳልተሳካ ገልጸዋል፡፡
ከሰአታት ጥበቃ በኋላ የተሰየመው የልደታው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የፍርድ ሂደቱን ለታህሳስ 27 በመቅጠር ተጠናቋል፡። በእለቱ የጦማሪ ዘላለም ክብረት የልደት ቀን መሆኑን አስመልክቶ ብዙዎች ወዳጆቹ የመልካም ልደት ምኞታቸውን ገልጸውለታል፡። ጦማርያኑ ሲገቡ በጀርባ በር በኩል አንዲገቡ በመደረጋቸው ከሚጠብቃቸው ቤተሰብ እና ወዳጅ ጋር በደምብ ሰላምታ ለመለዋወጥ ባይችሉም በጠንካራ መንፈስ ጥንካሬ እና ፈገግታ ታይተዋል፡፡
#Ethiopia #FreeZonebloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsemamaw![]() |
|
| The bloggers and journalists outside at lideta court |
![]() |
||
| Edom Kassaye (journalist) and Mahilet Fantahun (bloggers) today outside court |
![]() |
|
| Birthday man, Zelalem Kibret with Zone9bloggers and Journalists |
“History was giving us another chance to redeem two opportunities in less than a generation is a privilege seldom granted to a people; squandering both of them is a crime that will not be forgiven by posterity”
ታኀሳስ ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ የፌደራልና የክልል የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊዎች በባህርዳር በተሰባሰቡበት ወቅት የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር የሆኑት ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም ፣ ይህን የተናገሩት የሃይማኖት ተቋም የፖለቲካ ፍላጎት ማራመጃ መሆኑን ለማስረዳት ነው። ዶ/ር ሽፈራው ከአፋር የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ” መንግስት ለምን በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ ይገባል? ለምንስ በአገራችን የሌለ ችግር ያመጣብናል?” በሚል ጥያቄ ቀርቦላቸዋል። …
ታኀሳስ ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአካባቢው ሰዎች እንደገለጹት በአፋርና በኢሳ መካካል ያለውን የቆየ የድንበር ውዝግብ ተከትሎ መንግስት የተወሰኑ ቦታዎች ወደ አፋር ክልል እንዲካተቱ መወሰኑን ተከትሎ በተነሳ ተቃውሞ 7 ሰዎች በጸጥታ ሃይሎች ሲገደሉ ከ30 በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆስለዋል። በርካታ ሰዎችም ተይዘው ወደ አልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። አሁንም በአካባቢው ከፍተኛ ውጥረት የሰፈነ ሲሆን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች መንግስትን …
ታኀሳስ ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ንግድ ሚኒስቴር የዋጋ ቅናሹን ካደረገ በሃላ ማደያዎች አዲሱ ታሪፍ አያወዋጣንም በሚል መናገራቸውን ተከትሎ የአቅርቦት እጥረት የተፈጠረ ሲሆን ሚኒስቴሩ የተወሰኑ ማደያዎችን በማሸግና በማስፈራራት ነገሩን ለማርገብ ቢሞክርም ችግሩ ሳይቀረፍ 8ኛ ቀኑን ይዞአል፡፡ በቦሌ፣ በካዛንቺስ፣ በንፋስስልክ በሌሎችም የከተማዋ አካባቢዎች በየማደያው ረጃጅም ሰልፎች የሚታዩ ሲሆን የችግሩ ትክክለኛ መንስኤ ምን እንደሆነ እንዳላወቁያ ያነጋገርናቸው …
ታኀሳስ ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቢቢሲ ባለስልጣናትን ጠቅሶ እንደሰገበው በታሊባን የተፈጸመ ነው በተባለው በሲህ ጥቃት ከሞቱት መካከል በርካታዎቹ ህጻናት ናቸው። ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱ አምስት ወይም ስድስት የሚሆኑ ታጣቂዎች ወደ ትምህርት ቤቱ መግባታቸውን የትናገሩት ባለስልጣናቱ፤ ወዲያውኑ አካባቢው በደህንነቶች እንዲከበብ መደረጉን ተከትሎ የተኩስና የፍንዳታ ድምጽ መሰማቱን ተናግረዋል። ወደ 500 ከሚጠጉ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በርካቶቹ ማምለጣቸውን …
በጁባ ጭፍጨፋ የተፈጸመበት አንደኛ ዓመት ያሉትን በጋዜጣዊ መግለጫ ያስታወሱት የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚዎች ፕሬዚደንት ሳልቫኪር ማያርዲት የኑዌር ተወላዶችን ለይተዉ አጥቅተዋል ሲሉ ወንጅለዋል።
(አሥራት አብርሃም – የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ‹‹የአንድነት እስትራቴጂ ከሁሉም ይለያል!›› በሚል ርዕስ በፌስቡክ ገጹ ያተመው) በምርጫው እንደሚሳተፉ እርግጠኛ ሳይሆኑ የምርጫ ምልክት ከወሰዱ ፓርቲዎችና በሂደቱ በደመነፍስ ከገቡ ፓርቲዎች አንድነት በእርግጠኝነት የተሻለ አቅጣጫ ያስቀመጠ ፓርቲ ነው። የፖለቲካውን ምህዳር ህዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር በማስፋት በምርጫው ላይ በሙሉ ልብ ለመሳተፍ ወስኗልና። አንድነት በባዶ መሬት ህዝቡን ሳያደራጁ ህዝባዊ አመፅ ከሚጠሩትም በእጅጉ የተሻለ እቅድ ያለው ፓርቲ ነው! አሥር ሰው ይዞ ፓርቲ መመስረት ይቻል ይሆናል አሥር ሰው ይዞ ስርዓት መቀየር ግን የሚታሰብም፤ የሚቻልም አይደለም። ስለዚህ እስኪ በመጀመሪያ ህዝቡ ከጫፍ እስከጫፍ ይደራጅ፤ እስኪ በምርጫው ሂደት በንቃት እንዲሳተፍ እናድርገው፤ ከዚያ ባግባቡ የተደራጀ ህዝብ ምን ማድረግ እንደሚችል ለማየት ቀላል ነው የሚሆነው። መምረጥ የሚችል ዜጋ ሁሉ በትክክል የህዝብ ታዛቢዎች ይምረጥ፤ የምርጫ ካርድ በነቂስ ወጥቶ ይያዝ፤ እንደገናም በነቂስ ወጥቶ ይምረጥ ይህን ሁሉ ሂደት ከታለፈ በኋላ ምርጫው የሚዘረፍ ከሆነ ያኔ ይህ የተደራጀ ህዝብ ህዝባዊ እምቢተኝነት ለማካሄድ በቂ የሆነ ምክንያት ይኖረዋል። የአንድነት እቅድ ይሄ ነው፤ ሌላ እቅድ አለኝ የሚል ካለ መብቱ ነው፤ አንድነት በእኔ እቅድ አጨብጫቢ ሆኖ ይሰለፍ ማለት ግን ተገቢ አይደለም፤ ተቀባይነትም የለውም። አንድነት በመላ ሀገሪቱ ሰፊ መዋቅር ያለው፣ ስለአባላቱና ስለህዝቡ ሀላፊነት የሚሰማው ፓርቲ ንው። ከዚህም ባሻገር የነገው መንግስት መሆን የሚያስችለው ቁመናና ስብስብ ያለው ፓርቲ ነው። በዚህ ምክንያት በእርሱ ክብደት ድልድዩን አንቀጠቀጥነው ለማለት ለሚመኙ ሁሉ የሚመች ፓርቲ አይሆንም፤ ከሆያሆዬ ፖለቲካ ነጥሮ ከወጣም ቆይቷል። […]
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የሊማዉ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤ የበለፀጉትና ደሀ ሃገራት ለአየር ንብረት ለዉጥ ሊደረግ ይገባል የሚሏቸዉ አጣዳፊ ጉዳዮች በመለያየታቸዉ ምክንያት ብዙም ዉጤት ያመጣል የሚል ተስፋ ሳያሳድር ነበር የተጀመረዉ።
በምዕራብ አፍሪቃዉያኑ ሃገራት ማለትም በሴራሊዮን በጊኒና ላይቤርያ የኤቦላ ወረርሽኝ ስርጭት አሁንም አልተገታም። ናይጀርያዊዉ የተዋሐሲ ጉዳዮች ጥናት ባለሞያ ከዶቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ በምዕራብ አፍሪቃ የኤቦላ ተዋሐሲ ጨርሶ አለመጥፋት ዋና ምክንያት የአፍሪቃዉያኑ ዉሳኔ ሰጭዎች የአሠራር ጉዳይ ነዉ፤
የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪርን በሚደግፉ የመንግሥት ወታደሮችና በቀድሞዉ ምክትል ፕሬዚዳንት ሪክ ማቻር ደጋፊ ኃይላት መካከል የተጀመረዉ ጦርነት አንድ ዓመት አስቆጠረ።
ዘጠኝ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባለፈው ሳምንት የጠሩትን ሰልፍ ተከትሎ የፓርቲው አባላት መታሰራቸው ከፖለቲካ ጥላቻ የመነጨ ነው ሲሉ የፓርቲዎቹ ትብብር ሊቀ መንበር ኢንጅንየር ይልቃል ጌትነት ገለጹ።
በደቡብ ጀርመን ኑርንበርግ ከተማ አቅራቢያ ለስደተኞች በተሰናዱ መጠለያዎች ላይ ቃጠሎ ከደረሰ በኋላ ፤ ቃጠሎውም ሆን ተብሎ እንደደረሰ የሚጠቁሙ የፅንፈኞች ምልክቶች በመገኘታቸው ፖሊስ ምርመራውን አጠናቅሯል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በተለያዩ ከተሞች ዘረኝነትን የሚቃወሙ እና የሚደግፉ ሰልፎች በመካሄድ ላይ ይገኛሉ።
በጊኒ፣ ላይቤሪያ እና ሲየራ ልዮን የብዙ ሺዎችን ሕይወት እያጠፋ ያለውን የኤቦላ ወረርሽኝ ለማጥፋት ከያቅጣጫው ጥረቱ ተጠናክሮዋል። በዚሁ መሠረትም፣ በርካታ ሀገራት እና ድርጅቶች ባለፈው ዓርብ የአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን የፀረ ኤቦላ ትግል ግብረ ኃይል አስተባባሪ በጠራው ስብሰባ ላይ በመገኘት
ሀሳን አሊ ለበርካታ አመታት የአሸባብ አባል ሆነው ሰርተዋል። መፃፍ እና ማንበብ በመቻላቸውም በተለያዩ የቡድኑ ዘርፎች ተሰማርተው ነበር። ሀሳን አሊ የአሸባብ ቡድንን እንዴት እንደተቀላቀሉ እና በምን ምክንያት ቡድኑን እንደከዱ፤ ለዶይቸ ቬለ ገልፀዋል።
በምዕራብ አፍሪቃዉያኑ ሃገራት ማለትም በሴራሊዮን በጊኒና ላይቤርያ የኤቦላ ወረርሽኝ ስርጭት አሁንም አልተገታም። ናይጀርያዊዉ የተዋሐሲ ጉዳዮች ጥናት ባለሞያ ከዶቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ በምዕራብ አፍሪቃ የኤቦላ ተዋሐሲ ጨርሶ አለመጥፋት ዋና ምክንያት የአፍሪቃዉያኑ ዉሳኔ ሰጭዎች የአሠራር ጉዳይ ነዉ፤
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሚልዮኖች ድምጽ ለነጻና ፍትሀዊ ምርጫ ባለው ዘመቻ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣን ባለቤት አደርጋለሁ አለ። ፓርቲው በአሁኑ ጊዜ በመላ የሀገሪቱ ክፍሎች መዋቅሩን መዘርጋቱናን በየትኛውም ደረጃ የምክር ቤት እጩዎችን ለማቅረብ እንደሚችል ገልጿል።
“ሰማያዊ/ትብብሩ ምርጫዉን ያለ ቅድመ ሁኔታ ለመሳተፍ መወሰናቸው ታወቀ” በሚል የትብብሩን ዋና ጸሐፊ አቶ ግርማ በቀለን በመጥቀስ መዘገባችን ይታወቃል። አቶ ግርማ በቀለ “NO Precondition is set by members of Tibibir. We decided to be part of the election and advised all members to take their election Sign. Believe me, it is all the decision of Tibibir […]
በዩናይትድ ስቴትስ የፖሊስ ኃይል ፀጥታ የማስጠበቅ አሠራሮችን የሚለውጥ ህግ እንዲወጣ አሜሪካዊያን ቅዳሜ – ታኅሣስ 4/2007 ዓ.ም ትዕይንተ-ህዝብ አካሂደዋል።
March for Justice – Washington, DC – Dec 13-2014
ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ አንድነት ፓርቲ ከአሁን በፊት ቀደም ብሎ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በሚል ሰፊ የሆነ ህዝባዊ ንቅናቄ ማድረጉ የሚታወቅ ነው። በመቀጠል ደግሞ የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነትና የሚሊዮኖች ድምፅ ለህሊና እስረኞች የሚሉ ዘመቻዎች በተከታታይ አካሄዷል። የዚህ ዘመቻ የመጨረሻው ምዕራፍ የሆነው የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃና ፍትሀዊ ምርጫ በዚሁ እጅግ የተሳካ ጉባኤ ባካሄድንበት ማግስት የሚካሄድ በመሆኑ ፓርቲያችን ባሁኑ […]

Eyasped Tesfaye
ይህን ሁለት ቀን በማህበራዊ ድህረ-ገፆች ላይ በትብብሩ እና በፓርቲዬ ላይ እየተናፈሰ ያለውን አቧራ ማጥራት ግዴታ ስለሆነብኝ የሚከተለውን ፅፊያለሁ፡፡ ልቦና ያለው ልብ ይበል፡፡
ሰማያዊ እና ትብብሩ የምርጫ ምልክት ወስደዋል እንዲሁም ደግሞ የትብብሩ ዋና ፀሀፊ ያለምንም ቅድመ ሁናቴ በምርጫው እንደሚሳተፉ በፌስቡክ ገፃቸው መግለጫ ሰጥተዋል በሚል ከተለያዩ አቅጣጫዋች የተለያዩ ድንጋዮች እየተወረወሩ ነው፡፡ የዚህ ነገር መነሾ ለእኔ ሁለት ምክንያት ያለው ይመስለኛል፡፡
1ኛ፡- ከጥቂት ሳምንታት በፊት አንድነት ፓርቲ ያለምንም ቅድመ ሁናቴ በምርጫው እሳተፋለሁ ማለቱን ተንተርሶ በሶሻል ሚዲያው ላይ አንድነት ፓርቲን የሚያጥላሉ ፅሁፎች በርክተው ነበር፡፡ አሁን እንደገባኝ ከሆነ ወንድሜ አስራት አብርሀምን ጨምሮ የተወሰኑ ሰዎች አንድነት ላይ ዘመቻውን የከፈቱት ሰማያዊዎች ናቸው የሚል ግንዛቤ ወስደው የነበረ ሲሆን የአሁኑ ፅሁፋቸው የመልስ ምት እንደሚሉት አይነት መሆኑ ነው፡፡ በወቅቱ ግን ወዳጄ ዮናታን ተስፋዬ(የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ) በፌስቡክ ገፁ ላይ ከዚህ በታች በፎቶ ያያዝኩትን ፅሁፍ ፅፎ ነበር፡፡ ሰሚ አላገኘም እንጂ፡፡
2ኛ፡- የሰሞኑን አቧራ ያስነሱት ሰዎች ምርጫውን ያለምንም ቅድመሁናቴ እንሳተፋለን ብሎ መግለጫ በመስጠት እና ‹ነፃነት ለፍትሀዊ ምርጫ› ብሎ ምርጫው ፍትሀዊ እንዲሆን በመታገል መካከል ያለውን ልዩነት በቅጡ ያልተገነዘቡ ናቸው፡፡
ማብራሪያ፡-
ሰማያዊ ፓርቲና ሌሎች ስምንት ፓርቲዎች በጋራ በመሆን ነፃነት ለፍትሀዊ ምርጫ የሚል እንቅስቃሴ እያደረጉ እናዳለ ሁሉም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ የዚህን እንቅስቃሴ ስያሜ እንኳን በቅጡ ብናየው ሁለት ነገሮችን እንገነዘባለን፡፡ የመጀመሪያው ነገር ነፃነት ሳይኖር ምርጫ ሊኖር አይችልም ስለዚህም ነፃነት የምርጫ ቅድመሁናቴ ነው የሚል ሀሳብ የያዘ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በነፃነት የሚደረግ ምርጫ እንዲኖር ትግል እንደሚደረግ አመላካች ነው፡፡
ከፊታችን የሚደረገው የ2007ቱ ምርጫ ነፃና ፍትሀዊ እንዲሆን ታግዬ ነፃ ሲሆን እሳተፋለሁ ማለት እና ያለምንም ቅድመ ሁናቴ በምርጫ እሳተፋለሁ ብሎ መግለጫ መስጠት ልዩነቱ እዚህ ላይ ነው፡፡ ለነገሩ የዛሬው ጫጫታ ከጀርባው ሌላ ተንኮል እንዳለው አንዱ ማሳያ የትብብሩ ፀሀፊ የሆኑት አቶ ግርማ ከዛሬ 10 ቀን በፊት ከግርማ ካሳ ጋር በኮመንት ሲከራከሩ ኮመንት ያደረጉትን ነገር አዲስ መግለጫ እንደሰጡ በማስመሰል ‹‹ሰማያዊ ያለምንም ቅድመ ሁናቴ በምርጫው እንደሚሳተፍ ገለፀ›› ብሎ ዜና መስራቱ በራሱ የጤነኝነት አይመስልም፡፡ ምናልባትም ሰማያዊም ሆነ ትብብሩ ነፃነት ከሌለ ምርጫ የለም በሚል በያዙት ጠንኳራ አቋም ምክንያት ያገኙትን ሰፊ የህዝብ ድጋፍ ለማሳጣት የታለመም ይመስላል፡፡
ሰማያዊ የምርጫ ምልክት ወሰደ ማለትስ በምርጫው ውስጥ ያለምንም ቅድመሁናቴ በምርጫው እሳተፋለሁ ብሎ መግለጫ ሰጠ ወይም ወሰነ ማለት የሚሆነው እንዴት ነው??? ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫ 2007ትን ከወዲሁ ቦይኮት ማድረጉን ቢገልፅ እና ከሂደቱም ራሱን ቢያገል፤ በአንፃሩም ሰማያዊ እና ትብብሩ ነፃነት ለፍትሀዊ ምርጫ በሚል እያደረጉ ያሉት እንቅስቃሴ ውጤት ቢያመጣና ምርጫው ነፃ ቢሆን ማን በጠረገው መንገድ ማን ሊሄድ ነው??? ይህ የነፃነት ለፍትሀዊ ምርጫ የሚለው ትግል እኮ ቢያፈራ ፍሬውን ለመሰብሰብ በሂደቱ ውስጥ መቆየት ግድ ነው፡፡
አንድነት ያለምንም ቅድመሁናቴ በምርጫው እሳተፋለሁ ብሎ መግለጫ መስጠቱን አልቃወምም፡፡ አባላቶቼን ከወዲሁ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ይረዳኛል ብሎ ይሆናልና፡፡ ልክ እንደዚሁም ሁሉ ሌላውም የእኛን አቋም እንዲያከብርልን እሻለሁ፡፡ ሰማያዊ እና ትብብሩ ምርጫ የሚኖረው ነፃነት ሲኖር ነውና ነፃነት ለፍትሀዊ ምርጫ ብለው እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው፡፡ ከዚህ ውጪ አዲስ ነገር የለም! አይኖርምም!!!

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለ በማህበራዊ ድረ ገጽ በሰጡት አስተያየት ትብብሩ ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ ምርጫ እንደሚገባ በማህበራዊና በሌሎች ሚዲያዎች ተላልፏል፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አቶ ግርማ እንደሚከተለው መልስ ሰጥተውበታል፡፡
አንድ የሌላ ፓርቲ ደጋፊ ማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ ምርጫው ውስጥ ስለመግባትና አለመግባት ላይ ባነሳው ክርክር የግል አስተያየቴን ሰጥቼ ነበር፡፡ ይህ የግል አስተያየትም ትብብሩም ሆነ አባል ፓርቲዎች በምርጫው ሂደት ላይ ምንም አይነት ጥያቄ ሳያነሱ ወደ ምርጫው እንደሚገቡ ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያዎች ተሰራጭቷል፡፡
አንድ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ተመዝግቦ በሰላማዊ መንገድ እንቀሳቀሳለሁ ሲል የምርጫ ፓርቲ ነው ማለት ነው፡፡ በመሆኑም የምርጫ ፓርቲ ሆኖ እንደ ስልት በምርጫ ላይ ቅድመ ሁኔታ ሊያቀርብ አይችልም፡፡ ቅድመ ሁኔታ ሊያቀርብ የሚችለው በምርጫው ሂደት ላይ ነው፡፡ በሌላ በኩል አንድ በሰላማዊ መንገድ እንቀሳቀሳለሁ የሚል ፓርቲ ስልጣን ሊይዝ የሚችለው በምርጫ ነውና ምርጫ እገባለሁ ብሎ ሊያውጅ አይችልም፡፡ የምርጫው ሂደት ላይ ጥያቄ ሲያነሳ ደግሞ ከምርጫው ራሱን አገለለ ማለት አይደለም፡፡ እኛ በምርጫው ሂደት ላይ ጥያቄ በማንሳታችን ከአሁኑ ራሳችን ከምርጫ ያገለልን የሚመስላቸው አካላት አሉ፡፡ ግን እኛ ራሳችን አላገለልንም፡፡ ከአሁኑ ምርጫ እንሳተፋለን ብሎ ማወጅም አላስፈለገንም፡፡ ከዚህ ይልቅ ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል ምርጫው ፍትሓዊ እንዲሆን እየታገልን ነው፡፡
ስለሆነም ምርጫው ሂደት ላይ ጥያቄዎችን አንስተን ምርጫው ፍትሓዊ እንዲሆን እየታገልን ነው፡፡ ስለሆነም በምርጫው ሂደት ላይ አለን ማለት ነው፡፡ ነገር ግን በሂደቱ ላይ አለን ማለት ጥያቄዎቹ ሳይመለሱ ምርጫውን እንሳተፋለን ማለት አይደለም፡፡ በምርጫው ሂደት ሲሳተፍ ቆይቶ ሂደቶቹ ፍትሓዊ ባለመሆናቸው፣ የተነሱት ጥያቄዎች ባለመመለሳቸውና በሂደቱ ላይ የተቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው ምርጫው አንድ ቀን ሲቀረው ራሱን ከምርጫው ያገለለ ፓርቲ አውቃለሁ፡፡
ከአሁኑ ምርጫው ላይ ጥያቄ በማንሳታችን ከምርጫው ራሳችን አግልለናል ማለት አይደለም፡፡ እኛም ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጥነው ምርጫ ላይ ሳይሆን የምርጫ ሂደቱ ላይ ነው፡፡ ሂደቱ ፍትሓዊ ካልሆነ አጃቢ መሆን አንፈልግም፡፡ ለዛም ነው ሂደቱን ለማስተካከል ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል እየታገልን ያለነው፡፡ በትግላችን መሰረት ሂደቱን እናስተካክለዋለን ብለን እናስባለን፡፡
ፓርቲያችን አንድነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሠላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ በሠላማዊ ትግል ትንቅንቅ ውስጥ ካሉ ፓርቲዎች ግንባር ቀደሙ ነው!
በትግሉ ውስጥ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ልዕልና እየተጋ ያለው ፓርቲያችን በየጊዜው በሚገጥሙት መሠናክሎች ከመዳከም ይልቅ እየጠነከረ፤ ውስጣዊ ዴሞክራሲው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያጎለበተ የመጣ እንዲሁም የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥያቄ በአስተማማኝ መንገድ ለመመለስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ቁርጠኛ አባላትን ያፈራ በመሆኑ ኩራታችን ከፍ ያለ ነው፡፡
አንድነት በ2ዐዐ7 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ አሸናፊ ኃይል ሆኖ ለመውጣት መሠረተ ሠፊ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ ሠፊ እንቅስቃሴያችን ምክንያትም ገዢው ፓርቲ በአባላትና አመራሮቻችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የእስር፣ የማሳደድና የማጥፋት ሥራ እየሰራ ቢሆንም ፓርቲያችን ይህንን ሁሉ ጫና በመቋቋም አሁንም በሠላማዊ ትግል የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት ለማድረግ በቁርጠኝነት ቆሟል፡፡
ለዚህ ቁርጠኝነታችንና ፓርቲያችን ስላለው መሠረተ ሠፊ አደረጃጀት ከዚህ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ በላይ ምስክር የለም፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ጉባኤ ለማድረግ ችለናል፡፡ ይሄ ፓርቲያችን የደረሰበትን እድገት የሚጠቁም ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ፓርቲዎችም አርአያ ለመሆን የሚበቃ ነው፡፡
እኛ የእዚህ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አባላትም በዛሬው እለት ባደረግነው አስቸኳይ ስብሰባም የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፈናል፡፡
1. የፓርቲው ብ/ም/ቤት የቀድሞው የፓርቲው ፕሬዚደንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ተከትሎ ብ/ም/ቤቱ ባለው የጠቅላላ ጉባኤ ውክልና መሠረት ያካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ተገቢና ሕገ-ደንባዊ መሆኑን አረጋግጦ አቶ በላይ ፍቃዱን እስከሚቀጥለው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ የፓርቲው ፕሬዚደንት እንዲሆኑ በከፍተኛ ድምጽ ወስነናል፡፡
2. በመተዳደሪያ ደንቡ ውስጥ ከብ/ም/ቦርድ የሚፈለጉ ማብራሪያዎችን እና ሃሳቦች ተከትሎ ጠቅላላ ጉባኤው የተወሰኑ ማሻሽያዎች አድርጓል፡፡
3. መድረክን በተመለተ በፓርቲያችን ላይ የጣለውን ሁለተኛ እገዳ ተከትሎ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ በወሰነው መሠረት ብ/ም/ቤቱ ከመድረክ እንዲወጣ የወሰነውን ውሳኔ ተገቢ ሆኖ ስላገኘው በከፍተኛ ድጋፍ አፀድቋል፡፡
4. ገዢው ፓርቲ ህገ መንግሥቱን በመጣስ በእየእስር ቤቱ ያጎራቸውን የዴሞክራሲ አርበኞች በአስቸኳይ እንዲፈታ ጉባኤው አጥብቆ ይጠይቃል፡፡
5. የዜጎችን በነፃ የመደራጀት ነፃ አመለካከታቸውን በአምባገነንነት በማፈን ያሰራቸውን የነፃነት አርበኞች ፖለቲከኞች ፣ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮች፣ የቤተ እምነት መሪዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እየጠየቅን መንግሥት በሩን ለብሔራዊ ውይይት ክፍት እንዲያደርግ ጉባኤው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
6. የተቀማነውን ነፃነታችንን በድምፃችን ለማስከበር ‹2ዐዐ7 ለለውጥ› የሚል የህዝባዊ ንቅናቄ ዘመቻ አንድነት በዛሬው እለት ጠቅላላ ጉባኤው አውጇል፡፡ ስለዚህ መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ በምርጫ ካርዱ ነፃነቱን እንዲያስከብር አንድነት ፓርቲ ጥሪውን ለመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ነፃነታችንን እናስከብር!
የአንድነት አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሣሥ 3/2ዐዐ7 ዓ.ም
አዲስ አበባ
* ምርጫው ላይ ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠናል
* በምርጫው ልንሳተፍም ሆነ ላንሳተፍ ውሳኔ የምናሳልፈው እኛ ሳንሆን ሂደቱ ነው
ትንሽ ስለ አንዳንድ ጉዳዮች ማብራሪያ አቀርባለሁ ዮናታን ተስፋዬ ረጋሣ
ኢትዮጵያ ውስጥ በህጋዊ መንገድ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ ፓርቲ ምርጫ ስላለመግባቱ እንጂ ምርጫ ስለመግባቱ ዜና ሲሆን በጣም ግራ ያጋባል፡፡ ምርጫን መሳተፍ አንዱ የትግል አካል የሆነውን ያህል አለመሳተፍ የራሱ የሆነ ፋይዳ አለው፡፡ ያን የሚወስነው ግን ሂደቱ እንጂ ፓርቲዎቹም ይሁኑ ምርጫ ቦርዱ አይደለም፡፡ ከዚህ አንፃር በሂደቱ ውስጥ አንድ ፓርቲ ወይም ፓርቲዎች አንሳተፍም ሊሉ ይችላሉ (ህጋዊነትም አለው)፡፡ ምክንያታቸውንም በዝርዝር አስቀምጠው መግለጫም ይሁን ሌላ ሌላ ነገር ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ያም ዜና ከመሆን ባለፈ ባጠቃላይ የህዝቡንም የዓለም አቀፍ ማሕበረሰቡንም ትኩረት ያገኛል፡፡
ከዚህ ውጪ ግን አንዱ ያለ ቅድመ ሁኔታ ምርጫ እሳተፋለሁ ስላለ እና ሌላው ደግሞ ሂደቱ እንዲወስን እድል ስለሰጠ ምርጫ ተሳታፊና ምርጫውን የማይሳተፍ ብሎ ማቅረቡ በራሱ አንድም ስህተት ነው ሲልም ከንቱ ራስ ማዋደጃ ፕሮፖጋንዳ ነው፡፡ ይህ ግልፅ ነገር እንዲገባው ያልፈለገ እና ህመም የሆነበት ማስታገሻ ወስዶ ቢያርፍ መልካም ነው፡፡
ጓደኞቼም ሆነ እኔ ኢሳትና ቪኦኤን ጨምሮ በብዙ መገናኛ ብዙኃን እና በዲፕሎማቶች በኩል በተደጋጋሚ በምርጫው ጉዳይ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ የያዘውን አቋም በተጠየቅንበት ወቅት የሰጠነው የማያሻማ መልስ ከላይ ያሰፈርኩትን ነው (ሚዲያዎቹ ላይ ፈልጎ መስማት ይቻላል)፡፡ ‹‹ምርጫ ለመሳተፍም ሆነ ላለመሳተፍ አሁን የመወሰኛ ጊዜ አይደለም፤ ሂደቱ እንጂ እኛ(ተቃዋሚም ይሁን ኢህአዴግ) አሁን ልንወስነው የሚገባ ጉዳይ አይደለም፡፡›› ይህ በግልፅ የሚያሳየው ነገር ሂደቱ ውስጥ ተሳታፊ እንደምንሆን ሲሆን ለመጨረሻው ውሳኔ ግን በወቅቱ የሚፈጠረው ሁናቴ እንደሚወስን ነው!
እንደ አንድ ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምርጫ ጉዳይ ኮሚቴና ጊዜውን መሰረት ባደረገ 70 ሰው ያቀፈ የምርጫ ግብረሃይል አቋቁመን፣ የዓመቱ እቅዳችንም በምርጫ ላይ ሆኖና በትብብሩም የጀመርነው ዘመቻ ‹‹ነፃነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› እያለ ለምርጫ የማንዘጋጅ አስመስሎ ማቅረቡ ምንአልባት ከተሳሳተ ግንዛቤ አልያም ከተንኮል ያለፈ ሊሆን እንደማይችል ግልፅ ነው፡፡ የምርጫ ምልክትን መውሰድም የሂደቱ አካል እንጂ የመጨረሻው ውሳኔ አይደለም፡፡ ከዚህ ተነስቶም በእርግጠኛነት ምርጫ ይሳተፋሉ ብሎ መደምደም ተገቢ ነው ብዬ አላምንም! ባጠቃላይ ግን ለምርጫው ያስቀመጥናቸውን ቅድመ ሁኔዎች በሂደቱ የማይመለሱ ከሆነ ያኔ ውሳኔው ከነምክንያቱ ይፋ ይሆናል ማለት ነው፡፡
በግልፅ ቋንቋ ምርጫውን ለመሳተፋችንም ሆነ ላለመሳተፋችን አጠቃላይ ሂደቱ፣ በሂደቱ ውስጥም ያነሳናቸው ጥያቄዎችና ያስቀመጥናቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንጂ ማናችንም ወሳኝ ልንሆን አንችልም! የምርጫ ምልክትም ስንወስድ መነሻችን ይኸው እውነታ እና ነባራዊ ሁኔታ ብቻ ነው! ይህ የኛ መንገድ ሲሆን ሌሎች ደግሞ ያለ ቅድመ ሁኔታ ባለው የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ምርጫ እሳተፋለሁ ብለው ይንቀሳቀሳሉ፡፡ ምንም ይሁን ምንም፣ ሂደቱ ይመርም አይመርም ምርጫውን ለመሳተፍ ወስነው ወደ ስራ የገቡትን ውሳኔያቸውን አከብራለሁ፡፡
የመረጥነውን መንገድ መደገፍም መንቀፍም ያባት ነው፤ እየጠመዘዙ ሌላ መልክ እንዲይዝ ማድረግ ግን ራስን ከማስገመት ያለፈ ጥቅም ያለው መስሎ አይሰማኝም፡፡
(ይህ ርዕስ ከዚህ በላይ መወያያ ባይሆን ምኞቴ ነው!)
ሊንኩን በመጫን ለምርጫ ቦርድ የስገባውን ደብዳቤ እና ያስቀመጥናቸውን ቅድመ ሁኔታዎች ይመልከቱ፡-
https://www.facebook.com/semayawiethio/ … =3&theater
የግንቦት ሰባት ከፍተኛ ኣመራሮች ኣስመራ ገቡ ሲሉ የድርጅቱ ካድሬዎች ተናግረዋል
በዚህ ሰሞን የሚወጡ ዘገባዎች አንደሚያመለክቱት የተከበሩ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ አና የግንቦት ሰባት ሚዲያ ኢሳት ሃላፊ አና የግንቦት ሰባት ምክትል የሆነው ኣቶ ነእመን ዘለቀ ያሉበት ቡድን ኣስመራ ገብተዋል ሲሉ የድርጅቱ ካድሬዎች ውስጥ ውስጡን የሚያናፍሱት መረጃ ጠቁፙል፥፥
ዶክተር ብርሃኑ ኣስመራ በተደጋጋሚ በኢሳያስ ኣወርቂ ተጠርቶ አንዳልሄደ የሚናገሩት ኣስተያየት ሰጪዎች በሃሰት አና በተስፋ ህዝቡን ለመደለል የሚደረግ ፕሮፓጋንዳ ነው፥፥ተደብቆ መህዐድ ምን ኣስፈለገ ከሄዱ በህWላስ ለምን ይፋ ኣይደረግን ማበረታቻ ይሆናል ሲሉ ተደምጠዋል፥፥አንዲህ ኣይነት የውስጥ ሹክሹክታ ድርጅቱን ለፖለቲካ ኪሳራ አንዳይዳርገው ሲፈራ ከኣሁን ቀደም በኣንዳርጋቸው የመጣውን የፖለቲካ ቁስል ሳያክም ወሬ ማናፈስ አንደማያዋጣ ኣስተያየት ሰጪዎች ኣስረግጠው ተናግረዋል፥፥
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በኦሞ ስምጥ ሸለቆ ለሽርሽር የሄዱት በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች 12 ስዊድናውያን የተኩስ እሩምታ ወረደባቸው
ኢሳት ራድዮ ታህሳስ 6/2007 ዓም እንደዘገበው በግድያ ሙከራው ላይ የስዊድን የመገናኛ ብዙሃን በብዛት እየዘገቡበት መሆኑን ያብራራል።እንደ ዘገባው በኦሞ ስምጥ ሸለቆ ለሽርሽር የሄዱት በኢትዮጵያ የስዊድን አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች 12 ስዊድናውያን የነበሩ መሆኑን እና የተኩስ እሩምታ እንደወረደባቸው ይገልፃል።አቶ ሞላ ይግዛው በስዊድን የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፎረም ምክትል ሊቀመንበር በጉዳዩ ላይ በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል –
”አስራ ሁለት የስዊድን ዜጎች አምባሳደሩን ጨምሮ ይላልእዛ ላይ አራት ሰዎች የጫነው መኪና ላይ ስዊድናውያንን ለመግደል ያለመ እና ያነጣጠረ ተኩስ ነው የተከፈተው።ከእዚህ ጋር በጥያየዘ ባለፈው ጊዜ H&M የተሰኘው ድርጅትን ያጋለጠ አንድ ጋዜጠኛ በእዛ አካባቢ ወይም ደቡብ ኢትዮያ የሚደረገውን ግፍ ለዓለም ማጋለጡ እና በዓለም የሌለ ዲክታተር መባሉ ይታወቃል።ከእዛ በፊት አንድ ቀን የስዊድን የጦር ፍርድቤት ያቀረብነውን የወንጀል ክስ ተቀብሎ ክስ እንደሚመሰርት አስታውቆ ነበር።በመሆኑም ይህንን ያደረገው ወያኔ ነው ሌላ ሊሆን አይችልም” ብለዋል።
ኢሳት ራድዮ በመጨረሻ ላይ እንደገለፀው ጉዳዩን የስዊድን ጋዜጦች፣ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ሌሎች የመገናኝ ብዙሃን ሽፋን ቢሰጡትም ኢህአዲግ ም ሆነ የሚቆጣጠራቸው ራድዮ እና መገናኛ ብዙሃን እስካሁን ምንም ያሉት ነገር እንደሌለ ይገልፃል።

በቅርቡ የአንድ ወር መርሃ ግብር አዉጥቶ ሲንቀሳቀስ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲና የዘጠኝ ድርጅቶች ስብስብ፣ ፓርቲዎች ትብብር፣ ያለ ቅድሜ ሁኔታ በመጪው የ2007 ምርጫ እንደሚሳተፍ አሳወቀ። ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን የምገልጹ አንዳንድ ዘገባዎች በተለይም በዳያስፖራ አካባቢ የሚሰሙ እንደሆነ ቢታወቅም፣ የትብብሩ ዋና ጸሃፊ አቶ ግርማ በቀለ በፌስ ቡክ በግልጽ በሰጡት አስተያየት፣ ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ አለማስቀመጡን ገልጸዋል።
“NO Precondition is set by members of Tibibir. We decided to be part of the election and advised all members to take their election Sign. Believe me, it is all the decision of Tibibir that is under action by its members and Blue is not an exception to present and decisions are being made in participatory process.” ሲሉ የትብብሩ አባል ድርጅቶች ለምርጫ የሚያስፈልገውን የምርጫ ምልክት በአስቸኳይ ለመዉሰድ መስማማታቸውንም አቶ ግርማ በቀለ ገልጸዋል።
በዚሁም መሰረት፣ የሰማያዊ ፓርቲንም ጨምሮ ሌሎች የትብብሩ አባል ድርጅቶች የምርጫ ምልክት ከሌሎች ድርጅቶች ቀድመው እንደወሰዱም የሚገልጹ መረጃዎች እየደረሱን ነው። ምርጫ ቦርድ ከአንድ ሳምንት በኋላ የድርጅቶቹን ምልክት ይፋ የሚያደርግ ሲሆን፣ የሰማያዊን ጨመሮ የሌሎች ድርጅቶች የምርጫ ምልክትም ምን እንደሆነ ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው የፖለቲካ ተንታኝ የትብብሩን ዉሳኔ አስፈላጊና ጠቃሚ ዉሳኔ ሲሉት፣ ሰማያዊ/ትብብሩ ወደ ምርጫ ያለ አንዳች ቅድሜ ሁኔታ ለመሳተፍ በመወሰኑም፣ በምርጫው ረገድ ከአንድነት ፓርቲ ተመሳሳይ አቋም እንደያዘ በግልጽ ያመላከት እንደሆነም አስረድተዋል።
“ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ ምርጫ ለመግባት ሰማያዊ/ትብብር ከወሰኑ፣ ለምርጫው መዘጋጀት አለባቸው። ድርጅታዊ ሥራ ላይ ማተኮሩ የድግ ነው። ተመሳሳይ ፕሮግራም ካላቸው ከነ አንድነት ጋር በምርጫው ረገድ መተባበር ያስፈልጋቸዋል” ሲሉ እኙ ተንታኝ ትብብሩ ወደ ምርጫ ከገባ ዘንዳ የምርጫ ዘመቻውን አብሮ ከሌሎች ጋር ለማቀናጀት እንዲዘጋጅም ጠይቀዋል።
በተያይዘ ዜና የአንድነት ፓርቲ የምርጫ ታዛቢዎች በማስመረጥ ዙሪያ በተቻለ መጠን ገለልተኛ የሆኑ የሕዝብ ታዛቢዎች እንዲመረጡ ለማድረግ በየዞኖቹና በየወረዳዎች ስምሪት እንደጀመረም ለማወቅ ችለናል።
አቡጊዳ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ሲጠቀሱ በቅድሚያ የሚታወሱት በላስታ አውራጃ፣ በ“ሮሃ” (ላሊበላ) ከተማ አጠገብ ከአንድ-ወጥ ድንጋይ ተፈልፍለው የተሰሩት አስራ አንድ ቤተ ክርስቲያናት ናቸው፡፡ የአስራ አንዱ ቤተ ክርስቲያናት ስም እንደሚከተለው ነው፡፡በቅርቡ የአንድ ወር መርሃ ግብር አዉጥቶ ሲንቀሳቀስ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲና የዘጠኝ ድርጅቶች ስብስብ፣ ትብብር፣ ያለ ቅድሜ ሁኔታ በመጪው የ2007 ምርጫ እንደሚሳተፍ አሳወቀ። ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን የምገልጹ አንዳንድ ዘገባዎች በተለይም በዳያስፖራ አካባቢ የሚሰሙ እንደሆነ ቢታወቅም፣ የትብብሩ ዋና ጸሃፊ አቶ ግርማ በቀለ በፌስ ቡክ በግልጽ በሰጡት አስተያየት፣ ትብብሩ ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ አለማስቀመጡን ገልጸዋል። “NO Precondition […]
ኢቦላን ለመዋጋት ወደ ምዕራብ አፍሪካ ይጓዛሉ ለተባሉት ከ200 በላይ ሐኪሞችና ሌሎችም ባለሙያዎች አሁን በአዲስ አበባ ሂልተን አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል፡፡
የኢትዮጵያን የኢቦላ ምላሽ የሚያስተባብረ ው የማኅበረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አቤል የሻነህ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ ሽኝቱ የተዘጋጀው ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዘማቾች ነው፡፡
ኢትዮጵያዊያኑ ባለሙያዎች ወደ ምዕራብ አፍሪካ የሚጓዙት የአፍሪካ ኅብረት ፀረ-ኢቦላ ምላሽ አካል ሆነው እንደሚሆን ተገልጿል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ እስከአሁን የኢቦላ ተጠርጣሪም ሆነ የወረርሽኙ ምልክት ኢትዮጵያ ውስጥ አለመታየቱ በአይሮፕላን ጣቢያዎች ላይ እየተካሄደ ያለው ፍተሻና ክትትልም እንደቀጠለ መሆኑን ዳይሬክተሩ አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
ዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት – አይሲሲ አቃቤ ሕግ ዳርፉር ውስጥ የሚያካሄዱትን ምርመራ ለጊዜውም ቢሆን እንደሚያቋርጡ ከገለፁ በኋላ የሃገሪቱ “ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አልበሽር ንፁህ ሰው ስለመሆናቸው ማረገገጫ ነው” ሲሉ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አሕመድ ቢላል አስታውቀዋል፡፡
የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አልበሽርን “የሰላም ሰው” ብለዋቸዋል ዛሬ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ፡፡
ዳርፉር ላይ ሲያካሂዱ የቆዩትን ምርመራ እንደሚያቆሙ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ፋቱ ቤንሱዳ ያሳወቁት “ለጊዜውም ቢሆን” በሚል ቢሆንም የማስታወቂያ ሚኒስትሩ ግን ይህ የቤንሱዳ ውሣኔ ከኦማር ሁሴን አል በሽር የሚገኝ “አንዳች ጥፋት ላለመኖሩ ማረጋገጫ ነው” ሲሉ የድል ብሥራት ከማውጣት አልቦዘኑም፡፡
አቃቤ ሕጓ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ባለፈው ሣምንት ሲናገሩ…
Ethiopia – Ebola – medics – farewell
Sudan – Vindication – ICC
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራስያዊ አንድነት መድረክ ትላንት በአዲስ አባባ ባካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በመጪው ግንቦት የሚካሄደው ምርጫ ነጻና ፍትሀዊ እንዲሆን ጠየቀ።
የታሰሩ የፖለቲካ መሪዎች፣ ጋዜጣኞችና የሙስሊሙ ህብረተሰብ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱም ጥሪ አቅርቧል። የዘገባውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤
(ቢልልኝ ሀብታሙ አባቡ) የተቃዋሚዉ ጎራን በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለት አብይት ፖለቲካዊ ክስተቶችን አስተናግዷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ትግል ሲኮላሽ የመድረክ ደግሞ ቀዝቀዝ ያለ በሚመስል መልኩ ተስተናግዷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ ፕሮግራም በተስተጓጎለ በሳምንቱ የመድርኮቹ መሳካቱ ምን ሊያመላክት ይችላል የሚለውን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የመድርኩን ሰልፍ ከራሱ ከመድርክ፣ ከመንግስትና ከህዝብ አንፃር ሊኖረው የሚችለውን እንድምታ አጠር ባለ መልኩ ለማየት እንሞክራለን፡፡ ሀ) ከመድረክ አንፃር መድርክ ከሌሎችና ፓርቲዎችና ከራሱም ያለፈ የትግል ልምድ የተማረው ነገር ያለ ይመስላል፡፡ ፓርቲው ቀድሞ ከነበረበት ጽንፍ ይዞ የመታገል አቅጣጫ በተወሰነ መልኩ ለዘብ እያለ መምጣት የሚያሳዩ ሁሄታዎችን መታዘብ ይቻላል፡፡ መድረክ ከሌጋሲው የተማረው ጉዳይ ቀድም ሲል በነበው ፅንፍ ይዞ የመታገል አቅጣጫ የመንግስትን የቁጥጥር ጫና እንዲሚያጠብቀው ሳይማር እንዳልቀረ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ባልተለመደ መልኩ ሌሎች ተቃዋሚዎች ክፉኛ የሚጥሉትንና መንግስት እየተጠቀመበት ያለውን ባንዲራ በሰልፍ ውስጥ መጠቀሙ በተወሰነ መልኩ ከአክራሪነት ለዘብ ያለ አቋም እያሳየ ለመምጣቱ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡ ፓርቲው ወዶም ይሁን ተገዶ በወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ከኢህአዴግ ጋር መመሳሰል ባይችል እንኳን መንግስት ከሚፈልገው የአቋም መለሳለስ ደረጃ ላይ ሊደርስ እንደሚችል የሚጠቁሙ ፍንጮች እንዳሉ መውሰድ ይቻለላል፡፡ በሌላ መልኩ መድረክ የሰላማዊ ሰልፉን ዉጤት ተከትሎ መንግስት የሚሰጋባቸውን ችግሮች እንዳይከሰቱ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ለማድርግ ከመንግስት ጋር ስምምንት ላይ ሳይደርስ እንዳልቀረ የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ፡፡ በአቋም እየተለሳለሰ መምጣቱና ለሰልፉ ኃላፊነቱን ከመንግሰት ጋር መጋራቱ ሰልፉን ስኬታማ ለማድረግ ሳይግዘው እንዳልቀረ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በ2002 ምርጫ ከኢህአዴግ ጋር […]