የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክር ቤቱ ህዳር 30/ 2007 ዓም ባወጣው መግለጫ “በሀገራችን ህዝባዊ ሥርዓት ለማምጣትና በህግ የበላይነት የሚያምን መንግስት ለመመስረት በምናደርገው ትግል ሁሉ የሚጠበቅብንን መስዋእትነት ለመክፈልና ሀገራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ዝግጁ” ነን ብሎአል። “ሰማያዊ ፓርቲን ጨምሮ ዘጠኝ ትብብር የፈጠሩ ፓርቲዎች በህዳር ወር ያወጡት መርሐ ግብር አንድ አካል የሆነውን የ24 ሰዓት የተቃውሞ የአደባባይ …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንዳንድ ተጓዞች ለኢሳት እንደገለጹት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታየው ፍተሻ ጨምሯል። ከዲላ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ ተሳፋሪ ለኢሳት እንደገለጸው ፖሊሶቹ ተሳፋሪውን ወዴት ነው የምትሄዱት? ለምንድነው የምትሄዱት በማለት ከመጠየቅ ጀምሮ የሰዎች ኪሶች በመግባት ፍተሻ ያደርጋሉ። በሽተኞችንና ህጻናትን የታቀፉ እናቶች ሳይቀሩ ፍተሻ በሚል ፖሊስ ጣቢያ ታጉረው መዋላቸውን …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ወደ የመን ሲጓዝ የነበረ ጀልባ ሰጥሞ ከ79 ያላነሱ ኢትዮጵያዊያን ያለቁ ሲሆን እስካሁን ከ14 ያልበለጡ ሰዎች ብቻ አስከሬን መገኘቱን ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት ገልጿል። የሟቾች ቁጥር አስቀድሞ በመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ሳይሆን 79 መሆኑን ግሩም አክሎ ተናግሯል። በሌላ በኩል ደግሞ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕጋዊ ጉዞን ከአንድ ዓመት በላይ አግዶ …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት  አስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት በካውች ማሞና ኦብዱል ኦቻር የሚባሉትን ባለስልጣኖች አውርዷቸዋል። ግለሰቦቹ ያለመከሰስ መብታችን የተነሳው በህገወጥ መንገድ ነው በማለት ወደ አዲስ አበባ ተጉዘው የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትን ለማግኘት ሙከራ ቢያደርጉም፣ ደህንነቶች ይዘው አስረዋቸዋል። ባለስልጣኖቹ ከውጭ ሃይሎች ጋር ትገናኛላችሁ በሚል መከሰሳቸውን የአኝዋ ሰርቫይቫል ዋና ሃላፊ አቶ ኒካው …

ታኀሳስ ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋቢያችን በአራት ኪሎ፣ በቦሌ፣ በካዛንቺስ፣ በልደታ አካባቢዎች የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ተዘዋውሮ እንደተመለከተው በብዙዎቹ ማደያዎች በዛሬው እለት ነዳጅ ቢኖርም ነዳጅ ለመቅዳት የተሰለፉ ተሸከርካሪዎች በመብዛታቸው ረጃጅም ሰልፎች መታጣቸውንና የትራፊክ መጨናነቅ መከሰቱን መታዘብ ችሎአል፡፡ በዓለም ገበያ ላይ የነዳጅ ዋጋ መቀነስን ተከትሎ ከትላንትና ህዳር 30 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ ንግድ ሚኒስቴር መጠነኛ …

ዛሬ የኖቤል መሥራች አልፍረድ ኖቤል የሞተበት ዕለት መታሰቢያ ሲሆን የሚታሰበውም ለዓለም ሰላም ጉልሕ አስተዋጽዎ ለሚያደርግ ለሚያደርጉ የኖቤል የሰላም ሽልማት በመሰጠት ነው። የሚሰጠውም በኖርዌይ መዲና በኦስሎ ሲሆን ፤በተለያዩ የሳይንስ ዘርፎች ፤ ውጤታማ ለሆኑ ድግሞ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ነው ሽልማቱ የሚሰጠው።


(አፈንዲ ሙተቂ)
——
በኢትዮጵያ የታሪክ ሂደት የተፈጠሩ የፖለቲካ ድርጅቶችና ሽምቅ ተዋጊ ቡድኖች በትግል ዘመናቸው ከወደቁ ሰማዕቶቻቸው ሁሉ አግዝፈው የሚመለከቱት አንዳንድ ጀግና አላቸው፡፡ ለምሳሌ የተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ ( ጀብሃ) ትልቁ ሰማዕት “ዑመር እዛዝ” ይባላል፡፡ የህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ሻዕቢያ) ታላቅ ሰማዕት ደግሞ “ኢብራሂም አፋ” ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) ትልቁ ሰማዕት “ተስፋዬ ደበሳይ” ነው፡፡ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) “ታላቁ ሰማዕት” ኤሌሞ ቂልጡ ይባላል፡፡ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት በበኩላቸው እንደ ትልቁ ሰማዕት የሚያዩት ሃየሎም አርኣያን ነው፡፡
Hayelom Ar’aya
  ታዲያ ሃየሎም ከሌሎቹ ሰማዕታት የሚለይበት አንድ ጠባይ አለ፡፡ ይህም በጀግንነቱ በህወሓት ብቻ ሳይሆን የህወሓት ቀንደኛ ጠላት በሚባሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ጭምር የሚወደስ መሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ስለሃየሎም ጀግንነት በስፋት መጻፍ የጀመረው እርሱ ከተገደለ በኋላ ነው፡፡ ሆኖም ሃየሎም በህይወት እያለ እንኳ ስለጀግንነቱ ሲሰጡ የነበሩ የምስክርነት ቃሎችን በልዩ ልዩ የፕሬስ ውጤቶች ላይ አንብበናል፡፡ ለምሳሌ የቀድሞው የኢህዴን ሊቀመንበር ያሬድ ጥበቡ (ጌታቸው ጀቤሳ) “መስታወት” በተሰኘ መጽሔት ላይ በጻፉት አንድ ጽሑፍ ሁሉንም የኢህአዴግ መሪዎች በፈሪነት ከፈረጇቸው በኋላ ሃየሎም አርኣያን ብቻ በጀግንነት አወድሰዋል፡፡ በኤርትራና በትግራይ ሲዋጉ የነበሩ የደርግ የጦር መኮንኖችም በተለያዩ መጽሔቶች ስለሃየሎም ኣርኣያ ጀግንነት ሲያወሱ ነበር፡፡
 በመሆኑም በሃየሎም የጦር ሜዳ ጀግንነትና በወታደራዊ ጥበብ አዋቂነቱ ላይ ጥርጣሬ የሚቀርብ አይመስለኝም፡፡ ሆኖም የሃየሎምን አሟሟት ያየ ሰው “ሰውዬው ሰማዕት ነው ሊባል ይችላልን?” የሚል ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል፡፡ ምክንያቱም በተለምዶ ሰማዕታት የሚባሉት በትግሉ ሂደት ሲዋጉ የወደቁ ሰዎች ናቸውና፡፡ ሃየሎም የተገደለው ግን የትጥቅ ትግሉ ካበቃ ከአራት ዓመታት በኋላ በተከሰተ ጸብ ነው፡፡
 የኢህአዴግ ሰዎች “ሃየሎም በሰላም ጊዜ በሚደረገው ትግል መሃል የወደቀ ጓዳችን በመሆኑ ሰማዕት ነው” እንደሚሉ ይታወቃል፡፡ ከሰማዕታቱ መካከል የተናጥል ሃውልት ያቆሙትም ለርሱም ብቻ ነው፡፡ ሌሎች ወገኖችስ በሰማእትነቱ ላይ ምን ይላሉ? በጉዳዩ ላይ ያላቸውን አቋም እንዲነግሩን እንጠብቃለን፡፡
*****
ሃየሎም አርኣያ ህወሓት (በኋላም ኢህአዴግ) ባካሄዳቸው ዋና ዋና ዘመቻዎች ላይ የመሪነት ሚና ነበረው፡፡ ከነዚያ ዘመቻዎች መካከል ከስሙ ጋር ተቆራኝቶ የቀረው በየካቲት ወር 1978 የተካሄደው “ኦፕሬሽን አግአዚ” ነው፡፡ ይህንን ኦፕሬሽን የሚመለከት ጽሑፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት በሚያዚያ 1985 በታተመው “እፎይታ” መጽሔት ላይ ነው፡፡ ተራኪው ደግሞ ሃየሎም አርኣያ ራሱ ነበረ፡፡
 ታዲያ ጽሑፉ በጣም የሚያስደምም በመሆኑ ብዙዎች ታሪኩን በመጠራጠር “ሰውዬው የተናገረው ልብወለድ ነው እንጂ እውነተኛ ነገር  አይደለም” ብለው ነበር፡፡ በዘመኑ ከኢህአዴግ በታቃራኒነት የተሰለፉት የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣናት “ኦፕሬሽን አግአዚ” በትክክል የተፈጸመ ዘመቻ መሆኑን መናገር ሲጀምሩ ግን የሃየሎም ትረካ እውነተኛት ሊረጋገጥ በቅቷል፡፡ በዚህ ረገድ የመጀመሪያውን ምስክርነት የሰጡት ጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያም እራሳቸው ናቸው (በ1994 የታተመውን የሌ/ኮ/ መንግሥቱ ኃይለማሪያም ትዝታዎችን ያስታውሱ)፡፡ በማስከተልም “ነበር” የተሰኘውን ተወዳጅ መጽሐፍ የጻፉት ገስጥ ተጫኔ (ዘነበ ፈለቀ) “ኦፕሬሽን አግአዚ” በትክክል መፈጸሙን አረጋግጠዋል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡
   “ኦፕሬሽን አግአዚ” በመቀሌ እስር ቤት ታስረው የነበሩ ከሶስት ሺህ የሚበልጡ የህወሐት ታጋዮችንና ደጋፊዎችን የማስለቀቅ ተልዕኮ ነበረው (ኦፕሬሽኑ የተሰየመለት “አግዓዚ” የሚባለው ታጋይ ከህወሐት መስራቾች አንዱ ነው፤ “አግዓዚ” የትግል ስሙ ሲሆን እውነተኛ ስሙ “ዘርዑ ገሠሠ” ነበር)፡፡ እንደ ጄኔራል ሃየሎም አርኣያ አገላለጽ ኦፕሬሽኑን ለማካሄድ የሚያስፈልገው ቅድመ ዝግጅት ለስድስት ወራት ያህል ተካሄዷል፡፡ በኦፕሬሽኑ የሚሳተፉ ኮማንዲስቶች በሚስጢር ነው የሰለጠኑት፡፡ ሆኖም ሰልጣኞቹ በስልጠናው ላይ በነበሩበት ወቅት ስለኦፕሬሽኑ ምንም መረጃ አልነበራቸውም፡፡ በመሆኑም እነዚያ ሰልጣኞች ለስልጠናው ወደተዘጋጁት የአሸዋ ቤቶች በሚወሰዱበት ጊዜ ከፊሉ “ይህ የመቀሌ ቤተ መንግሥት ነው” ይሉ የነበረ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ “አይ! የአየር ማረፊያው ነው” እያሉ ልዩ ልዩ መላምቶችን ይደረድሩ ነበር፡፡
  “ኦፕሬሽን አግአዚ” በታቀደለት ጊዜ ተካሄደ፡፡ የህወሓት አሸማቂዎችም ማንም ባልጠበቀው ሁኔታ ወደ መቀሌ እስር ቤት በመግባት የሚፈልጓቸውን ታሳሪዎች በሙሉ አስለቀቁ፡፡ በማግስቱ ወሬው በአዲስ አበባ ሲሰማ በሊቀመንበር መንግሥቱና በጦር ጄኔራሎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ ተቀሰቀሰ፡፡ መቀሌ ያሉ የጦር መሪዎችም ለአስቸኳይ ግምገማ ተጠሩ፡፡ በግምገማው ማብቂያም “ለኦፕሬሽኑ መሳካት ትልቁን ሚና የተጫወተው በአካባቢው የነበረው አብዮታዊ ጦር አዛዥ የነበረው ብ/ጄኔራል ታሪኩ ዐይኔ ያሳየው እንዝህላልነት ነው” ተባለ፡፡
  የደርግ መንግሥት ባለስልጣናት ታሪኩን ሲጽፉ “የህወሓት ጦር በእስር ቤቱ ላይ ወረራ በፈጸመበት ወቅት የእስር ቤቱ ሃላፊ ወደ ጄኔራል ታሪኩ በመደወል “በወንበዴ ተወርሬአለው፤ ባሉኝ ጠባቂዎች መከላከል ስለማልችል ረዳት ጦር በአስቸኳይ ይላኩልኝ” በማለት ሲጠይቀው ጄኔራል ታሪኩ “እኔ መደበኛ ወታደር እንጂ የእስር ቤት ጠባቂ ዘበኛ አይደለሁም” የሚል የሹፈት መልስ ሰጥቶት ከቤቱ ገብቶ ተኝቷል፤ የአንድ አብታዊ ጦር ዋና ዓላማ ሀገሩን ከውጭ ወራሪዎችና ከውስጥ ወንበዴዎች መከላከል ሆኖ ሳለ ጄኔራል ታሪኩ ረዳት ጦር ለወህኒ ቤቱ እንዳይደርስ በማድረጉ ወያኔ ታሳሪዎቹን በቀላሉ ለማስመለጥ ችሏል፤ በዚህም ጄኔራሉ የወንበዴዎቹ ዓላማ ተባባሪ ሆኗል” ይላሉ፡፡
 በተለይ ግን ጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያም “ኦፕሬሽን አግአዚ”ን በምሬት ነው የሚያነሱት፡፡ ጓድ መንግሥቱ “ወያኔ በዚያ ድንገተኛ ወረራ ሊያመልጡ የማይገባቸውን ወንጀለኞች ለማስለቀቅ ችሏል” በማለት ለጋዜጠኛ ገነት አየለ አንበሴ ነግረዋታል፡፡ ሆኖም ለወንበዴዎቹ ድጋፍ ሰጥተዋል በተባሉት ጄኔራል ታሪኩ ዐይኔ ላይ መጥፎ እርምጃ አልተወሰደም፡፡ ጓድ መንግሥቱ ይህንንም ሲያብራሩ “የታሪኩ ጓደኛ የሆኑ የጦር መሪዎች በአማላጅነት ወደኔ መጥተው “ጓድ ሊቀመንበር! ታሪኩን በዚሁ ብቻ ከምንመዝነው ወደ ኤርትራ ይላክና ችሎታውን ያሳይ” ስላሉኝ እኔም ቃላቸውን በመቀበል ወደ አፋቤት ልኬዋለሁ” ብለዋል (ሆኖም ጄኔራል ታሪኩ ወደ አፋቤት ቢቀየርም ከአራት ዓመታት በኋላ ተረሽኗል)፡፡
እነ ሃየሎም አርኣያ በበኩላቸው በጄኔራል ታሪኩ ላይ የቀረበውን ክስ አይቀበሉም፡፡ ሃየሎም ስለጉዳዩ ሲናገር “ጄኔራሉ ጦሩን ለማንቀሳቀስ ያልቻለው በእንዝህላልነት ሳይሆን የኛ ጦር በመቀሌ ከተማ የተለያዩ ስፍራዎች የማዘናጊያ ውጊያዎችን በመክፈቱ መደበኛው ወታደር በነዚያ ውጊያዎች ስለተወጠረ ነው፤ እኛም የማዘናጊያ ውጊያዎቹን ሽፋን በማድረግ ያለምንም ስጋት እስረኞቹን ለማስለቀቅ ችለናል” ብሏል፡፡ 
   “ኦፕሬሽ አግዓዚ”ን በተመለከተ አከራካሪ ሆኖ የዘለቀ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ ይህም ኦፕሬሽኑን ለማካሄድ የወሰደውን ጊዜ የሚመለከት ነው፡፡ ጄኔራል ሃየሎም አርኣያ “ኦፕሬሽኑ የተካሄደው በአስራ አምስት ደቂቃ ውስጥ ነው፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ስራችንን ሙሉ በሙሉ መጨረስ እንደምንችል ያወቅነው ስልጠናው በሚካሄድበት ወቅት ነው” ብሏል፡፡ የደርግ ባለስልጣናት ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ዘርዘር ያለ ነገር ባይጽፉም ኦፕሬሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፈጸሙን በደፈናው ያምናሉ፡፡  (በነገራችን ላይ የ“ኦፕሬሽን አግአዚ”ን ታሪክ መሰረት ያደረጉ ሁለት ፊልሞች ተሰርተዋል፤ አንደኛውን ፊልም ያዘጋጀው ታዋቂው አርቲስት ኪሮስ ኃይለ ሥላሤ ሲሆን የሁለተኛውን ፊልም አዘጋጅ ማንነት በትክክል አላውቅም፤ ሆኖም ሁለቱ አዘጋጆች “ኦሪጂናሌው ታሪክ የኔ ነው” በሚል ውዝግብ ፈጥረው እንደነበረ አስታውሳለሁ)፡፡
*****
ሃየሎም አርኣያ የተገደለው በየካቲት ወር 1988 ነው፡፡ ታዲያ የርሱ ሞት ከፍተኛ የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ ነበር፡፡ በኦፊሴል የወጣው የኢትዮጵያ መንግሥት መግለጫ አሟሟቱን ሲያስረዳ “ጄነራል ሃየሎም አርኣያ ጀሚል ያሲን ከሚባል ኤርትራዊ ወጣት ጋር በተፈጠረ ጸብ ተገድሏል” ነው ያለው፡፡ ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ግን የሞቱን ምክንያት ሲያስረዱ “ኤርትራ በሓኒሽ ወደቦች ምክንያት ከየመን ጋር በተጣላችበት ወቅት ሃየሎም አርኣያ “ከኤርትራ መንግስት ጋር ያለን ግንኙነት እንደማንኛውም ኢንተርናሽናል ግንኙነት መታየት አለበት፤ በተለይም በወታደራዊ መስክ ያለን ግንኙነት በሀገራችን ላይ አደጋ የሚጋብዝ መሆን የለበትም፤ ከኤርትራ ጎን ሆነን የምንዋጋበት ምክንያት ሊኖር አይገባም” የሚል አቋም በማራመዱ የሻዕቢያ ጥይቶች ሰለባ ለመሆን በቅቷል” ብለው ነበር፡፡ እነዚህ ወገኖች “የሃየሎም አርኣያ ገዳይ ኤርትራዊ መሆንም ይህንኑ ያረጋግጣል” በማለትም አክለዋል፡፡ ከዚህም አልፎ “በስልጣን ላይ የነበረው የአቶ መለስ ዜናዊ አመራር የግድያው ተባባሪ ነው” የሚሉ በርካታ ሰዎች አሉ፡፡
  ሃየሎምን ተኩሶ የገደለው ወጣት ጀሚል ያሲን ከመሞቱ በፊት ከእፎይታ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ “በምሽቱ ሐሺሽ ወስጄ ነበር፤ በሐሺሽ ተገፋፍቼ ነው የገደልኩት እንጂ የተለየ ጠብ ኖሮን አይደለም” የሚል ቃል ነው የተናገረው፡፡ ሃየሎም በሞተበት ወቅት በአጠገቡ የነበሩት ሰዎችም “ወጣት ጀሚል በስካር ጥንብዝ ብሎ ሃየሎምን በባለጌ ስድቦች ይሳደብ ነበር፤ ሃየሎም ለረጅም ጊዜ ከታገሰው በኋላ ትዕግስቱ ሲያልቅበት ሁለት ጥፊ አቀመሰው፣ በዚህ የተናደደው ጀሚል ሽጉጡን ከመኪናው ውስጥ አምጥቶ ገደለው” የሚል ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡
  መንግሥታት በርካታ ጉዳዮችን ሚስጢራዊ ማድረጋቸው የተለመደ ቢሆንም የሃየሎም ሞት ሙሉ በሙሉ ሚስጢራዊ ሆኖ ቀርቷል ለማለት ምንም ዋስትና የለንም፤ እንዲህ የምንለው ከበርካታ ማዕዘናት በመነሳት ነው፡፡ ለምሳሌ የህወሐት (ኢህአዴግ) ባለስልጣናት በየጊዜው ፓርቲውን ለቀው ይኮበልላሉ፡፡ ሆኖም ከነዚያ ባለስልጣናት መካከል አንዳቸውም ቢሆኑ “ሃየሎም ሻዕቢያ በሸረበው ሴራ ነው የተገደለው” በማለት ሲናገሩ አልሰማናቸውም፡፡ ከአቶ መለስ ጋር ተጋጭተው ከድርጅቱ የወጡትና ከመለስ በላይ ሃየሎምን በቅርበት የሚያውቁት አቶ አረጋዊ በርሀም አቶ መለስን በሃየሎም ግድያ ሲከሷቸው አልተሰሙም፡፡ ከህወሐት ጋር ታሪካዊ ጠላት ሆነው የዘለቁት አቶ አብረሃም ያየህም “ኤርትራ ኢትዮጵያን የወረረችው በአቶ መለስ ዜናዊ አደፋፋሪነት ነው” እያሉ ቢጽፉም ለሃየሎም ሞት ሻዕቢያንም ሆነ አቶ መለስ ዜናዊን ተጠያቂ ሲያደርጉ አላየናቸውም፡፡ ከህወሓት ያፈነገጡት እነ ተወልደ ወልደማሪያምና ስየ አብረሃም ለሻዕቢያ ወረራ በየጊዜው የአቶ መለስን ቡድን ተጠያቂ ማድረጋቸው እንደተጠበቀ ሆኖ የሃየሎምን ግድያ ከኤርትራ ጉዳይ ጋር  ሲያገናኙት አልተደመጡም፡፡
ሻዕቢያ ሃየሎምን አስገድሎት ሊሆን ይችላል የሚሉ ሰዎች በበኩላቸው “ሴራውን ይገልጻሉ” የሚሏቸውን አንዳንድ ምልክቶችን ይደረድራሉ፡፡ ለምሳሌ ሃየሎም ከሞተበት ዕለት ጀምሮ የኤርትራ ሚዲያዎችና ዌብሳይቶች ሰውዬውን በጀግንነቱ ሲያደንቁት እንጂ በአሉታዊ መልኩ ሲያነሱት አይታዩም፡፡ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በሚካሄድበት ወቅት እንኳ የኤርትራ ሬድዮ “የአቶ መለስ አገዛዝ ሃየሎምን የመሰለ የጦር ጀግና ያስበላ የወንበዴ ቡድን ነው” ይል ነበር፡፡ እናም በርካታ ሰዎች “እነዚህ የኤርትራ ሚዲያዎች ሃየሎምን የሚያደንቁት የግድያው ሚስጢር እንዳይወጣ ለማፈን ቢሆንስ?” የሚል የጥርጣሬ ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡
 በኛ በኩል “ተጨባጩ እውነታ ይህ ነው” ብለን ምስክርነት መስጠት አንችልም!! በግድያው ዙሪያ በኢንተርኔትም ሆነ በፕሬስ ሲጻፍ የነበረው ሁሉ ጥርጣሬ እንጂ ሐቅ ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ጥርጣሬ እውነትም ሊሆን ይችላል፤ ውሸትም ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም የታሪክ ተመራማሪዎች  አንድ ቀን ሐቁን ያሳውቁናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን!! በዚህ አጋጣሚ የማንክደው ነገር ቢኖር ሃየሎም አርኣያ የጦር ሜዳ ጀግና የነበረ መሆኑን ነው፡፡
—-
  አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 7/2007
ገለምሶ-ሀረርጌ

በሰሜን ምሥራቅ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሬፓብሊክ ውስጥ እየደረሰ ያለዉ ጥቃት ማሕበረሰቡን ከፍተኛ ስጋት ላይ እደጣለዉና መፍትሄ አልባ እንዳደረገዉ ተገልፆአል። የሲቪሉ ማሕበረሰብ ድርጅቶች አማፅያን የሚያደረሱት ጥቃት ለመከላከል የዓለም አቀፉን ርዳታ ጠይቀዋል።

የአሜሪካው የስለላ ተቋም «CIA» በሽብርተኝነት ተጠርጣሪ እስረኞችን በምርመራ ወቅት በከፍተኛ ሁናቴ ማሰቃየቱን የሚያጋልጠው ሠነድ በስተመጨረሻ ይፋ ሆኗል። የሰብአዊ መብት ተሟጋቿ ሎውራ ፒተር ሠነዱን፦ «ለበርካታ አሜሪካውያን እጅግ አስደንጋጭ ነው» በማለት ገልፀዋል።

በተለይ አዲስ አበባ ከተማ በሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎችና የሴቶች ጥቃት ፖሊሶችና የሕግ ተርጓሚዎች ተገቢዉን ድጋፍ እንደማያደርጉ ይባስ ብለዉም ወንጀሉን የሚያባብሱ ተግባራት እንደሚፈጽሙ ተገለጸ።

ከአፍሪቃው ክፍለ ዓለም ፣ ሞሮኮ፣ ለኃይል ምንጭ ፣ ከነዳጅት ዘይት ይልቅ ለፀሐይ ሙቀትና ብርሃን የላቀ ግምት የሰጠችበት እንቅሥቃሤ በአወንታዊነት ሲጠቀስ፣ ዩጋንዳ ለተፈጥሮ ተስማሚ ነው ያለችውን በኤሌክትሪክ የሚሽከረከር አውቶሞቢል መሥራት ብቻ

‹‹አገዛዙ የወሰደውና ወደፊት የሚወስደው ከእስካሁኑ የባሰ አረመኔነት እርምጃ ይበልጡን ያጠናክረናል›› የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት ትናንት ህዳር 30/2007 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ትግሉን ያጠናክራሉ ያላቸውን ውሳኔዎችን አስተላለፈ፡፡ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ያስተላለፋቸው ውሳኔዎች ‹‹ህወሓት/ኢህአዴግ በፈፀመው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እና እስር ምክንያት ክፍተት ሳይፈጠር የፓርቲው እንቅስቃሴ እንዲቀጥልና ትግሉም እንዲጠናከር የሚያስችሉ ናቸው›› ሲሉ የብሄራዊ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሰይድ […]

ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄና የኮሚቴው መፈታት ጥያቄ በአስቸኳይ ሊመለስ ይገባል:: ሙስሊም ወገኖቻችን ለሃገራቸው እና ለነጻነታቸው ምን ያህል ቀናኢ መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል:: ወቅሰን ወቅሰን ወንጅለን ወንጅለን የሰለቸን ለመስማትም የታከተን ነገር ቢኖር ያለፉት ስርአቶች ላይ እና ሌላው ላይ ማሳበብን አንዱን ከአንዱ ለማፋጀት ማፈራረጅን መጠቋቆምን የመሳሰሉት ኢሕአዴጋዊ ባህርያት ናቸው::ወያኔ ኢሕኣዴግ የጭንቅ ነገር […]

በመቀሌ ዞን የአንድነት አመራር አባል የነበረው ወጣት ሺሻይ አዘናው ጥቅምት 22 በደህንነት ኃይሎች ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ በመቀሌ በሚገኝ አንድ እስር ቤት ኮማንደር ሰዓረ በሚባል የፖሊስ አዛዥና እርሱ በሚመራቸው ፖሊሶች ከፍተኛ የሆነ ድብደባ ተፈፅሞበታል። ከዚያ በኋላ የት እንዳለ ሳይታወቅ ተሰውሮ ቢቆይም፤ በአሁኑ ሰዓት ማዕከላዊ እየተባለ በሚጠራው የማሰቃያ እስር ቤት እንደሚገኝና በዚህም ቦታ በተከታታይ ለአራት ቀናት ሌሊት […]


አፈንዲ ሙተቂ
——
ዶ/ር ሃይሌ ፊዳ በፎቶግራፉ ላይ የምትመለከቱት ነው፡፡ ፎቶውን የሰጡን አንጋፋው ደራሲ አበራ ለማ ናቸው፡፡ ጋሼ አበራን እያመሰገንን በሃይሌ ፊዳ አሟሟት ዙሪያ የተጠናቀረውን ይህንን ጽሑፍ ጀባ ብለናችኋል፡፡
                                                                          *****
ኮ/ል መንግሥቱ ሀይለማሪያም “ሀይሌ ፊዳ የተገደለው በገበሬዎች ነው” ባይ ናቸው፡፡ ከጋዜጠኛና ደራሲ ገነት አየለ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ የሀይሌ ፊዳን ሞት እንዲህ በማለት አስረድተዋል፡፡
ገነት፡ ሀይሌ ፊዳስ? በነሐሴ 1970 ተይዞ ከአንድ ዓመት በኋላ ነገር ከበረደ፤ ሁሉ ነገር ከተረጋጋ በኋላ ነው የተገደለው፡፡ በዚያን ጊዜ የኃይሌ ፊዳ በህይወት መኖር መንግሥትን ያሰጋ ነበር?
መንግሥቱ፡ መቼ ነው የሞተው ሀይሌ ፊዳ?
ገነት፡ በሀምሌ 1971 ነው::
መንግሥቱ፡ ማነው የገደለው?
ገነት፡ እኔ ምን አውቃለሁ? አስከሬኑ ከቀድሞው የራስ አስራተ ካሣ ግቢ ነው ተቆፍሮ የወጣው፡፡ እዚያ ነው የተገኘው፡፡
መንግሥቱ፡ ሀይሌ?
ገነት፡ አዎን! ሀይሌ ፊዳ፡
መንግሥቱ፡ እዚያ ምን ሲሰራ?
ገነት፡ እዚያ ነው አስከሬኑ የተገኘው፡፡
መንግሥቱ፡ እኔ አላውቅም፡፡
ገነት፡ መሞቱንም አያውቁም? እርሱንም እዚህ ከመጡ በኋላ ነው የሰሙት?
መንግሥቱ፡ መኢሶኖች እኮ ጥለውን ሄደዋል፡፡ የሶማሊያ ጥቃት አይሎ ሲመጣ የሻዕቢያዎች ጎራ ስለጠነከረ ከዚህ ከደከመ መንግሥት ጋር ምን እንሰራለን ብለው አይደል እንዴ ጥለው የነጎዱት? በነሱ ሃሳብ እኛ በመዳከማችን ወደፊት ከኛ ጋር በመቀጠል የስልጣን ጥማታቸውን የሚያረኩበት መንገድ ስለማይኖር ልዩ ልዩ ምክንያት ሲያቀርቡ ቆይተው በመጨረሻ ፈርጥጠዋል፡፡ በዚህን ጊዜ እነ መስፍን ካሱ ወደ ሲዳሞ፡ እነ ሀይሌ ፊዳ ወደ ወለጋ ሲሄዱ አግኝቶ ገበሬ ነው የከሰከሳቸው፡፡
ገነት፡ እዚያ ነው የተገደሉት?
መንግሥቱ፡ በሙሉ!
(ገነት አየለ አንበሴ፡ የሌተና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም ትዝታዎች፡ 1984፣ ገጽ 207-208)
                                                                          *****
ሊቀመንበር መንግሥቱ “የሀይሌ ፊዳን መሞት ሰው ነው የነገረኝ” ነው የሚሉት፡፡ ነገር ግን ሀይሌ በነሐሴ 1969 ከተያዘ በኋላ በደርግ ምርመራ ክፍል ሲሰቃይ ቆይቶ እንደተገደለ ይታወቃል፡፡ ለዚህ ማስረጃ የሆነውንና ሀይሌ ከመሞቱ በፊት የሰጠውን ባለ 36 ገጽ የምርመራ ቃል በልዩ ልዩ መንገዶች ታትሞ አንብበነዋል፡፡ ከሀይሌ ጋር በአንድ ክፍል ታስረው የነበሩ ጓዶችም ሀይሌ በዚያ ወር እንደተገደለ ተናግረዋል፡፡ የደርግ የቅርብ ሰው የነበሩት አቶ ገስጥ ተጫኔ (ዘነበ ፈለቀ) “ነበር” በሚል ርዕስ በጻፉት ባለሁለት ቅጽ መጽሐፍ የምርመራ ቃሉን ከማተማቸውም በላይ ሀይሌ ከሱሉልታ ኬላ ተይዞ ወደ ደርግ ጽ/ቤት በመጣበት ወቅት በብሄራዊ ቤተመንግሥት እንዳዩት መስክረዋል፡፡
    
  በዚህም መሰረት “ሊቀመንበር መንግሥቱ ሀይሌን በእርግጥ ገድለውታል ወይ?” የሚለው ጥያቄ ለአሁኑ ዘመን አይሰራም፡፡ “መንግሥቱ ሀይሌን ለምን ገደሉት?” የሚለው ግን አሁንም ያከራክራል፡፡ ገነት አየለ እንደገለጸችው ሀይሌ በተገደለበት ወቅት ነገሮች ሁሉ በጣም በርደዋል፡፡ የሶማሊያ ወራሪዎች ከምስራቅ ኢትዮጵያ ከተባረሩ አንድ ዓመት አልፎአቸዋል፡፡  ሻዕቢያና ጀብሃ በሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ክፉኛ ተደቁሰው ወደ ሱዳንና ወደ ሳሕል በረሃ ገብተዋል፡፡ ከነዚህ ሁለት ክስተቶች ቀደም ብሎም ሀገር ያተራመሰውና ሺዎችን የቀሰፈው የቀይ ሽብር ዘመቻ ደርግ በሚፈልገው መልኩ ተጠናቋል፡፡ አብዮታዊው መንግሥት ከዚያ በፊት ያላየው ሰላምና እርጋታ በሀገሪቱና በሁሉም የስራ መስኮች ሰፍኗል፡፡ ታዲያ በዚህ ሰላማዊ ወቅት ሀይሌ ፊዳን ማስገደሉ ለምን አስፈለገ?
  
  
በርካታ ተመልካቾች የየራሳቸውን ግምት አስቀምጠዋል፡፡ አንዳንዶች ነገሩን ከቂም በቀል ጋር ያያይዙታል፡፡ “መንግሥቱ አንድ ቀን የገላመጠውን እንኳ የማይምር ቂመኛ ነው” -ይላሉ እነዚህ ወገኖች፡፡ የተወሰኑት ደግሞ መንግሥቱ በችሎታና በእውቀት ከርሱ የሚበልጥ ሰው ከታየው ወደፊት ስልጣኔን ይነጥቀኛል በሚል እንደሚያስገድለው ያወሳሉ፡፡ እነዚህኛዎቹ ክርክራቸውን ሲቀጥሉ “መንግሥቱ ሀይለማሪያም ሀይሌ ከእስር ቢለቀቅ ወይም ቢያመልጥ የራሱን ቡድን አደራጅቶ ወይ አንዱን ጄኔራል ተጠግቶ ከስልጣኔ ሊያሽቀነጥረኝ ይችላል” የሚል ፍራቻ ነበረው” ባይ ናቸው፡፡
     
   ከሁለቱ ወገኖች የሚለይ አስተያየት የሚሰጡ ጸሐፊያንና የታሪክ ሰዎችም አሉ፡፡ እነዚህኛዎቹ እንደሚሉት ኮሎኔል መንግሥቱ ሃይለማሪያም በሀይሌ ጉዳይ ላይ የሞት ውሳኔ ያሳለፉት እርሳቸውን ያስደነገጠ አንድ አደገኛ ክስተት ስለተፈጠረ ነው፡፡ እስቲ ታሪኩን አብረን እንየው፡፡
                                                                          *****
     ሊ/ር መንግሥቱ ለጉብኝት ወደ ኩባ ይጋበዛል፡፡ ከጓድ ፊደል ካስትሮ ጋር ጉብኝትና ስብሰባውን ማካሄድ ይጀምራል፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ለስራ ጉዳይ ወደ ውጪ ሀገር በመሄዱ ህይወቱ ለጥቂት የተረፈችው የመኢሶኑ ዶ/ር ነገደ ጎበዜ አዲስ አበባ መግባቱ ይነገረዋል፡፡ “እንዴት መጣ?” ብሎ ቢጠይቅ “የደቡብ የመንን ፓስፖርት ይዞ፤ ከደቡብ የመን ልዑካን ጋር ተቀላቅሎ” ሆነ መልሱ! (ደቡብ የመን አሁን ከሰሜን ጋር ተዋህዳለች)፡፡ “ዶ/ር ነገደ ተይዟል ወይ?” ብሎ ሲጠይቅ አለመያዙ ተነገረው፡፡ ያለበትን ቦታ ጠይቆ የተሰጠውን መልስ ሲሰማ ደግሞ ሊ/ር መንግሥቱ በድንጋጤ ፈዝዞ ቀረ!
                                                                          *****
 በርግጥ ዶ/ር ነገደ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ነገር ግን መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ ድሮ ከሚያውቀው የኤርፖርት ደህንነት ሃላፊ ጋር አይን ለአይን ተገጣጠመ፡፡ ደህንነቱ ነገሩን ወዲያኑ ለደርጎች አስታወቀ፡፡ ደርጎችም ነገደ ጎበዜን ለመያዝ ተንቀሳቀሱ፡፡ ሆኖም ዶ/ሩ ኩባ ኤምባሲ ገብቶ ተደበቀ፡፡ ሁኔታው ለጓድ ፊደል ካስትሮ ሲነገራቸው ካስትሮ አማላጅ ሆኑና በነገሩ ውስጥ ገቡ፡፡ በርሳቸው ተማጽኖም ዶ/ር ነገደ ከኤምባሲው ወጥቶ ወደ አውሮጳ ተመለሰ፡፡
  
   ይህ ድርጊት የተከሰተው የሶማሊያ ወረራ ካበቃ ከጥቂት ወራት በኋላ ነበር፡፡ ደርጎች ነገሩን እንደ ኩዴታ ነው የወሰዱት፡፡ ለዚህም ነው በውስጣቸው ከፍተኛ መሸበር የተፈጠረው፡፡ እርግጥ ሀገራቱ ኩዴታ እናድርግ ቢሉ የማስፈጸም አቅሙ ነበራቸው፡፡ በወቅቱ የ”ሶማሊያን ወረራ ለመቀልበስ በተደረገው ዘመቻ አብዮታዊ አጋር ሆኖ የመጣው የኩባ ሀያ ሺ ሜካናይዝድ ጦርና የየመን ሁለት ሺህ መድፈኛ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ ስለነበሩ እነርሱን ይዘው አንድ ነገር ማድረግ ይችሉ ነበር ተብሎ ይገመታል፡፡ የዘመኑ ሀያል ሶሻሊስት ሀገር የሆነችውን ሶቪየት ህብረትንም ለእርዳታ ቢጠሯት “በጄ” ከማለት የምትመለስ አይሆንም-ከመንግሥቱ ይልቅ ኩባና ደቡብ የመን ይበልጡባታልና፡፡ ሆኖም የዶ/ር ነገደን መምጣት ብቻ በማየት “ኩዴታ” ተጠንስሷል ለማለት ይከብዳል፡፡
     ሊ/ር መንግሥቱ በዚህ መረጃ ላይ በመመርኮዝ “ኩዴታ” እንደታቀደባቸው አሰመሩበት፡፡ ሀገራቱ ፈጸሙብኝ ላሉት በደል ደግሞ ቀጥተኛ ምላሽ ከበዳቸው -ምክንያቱም የክፉ ቀን ወዳጆች ናቸውና፡፡ በሌላ በኩል ግን ሊቀመንበሩ ቁጭታቸውን መዋጥ አቃታቸው፡፡    ለምን ቢባል እንኳንስ እንዲህ ዓይነቱን ምልክት አግኝተው ይቅርና በጥርጣሬ ብቻ ብዙዎችን ቀስፈዋልና፡፡ የቀይ ሽብሩ ትርዒት ሳይደመር የተፈጁትን ሰዎች ቤት ይቁጠረው፡፡ ሌ/ኮ/ አጥናፉ አባተን “ለሀገራችን ሶሻሊዝም አይጠቅማትም፤ እንደ ዩጎዝላቪያ የቅይጥ ኢኮኖሚ መርህ መከተል አለብን” በማለታቸው ብቻ አስገድለዋቸዋል፡፡ “ለኤርትራ ጥያቄ ሰላማዊ መፍትሔ ያስፈልጋል” ያሉ በርካታ ጓዶቻቸውን አስረሽነዋል፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ፣ ቄስ ጉዲና ቱምሳ እና ሼኽ ሰይድ ቡደላ (የአብሬት ሼኽ) የመሳሰሉ የሀይማኖት አባቶች ያለ አንዳች ምክንያት ተገድለዋል፡፡ ከዚህ አንጻርም ለዶ/ር ነገደ ጎበዜ ድፍረት የሚሰጡት ቅጣት ከፍተኛ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ግን ዶ/ር ነገደ አልተያዘም፡፡ ስለዚህ ቁጭቱ በምን ይውጣላቸው?
    እንግዲህ በአንዳንዶች እምነት ዶ/ር ሀይሌ ፊዳ የተገደለው በዚህ እርግጠኛነቱ ባልታወቀ የዶ/ር ነገደ ጎበዜ “ኩዴታ” ጦስ ነው፡፡ ኩባና የመንን መበቀል ሲያቅታቸው ቁጭታቸውን በግቢአቸው ባጎሩት እስረኛ ላይ ተወጡት፡፡ ሀይሌን በአንድ ቀዝቃዛ ምሽት አሰናበቱት፡፡
                                                                          *****
     በቅርብ ጊዜ የተገኙ መረጃዎች ግን ከላይ የቀረበውን ታሪክ ዋጋ ቢስ አድርገውታል፡፡ እነዚህ መረጃዎች እንደሚሉት ዶ/ር ነገደ ጎበዜ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው የመጡት በሊቀመንበር መንግሥቱ እውቅና ነው፡፡ ለምሳሌ ዶ/ር መረራ ጉዲና በቅርቡ ባሳተሙት መጽሓፋቸው “ነገደ ጎበዜ በመንግሥቱና በኩባዊያን እውቅና መምጣቱን ነግሮኛል” በማለት ጽፈዋል፡፡ ከአሜሪካ የስለላ ምንጮች የተገኘው መረጃም ይህንኑ ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ደርጎች “መፈንቅለ መንግሥት ሊካሄድ ነበር” እያሉ ወከባ ይፈጥሩ የነበረው ህዝቡንና የተቃዋሚውን ክፍል ለማደናገርና የበለጠ ጸጥ ለማድረግ ነው ማለት ነው፡፡ የሀይሌ ፊዳ ግድያም ከመፈንቅለ መንግሥቱ ጋር አንዳች ግንኙነት አልነበረውም፡፡
  
     በአንጻሩ ደግሞ ሀይሌ ፊዳ የተገደለበት ሀምሌ 1971 በውል ሊመረመር የሚገባው የታሪክ ወቅት ሆኖ ሳለ ምሁራን በጥልቀት ሳያስሱት መቅረታቸው ይገርማል፡፡ ይህ ወር መንግሥቱ ከቀይ ሽብርና ነጭ ሽብር የተረፉ በርካታ ተቃዋሚዎቹን፣ አማካሪዎቹንና ታዋቂ ግለሰቦችን በድብቅ የገደለበት ጊዜ ነበር፡፡ እነ አቡነ ቴዎፍሎስን ጨምሮ የኢህአፓው ብርሀነ መስቀል ረዳ፣ የመኢሶኖቹ ከበደ መንገሻ፣ ንግሥት አዳነ፣ ደስታ ታደሰ፣ መስፍን ካሱ ወዘተ… በዚሁ ጊዜ ነበር የተገደሉት፡፡ “የማዕከል” ጥያቄ ደርጎችን ያናቆረው በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ ኢማሌድህ የሚባለውን የማርክሲስቶች ህብረት ከመሰረቱት አምስት ድርጅቶች (አብዮታዊ ሰደድ፣ መኢሶን፣ ወዝሊግ፣ ኢጭአት እና ማሌሪድ) መካከል መንግሥቱ ከሚመሩት “ሰደድ” ጋር በመድረኩ ላይ የቀረው የማሌሪድ መሪ ተስፋዬ መኮንን የታሰረውና የማሌሪድ ግብአተ ሞትም የተፈጸመውም በዚህ ወር ነበር፡፡ ስለዚህ ያ ታሪካዊ ወቅት የምሁራን እይታ ሊያርፍበት ይገባል፡፡
——
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 21/2006

የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ስብስብ የሆነው መድረክ የኢህአዴግ አገዛዝ በህዝባችን ህገመንግስታዊ ነጻ የመምረጥ መብት ላይ የሚፈጽማቸውን የመብት ረገጣዎች እንዲያቆም፣ በሃገራችን ነፃ ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ተአማኒነት ያለው ምርጫ እውን እንዲሆና የምርጫ ሜዳውም ለሁሉም እኩል የተመቻቸ እንዲሆን ለመጠየቅ ለታህሳስ 5 ቀን 2007 ዓም የተቃውሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ መጥራቱን አስታውቋል። መድረክ ለኢህአዴግ አገዛዝ የውይይትና የድርድር ጥያቄዎችን በተደጋጋሚ ቢያቀርብም፣ አገዛዙ …

ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ የሽግግር ካውንስል ለኢሳት በላከው መግለጫ የአፓርታይድ ስርአትን እአካሄደ ያለው የወያኔ አገዛዝ በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የወሰደው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ሊወገዝ ይገባዋል ብሎአል። የኢኮኖሚ እድገት አምጥቻለሁ እያለ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛ መንግስት ፣ በስልጣን ላይ ለመቆየት ብቸኛ መተማመኛው ሃይል መሆኑን አሳይቷል ያለው የሽግግር ካውንስል፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችና የአለማቀፉ ማህበረሰብ ድርጊቱን እንዲያወግዙ …

ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ የጸጥታ ሃላፊ እንደገለጹት በደቡብ እና በቤንሻንጉል ክልሎች አጎራባች ወረዳዎች አሉ ችግሮችን ለመፍታት አንዳንድ ሙከራዎች ቢደረጉም፣ ከሶማሊ ክልል ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት አለመቻሉን ገልጸዋል። በደቡብ ክልል በአንዳንድ ወረዳዎች የድንበር ችግር መኖሩን የገለጹት ሃላፊው፣ ችግሩን ለመፍታት እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል። ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ጋር ያለውን የድንበር ውዝግብ ለመፍታት ተደጋጋሚ ሙከራ መደረጉን …

ኀዳር ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በደራ ወረዳ ጉንዶመስቀል ከተማ ላይ አንድ ከተማ ውበቱ የተባለ ሰው ሃብታሙ ሺበሺ የተባለን ሰው መግደሉን ተከትሎ፣ ገዳይን ለመያዝ በተደረገ ጥረት ሰኞ ህዳር 29፣ 2007 ዓም በአካባቢው ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ ተካሂዷል። ከተማ ውበቱ የተባለው ሰው በ1999 ዓም የሰዎች ለሰዎች የተባለውን ድርጅት ገንዘብ ከዘረፈ በሁዋላ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ቅዳሜ በአል-ማካ የወደብ ከተማ አካባቢ ስደተኞችን የጫነች ጀልባ መስመጧን እና 70 ኢትዮጵያውያን መሞታቸውን የየመን አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ-ገፁ አስታውቆ ነበር። ይህ መረጃ እስካሁን አልተረጋገጠም

ህዝብን በማይሽር ቁስል አየጎዱ በፕሮፓጋንዳ ማከም አይቻልም:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎EthioMuslims‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ላይ ሽብር ግድያ እስር ድብደባ እንግልት በጅምላ አፈሳ ዘረፋ ንጥቂያ እና ከፍተኛ የሆነ ኢሰብአዊነት እና ጭፍጨፋ በመንግስት ነኝ ባይ ሃይሎች በይፋ በአደባባይ ተፈጽሟል::ይህንን መንግስታዊ ሽብር የማይሽር ጠባሳ በመላው ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቁር ነጥብ አስቀምጧል:: የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ጥያቄና የኮሚቴው መፈታት ጥያቄ በአስቸኳይ ሊመለስ ይገባል::ሙስሊም ወገኖቻችን ለሃገራቸው እና ለነጻነታቸው ምን ያህል ቀናኢ መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል::
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … ost_9.html

Image

የዛሬ አምስት ዓመት ኮፐንሃገን የተካሄደዉ የአየር ንብረት ለዉጥ ጉባኤ ብዙ ተብሎለትና ብዙ ተጠብቆበት ካለ ዉጤት መጠናቀቁ ብዙዎችን ግራ ያጋባ ብቻ ሳይሆን ተስፋም ያስቆረጠ መስሎ ነበር።

ድርጅቱ ቀደም ሲል ሆስፒታሉን አዲስ አበባ ዉስጥ ለመገንባት ጥያቄ ቢያቀርብም የከተማይቱ መስተዳድር ለሆስፒታሉ ማስገንቢያ የሚሆን መሬት ባለመፍቀዱ ትግራይ ዉስጥ ለማስገንባት ወስኗል።

ፈረንሳይ በሚኖሩ አይሁዶች በሚታየው ዘረኝነት እና በሚፈፀምባቸው ጥቃት አንፃር በርካታ ሰዎች ባለፈው እሁድ በፓሪስ አቅራቢያ በምትገኘው ክሬቴይ ሰልፍ ወጥተዋል።አይሁዶች ሀብታሞች ናቸው የሚል የቆየ አነጋገር እንዳለ ይሰማል። ይኸው አነጋገርም ዛሬም ድረስ ብዙ ጠላት አፍርቶባቸዋል።

ትናንት በተጀመረዉ ሥብሰባ ላይ የአፍሪቃ መንግሥታት ፍርድ ቤቱ ከዓለም አቀፍነቱ ይልቅ አፍሪቃዉያንን ለመክሰስና ለመቅጣት ያለመ ነዉ በማለት ወቅሰዉታል። ፍርድ ቤቱ ከተመሠረተ ጀምሮ የከሰሳቸዉ ወይም የቀጣቸዉ በሙሉ አፍሪቃዉያን ፖለቲከኞች ናቸዉ።

The first female stage Actress, Artist Selamawit G. selassie passed away .. በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ተዋናይት ወ/ሮ ሰላማዊት ገብረሥላሴ ማረፋቸው ተነገረ። ነፍስ ይማር ። ከአንድ ዓመት በፊት ድንቅ መጽሔት ከቤታቸው ቃለ መጠይቅ አድርጎላቸው ነበር፣ እነሆ ለማስታወሻ ….

ሠላማዊት ገ/ሥላሴ – የመጀመሪያዋ የሴት አርቲስት (በጽጌ አይናለም የድንቅ መጽሔት ሪፖርተር ከአዲስ አበባ)
አብዛኛውን ጊዜ አስቸጋሪው ነገር ለአንድ ነገር የመጀመሪያ ሆኖ መገኘት ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ማህበረሰቡ…


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
——-
   
 አትሳሳቱ! በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ሰው ዐረብ አይደለም፡፡ ኢራናዊም አይደለም፡፡ ህንዳዊም አይደለም፡፡ በቀዳሚ ዘመኑ የኢትዮጵያ ፖስፖርት ነበረው፡፡ በኋላ ላይ ግን “ኤርትራ ነጸ መውጣት አለባት” ብሎ ኤርትራዊነትን ሰብኳል፡፡ ለዚህም በረሃ ወርዶ ብረት አንስቷል፡፡ በውጪ መዲናዎች “ሓርነት” እያለ ጮኋል፡፡ ይሁንና ያሰበው ከግቡ ሳይደርስለት ይህቺን ዓለም ተሰናብቷል፡፡ በአንድ ወቅት እርሱ ይመራቸው የነበሩ ወጣቶች ግን ዓላማውን አሳክተዋል፡፡
                                                                          *****
     “ጀብሃ” እና “ሻዕቢያ” በሚል ርዕስ የቀረበውን ተከታታይ ጽሑፍ ተከታትላችኋልን? እንዲያ ከሆነ “ሻዕቢያ” የተሰኘው ድርጅት ከጀብሃ ተገንጥሎ በሁለት እግሩ እንዲቆም የረዳው አንድ አደገኛ “ዲፕሎማት” እንደሆነ ተረድታችኋል ማለት ነው፡፡ ያ “ዲፕሎማት” በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ሰው ነው፡፡ የዚህ ሰው ልደት የተበሰረው በሞቃት አየሯ በምትታወቀው ውቢቷ የምጽዋ ከተማ አጠገብ ባለችው “ሀርጊጎ” በተሰኘች ባህረ-ገብ መንደር ነው፡፡ ወላጆቹ በምሥራቅ ኤርትራ ከሚኖሩት የአሳውርታ (ሳሆ) ብሄረሰብ ነው የተገኙት:: የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በምጽዋ ካገባደደ በኋላ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ አበባ ከተማ አጠናቋል፡፡ በ1950ዎቹ ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ በመምህርነት ተመርቋል፡፡ በስራው ዓለም ወደ ምጽዋ ከተማ ተመልሶ በትምህርት ቤት ዳይሬክተርነት አገልግሏል፡፡ በዚህ ሙያ ላይ እያለም ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር እንድትቀላቀል ሲደረግ እርምጃውን የተቃወመው “ማህበር ሸውአተ” (ሀረካ) አባል ሆኗል፡፡ በ1961 “ተጋድሎ ሐርነት ኤርትራ” (ጀብሐ) ሲመሰረት ደግሞ ከሀረካ ወጥቶ ጀብሃን ተቀላቅሏል፡፡ ድርጅቱንም ለረጅም ጊዜ በውጪ ጉዳይ ኃላፊነት አገልግሏል፡፡ ድርጅቱ እስከ አሁን ድረስ የሚታወቅበትን “ሰውራ” የተሰኘ መጽሔት መስርቷል፡፡ ከ1970 በኋላ ግን የድርጅቱን አካሄድ በመቃወም “ህዝባዊ ሀይሊ” የተሰኘ ንቅናቄ ጀምሯል፡፡ ይህንን ቡድን “ሰልፊ ነጻነት” ከተሰኘው የደገኛ ኤርትራዊያን ቡድን ጋር በማዋሃድ በታሪክ ገጾች “ህዝባዊ ሓርነት ሀይልታት” ወይንም “ሻዕቢያ” የተሰኘውን ጥምረት መስርቷል፡፡ ጥምረቱንም እንደ “ውስጠ ዘ” (defacto) ሊቀመንበር እና እንደ ውጪ ጉዳይ ሃላፊ ሆኖ አገልግሏል፡፡ በስተመጨረሻው ግን ከወጣቶቹ ጋር መግባባት ስላልቻለ በልዩነት ተሰናብቷል፡፡
     ይህ ሰው እ.ኤ.አ. በ1978 ከጀብሃ ጋር በጋራ አብሮ የመስራት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን በ1980 ገደማም የርሱን መስመር ከሚከተሉ ሌሎች ታጋዮች ጋር “ህዝባዊ ሓርነት ሀይልታት ሰውራዊ ባይቶ” የተሰኘ ድርጅት መስርቶ ነበር፡፡ ሆኖም በወቅቱ “ሻዕቢያ” የተሰኘው ግንባር ከርሱ ጋር በሀሳብ የተለዩትን ድርጅቶች እያሳደደ ይመታ ስለነበር ወደ ሀገር ቤት ገብቶ የትጥቅ ትግል ለመጀመር አልቻለም፡፡ ቢሆንም ሰውዬው በፖለቲካው መስክ አልሰነፈም፡፡ በውጪው ዓለም ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ትግል ማድረጉን ቀጥሏል፡፡ በ1987 ግን ይህችን ዓለም ተሰናብቷል፡፡
                                                                          *****
  ሰውየውን አውቃችሁታል አይደል? አዎን! ዑስማን ሳልህ ሳቤ ነው፡፡ ዛሬ በኢሳያስ የሚመራውን ህዝባዊ ግንባር (ሻዕቢያ) የመሰረተው እርሱ ነው፡፡ ይህ ሰው በታሪክ ምሁራን እጅግ ከፍተኛ ችሎታ ያለው ፖለቲከኛ ተብሎ ነው የሚጠቀሰው፡፡ በርካታ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች በጨቅላነታቸው ዘመን የርሱ እርዳታ በእጅጉ አስፈልጎአቸዋል፡፡ የኢህአፓ ታጋዮች የትጥቅ ትግል እንዲጀምሩ ያበቃቸውን ስልጠና ያገኙት በርሱ አማካኝነት ነው፡፡ ከአስር የማያንሱ ጠመንዣዎችንም ያስገኘላቸው እርሱ ነው፡፡ የኦነግ ጠንሳሾች የሚባሉት እነ ጃራ አባገዳ በመሳሪያ ተደራጅተው ትግሉን ለመጀመር የበቁት እርሱ ባደረገላቸው እርዳታ ታግዘው ነው፡፡ ለሌሎችም እንዲሁ የእርዳታ እጁን ዘርግቷል፡፡
  “ሻዕቢያዎች” ከዑስማን ሳልህ ሳቤ ጋር መጣላታቸው እሙን ነው፡፡ በአንድ ዘመን ሀይለኛ የፕሮፓጋንዳ ጦርነት አካሂደውበታል፡፡ ከነጻነት በኋላ ግን በትግሉ ላበረከተው አስተዋጽኦ እውቅና ሰጥተዋል፡፡ በርሱ ስም ትምህርት ቤትና ጎዳና ሰይመዋል፡፡ ይህም ከጀብሃ ጋር ንክኪ የነበረው ማንኛውም ግለሰብ ያላገኘው እድል ነው፡፡ ከርሱ ጋር ይህንን እድል በጥቂቱ ለመጋራት የቻለው አንጋፋው የጀብሃ ታጋይ ኢድሪስ ገላውዴዎስ ብቻ ነው፡፡
 —–
አፈንዲ ሙተቂ
ታሕሳስ 1/2006

አፍሪካውያን ቀደምት አያቶቻችን እንዲህ የሚል ትንቢት አዘል አባባል ነበራቸው፡፡ ‹‹የዚህ ትውልድ ትልቁ አደጋ ራታቸውን በቁርስ ሰዓት ለመብላት መፈለጋቸው ነው››፡፡ ሰው እንደ መላእክት አይደለምና በሂደት እየበሰለ፣ በሂደት እየተገነባ፣ በሂደትም የበለጠ እየተማረ የሚሄድ ፍጡር ነው፡፡ ይኼ ደግሞ የመንፈስ፣ የአካል፣ የስሜትና የአእምሮ ዕድገትና ለውጥን ይጠይቃል፡፡ ሰው ሲወለድ ለማደግና ለመለወጥ ከሚያስችል ዐቅም ጋር ነው፡፡ ይህንን ዐቅም ተጠቅሞ ለማደግና ለመለወጥ ግን ልምድ፣ ትምህርትና የሰውነት ግንባታ ያስፈልጉታል፡፡ ልምድ የሚባለው ከተወለደ ጊዜ ጀምሮ በሕይወት ውጣ ውረድ የሚደርስበት ተሞክሮ ነው፡፡ ይህም የሕይወት ተጋድሎ ይባላል፡፡ ትምህርት ከሰዎች፣ ከትምህርት ቤት፣ ከመጻሕፍት፣ ከአካባቢውና ከሌሎችም የዕውቀት ምንጮች የሚያገኘው ጥበብ ነው፡፡ የሰውነት ግንባታ የሚባለው ደግሞ በምግብና በእንቅስቃሴ የሚያበለጽገውን አካል ነው፡፡
እነዚህ ነገሮች የሚመጡትና የሚከናወኑት በሂደት ውስጥ በመሆኑ ሰዎች ለተለያዩ የኑሮ ደረጃዎች የሚበቁበት ጊዜ ይለያያል፡፡ በልጅነት፣ በወጣትነት፣ በዐዋቂነትና በአረጋዊነት ጊዜ የሚከናወኑት ተግባራት በዚያው በየዘመናቸው እንዲከናወኑ የሚያስገድዱት ሰዎች እነዚህን ነገሮች ለማከናወን የብስለታቸው ደረጃ እንደ ዕድሜያቸውና በዚያ ዕድሜ የተነሣ እንደሚያገኙት ልምድና ዕውቀት ብሎም አካላዊ ዝግጁነት ስለሚለያይ ነው፡፡ የልጆች ጋብቻንና የልጅነት ጊዜ ወሊድን የምንቃወመው፣ ጋብቻም ሆነ ወላጅነት የሚፈልጓቸው የመንፈስ፣ የአካል፣ የስሜትና የአእምሮ የዕድገት ደረጃዎች ስላሉ ነው፡፡

የመንፈስ ዕድገት የምንለው በመንፈሳዊው ዓለም ሰው የሚኖረው ዕድገትና ለውጥ ነው፡፡ በእምነት፣ በአመለካከት፣ በመርሕና በአተያይ የሚኖረው የብስለት ደረጃ፡፡ የስሜት ዕድገት ለነገሮች የሚኖረንን ፍቅርና ጥላቻ፣ ቀረቤታና ርቀት፣ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ስበትና ግፊት የምንለካበት የዐቅም መጠን ማደግ ነው፡፡ እነዚህን ነገሮች ለመቆጣጠር፣  ሕጋዊ፣ ሰላማዊ፣ ትክክልና ተገቢ በሆነው መንገድ ለመምራት ያለን ዐቅም ማለት ነው፡፡ የአእምሮ ዕድገት ስንል ደግሞ በዕውቀት ማደግን ነው፡፡
በትምህርት፣በልምድና በሰውነት ግንባታ እያደገና እየተለወጠ የሚሄደው ሰው፣ ሕይወቱ ተከታትለው በሚመጡ ሦስ ነገሮች  የሚዘወር ነው፡፡ ዐሉላ ጥላሁን ‹‹የሕይወት ሙሻዙር›› ይለዋል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ጉጉት፣ ተጋድሎና ስኬት ይባላሉ፡፡ በሰው ሕይወት ውስጥ የሚያጓጓ፣ ይደረስበታል ተብሎ የሚታሰብ፣ የሚናፈቅና ተስፋ የሚደረግ ነገር ከሌለ ተጋድሎ የሚባለው የሕይወት ዋነኛ አጣፋጭ፣ ሰውንም ወደ ሙሉ ሰውነት የሚያደርሰው ታላቁ ድልድይ ተሰብሯል ማለት ነው፡፡ እርሱ ከተሰበረ ደግሞ ስኬት የሚባለው  ነገር አይታሰብም፡፡ በዓለማችን ላይ ከፍተኛ ሥልጣኔ የተመዘገበባቸው ሀገሮችና ዘመናትን ታሪክ ብናጠና እነዚህ ሦስቱ ነገሮች ገንዘባቸው የነበሩ መሪዎችን፣ ሊቃውንትንና ሕዝቦችን እናገኛለን፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በኋላ ቀርነት ይሰቃዩ የነበሩና አሁንም የሚሰቃዩትን ሕዝቦች ስናይም እነዚህ ነገሮች ሲያጥሯቸው እናስተውላለን፡፡
ሰው ይህንን የሕይወት ሙሻዙር ዘውሮ ሕይወቱን ወደ ልዕልና እንዳያደርሳት የጉጉት፣ ተጋድሎና ስኬትን መሥመር የሚሰብሩ አራት ነገሮች አሉ፡፡ የመጀመሪያው ዋናን የሚያጠፋ ርዳታ ነው፡፡ ርዳታ ወይም እገዛ መልካም የሚሆነው ዓሣ ሊያሰግር የወጣውን ሰው በቀላሉ ብዙ ዓሣዎች እንዲያሰግር የሚያስችለውና እርሱም የተሻለ ማስገሪያ እንዲሠራ የሚያበቃው ዓይነት ርዳታ ከሆነ ነው፡፡ ሰውዬው ቁጭ ብሎ ዓሣ እንዲያገኝና ምንም እንዳያስብ የሚያደርገው ርዳታ ግን ርዳታ ሳይሆን ግድያ ነው፡፡ መጀመሪያ ብዙ ዓሣ ለማስገር የነበረውን ጉጉት ይገድልበታል፡፡ ቀጥሎ ያንን ጉጉት ለማሟላት እንዳይጋደል ያሰንፈዋል፡፡ በመጨረሻም ስኬት አይኖረውም፡፡ ስኬት ማለት የጥረት ውጤት ነውና፡፡ ያለ ጥረት በዱብ ዕዳ የተገኘ ነገር ሁሉ ስኬት አይደለም፡፡ ዕድል፣ ዕጣ ወይም ስጦታ ይሆናል እንጂ፡፡ ሰውን ወደ ዕድል፣ ዕጣና ስጦታ ደረጃ ማውረድ ደግሞ ከሰውነት አሳንሶ ‹መትኅተ ሰብእ መልዕልተ እንስሳት› ማድረግ ነው፡፡ ራቱን ቁርሱ ላይ እንዲበላው ማድረግ፡፡ ነገ ልታገኘው የምታስበውና የምትለፋለት አዲስ ነገር ከሌለህ ‹ነገ› ለምን ይምጣ? ‹ነገ› ስ  ከአንድ ተጨማሪ ቀን ውጭ ሌላ ምንድን ነው?
ሁለተኛው ሰባሪ አደጋ ደግሞ በወንጀል የተገመደ አቋራጭ መንገድ ነው፡፡ በስርቆት፣ በጉቦ፣ በማስመሰል፣ በሥልጣን በመባለግ፣ የሰዎችን ዕድል በማበላሸት፣ ትውልድን በመግደል፣ ሀገርን በማጥፋት፣ ወዘተ በኩል የሚገኝ አቋራጭ መንገድ፡፡ በቀላሉ ሥልጣን፣ ገንዘብ፣ ክብር፣ ስምና ዝና የሚገኝበት፡፡ ይህ መንድ ምናልባት ገንዘብ፣ ስምና ክብር፣ ሥልጣንና ዝና ያስገኝ ይሆናል፡፡ ውስጣዊ ደስታ ግን አያስገኝም፡፡ ደስታ ከስኬት የሚገኝ ነውና፡፡ ሌሎቹን ነገሮች ማስመሰል ቢቻልም ውስጥን ማስመሰል ግን አይቻለም፡፡ ደስታ ውስጣዊ ስለሆነ ነው አስመስሎ መሥራት የማይቻለው፡፡
እንዲህ ባደረገ ሰው ውስጥ የሚፈጠረው ጦርነት የትም ቦታ የማይፈጠር ነው፡፡ የሕግ መውጣት፣ የሥርዓት መለወጥ፣ የዳኝነት ሥርዓት መጠንከር፣ የሚዲያ ምርመራ መጀመር፣ የሰዎች ዕውቀት መጨመር፣ እርሱ የፈጸማቸውን ነገሮች የሚቃወሙ አሠራሮች መምጣት፣ የዓለም አስተሳሰብ እየተቀየረ መሄድ ያሳስበዋል፡፡ ያስጨንቀዋል፡፡ ለዚህም ነው እውነተኛውን ደስታ የማያገኘው፡፡ ድሮ ‹‹ከዕለታት አንድ ቀን›› የሚለው መግቢያ ለተረት የሚያገለግል ነበረ፡፡ ዛሬ ዛሬ ግን ለሰዎችም ያገለግል ጀምሯል፡፡ ‹‹ከዕለታት አንድ ቀን እገሌ ድንገት ኢንቨስተር ሆነ፣ ድንገት ባለ ሀብት ሆነ፣ ድንገት ባለ ዘጠኝ ፎቅ ሆነ፣ ድንገት ባለ ሥልጣን ሆነ፣ ድንገት ባለ ኩባንያ ሆነ፣›› ከየት ተነሥቶ፣ በየት በኩል ሄዶ፣ ምንም አድርጎ? መልስ የለም፡፡ ‹‹እንዴው ከዕለታት በአንድ ቀን›› ነው መልሱ፡፡ በዚህ መንድ የሚመጡ ሰዎች ስኬታማ አይደሉምና ደስተኛም አይደሉም፡፡ ደስተኛ ግን ይመስላሉ፡፡ ራታቸውን ቁርሳቸው ላይ ስለበሉት ምንጊዜም የራት ነገር ሲያሳስባቸው ይኖራል፡፡ ራት ያልበላ ሰው የሚተኛውን የረሃብ ዕንቅልፍ ስለሚተኙ፤ አልጋ እንጂ ዕንቅልፍ አይኖራቸውም፡፡ ቅዠት እንጂ ሕልም አይታያቸውም፡፡
ሦስተኛው ሰባሪ አደጋ ዕድል፣ አጋጣሚና የተመቻቸ ሁኔታ የሚፈጥሩት ግሽበት ነው፡፡ የማስተማሪያ ዐቅምና ዕድል ስላገኘን ብቻ ልጃችንን ያለ ዕድሜው ወደ ትምህርት ቤት ብንልከው ልጁ እየተማረረ እንጂ እየተማረ አይመጣም፡፡ በኋላም ከፍ ሲል ትምህርት ጠል ከሚሆንባቸው ምክንያቶች አንዱ ያለ ዕድሜ ወደ ትምህርት ቤት መግባትና መደበኛ ትምህርት መጀመር ናቸው፡፡ ዕድልና አጋጣሚ አገጣጥሞላቸው ያለ ከዕድሜና ከዕውቀት በፊት ገንዘብ ማግኘት ያቻሉ አንዳንድ ሰዎች ገንዘቡ መጥፊያቸው ሲሆን አይተናል፡፡ አካባቢያቸውን ለማስተዳደር መጀመር ባለባቸው ጊዜ አገር ማስተዳደር የሚጀምሩ፣ ቤተሰባቸውን መምራት ከመጀመራቸው በፊት የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት መምራት የጀመሩ ሰዎች ዕድሉን ለስኬት ከመጠቅም ይልቅ ሀገር ለማጥፋት የሚጠቀሙበት በዚህ ስኬት ሰባሪ አደጋ የተነሣ ነው፡፡ ራታቸውን ቁርስ ላይ በልተውት፡፡ 
ዛሬ ዛሬ በጋብቻ ውስጥ ብቻ ሊደረጉ የሚገባቸው ነገሮች ከጋብቻ በፊት፣ በበሳል ዕድሜ ሊፈጸሙ የሚገባቸው ጾታዊ ግንኙነቶች በሚዲያ፣ በፊልም፣ በማኅበራዊ ድረ ገጾችና በአንዳንድ አቀንቃኞች ምክንያት በሚፈጠሩ የስሜት መመቻቸቶች የተነሣ በልጅነት ዕድሜ እየተፈጸሙ በመምጣታቸው ሰዎች ራታቸውን ቁርስ ላይ በልተው የሚጓጉለት ነገር እንዳይኖር አድርጓቸዋል፡፡ ልጆች ተምረው ሊያገኙት የሚገባውን ነገር የድመት ፍቅር በያዛቸው ወላጆች ምክንያት ሳይማሩ ስለሚያገኙት ለትምህርት ሊያውሉት የሚያስፈልግ ጉጉትና ጥረት ተሟጥጦባቸዋል፡፡ በምዕራቡ ዓለም ታላላቅ ሰዎች ልጆቻቸውን በኩባንያቸውና በፖለቲካ መሥመራቸው መተካት የቻሉት፣ ልጆቹ መሥመሩን ተከትለው በመጋደል መሥመሩ የሚያስገኝላቸውን እያገኙ እንዲያድጉ በማድረጋቸው ነው፡፡ የአባታቸው ሀብት ስለሆነ ብቻ አያገኙትም፤ ተምረው፣ ሠርተው፣ ከሌሎቹ ጋር ተወዳድረው፣ ከታች እስከ ላይ ያለውን የዕድገት መሰላል በመንፈስ፣ በትምህርት፣ በልምድና በአካላዊ ዕድገት እየዳበሩ አልፈው፣ በተወዳዳሪነትና በአሸናፊነት ተጋድሎ ተፈትነው ሲደርሱ፤ ያን ጊዜ ወላጆቻቸው ‹ተቀመጥ በወንበሬ፣ ተናገር በከንፈሬ› ብለው ያስረክቧቸዋል፡፡ ሳንቲሞች እንዴት እንደመጡ ሳያውቁ ብሮችን አያስነኳቸውም፡፡ ነገ ሊደርሱበት የሚገባውን ራት ዛሬ በቁርስ ሰዓት አያበሏቸውም፡፡ ልጅ ምንም ያህል ቢፈለግ በሦስት ወር ይወለድ አይባልምና፡፡
አራተኛው ሰባሪ አደጋ የሚመጣው በጋሸበ አድናቆትና ግፊት ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከሰዎች የሚሰጠንን አስተያየት፣ ድጋፍ፣ ተቃውሞ፣ ክብር፣ ዝና፣ ስምና ታላቅነት ከውስጣችን ዐቅም ጋር መዝነን ካላስተናገድነው አደጋ ያስከትላል፡፡ ሰዎች ትችላላችሁ፣ ያለ እናንተ ሰው የለንም፣ ጀግና ናችሁ፣ ስላሉን ያሉንን ሁሉ አንሆንም፡፡ ጭብጨባውን፣ ሙገሳውን፣ አድናቆቱን ለችሎታ መመዘኛነት ከወሰድነው ከራሳችን ጋር እንጣላለን፡፡ ቀስ በቀስ በዕድገትና በልምድ፣ በትምህርትና በተጋድሎ ልንደርስበት የሚገባንን ገፋፍተው ሲያወጡን ከተቀበልንና ‹ሕዝብ ከመረጠኝ፣ ሕዝብ ካለ፣ ሕዝቡ ከደገፈኝ› ካልን ራታችንን ቁርስ ላይ ያስበሉናል፡፡ እላይ ከወጣን በኋላም የምናደርገው ይጠፋናል፡፡ በውጫዊ ግፊትና አድናቆት ‹ነህ› የሚሉንን ከመቀበል በውስጣዊ ዕውቀት ‹አይደለህም› የሚለንን መቀበሉ ያዋጣናል፡፡ ዛሬ ዓለምን ለበሽታ የዳረጓት ዕንቁላል ሳይሆኑ ዶሮ የሆኑት ናቸው፡፡
ሰው በሂደት የሚሟላ ፍጡር ነው፡፡ የሚያሟሉትም ትምህርት፣ ልምድና የሰውነት ግንባታ ናቸው፡፡ እነዚህ ደግሞ የሚፈጸሙት በጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ አንድን ነገር ዕድል ስላገኘን፣ ነገሮች ስለተመቻቹ፣ አቋራጭ መንገድ ስላለው፤ በአድናቆትም ሆነ በተቃውሞ ስለተገፋፋን፣ ጊዜ የሰጠው ቅል ስለሆንን ወይም ደግሞ በምናያቸው ፊልሞች፣ በምናነባቸው ስሜት ቀስቃሽ ጽሑፎች፣ ከጓደኞቻችን በሚፈጠሩብን ግፊቶች ተስበንና ተገፍተን ራታችንን ቁርስ ላይ መብላት የለብንም፡፡ ጉጉት የሌለው ነገ፣ የማይጋደሉበትም ሕይወት ስኬትን አያመጣምና፡፡ ስኬትን የማያጣጥም ሰውነት ደግሞ ምንጊዜም ውስጡ ክፍተት ይኖረዋል፡፡ ያ ክፍተት ነው ተስፋ መቁረጥን፣ ትካዜን፣ ራስን መጥላትን፣ የበታችነትን፣ ወራዳነትንና ራስን መጥፋትን የሚፈጥረው፡፡   

ባለፈው ሣምንት ውስጥ የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ትብብር ተቋሙ ኢጋድ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሮችና ባለሙያዎች አዲስ አበባ ላይ ተሰብስበው ኢቦላ ተከስቶ በነበረባቸው አካባቢዎችና ዓመታት የነበረውን ልምድ መነሻ በማድረግ ሊደረግ በሚገባው ጥንቃቄና ዝግጅት ላይ ተነጋግረዋል፡፡

በስብሰባው ላይ ጥናታዊ ፅሁፎችን ካቀረቡት ባለሙያዎች መካከል የሕክምናና የኅብረተሰብ ጤና አጠባበቅ ባለሙያው፣ በኢትዮጵያና በሌሎችም የአፍሪካ ሃገሮች የበሽታዎች ሥርጭትና ቁጥጥር ላይ የሠሩት ዶ/ር አያና የኔአባት ይገኙበታል፡፡

እስክንድር ፍሬው አነጋግሯቸዋል፤ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡


ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
——-
አንዳንዶች “ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ትጠላላችሁ፤ በነቢዩ ላይ ሰለዋት አታወርዱም” ይሉናል፡፡ ሐቁ ግን የተገላቢጦሽ ነው፡፡ በነቢዩ ላይ ሰላምና ሰለዋት በማውረድ ከኛ የሚቀድም ማን ነው? እንዲያውም የነቢዩን ታላቅ ደረጃ በዜማ እየዘከርን እና ገድላቸውን እየተረክን ነው በርሳቸው ላይ ሰላምና ሰለዋት የምናወርደው:: ይህንን እውነታ ያስረዳልን ዘንድ የሱፊ ሼኾቻችን ትተውልን ያለፉትን አንድ “ነሺዳ” (የነቢዩ ውዳሴ”) እንጋብዛችሁ፡፡
  *****  *****  *****
    ነሺዳው መጠሪያ “አሕመድ ያ ሐቢቢ” ይሰኛል፡፡ “አሕመድ ወዳጄ ሆይ” እንደማለት ነው፡፡ እኛ ስናሰፋው “ አሕመድ የልቤ ወዳጅ”፤ “አሕመድ የነፍሴ ስር” ልንለው እንችላለን፡ (“አሕመድ” የነቢዩ ሙሐመድ -ሰ.ዐ.ወ- ሁለተኛ ስም ነው፡፡ ነቢዩ በመጨረሻው ቀን/የውመል ቂያማ የሚጠሩት አሕመድ በተሰኘው ስማቸው ነው)፡፡
    
   ይህንን “ነሺዳ” ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት በ1995 ዓ.ል. ይመስለኛል፡፡ ነሺዳውን በህብረት ሲዘምሩ የነበሩት መሰረቱን በኦምዱርማን ከተማ ባደረገውና “ፊርቀቱ-ሳሕዋ” በሚባለው ዝነኛ የሱዳን የነሺዳ ቡድን የታቀፉት ስድስት ወጣቶች ነበሩ፡፡ የቡድኑ አባላት የሚያዜሙት በአብዛኛው በታዋቂው ሼኽ ዐብዱረሒም አል-ቡረኢ የተጻፉትንና “መዲሕ” የሚባሉትን የነቢዩን ግጥማዊ መወድሶች በመሆኑ “አሕመድ ያ ሐቢቢ”ም የሼኽ አል-ቡረኢ ድርሰት ይመስለኝ ነበር፡፡ በ2001 ወደ ሀረር ከመጣሁ ወዲህ ግን “አሕመድ ያ ሐቢቢ” በአንድ ዘመንና በአንድ ስፍራ ያልተገደበ ውዳሴ እንደሆነ ለማወቅ ችያለሁ፡፡ ለዚህ ያበቃኝ ደግሞ በቀድሞ ዘመናት የተጻፈ አንድ “የመዲህ” ኪታብ (መጽሐፍ) በሀረር ለማየት መታደሌ ነው፡፡
     በርግጥም “የፊርቀቱ ሳሕዋ” ወጣቶች የሚዘምሩት “አሕመድ ያ ሐቢቢ” እና ከሀረር ያገኘሁት “አሕመድ ያ ሐቢቢ” አንድ መሰረት ያላቸው መሆኑን ከግጥሞቹ አሰካክ ለመረዳት ይቻላል፡፡ ሆኖም በመካከላቸው መጠነኛ ልዩነቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ሱዳናዊያኑ ወጣቶች “አሕመድ ያ ሐቢቢ” በሚል ሐረግ የሚጀምረውን ባለሁለት መስመር ግጥም እንደ አዝማች አድርገው ይደጋግሙታል፡፡ የሀረሩ “አሕመድ ያ ሐቢቢ” ግን አዝማች የለውም፤ በዚህኛው ስልት “አሕመድ ያ ሐቢቢ” የሚለው ሐረግ አንድ ጊዜ ከታየ በኋላ አይደገምም፡፡ በሁለተኛ ደረጃም ሁለቱ የ“አሕመድ ያ ሐቢቢ” ስልቶች በግጥሞቻቸው ብዛት ይለያያሉ፡፡ የሀረሩ ስልት በኦምዱርማኑ ስልት ውስጥ የሌሉ ግጥሞቹ አሉት፡፡ በመሆኑም በግጥሞቹ ብዛት ከኦምዱርማኑ ስልት ይበልጣል፡፡
  
   የሀረሩ ስልት በትርፍነት ከያዛቸው ግጥሞች ውጪ ባሉት ግጥሞቹ ከኦምዱርማኑ ስልት ጋር የመመሳሰል ነገር ይታይበታል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን በሁለቱ ስልቶች ያሉት ግጥሞች መቶ በመቶ የሚመሳሰሉበት ሁኔታ የለም፡፡ ግጥሞቹ አንዳንዴ በሁለት ስንኞቻቸው ብቻ ይመሳሰሉና በሶስተኛው ስንኝ ይለያያሉ፡፡ ሲያሻቸው ደግሞ በተመሳሳይ ሁኔታ እየተጓዙ በቃላት ደረጃ ይለያያሉ፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ሁሉም ስንኞች እኩል ርዝመት ነው ያላቸው፡፡ ሁላቸውም “ሰላም ዓለይከ” በሚል ሐረግ የሚጀምሩ መሆናቸው ደግሞ የነሺዳው ኪናዊ ውበት ምንጭ ሆኗል፡፡
 
   በዚህ መጣጥፍ የምጋብዛችሁ የኦምዱርማኑን “አሕመድ ያ ሐቢቢ” ነው፡፡ ከኔ ጋር ነሺዳውን በ“ፊርቀቱ ሳሕዋ” ዜማ ለመዘመር ተዘጋጁ! ዳይ!!!
(ዐረብኛውን ወደ አማርኛ መተርጎም ይከብዳል፡፡ ስለዚህ እንዳለ ልተተው ተገድጃለሁ)፡፡
  *****  *****  *****
አሕመድ ያ ሐቢቢ ሰላም ዓለይከ
ያ ሚስኪ ወጢቢ ሰላም ዓለይከ
ሰላም ዓለይከ ዜይነል አንቢያኢ
ሰላም ዓሌይከ አትቀል አትቂያኢ
ሰላም ዓለይከ አስፉል አስፊያኢ
ሰላም አለይከ ሚን ረብቢ-ሰማኢ
ሰላም ዓለይከ ዳኢመን ቢላ ኢንቲሃኢ
ሰላም ዓለይከ
—-
ሰላም ዐለል ሙቀደም ሊል ኢማማ
ሰላም ዐለል ሙዘለል ቢል ጘማማ
ሰላም ዐለል ሙዘወጅ ሊል ከራማ
ሰላም ዐለል ሙሰቢህ ሊል ሰላማ
ሰላም ዐለል ኹላሳ ሚን ቱሐማ
ሰላም ዐለል ሙሸፍፊዕ ቢልቂያማ
ሰላም ዓለይከ
—–
ሰላም ዐለይከ ጣሃ ያ ሐቢቢ
ሰላም ዐለይከ ያ ሚስኪ ወጢቢ
ሰላም ዐለይከ ያ -ማሂ ዙኑቢ
ሰላም ዐለይከ ያ ጃሊል ኩሩቢ
ሰላም ዓለይከ
 —–
ሰላም ዐለይከ ያ ኸይረል አናሚ
ሰላም ዐለይከ ያ በድረ ተማሚ
ሰላም ዐለይከ ያ ኑረል ዘላሚ
ሰላም ዐለይከ ያ ኩለል ጉራም
ሰላም ዐለይከ
—-
ሰላም ዐለይከ ያ ዘል ሙእጂዛቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ዘል በይናቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ሐቢቡ ዛቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ሐሱነ-ስ-ሲፋቲ
ሰላም ዐለይከ ያ ዙኽረል ዑሳቲ
ሰላም ዐለይከ
—-
ሰላም ዐለይከ አሕመድ ያ ሙሐመድ
ሰላም ዐለይከ ያ ጣሃ ያ ሙመጀድ
ሰላም ዐለይከ ዘል መንተፈረጅ
ሰላም ዐለይከ
ሰላም ዐለይከ ያ ሩክነ-ሰላሂ
ሰላም ዐለይከ ያ ዘይነል ኢላሂ
ሰላም ዐለይከ ያ ዳኢል ፈላሒ
ሰላም ዐለይከ
አሕመድ ያ ሐቢቢ ሰላም ዓለይከ
ያ ሚስኪ ወጢቢ ሰላም ዓለይከ
  *****  *****  *****
አፈንዲ ሙተቂ
ሸገር- አዲስ አበባ
ጥቅምት 2/2006

በዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር ላይ የተወሰደውን እርምጃ ተከትሎ አንድነት ፓርቲ መግለጫ አወጣ፡፡ አንድነት በመግለጫው በትብብሩ አመራሮችና አባላት ላይ የተወሰደውን እርምጃ አውግዟል፡፡ ፓርቲው በዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር አመራሮችና አባላት ላይ የተወሰደውን ህገ-ወጥ እርምጃ ተከትሎ አስፈላጊውን መረጃዎች ካሰባሰበ በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡ ሙሉውን መግለጫ ከታች ተመልከቱ፡፡ በዘጠኙ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይ የተወሰደውን ህገወጥ እርምጃ እናወግዛለን! አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት ሰላማዊ […]

ኀዳር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ስደትን የህይወታቸው የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ በጅቡቲ በኩል አድርገው ወደ የመን ለመግባት የሞከሩ 70 ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር ላይ ሰጥመው መሞታቸውን የየመን ባለስልጣናት ገልጸዋል። ታይዝ በምትባለዋ ግዛት የሚገኙ ባለስልጣናት ለአሶሴትድ ፕሬስ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያውያኑን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረችው ጀልባ ባጋጠማት ከባድ አውሎ ንፋስና ማእበል አል ማክታ እየተባለ ከሚጠራው ወደብ ራቅ ብሎ …

ኀዳር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የምርጫ ስርዓት ለውጥ እንዲደረግ ለመጠየቅ ህዳር 27 ቀን የአዳር ተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ወደ አደባባይ በወጡት 9 የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ላይ የፌደራል ፖሊስ አባላት ድብደባ በመፈጸም ወደ እስር ቤት ቢወስዱዋቸውም፣ የትብብሩ አመራሮች ግን ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ኢትዮጵያውያን ለትግሉ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። ሶስተኛ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት …