እስካሁን አስራ-አንዱ ለሞት፥ ቁጥራቸዉ በዉል ያልታወቀ ሌሎችን ለበሽታ እና የተቀሩትን በሙሉ ለስቃይ የዳረገዉ ችግር የሚወገድበት ብልሐት አሁንም ግልፅ አይደለም። የስዑዲ አረቢያ ፀጥታ አስከባሪዎች ወደ ሐገራቸዉ ለመመለስ ካሰሯቸዉ ኢትዮጵያዉያን መካካል ጂዘን ዉስጥ አምስቱ ከነሱ በፊት ጂዳ ዉስጥ ደግሞ ሌሎች ስድስት መሞታቸዉ …

የኢትዮጵያውን ሥደተኞች ሞት በሳውዲ አረቢያ Read more »

(DW) — «ሜራፒ» ከፈነዳ፤ በረጅሙ ታሪክ እጅግ በዛ ያሉ የአሳተ ገሞራ ፍንዳታዎች አጋጥመዋል፣ የነፋሱ አቅጣጫ ትክክል ነው፤ እናም፤ በኢንዶኔሺያም ሆነ እስያ ውስጥ በእሳተ ገሞራ አካባቢዎች፤ እዚህ መሃል አውሮፓ የታየው ዓይነት መዘዝ ነው የሚኖረው።» ባለፈው ሚያዝያ፤ በአይስላንድ የፈነዳው እሳተ-ገሞራ የአየር በረራን …

«ኔብራ ስካይ ዲሽ» እና እሳተ ገሞራዎች Read more »

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ለ2003 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን አዲስ ተማሪዎችን ለመቀበል የሚወጣ ማንኛውንም ማስታወቂያ በቴሌቪዥን፣ በሬድዮ ወይንም በጋዜጣ እንዳይተላለፍ ከለከለ፡፡

– ባለአራትና ባለአምስት ኮከብ ሆቴሎች ይገነባሉ – የሄሊኮፕተር ማረፊያ ይኖዋል– ግንባታው በሦስት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል– መንግሥት የ20 በመቶ ድርሻ አለው – ዓለም አቀፉ ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴሉን ያስተዳድራል – ሆቴሉ  ለፕሬዚዳንቶች ልዩ ማረፊያዎች ይኖሩታል (በኃይሌ ሙሉ) አክሊለ ብርሃን መኮንን ኃይለ …

ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ግዮን ሆቴልን በሰባት ቢሊዮን ብር ሊገነቡ ነው Read more »

– የአንድ ዶላር መመንዘሪያ የመነሻ ዋጋ ብር 16.35 ሆነ (በጋዜጣው ሪፖርተር) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዛሬ ጀምሮ አንድ የአሜሪካ ዶላር በ16.3514 ብር ግዢ፣ በ16.6784 ሽያጭ እንዲመነዘር መመሪያ አወጣ፡፡ የምንዛሪ ለውጡ የብር የመግዛት አቅምን (ከሌሎች ገንዘቦች አንጻር) ከ22 በመቶ በላይ ያወርዳል፡፡

– ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አውጥቷል (በታምሩ ጽጌ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በአገልግሎት ላይ የሚገኘውን ባለ አንድ ብር የወረቀት ገንዘብ ለመተካት ያሠራቸውን ባለ አንድ ብር ሣንቲሞች ለመንግሥትና ለግል ንግድ ባንኮች ነሐሴ 19 እና 21 ቀን 2002 ዓ.ም. ማሠራጨቱን ምንጮች ለሪፖርተር …

ብሔራዊ ባንክ ያሠራቸውን ባለ አንድ ብር ሣንቲሞች ለንግድ ባንኮች አሠራጨ Read more »

– ‹‹መንግሥት ከዚህ በኋላ ምንም ዓይነት የይቅርታ ጥያቄ አይቀበልም›› አቶ ታደለ ይመር (በብርሃኑ ፈቃደ) የኢትዮጵያ አሠሪዎች ፌዴሬሽን 10 ያህል ሆቴሎች ከቀረጥ ነፃ የገቡ ዕቃዎችን ያለ ፈቃድ በመሸጥ፣ ታክስ ባለመክፈልና ለሌላ ተግባር በማዋላቸው በወንጀል እንደሚጠየቁና ክስ እንደሚመሠረትባቸው ቢታወቅም፣ በሆቴሎቹ ስም ፌዴሬሽኑ …

አሠሪዎች ፌዴሬሽን በሆቴሎች ስም መንግሥትን ይቅርታ ጠየቀ Read more »

. ዕቃዎች በማዕከል ተገዝተው ለግል ተቋራጮች ይቀርባሉ. የመንግሥት የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ ይገባሉ. 80 አዳዲስ የግል ሥራ ተቋራጮች ሥራ ያገኛሉ (በውድነህ ዘነበ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የግንባታ ዋጋ ንረት ለመቆጣጠር ያስችለኛል ያለውን አዲስ የዋጋ ንረት መቆጣጠርያ ዕቅድ አዘጋጀ፡፡

– የመተዳደሪያና የሥነ ምግባር ደንብ አርቅቀዋል (በታምሩ ጽጌ) የኦሮሞ ብሔራዊ ኮንግረስ (ኦብኮ)፣ የመላው ኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ንቅናቄ (መኢብን)፣ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ንቅናቄ (ኢዴአን) እና የመላው ኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኦህዴፓ) ከነሐሴ 25 ቀን 2002 ዓ.ም. ጀምሮ በጥምረት ለመንቀሳቀስ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን …

ኦብኮ፣ መኢብን፣ ኢዴአንና መኦህዴፓ ጥምረት ለመፍጠር ተስማሙ Read more »

የአፋርንና የሰሜን ሱማሌን ክልልች የሚያዋስኑትን የአማራ ቆላማ ስፍራዎችን ጨምሮ፣ በአገሪቱ ዉስጥ ባለፉት ጥቂት ቀናት አዳዲስ የጎርፍ ማጥለቅለቅ መድረሱን በተባበሩት መንግስታት ድር፡ጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታዉቋል። በሰሜን ወሎ ዞን ባለፈዉ ነሃሴ 16 የጣለዉ ዝናብ ያስከተለዉ መሬት መንሸራተት የ19 ሰዎችን …

በኢትዮጵያ ሰሜን ወሎ 19 ሰዎች በጎርፍ አደጋ ሞቱ 24 ቆሰሉ Read more »

የሎስ አንጀለስ ቅድስት ሥላሴ ወገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን  ሰበካ ጉባኤ ይህንን ዌብሳይት (http://www.kidistselassie.org) የዕለት ከዕለት የሰበካ ጉባኤ እንቅቃሴ እንድንዘግብበት ጥያቄ ሰላቀረበልን  ከዛሬ ጀምሮ አብነት ትምህርት ቤታችንን  “ደበሎ”  በሚል ስያሜ፤ http://debelo.org በማለት የቀየርነው መሆኑን ተጠቃሚዎቻችን እንዲያውቁት ስንገልጽ ይህ አጋጣሚ ግን የአብነት …

ማስታወቂያ፦ የድረ ገጽ አድራሻ ለውጥ Read more »

የሁለት ሺህ ሶስት አዲስ የትምህርት ዓመት በተቃረበበት ባሁኑ ሰዓት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የሚመለከተው መመሪያ መነጋጋሪ ሆኗል። የውሳኔው ተቃሚዎች ርምጃው የተማሪዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እንደሚቀንስ ሲናገሩ መንግሥት ከቁጥር ይልቅ ለጥራት ቅድሚያ ለመስጠት ተብሎ ነው ብሏል ። ሁለት ሳምንት ከቀሩት አዲስ ዓመት …

በኢትዮጲያ የርቀት ትምህርት ተከለከለ Read more »

(DW) — ወደ ኢራቅ በመዝመት በዚያ ሠፍሮ የቆየው የአሜሪካ ጦር ኃይል አገሪቱን ለቆ በመዉጣት ላይ ነዉ። ከተዋጊው ጦር ኃይል የመጨረሻው ክፍል፤ እስከዛሬ በተሰጠው የመጨረሻ የጊዜ ሰሌዳ አብዛኛው በዚህ ወር መዉጣቱ ተመልክቶአል። ቀሪዉ 50 ሺህ ወታደር ደግሞ ከመስከረም ወር ጀምሮ ለኢራቅ …

የዩናይትድ እስቴትስ ተዋጊ ጦር ከኢራቅ ነቅሎ መውጣቱ Read more »

(DW) — ትናንት እዚህ ጀርመን ገበያ ላይ የዋለው የጀርመን ቡንደስ ባንክ የቦርድ አባል የቲሎ ዛራትሲን መጽሐፍ ጀርመን ውስጥ አሁንም የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ እንደቀጠለ ነው። ጀርመን ራሷን ለውደቅት እየዳረገች ነው” የሚል ሀሳብ የያዘው የዚህ መፀሀፍ ደራሲ የእስልምና ባሕል ጀርመን የሚኖሩ ሙስሊሞች …

አወዛጋቢው የዛራትሲን መጽሐፍ Read more »

(DW) — በሰሜን ምዕራብ ኢትዮዽያ በአማራ ዝቅተኛ በሆኑ አከባቢዎች እየጣለ ባለው ዝናብ የተነሳ በደረሰው የ ጎርፍ አደጋ ህይወትና ንብረት ጠፍቷል። ዝናቡ በዚሁ ከቀጠለ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ኢትዮዽያዊ አደጋ ውስጥ ይገባል። የክረምቱ ዝናብ ህይወት እያጠፋ፤ ንብረት እያወደመ ነው። ባለፈው ሳምንት በደረሰው …

በጎርፍ ሳቢያ ግማሽ ሚሊዮን ኢትዮዽያዊ አደጋ ውስጥ ነው Read more »

(ደጀ ሰላም፤ ኦገስት 31/2010፤ ነሐሴ 25/2002 ዓ.ም)፦ ምእመናን ስለ ቤተ ክርስቲያናቸው ወቅታዊ ሁናቴ የሚያውቁባቸው አዳዲስ የጡመራ መድረኮች በየጊዜ እየተመለከትን ነው። ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ላለፉት አራት ወራት ግሩም ግሩም ጽሑፎችን እና የመወያያ ነጥቦችን እያነሣ ሲሆን ሌላው ሰባኬ ወንጌል ቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅንም …

አዲስ የጡመራ መድረክ (ብሎግ) በቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅን Read more »

«መድበለ ፓርቲ ከ2002ቱ ምርጫ በኋላ አብቅቶለታል፤» የሚሉ ወገኖች «ኢትዮጵያ ወደ አንድ ብቸኛ ፓርቲ አገርነት እያመራች ነው፤» ሲሉ፤ ይሄን የሚከራከሩት ደግሞ «ሊባል የሚችለው፤ ኢትዮጵያ አብላጫ ድምፅ ባገኘ ጉልህ ፓርቲ እየተመራች ነው፤» ይላሉ። «የአንድ ፓርቲ በተቀባይነት ጎልቶ መውጣት ወይስ የአንድ ፓርቲ ብቸኛ …

የመድብለ ፓርቲ ዕጣ በኢትዮጵያ! Read more »

በቫንኩቨር ካናዳ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው የኢትዮጵያ የክረምት ፌስቲቫል ከአሁን ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በፖለቲካ በሀይማኖትና በተለያዩ የማህበራዊ ችግሮች ምክንያት ተራርቆ የነበረው ነዋሪ በሙሉ በአንድ ላይ በመሰባሰብ በደማቅ ሁኔታ መከበሩ ታወቀ። በፌስቲቫሉ ላይ የቫንኩቨር ነዋሪዎችን ጨምሮ ከአምስት ሺህ በላይ ከሲያትልና ከካልጋሪ …

በቫንኩቨር የኢትዮጵያዊያን የክርምት ፌስቲቫል ደምቃ ዋለች Read more »

በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ካናዳዊያንና አሜሪካዊያን ተገኝተው ነበር “ብርቱካን መፈታት አለባት” የካናዳ ፓርላማ ተመራጭ ሚስተር ፒተር ጁሊያን በቫንኩቨር ካናዳ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው የኢትዮጵያ የክረምት ፌስቲቫል ከአሁን ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በፖለቲካ በሀይማኖትና በተለያዩ የማህበራዊ ችግሮች ምክንያት ተራርቆ የነበረው ነዋሪ በሙሉ በአንድ …

ቫንኩቨር በመጀመሪያው የኢትዮጵያዊያን የበጋ ፌስቲቫል ደምቃ ዋለች Read more »

በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ ጎርፍ መከሰቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ። በአካባቢው የሚገኝ የሁለተኛ ድረጃ ትምህርት ቤት ክፉኛ በጎርፍ መመታቱን ቦሩ ሮባ የተባሉ የፈንታሌ ወረዳ ነዋሪ ለቮኦኤ ገልጸዋል። “የደረሰው ጉዳት በጣም ከባድ ነው። ጉዲና ቱምሳ GTS የተባለ ሃይስኩል (ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት) …

በኦሮሚያ ክልል የፈንታሌ ወረዳ ነዋሪዎች በጎርፍ ተጠቃን ይላሉ፤ አስተዳደሩ ጉዳቱ መጠነኛ ነው ብሏል Read more »

«ሩባያት፤» እና «ሃይኩ፤» የተባሉትን የሥነ ግጥም ዘይቤዎች የተከተሉትን መፅሃፎቹን ጨምሮ «ግራፊቲ፤» በሚል ርዕስ ካሳተማት ሌላ መፅሃፍ ጋር ሦሥት የግጥም መድብሎች ለንባብ አብቅቷል። ዓለማየሁ ታዬ ይባላል። ለበርካታ ዓመታት በራዲዮና በህትመት ጋዜጠኝነትም ሠርቷል። በግጥም ሥራዎቹ፥ በህይወትና ስነ ፅሁፍ ዙሪያ ከአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ …

የዓለማየሁ ሩባያት፤ ሃይኩ፤ እና ግራፊቲ Read more »

በኤርትራ አስተናጋጅነት የተካሄደው የምስራቅና መካከለኛዉ አፍሪቃ ከሃያ ዓመት በታች የሚገኙ ወጣቶች የእግር ኳስ ፉክክር በዑጋንዳ አሸናፊነት ተጠናቋል። የኤርትራ ቡድን የሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ ለደረጃ ከቀረቡት ኬንያ ድል ቀንቷት ሶስተኛ ሆናለች። ሳምንታዊዉ ስፖርት በአገር ዉስጥ ስፖርታዊ ዜና ጀምሮ የአዉሮጳን እግር ኳስ ዉድድር …

የዩጋንዳ ቡድን በኤርትራ የተካሄደውን የወጣቶች ዋናጫ አሸነፈ Read more »

(DW) — ለሀያሉ አለም በርግጥ ኢራቅ አይደለችም። አፍቃኒስታን፥ ፓኪስታን ልትሆን አትችልምም።ሁሉም ግን ያያታል።ግን አያስተዉላትም።ሁሉም ይሻታል ሊያድናት ግን ይፈራል።ልትድንም አትሻም። ሶማሊያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 1991 እንዳደረገዉ ሁሉ የአፍሪቃ ሕብረትም ጦር ያስ-ዘምታል።ሶማሊያም ከጎሳ ግጭት ዉጊያ አልፋ በሽብር ፍጅት ማዕበል ትላጋለች።ፕሬዝዳት ጆርጅ ሔርበርት …

ሶማሊያ ከእርስበርስ ውጊያ ወድ ሽብር Read more »

የሱዳኑ ፕሬዝደንት ኦማር ሃሰን አልበሽር በዳርፉር ግዛት የጦር ወንጀል እና የዘር ማጥፋት ፈጽመዋል በሚል ሄግ ኔዘርላንድ የሚገኘዉ አለም ዓቀፍ የጦር ወንጀለኞች መዳኛ ፍርድ ቤት ተይዘዉ እንዲሰጡት ከጠየቀ ዓመት አለፈ። አልባሽርን ግን ለህግ የሚያቀርብ የአፍሪቃ መንግስት እስካሁን አልተገኘም። እንዲያዉም በዚሁ ጉዳይ …

አልበሽር እና ዓለም ዓቀፉ የጦር ወንጀለኞች ችሎት Read more »

(ደጀ ሰላም፤ ኦገስት 29/2001፤ ነሐሴ 23/2002 ዓ.ም):- በ‹‹የሐውልቱ ሥር ቁማርተኞች›› መጽሐፍ ምክንያት በወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ፣ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ እና በጋሻው ደሳለኝ የስም ማጥፋት ወንጀል ክስ በቀረበበት ሊቀ ትጉሃን ዘሪሁን ሙላቱ ላይ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሳቢያ …

ፍርድ ቤቱ በ‹‹የሐውልቱ ሥር ቁማርተኞች›› ደራሲ ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ Read more »

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰበት፣ ከግብርናው ዘርፍ ቀጥሎ በርካታ የሰው ኃይል የተሰማራበትና በአገሪቱ ውስጥ ካሉ ሌሎች የኢኮኖሚው ዘርፎች ከፍተኛ ትኩረትን የሳበ ነው፡፡ ዘርፉ በአገሪቱ የመሠረተ ልማት እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ የሚገኝ ቢሆንም በበርካታ ችግሮች የተተበተበ ነው፡፡ ቀጣዩ ልዩ …

የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ፈተናዎችና ገመናዎች Read more »

–  የመንግሥትም ሆነ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቅድመና በድኅረ ምረቃ የርቀት ትምህርት አይሰጡም–  የሕግና የመምህራን ትምህርት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሰጠት ይቆማል –  ‹‹ሥርዓቱ ሙሉ ለሙሉ የትምህርቱን ዘርፍ የሚገድብ ነው›› ረዳት ፕሮፌሰር ወንድወሰን ታምራት– ‹‹ግብታዊ ውሳኔ ነው፤ የአቤቱታ ደብዳቤ እናስገባለን›› …

የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የወጣው መመሪያ ተቃውሞ ገጠመው Read more »

(በውድነህ ዘነበ) ቦታ ወስዳችሁ ግንባታ አላካሄዳችሁም በሚል ካርታቸው እንዲመክን የተደረገባቸው የሪል ስቴት አልሚዎች፣ ቅሬታቸውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ቢሮ ማቅረብ ጀመሩ፡፡

‹‹የ40 ዓመት ዕድሜ እያለን ስማችንን ተነጥቀናል››  (የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር)‹‹የኢትዮጵያ ጠበቆች ማኅበር የሚባል ከእኛ በፊት አልነበረም››  (የኢትዮጵያ ጠበቆች ማኅበር) ‹‹ሙያውና ስያሜው አንድ ዓይነት ያልሆነ ማኅበር ፈቃድ ሊሰጠው አይችልም››  (የኢትዮጵያ የበጎ አድራጎትና ማኅበራት ኤጀንሲ) (በብርቱካን ፈንታ) የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበርና የኢትዮጵያ …

ጠበቆች ለተመሳሳይ ዓላማ ሁለት ስያሜ ይዘው እየተወዛገቡ ነው Read more »

(በሔኖክ ያሬድ) ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የቱሪዝም ገበያ ፉክክር ውስጥ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን በሚያስችላት የቱሪዝም ፖሊሲዋ አማካይነት አሁን ያለውን የ13.5 በመቶ አማካይ የቱሪስት ፍሰትን ከ20 በመቶ በላይ ለማሳደግ መታቀዱን፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሥራ ላይ ያለው የባህል ፖሊሲንም እንደሚያሻሽለውም ገለጸ፡፡

(በኃይሌ ሙሉ) በአራዳ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ትዕዛዝ ማንኛውም ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረታቸው እንዲታገድ ለባንክ የተጻፈባቸው ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ፣ ከግብር ጋር በተያያዘ ንብረታቸው እንዲታገድ መደረጉ አግባብ አለመሆኑንና ጥሩ ግብር ከፋይ መሆናቸውን ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

– ኢንስቲትዩቱ በአምስት የአፍሪካ አገሮች ቅርንጫፉን ሊከፍት ነው (በብርቱካን ፈንታ) የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሚኒስትሩን አቶ በረከት ስምዖንን ጨምሮ ሚኒስትሮችና ባለሥልጣናት ከኢንተርናሽናል ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት በትራንስፎርሜሽናል ሊደርሽፕ ኤንድ ቼንጅ በድኅረ ምረቃ በቅርቡ እንደሚመረቁ ተገለጸ፡፡

(በትዕግሥት ዘሪሁን) ምንም ዓይነት ወንጀል ሳይፈፅሙ ‹‹የሲአይኤ ሰላይ ናችሁ፤ ፈላሾች ናችሁ፤›› በሚል ለስምንት ዓመታት ያህል ያለክስና ያለፍርድ በሊቢያ መንግሥት ታስረው የቆዩ ኢትዮጵያውያን፣ በመንግሥት ትብብር ከ10 ዓመት በፊት ወደ አገራቸው ቢመለሱም፣ እስካሁን ድረስ በኤግዚቢትነት የተያዘ ንብረታቸው አለመመለሱን፣ በይፋ ይቅርታ እንዳልተጠየቁና ያለፍርድ …

በሊቢያ ለስምንት ዓመታት በግፍ ታስረን ነበር ያሉ ዜጐች መብታችን ይከበር እያሉ ነው Read more »

– ሕንጻው በቅርቡ ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል (በኃያል ዓለማየሁ) የናኒ ሕንጻ ግንባታ ለረጅም ዓመታት በመዘግየቱ ሕንጻውን በባለቤትነት የሚገነባውን የሚድሮክ ኢትዮጵያ እህት ኩባንያ የሆነውን ሁዳ ሪል እስቴትን ከ360 ሚሊዮን ብር በላይ ሊያስወጣው መቻሉን ለፕሮጀክቱ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

‹‹ለአፈርና ለዘር ጥበቃ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል››ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር. ምግብ አምራቹ ኢንዱስትሪ ደካማና ብቃት የሌለው ተብሎ ተተቸ(በብርሃኑ ፈቃደ) የግብርና ዘርፍ የዓለምን የብዝኅ ሕይወትና የሰብል ዘር አመናምኗል ተባለ፡፡

አቡጊዳ – ነሕሴ 22 ቀን 2002 ወደ አንድ ሺህ የሚጠጉ የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ የሚገኙ በለድሃዋና ኤልዋክ የተሰኙ ከተሞች እያመሩ እንደሆነ፣ በዶሎ (ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለች ለሶማሌና ለኬንያ ቅርብ የሆነች ከተማ) ያሉ ምንጮችን በመጥቀስ አዲስ ነገር ድህረ ገጽ ዘገበ። በተጨማሪ ወደ ስድስት …

የኢትዮጵያ ወታደሮች ሶማሊያ እንደገቡ ተዘገበ Read more »

የመጨረሻው የኢትዮጵያ ንጉስ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ የመሞታቸውን መርዶ በወቅቱ ስልጣን ጨብጦ በነበረው ደርግ ይፋ የተደረገው ከ35 በፊት በዛሬዋ ዕለት ነበር ። የአፄ ኃይለ ስላሴ አሟሟት እስከ ዛሬ ድረስ እንቅልልሽ ነው። በዕርጅናም ሆነ በህመም ሳቢያ መሞታቸው ወይም በሰው እጅ ህይወታቸው ማለፉ …

የአፄ ኃይለ ስላሴ 35ኛ ሙት ዓመትና ዝካሬ Read more »

በአማራ ክልል በሰሜን ወሎ ዞን በሃብሩ ወረዳ፣ በግዳን፣ ዋድላና በራያና ቆቦ ወርዳዎች፣ በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በደቡብ ወሎና በተለያዩ አካባቢዎች ጎርፍና የመሬት መንሸራተት በሰው ሕይህወት፣ በከብቶችና በሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል። አከታትሎ በመጣል ላይ ያለው ዝናብ በአምስት ወረዳዎች 37 ሰዎችን ሲገድል …

በአማራ ክልል ከጎርፍና ከመሬት መንሸራተት ጋር በተያያዘ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 37 ደረሰ Read more »

(Ginbot7.org) — አንድን ነገር ደጋግሞ እየሠራ የተለየ ውጤት የሚጠብቅ አዕምሮው በትክክል የማይሠራ ሰው ብቻ ነው ይባላል። ወያኔ አዕምሮዓቸው በትክክል መሥራት በማይችል ሰዎች የተሞላ ድርጅት መሆኑ ድርጊቱ ይመሰክራል። ባለፉት አምሳ ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ሲደረግ የቆየው በባዶ ቁጥሮች በተነፋ እቅድ የመኩራራትን “ስልት” …

የኛ “ትራንስፎርሜሽን ፕላን” ኢትዮጵያን ከዘረኝነት ማጽዳት ነው Read more »

ከዝግጂት ክፍላችን በዘረኛውና አምባገነናዊው የወያኔ አገዛዝ ቁጥጥር ስር የምትገኘው አገራችን ኢትዮጵያ ከሰሞኑ ብዙ የድህነት ሽልማቶችን ተቀብላለች። ዴሞክራሲ እና እኩልነትን የማስፈን ጭንብሎቹ የወደቁበት ዘረኛ አገዛዝ ህልውናውን ለማስጠበቅ ሲል “ልማት ልማት” የሚለውን ዘፈን መዝፈን እና ማስዘፈን ከጀመረ እንደሰነባበተ እናውቃለን። በተለይም የምርጫ 97 …

ከአንድ ዘር የተውጣጣ የገዢ መደብ ለመፍጠር ሌት ከቀን የሚሰራው የወያኔ ቡድን ለኢትዮጵያችን መልካምን ለማድረግ አይቻለውም! Read more »

በቅርብ ቀን ይፋ የሆነው የአምባገነኑና ዘረኛው መለስ ዜናዊ የአምስት ዓመታት የልማት ግብ ርቆ የተሰቀለ ዳቦ ወይንም የህልም እንጀራ ነው እየተባለ መተቸቱን የገለጸው የቪ ኦ ኤ ው አማርኛ ክፍል በአምስት አመቱ የልማት መርኃ ግብር ዙሪያ በሀርፐር ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ መምህር የሆኑትን ዶ/ር …

የወያኔው አገዛዝ የአምስቱ አመት የኢኮኖሚ ልማት ትራንፎርሜሽን እቅድ የህልም እንጀራ ነው ሲሉ ታዋቂ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች አጣጣሉት Read more »