የኢትዮጲያ የውጭ ዕዳ ከ134 ቢሊዮን ወደ 200 ቢሊዮን ብር ማሻቀቡ ተነገረ የመንግሥት የአገር ውስጥ ዕዳ ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ነው (ሪፖርተር)
የኢትዮጵያ የውጭ ብድር ክምችት በከፍተኛ እያሻቀበ በመሄድ ላይ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት የነበረው 134 ቢሊዮን ብር ወደ 200 ቢሊዮን ብር ማደጉን መረጃዎችና የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባለሙያዎች አመለከቱ፡፡ የመንግሥት የአገር ውስጥ ዕዳም ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር መገባደጃ ላይ የአገሪቱ የውጭ ዕዳ በወቅቱ በነበረው ምንዛሪ 134 ቢሊዮን ብር መድረሱን መረጃዎቹ አመልክተው፣ […]