70ሺህ ኢትዮጵያዊያን በግዳጅ ተፈናቀሉ

አስገድዶ መድፈርና ከፍተኛ የመብት ረገጣ ተፈጽሞባቸዋል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥር 9 ቀን 2004 ዓ.ም. January 18, 2011)፦ በኢትዮጵያ ለም የሆኑ የእርሻ መሬቶችን ለኢንቨስትመንት ለመስጠት መንግስት በያዘው ፕሮግራም ሳቢያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከሚኖሩባቸው አካባቢዎች በግዳጅ እየተነሱ ለኑሮ ተስማሚ ወዳልሆኑ ቦታዎች መወሰዳቸውን ሂዩማን ራይትስ ወች አጋልጧል።