የተመድ ፀጥታ ጥበቃ ም/ቤት በኤርትራ ላይ በጎርጎሪዮሳዊው 2009 ዓም የጣለውን የጦር መሪያ ማዕቀብ ባለፈው ሳምንት እስከ እስከ ኅዳር፣2016 ዓም አራዘመ። ምክር ቤቱ የወሰደው ይህ ውሳኔ የአውሮጳ ኅብረት በስደተኞች ጎርፍ የገጠመውን ቀውስ የስደተኞች መፍለቂያ ከሆኑት ኤርትራን ከመሳሰሉ ሃገራት ጋር ባንድነት መፍትሔ ለመሻት በያዘበት ወቅት ነው።

(በብአዴን/ኢህዴን 35ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ የጻፍኩት) የህወሓት ፈተና – ‹‹የታገልኩት፣ የቆሰልኩት፣ የሞትኩትም እኔ ብቻ ነኝ እና የታሪኩ ባለቤትም የትግሉ ውጤት ይበልጥ ተጠቃሚም መኾን ያለብኝ እኔ ነኝ››። ይህ ትርክት ጫፍ ሄዶ ሄዶ ኢዲሞክራሲያዊነት እና ጠባብነት የወለደው ኾኖ ወደ ትምክህተኝነት ሊያድግ ይችላል። ኣብዛኞቹ የዚህ ፈተና ሰለባ የኾኑ የድርጅቱ ኣባሎች ብ1993ቱ የድርጅቱ የውስጥ ትግል የተሸኙ ሲኾን የነሱ ደጋፊዎች እዚሁ የማሕበረሰብ ሚዲያ ላይ የሚያሳዩት ትምክህት አሁንም አለ። ድርጅቱ የዚህ አይነቱ አዝማሚያ ዋናው ፈተናው ሲኾን በቀጣይ የቀሩ ትርፍራፊ የማጽዳት ስራዉን አጠናክሮ የማካሄድ ሓላፊነት አለበት። ይህንን ፈተና ተቋቁሞ እኩልነት በመቀበል የታገልነው በጋራ እና ለጋራ ጥቅም ነው በማለት እዚህ ለበቃ አብዛኛው አባሉን በዚህ አስተሳሰብ ዙሪያ ማሰለፍ ከቻለ ህወሓት ውጤታማ ይኾናል። ብአዴን፦ ያለፉ ስርዓቶች፣ በተለይ የአጼኣዊው የዘውድ ስርዓት፣ ናፍቆት። ይህ በእኩልነት ያለማመን የአንዳንድ የብአዴን ትልቁ ፈተና ነው። የጥንት ታሪኮች የአንድ ብሔር ይኾኑ ዘንድ የመመኘት ከዚህ በዘለለም የትምክህት ሃይሉ የሚያራምደው በአለፉት ስርአቶች የተፈጸሙ በደሎች የመካድ አዝማሚያ። ብአዴን የዚህ አይነቶቹ አባላት ሽኝቶ ብቻ ሳይኾን የተፈጠረው አዲስ የኢትዮጵያዊነት የእኩልነት ትርጉም አልጥም ብሏቸው ወደ ድሮ አመለካከታቸው በመኮብለል ብዙ አባላቶቹ እና አመራሮች ሳይቀር ከመስመሩ ወጥተዋል። አንዳንዶቹ ወደ ትክክለኛ ቀለማቸው በመሄድ ፓርቲዎች አቋቁመው ብአዴንን ዞረው ታግለዉታል። ይህንን ፈተና ተቋቁሞ የጋራ ሀገር ነው ያለን የልፉት ስርዕእቶች ሁላችንንም በድለዋል። እነዚህ ስርዓቶች ላይመለሱ በተባበረ ክንድ ተወግደዋል። ስርዓቶቹን ለማስወገድ የአማራ ብሔር ተወላጆችም አኩሪ ተጋድሎ መፈጸማቸውን ማስተማር […]

አትሌት ከላሊ ንጉሴ አብርሃ

ከላሊ ንጉሴ ይባላል፡፡ የረዥም ርቀት እና ማራቶን ሯጭ ሲሆን አሁን የሚገኘው በስደት ቶሮንቶ፣ ካናዳ ውስጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በነበረበት ወቅት ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ያሳለፈውን የህይወት ተሞክሮ በማስመልከት ከኢትዮጵ ዛሬ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፤ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ማጣርያ ግጥሚያ ለመሳተፍ ወደ ቦትስዋና በቅርብ ለሄዱት 10 የኤርትራ ብሔራዊ የእግር ኳስ ተጫዋቾች የፖለቲካ ጥገኝነት የቦትስዋና መንግስት ፈቅዶላቸው እንደነበር ይታወሳል። ስፖርተኞቹ ጥቅምት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. ከቦትስዋና ቡድን ጋር ከተጫወቱ በውኃላ ነው ወደ ሃገራቸው በሚወስዳቸው አውሮፕላን ላይ አንሳፈርም በማለት በቦትስዋና ጥገነት የጠየቁት።

ጥቅምት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የፖሊስ ምንጮች እንደገለጹት አንድ የአየር ጤና የፖሊስ ባልደረባ በህክምና እጦት መሞቱን ተከትሎ፣ የክፍለከተማው ፖሊሶች ስራ በማቆም ተቃውሞአቸውን ከገለጹ በሁዋላ፣ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ፖሊሶች መልቀቂያ አስገብተዋል። የመቀሌ ከተማ ተወላጅ የሆነው ኦፊሰር የማነ በኩላሊት ህመም ሲሰቃይ ከቆዬ በሁዋላ፣ በፖሊስ ሆስፒታል ተገቢውን ህክምና ባለማግኘቱ፣ በግል ለመታከም 16 ሺ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

በውጭ ከሚኖሩ ዜጎች፣ ወደ ኢትዮጵያና ኬንያ የሚላከው ገንዘብ መጠን እያደገ በመሄድ ላይ መሆኑ ተገለፀ። በዚህ መንገድ ወደ ሁለቱ ሃገራት የሚገባው የውጭ ምንዛሬ ከሰሃራ በስተደቡብ ከሚገኙ የአፍሪቃ ሃገራት ጋር በንፅፅር ሲታይ ከፍተኛ መሆኑን የዓለም ባንክ አስታውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወሳኝነታቸውን ያሳዩበት መድረክ

በኢትዮጵያ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ እስከዛሬ ሲደረጉ ከነበሩ ከንግግር ያልዘለሉ የቁርጠኝነት ማሳያዎች አንድ እርከን የዘለለ እንደሆነ የተነገረለት በጥናት ላይ የተመሠረተ ውይይት፣ በቅርቡ በመንግሥት ከፍተኛው አስፈጻሚ አካል ተካሂዷል፡፡

ይህ ለሕዝብ ከወትሮው በተለየ በከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከል ወቀሳና ተጠያቂነትን ያስነሳው ውይይት፣ መነሻ ምክንያቱ ታች መሬት ተወርዶ በመልካም አስተዳደር ችግሮች ላይ የዳሰሳ ጥናት መካሄዱ ነው፡፡ የጥናቱ አቅራቢዎች በውይይቱ ወቅት የችግሩን ስፋትና መጠን ሲያስረዱ፣ ለወትሮው የሐሳብ ልዩነቶቻቸውን ከመጋረጃ በስተጀርባ በመጨረስ ለሕዝብ አንድ ሆነው በመቅረብ የሚታወቁት የኢሕአዴግ ቱባ ባለሥልጣናት፣ በአደባባይ ልዩነቶቻቸውን በግልጽ ያወጡበት ውይይት እንደነበር ታይቷል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአገሪቱ ቁንጮ ባለሥልጣን ሆነው ከመጡበት ጊዜ  ጀምሮ፣ በግልጽ የሥልጣን ባለቤትና የገዥው ፓርቲ አቅጣጫ የመወሰን ሥልጣን እንዳላቸው ያሳዩበትም ነበር፡፡ በተለይ በመሬት፣ በኢንቨስትመንት፣ በፍትሕና በተለያዩ መስኮች በጥናቱ የቀረበው አሳሳቢ ሥጋት ካልተወገደ አደገኛነቱንም በማስጠንቀቅ አውስተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፅንኦት በመስጠት ለአገሪቱም ሆነ ለሕዝቡ አደገኛ የሆነውን የመልካም አስተዳደር ችግር መታገል የሕዝብ አመኔታን እንደሚያስገኝ አስታውቀው፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትም በውስጣቸው መደንገጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ ከውይይቱ በኋላ ባለሥልጣናት በብሔር፣ በዝምድና፣ በጥቅማ ጥቅምና በመሳሰሉት ከተሳሰሯቸው ኔትወርኮቻቸው እንዲላቀቁም አስጠንቅቀዋል፡፡ ዝርዝሩን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ ወይም በ ፖለቲካ ገጽ ይመልከቱ፡፡

 

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአንድነት መግባባትና መተባበር ሊቀመንበር የሆኑት የአቶ ፈንታሁን ብርሃኑ የ13 አመት ሴት ልጅ በአንድ ወጣት በስለት በአሰቃቂ ሁኔታ ስትገደል፣ ሌላው የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል አቶ አበራ ሃይለማርያምም በዚሁ ወጣት ተገድለዋል። አቶ ፋንታሁን ለኢሳት እንደተናገሩት ጎረቤታቸው የሆኑት አቶ አበራ የተገደሉት ምናልባትም ጩኸት ሰምተው ልጃቸውን ለመታደግ በመሞከራቸው ሳይሆን …

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታይዋን በሚባለው አካባቢ ይሰሩ የነበሩ ነጋዴዎች፣ ሆን ተብሎ በተቀሰቀሰ እሳት ድርጅታቸው እስከ ሙሉ ንብረታቸው እንደወደመባቸው ለኢሳት ተናግረዋል። ድርጊቱ ከሌሊቱ 11 ሰአት ላይ የተፈጸመ ሲሆን፣ መንግስት በአካባቢው ለሚያሰራው መንገድ ድርጅቶችን በማቃጠል ካሳ እንዳይከፍል ለማድረግ ነው በማለት ነዋሪዎች ተናግረዋል። በቃጠሎው ከ15 በላይ የንግድ ድርጅቶች የወደሙ ሲሆን፣ ፖሊሶች ህዝቡ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

የጀርመኑ ኮሜርስ፤የዩናይትድ ስቴትሱ ሲቲ እና የኬንያው ንግድ ባንኮች በአዲስ አበባ ቢሮ የመክፈት እቅድ ሰንቀዋል። በኢትዮጵያ ቢሮዎቻቸውን የከፈቱት የውጭ ኩባንያዎች ግን በዘርፉ ያለምንም ገደብ የመስራት ፈቃድ የላቸውም።

በአማራ ክልላዊ መንግሥት በድርቅ በተጠቁ በተለያዩ ዞኖች የተከለሉ ውኃ ምንጮች ውስንነት፣ ከንፅህና ጋር ለተያያዙ በሽታዎች መፈጠር ምክንያት መሆኑ ተገለጸ፡፡ 

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በዚህ ሳምንት በወጣው ሪፖርት፣ ‹‹ስካቢስ›› የተሰኘ ወረርሽኝ በምሥራቅ ጎጃም፣ በሰሜን ጎንደር፣ በደቡብ ወሎና በዋግ ህምራ ዞኖች በሚገኙ 20 ወረዳዎች መከሰቱን አስታውቋል፡፡ በዋግ ህምራ ዞን ብቻ 88,905 ግለሰቦች በወረርሽኙ መያዛቸው ታውቋል፡፡ የጤና ጥበቃ  ሚኒስቴር በበሽታው ለተጠቁ ሥፍራዎች መድኃኒቶችን በመላክ ላይ መሆኑን የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ የችግሩ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ የተለያዩ ዘርፎችን ትብብር የሚጠይቅ እንደሆነ ጠቁሟል፡፡ 

በሽታው ተዛማች በመሆኑ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተጀመረው ጥረት በአፋጣኝ ተስፋፍቶ መቀጠል እንደሚኖርበት የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ ወረርሽኙ የተከሰተው ከድርቁ ጋር ተያይዞ እንደሆነ በሪፖርቱ አስፍሯል፡፡ 

ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ በምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናት ቁጥር እየጨመረ መጥቷል፡፡ ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ የምግብ ፕሮግራም የሚያስፈልጋቸው ሕፃናት ቁጥር ከሌላው ጊዜ በ20 በመቶ መጨመሩን፣ የተጎጂዎቹ ቁጥር በየወሩ እየጨመረ መሄዱን ጽሕፈት ቤቱ በሪፖርቱ አመልክቷል፡፡

በመስከረም ወር የተመዘገቡ በምግብ ዕጦት የተጎዱ ሕፃናት ቁጥር 35,216 የነበረ ሲሆን፣ በነሐሴ ወር ከተመዘገቡት 43,391 ሕፃናት የ19 በመቶ ቅናሽ ያሳየ ቢሆንም፣ በአገር አቀፍ ደረጃ በመስከረም ወር የተመዘገበው በምግብ ዕጦት የተጎዱ ሕፃናት ቁጥር ከሌላው ማንኛውም ዓመት የ20 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ 

ከፍተኛው ቁጥር የተመዘገበው በአማራ ክልል እንደሆነ የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ በየወሩ በክልሉ 6,489 በምግብ ዕጦት የተጎዱ ሕፃናት ወደ ምግብ ፕሮግራም እንደሚገቡ ጠቁሟል፡፡ 

በኤልኒኖ ምክንያት በተፈጠረው አየር መዛባት የተከሰተው ድርቅ እየተባባሰ መምጣቱን ጠቅሶ፣ እየጨመረ የመጣውን የምግብ ዕርዳታ ፍላጎት መጠን ለማሟላት የኢትዮጵያ መንግሥት ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያቀርብም አጥጋቢ ምላሽ አለመገኘቱን አስታውቋል፡፡ እ.ኤ.አ. የ2015 እና የ2016 የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ ፍላጎት ማሟላት የሚያስችል የገንዘብ ምንጭ አለመኖሩ አሳሳቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ እ.ኤ.አ. ለ2016 የሚያስፈልገው ዕርዳታ በአስቸኳይ መገኘት እንዳለበት የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ፣ ዕርዳታውን አጓጉዞ ከሚፈለገው ሥፍራ ለማድረስ ከሦስት እስከ አምስት ወራት ቀድሞ መዘጋጀት እንደሚኖርበት ጠቁሟል፡፡ 

መንግሥት ከለጋሾች የሚፈለገውን ያህል የገንዘብ ድጋፍ ባለማግኘቱ ሁኔታዎች በከፉበት አካባቢ በራሱ ወጪ ዕለታዊ ዕርዳታዎች በማድረግ ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ 

ከመንግሥት የመጠባበቂያ ምግብ ክምችት 50,000 ሜትሪክ ቶን ስንዴና 300 ሜትሪክ ቶን የምግብ ዘይት በመከፋፈል ላይ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የከብቶች መኖ በመታደል ላይ መሆኑን፣ የውኃ ጉድጓዶች ጥገና ሥራ እየተከናወነ እንደሆነና የውኃ ማጣሪያ ኬሚካሎች በመሠራጨት ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት በተፈጠረው ድርቅ ምክንያት 8.2 ሚሊዮን ዜጎች የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፣ የዕርዳታ አቅርቦቱ ካልተፋጠነና የአየር ፀባዩ ካልተለወጠ የተረጂዎች ቁጥር በሁለት ወራት ውስጥ 15 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ 

 

በሽብር ድርጊት ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው ዓቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ካቀረበባቸው በኋላ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ የተሰናበቱት የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች፣

ዓቃቤ ሕግ ያቀረበባቸው ይግባኝ ተመርምሮ እንደሚያስቀርብና እንደማያስቀርብ ለመንገር በድጋሚ ተቀጠሩ

የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔን በመቃወም የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ይግባኝ ተከትሎ ውሳኔው እንዳይፈጸም ዕግድ የሰጠው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ጥቅምት 22 ቀን 2008 ዓ.ም. የውሳኔ መዝገቡን መርምሮ ዓቃቤ ሕግ ባቀረበው የይግባኝ አቤቱታ ላይ ‹‹ያስቀርባል ወይም አያስቀርብም›› ብሎ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ ዓቃቤ ሕግ የተቃወመው የሥር ፍርድ ቤት የውሳኔ መዝገብ እንዳልቀረበለት ገልጿል፡፡ በመሆኑም ውሳኔውና ዝርዝር ማስረጃዎቹ ተያይዘው እንዲቀርቡለት ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ 

በዕለቱ ይግባኝ የተጠየቀባቸው የአንድነት አመራር የነበሩት አቶ ሀብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአረና ፓርቲ አመራር የነበሩት አቶ አብረሃ ደስታና የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበሩት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ እንዲሁም አብረዋቸው ይግባኝ የተባለባቸው አቶ አብረሃም ሰለሞን በችሎት አልተገኙም፡፡ ፍርድ ቤቱ በችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መዝገቡን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 29 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ 

 

አፌን መረረኝ፤ ጠረን አመጣብኝ፤ የተለያዩ ሰዎች ሲናገሩት የሚደመጥ ችግር ነዉ። የአፍ ምሬት ከምን ይመጣል? ዉስጥ ደዌ ከፍተኛ ሃኪም ዶክተር ቶሌራ ወልደየስ፤ አፍን ሊያመርሩ የሚችሉ የተለያዩ ምክንያቶች ሊሆኑ እንደሚችሉ ነዉ በዝርዝር ያብራሩት። ዶክተር ቶሌራ የተለያዩ በሽታዎችም አፍ ላይ ምሬት እንዲሰማን ሊያደርጉ …

የአፍ ምሬትና ጠረን መንስኤዎቹ Read more »

ጥቅምት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋቢያችን ነዋሪዎችን በማነጋገር እንደገለጸው፣ በአድማው የተሳተፉትን ሹፌሮችን ወደ እስር ቤት የወሰዱ ሲሆን፣ ከፖሊስ የሚደርስባቸውን ጫና በመፍራት ስራ እንጀምራለን ያሉት ደግሞ 500 ብር ቅጣት ካልከፈሉ እንደማይጀምሩ ተነግሯቸዋል። ከፖሊስ የሚደርሰውን ወከባ በመፍራት ብዙ ሹፈሮች አሁንም ራሳቸውን ደብቀዋል። አንድ የባጃጅ ባለሃብት መንግስት ለምን አድማ አደረጋችሁ በሚል እየተበቀለ ነው ብለዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

መንግሥት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ከሚያወጣው ወጪ ባነሰ ታሪፍ አገልግሎት እንደሚሰጥ በመግለጽ፣ ወጪውን ለማካካስ 50 በመቶና ከዚያም በላይ ሊደርስ የሚችል ዋጋ ሊያስከፍል ይችላል መባሉን የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ ኃይል አስተባበለ።

ጥቅምት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኬንያዋ የድንበር ከተማ ሜሩ ኢዞሎ አቅራቢያ በቦረና እና ሜሩ ጎሳዎች መሃከል በተቀሰቀሰ ግጭት አስር የአካባቢው ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ ከ2 ሺ በላይ የሚሆኑ ቤተሰቦች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል። የከተማው አሽከርካሪዎች ግጭቱ እጅግ አስፈሪ እንደነበርና ሁኔታዎቹ አሳሳቢ መሆናቸውን ገልጸው የሜሩ ብሔር አባላት ወደ ከተማቸው የሸሹ ሲሆን የቦረና ጎሳ አባላትም …

ፍሪደም ሃውስ የተባለው የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት በዓለማችን ላይ የኢንተርኔት አፈና እየጨመረ መሄዱን በ2015ቱ የኢንተርኔት ነጻነት ሪፖርቱ ላይ ገለጸ። ድርጅቱ በጥናቱ ካካተታቸው 65 ሃገራት መካከል 32ቱ የኢንተርኔት ሳንሱርና አፈናን አጠናክረዋል ብሏል።

ለመሪ ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ከአምስት ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቧል የቤተ ክርስቲያንን ኹለንተናዊ ችግር የሚያጠና ዐቢይ ኮሚቴ አቋቁሟል የሙስና እና የመልካም አስተዳደር ዕጦት በኮሚቴው ጥናት ተካተዋል የጥናቱ ግኝትና መፍትሔ ተቋማዊ ህልውናዋንና አቅጣጫዋን ይወስናል

«ወቅቱ ክረምት ነዉ ካፊያ የሚጥልበት፤
መንገዱ ጠባብ ነዉ፤ ኮሮኮንች የበዛዉ ሰዉ የማይሄድበት፤
ላይጨልም ጨልሞ አይን ያጭበረብራል፤
ይህ የሕይወት አረም ወቅትን ተገን አድርጎ፤
ዓይንን ከጋረደ ማ ማንን ይለያ።»

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት «ድሕነትን ታሪክ እናደርጋለን» ባለበት፤ የሐገሪቱ ምጣኔ ሐብት በድርብ አሐዝ ማደጉ በሚነገርበት ባሁኑ ወቅት ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዉያን ዳግም ምፅዋት መማፀናቸዉ በርግጥ ግራ-አጋቢ አነጋጋሪም ሆኗል

 በበፍቃዱ ዘ ኃይሉ
የሰለሞን ስዩምን ‹‹የኦሮሞ ጉዳይ እና የኢትዮጵያ ብያኔ›› የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ (ሁለተኛ እትም) አነበብኩት፡፡ በጥቅሉ ወድጄዋለሁ፡፡ ጥቂት ቅሬታዎች ግን አሉኝ፡፡ ሰለሞን በአማርኛ የኦሮሞ ጉዳይን ከጻፉ (እና እኔ ካነበብኩላቸው) ጸሐፍት ሁሉ በተሻለ ልለው በምደፍረው ደረጃ ምሁራዊ ታማኝነት (intellectual honesty) ተስተውሎበታል፡፡ አልፎ፣ አልፎ ግን ምሁራዊ ታማኝነቱ ከሚጎድላቸው ምሁራን ማጣቀሱ ሚዛን አስቶ ያንገዳገደው ይመስለኛል፡፡ ለምሳሌ የታቦር ዋሚ ‹‹የውገና ድርሰቶችና የታሪክ እውነቶች››ን ማንሳት ይቻላል፡፡ ታቦር ትልቅ ርዕስ ይዞ ትንንሽ ክርክር የተከራከረባቸው ቦታዎች አሉ፡፡ አንዱ የቋንቋ ተናጋሪዎች ብዛትን በተመለከተ የሚሰጠው ምንጭ አልባ ድምዳሜ ነው፡፡ ሰለሞን ያንን በኦሮሞ ጉዳይ ላይ ያንፀባርቀዋል፡፡ ‹‹. . . መረጃዎች አሉ›› በሚል ብቻ፡፡ በተጨማሪም አጠራጣሪ (አከራካሪ) ሁኔታዎች ላይ እምነቱን ለዘውግ ብሄርተኞቹ ትርክት ወደመስጠቱ አዘንብሎብኛል፡፡

ይህ በእንዲህ አያለ፣ መጽሐፉን አንብቤ ስጨርስ የጎደለ ነገር ያለ-ያለ ተሰማኝ፡፡ ታዲያ የጎደለ የመሰለኝን ምዕራፍ ለምን አልጽፈውም አልኩና ተነሳሁ፡፡ ጽሑፉን የምጽፈው የሰለሞንን ሐሳብ እየተዋስኩ፣ የኔን እየጨመርኩበት ነው፡፡ እሱም ይጭንብኛል፤ እኔም እጭንበታለሁ፡፡ ስለዚህ ከታች የማሰፍረው ጽሑፍ ላይ ‹እኔ›› እኔ አይደለሁም፡፡ ሰለሞን ስዩም ነው፡፡ እኔ ሁን እንዳልኩት፡፡

የተጣመመው የብሔርተኝነት ቅርንጫፍ
በኢትዮጵያ ቀኝ ዘመሞች አና ግራ ዘመሞች ሁሌም እርስ በርስ እንደተዋቀሱ ነው፡፡ እነዚህ ‹‹ትምክህተኛ ብሔርተኞች ፍፁም አሀዳዊ አገር ለመፍጠር ሊፍጨረጨሩ አገሪቱን ይበታትኗታል፡፡ ሲሉ፣ እነዚያ ‹‹ጠባብ ብሔርተኞች ሁሉንም ነገር በዘውግ ዓይን እያዩ አገሪቱን ሊበጣጥሷት ነው›› ይላሉ፡፡ መጽሐፉ በኦሮሞ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ ስለሆነም አሁን ማተኮር የምፈልገው የዘውግ ብሔርተኞች የሚከሰሱባቸው ችግሮች እና መፍትሔዎች ላይ ነው፡፡

አማራ-ሰግነት (Amhara Phobia)
ኦሮሞ ብሔርተኝነት ከገጠሙት ፈተናዎች መካከል አንዱ የኦ&#4654

መንግሥት የኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ 50 በመቶ እንደሚጨምር ይፋ አደረገ

ፋብሪካዎች ተቃውሟቸውን አሰምተዋል

መንግሥት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ከሚያወጣው ወጪ ባነሰ ታሪፍ እየደጎመ ሲያቀርብ መቆየቱን በመግለጽ፣ በአሁኑ ወቅት ቢያንስ ወጪውን የሚሸፍን ታሪፍ ማስከፈል በማስፈለጉ 50 በመቶና ከዚያም በላይ ሊደርስ የሚችል ጭማሪ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ 

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀ እንዳስታወቁት፣ መንግሥት ለበርካታ ዓመታት በድጎማ ሲያቀርበው የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ በጣም ዝቅተኛ ነበር፡፡ ዝቅተኛ ብቻም ሳይሆን በአሁኑ ወቅት ኃይል አምርተው ለመንግሥት ለመሸጥ ፍላጎት ካላቸው ኩባንያዎች ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ፣ የታሪፉ ዝቅተኛነት የድርድር አቅሙን እንዳዳከመበት አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም መንግሥት የታሪፍ ለውጥ የማድረግ አቋም እንዳለው፣ ዘ ኢኮኖሚስት ሰሞኑን በአዲስ አበባ ባካሄደው የኢትዮጵያ ጉባዔ ላይ ለታደሙ ኢንቨስትሮች ገልጸዋል፡፡ 

ኢንጂነር አዜብ እንዳብራሩት፣ መንግሥት በአሁኑ ወቅት አንድ ኪሎ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ዘጠኝ የአሜሪካ ሳንቲም እያወጣ ይገኛል፡፡ በአንፃሩ አንድ ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ ስድስት የአሜሪካ ሳንቲም እያስከፈለ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የ50 በመቶና ከዚያም በላይ ለውጥ ሊሆን እንደሚችል ይፋ አድርገዋል፡፡ 

ኢንጂነሯ ለሪፖርተር እንዳብራሩት፣ ዝቅተኛ ነው ያሉት ታሪፍ በኃይል ማመንጨት ዘርፍ የሚፈለገውን ያህል የውጭ ኢንቨስትመንት እንዳይመጣ በማድረግ ሲጎዳው ቆይቷል፡፡ በመሆኑም የታሪፍ ለውጥ እንደሚደረግ በመገለጹ 14 ያህል የውጭ ኩባንያዎች ኃይል አመንጭተው ለመንግሥት ለማቅረብ ድርድር ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች መካከል የአራት ቢሊዮን ዶላር የጂኦተርማል ኃይል ፕሮጀክት ይዞ የመጣው ሬይክቪክ ጂኦተርማል፣ ጄነራል ሞተርስና ብላክ ራይኖ የተሰኙት ይጠቀሳሉ፡፡ 

ብላክ ስቶን ለተባለው የአሜሪካ ኩባንያ እህት የሆነው ብላክ ራይኖ፣ በአሁኑ ወቅት ከጂቡቲ እስከ አዋሽ 550 ኪሎ ሜትር የሚዘረጋውን የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ይህ ኩባንያ ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት ከኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ስምምነት ከመድረሱም በተጨማሪ፣ በመጪዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ወሳኝ ወደሆነው ምዕራፍ እንደሚሸጋገር ኩባንያውን በመወከል የተገኙት ሺሌሽ ሙራሊዳሃ አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም በኃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ሥራ ላይ ለመግባት ፍላጎት እንዳለውም ለመንግሥት ማስታወቁን ኢንጂነር አዜብ ጠቁመዋል፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል የታሪፍ ማሻሻያ እንደሚደረግ ይፋ መደረጉ ካስደነገጣቸው መካከል የኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ጨርቃ ጨርቅና ጥጥ ኢንዱስትሪዎች ፌደሬሽን የቦርድ አባል አቶ ፋሲል ታደሰ አንዱ ናቸው፡፡ ኢንጂነር አዜብ የጠቀሱት የታሪፍ ጭማሪ ኢንዱስትሪዎችን ሳይሆን ኃይል ወደ ውጭ የሚልኩትን ኩባንያዎች የሚመለከት ነው በማለት ለመከራከር ቢሞክሩም፣ ጭማሪው ሁሉንም እንደሚመለከት ኢንጂነር አዜብ አረጋግጠውላቸዋል፡፡ ‹‹ይኼማ ሙቱ ማለት ነው፤›› ያሉት አቶ ፋሲል፣ የታሪፍ ጭማሪ ከዚህ ቀደም ተነስቶ አምራች ኢንዱስትሪዎችን እንደማይመለከት ከመንግሥት ጋር ስምምነት ተደርጎ እንደነበር በመግለጽ፣ የመረጃ ችግር እንዳይሆን በማለት ሥጋታቸውን ሲገልጹ ቢደመጡም፣ ኢንጂነሯ በድጋሚ አረጋግጠውላቸዋል፡፡ ሆኖም የታሪፉ ጭማሪ ሚዛናዊ እንዲሆን መደረጉን ኢንጂነር አዜብ ለማስረዳት ሞክረዋል፡፡

ይሁንና ይጨመራል የተባለው ታሪፍ ከመቼ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ኢንጂነሯ ባይገልጹም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ እንደሚሆን ግን ተናግረዋል፡፡ 

ከሁለት ዓመት በፊት የአፍሪካ ልማት ባንክ በአፍሪካ በከፍተኛ ወጪ ኃይል የማመንጨት አዝማሚያዎችን የሚያስቃኘው ጽሑፍ ላይ እንዳሰፈረው፣ መንግሥታት ኃይል የማመንጨት አቅማቸው ደካማ እንዲሆን ከሚያደርጉ ፈተናዎች መካከል ከፍተኛ ወጪ አንዱ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥታት የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎትን ለማሟላት በድጎማ ለማቅረብ መገደዳቸውን ባንኩ አስፍሯል፡፡ 

በሌላ በኩል መንግሥት በኢነርጂው መስክ ማስተካከል ይገባዋል ከተባሉት ችግሮች መካከል የውጭ ምንዛሪ ለውጥና ሊያስከትል የሚችለውን የኪሳራ ሥጋት እንዴት እንደሚመለከተው ተጠይቋል፡፡ የቢሮክራሲ ጣጣዎች፣ በጂኦተርማል መስክ የፋይናንስና የማበረታቻ ፓኬጆችን ማሻሻል እንዳለበት የሬይክቪክ ጂኦተርማልና የብላክ ራይኖ ኃላፊዎች መንግሥትን አሳስበዋል፡፡ 

 

የመምህር ግርማ ቤት ተበረበረ

በማታለል ወንጀል ተጠርጥረው ጥቅምት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት መምህር (አጥማቂ) ግርማ ወንድሙ፣ አያት የሚገኘው መኖርያ ቤታቸው በፖሊስ መበርበሩ ታወቀ፡፡ 

ፖሊስ ቤታቸውን ሲበረብር ያገኘው ነገር ባይገለጽም፣ ለተጠረጠሩበት የወንጀል ድርጊት ማስረጃ የሚሆነውና ሌሎች ተጨማሪ ነገሮች ፍለጋ ሳይሆን እንዳልቀረ ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ 

መምህር ግርማ ከሁለት ወራት በፊት የእስር ትዕዛዝ ተሰጥቶባቸው እንደነበር ተጠቁሞ፣ አንድ ቀን ፖሊስ ጣቢያ አድረው ጥቅምት 18 ቀን 2008 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ በወቅቱም ፖሊስ የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸው ነበር፡፡ የፖሊስን ጥያቄ በመቃወም የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ ከእስር እንዲፈቱ በጠበቃቸውና በራሳቸው የጠየቁ ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ አልተቀበላቸውም፡፡ 

መምህር ግርማ የተጠረጠሩበትን የማታለል ወንጀል የፈጸሙት፣ በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም. እንደሆነና በየካ ክፍለ ከተማ ወሰን ግሮሰሪ አካባቢ ነዋሪ መሆናቸው ከተጠቆመው አቶ በላይነህ ከበደ መኖርያ ቤት ጋር የተገናኘ መሆኑ በምርመራው ተገልጿል፡፡ 

ፖሊስ በምርመራው እንዳረጋገጠው አቶ በላይነህ ከትዳር አጋራቸው ጋር የሚኖሩበት በ400 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ መኖርያ ቤት ነበራቸው፡፡ አቶ በላይነህ ቤታቸውን በአጭር ጊዜ ውስጥ ካልሸጡ ሊሞቱ እንደሚችሉ መምህር ግርማ ሲነግሯቸው፣ ከፍተኛ ዋጋ ያወጣላቸው የነበረ ቤታቸውን በ800 ሺሕ ብር ለመሸጥ መገደዳቸውን የፖሊስ ምርመራ ይጠቁማል፡፡ 

መምህር ግርማ ቤቱን ማሸጥ ብቻ ሳይበቃቸው፣ ገንዘቡ እንዲበረክትላቸው እንዲፀለይበት እንዲሰጧቸው የተጠየቁት አቶ በላይነህ፣ ገንዘቡን መስጠታቸውን ፖሊስ ለፍርድ ቤት አስረድቷል፡፡ ሊፀለይበት ወደ መምህር ግርማ ቤት ተወስዷል የተባለው ገንዘብ ውሎ በማደሩ፣ አቶ በላይነህ ወደ መምህር ግርማ ቤት ስልክ ሲደውሉ ስልኩ አልሠራ እንዳላቸውና ወደ ውጭ አገር መሄዳቸውን እንደሰሙ መግለጻቸው በፖሊስ ተጠቅሷል፡፡ 

ተጠርጣሪው መምህር ግርማ ለፍርድ ቤቱ ከሳሻቸውን ቀይ ይሁኑ ጥቁር እንደማያውቋቸውና ሆን ተብሎ የተሸረበባቸው ሴራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የተጠረጠሩበት ወንጀል ዋስትና የማያስከለክል መሆኑን በመግለጽ በዋስ እንዲለቀቁ ቢጠይቁም፣ ፍርድ ቤቱ አልተቀበላቸውም፡፡ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ባለመቀበል ሰባት ቀናትን በመፍቀድ ለጥቅምት 25 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ 

 

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለምስክርነት እንዲቀርቡ የተላለፈው ትዕዛዝ ታገደ

ተጠርጣሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩና የእንግሊዝ ኤምባሲ እንዲጠየቁ አመለከቱ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሽብር ድርጊት ወንጀል ተጠርጥረው ለተከሰሱት ለእነ ዘመኑ ካሴ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ያስተላለፈውን ትዕዛዝ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት አገደው፡፡ 

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የሥር ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡ ሐምሌ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. የሰጠውን ብይን ያገደው፣ የፌዴራል ማዕከል ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ይግባኝ ሲመረምር የሚያስቀርብ ሆኖ በማግኘቱ መሆኑን ባስተላለፈው ትዕዛዝ አስታውቋል፡፡

አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት በቆጠሯቸው በእነ ዘመኑ ካሴ የክስ መዝገብ (አሥር ሰዎች) የተካተቱት አቶ አሸናፊ አካሉ፣ አቶ ደህናሁን ቤዛ፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁንና አቶ አንሙት የኔዋስ ሲሆኑ እንዲመሰክሩላቸው የፈለጉትም፣ ተከሳሾቹ ኤርትራ ሄደው ከአቶ አንዳርጋቸው ትዕዛዝና መመርያ እንደተቀበሉ ዓቃቤ ሕግ የጠቀሰባቸውን ክስ እንዲያስረዱላቸው እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል፡፡ 

በወቅቱ ከሳሸ ዓቃቤ ሕግ፣ ‹‹አቶ አንዳርጋቸው በተለያዩ ጊዜያት በተመሠረቱባቸው የወንጀል ክሶች በአንዱ ዕድሜ ልክ ሲፈረድባቸው በሌላኛው ሞት ተፈርዶባቸዋል፡፡ በመሆኑም ለምስክርነት ስለማይበቁና ሕግም ስለሚከለክላቸው ቀርበው ሊመሰክሩ አይገባም፤›› ብሎ ተቃውሞ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ግን የዓቃቤ ሕግን ክርክር ውድቅ በማድረግ አቶ አንዳርጋቸው ቀርበው እንዲመሰክሩ ሦስት ጊዜያት ትዕዛዝ የሰጠ ቢሆንም፣ ማረሚያ ቤቱ የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት ሳያቀርባቸው ቀርቷል፡፡ በአራተኛው ቀጠሮ ‹‹አቶ አንዳርጋቸው ማረሚያ ቤት የሉም›› ብሎ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. በደብዳቤ ገልጿል፡፡

ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤቱ ምላሽ ተማረው የተወሰኑት ‹‹ብይን ይሰጠን›› ሲሉ፣ አቶ ደህናሁን ቤዛና አቶ ሞንዳዬ ጥላሁን ቀርበው መመስከር እንዳለባቸው በመግለጽ፣ ፍርድ ቤቱ ከውጭ አገር (የመን ሰንዓ) ይዞ ያመጣቸው ፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉና ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲጠየቁ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀው ነበር፡፡

ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. በችሎት ያመለከቱትን አቤቱታ በማጠናከር፣ ጥቅምት 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ጉዳያቸውን እያየው ለሚገኘው ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ጽፈዋል፡፡ ተከሳሾቹ ለፍርድ ቤቱ በጻፉት ደብዳቤ እንደገለጹት፣ አቶ አንዳርጋቸው በትውልድ ኢትዮጵያዊ ቢሆኑም በዜግነት እንግሊዛዊ በመሆናቸው፣ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ጉዳያቸውን እንደሚከታተሉ ጠቁመዋል፡፡ በመሆኑም የእንግሊዝ ኤምባሲ፣ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉና ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲጠየቁ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው አመልክተዋል፡፡

የሥር ፍርድ ቤት በተከሳሾቹ ደብዳቤ ላይ ብይን ከመስጠቱ በፊት ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ይግባኝ የመረመረው ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የሥር ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዳይፈጸም በማገድ፣ ያስቀርባል ባለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለኅዳር 8 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ 

 

    ነገሩ፣ ለዘመናት ከምናውቀው እውቀት የተለየ በመሆኑ ግራ ማጋባቱ አይቀርም፡፡ እስካሁን ለሕፃናት ዕድገትና ጥንካሬ ጥሩ ነው በማለት ሕፃናትን ስንመግብ የኖርነው ወተት፤ በተቃራኒው ለሕፃናት ዕድገት ጥሩ አይደለም፤ ያቀጭጫቸዋል ቢባሉ ምን ይላሉ? የሚገርም ነው!ሰሞኑን በሂልተን ሆቴል ሲካሄድ በቆየው 4ኛ የአፍሪካ የምግብና የኑትሪሽን ፎረም ላይ አንድ ተመራማሪ፤ በመርዛማ ኬሚካሎች (አልፋ ቶክሲን) ላይ ያደረጉትን የምርምር ውጤት ሲያቀርቡ፤ እግረ መንገዳቸውን የአዲስ አበባና አካባቢዋ ወተት ከመጠን በላይ መርዛማ ኬሚካል (አልፋ ቶክሲን) እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ተመራማሪው ዶ/ር አሻግረ ዘውዱ፤ ዓለም አቀፉ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት (ILRI) ባወጣው ሪፖርት፤ በ2016 በአዲስ አበባና አካባቢዋ ባደረገው ጥናት፣ ከተሰበሰቡት 140 ናሙና ከ90 በመቶ በላይ ዓለምአቀፍ ሕግ ከሚፈቅደው በላይ መርዛማ ኬሚካል (አፍላቶክሲን M1) እንዳለው ማስታወቁን ተናግረዋል፡፡
አልፋ ቶክሲን በሻጋታ ምክንያት የሚፈጠር መርዛማ ኬሚካል ነው ያሉት ተመራማሪው፤ መርዛማ ኬሚካሉ ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች ቢጐዳም በሕፃናት ላይ የበለጠ ጉዳት ያደርሳል፣ መቀጨጭና መጫጫት ያስከትላል፡፡ በዕድሜያቸው ልክ ቁመታቸው አያድግም፡፡ በኢትዮጵያ 40 በመቶ ሕፃናት ቀጫጫ ናቸው፡፡ መርዛማ ኬሚካሉ ከማጫጨት በተጨማሪ ረዥም ዕድሜ ሲቆይ የጉበት ካንሰር ያስከትላል ብለዋል፡፡
አልፋ ቶክሲኖች የተለያዩ ናቸው፡፡ እህል ላይ የሚገኙትና በይበልጥ የሚታወቁት 4 ናቸው፡፡ እነሱም B1 B2 G1 G2 ይባላሉ ያሉት ዶ/ር አሻግሬ፤ እህሉ ላይ የሚገኘውን B1 አልፋ ቶክሲን የበላ ከብት በሰውነቱ ውስጥ በሚካሄደው ሜታቦሊዝም፣ B1 መርዛማ ኬሚካል ወደ M1 ይቀየራል፡፡ ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ እንደምታስተላልፍ እናት ለልጇ ጡት ስታጠባ መርዛማውን ኬሚካል ወደ ሕፃኑ ታስተላልፋለች፡፡ ከብትም እንደዚሁ፡፡ ሕፃኑ በአልፋ ቶክሲን የሚጠቃው፣ ጡት መጥባት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡ ወተት ለሕፃናት ዕድገት ጥንካሬና ውፍረት ጥሩ ነው ስለሚባል ወተት እየጠጡ ያድጋሉ፤ ለአልፋ ቶክሲን እየተጋለጡ ናቸው ያሉት ተመራማሪው፤ “በወሎ ድርቅ ጊዜ የእርጐ ፈንገስ የሚባል ነገር ተፈጥሮ ነበር፡፡ የሚበላ ነገር ሲጠፋ ፈንገስ የተቀላቀለበት ምግብ በልተው፤ ጋንግሪን ተፈጥሮባቸው እግራቸው የተቆረጠ ብዙ ሰዎች ነበሩ፡፡” ብለዋል፡፡ ዓለምአቀፉ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ያወጣውን መረጃ በተመለከተ፤ መንግስት ከኢትዮጵያ ፐብሊክ ኢንስቲትዩት፣ የደረጃዎች ምዘናና ተስማሚነት፣ የምግብ ሳይንስና ኑትሪሽን ማዕከል እንዲሁም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ ባለሙያዎች ጥናት እንዲያደርጉበት ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡ ውጤቱ ልክ እንደተባለው ከሆነ ምን እናድርግ? በማለት ምክክር ይደረጋል ያሉት ዶ/ር አሻግሬ፤ ልክ ካልሆነ ደግሞ ኅብረተሰቡ ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ስታንዳርድ ባንክ ኢትዮጵያዊቷን የባንክ ባለሙያ ለኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤቱ ሾመ

በአፍሪካ ባካበተው ሀብት ቁንጮ በመባል የሚታወቀው የደቡብ አፍሪካው ስታንዳርድ ባንክ፣ የኢኮኖሚና የባንክ ባለሙያዋን ወይዘሪት ጣይቱ ወንድወሰንን የኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤቱ ተጠሪ አድርጎ ሾመ፡፡ 

ወይዘሪት ጣይቱ የግዙፉ ባንክ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን የኢትዮጵያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ከተሾሙ ቢቆዩም፣ የጽሕፈት ቤቱ በይፋ ሥራ መጀመር በተበሰረበት ጥቅምት 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በተካሄደ ሥነ ሥርዓት ወቅት ሹመታቸው ታውቋል፡፡ ስታንዳርድ ባንክ የጽሕፈት ቤቱን አድርሻ ቦሌ አካባቢ፣ ከሞናርክ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው ፕላኔት ሌን ታወር ሕንፃ ላይ አድርጓል፡፡ 

የስታንዳርድ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቤን ክሩገር የጽሕፈት ቤቱን መከፈት በማስመልከት እንደተናገሩት፣ ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ማድረግ ለሚፈልጉ ደንበኞቹ ድልድይ ሆኖ ይሚሠራል፡፡ ከደቡብ አፍሪካ በሚሰጠው መመርያ መሠረት ጽሕፈት ቤቱ እንደሚመራ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ የኢነርጂ እምብርት በመሆን ላይ እንደምትገኝ ያስታወቁት ክሩገር፣ ወደፊት የኃይል ኤክስፖርት የአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ገቢ አስገኝ እንደሚሆንም አክለዋል፡፡ 

ወይዘሪት ጣይቱ ከሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳብራሩት፣ ባንኩ ትኩረት ከሚያደርግባቸው መስኮች መካከል የኢነርጂ፣ የመሠረተ ልማት፣ የአግሪ ቢዝነስና የፍጆታ ሸቀጦች ትልቁን ቦታ ይይዛሉ፡፡ የጽሕፈት ቤቱ መከፈት ከደንበኞች እየመጣ ያለውን ጥያቄ ለማስተናገድ ስለሆነ ለጥያቄያቸው ምላሽ እንደሚሰጥ አብራርተዋል፡፡ ‹‹እዚህ የመጣነው ሰዎች እንዲያውቁን፣ ገበያውን ለመረዳት፣ የጥናት አቅማችንን ለማሳደግ፣ ነገሮች እንዴት እንደሚጓዙ ለማየትና ኢኮኖሚው እንዴት እንደሚንቀሳቀስ ለመረዳት ነው፤›› ያሉት ኃላፊዋ፣ የባንኩ ደንበኞች በዚህ አገር ለመሠማራት ቢፈልጉም ድጋፍ ለመስጠት ባንኩ ጽሕፈት ቤት ከፍቷል ብለዋል፡፡ ባንኩ ከአፍሪካ በተጨማሪ በአሜሪካ፣ በአውሮፓ፣ በእስያ፣ በደቡብ አሜሪካና በሌሎችም አገሮች ደንበኞች እንዳፈራ ገልጸዋል፡፡ 

ኢትዮጵያ ተወልደው ያደጉት ወይዘሪት ጣይቱ በአሜሪካ የኢኮኖሚክስና የፋይናንስ ትምህርቶችን ተከታትለዋል፡፡ በአሜሪካ ታዋቂና ግዙፍ ከሆኑት መካከል በኒው ዮርክ ፌደራል ሪዘርፍ ባንክ፣ እንዲሁም በጂፒ ሞርጋን ባንክ በኮርፖሬት ባንክ ዘርፍ በማገልገል የካበተ ልምድ አላቸው፡፡ በኒው ዮርክ ሪዘርቭ ባንክ በነበራቸው ቆይታ ወቅት የአሜሪካ ባንኮችን ጨምሮ የዓለም የፋይናንስ ተቋማትን ቀውስ ውስጥ የከተተውን አጋጣሚ አስተናግደዋል፡፡ 

ከስምንት ዓመት በፊት የተከሰተው ቀውስ ሌህማን ብራዘርስ የተባለውን የአሜሪካ ባንክ የውኃ ሽታ ማድረጉ አይዘነጋም፡፡ የኒው ዮርክ ሪዘርቭ ባንክ በወቅቱ የተከሰተውን ቀውስ የማጣራት ተግባር እንዲያከናውን በተደረገበት ወቅት ወይዘሪት ጣይቱ የባንኩ ባልደረባ ነበሩ፡፡ 

ስታንዳርድ ባንክን ጨምሮ የናይጄሪያው ኤኮ ባንክ፣ የእንግሊዙ ኤችኤስቢሲ፣ የህንዱ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ ኦፍ ኢንዲያ ጽሕፈት ቤቶቻቸውን በአዲስ አበባ ከከፈቱት መካከል ይጠቀሳሉ፡፡ 

 

የሩሲያ A-321 የመንደኞች አዉሮፕላን ሲና በረሃ ግብፅ ዉስጥ ዛሬ ተከሰከሰ። 217 መንገደኞች እና 7 ሠራተኞችን የጫነዉ አዉሮፕላን በደረሰበት አደጋ ተሳፋሪዎቹ እንዳልተረፉ በግብፅ የሩሲያ ኤምባሲ በፌስቡክ ገጹ ላይ መግለፁን አዣንስ ፍራንስ ፕረስ ዘግቧል።

የሳተላይት ሥርጭቱ መካከለኛው ምሥራቅን፣ ደቡብ አውሮፓንና ሰሜን አፍሪቃን ያካልላል (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፮ ቁጥር ፰፻፳፬፤ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ በሀገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ አገልጋዮችዋ እና ምእመናንዋ ድምፅዋን የምታሰማበትና መረጃ የምትሰጥበት የ24 ሰዓት የቴሌቪዥን አገልግሎት እንድትጀምር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ፡፡ ከጥቅምት 12 ጀምሮ የዓመቱን የመጀመሪያ የምልአተ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ በማካሔድ …

ግድያ ለመፈፀም ዝቷል- አቃቤ ህግ
    በፌስቡክ፤ “አይኤስ ነኝ” ከሚል መልእክት ጋር የግድያ ዛቻ በማስተላለፍ የሽብር ወንጀል ፈፅሟል ተብሎ የተከሰሰው ወጣት ላይ፤ የአቃቤ ህግ ከትናንት በስቲያ ምስክሮችን አቀረበ፡፡ አቃቤ ህግ ያቀረበው ክስ፣ ሰይድ መሃመድ፣ በሚያዚያ ወር 2007 ዓ.ም፤ “አይኤስ ነኝ” በማለት በፌስቡክ እንደጻፈ ይገልጻል፡፡ የአይኤስ ወታደር ነኝ … በቅርቡ በረመዳን ወር የሚታረዱትን ለመያዝ ወደ ባቲ እመጣለሁ” የሚል የዛቻ መልዕክት በግል በፌስቡክ ገፁ ላይ ለጥፏል ብሏል – አቃቤ ህግ፡፡
1ኛ የአቃቤ ህግ ምስክር፤ ከላይ የተጠቀሰው መልዕክት ላይ ሰዎች አስተያየት በሰጡበት ወቅት ይህንን መልዕክት በፌስቡክ መመልከቱን  የገለፀ የአቃቤ ህግ ምስክር፤ ከአካባቢዬ ወጣቶች ጋር በመመካከር ለፖሊስ ጠቁሜያለሁ ብሏል፡፡
የባቲ ከተማ ፖሊስ መሆናቸውን የገልፁ ሌላ የአቃቤ ህግ ምስክር በበኩላቸው፣ ጥቆማ ከደረሰን በኋላ ተጠራጣሪውን በቁጥጥር ስር አውለናል ብለዋል፡፡ በተጠርጣሪው የፌስቡክ ገፅ ላይም፤ “አይኤስ ማለት እንደኔ አይነት ነው፡፡ በረመዳን ወር ለእርድ ወደ ባቲ እመጣለሁ” የሚል መልዕክት አይቻለሁ ብለዋል፡፡
በወቅቱ “ለምን ይሄን አደረግህ” ብዬ ጠይቄዋለሁ፤ እሱም፤ “እኔ ጓደኞቼን ለማስፈራራት ነው  እንጂ አይኤስ አይደለሁም” ሲል መልሶልኛል ብለዋል – እኚሁ የአቃቤ ህግ ምስክር፡፡ በሚያዚያ ወር፤ አይኤስ የተሰኘው አሸባሪ ቡድን፣ በሊቢያ በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን በሚያዝያ ወር፣ አይ ኤስ የተሰኘው አሸባሪ ቡድን በሊቢያ በርካታ ኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ግድያ ለማውገዝ፤ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመሄድ እየተዘጋጀሁ እንደነበር አስታውሳለሁ፤ ተጠርጣሪው የተያዘውም በዚያኑ እለት ነው በማለት ምስክሩ ተናግረዋል፡፡ ከዚያ በኋላ ነው፤ ተጠርጣሪው ለምርመራ ወደ አዲስ አበባ የመጣው ተብሏል፡፡
የአቃቤ ህግ 3ኛ ምስክር የአዲስ አበባ ነዋሪ እንደሆኑ ጠቅሰው፤ ተጠርጣሪው የፌስቡክ ገፁ የራሱ መሆኑን አምኖ ሲፈርም እኔ በታዛቢነት ፈርሜያለሁ ብለዋል፡፡ በፌስቡክ አካውንቱ ላይ የተፃፈውንም መልዕክት እንደተመለከቱ ተናግረዋል፡፡
ፍ/ቤቱም የምስክሮቹን ቃል ካደመጠ በኋላ በመቅረፀ ድምፅ የተቀረፀው ምስክርነት ወደ ፅሁፍ ተገልብጦ የመዝገቡ አካል እንዲሆን ትዕዛዝ ያስተላለፈ ሲሆን ምስክርነቱን መርምሮ ብይን ለመስጠትም ለህዳር 30 ቀን 2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
 ተከሳሹ ወጣት፤ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ እስከማገኝ ድረስ በንፁህነት የመታየት መብቴን እንዳላጣ፣ የፍርድ ሂደቱ፤ ተመልካችና ጋዜጠኛ ሳይኖር፤ በዝግ ይታይልኝ ሲል ጠይቋል በጠበቃው አማካኝነት፡
፡ ፍ/ቤቱ ግን፤ ክሱ መታየት የጀመረውና የተነበበው ተመልካቾች ባሉበት በግልፅ ችሎት መሆኑን በመጥቀስ፣ አቤቱታውን ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በተከሳሹ የፌስቡክ ገፅ ላይ የተለጠፈው መልእክት፤ “እኔ አይኤስ አይኤስ ነኝ፣ የስራ ድርሻዬም ሰውን እጅና እግሩን አንጋልዬ መያዝ ነው፤ ደሞዝ የሚከፈለኝ በያዝኩት ሰው ልክ ነው፣ የአይኤስ ወታደር ነኝ፤ በቅርቡ ወደ ባቲ ለእርድ እመጣለሁ” የሚል ነው ብሏል – አቃቤ ህግ፡፡ ተከሳሹ በበኩሉ፤ “የፃፍኩት ለቀልድ ነው” ማለቱ ተገልጿል፡፡

መምህር ግርማ የታሰሩት 800ሺህ ብር በማታለል ተጠርጥረው ነው ተጠርጣሪው አስተባብለዋል

      ታዋቂው መምህር ግርማ ወንድሙ የታሰሩት እምነትን መነሻ በማድረግ፣ በተፅዕኖ መኖሪያ ቤት በማሸጥና ገንዘብ አታሎ በመውሰድ ወንጀል ተጠርጥረው መሆኑን ፖሊስ ለፍ/ቤት ያስረዳ ሲሆን ተጠርጣሪው ግን አስተባብለዋል፡፡
ባለፈው ረቡዕ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ዘንድ በአጥማቂነት የሚታወቁት መምህር ግርማ ወንድሙ፤ በተጠረጠሩበት ወንጀል ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ያስፈልገኛል በማለቱ ፍ/ቤቱ 7 ቀን ሰጥቷል፡፡
በተጠርጣሪው ላይ እየተጣራ ያለው የፖሊስ የምርመራ መዝገብ፤ መስከረም 2006 ዓ.ም አቶ በላይነህ ከበደ የተባሉ ግለሰብን ሃይማኖትና እምነትን መነሻ በማድረግ በየካ ክፍለ ከተማ ወሰን ግሮሰሪ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ ከሚገኝ መኖሪያ ቤቱ እስከ ጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም ሸጦ ካልወጡ አስከሬናቸው መውጣቱ የማይቀር መሆኑን በመንገር ግለሰቡ ቦታውን እንዲሸጡ አድርገዋል ይላል፡፡
ግለሰቡም ከባለቤታቸው ጋር በመሆን እንደተባሉት ቤቱን በ800ሺህ ብር ይሸጣሉ፡፡
 ቤቱ በተጠቀሰው ዝቅተኛ ዋጋ እንዲሸጥ ተጠርጣሪው መምህር ግርማ አስተዋጽኦ ነበራቸው ይላል የፖሊስ የምርመራ መዝገብ፡፡ ግለሰቡ ቤታቸውን ከሸጡ በኋላ ተጠርጣሪው “በራዕይ ያየሁት ቦታ “ቦሌ” አለ፤ እሱን ነው መግዛት ያለብህ፣ ቤቱ የተሸጠበትን 800ሺህ ብር አምጣና እንዲበረከትልህ ልፀልይበት” ብለው ወሰዱት፡፡ የግል ተበዳይ ገንዘባቸውን ለማስመለስ ያደረጉት ጥረት እንዳልሠመረላቸውና ከሀገር ወጥተዋል እንደተባሉ የፖሊስ ምርመራ መዝገብ ያብራራል፡፡
 የግል ተበዳይ ጉዳዩ ውሎ ሲያድር ማታለል መሆኑን በመረዳታቸው በመጋቢት 2007 ዓ.ም ወር ገደማ ለፖሊስ ያመለከቱ ሲሆን ፖሊስ ከሄዱበት ሀገር እስኪመለሱ የተበዳዩን ቃልና የምስክሮችን ቃል ሲቀበል መቆየቱን ያትታል፡፡
መምህሩ በበኩላቸው፤ ከሣሽ የተባለውን ግለሰብ ጥቁር ይሁን ቀይ አንድም ቀን አይተውት እንደማያውቁ በመግለጽ ከጀርባዬ የተሴረብኝ ሴራ አለ ሲሉ ለፍ/ቤቱ ተናግረዋል፡፡
 ጉዳዩን የያዘው የፖሊስ የምርመራ ቡድን ከትናንት በስቲያ ተጠርጣሪውን በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወ/ችሎት ያቀረባቸው ሲሆን ግለሰቡ በተጠረጠሩበት የማታለል ወንጀል ቀሪ የምርመራ ስራ ስላለኝ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ይሰጠኝ ብሎ ፍ/ቤቱን ቢጠይቅም ፍ/ቤቱ የ7 ቀን ጊዜ በመፍቀድ ጉዳዩን ለጥቅምት 25 ቀጥሯል፡፡
ተጠርጣሪው ፖሊስ የተጠየቀውን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ የተቃወሙና የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው የጠየቁ ቢሆንም ፖሊስ በዋስ ቢለቀቁ መረጃ ያሸሹብኛል በማለቱ ፍ/ቤቱ የመምህር ግርማን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አድርጓል፡፡

አሜሪካ ስመጣ ሦስት ቦታ ያለው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ይማርከኛል፡፡ ላስቬጋስ  ኪዳነ ምሕረትና ቅዱስ ሚካኤል፣ ዴንቨር መድኃኔዓለምና ሚነሶታ ቅድስት ሥላሴ፡፡ ሃይማኖታቸውን የተረዱ፣ ለአገልግሎት የተጉና ምራቃቸውን የዋጡ ክርስቲያኖች ያሉበት ቦታ፡፡ ወደነዚህ ቦታዎች ስመጣ ከማስተምረው የምማረው ይበልጣል፡፡ በአስቸጋሪው የአሜሪካ ኑሮና ፈተና ውስጥ የቤተ …

ላስቬጋስ – ጎንደር (ዳንኤል ክብረት) Read more »

ጥቅምት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከትናት ጀምሮ የአርበኞች ግንቦት7 አባሎች በሰገን ዞን ኮንሶ ወረዳ ውስጥ ገብተዋል በሚል የፖሊስ አባላት በከተማው የሚገኙ ወጣቶችን ሲያድኑ ከዋሉ በሁዋላ ፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ወጣቶችን ይዘው አስረዋል። በአካባቢው ሰሞኑን በፖሊስ አባላት ላይ የተፈጸመ የተባለ ጥቃትና ወጣቱን የሚያነሳሱ በራሪ ወረቀቶች መበተናቸው ለአሰሳው ተጨማሪ ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ ነዋሪዎች …

ጥቅምት 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ ሰባራ ባቡር አካካቢ ከሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በመከላከያ ምስክርነት ሊቀርቡ ከነበሩት ሦስት እስረኞች መካከል፣ ሁለቱ የማምለጥ ሙከራ ሲያደርጉ አንዱ ሲገደል አንዱ ማምለጡ ተገለጸ፡፡ 

የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ሕዝብ ግንኙነት ተወካይ ምክትል ሰርጀንት ሳህለ ገብርኤል ይትባረክ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ እስረኞቹ ያመለጡት ፍርድ ቤት ደርሰው ለመውረድ ሲቃረቡ የመኪና በር በመስበር ነበር፡፡ በተለያዩ የውንብድና ወንጀሎች 31 ዓመት የተፈረደበት አንደኛው እስረኛ ሲያዝ፣ በተመሳሳይ ወንጀል የዘጠኝ ዓመት ከስድስት ወራት ፍርደኛ የሆነውና ተጨማሪ ሦስት ክሶች የነበሩበት ሁለተኛው እስረኛ ለማምለጥ ባደረገው ሙከራ ተገድሏል፡፡

እስረኛውን አሳዶ ለመያዝ ከፍተኛ ጥረት የተደረገ ቢሆንም መንደር ውስጥ በመግባቱ ሁኔታዎች አስቸጋሪ በመሆናቸው፣ በመጨረሻ መተኮስ ግድ እንደነበር የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው አስረድተዋል፡፡ ‹‹እስረኛውን ረዥም ርቀት ተከታትለነዋል፡፡ ላለመተኮስ ከፍተኛ ጥረት  ተደርጓል፡፡ ነገር ግን መንደር ውስጥ በመግባቱ የተወሰደው ዕርምጃ የግድ የመጨረሻው አማራጭ ሆኗል፤›› ብለዋል፡፡

ለማምለጥ ከሞከሩት ሁለት እስረኞች ጋር በአንድ መኪና ውስጥ የነበረው ሌላ እስረኛ ለመንቀሳቀስ ምንም ዓይነት ሙከራ አድርጎ እንዳልነበር የገለጹት ምክትል ሰርጀንት ሳህለ ገብርኤል፣ ያመለጠውን እስረኛ ለመያዝ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ክትትሉ እየተደረገ ያለው ከአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጋር መሆኑንና የእስረኛው ፎቶግራፎችም መበተናቸውንም አክለዋል፡፡

አልፎ አልፎ እስረኞች ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ሲሉ የማምለጥ ሙከራ እንደሚያጋጥም፣ ነገር ግን እስካሁን አምልጦ ሳይያዝ የቀረ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡ ሪፖርተር የእስረኞቹን ሙሉ ስም በሚመለከት መረጃ ያለው ቢሆንም የሕዝብ ግንኙነት ተወካዩ እንዳይገለጽ ጠይቀዋል፡፡

 

የ.ተ. መ.ድ. 3ኛ ኮሚቴ በኤርትራ ውስጥ ስለሚገኘው የሰብአዊ መብት ሁኔታ ሪፖርት አድምጧል። ሪፓርቱን በተመለከተ በመንግሥታቱ ድርጅት የኤርትራ አምባሣደር ግርማ አስመሮም መልስ ሰጥተዋል።

ጥቅምት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎች እንደሚሉት ከድርቁ ጋር ተያይዞ የውሃ ችግሩ በመባባሱ ፣ ህዝቡ ውሃ ለማግኘት በእጅጉ ተቸግሯል። የውሃ ችግሩ በመባባሱና በየአካባቢው የሚታየው የውሃ ጀሪካም ብዛት ” ሳምንቱን ” ቢጫው ሳምንት” አስብሎታል በማለት ነዋሪዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። የውሃ ችግሩ ከሰቆጣ በተጨማሪ በተለያዩ አገሪቱ ክፍሎች ይታያል። በሌላ በኩል ደግሞ ክልሉን እመራዋለሁ የሚለው …

ጥቅምት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአርባምንጭ ምንጮች እንደተናገሩት በቅርቡ የአርበኞች ግንቦት 7 ደጋፊዎች ኢህአዴግን የሚያወግዙና ወጣቱ ለመብቱ እንዲነሳ የሚቀሰቅሱ በራሪ ወረቀቶችን ከበተኑ በሁዋላ፣ ድርጊቱን ፈጽመዋል ብለው የጠረጠሩዋቸውን ወጣቶች በጅምላ ለማሰር ከትናንት ጀምሮ አሰሳ አካሂደዋል። አሰሳውን ተከትሎ የ70 አመት አዛውንት እናትን ጨምሮ ሴቶችና ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ወጣቶች ተይዘዋል። ከተያዙት መካከል የሰማያዊ …