ጥቅምት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ ሞያሌ፣ የመንግስት ባለስልጣናት ወጣቶችን ለውትድርና ለመመዝገብ በድምጽ ማጉያ የታገዘ ቅስቀሳ ቢያካሂዱም፣ አንድም ለምዝገባው ፈቃደኛ ሆኖ የሄደ ወጣት አለመኖሩን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ። ወጣቶቹ የተደረገላቸውን የስብሰባ ጥሪ ባለመቀበላቸውም፣ መንግስት በሞያሌና አካባቢዋ አዳዲስ ምልምል ወታደሮችን ለመመዝገብ ያቀደው እቅድ ሳይሳካ ቀርቷል። አምና 10ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ወጣቶችን ለወትድርና …

ጥቅምት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-35ኛ አመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ ያለው ብአዴን ፣ በአማራ ክልል የሚኖረው ህዝብ ለበአሉ ማድመቂያ ገንዘብ እንዲያዋጣ እያስገደደ ነው። ነጋዴዎች ከብአዴን ጽ/ቤት የተጣለባቸውን ክፍያ ያለፍላጎታቸው በግድ እንዲከፍሉ ታዘዋል። ከፍተኛ የረሃብ አደጋ በክልሉ ባንዣበበት በዚህ ወቅት፣ ብአዴን እንደ ህወሃትና ኦህዴድ መቶ ሚሊዮኖችን አፍስሶ በአሉን ለማክበር መሞከሩ ፣ ከታሪክ …

ጥቅምት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኬንያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሳምብሩ ምስራቃዊ ኢዞሎ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ሎሲሳ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ገቡ ያላቸውን አስራ አምስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ማሰሩን አስታውቋል። ባለፈው እሁድ ሃያአራት፣ ሰኞ ደግሞ ስድስት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በአካባቢው በታጣቂዎች በከበባ መያዛቸውን ገልጸዋል።ስደተኞቹ በሕገወጥ መንገድ ካለምንም ሕጋዊ ፍቃድ ድንበር አቋርጠው እንደሚገቡና አስራ አምስቱ ኢዞሎ …

በሣይንሳዊው መላ ምት ዘመናዊው የሰው ልጅ ምድር ላይ ተገኘ የሚባለው ከዛሬ 200,000 ዓመት በፊት ነው። ይኽ በሣይሳዊ አጠራሩ ሆሞ ሳፒያንስ (Homo Sapiens)፥ በላቲን ትርጓሜው ደግሞ «ጥበበኛው ሰው» አለያም «አዋቂው ሰው»፣ «ብልሁ ሰው» የሚል ስያሜ ያገኘው ዘመናዊ ሰው ምንጩ ከአፍሪቃ ብሎም ከኢትዮጵያ እንደሆነ ይነገራል።

በጠቅላይ ጽ/ቤቱ ትግበራው የተጀመረው ዘመናዊው የኹለትዮሽ ሒሳብ አሠራር፣ በሥልጠና ተደግፎ ግልጽና ተጠያቂ በኾነ መንገድ እስከ አጥቢያ መዋቅር እንዲተገበር የጋራ አቋም ተይዟል ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ላለፉት አራት ቀናት ሲካሔድ የቆየው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 34ኛ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ፣ ዛሬ ቀትር ላይ ተጠናቋል፡፡ የሀገር ውስጥ ኃምሳ አህጉረ ስብከት እና የውጭ ስምንት አህጉረ ስብከት የሥራ ክንውን …

ዓቃቤ ሕግ ክስ እንዲመሠርት ቀን ተቆርጦለታል 

ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀም ከፍተኛ የሆነ ጉቦ በመቀበል አገራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከቀረጥ ነፃ ተሽከርካሪዎችን በማስገባት፣ በዘመዶቻቸውና በጓደኞቻቸው ስም ሀብት በማስቀመጥ፣ እንዲሁም ለመንግሥት መግባት የነበረበትን

ታክስና ቀረጥ ለግላቸው በማድረግ ከባድ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ወንድሙ ቢራቱ፣ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

ፍርድ ቤቱ ትዕዛዙን የሰጠው፣ በተጠርጣሪው ላይ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ምርመራውን ማጠናቀቁን ካስታወቀ በኋላ ነው፡፡ ቡድኑ ምርመራውን ጨርሶ ለዓቃቤ ሕግ ማስተላለፉን ገልጾ፣ ዓቃቤ ሕግ አቶ ወንድሙን ጨምሮ በአራት ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ ለመመሥረት የሚያስችለውን በወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ 109 (1) መሠረት የ15 ቀናት ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡

የአቶ ወንድሙ ጠበቃ የተጠየቀውን ጊዜ በመቃወም፣ ደንበኛቸው ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀው ነበር፡፡ ዓቃቤ ሕግ ተጠርጣሪውን ዋስትና በሚያስከለክል ወይም በማይከለክል አንቀጽ ስለመክሰሱ ማወቅ እንደማይቻል ፍርድ ቤቱ ገልጾ፣ የዋስትናውን ጥያቄ ውድቅ በማድረግ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡  

በመሆኑም ዓቃቤ ሕግ በአቶ ወንድሙና በሦስት ተጠርጣሪዎች ላይ ጥቅምት 19 ቀን 2008 ዓ.ም. ክስ እንዲያቀርብ ታዟል፡፡ 

 

ከዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት አምደኞች /ብሎገሮች/ እና ጋዜጠኞች እሥር ቤት ቀርቶ የነበረው በፈቃዱ ኃይሉ በሃያ ሺህ ብር ዋስ እንዲፈታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርጅ ቤት አሥራ ዘጠነኛ ወንጀል ችሎት አዝዟል።

በሀ/ስብከቱ÷ 55 ከእስልምና 115 ከሌሎች እምነቶች በጥምቀተ ክርስትና ተመልሰዋል   በመካከለኛው ምሥራቅ(በሊባኖስ እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ) ሀገረ ስብከት፣ በዱባይ ከተማ ቤሪያ በተባለ አካባቢ፣ በቤተ ክርስቲያን ስም የሚነግዱ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ምንደኞች ከቅዱስ ሲኖዶስ ዕውቅና ውጭ ስለከፈቱት ኮሌጅ ውሳኔ እንዲሰጥ ሀገረ ስብከቱ ጠየቀ፡፡ ሀገረ ስብከቱ፣ ዛሬ ሦስተኛ ቀኑን በያዘው የመንበረ ፓትርያርክ የሰበካ አስተዳደር አጠቃላይ ጉባኤ 34ኛ ዓመታዊ …

ኢሳት (ጥቅምት 10 ፡ 2008) በኢትዮጵያ ተከስቶ ያለው የድርቅ አደጋ እስከተያዘው አመት ማጠናቀቂያ ነሀሴ ወር ድረስ ቀጣይ ሊሆን እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዛሬ ማክሰኞ አሳሰበ ። በሀገሪቱ ተከስቶ ያለው የምግብ እርዳታ ፍላጎትም ከአራት አመት በፊት በአፍሪካ ቀንድ ተከስቶ ከነበረው አጠቃላይ መጠን ጋር ሲነጻጸር ከፍ ብሎ መገኘቱን ድርጅቱ ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል። በጉዳዩ ዙሪያ ከለጋሽ ሀገራት የተጠየቁት …

ጥቅምት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ረዩተርስ እንደዘገበው የኢህአዴግ መንግስት ባለፉት 10 ወራት 1 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከ20 ቢሊዮን ብር ያላነሰ ገንዘብ ከግል የውጭ አበዳሪ ባንኮች ከተበደረ በሁዋላ፣ አሁን ደግሞ 2 ቢሊዮን ዶላር ወይም 40 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመበደር በድርድር ላይ መሆኑን ረዩተርስ ዘግቧል። አዲሱ ብድር የኢትዮጵያን እዳ ከ32 ቢሊዮን ዶላር ወይም …

ጥቅምት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች እንደገለጹት በአሜሪካ ጊቢ ፣ በአዲስ ከተማና በሌሎች አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ለአመታት ከኖሩበት ቤት ያለበቂ ካሳ እና ተለዋጭ ቤት ቤቶቻቸው እየፈረሰባቸው ነው። መንግስት ቤታቸው ለሚፈርስባቸው የኮንዶሚኒየም ቤቶችን ተላዋጭ አድርጎ ቢሰጥም፣ ተከራዮች ግን ኪራዩን የመክፈል አቅም የላቸውም መንግስት ከህዝቡ ጋር ሳይማከር የሚወስደው እርምጃ፣ …

ጥቅምት ፲ (አስር) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንድ ዓመት ከአምስት ወር በሽብር ክስ ተከሰው በእስር ሲንገላቱ የነበሩት የዞን 9 አምደ መረብ ጸሐፍት ውስጥ ብቻውን እንዲቀር ተደርጎ የነበረው ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ክሱን ውጪ ሆኖ እንዲከታተል የሃያ ሽህ ብር የዋስትና መብት የልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት19ኛ ወንጀል ችሎት በመፍቀዱ ከእስር ተለቋል። በተጨማሪም የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

“ሦስተኛ ሲኖዶስ አቋቁመዋል” በሚል ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱን ለመክሠሥ ተዘጋጅተው ነበር “ቤተ ክርስቲያን ለ30 ዓመት በሰላም ኖራ እየተናወጠች ትገኛለች”/ሊቀ ካህናት መርዓዊ ተበጀ/ “መጥነው እንዲያወሩ ዕድል ቢሰጣቸው ተዋረዱ፤ የእግዚአብሔር ሥራ ነው”/ብፁዕነታቸው/   ከሦስት ዐሥርት ዓመታት በላይ በጀርመን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሓላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩትና ከደቡብ ምሥራቅ እና ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ጋር ውዝግብ ውስጥ የገቡት፣ ሊቀ …

የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ መቃረብን ተከትሎ መስዋእት ከሆኑት  የዞን ዘጠኝ ጦማር አባላት ውስጥ የሽብር ክሱ ወደ ወንጀል ክስ ተቀይሮ ዛሬም በግፍ እስር በብቸኝነት የሚገኘው በፍቃዱ ዘ ኃይሉ አመጽ ለመቀስቀስ አስበህ ነው የጻፍከው የተባለውን ጽሁፍ እንዲከላከል ተወስኖበታል፡፡ ይህ የአመጽ መቀስቀስ የተባለው ጽሁፍ ራሱን ሳይሆን የበፍቃዱን የማእከላዊ ምርመራ ቃል ብቻ የተመለከተው ፍርድ ቤቱ ቃሉን ብቻ መሰረት በማድረግ ይከላከል በማለት የማእላዊ ምርመራን በማሰቃየት ውስጥ የተሰጠ ቃል ተቀብሎታል ማለት ነው ?

በአስገዳጅ ሁኔታ የተገኘ ማስረጃ እንደማስረጃ አይቆጠርም የሚለው የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው የሚገባለው እና በፍቃዱ ከጓዶቹ ጋር ሆኖ ይከበር! ሲል የነበረው ሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 19.5 እንዲህ ይላል

‹‹የተያዙ ሰዎች በራሳቸው ላይ  በማስረጃነት ሊቀርብ የሚችልየእምነት ቃል እንዲሰጡ ወይም ማናቸውንም ማስረጃ እንዲያምኑ አይገደዱም፡፡ በማስገደድ የተገኘ ማስረጃ ተቀባይነትአይኖረውም፡፡››

ከወራት በፊት የጦማርያኑን እስር አንደኛ ዓመት አስመልክቶ የመብት ጥሰቶችን ዞን ዘጠኝ ጦማር ባስታወሰበት ወቅት በበፍቃዱ የደረሰበት የማሰቃየት ወንጀል እንዲህ ገልጾት ነበር ፡፡

‹‹ማዕከላዊ ምርመራ በቆየሁባቸው ቀናት ከእሁድ በስተቀር ጠዋት ከሰአትማታ እየተጠራሁ በዛቻ በአጸያፊ ስድብ ጭካኔ የተሞላበት ግርፊያ ጥፊና እርግጫ አንዲሁም ከአቅሜ በላይ የሆነ ስፓርት እየሰራሁቃሌን እንድሰጥ ተገድጃለሁ፡፡ የተያዝክበትን ድብቅ አጀንዳ ንገረን በማለት ራሴን እንድወነጅል ተገድጃለሁ፡፡

  1. መርማሪው በመጀመሪያ ቀን ምርመራ በጥፊ መማታት የጀመረ ሲሆን እያንዳንዱን ጥያቄ ከጠየቀኝ በኋላ በጥፊ ይመታኝ ነበር
  2. የዞን9 ዓላማ ጠይቆኝ ስነግረው ድብቁን አውጣ በማለት መሬት ላይ አንድቀመጥ እና ያደረኩትን ነጠላ ጫማ እንዳወልቅ አዞኝ በኮምፒውተር ገመድ እግሬን መግረፍ ጀመረ፡፡ በተጨማሪም በሆዴአንተኛ በማዘዝ እና እግሬን አጥፌ ከፍ አንዳደርገው በማድረግ ውስጥ እግሬን ገርፎኛል፣ግርፊያው ውስጥ እግሬን ሲለበልበኝ ነበር ፡፡
  3. ድብቁን አጀንዳህን ካልተናገርክ ነገ እዘለዝልሃለሁ በሚል አስፈራርቶኛል፡፡
  4. ድምጽ እንዲያፍን ሆኖ ወደተሰራው የስብሰባ አዳራሽ ተወስጄ በጥፌ እየደበደቡኝ የዞን9አላማ ተናገር ተብዬ ተደብድቤያለሁ፡፡ ስቃዬ ሲበዛብኝም የፈጠራ ታሪክ እንዳወራ ተገድጃለሁ፡፡ እኔ የምጽፈው ኢትዮጵያ ውስጥ አብዬት ለማስነሳት ነው ብዬ እንድፈርምም አስገድደውኛል››
  5. በምርመራ ወቅት እጄ በካቴና እነደታሰረ ለሰአታት ቁጭ ብድግ አንድል ተገድጃለሁ፡፡
  6. መርማሪው በአንድ ወቅት አራት የዞን9 አባላት ሆናችሁ ስለአላማው የተወያያችሁትን በቃል መስጫው ክስ ላይ ልጽፍ ነው ሲለኝ አንደዛ አይነት ውይይት ማድረጋችንን አላስታውስም ስለው እንዴት አታስታውስም ብሎ በጥፊ መማታት ጀመረ። በተደጋጋሚ ከመደብደብም በላይ እስክስታስታውስ እዚሁ ታድራታለህ በማለት ድብደባው በመቀጠሉ አስታውሳለሁ ብዬ ተገላገልኩ ፡፡ የሰጠሁት ቃል ላይም እንደፈለገው አድርጎ ጻፈው፡፡  እኔም በድብደባ ብዛት መርማሪው አለ ብሎየጻፈውን ፈርሜያለሁ ፡፡
  7. ዞን9 ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት የሌለው ከሆነ ይህንን ህዝብ አንዴት ነው ነጻ የምታወጡት በሚል ሲጠይቁኝ የነጻ አውጪነት ሚና የለንም ስላቸው ከወንበሬአንድነሳ አዘዙኝ፡ ከዚያም በቆምኩበት ግራ ብብቴን እና እጄን በአንድ እጁ አንዳልወድቅ ወጥሮ ይዞ በእግሩ ጭኔን በሃይል ደበደበኝ ፡፡ ከድብደባው በማስከተል ደግሞእግሬ መሃል እግሩን በማስገባት ወደግራ እና ወደቀኝ በመምታት ተዘርጥጬ እንድቆይ በማድረግ እጄን ወደላይ አድርጌ እግሬ ግራና ቀኝ ተዘርጥጦ ( በተ<a></a>ለምዶ ስፕሊት ሚባለው) በግራ እና ከቀኝ በመደብደብ እጄን ወደላይ አድርጌ እነድመረመር ተደርጌያለሁ፡፡ከዚህ ምርመራ በኋላ ለሁለት ቀን እያነከሰኩ ነበር፡፡››

በፍቃዱ ሃሳቡን በነጻነት በመግለጹ ብቻ እንደወንጀለኛ ተቆጥሮ እስካሁንለ542 ቀናት አግባብ ባልሆነ እስር ላይ ይገኛል፣ በዚህ ሁኔታ የተሰጠ ቃል ተቀባይነት ማግኘት ስለማይገባው በፍቃዱ ሃይሉእሮብ ከቤተሰቡ ጋር ሊቀላቀል ይገባል ፡፡

ጥቅምት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእስር ላይ የሚገኙትን የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ህገወጥ እስር አስመልክቶ የእንግሊዝ ባለስልጣናት ነገ በሚጀመረው የኢትዮጵያና የእንግሊዝ የንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ ላይ ሊያነሱት እንደሚገባ አቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ የሚከታተለው ሪፕሪቭ የተባለው ተቋም ጠይቋል። የንግድ እና የኢንቨስትመንት ስብሰባው ከፍተኛ ቦታ የተሰጠው እንደመሆኑ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ግራንት ሻፕስ ለኢትዮጵያ …

ጥቅምት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-18 የእስር አመታት በግፍ ተፈርዶበት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የፔን ካናዳ የ2015 አሸናፊ ሆነ መመረጡን ድርጅቱ አስታውቋል። ለብዙዎች የዲሞክራሲ ሃይሎች የጽናት ምልክት ተደርጎ የሚቆጠረው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በሽብር ወንጀል ተከሶ ያለፉትን ሶስት አመታት በእስር ቤት አሳልፏል። የእስክንድር ስራዎቹ ድንበር እና ባህል ተሻጋሪ ናቸው በማለት ያወደሰው …

ጥቅምት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎች “መሰረታችን ሕገ መንግስቱ ነው ተብሎ የወልቃይት ነዋሪዎች ቋንቋን ብቻ መሰረት ያደረገና የሕዝቡን ስነ ልቦናዊ፣ ባሕላዊ ወግን ያላማከለና ያላጠቃለለ ክልላዊ አከላለል በማድረግ የወልቃይት ሕዝብ የማይፈልገውንና የማያምንበትን በመጫን በግድ ወደ ትግራይ እንድንካለል መደረጋችን በውስጣችን ያለውን ማንነታችንን በመጨፍለቅ እንድንቀበል እየተደረግን ነው ፣ዛሬ ስነ ልቦናችን የማይቀበለውን ሕወሃት በዘዴ ማንነታችንን ለማሸማቀቅ …

ጥቅምት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሽብርተኝነት ተከሶ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኘው አቶ አበበ ካሴ እስር ቤት ውስጥ በማንነቱ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየደረሰብኝ ነው ሲል ለፍርድ ቤቱ አቤቱታውን አሰምቷል፡፡ በእነ አበበ ካሴ የክስ መዝገብ ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው አቶ ታጠቅ አስማረ የተከላካይ ጠበቃ ለማቅረብ ዛሬ ጥቅምት 9/2008 ዓ.ም ፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት ለልደታ ፍርድ …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ አሜሪካን ግቢ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ወደ ሶስት ሺ የሚጠጉ የንግድ ተቋማት ቦታው ለልማት ይፈለጋል ተብሎ ንብረታቸው መታሸጉን ነዋሪዎች ለኢሳት ገለጡ። የንግድ ተቋማት መታሸግን ተከትሎም የአካባቢው ነዋሪዎች መሰረታዊ የፍጆታ እቅርቦቶችን ለማግኘት ተቸግረው እንደሚገኙ የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት በሰጡት ቃለ-ምልልስ አስታውቀዋል። ወፍጮ ቤቶች ሱቆችና ምግብ ቤቶች ከታሸጉበት የንግድ ተቋመት መካከል እንደሚገኙበት …

 

ሰሞኑን የቀድሞው የደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣን ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ የጻፉትንና ‹አብዮቱና ትዝታዬ› የተሰኘውን መጽሐፍ ሳነብብ ስለ አቡነ ቴዎፍሎስ አሟሟት የጻፉትን አገኘሁ፡፡ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ እስካሁን ከጻፉት የቀድሞ ባለሥልጣናት በሁለት ነገር ተለይተውብኛል፡፡ የመጀመሪያው በቡድንና በጋራ ለሠሯቸው ስሕተቶች ይቅርታ መጠየቃቸው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በሁሉም ወገኖች የተፈጠሩትን ያለፉትን ስሕተቶች ለማረም ያስችላል ያሉትን የጋራ መድረክ ሐሳብ ማቅረባቸው ነው፡፡
ምንም እንኳን በዘመነ ደርግ የተፈጠሩት ስሕተቶችና ጥፋቶች ደርግ ብቻውን ያደረጋቸው ባይሆኑም አንዱና ዋነኛው ተዋናይ ደርግ ነበርና ለተሠሩት ጥፋቶች ይቅርታ መጠየቃቸው ለሌሎች አካላትም አርአያነት ያለው ነው፡፡ ዋናው የደርጉ መሪ ያ ሁሉ ጥፋት ሲሠራ ‹እኔ አላውቅም ነበር›› ብለው በካዱበት ሁኔታ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ የራሳቸውን ይቅርታ መጠየቃቸው ለሰማዩም ለምድሩም ጉዟቸው ምትክ አልባ ተግባር የሚሆን ነው፡፡ ክብር ይስጥልን፡፡

ያ ዘመን በተሻለ እንመራለን ብለው የተነሡ ፖለቲካዊ ኃይሎች እንደየዐቅማቸው ስሕተቶችን የሠሩበትና ጥፋቶችን ያጠፉበት ዘመን ነው፡፡ ሁሉንም ጥፋት ለደርግ በመስጠት እጅን መታጠብ አይቻልም፡፡ እርሳቸው እንዳሉትም የደርግን ባለ ሥልጣናት ብቻ ወደ ፍርድ ከማቅረብ ይልቅ የነበረው ጥፋት ከየአቅጣጫው የሚፈተሽበትና ሁሉም እንደ ጥፋቱ የሚከሰስበት ወይም የሚወቀስበት አለበለዚያም ደግሞ ይቅርታ የሚጠይቅበት መንገድ ቢመቻች መልካም ነበር፡፡ ችግሩንም በተቻለ መንገድ ሊፈታው የሚችለው ሁሉን አቀፍ የሆነው አካሄድ ነበር፡፡ አሁንም መሪ ተዋናዮቹ ከማለፋቸው በፊት ሁሉም እንደየድርሻው ኃላፊነቱን የሚወስድበትና ይቅርታ የሚጠይቅበት ሥርዓት ቢመቻች መልካም ነበር፡፡
ያ ካልሆነ ግን ሥርዓት በተቀየረና ሕጎች በተሻሻሉ ቁጥር ተከድነው የሚንተከተኩ ነገሮች እንደገና የመውጣታቸውና በመድረቅ ላይ ያሉ ቁስሎችን የማመርቀዝ ዕድላቸው ሰፊ ነው፡፡ ፕላስተር የተለጠፈበት ቁስል ሁሉ አይድንምና፡፡
ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ በጻፉት መጽሐፍ ላይ ግን ጥያቄ እንዳነሣ ያደረገኝ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን የተመለከተ፡፡ በመጽሐፉ ላይ የሚከተሉት ነገሮች ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ መገደል ጋር ተያይዘው ቀርበዋል፡፡
1.      1. ቤተ ክህነት መሬቷ ስለተነጠቀ አብዮቱን እንደተቃወመች

እግዚአብሔር የለም ብሎ የሚክደው ኮሚንስታዊ መንግሥት ሲመጣ ቤተ ክህነት ባትቃወም ነበር የሚገርመው፡፡ በተለይም የመሬት ለአራሹ አዋጅ የጭሰኛውን የዘመናት ጥያቄ የመለሰ ቢሆንም የፈጠራቸውም ጥያቄዎች ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የተመሠረተው በመሬት ላይ በመሆኑ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማትም የመተዳደሪያ መሬት ነበራቸው፡፡ ልክ ዛሬ የመተዳደሪያ ሕንጻና ገንዘብ እንዳላቸው ሁሉ፡፡ ነገሥታቱና መኳንንቱ አብዛኞቹ ክርስቲያኖች ስለነበሩም ለቤተ ክርስቲያን የመሬት ስጦታ ሰጥተዋል፡፡ የመሬት ላራሹ ዐዋጅ ሲታወጅ ግን የካህናትንና የገዳማውያን ሁኔታ ግምት ውስጥ ሊያስገባ አልቻለም፡፡ እንደ አንድ በመሬት የሚተዳደር ኢትዮጵያዊ ዜጋ ካህናቱና መነኮሳቱ ለአንድ ገበሬ የተመደበውን መሬት እንዲያገኙ እንኳን አልተደረገም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ስም መኳንንቱ ይዘውት የነበረው  መሬት ከግምት ውስጥ አልገባም፡፡ ቢያንስ በቶፍነት ሥርዓት ውስጥ የነበሩትን ካህናት እንኳን አብዮቱ ሊያያቸው አልፈቀደም፡፡ ሲሆን ቅርስና ባሕል ጠባቂ እንደመሆናቸው በተለይ ገዳማቱ ተጨማሪ የጋራ መሬት ያስፈልጋቸው ነበር፡፡ የወቅቱ የደርግ ባለሥልጣናት ግን ቤተ ክርስቲያኒቱን ከመጀመሪያው በጠላትነት ስለፈረጁ የድርሻዋን እንኳን ለመስጠት አልቻሉም፡፡ በምዕራብ ሸዋ የነበረው ደብረ ጽሙና ገዳም መሬቱን ሙሉ በሙሉ አጥቶ ሊፈርስ ሲል ኮሎኔል ደበላ ዴንሳ በሰጡት መመሪያ ጥቂት መሬት አግኝቶ መትረፉን አረጋውያኑ ዛሬም ከምስጋና ጋር ያስታውሱታል፡፡
ገዳማትና አድባራቱ ከልክ በላይ የያዟቸው መሬቶች ከነበሩ መጠኑን መቀነስና በቂ ነው የተባለውን ያህል መስጠት እንጂ ያላቸውን በሙሉ ነጥቆ በድህነት እንዲማቅቁ ማድረግ በምንም መልኩ ፍትሐዊ ሊሆን የማይችል ነው፡፡ ‹‹ኮሚኒዝም ማለት ድህነትን እኩል ማካፈል ነው – an even distribution of poverty›› የተባለው ነው የተፈጸመው፡፡ ፍትሐዊነት ያላገኘውን አካል እንዲያገኝ አድርጎ እኩል ማድረግ እንጂ ያገኘውን እንዲያጣ አድርጎ በድህነት ማስተካከል አይደለም፡፡ ይኼንን የወቅቱ ቤተ ክህነት ብትቃወመውና ከአብዮቱ ጋር ለመጓዝ ቢቸግራት ተገቢ ነው፡፡ ያውም በበቂ ሁኔታ አልሄደችበትም፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ በ1967 ዓም ለዘመን መለወጫ ባስተላለፉት መልእክት ‹‹በጦር ኃይሉና በሕዝቡ የተጀመረው የተቀደሰ እንቅስቃሴ መልካም ውጤት እንዲያስገኝ ፈጣሪያችን ይርዳን›› ነበር ያሉት፡፡(ሐዲስ ሕይወት፣ ግንቦት 1፣ 1967 ዓም፣ ገጽ 17)፣ የዕድገት በኅብረት ዘመቻንም ፓትርያርኩ በበጎ ነበር ያዩት፤ ይህም ጥቅምት 3 ቀን 1967 ዓም በሰጡት መግለጫ ላይ ተመልክቷል፡፡(ገጽ 17)
ይኼ ጉዳይ በከተማ ቦታና ትርፍ ቤት ዐዋጁም ጊዜ ተከሥቷል፡፡ ብዙ ምእመናን ብጽዐት ገብተው እየሠሩ፣ ሲሞቱም እያወረሱ ለአድባራትና ገዳማት የሰጧቸው ቤቶች ነበሩ፡፡ እነዚህ ቤቶች በሀገር ቤት ብቻ ሳይሆን በኢየሩሳሌም ከተማ ሳይቀር ይገኙ ነበር፡፡ የከተማ ቦታና ትርፍ ቤት ዐዋጅ ሲታወጅ ግን ለአንድ ሰው የሚኖርበት የ500 ካሬ ሜትር ቦታና አንድ ቤት ሲፈቅድ ለአድባራትና ገዳማት ግን ምን አልተፈቀደም፡፡ በሙሉ ነው የተወረሰው፡፡ ራሳቸው ፍሥሐ ደስታ እንደመሰከሩት ዐዋጁ ጠላ ሽጣ፣ ማገዶ ቸርችራ ድኻዋ የሠራቺውን፣ ኮርያና ኮንጎ ዘምተው ባገኙት የደም ዋጋ መለዮ ለባሾች የገነቡትን ሁሉ ሀብት ከተትረፈረፋቸው ጋር እኩል በመውረሱ ‹‹ብዙዎች አብዮቱን የደገፉ ጭቁኖች ከበዝባዦች ጋር አብዮቱን ያጥላሉ ጀመር››(ገጽ 160)፡፡
ከነዚህ በዐዋጁ ከተጎዱት መካከል አብያተ ክርስቲያናቱ አንዱ ናቸው፡፡ ቢያንስ የተወሰነውን ቤት እንዲያገኙ መደረግ ነበረባቸው፡፡ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቱን ደርግ የተመለከተበት መነጽር ችግሩን እንዳያይ የሚጋርደው ነበር፡፡ ለዚህም ነው ቤተ ክህነት ለውጡን በበጎ ልታየው ያልቻለቺው፡፡ በርግጥ መንግሥት 4 ሚሊዮን ብር ምትክ ካሣ ሰጥቻለሁ ብሎ ነበር፡፡ በጎላ ወስዶ በጭልፋ መመለስ ማለት እንዲህ ነው፡፡ ያውም አራት ሚሊዮን ብሩ ሳይጨመር ሳይቀነስ በደርግ ዘመን ሁሉ የኖረ ነው፡፡
አቡነ ቴዎፍሎስ በ60ው ባለ ሥልጣናት የግፍ ግድያና በንጉሠ ነገሥቱ ሞት በእጅጉ አዝነው ነበር፡፡ የንጉሠ ነገሥቱን አስከሬን ወስደው በክብር ለመቅበር በነሐሴ 1967 ዓም ደርግን ጠይቀው አልተፈቀደላቸውም፡፡ ከዚህም አልፎ ለንጉሠ ነገሥቱ በይፋ የፍትሐት ጸሎት እንዳያደርጉም ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው(ፍሥሐ ደስታና ሌሎችም ቢዘሉትም)፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ ከዚህ በኋላ ነው ለውጡን በሥጋት ማየት የጀመሩት፡፡
2     2. አቡነ ቴዎፍሎስ የራሳቸውን ወገኖች በመሾም በአብዮቱ ላይ ውስጥ ውስጡን ሤራ እንደሠሩ
አቡነ ቴዎፍሎስ የራሳቸውን ሰዎች ሾሙ ያሰኛቸው ሦስት አባቶችን በጵጵስና መሾማቸው ነው፡፡ ደርግ መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን ተለያይተዋል፤ እንዱ በሌላው ጣልቃ አይገባም ብሎ ዐወጀ፡፡ ፓትርያርኩ ይህንን ተከትለው ደርግን ሳይጠይቁ ሦስት አባቶችን ሾሙ፡፡ አቡነ ጳውሎስን፣ አቡነ ባስልዮስና አቡነ ጴጥሮስን፡፡ ሦስቱም አባቶች በነበራቸው ዕውቀት የተሾሙ እንጂ ለአቡነ ቴዎፍሎስ በነበራቸው ዝምድና አልነበረም፡፡ በሀገር ልጅነትም ሆነ በዝምድና አይገናኟቸውም ነበር፡፡ ደርግን ተደፈርኩ አስብሎ ፓትርያርኩን እንዲያሥር ያደረገው ይኼ የፓትርያርኩ ሳያስፈቅዱ መሾማቸው ነው፡፡ ያሠረውም ፓትርያርኩንና አዲስ የተሾሙትን ኤጲስ ቆጶሳትን ነው፡፡  
3  3. አቡነ ቴዎፍሎስን በተመለከተ የቤተ ክህነት ሰዎች ለመንግሥት አቤቱታ አቅርበው ነበረ ፡፡
  በሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ መጽሐፍ ላይ የቤተ ክህነት ሰዎች አቡነ ቴዎፍሎስን በተመለከተ ያቀረቧቸው ክሶችና አቀራረቡን ገልጠውታል፡፡ የመጀመሪያው ክስ አቡነ ቴዎፍሎስ አባ መልእክቱ ተብለው መነኩሴ እያሉ በአቡነ ጴጥሮስ ግድያ ላይ እጃቸው አለበት የሚለው ነው፡፡ አቡነ ቴዎፍሎስ ወደ አዲስ አበባ ከቤተሰቦቻቸው ጠፍተው የመጡት በ1920 ዓም ነው፡፡ የሄዱትም በአዲስ ዓለም ማርያም ወደነበሩት ሐዲስ ተክሌ ዘንድ ነው፡፡ ሐዲስ ተክሌ በቀለም አያያዛቸው ስለወደዷቸው አቀረቧቸው፡፡ አባ መልእክቱ ከአዲስ ዓለም ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው በ1930 መነኮሱ፡፡ ጣልያን ሀገሪቱን ሲወር እርሳቸው የመምህራቸው የሐዲስ ተክሌ ደቀ መዝሙር ሆነው በአዲስ አበባ ነበሩ፡፡
በወቅቱ የነበሩት አባቶች የጣልያን ወረራን በተመለከተ ሁለት ዓይነት ሐሳብ ነበራቸው፡፡ እንደ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስና አቡነ ሚካኤል ያሉት ከዐርበኞች ጋር ሆነው ጣልያንን ለመፋለምና ሀገሪቱን ነጻ ለማውጣት ወሰኑ፡፡ ሌሎች አባቶች ደግሞ ሕዝቡ ያለ እረኛ መቅረት የለበትም የሚለውን ሐሳብ ደግፈው የሊቃውንት ጉባኤ በማቋቋም ወደ ሀገራቸው የሄዱትን  ግብጻዊውን አቡነ ቄርሎስን ተክተው መሥራት ጀመሩ፡፡
አቡነ ቴዎፍሎስ የአቡነ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር እንደመሆናቸው መምህራቸውን ተከትለው ከማገልገል ያለፈ በአቡነ ጴጥሮስ ላይ በተፈጸመው ግፍ እጃቸው ነበረበት የሚል ምንም ዓይነት ማስረጃ እስካሁን አልቀረበም፡፡ ደግሞም በዚያ ጊዜ በነበራቸው ሁኔታ ይህንን ለመፈጸም የሚበቃ ሥልጣን አልነበራቸውም፡፡ የጠሉትን ሰይጣን፣ የወደዱትን መልአክ ማለት ልማድ ሆኖ ጠላቶቻቸው ለውጡን ተጠቅመው ለጥብስ አቀረቧቸው እንጂ ማስረጃ ሊያቀርቡበት የሚችሉበት ነገር አልነበረም፡፡ ደርግም ማስረጃ አልጠየቀም፤ ለማጣራትም አልሞከረም፡፡ ሌ/ ኮሎኔል ፍሥሐም አገላለጣቸው ‹ቤተ ክህነቱ ስለከሰሳቸው አሠርናቸው እንጂ ነገሩ ከኛ አልመጣም› ዓይነት ነው፡፡ የአቡነ ቴዎፍሎስን ሕይወት የቀጠፈው ግን ክሱ ሳይሆን ‹ከፍርድ በፊት ወንጀለኛ የሚያደርገው› የደርግ አሠራር ነበር፡፡ በዚያ ላይም ሳያስፈቅዱኝ ሾሙ ብሎ ደርግ ምክንያት ፍለጋ ላይ ነበር፡፡
ሁለተኛው ክስ ‹በቤተ ክህነት ሤራና አሻጥር ይሠራሉ› የሚለው ነው፡፡ ምን ዓይነት ሤራና አሻጥር እንደሆነ አልተገለጠም፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ በመጣ ቁጥር ሰውን የመክሰሻ ቀላሉ መንገድ ‹ለውጡን ይቃወማል፣ ያለፈውን ሥርዓት ይደግፋል፣ ውስጥ ውስጡን አድማ ይመታል› የሚሉት አቤቱታዎች ናቸው፡፡ ምግቡን ለበዪው እንዲስማማ አድርጎ ማቅረብ፡፡ ይህንን እንድገምት ያደረገኝ ክሱን ያቀረቡትን አካላት በተመለከተ ኮሎኔሉ የሰጡን መረጃ ነው፡፡ ‹ዘጠና በመቶ የሚሆኑት ገዳማት ፈርመውበት ነበር›(ገጽ 199) ይላል፡፡
እጅግ አስገራሚ መረጃ ነው፡፡ ሳይበጠር ይከካ፣ ሳይለቀም ይፈጭ እንደነበር የሚያሳይ፡፡ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በ1972 ዓም ባካሄደው የሰበካ ጉባኤ ቆጠራ የኢትዮጵያ ገዳማት ቁጥር 1000 እንደነበረ ያመለክታል፡፡(ከ1966-1972 ባለው ጊዜ እንኳን አዲስ የሚቋቋምበት ያሉትም በፕሮፓጋንዳውና በለውጡ እየተንገዳገዱ ነበር) ያ ዘመን እንዳሁኑ መንገድ ያልተስፋፋበት፣ ሞባይል ስልክ የሌለበት ጊዜ ነው፡፡ ወቅቱም የግርግር በመሆኑ ገዳማውያን ከበኣታቸው እንዲወጡ የሚያበረታታ አይደለም፡፡ በዚህ ላይ ራሳቸው ፍሥሐ ደስታ እንደነገሩን ገዳማቱ ሁሉ መሬታቸውን ተወርሰዋል፡፡ እንዴት ሆነው ነው በአብዮቱ ቅር የተሰኙ 900 ገዳማት ተገናኝተው በአቡነ ቴዎፍሎስ ላይ ሊፈራረሙ የሚችሉት? በየቦታቸው ሆነው ፈረሙ ቢባል እንኳን ማነው በዚያ ዘመን ከዋልድባ እስከ ማንዳባ፣ ከደብረ ዳሞ እስከ ደብረ ወገግ፣ ከማኅበረ ሥላሴ እስከ ዝቋላ፣ ከደብረ ቢዘን እስከ ደብረ ሊባኖስ ተዘዋውሮ ገዳማቱን ሊያስፈርም የሚችለው(ያውም ያኔ የኤርትራንም ገዳማት ይጨምራል)፡፡ ገዳማቱ ያሉበት አስቸጋሪ አካባቢ፣ የገዳማቱ ብዛትና የወቅቱ ሁኔታ ተደምሮ 10 በመቶ ገዳማት እንኳን ሊፈርሙ አይችሉም፡፡ አብያተ ክርስቲያናቱ ናቸው የፈረሙት እንዳንል እንኳን እነርሱም ቁጥራቸው በ1972 ዓም ከ25 ሺ በላይ ነበሩ፡፡ ፈጽሞ ሊሆን የማይችል ነው፡፡
የአቡነ ቴዎፍሎስ ሞትና አሟማት አሁንም ያልተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ በሞታቸውና አሟሟታቸው ሦስት አካላት የነበራቸው ሚና አሁንም በሚገባ መፈተሽ አለበት፡፡ ቤት ክህነት(ከጳጳሳት ጀምሮ)፣ ደርግና ሌሎች አካላት(ለምሳሌ አስያዛቸው የሚባለው ሰው እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ጎፋ አካባቢ ነበረ)፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ የእኒህን አባት ሁኔታ በሚገባ ማጣራት ይኖርባታል፡፡ አንድም ዋና ተዋንያን የነበሩት የቤተ ክህነትና የቤተ መንግሥት ሰዎች መረጃውን ይዘውት ጨርሰው ከማለፋቸው በፊት፤ ሁለት ቤተ ክህነቱንም ሆነ ደርግን የሚያስወቅስ ያልተሰማ መረጃ ነገ ከመውጣቱና ማጣፊያው ከማጠሩ በፊት፡፡ ቤተ ክህነት አንድ አጣሪ አካል አቋቁማ ታሪኩ የተጣራ እንዲሆን ማድረግ አለባት፡፡ የአብዮቱን ዘመን ታሪክ የምትነግሩን አካላትም መጻፋችሁ የሚያስመሰግናችሁ ቢሆንም የምትሰጡን መረጃ ግን እውነትና ሊታመን የሚችል ቢሆን በታሪክ ውስጥ የሚኖራችሁን ሥፍራ ምቾት የሚሰጠው ይሆናል፡፡
የአቡነ ቴዎፍሎስን አሟሟት በተመለከተ ሻለቃ ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስም ሆኑ ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ በሁለተኛው እትሞቻቸው የሚያብራሩት ነገር ሊኖር ይገባል፡፡ አዲስ እየጻፋችሁ ያላችሁም አስቡበት፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፡- ቤተ ክርስቲያናችንን ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በቊጥር እጅግ የላቀ የውሉደ ክህነት ብዝኅነት ያላት ስትኾን ስብከተ ወንጌልን ለውሉደ ሰብእ በማዳረስ ረገድ ያለን ውጤት ግን አናሳ ነው ማለት ይቻላል ባሕርን አቋርጦ፣ ድንበርን ተሻግሮ እስከ ጽንፈ ምድር ተጉዞ፣ አስተምሮና ያላመነውን አሳምኖ የቤተ ክርስቲያን ልጅ ማድረጉ ይቅርና በሀገር ውስጥ ያሉትን ወገኖች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አሰባስቦ ምእመናንን ማብዛት …

ኤሪትራዊው ፍልሰተኛ የሞተው በስህተት በተተኮሰበት ጥይት ሲሆን፤ የተኩሱ ዒላማ ግን፣ አንድ የእሥራኤል ወታደር በመግደል ሌሎች 10 ሰዎችን አቁስሎ በኦቶቡስ ያመለጠ ተጠርጣሪን ለመግደል ያነጣጠረ እንደነበር ታውቋል።

ጥቅምት ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ብአዴን የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ወጪ በማድረግ የተለያዩ ጋዜጠኞችንና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችን ያካተተ ጉዞ ላይ ፣ የትግል ተሞክሮ እንዲያካፍሉ የተጋበዙት የቀድሞ ታጋዮች በርካታ ጓዶቻቸው መጠለያ በማጣት በየከተማው በላስቲክ ቤት መንገድ ላይ እንደሚኖሩ ለጎብኝዎች ተናግረዋል፡፡ ‹‹ ህዝብ እንደኖረው ለመኖር ዕድሉን …

ጥቅምት ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፖሊሱ የተገደለው በከተማዋ ውስጥ ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ተጣልቶ ነው። ፖሊሶች አንድ የግሮሰሪ ሰራተኛን ሲደበድቡ ፣ ወጣቶች በብስጭት በፌደራል ፖሊሱ ላይ እርምጃ መውሰዳቸውን ለማወቅ ተችሎአል። በከተማዋ ከፍተኛ ግርግር መኖሩን የተናገሩት ነዋሪዎች፣ በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት ገዳዮችን ለመያዝ ጥረት እያደረጉ ነው። የከተማው ወጣቶች የፌደራል ፖሊስ አባላት ከፍተኛ የሆነ ጫና …

ጥቅምት ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከታላላቆቹ የአለም የመገናኛ ብዙሃን መካከል ዘ ኒውዮርክ ታይምስና ቢቢሲን ጨምሮ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ስለተከሰተው ድርቅ የዜና ሽፋን በመስጠት ላይ ሲሆን፣ ዘ ኒዮርክ ታይምስ ባወጣው ዘገባ ድርቁ አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል። “ያሲን ሙሃመድ ከአነስተኛ የእርሻ ማሳው ላይ እየወሰደ ጫት ይቅማል፣ ለምን ተብሎ ሲጠየቅ ፣ ጫት ረሃብን ያስታግሳል “የሚል …

ጥቅምት ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ስብሰባ አውካችሁዋል በሚል ወንጀል የተከሰሱት የቀድሞ የአንድነት ፓርቲ ማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አለነ ማህፀንቱና የቀድሞ የፓርቲው አባል አቶ እስማኤል ዳውድ መከላከያ ምስክሮቻቸውን ሳያሰሙ እንደተቀጠሩ ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡ አቶ እስማኤል ዳውድና አቶ አለነ ማህፀንቱ እስር ቤቱ” መኪና ላገኝ ስላልቻልኩ” ተከሳሾቹን ላቀርብ አልቻልኩም፤ በማለቱ የተነሳ መዝገባቸውን እየተመለከተ የሚገኘው የአራዳ …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

የሥርዐት ለውጡ÷ ጽ/ቤቱ፣ ከሐምሌ 2002 – ሰኔ 2005 ዓ.ም. ያለውን የሒሳብ አሠራሩን በውጭ ኦዲተሮች ካስመረመረ በኋላ የተሰጠውን አስተያየት ተከትሎ የተካሔደ ነው የፋይናንስ ፖሊሲው እና ማኑዋሉ፣ የቤተ ክርስቲያንን የምጣኔ ሀብት እና የሙዓለ ንዋይ አስተዳደር መመሪያዎች በሚያወጣው በቅዱስ ሲኖዶስ ተመርምሮ የተወሰነ ነው ከኹለትዮሽ የአመዘጋገብ ሥርዐት ጋር ጽ/ቤቱ በተከተለው ማእከላዊ የበጀት አሠራር (budget centralization)፤ ወጪ ቆጣቢ፣ ውጤታማ እና …

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ልደታ ምድብ፤ 19ኛ ወንጀል ችሎት በስድስት ጦማርያን እና በሶስት ጋዜጠኞች ላይ በ08/11/2006 ዓ.ም ከፍትህ ሚኒስትር የቀረበለትን ክስ በቀን 11/11/2006 በይፋ አንብቦ ክሱን ከከፈተ ወዲህ መሰረታዊ ውሳኔ ያሳለፈው ጥቅምት05/2008 ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይሄውም ክሳቸው በሰኔ 30/2007 ተቋርጦ ከተፈቱት ሶስት ጋዜጠኞች እና ሁለት ጦማርያን ውጭ ክሳቸው ቀጥሎ ከነበሩት አምስት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን መካከል አራቱ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱና ከጦማርያኑ መካከል በፍቃዱ ሃይሉ ግን የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ ተጠቅሶበት የተከሰሰው ክስ ተሰርዞ በመደበኛው ወንጀል ሕግ አንቀፅ 257/ሀ መሰረት‹‹[ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል የመናድ ወንጀል] … እንዲፈፀም ለማድረግ … በንግግር፣ በሥዕል ወይም በፅሁፍ አማካይነት በግልፅ የመቀስቀስ ወንጀል ክስ›› በሚል ተሻሽሎ ክሱን እንዲከላከል ብይን መስጠቱ ነው፡፡
ነፃ የተባሉትና በአሁኑ ወቅት በእስር ላይ የሚገኙት አቤል ዋበላ፣ አጥናፉ ብርሃኔና ናትናኤል ፈለቀ ምንም እንኳን ፍርድቤቱ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም ይህ ፅሁፍ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ አልተፈቱም፡፡ አቃቤ ሕግ እግድ አስወጥቶ ይግባኝሊጠይቅባቸው ይችላል የሚል ከፍተኛ ግምትም በብዙዎች ዘንድ አድሯል፡፡ ይሄም በትናንትናው እለት በፍርድ ቤቱ የተሰጠውን ‹የነፃናቸው› ውሳኔ ትርጉም አልባ የሚያደርግና የጦማርያኑንም ሕገ መንግስታዊ መብት የሚጥስ ተግባር ከመሆን አይዘልም፡፡ (ይሄን ጉዳይበሚመለከት ሌላ ፅሁፍ ይዘን እንወጣለን)፡፡
በዚህ ፅሁፍ ለማየት የተሞከረው ግን ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ‹ተከላከል› ስለተባለበት ጉዳይ እና ለረቡዕ ጥቅምት10/2008 ለዋስትና ጉዳይ ስለተቀጠረው ጉዳይ ነው፡፡ በፍቃዱ የሚከላከለው ምኑን ነው የሚለውን የፍሬ ነገር (substantive)ጉዳይ በዚህ ፅሁፍ ለማየት አልተሞከረም፡፡ ይልቁንም የበፍቃዱ የዋስትና ጥያቄ ምላሽ ምን መሆን አለበት? እና በፍቃዱ የተከሰሰበት የሕግ አንቀፅ ምን ይነግረናል? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀ ፅሁፍ ነው፡፡
ዋስትና ሕገ መንግስታዊ መብት ነው?

አዎ! የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት በአንቀፅ 19 ላይ የተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ፤ ንዑስ አንቀፅ 6 ላይ እንዲህ ይላል፡

የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት አላቸው፡፡ ሆኖም በሕግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ ይችላል፡፡

ለመሆኑ በአንቀፁ እንደ ልዩ ሁኔታ (exception) ፍርድቤቱ ዋስትና ላለመቀበል የሚችልባቸውን ሁኔታዎች ምንድን ናቸው?

ዋስትና በኢትዮጵያ ሕግ በምን አግባብ ነው የሚፈቀደው? የሚከለከለውስ?
አንድ ሰው የተከሰሰበትን የወንጀል ክስ ከእስር ቤት ውጭ ሆኖ መከታተል ይችል ዘንድ እና ጥፋተኛ ላልተባለበት የወንጀል ድርጊት ታስሮ መቆየት ስለሌለበት ዋስትና ከታሰሩ ሰዎች መብቶች አንዱና ዋነኛው በመሆን ተደንግጓል፡፡ ነገር ግን ይህ ህገ መንግስታዊ መብት ለሁሉም ተከሳሾች እንዲሁ (for granted) የሚሰጥ አይደለም፡፡ ይልቁንም በኢትዮጵያ ሕግ ዋስትና የሚያስፈቅዱ (bailable)እና ዋስትና የሚያስከለክሉ (non-bailable) ወንጀሎች በተለያ ቦታዎች በግልፅ ተደንግገዋል፡፡ ዋስትና በመርህ ደረጃ የሚያስከለክሉ ወንጀሎች ምን አይነት ናቸው? የሚለውን ስንመለከት፤ በመጀመሪያ የምናገኝው የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር63ን ሲሆን፣ በዚህ አንቀፅ ንዑስ ቁጥር 1 መሰረትም፡

ማንኛውም የተያዘ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል የሞት ቅጣትን ወይም አስራ አምስት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ የሆነ ፅኑ እስራት የማያስቀጣው ከሆነና ወንጀል የተፈጸመበት ሰው በደረሰበት ጉዳት የማይሞት የሆነ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ለመልቀቅ ይችላል፡፡

  ይህ ለሁሉም የወንጀል አይነቶች የሚሰራ መርህ ሲሆን አንድ ሰው የተከሰሰበት የወንጀል ድርጊት ከአስራ አምስት ዓመት ፅኑ እስራት በላይ የሚያስቀጣው በሆነ ጊዜ እና ወንጀል የፈፀመበት ሰው የሞተ እንደሆነ የዋስትና መብቱን ይነፈጋል ማለት ነው፡፡ከዚህ አጠቃላይ መርህ ባለፈ በተለያዩ ህጎች ላይ ዋስትና በመርህ ደረጃ ተከልክሎ እናገኘዋለን፡፡ በዚህም መሰረት በተሻሻለው የጸረሙስና ልዩ ስነ ስርአትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 434/1997 አንቀፅ 4 መሰረት የሙስና ወንጀል አስር ዓመትና ከዛ በላይየሚያስቀጣ ከሆነ ዋስትና ያስከለክላል ፡፡ እንዲሁም የሽብርተኝነት ወንጀልም በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ20 መሰረት ዋስትና የማያሰጥ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡ እንግዲህ አሁን ባለው የኢትዮጵያ የሕግ ስርዓት የዋስና መብት በመርህ ደረጃ የሚከለከለው በነዚህ ሶስት ሁኔታዎች ብቻ ነው ማለት ነው፡፡

ይህ ማለትም በመርህ ደረጃ ዋስትናን ከሚከለክሉት የሕግ ድንጋጌዎች ውጭ ያሉ ሌሎች የወንጀል ክሶች ዋስትና የሚያስፈቅዱ(bailable) ናቸው ማለት ነው፡፡ እዚህም ላይ ግን ሌላ እቀባ አለ – የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ67፡፡ በዚህ የስነ ስርዓት ሕጉ አንቀፅ መሰረት አንድ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል በመርህ ደረጃ ዋስትና የማያስከለክል ቢሆንም (ማለትም ከአስራ አምስት ዓመት ፅኑ እስራት በታች የሚያስቀጣ ቢሆንም፣ ከአስር ዓመት በታች የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል ቢሆንም፣ ከሽብርተኝነት ወንጀል ውጭ ቢሆንም) ፍርድ ቤቱ በሶስት የተለያዩ ምክንያቶች ተከሳሹን ዋስትና ሊከለክለው ይችላል፡፡ ይሄውም፡
  1. መጥፋት (Disappearance)፡ተከሳሹ በዋስትና ቢወጣ ይጠፋል ተብሎ ሲገመት፣
  2. ማጥፋት (Commits another offense)፡ ተከሳሹ በዋስና ቢወጣ ሌላ ወንጀል ይፈፅማል ተብሎ ሲገመትና፣
  3. አሁንም ማጥፋት (Witness Interference)፡ ተከሳሹ በዋስትና ቢወጣ ምስክሮች ላይ ጫና ይፈጥራል፣ ሌሎች ማስረጃዎችንም ያጠፋል ተብሎ ሲገመት ነው፡፡
ፍርድ ቤቱ ምንም እንኳን ተከሳሹ የተከሰሰበት የወንጀል ድርጊት በመርህ ደረጃ ዋስትና የማያስከለክል (bailable) ቢሆንም ከነዚህ ሶስት ምክንያቶች አንዱ አለ ብሎ ካመነ ተከሳሹን ፍርድ ቤቱ ዋስትና ሊከለክለው ይችላል፡፡  
የበፍቃዱ የዋስትና ጉዳይ
እንግዲህ በመግቢያችን እንዳነሳነው ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ተከሶበት የነበረው የሽብርተኝት ወንጀልን ለመፈፀም ማቀድ፣ ማነሳሳት፣ መሞከር፣ መዘጋጀትና ማሴር ክስ ውድቅ ተደርጎ በፃፋቸው ፅሁፎች ‹‹[ሕገመንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል የመናድ ወንጀል]… እንዲፈፀም ለማድረግ … በንግግር፣ በሥዕል ወይም በፅሁፍ አማካይነት በግልፅ የመቀስቀስ ወንጀል›› ፈፅመሃል፣ ክሱንም ተከላከል መባሉን አይተናል፡፡ ታዲያ በፍቃዱ አሁን ተከላከል የተባለበትየወንጀል ክስ በፍቃዱን የዋስትና መብት ያስከለክለዋልን? ከላይ ካነሳናቸው አጠቃላይ የኢትዮጵያ የዋስትና ሕግ መርሆዎች አንፃር እንመልከት፡፡
የቀረበበት ክስ Bailable ነው ወይስ Non-bailable?
Bailable ነው፡፡ ምክንያቱም፡
 አሁን በፍቃዱ ተከላከል የተባለበት የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 በአጠቃላይ የሚያስቀጣው ከአንድ ቀን እስከ አስር ዓመት ፅኑ እስራት ሲሆን፤ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ‹‹…ግልፅነትና ተጠያቂነትን ባረጋገጠ መልኩ ውጤታማና ተገማችነት ያለው ቅጣት የሚሰጥበትን ስርዓት…›› ለመመስረት በማሰብ በጥቅምት 2006 ዓ.ም ያወጣው የተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 02/2006 አንቀፅ 9 ላይ በማያሻማ ሁኔታ እንደደነገገው ደግሞ በፍቃዱ ሃይሉ የተከሰሰበት የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257/ሀ ማለትም አጥፊው ድርጊቱን በንግግር፣ በስዕል፣ ወይም በፅሁፍ አማካኝነት በግልፅ የቀሰቀሰ እንደሆን የእስራት ቅጣቱ ሁለት እርከን ነው ይላል፡፡ ይሄም ማለት በመመሪያውአባሪ አንድ ላይ አንደተገለፀው እርከን ሁለት የሚያስቀጣው ከአስርቀን እስከ ስድስት ወር እስራት ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም በፍቃዱ ጥፋተኛ እንኳን ቢባል ሊቀጣ የሚችለው ከፍተኛ ቅጣት የስድስትወራት እስራት ብቻ ነው፡፡ በአጠቃላይ በፍቃዱ የተከሰሰበት ወንጀል ከ15 ዓመት ፅኑ እስራት በላይ የሚለውን የመከልከያ መርህ አያሟላም፡፡
በበፍቃዱ ላይ ተመስርቶ የነበረው ‹የሽብርተኛ ድርጅት በማቋቋም የሽብርተኝነት ወንጀልን ለመፈፀም ማቀድ፣ ማነሳሳት፣ መሞከር፣ መዘጋጀትና ማሴር› ክስን ፍርድ ቤቱ ‹ዞን ዘጠኝ የሽብርተኛ ድርጅት አይደለም የጦማርያን እና የአራማጆች ቡድንእንጂ› በማለት በብይኑ በግልፅ ውድቅ ስላደረገው፤ የፀረ-ሽብርተኝነት ህጉ ከዚህ በኋላ በበፍቃዱ ላይ ተፈፃሚነት የለውም፡፡
 ሶስተኛውና በኢትዮጵያ በመርህ ደረጃ ዋስትና የሚያስከለክለው የወንጀል አይነት ከአስር ዓመት ፅኑ እስራት በላይ የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል (grand corruption) ሲሆን፤ የበፍቃዱ ክስደግሞ ከሙስና ወንጀል ጋር ፈፅሞ ግንኙነት የሌለው ነው፤
በአጠቃላይ በመርህ ደረጃ በፍቃዱን ዋስትና ሊያስከለክል የሚችል ምንም አይነት የህግ አግባብ የለም፡፡
መርሁ ሲፈቅድ፤ ዳኝነቱ ይከለክለዋልን?
በፍፁም ሊከለክለው አይችልም፡፡ ምክንያቱንም እንመልከት፡፡
በኢትዮጵያ ሕግ ዋስትና በመርህ ደረጃ ተፈቅዶ በዳኞች ስልጣን (discretionary power) ሊከለከል የሚችልባቸውሶስት ምክንያቶች የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ 67 መደንገጉን ከላይ ተመልክተናል፡፡ የበፍቃዱን ጉዳይም ከዚህ አንፃር ስንመለከት፡
  1. ‹ይጠፋል› ፡ ተከሳሾች ይጠፋሉ ተብለው የሚገመቱት በተከሰሱበት ድርጊት ጥፋተኛ ከተባሉ ውሳኔው የሚያስከትልባቸውን እስር ለማምለጥ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በፍቃዱ የተከሰሰበት የሕግ አንቀፅ (የወንጀል ሕጉ አንቀፅ257/ሀ) ሊያስቀጣ የሚችለው ከአስር ቀናት እስከ ስድስት ወራት እስራት ብቻ ሆኖ እያለ በፍቃዱ ደግሞ ከአንድ ዓመት ከስድስት ወራት በላይ በእስር ላይ ያለ ነው፡፡ ይሄም መታሰር ከሚገባው ከእጥፍ በላይ ታስሯል ማለት ነው፡፡ ታዲያ ለምን ይጠፋል?
  2. ያጠፋል ፡ ተከሳሹ ቢፈታ ሌላ ጥፋት ያጠፋል ተብሎ ሲገመት ፍርድ ቤቱ ተከሳሹን ዋስትና ሊከለክለው ይችላል፡፡ ይህ ክልከላ በዋናነት ለደጋጋሚ ወንጀለኞች (recidivists) የተደነገገ ነው፡፡ በፍቃዱ እንኳን ደጋጋሚ ወንጀለኛ ሊሆን በሕይወት ዘመኑ አንድም ክስ ተመስርቶበት የማያውቅ መልካም ጠባይ ያለው ሰው ነው፡፡ በመሆኑም ቢፈታ ሌላ ወንጀል ሊፈፅም ይችላል የሚለው መከልከያ በፍፁም እሱ ላይ አይሰራም፡፡
  3. አሁንም ያጠፋል ፡ ሌላው ዋስትና ሊያስከለክል የሚችለው ምክንያት ተከሳሽ ከእስር ቢፈታ እሱ ላይ ሊቀርቡ የሚችሉ ምስክሮችን እና ሌሎች ማስረጃዎችን ያጠፋል ተብሎ ሲገመት ነው፡፡ በፍቃዱ ላይ ደግሞ ዓቃቤ ህግ አለኝ ያለውን ሁሉ ማስረጃ አሰምቷል/አቅርቧል፡፡ ሊጠፋ የሚችል ምንም ነገር የለምና እሱ ላይ ይሄ ምክንያት እይሰራም፡፡
በአጠቃላይ በፍቃዱ ሃይሉ የተከሰሰበት ወንጀል በመርህም ሆነ በዳኝነት ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል የሚችል አንዳችም ሕጋዊ ምክንያት የለውም፡፡ እንዲያውም የዋስትና መብቱን የሚከለክል አንዳችም ሕጋዊ ምክንያት ካለመኖሩም ሌላ የበለጠ የዋስትና መብቱን መከበር የሚገፋ ምክንያት አለ፤ ይሄውም በኢትዮጵያ ህግ አንድ ሰው ያላግባብ ለታሰረበት የእስር ጊዜ ካሳ የሚያስከፍል ስርዓት በሌለበት እና በፍቃዱ ደግሞ ጥፋተኛ እንኳን ቢባል ሊታሰር ከሚችለው ከአስር ቀናት እስከ ስድስት ወራት እስራት ከእጥፍ በላይ ታስሮ እያለአሁንም ዋስትና በመከልከል ሌላ ተጨማሪ እስር እንዲታሰር ማድረግ እጅጉን ኢፍትሃዊነት ከመሆኑም በላይ የወንጀል ህግ መርሆዎችን በሙሉ የሚገረስስ በመሆኑ ነው፡፡
257 – ያልተዘመረለት ሃሳብን የመግለፅ ነፃነት ጠላት

በፍቃዱ ሃይሉን ዋስትና ሊያስከለክል የሚችል አንዳችም ህጋዊ ምክንያት አለመኖሩን ከላይ ተመልክተናል፡፡ በዚህም መሰረት በፍቃዱ መብቱ ተከብሮለት በቀላል ዋስትና እንደሚወጣ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ነገር ግን ይሄን ፅሁፍ ከመቋጨታችን በፊት አሁን በፍቃዱ ተከላከል ስለተባለበት የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 ትንሽ ነገር ብለን እንጨርስ፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ላለፉት ስድስት ዓመታት የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉን አዋጅ ቁጥር 652/2001 ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ለመደፍጠጥ እየተጠቀመበት እንደሆነ ከተለያዩ አካላት ትችት እየተሰነዘረበት ይገኛል፡፡ የተለያዩ ጋዜጠኞች እና ፀሃፊዎችም የዚህ አዋጅ ሰለባ መሆናቸው በየቀኑ የምናየው እውነታ ነው፡፡ ነገር ግን ከዚህ አዋጅ ባለፈ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መደበኛውን የወንጀል ሕግ እንደገና ወደመጠቀሙ ያዘነበለ ይመስላል፡፡ ዋነኛው የህግ አንቀፅ ደግሞ የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 ነው፡፡
ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የሶስት አመት እስራት የተፈረደበት (ጥቅምት 2007)፣ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው ማስተዋል አሳታሚ ድርጅት የአስር ሺህ ብር  የገንዘብ ቅጣት ተቀጥቶ የተዘጋው ፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የአዲስ ጉዳይ መፅሄት ስራ አስኪያጅ እና ጋዜጠኛ እንዳልካቸው ተስፋዬ ላይ የሶስት ዓመት ከሶስት ወራት እስራት የተፈረደበት (መስከረም 2007)፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የሎሚ መፅሄት ዋና ስራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ ግዛው ታየ ላይ የሶስት ዓመት ከሶስት ወራትእስራት የተፈረደበት (መስከረም 2007)፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የፋክት መፅሄት ስራ አስኪያጅ ፋጡማ ኑሪያ ላይ የሶስትዓመት ከአስራ አንድ ወራት እስራት የተፈረደባት (መስከረም 2007)፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የቀድሞው የዕንቁ መፅሄትዋና አዘጋጅና ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ላይ ክስ ተመስርቶበት በአሁኑ ወቅት ክሱን እየተከታተል የሚገኘው … አሁን ደግሞ በፍቃዱ ሃይሉ በፃፋቸው ፅሁፎች ምክንያት ይህ የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 ተጠቅሶበት ተከላከል ተብሏል፡፡ የበፍቃዱን ከሌሎች ለየትየሚያደርገው በአንቀፁ ቀላል ቅጣት (ከአስር ቀናት እስከ ስድስት ወራት ብቻ) የሚያስከትለው አንቀፅ 257 ንዑስ አንቀፅ ‹ሀ› የተጠቀሰበት መሆኑ ነው፡፡
እንግዲህ ይህ የሕግ አንቀፅ ነው የቅርብ ጊዜ ሃሳብን ከመግለፅ ነፃነት ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ላሉ ክሶች ዋነኛ መሰረትእየሆነ ያለው፡፡ በፍቃዱ ሃይሉም የቅርቡ አንቀጽ ሰለባ ነው፡፡
በፍቃዱ ሃይሉ 

አሜሪካና አውሮፓ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለህዳሴ ግድብ የታሰበውን ያህል ገንዘብ አልተዋጣም

መንግሥት ከዳያስፖራው በተለይም አሜሪካና አውሮፓ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ለመሰብሰብ የታሰበውን ያህል የገንዘብ መዋጮ አለማግኘቱን፣ በምክትል ጠቅላይ

ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል አስታወቁ፡፡ 

ዶ/ር ደብረ ጽዮን ይህን ያስታወቁት፣ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም. በጽሕፈት ቤታቸው ለጋዜጠኞች የግድቡን አጠቃላይ የሥራ ሒደትና ክንዋኔ ለመግለጽ በጠሩት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነው፡፡ 

‹‹አገር ውስጥ ካሉ ሠራተኞችና ዜጎች የተሰበሰበው የገንዘብ መጠን ከበቂ በላይ ነው፡፡ በተለይ በሠራተኛው በኩል የተለየ ቁርጠኛነት አስተውለናል፤›› በማለት አገር ውስጥ ያለው የገንዘብ አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡ ‹‹የውጭ የገንዘብ አስተዋጽኦ የተለያየና ቅልቅል የሚስተዋልበት ነው፡፡ በዋናነት የፍላጎት አይደለም፡፡ ነገር ግን የውጭው የገንዘብ አስተዋጽኦ በአጠቃላይ ጥሩ የሚባል አይደለም፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡ 

ከውጭ የተጠበቀውን ያህል ገንዘብ መሰብሰብ ያልተቻለበት የተለያዩ ምክንያቶች እንዳሉ የገለጹት ዶ/ር ደብረ ጽዮን፣ ‹‹ለምሳሌ አሜሪካ የገጠመን የአሜሪካ መንግሥት ደስተኛ አይደለም፡፡ ምክንያቱም እዚያ አገር ውስጥ የምትከተለው የራሱ ሕግ አለው፡፡ መዋጮ አዋጣ ወይም ቦንድ ግዛ ለማለት የምትከተለው ሕግ አለ፡፡ በቀላሉ የሚሠራ አይደለም፤›› በማለት ባለው የሕግ ክፍተት ምክንያት የታሰበውን ያህል ገንዘብ አለመገኘቱን አብራርተዋል፡፡ 

‹‹ትውልደ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያንን ስብሰባ ጠርተን አንዱ 400 ዶላር ወይም አንድ ሺሕ ዶላር ይላል፡፡ ነገር ግን ይህ አካሄድ ሕገወጥ ነው በመባላችን አቁመነዋል፤›› ብለዋል፡፡

አሜሪካ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ብዙ ተጠብቆ እንደነበር የገለጹት ዶ/ር ደብረ ጽዮን፣ ‹‹አሁን ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት አጠናክረን ዘንድሮ እንጀምራለን፤›› ብለው፣ የተፈጠረው የሕግ ክፍተት ተሞልቶ በከፍተኛ ሁኔታ ለመንቀሳቀስ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን አስረድተዋል፡፡ በተመሳሳይ ‹‹አውሮፓ ያለው የገንዘብ መዋጮም ደከም ያለ ነው፤›› በማለት አክለው አስረድተዋል፡፡ 

ምንም እንኳን በአሜካሪና በአውሮፓ ለግድቡ የሚደረገው አስተዋጽኦ ከተጠበቀው በታች ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ያሉ ዜጎች በከፍተኛ ሁኔታ ለግድቡ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ ተገልጿል፡፡ 

‹‹መካከለኛው ምሥራቅ ጥሩ ነው የሄደው፡፡ ተሳትፎውም ሆነ መጠኑ ጥሩ ነው፡፡ አገር ውስጥ ካለው በስሜትም የሚለይ አይደለም፡፡ የሕግ ጉዳይም የለም፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡ 

የተጠበቀውን ያህል ገንዘብ ያልተገኘበት ምክንያት በምንም ዓይነት ሁኔታ ከተቃውሞ ጋር እንደማይገናኝ የገለጹት ዶ/ር ደብረ ጽዮን፣ ‹‹ተቃውሞ ይነሳል አዲስ ነገር አይደለም፡፡ እነርሱ ግን ከዳያስፖራው ማኅበረሰብ አንፃር በጣት የሚቆጠሩ እብዶች ናቸው፡፡ በጣት የሚቆጠሩ እብዶች ደግሞ የትም ቦታ አሉ፡፡ እነርሱን እንደ ዳያስፖራ አንወስዳቸውም የተነጠሉ ናቸው፤›› በማለት የታሰበውን ያህል ገንዘብ መሰብሰብ ያልተቻለው ከተቃውሞ ጋር በተገናኘ እንዳልሆነ አብራርተዋል፡፡ 

የአገር ውስጥ አስተዋጽኦን በተመለከተ፣ ‹‹አሁን ካለበት መጨመር ነው እንጂ መልካም የሚባል ነው፡፡ ነገር ግን ከባለሀብቱ በኩል አንድ ዓይነትና ወጥ የሆነ አስተዋጽኦ አይደለም ያለው፡፡ ደከም ያሉ አሉ፣ ጥሩ የሄዱ አሉ፤›› ብለዋል፡፡

‹‹በድምር ውጤት ስንመለከተው ከውጤት አንፃር ከውጭና ከባለሀብቱ በቂ አላገኘንም ማለት ይቻላል፡፡ ከምንም በላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተው ሠራተኛው ነው፤›› ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

የፕሮጀክቱን አፈጻጸም መንግሥት አሳንሶ እያቀረበ ነው የሚለውን አስተያየት በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳላቸው ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹የምናሳንስበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ደብቀው እየሠሩ ነው የሚሉ የተወሰኑ ጽሑፎች ተመልክቻለሁ፡፡ ነገር ግን ያለውን ነው እየገለጽን ያለነው፡፡ እንደዚያ ቢሆንልን እንመኝ ነበር፤›› ሲሉ አስተያየቱ መሠረተ ቢስ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ 

በአሁን ወቅት ከአጠቃላይ የግድቡ ግንባታ 47 በመቶ የተጠናቀቀ መሆኑን፣ ለዚህም እስከ ሐምሌ 2007 ዓ.ም. በተሰበሰበ መረጃ መሠረት ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችና ተቋማት ቃል ከተገባው ገንዘብ ውስጥ በአገር ውስጥ ሰባት ቢሊዮን ብር፣ በውጭ አገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ደግሞ 600 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡ ተገልጿል፡፡ 

 

በቢሾፍቱ ከተማ ከታክስ ጋር በተገናኘ የልኳንዳ ቤቶቻቸው የታሸጉባቸው ከ42 በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች፣ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት አቤቱታ ማቅረባቸው ታወቀ፡፡ 

አዲስ በወጣ የግብር ክፍያ ተመን ወደኋላ ተመልሳችሁ አልከፈላችሁም ተብለው የንግድ ቤቶቻቸው እንደተዘጉባቸው የሚገልጹት ልኳንዳ ቤት ባለቤቶች፣ ላለፉት ሦስት ወራት ያለ ሥራ በመቆየታችን ለኪሳራ ዳርጎናል ሲሉም ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የከተማዋ ልኳንዳ ቤቶች ማኅበር አባል እንደገለጹት፣ ከከተማዋ ገቢዎችና ጉምሩክ ቢሮ ጋር የተፈጠረውን ችግር በመፍታት ችግራቸው እስከ ኢሬቻ በዓል ቀን ድረስ እልባት ሊያገኝ እንደሚችል ቢጠብቁም ያለመፍትሔ መዝለቁን አስረድተዋል፡፡

የውዝግቡን መነሻ ለሪፖርተር ያስረዱት ሌላ አባል ደግሞ፣ ቀደም ባሉ ዓመታት የትርፍ ግብር ይከፍሉ የነበሩት ከእርድ በፊት በበሬ መግዣ ዋጋ ይተመን የነበረ ሲሆን፣ ከ2007 ዓ.ም. ጀምሮ አዲስ ሕግ በመውጣቱ ወደኋላ በመሄድ የ2005 እና የ2006 ዓ.ም. የገቢ ግብር በአዲሱ ሕግ መሠረት ክፈሉ መባላቸውን አስረድተዋል፡፡ የ2005 እና የ2006 ዓ.ም. የገቢ ግብር በነባሩ ሕግ መሠረት የሚፈለግባቸውን ከፍለው የንግድ ፈቃዳቸው ቢታደስም፣ በአዲሱ ሕግ ወደኋላ በመሄድ ክፈሉ መባላቸው አግባብ አለመሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ነጋዴዎቹ አዲሱ ሕግ ከወጣበት ከ2007 ዓ.ም. ጀምሮ በሕጉ መሠረት ለመክፈል ፈቃደኛ መሆናቸውን፣ ያለፉት ሁለት ዓመታት ተጨማሪ የግብር ጥያቄ ውድቅ ተደርጎላቸው፣ የታሸጉ የልኳንዳ ቤቶቻቸው እንዲከፈቱላቸው የአቤቱታ ደብዳቤ ለክልሉ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ማስገባታቸውን ነው ለሪፖርተር የገለጹት፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት በአዲስ አበባም ተመሳሳይ ችግር ተነስቶ የነበረ ቢሆንም፣ ጉዳዩ ወዲያውኑ እልባት ማግኘቱ አይዘነጋም፡፡ ይልቁንም የአዲስ አበባ ልኳንዳ ቤቶች ከደረሰኝ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ጋር ተወዛግበው እንደነበረም ይታወሳል፡፡ 

የቢሾፍቱ ከተማ ገቢዎች ቢሮና የኦሮሚያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሕጉ በአገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ የሚደረግ እስከሆነ ድረስ፣ በክልሉ ውስጥ የተለየ የግብር ቅነሳ እንደማይደረግ በቅርቡ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ የቢሾፍቱ ከተማ የልኳንዳ ባለቤቶች ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ያስገቡትን አቤቱታ በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ ጥረት ቢደረግም፣ በአዳማ ከተማ ስብሰባ ላይ በመሆናቸው ምክንያት ምላሻቸውን ማግኘት አልተቻለም፡፡

 

በዛሬው ዕለት የልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ፩ኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ፪ተኛ ተከሳሽ በፍቃዱ ሃይሉ ፫ተኛ ተከሳሽ ናትናኤል ፈለቀ ፭ተኛ ተከሳሽ አጥናፍ ብርሃኔ እና ፯ተኛ ተከሳሽ አቤል ዋበላ ተጠርጥረው ከነበረበት የሽብርተኝነትና የኅብረተሰቡን ደህንነት አደጋ ላይ የመጣል ክስ ነጻ መውጣታቸውን በበጎ መልኩ የምንቀበለው ቢሆንም 
  1. ፪ተኛ ተከሳሽ በፍቃዱ ሃይሉ በሃይል ተገዶ ማዕከላዊ ምርመራ ውስጥ በማሰቃየት ስር የሰጠው ቃል ተቆጥሮ አመጽን በማነሳሳት ወንጀል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀጽ 257 መሰረት አንዲከላከል መባሉን አጥብቀን እንቃወማለን ፡፡ 
  2. ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ከአንድ አመት ከአምስት ወር በላይ በእስር የቆዬት የዞን9 ጦማርያን የመፈቻ ወረቀት ከችሎቱ መጠናቀቅ በኋላ በአስቸኳይ በፍርድ ቤቱ አማካኝነት ተጽፎ ለማረሚያ ቤቱ ተወካይ ቢሰጥም ማረሚያ ቤቱ እስከ አርብ የስራ ሰዓት መጠናቀቂያ ድረስ መፈቻው አልደረሰኝም በሚል ሰበብ ሶስቱን ጦማርያን በእስር ማቆየቱን አስጊ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ 

ይህ ተግባር ከዚህ በፊት እንደታየው ሁሉ አቃቤ ህግ ለይግባኝ ጊዜ አንዲገዛ ከማረሚያ ቤቱ የሚደረግለት የጓሮ ትብብር አንዳይሆን እጅግ ከፍተኛ ስጋት አለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተለመደው የፍርድ ቤቶችን ስልጣን ዝቅ አድጎ የማየት እና የማረሚያ ቤቶች የእጅ አዙር ፍርድ ሰጪነት ማሳያም ነው ፡፡ በመሆኑም ከዚህ በፊት አንደታየው በአደባባይ በሕግ አግባብ የተሰጠን ነጻነት በጓሮ ከሕግ ውጪ ሊነጠቅ የሚችልበት ከፍተኛ ስጋት አሁንም የዞን9 ጦማርያን ፊት ተጋርጧል ፡፡
539 ቀናት ያለአግባብ እስር መቆየታችን ሳያንስ በራሱ መቆም የማይችል እና ምንም ማስረጃ ያልቀረበበትን ክስ አቃቤ ሕግ በጓሮ ከማረሚያ ቤት ጋር በመመሳጠር የመንፈግ ሌላ ተጨማሪ ግፍ አንዳይሰራብን አጥብቀን እንጠይቃለን ፡፡

ስለሚያገባን አንጦምራን!
ዞን9

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩና ሌሎችም ከሙስና ጋር በተያያዙ ክሦች እሥር ቤት ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ጉዳይ ለፊታችን ማክሰኞ፤ ጥቅምት 9/2008 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ ጠበቆቻቸው ደንበኛቸው የተከሰሱበት መዝገብ አብረዋቸው ከተከሰሱት ሰዎች ጉዳይ ጋር የሚገናኝ ባለመሆኑ ተነጥሎ እንዲወጣና እንዲታይ እየጠየቁ ነው፡፡

የአምባሳደር ዘውዴ ረታ ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የእውቁ ጋዜጠኛ፣ ዲፕሎማት፣ የታሪክ ተመራማሪና ደራሲ የአምባሳደር ዘውዴ ረታ ሥርዓተ ቀብር ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

ለሥራ ጉዳይ በሄዱበት ለንደን ከተማ ድንገት በመታመማቸው በለንደን ቅድስት ማርያም ሆስፒታል ከፍተኛ የሕክምና ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩት አምባሳደር ዘውዴ፣ በ80 ዓመታቸው ያረፉት መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ነበር፡፡

በሥርዓተ ቀብራቸው ላይ በታሪክ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ የቀረበው ዜና ሕይወታቸው እንደሚያመለክተው፣ አምባሳደር ዘውዴ ጥልቅ በሆነ ጥናትና ምርምር ላይ ተመሥርተው በተጠናከሩ መረጃዎች የተደገፉ፣ ‹‹የኤርትራ ጉዳይ እ.ኤ.አ ከ1941 እስከ 1963››፣ ‹‹ተፈሪ መኰንን ረጅሙ የሥልጣን ጉዞ››፣ ‹‹የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ መንግሥት አንደኛ መጽሐፍ ከ1923 እስከ 1948 ዓ.ም›› በሚሉ ርዕሶች ሦስት ታላላቅ የታሪክ መጻሕፍትን በተባ ብዕራቸው፣ ውበትና ለዛ በማይለየው የቋንቋ ችሎታቸው በማሰናዳት፣ ለአገርና ለወገን እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ሥራዎችን አበርክተው አልፈዋል፡፡

በ18 ዓመታቸው በዚያን ጊዜ የጋዜጣና ማስታወቂያ መሥሪያ ቤት እየተባለ ይጠራ በነበረው የመንግሥት ተቋም በ1945 ዓ.ም. በጋዜጠኝነት ሲሠሩ፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮ ዜና አቅራቢነት ለሦስት ዓመታት ያህል አገልግለዋል፡፡

 በ1952 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሕዝብ የአገር ፍቅር ማኅበር ሥር ይዘጋጁ የነበሩት የኢትዮጵያ ድምፅና መነን መጽሔት ዝግጅት ዋና ዲሬክተር በመሆን እስከ 1954 ዓ.ም. ድረስ አገልገለዋል፡፡ ከዋና ዲሬክተርነት ኃላፊነታቸው በተደራቢ የእነዚሁ ሚዲያዎች የአማርኛ ቋንቋ አዘጋጅ ሆነው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፡፡

ቀድሞ አዣንስ ተብሎ የሚታወቀው የኢትዮጵያ ወሬ ምንጭ ዋና ዲሬክተር፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የፓን አፍሪካን ኒውስ ኤጀንሲ ፕሬዚዳንት፣ የማስታወቂያ ረዳት ሚኒስትር፣ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርም ነበሩ፡፡ በኢጣሊያና በቱኒዝያ የኢትዮጵያ መንግሥት ልዩ መልእክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር በመሆን ለአገራቸውና ለመንግሥታቸው በቅንነት በብቃትና በትጋት እስከ 1967 ዓ.ም. ድረስ ከፍተኛ አገልግሎት አበርክተዋል፡፡ በዘመነ ደርግ የስደት ዘመናቸውም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ በዓለም አቀፍ የእርሻ ልማት ፈንድ (The International Fund for Agricultural Development) የፕሮቶኮልና የመንግሥታት ግንኙነት ኃላፊ ሆነው ለአሥራ ሦስት ዓመታት ሠርተዋል፡፡ 

የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ቀድሞ ደጃዝማች ገብረ ማርያም በኋላ ደግሞ ሊሴ ገብረ ማርያም ትምህርት ቤት የተከታተሉት አምባሳደር ዘውዴ፣ ከ1948 ዓ.ም. እስከ 1952 ዓ.ም. ባሉት ዓመታት ፈረንሣይ አገር ፓሪስ ከተማ በሚገኘው “ECOLE SUPERIEURE DE JOURNALISM DE PARIS” በተሰኘው ታዋቂ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የጋዜጠኝነት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡

አምባሳደር ዘውዴ ረታ ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያሉ ባደረባቸው የደራሲነት ፍላጐት እኔና ክፋቴ፣ የገዛ ሥራዬ፣ ፍቅር ክፉ ችግርና እንግዳሰው የቡልጋው በሚሉ ርዕሶች አራት ቴአትሮችን ራሳቸው ጽፈውና አዘጋጅተው ለሕዝብ ዕይታ አብቅተዋል፡፡ 

በፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ አነጋገር፣ ‹‹ዘውዴ ረታ ስኬት በተሞላበት የሕይወት ዘመኑ ጋዜጠኛ፣ ዲፕሎማት፣ የታሪክ ጸሐፊ ሆኖ ሁሉንም ኃላፊነቱን በምልዓት የተወጣ ኢትዮጵያዊ ነበር፡፡ ሦስቱ ክህሎቶቹ ተወራራሾችም ነበሩ፡፡ በቅርቡ በከፍተኛ ደረጃ ለዓለም ዕይታ በበቃባቸው የታሪክ ሥራዎቹ የምናየውም ይህንኑ ነው፡፡ የጋዜጠኛውን ወዝ፣ የዲፕሎማትን ሥልት፣ የታሪክ ጸሐፊን ጥንቃቄ፡፡ ስለሆነም ነው ብዙውን ጊዜ በጎሪጥ የሚተያዩትን ጋዜጠኝነትንና የታሪክ ጸሐፊነትን ማጣጣም የቻለ ደራሲ ለመሆን የበቃው፤›› የሚል ምስክርነት በፕሮፌሰሩ የተሰጣቸው፡፡

በኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ከሃያ ሁለት ዓመት በላይ ላበረከቱት ውጤታማ ተግባር ከንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የምኒልክ የመኰንን ደረጃና የኢትዮጵያ የክብር ኮከብ አዛዥ መኰንን ኒሻን ተሸልመዋል፡፡ ከሃያ አምስት የተለያዩ የአፍሪካ፣ የአውሮፓና የእስያ አገሮች ኒሻኖች ተበርክተውላቸዋል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህም በባሕር ማዶና በአገር ውስጥም ልዩ ልዩ ሽልማቶችንም ተቀዳጅተዋል፡፡ 

የንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ማስታወሻ ያዥ (ልዩ ጸሐፊ)፣ እንዲሁም በተከታታይ የጦር ሚኒስትሮች የነበሩት የራስ ሙሉጌታ ይገዙና የራስ ብሩ ወልደ ገብርኤል ዋና ጸሐፊ ከነበሩት፣ ከአባታቸው ከቀኛዝማች ረታ ወልደ አረጋይና ከእናታቸው ከእማሆይ አፀደ ረድኤቱ ነሐሴ 7 ቀን 1927 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ የተወለዱት አምባሳደር ዘውዴ፣ እስከ ሕይወታቸው ፍጻሜ ካልተለዩዋቸው ከወ/ሮ ገሊላ ተፈራ ጋር መስከረም 21 ቀን 1959 ዓ.ም. በሕግ ተጋብተው የሁለት ሴቶችና የአንድ ወንድ ልጅ አባት ነበሩ፡፡ 

አንድ ሺሕ ያህል ሰዎች በተገኙበት የአምባሳደር ዘውዴ ረታ ሥርዓተ ቀብር ላይ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፣ ልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል፡፡

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች÷ በአህጉረ ስብከትና በሀገር አቀፍ ደረጃ የአንድነት መድረክ በመፍጠር፣ በፀረ ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄና በፀረ ሙስና ንቅናቄ፣ ለዕቅበተ እምነትና ለመልካም አስተዳደር መስፈን በየአጥቢያቸው ተጋድሏቸውን በአቀጣጠሉበት በአሁኑ ወቅት፤ ራሱን ከአማሳኞችና ከአፅራረ ቤተ ክርስቲያን ምንደኞች ጎራ በገሃድ አሰልፎ በሥልጣን ለመሰንበትና ምዝበራውን ለማጧጧፍ ለሚወራጨው የየማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የሀገረ ስብከት አስተዳደር፣ ወጣቶቹን በማሳደድና በመበተን እኩይ …

በጎጃም በርካታ ሰዎች እንዲረሸኑና በጅምላ እንዲቀበሩ አድርገዋል ተብሏል

በደርግ የአገዛዝ ዘመን ዜጎችን በመግደል፣ በማሰርና በማሰቃየት ተከስሰው ሞት የተፈረደባቸው አንድ ስማቸው ያልተገለጸ የቀድሞ የደርግ ባለስልጣን፤ በሆላንዷ ከተማ አምስቴልቪን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኤንኤል ታይምስ የተባለው የአገሪቱ ድረገጽ ትናንት ዘገበ፡፡
በሆላንድ የሚገኘው የአለማቀፍ ወንጀሎች ምርመራ ቡድን አቃቤ ህግ፣ ግለሰቡ እ.ኤ.አ በ1978 ባስተላለፉት ትዕዛዝ፣ በጎጃም አካባቢ ታስረው የነበሩ በርካታ ሰዎች ተረሽነው አስከሬናቸው በጅምላ መቃብር እንዲቀበር ተደርጓል ማለታቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡ተጠርጣሪው ከሁለት ሳምንታት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ የጠቆመው ዘገባው፣ አምስቴልቪን ከተማ ውስጥ በሚገኘው የግለሰቡ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ፍተሻ የተለያዩ ማስረጃዎች የተገኙ ሲሆን በሄግ የሚገኘው ፍርድ ቤትም ከትናንት በስቲያ በዋለው ችሎት፣ ግለሰቡ ለ90 ቀናት በእስር ላይ እንዲቆዩ ወስኖባቸዋል ብሏል፡፡የሆላንድ ፖሊስ ግለሰቡ የተጠረጠሩባቸውን የወንጀል ድርጊቶች ስለመፈጸማቸው ምርመራ ማድረግ መጀመሩን ዘገባው ገልጾ፣ ፖሊስም የምስክሮችን ቃል መቀበሉንና ተጠርጣሪው ድርጊቶቹን ስለመፈጸማቸው ምስክርነታቸውን ከሰጡ ግለሰቦች አብዛኞቹ በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን  እንደሆኑ አስታውቋል፡፡ምስክሮቹ በሰጡት ቃል ግለሰቡ በጎጃም አካባቢ የደርግ ባለስልጣን ሆነው ባገለገሉባቸው አመታት የተጠቀሱትን የወንጀል ድርጊቶች ስለመፈጸማቸው ተናግረዋል ያለው ዘገባው፣ የሆላንድ የወንጀል ምርመራ ባለስልጣናትም ግለሰቡን ለሞት ቅጣት ያበቃቸውን የወንጀል ክስ የተወሰነ መረጃ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት መረከቡን ገልጧል፡፡የአለማቀፍ ወንጀሎች ምርመራ ቡድን፣ በደርግ የአገዛዝ ዘመን በደብረ ማርቆስና በመተከል እስር ቤቶች ውስጥ የግድያና የስቃይ ድርጊቶችን በፈጸሙ ግለሰቦች ላይ ትኩረት በማድረግ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ ዘገባው አስታውቋል፡፡
61 አመታቸው እንደሆነ የተነገረላቸው እኒሁ ባለስልጣን፤ ከጥቂት አመታት ወዲህ ነዋሪነታቸውን በሆላንድ እንዳደረጉና የአገሪቱ ዜግነት እንደተሰጣቸው ያስታወሰው ዘገባው፣ ግለሰቡ በኢትዮጵያ ፍርድ ቤት በሌሉበት የእድሜ ልክ እስራትና የሞት ቅጣቶች እንደተጣሉባቸውም ገልጧል፡፡

“ያልተዘመረለት ትልቅ ሰው ነው” (የዌ. ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት)

    የቀድሞ የኢህአፓ ብርቱ ታጋይ እንደነበር የሚገርለት አንጋፋው ደራሲ አስማማው ኃይሉ (አያ ሻረው)፤ ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ባለፈው ረቡዕ በስደት በኖረባት አሜሪካ ህይወቱ አለፈ፡፡ አስማማው፤ “ከጎንደር ደንቢያ እስከ ዋሽንግተን” (ክፍል አንድና ሁለት) በተሰኙ ልብወለድ መፃህፍቱ በይበልጥ የሚታወቅ ሲሆን አምስተኛ የሥነ ፅሁፍ ሥራውን በቅርቡ ለአሳታሚዎች እንደሰጠ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በአሲምባ በረሃ ለአራት አመታት በትግል የቆየ ሲሆን፤ በ1975 ዓ.ም የኢህአፓ ሰራዊት ሲበተን በስደት ወደ ሱዳን ሄዶ ጥቂት ዓመታት ከቆየ በኋላ ወደ አሜሪካ አቅንቷል፡፡ ለረዥም ዓመታት በአሜሪካ በስደት የኖረው ደራሲው፤ በተለይ ከሶስትና አራት አመታት ወዲህ “ከጎንደር ደንቢያ እስከ ዋሽንግተን፤ ክፍል አንድና ሁለት”፣ “ኢ.ህአሰ፣ አሰብ ክፍል አንድና ሁለት” የተሰኙ አራት መፃህፍትን ለንባብ ያበቃ ሲሆን “አያ ሻረው” የተሰኘ የግጥም ሲዲ ማሳተሙንም የቅርብ ወዳጁ ደራሲና ሀያሲ አለማየሁ ገላጋይ ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ አስማማው በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አምስተኛ መፅሃፉን የረዥም ልብ ወለድ ሥራ ለአሳታሚዎች ከሰጠ በኋላ ልቡን ታሞ ቦሌ አካባቢ በሚገኘው አዲስ የልብ ህክምና ማዕከል ገብቶ እንደነበር ያስታወሰው አለማየሁ፤ ወደ አሜሪካ ከሄደ በኋላ ግን በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆኑን ደውሎ እንደነገረው ይገልፃል፡፡
ሌላው የአስማማው የቅርብ ወዳጅ በኢትዮጵያ የዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አቶ አቤይቱ መላኩ ስለሁኔታው ሲያስረዱ፤ አስማማው ቀደም ሲል የካንሰር ህመም አጋጥሞት በህክምና መዳኑን ጠቁመው፣ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅት በሳንባ ህመም መያዙንና ቦሌ በሚገኘው አዲስ የልብ ህመም ህክምና ማዕከል አስገብተው እንዳሳከሙት፣ ከህመሙም ድኖ ወደ አሜሪካ መመለሱን ገልፀዋል፡፡ አሜሪካ ከሄደ በኋላ እንደተሻለው ገልፆልኝ ነበር የሚሉት አቶ አቤይቱ፤ ሆኖም እንደገና ታሞ ኮሎምቦስ ኦሃዩ በሚገኝ ሆስፒታል ገብቶ መታከሙን ተናግረዋል፡፡ ከዚያም ፊላደልፊያ ሄዶ እዚያም መታመሙንና ሳንባው ውሃ ቋጥሮ ለህልፈት መዳረጉን አቶ አቤይቱ ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ ቀብሩ የትና እንዴት ይከናወን በሚለው ጉዳይ ላይ ከዘመድ ወዳጆቹ ጋር እየመከሩ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል፡፡ “አስማማው ያልተዘመረለት ትልቅ ሰው ነው” ያሉት አቶ አቤይቱ፤ “የእሱ ስራና ታሪክ በአግባቡ ሊዘከር ይገባል” ብለዋል፡፡
ሌላው የቅርብ ወዳጁ፤ ደራሲና ሃያሲ አለማየሁ ገላጋይ በበኩሉ፤ “አስማማው ብዙ ፅሁፍና ታሪክ ማምረት በጀመረበት ወቅት መሞቱ ያስቆጫል” ሲል በሀዘን ተሞልቶ ተናግሯል፡፡

ብዙ ጊዜ በብዙኃን መገናኛዎች ሳዳምጥና ስመለከት አንድ እጅግ የሚገርመኝን ነገር በተደጋጋሚ አዳምጣለሁ እመለከታለሁ፡፡ ነገሩ ምን መሰላቹህ፡- በስደትም በሥራም በተለያየ ምክንያት ከሀገር ወጥተው በባዕድ ሀገራት የሚኖሩ ወገኖቻችን በተለይም ፕሮቴስታንቶች (ተቃዋሚዎች) እንዲያ በምቾት በድሎት የሚኖሩበትን ሀገር “እግዚአብሔር አብዝቶ የባረከው ሀገር!” በማለት በተደጋጋሚ ይገልጻሉ፡፡ የእኛ ሀገር ደግሞ ሕዝብ በረሀብ በችግር በስቃይ የሚኖርበት ሀገር ስለሆነች እግዚአብሔር የረገማት የጠላት ሀገር […]

The post የተባረኩ ሀገራት ወይስ የተረገሙ? የተባረኩ ሕዝቦች ወይስ የተረገሙ? appeared first on ሳተናው .

ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንን ጨምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከአናሎግ ወደ ዲጂታል ለሚደረግ የቴክኖሎጂ ሽግግር ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ቢደረግም አልተሳካም። ፕሮጀክቱ በ2001 ዓም ተጀምሮ በ3 አመታት ውስጥ መጠናቀቅ ነበረበት። ከብሮድካስት ባለስልጣን የወጣ መረጃ እንደሚጠቁመው ስራው ሊሳካ ያልቻለው በሙስናና በብልሹ አሰራር ምክንያት ነው። ሀገር አቀፍ የሬዲዮና የቴሌቭዥን የማስፋፊያ …

ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአገሪቱ የሚታየው የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት እጥረት ካለፉት ስድስት ወራት ወዲህ ለታየው አጠቃላይ የዋጋ ንረት መባባስ አንድ ምክንያት መሆኑን ከንግድ ሚኒስቴር የተገኘ አንድ የጥናት ሰነድ ጠቆመ፡፡ በምግብ ነክ ምርቶች ላይ ማለትም በምግብ ዘይት፣ ዱቄት፣ ፓስታና ሞኮረኒ፣ በዳቦ ምርቶች ላይ የተሰማሩ አነስተኛና መካከለኛ አንዱስትሪዎች በኤሌክትሪክ እጥረት ምክንያት ከማማረት አቅማቸው …

ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንደኛ ተከሳሽ ሶሊያና ሽመልስ በሌለችበት፣ሶስተኛ ተከሳሽ ናትናኤል ፈለቀ ፣ አምስተኛ ተከሳሽ አጥናፍ ብርሃኔ፣ስድስተኛ ተከሳሽ አቤል ዋበላ፣ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ የተሰናበቱ ሲሆን፣ ሁለተኛ ተከሳሽ በፍቃዱ ኃይሉ ከሽብር ክስ ነፃ የተባለ ቢሆንም ማአከላዊ ምርመራ በኃይል እና በማሰቃየት የሰጠው ቃል ላይ አመፅ እንዳነሳሳ አምኗል በሚል በወንጀል ህጉ 257 መሰረት እንዲከላከል …

ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ማንነታቸው ያልተገለጸው የ61 አመቱ ኢትዮጵያዊ አምሰተልፊን በምትባል ከተማ ውስጥ የተያዙ ሲሆን፣ ግለሰቡን ወደ ኢትዮጵያ ይመለሱ ወይም አይመለሱ የሚልውን ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ የ90 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል። ግለሰቡ በደብረማርቆስና መተከል አውራጃዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸውንና ማሰራቸውን በውጭ አገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መረጃ መሰብሰቡን ፖሊስ አስታውቋል። በግለሰቡ ላይ ቀድም ብሎ …

ጥቅምት ፭ (አምት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ፣ዲፕሎማትና የታሪክ ተመራማሪ የነበሩት የቀድሞ አምባሳደር ዘውዴ ረታ ባለፈው ሳምንት እንግሊዝ ለንደን ውስጥ መንገድ ላይ በመውደቃቸው ባጋጠማቸው ድንገተኛ አደጋ ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል። አምባሳደር ዘውዴ በአዲስ አበባ ከተማ ነሐሴ 7ቀን 1927 ዓ.ም በወቅቱ ሥጋ ቤት ሠፈር ተብሎ በሚጠራውና በአሁኑ ወቅት ኦርማ ጋራዥ በሚባለው አካባቢ የተወለዱ ሲሆን የሦስት ልጆች …

ኢሳት ዜና (ጥቅምት 5፡ 2008) የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድቤት በሽብርተኛ ወንጀል ክስ፣ የክስ ሂደታቸው በመታየት ላይ የነበሩ አራት ጦማሪያን ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ ዛሬ አርብ ወሰነ። በጦማሪያኑ ላይ የመጀመሪያ ዙር ውሳኔውን ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀው ፍርድ ቤቱ በጦማሪያኑ ክሳቸውን መከላከል ሳያስፈልጋቸው በአንድ አመት በላይ የቆየው የእስር ጊዜያቸው አብቅቶ በነጻ እንዲሰናበቱ ትዕዛዝ መስጠቱ ታውቋል። ይሁንና …

ዞን ዘጠኝ በመባል በሚታወቁት አራት የድረገጽ ጸሐፍት እና አንድ ጋዜጠኛ ላይ በሽብርተኝነት የቀረበባቸዉን ክስ ፍርድ ቤት ዛሬ ዉድቅ አደረገ። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ላይ የቀረበዉ ማስረጃ ሁሉ ደካማ መሆኑን ማመልከቱን የፈረንሳይ የዜና ወኪል ከአዲስ አበባ ዘግቧል።

የፍትሕና ልዕልና ጋዜጦች፣ እንዲሁም የፋክትና የአዲስ ታይምስ መፅሔቶች ባለቤትና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ከታሠረ ፤ ጥቅምት 3 ቀን 2008 ዓ.ም አንድ ዓመቱን ደፍኗል፡፡ የተመስገን ጤና አሳሳቢ መሆኑን ቤተሰቡቹ ገልጸዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ግን ተመስገን ሕክምና እያገኘ መሆኑን ጤናማም እንደሆነ ይናገራል፡፡