ጥቅምት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኑዌር ዞን ዋና ከተማ ከሆነቸው ንያንግ 30 ኪሜ ራቅ ብሎ በሚገኘው የህንዱ ካራቱሪ ኩባንያ አጠገብ በሚገኘው አንዱራ የአነስተኛ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት ዙሪያ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የደቡብ ዲዛይንና ግንባታ ሲፐርቪዥን ኢንተርፕራይዝ ሰራተኛ የሆኑት ኢንጂር ሙሉጌታ ደሳለኝ እና የጋምቤላ የእርሻ ቢሮ ሰራተኛ የነበሩት ወ/ሮ ሃይማኖት ተገድለዋል። …

ጥቅምት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ በሽብረተኝነት ወንጀል የተከሰሱት አቶ ደህናሁን ቤዛና አቶ ምንዳዬ ጥላሁን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ቀርበው እንዲመሰክሩ ፍርድ ቤቱ ለተለያዩ አካላት ደብዳቤ እንዲጽፍላቸው ለልደታ ፍርድ ቤት 19ኛው ወንጀል ችሎት በድጋሜ ደብዳቤ ጽፈዋል። ቃሊቲ እስር ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፣ ቃሊቲ አለመታሰራቸውን ጥቅምት 12 ፣ 2008 ዓም …

ጥቅምት ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ገዳሪፍ አቅራቢያ በተቀሰቀሰ ውጊያ 16 ሱዳናዊያን መገደላቸውን፣ 12 መቁሰላቸውን እንዲሁም 7ቱ ታግተው መወሰዳቸውንና የደረሱበት እንደማይታወቅ ከ300 በላይ የቁም ከብቶችም መዘረፉን የቀድሞው የአገሪቱ ጦር አዛዥና የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ለፓርላማ ሪፖርት አቅርበዋል። ኢስማት አብዱረሕማን ” ሽፍቶች” ያሉዋቸው መሬታችንን አሳልፈን አንሰጥም ያሉ የኢትዮጵያ አርሶ …

በትናንትናው ዕለት አመሻሽ ላይ አስሩ የፌደራል ፖሊሶች መጀመሪያ አንድ አይሱዙ የጭነት መኪና በኃይል በማስገደድ አስቁመው የተሳፈሩ ሲሆን መኪናው መንቀሳቀስ ሲጀምር “የጫንካቸውን ፖሊሶች አራግፍ አለያ ከነንብረትህ አብረህ ትጋያለህ!” የሚል የስልክ ማስጠንቀቂያ መልዕክት ለአሽከርካሪው በመድረሱ አሽከርካሪው መኪናውን አቁሞ ፖሊሶቹን “አልሄድም” ይላቸዋል፡፡ ቀጥሎም ፌደራል ፖሊሶቹ ሾፌሩን ለማንገራገር ሞክረው ትዕዛዛቸውን በቀላሉ ሊቀበል ባለመቻሉ ስልክ ተደዋውለው ሌላ ላንድ ክሩዘር መኪና […]

ፍሪደም ሃውስ (Freedom House) መቀመጫውን እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገና በመናገር ነጻነት ላይ የሚሠራ ዓለም አቀፍ ተቋም ነው፡፡ይህ ተቋም መንግሥታት ለሕዝቦቻቸው የሚሠጡትን የኢንተርኔት ነጻነት አጥንቶ እያንዳንዱ ሀገር ያለበትን ደረጃ ‹‹Freedom on the net 2015 ›› በሚል ርዕስ ስር ሪፖርት አውጥቷል፡፡ በዚህ ሪፖርት ሰንጠረዥ‹‹ኢትዮጵያ ከቻይና፣ከሦሪያ እና ከኢራቅ ቀጥሎ ምንም ዓይነት የኢንተርኔት ነጻነት የሌለባት አገር ተብላለች፡፡ Listen

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር በትጥቅ ትግል መንግስት ለመቀየር የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ኃይሎች ውጤት አያመጡም ብለዋል። በአሥመራ የሚገኘውን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጨምሮ የሁለት ድርጅቶች ምላሽ ሰጥተዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ጥቅምት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ፣ “የአመጹ ወጣቶችን አጋልጡ” በሚል የመከላከያ ሰራዊት አባላት በግለሰቦች ቤት እየገቡ አዛውንቶችን፣ ወጣቶችንና ሴቶችን እየደበደቡ ሲያስሩ ከሰነበቱ በሁዋላ ትናንት ከምሽቱ ሶስት ሰአት ጀምሮ፣ ከጫካ በመጡ ወጣቶችና በመከላከያ ፖሊስ አባላት መካከል ለሰአታት የቆየ የተኩስ ልውውጥ ተካሂዷል። ኢሳት ከተለያዩ ነዋሪዎች ባደረገው ማጣራት ከቴፒ 7 ኪሎሜትር …

በየዓመቱስለጡት ጥቅምት ወር ካንሰር ግንዛቤ የማስጨበጫ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ ሃገራት ይካሄዳሉ። አመጋገብ ላይ ጥንቃቄ ከማድረግ አንስቶ የሰዉነት እንቅስቃሴ ማዘዉተር የትኛዉንም የአካል ክፍል ከሚያጠቃ ካንሰር ለመከላከል የሚረዳ ተቀዳሚ ርምጃ መሆኑን ሃኪሞች ይመክራሉ።

Prof. Merara Gudina
የኦሮሞ ፌደራሊስት ሊቀመንበር እና የመድረክ የአመራር አባል የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና ይህን ምላሽ የሰጡት ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀረበውን የውይይት ግብዣ ተቃዋሚዎች ውድቅ ማድረጋቸውን ለፓርላማ አባላት መናገራቸውን ተከትሎ ነው። መንግስት በጠራው የአምስት ኣመታት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውይይት ላይ ያልተሳተፉ እንደመድረክ፣ ሰማያዊ እና መኢአድ ያሉ ፓርቲዎች ያቀረቡት ምክንያተ ውሃ ያማያነሳ ነው ያሉት አቶ ሃይለማርያም ፣ ፓርቲዎቹ ያልተሳተፉት በሕጋዊ መንገድ የተመረጠ መንግስት አይደለም በማለት መሆኑን ጠቅሰው ወደፊት ከየትኛው መንግስት ጋር እንደሚወያዩ እናያለን ሲሉ ዝተዋል፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ከ30 ዓመታት በፊት የክብር ዶክተር ወ/ሮ አበበች ጎበና ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ያቀናሉ። እናም ያኔ ወቅቱ በሀገሪቱ የረሃብ አደጋ ያጠላበት ጊዜ ነበርና አንዲት ሕፃን የእናቷ አስክሬን እቅፍ ስር ሆና ጡት ለመጥባት ትሞክራለች። ይህ ትዕይንት እጅግ ከፍተኛ ሐዘን ውስጥ ይከታቸዋል።

ጥቅምት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ሽመልስ ፣ አቶ በረከት ስምኦን ከኮምኒኬሽን ሚኒስትርነት ተነስተው በአቶ ሬድዋን ሁሴን ከተተኩበት ካለፉት ሁለት ዓመት ተኩል ወዲህ ከአቶ ሬድዋን ጋር መስማማት ባለመቻላቸው በስራ ገበታቸው ላይ የሚገኙት አልፎ አልፎ ነበር፡፡ የሁለቱ ሚኒስትሮች አለመግባባት በኢሳት ከቀረበ በኃላ ችግር የለብንም ለማለት ለአንድ ቀን አብረው መግለጫ በመስጠት ጎን ለጎን …

ጥቅምት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ብአዴን ወጪውን የሚሸፍነው በዋነኝነት ከነጋዴዎችና ከነዋሪዎች ነው። በርካታ የክልሉ ነጋዴዎች ገንዘብ እንዲለግሱ የጥሪ ወረቀት ደርሶአቸዋል። ድርጅቱ ከህወሃትና ከኦህዴድ ባላነሰ መልኩ በአሉን እንደሚያደርግ እየገለጸ ሲሆን፣ አገሪቱ ከፍተኛ የረሃብ አደጋ አንዣቦባት ባለበት እንዲሁም የኑሮ ውድነቱ የህዝቡን ኑሮ ፈተና ውስጥ በጣለበት ሰአት ይህን ያክል ገንዘብ ህዝቡን …

የአቅም ግንባታ ፕሮጀክቱ፣ በአህጉረ ስብከት እና በአጥቢያ ሠራተኞች ሥልጠና ይቀጥላል “ለቤተ ክርስቲያን መልካምነትም ኾነ ውድቀት መሪዎች ትልቁን ድርሻን ይወስዳሉ፡፡” /ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል/ በመንፈሳዊ አመራር እና በዘመናዊ የሙዓለ ንዋይ አስተዳደር፣ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችን አቅም በማጎልበት ክሂሎታቸውን ለማዳበር ያስችላል የተባለ የከፍተኛ ሓላፊዎች ሥልጠና በልማት እና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ተሰጠ፡፡ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እና በመላው አህጉረ …

ጥቅምት ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መነሻቸውን ከሶማሊያ የባሕር ዳርቻዎች በማድረግ በሕገወጥ መንገድ ሕይወታቸውን ለአደጋ አልጋልጠው በጦርነት ሰላሟ ወደራቃት የመን የሚሰደዱ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ቁጥር መጨመሩን ዓለምአቀፉ የስደተኞች ድርጅት በምህጻረ ቃል /UNHCR/ አስታውቋል። ባለፈው ዓመት ብቻ ከ70 ሺ በላይ አዲስ ስደተኞች የመን መግባታቸውን የገለጸው ድርጅቱ፣ ጥቂት የሶማሊያ ዜጎች ሲገኙበት አብዛኞቹ ስደተኞች ኢትዮጵያዊያን ናቸው። …

የመቅደላው ጀግና ዐፄ ቴዎድሮስ በመጨረሻዋ ሰዓት ለጄኔራል ናፒየሪ በጻፉት ደብዳቤ አበክረው የጠየቁት ነገር ከሁለት ቀናት በፊት በተደረገው ውጊያ የወደቀውን የወዳጃቸውንና የጦር መሪያቸውን የፊታውራሪ ገብርዬን አስከሬን ለመቅበር እንዲፈቀድላቸው ነበር፡፡ ‹‹ፊታውራ ገብርዬን የኔን ወዳጅ ሳላነሣው ያደርኩ ከሞትኩኝ ሁሉንም አብረው ይቅበሩኝ ብየ ነበር፡፡ …

የወታደሮቻችን ነገር (ዳንኤል ክብረት) Read more »

ራያ ቆቦ አካባቢ በኢትዮጵያ እጅግ ለም ከሚባሉ መሬቶች አንዱ ነው። ወያኔ በምስራቁ አቅጣጫ ከዓለታማ ክልላቸው ባሸገር ያሉትን ለም የወሎ ወረዳዎች ከወሰዱ ቆዩ ኮረም፣መሆኒ፣ራያ፣አዘቦ….ልጆቹም የአማርኛ መጻህፍቶች እየተቃጠሉ በትግርኛ እንዲማሩ ተደረገ። አሁን ደግሞ ዓይን ባወጣ መልኩ ቆቦ ወረዳን ለመዋጥ አሰፍስፏል። ድንበራችን አለውሃ ድረስ ነው የሚለውን ትርክት በየቀኑ ከሊቅ እስከ ደቀቅ የሚያነበንቡት ነው። የህወሀት ማባበያ የሚሆኑ አሳሂ ስልቶችም […]

ይህ ጽሁፍ የዞን፱ ጦማርን አስልክቶ በቀለም ቀንድ ጋዜጣ ላይ የወጣ ነው ፡፡ አርታኢው በጠየቁን መሰረት ለዞን9 ነዋርያን ይነበብ ዘንድ እዚህ አትመነዋል፡፡

በሙሉቀን ተስፋው

ብዙዎቻችን ስለ ዞን ፱ ጦማርያን እንጅ ስለ ‹ዞን ፱› ብሎግ ያለን ግንዛቤ ውስን ሊሆን ይችላል፡፡ እንዴት ተመሰረተ? ለምን ዞን ፱ ተባለ? ጦማርያኑ ተጠራርገው ወደ እስር እስኪወርዱ ድረስ ምን አከናወኑ? ለምን ሁሉም ሊታሰሩ ቻሉ? እንዴት ተፈቱ በሚለው ላይ ዘርዘር አድርገን ለማዬት ወደድን፡፡
በ2004ዓ.ም. ከወደ ቤሩት አንድ መጥፎ ነገር ተከሰተ፡፡ ‹ዓለም ደቻሳ› የተባለች ኢትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ተገደለች፡፡ የሚያሰሯት ሰዎች ታማ ነው የሞተች ቢሉም የሊባኖስ ቴሌቪዥን በአሰሪዎቿ በገመድ ስትጎተት የሚያሳይ ምስል ለቀቀ፡፡ ብዙ ኢትዮጵያውያንን አስቆጣ፡፡የበለጠ የሚያሳዝነው ደግሞ ‹ዓለም› የሁለት ልጆች እናት ስትሆን ወደ ቤሩት የሄደችውም ገንዘብ ተበድራ ነበር፡፡ ‹ልጆቼንና ቤተሰቦችን ከችግር አድናለሁ› የሚል ተስፋን ይዛ የተጓዘችው ዓለም የተበደረችውን ገንዘብ እንኳ ሳትከፍል ሕይወቷ ማለፉ ሀዘኑን የከበደ አደረገው፡፡‹ዓለምን› ዓለም ከዳቻት፡፡ በማህበራዊ ሚዲያው በሰፊው ተራገበ፡፡
ከአስር በላይ የሆኑ ሰዎች በፌስ ቡክ ‹‹የዓለምን ቤተሰቦች ለምን አንረዳም›› የሚል እንቅስቃሴ ጀመሩ፡፡ አንዳንዶቹ በርግጥም ቀደም ሲል ጀምሮ የራሳቸው ብሎግ ነበራቸው፡፡ ብዙ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ ሰው ሐሳቡን ደገፈው፡፡ ምናልባትም ማህበራዊ ሚዲያ መሬት የነካ ስራ በኢትዮጵያ የተሰራበት የመጀመሪያ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ዘመቻው ፍሬ አፈራና በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ለዓለም ደቻሳ ቤተሰቦች ድጋፍ የሚውል የገቢ ማሰባሰብ መርሐ ግብር በሚያዚያ 2004 ዓ.ም ተዘጋጀ፡፡ አዘጋጆቹ ደግሞ እኚሁ ከደርዘን በላይ የሆኑ ልጆች፡፡ ገቢማሰባሰቡ ውጤታማ ሆነና የተፈለገው ድጋፍ ለዓለም ቤተሰቦች ተሰጠ፡፡
ከአዘጋጆቹ ጥቂት የሚሆኑ ልጆች ለምን ይህ ሆነ? የሚል ጥያቄ አንስተው በሰፊው ተወያዩ፡፡ የሥርዓቱ ብልሹነት ዜጎችን ለዚህ እንደሚዳርጋቸው ለማወቅ ጊዜ አልፈጀባቸውም፡፡ አማካሪም ቀጥረውም ማስጠናት የሚጠይቅ አልነበረም፡፡ ከብላቴናዎቹ የእሳቤ አድማስ በላይም አልሆነም፡፡ለሁሉም ግልጽ የሆነ ነገር ነው፡፡ ሥርዓቱ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን እኩል የሆነች፣ ዜጎች በአገራቸው ሰርተው የሚያድጉበት መንገድ ዝግ የሆነባት፤ ዜጎቿ በሰው ሀገር እንደ ዓለም ደቻሳ ኢሰብዓዊ በሆነ መልኩ ሲገደሉ እንኳ መጠየቅ የማይችል እንደሆነ ለማወቅ የመጠቀ አእምሮ ባለቤት መሆን አይጠይቅም፡፡ ግልጽና ግልጽ ፍንትው ብሎ የሚታይ እውነታ ነው፡፡
ብላቴናዎቹ የችግሩን ምንጭስ አወቅን፤ ከዚህ በኋላ ምንድን ነው ማድረግ የምንችለው? የሚል ወሳኝ ጥያቄ አነሱ፡፡ የዚህን ጥያቄ መልስ ማገኘት ቀላል ነው፤ ግን መስዋትነት ይጠይቃል፡፡ ለዚያውም የወጣትነት የጌጥ ዘመንን የሚበላ መስዋትነት፡፡ መስዋትነቱ ወንጀል ስለሆነ አይደለም-ግን በአፋኝ ሥርዓት ውስጥ ለመብት ቦታ የለም፡፡ ሀገራችን የጋራ እናድርጋት፤ ስለሚያገባን ስለሀገራችን እንነጋገር፤ አማራጭ ሐሳብ እናቅርብ ማለት ያስወነጅላል፡፡ በሞት ፍርድ አሊያም በእድሜ ልክ እስራት ሊያስቀጣ ይችላል፡፡ የማን ደፋሮች ናቸው ፈርዖንን የሚናገሩ? በፈርዖን ላይ ማነው ከቶ ምላሱን የሚያነሳ? እንደሙሴ ኮልታፋ ለመሆን ካልሆነ በስተቀር? ያስብላል፡፡ ለፈርዖን የሰው ልጆች ደምናስቃይ የሰርግና የምላሽ ያክል ይጥሙታል፡፡ የጨቋኝነት ባህሪው ይኸው ነውና፡፡
ብላቴናዎቹግን ይህን አስበው ፈርተው ወደ ኋላ አላፈገፈጉም፡፡ የዓለምን ቤተሰቦች ለመርዳት ዝግጅቱን ካስተባበሩት 5 ልጆች፣ ፌስ ቡክ ላይ በንቃት ይከታተሉ ከነበሩት ደግሞ 4 ልጆች ሲደመሩ 9 ያክል ልጆች ሆነው የ‹አክቲቪዝም› ሥራ ለመስራት ዝግጅታቸውን አጠናቀቁ፡፡የፖለቲካ እስረኞችን በፕሮግራም ለመጠየቅ የእቅዳቸው አካል አደረጉት፡፡ በፌስ ቡክ፣ ቲዊተርና በየነ መረብ ዘመቻ ጀመሩ፡፡ በ2005ዓ.ም. ከእለታት በአንደኛው ቀን ‹ርዕዮት አለሙን› ለመጠየቅ 9 ሆነው ቃሊቲ ወረዱ፡፡ ርዕዮት አለሙ ጋር እያወሩ አንዲት ‹አሸባሪ› ሴት ‹‹እንዴት ናችሁ ዞን ፱ኞች?›› አለቻቸው፡፡ ስሟ ሒሩት ክፍሌ ይባላል፤ በግንቦት 7 አባልነት ቃሊቲ የወረደች ‹አሸባሪ ሴት› ናት፡፡ ብላቴናዎቹ ግራ ገባቸው፤ ‹ይህች ሴት እብድ ናት እንዴ?› ሳይሉ አይቀሩም፡፡ በእርግጥ በጠባብ አጥር ውስጥ ከብዙ ቶርቸርጋር መኖር ሊያሳብድ እንደሚችል ግልጽ ነው፡፡ ባሕታዊ እንዳይሏት ቃሊቲ ገዳም አይደለም፡፡
ርዕዮት አለሙ ብዙ እንዲጨነቁ አልፈቀደችም፡፡ በዝርዝር የ‹አሸባሪዋን ሴት› ንግግር ተረጎመችላቸው፡፡ ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ ቃሊቲ ማረሚያቤት በስምንት ዞን የተከፋፈለ ነው፡፡ ለካ የቃሊቲ ታሳሪዎች እኛን ከማረሚያ ቤቱ አጥር ውጭ የምንኖረውን ዜጎችን ‹ዞን ፱ኞች› እያሉ ነው የሚጠሩን፡፡ ስለዚህ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥ አንድ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ‹ልማታዊው አርቲስት ሸዋፈራው ደሳለኝ› ቢያዘጋጅ እንዲሁም ለተወዳዳሪዎቹ ‹‹ሰፊውና ብዙ እስረኛ ያለበት ዞን የትኛው ነው?›› ብሎ ቢጠይቅ መልሱ ‹‹ዞን ፱››የሚል ይሆናል፡፡ ሚስጥሩ ግልጽ ነው፤ በአምባገነን ሥርዓት ውስጥ ሁሉም ዜጋ እስረኛ ነው፤ ሁሉም ዜጋ የፈርዖን ግዞተኛ ነው፡፡
በበየነመረብ ለሚያደርጉት ዝግጅት ማን እንበለው? እያሉ ሲያነሱ ከብላቴኖቹ አንዱ ጆማኔክስ ‹የአሸባሪዋን ሴት› ቃል ‹‹ለምን ዞን ፱አንለውም?›› የሚል ሐሳብ አቀረበ፤ በሙሉ ድምጽ ጸደቀ (እንደ ኢህአዴግ ፓርላማ እንዳትሉ አደራ)፡፡ ብላቴኖቹ ‹‹ስለሚያገባን እንጦምራለን!›› የሚል መሪ ቃል ይዘው ዘመቻቸው ጀመሩ፡፡ ዘመቻው ፍጹም ሰላማዊ፣ ብዕር እንጅ ጥይት ያልያዘ፣ ሰላምን እንጅ ጥፋትንያልሻተ፣ በፊትም በኋላውም ምንም ኮልኮሌ የሌለው ነበር፡፡
ልጆቹ በጋራ ‹‹የሚያገባው ትውልድ ፍለጋ›› የሚል በጋራ ስለሀገራችን እንነጋገር፤ የጋራ ትርክት እንፈለግ የሚል ይዘት ያለው ጽሁፍ ጻፉ፡፡ድረ ገጹ በተከፈተ በ15ኛ ቀኑ ሀገር ውስጥ ያሉ ሰዎች እንዳያዩት ታገደ፡፡ ለፈርዖን ምን ይሳነዋል? ጌታውን አመስግኖ ማደር ያለበትን ምስኪን ሕዝብ ስለምን የእነዚህን ብላቴኖች ወግ ያነባል? በቃ ተከለከለ፡፡ ያም ሆኖ አራት ተከታታይ የበየነ መረብ ዘመቻዎች ተካሄዱ፡፡አንደኛው ሕገ መንግሥቱ የጸደቀበትን 18ኛ ዓመት በዓል ሲዘከር ‹‹ሕገ መንግሥቱ ይከበር›› ያልተከበሩ የሕገ መንግሥቱን አንቀጾች ዘርዝረው ተቹ፡፡ ‹‹ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት አሁኑኑ ለሁሉም!›› በማለት አንቀጽ 29ን መሰረት በማድረግ ዘመቻውን ደገሙት፡፡ሦስተኛም ‹‹የሰላማዊ ሰልፍ መብታችን ይመለስ!›› ሲሉ ሠለሱት፡፡ 4ተኛም ‹‹ኢትዮጵያዊ ሕልም ኑ አብረን እናልም!›› ሲሉ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡
የልጆቹ ድምጽ ቀልቃላ ነበር፤ ብዙ ርቀት ብዙ በጣም ብዙ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ የሚሰማ፡፡ እንቅልፍ የሚቀሰቅስ ድምጽ! ፈርዖንን የማያስተኛ፡፡እነዚህ ነገረኞች ‹‹የዞን ፱ ዐመታዊ መጽሐፍ›› ብለው በነጻ አደሉ፡፡ አዲስ ራዕይ በገንዘብ በሚቸበቸብበት አገር በነጻ አንብቡብሎ መስጠት ምን ይሉታል? ግን ሆነ፡፡ መጽሐፉ በደረ ገጻቸው በነጻ ተለቀቀ፡፡
ከዚህ በኋላ ፈርዖን ትዕግዙ አለቀ፡፡ በመጀመሪያ በጓደኞቻቸው ማስፈራሪያ ተላከባቸው፡፡ ‹ፈርዖን አምርሯል፤ ከዚህ በኋላ ውርድ ከራሴ›ተባሉ፡፡ በ2006 ዓ.ም. ሁለቱን ብላቴኖች ከመላእክት የፈጠኑ ደህንነቶች ጠርተው ‹‹ስለምን አትሰሙም? ጌቶቻችን ስለምን ታስደነብራላችሁ? ካላረፋችሁ ቀሳፊ መልኣክ እንልካለን›› አሏቸው፡፡
መደናገጥ ተፈጠረ፡፡ ልጆቹ አሁንም ጠየቁ- የሠራነው ወንጀል ምንድን ነው? አሉ፡፡ መልሱ ግን ምንም ነው፡፡ ሙሴስ ቢያንስ ወገኖቹን ለማዳን የሌላ ሰው ሕይወት አጥፍቶ ነው የተሰደደ፤ እኛ ግን ምንም አልሰራንም፡፡ ስለዚህ የጌቶች ንዴት እስኪበርድ እንጠብቅና እንቀጥል ሲሉ መከሩ፡፡ ያም ሆኖ ምርጫ 2007 እየቀረበ መጣ፡፡ ይህ ምርጫ ዝም ብሎ መሆን የለበትም፤ ምንም እንኳ ጌቶች ባይወዱትም ዜጎች በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ሕዝብ የማንቃት ሥራ እንጀምር አሉ- በምክር ቤታቸው፡፡ የነዚህ ልጆች ምክር ቤት 547 ወንበር ላይ ከተጎለቱ ሰዎች በላይ ማነቃቃት የሚችል ከቶ ምን አይነት ታምር ቢሆን ነው? ያስብላል፡፡
በሚያዚያ2006 ዓ.ም በብሎጋቸው ምርጫ 2007ን በተመለከተ በሰፊው እንደሚሰሩ ባበሰሩ በሳምንቱ ከሚያዚያም በ17ኛው ቀን ከፈርዖን ዘንድ የጥፋት መልእክተኞች 9 ልጆችን ለቃቅመው ወሰዱ፡፡ ስድስቱ ከጦማርያን ወገን ሲሆኑ ሦስቱ ደግሞ ሐሳባቸውን የሚደገፉ ጋዜጠኞች(ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይሉና ኤዶም ካሳዬ) የጥፋት መልእክተኞች ሰለባ ሆኑ፡፡ ከጦማርያኑ ሦስቱ ደግሞ ከጥፋት ውሃ እንዲድኑ እግዚአብሔር ስለፈቀደ ከነነዌ ወጥተው ነበር፡፡ ለወሬ ነጋሪ ሶልያና ሽመልስ፣ ጆማኔክስ ካሳዬና እንዳልካቸው ኃ/ሚካኤል ቀሩ፡፡ ‹ሙሴም ከምድያም ምድር የተመለሰው ፈርዖን እንደማይጎዳው ባወቀ ጊዜ ነው፤ እኛም የፈርዖን ብርታት እስኪደክም ወደ ነነዌ አንመለስም› ብለው ይመስላል እንደወጡ ቀሩ፡፡
የታሰሩት ግን የእድሜያቸው 84 ቀን በማዕከላዊ አለፈ፤ አንዲት አራስ ሴት ልጇን ወልዳ ክርስትና አስነስታ እንግዶቿን ሸኝታ ወደ ባሏ የምትመለስበትን ጊዜ ያክል፡፡ 75 ቀናት ግን በጨለማ ክፍል ውስጥ ፀሀይ የማታውቀው ሀገር – ማዕካላዊ ሳይቤሪያ፡፡ በሳይቤሪያ ጥፊና በትር የእለትምግባቸው ሆኖ ስድብ እንደ ምርቃት እየቆጠሩት ቶርቸር ከፈጣሪ የተላከላቸው መና ሆኖ፣ ከባድ ስፖርት እየሰሩ ያን ያክል ጊዜ ቆዩ እንጅ እንደ አራስ አጥሚት እየጠጡ ገንፎ እየሰለቀጡ አልነበረም፡፡
በ2006 ሐምሌ በገባ 11ኛው ቀን ሲሆን ክስ ተፈጠረባቸው፡፡ ሲያንስ 15 ዓመት በእስር በሚያቆየው ሲበዛ ደግሞ ከመሬት በሚስወግደው በሐሙራቢ ሕግ ጨካኝ አንቀጽ ‹ሽብር ማነሳሳት፣ ለማነሳሳት ማሰብ፣ ማሴር…› በሚለው ተወንጅለው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ‹‹የቀለም አቢዮት ለማስነሳትአስባችኋል›› አሏቸው፡፡ ምስክሮች ቀረቡ፡፡ ሠልስቱ ደቂቃን በናቡከደነፆር ዙፋን በቀረቡ ጊዜ ምስክሮቹ የተናገሩትን የመሰለ ነበር፡፡እነዚያ ምስክሮችስ ቢያነስ ለቆመው ምስል እንደማይሰግዱ ያውቃሉ፡፡ አለመስገድም ወንጀል የሆነበት ዘመን ነበር፡፡
ፍርዱ እየተጓተተ አንድ አመት አለፈ፡፡ እድሜም እንደዋዛ ቆጠረ፡፡ የጓጉለት ምርጫ ድራማ በቃሊቲ ሆነው አለፈ፡፡ በየጊዜው ፍርድ ቤት ይመላለሳሉ ግን ምንም ውሳኔ የለም፡፡ ምርጫ ካለፈ በኋላ ለብይን ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ተያዘ፡፡ ቀደም ብሎ ግንሐምሌ 1 ቀን 2007 ዓ.ም ክሱ ተቋርጦ 5ቱ ልጆች ማለትም በክስ መዝገብ 4ኛ ተከሳሽ ማህሌት ፋንታሁንና 6ኛ ተከሳሽ ዘላለም ክብረት (ሁለቱም ጦማርያን) እንዲሁም 8ኛ ተከሳሽ አስማማው ኃ/ጊወርጊስ፣ 9ኛ ተከሳሽ ኤዶም ካሳየና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋለም ወልደየስ(ሁሉም ጋዜጠኞች) ወጡ፡፡
ጥቅምት5 ቀን 2007 ዓ.ም. ደግሞ ከአንድ ዓመት ከአምስት ወር በኋላ 1ኛ ተከሳሽ ሶልያና፣ 3ኛ ተከሳሽ ናትናኤል፣ 5ኛ ተከሳሽ አጥናፍ እና 7ኛ ተከሳሽ አቤል በነጻ ተሰናበቱ፡፡ 2ኛው ተከሳሽ በፍቃዱ ኃይሉ ጽሑፎችህ ሽብር ያነሳሳሉ ተብሎ ተለይቶ ቀረ፡፡ የበፍቃዱ ክስ ወደ ወንጀል ተቀይሮ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 257/ ሀ ከአስር ቀን እስከ 6 ወር እስር ሊያስቀጣ በሚችል ወንጀል ተቀየረ፡፡ ምንም እንኳ የተከሰሰበት ወንጀል ሊያስቀጣ የሚችለውን ሦስት እጥፍ በእስር ቢያሳልፍም በ20000 ብር (ሃያ ሽህ ብር) ዋስ ከ544 ቀናት በኋላ በቂሊንጦ የተሰጠውን የሊዝ ቦታ ለተረኛ አስረክቦ ወጥቷል፡፡
ዞን ፱ኞች በአንድ ዓመት ከ5 ወር ጊዜ ውስጥ 39 ጊዜ ፍርድቤት ተመላልሰዋል፡፡ በፈቃዱ ለ40ኛ ጊዜ የፊታችን ህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ይቀርባል፡፡

በጨረሻም አልን ‹‹ኢትዮጵያዊ ህልም ኑ አብረን እናልም!››

አበቃሁ

(ይህጽሁፍ የተዘጋጀው ከእስር የወጡ የዞን 9 ጦማርያን ጋር በተደረገ ውይይት ነው፡፡) 

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም አመሻሽ ላይ አምሳሉ ተሾመ የተባለው ታጋይ ሰዎችን በመመልመል ወደ በረሃ ተልካለህ ተብሎ በመጠርጠሩ፣ ፖሊሶች ሊይዙት ሲሞክሩ፣ እጄን አልሰጥም በማለት በያዘው ሽጉጥ አንድ የመቶ እልቅና ያለው መኮንንና ሌላ አንድ ተራ ፖሊስን በመግደል፣ እንዲሁም 4 ታጣቂዎች በማቁሰል በመጨረሻም በያዘው ሽጉጥ ራሱን አጥፍቷል። ወጣቱ …

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በድቡብና ጋምቤላ የድንበር ከተማ በሆነቸው ቴፒ ራሳቸውን ያደራጁ ወጣቶች በመልካም አስተዳደርና ህዝቡን አፍኖ በመግዛት ለስቃይ ዳርገውታል ባሉዋቸው የመንግስት ታጣቂዎች እና ሹማምንት ላይ የሚያደርሱትን የሃይል ጥቃት መቆጣጠር እየተሳነው የመጣው መንግስት ካለፈው አርብ ጀምሮ፣ በተለያዩ የከተማው አካባቢዎች ጥቃቱን በማስፋት ነዋሪዎች ሲያሰቃይ ሰንብቷል። የመንግስት ታጣቂዎች፣ የነዋሪዎችን መኖሪያ ቤቶች ሰብረው …

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዛሬ ጥቅምት 15/2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 3 ሰዓት ላይ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት 3 ያህል እስረኞች ማምለጣቸውን የአይን እማኞች ገልፀዋል፡፡ እስረኞቹ በተለምዶ ሰባራ ባቡር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ፍርድ ቤት ፊት ለፊት አስፓልቱ ላይ ከመኪና ወርደው ወደ ፍርድ ቤቱ በሚገቡበት ወቅት መጥፋታቸውን የአይን እማኞች …

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአፍሪካ ቀንድ የሰብአዊ መብት ሊጉ ለኢሳት በላከው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት የጸረ ሽብር ግብረሃይል ለኬንያ መንግስት የ131 የኦሮሞ ተወላጆችን ስም በመዘርዘር በሽብረተኝነት የሚፈለጉ በመሆኑ ተላልፈው እንዲሰጡት ጠይቋል። በቅርቡ ኬንያ ውስጥ የደረሱበት ያልታወቁት የ80 አመት አዛውንቱ አቶ ደባሳ ጉዮ፣ ከ35 አመታት በላይ ከኖሩበት ኬንያ ታፍነው መወሰዳቸውን ገልጿል። ድርጅቱ …

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቤንሻንጉል ህዝብ ነጻ አውጭ ንቅናቄ፣ የጋምቤላ ህዝብ ነጻ አውጭ ንቅናቄ፣ የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ንቅናቄ፣ የኦሮሞ ነጻ አውጭ ግንባርና የሲዳማ ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር ” የህዝቦች የነጻነትና የዲሞክራሲ ጥምረት” የተባለ የጋራ ጥምረት መመስረታቸውን ለኢሳት በላኩት መግለቻ አስታውቀዋል። ጥምረቱ በመግለጫው ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን እድል በራሳቸው መወሰን የሚችሉበትን፣ በነጻ …

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ክፍል ባወጣው ዘገባ፣ አገሪቱ ለገጠማት አስከፊ ረሃብ አንዳንድ የምእራብ አገራት እርዳታ እያደረጉ ቢሆንም፣ እርዳታው አሁንም በቂ አይደለም ብሎአል። አንዳንድ መንግስታት ለልማት በሚል ለመንግስት ሊሰጡት ያሰቡትን እርዳታ፣ለተጎጂዎች ለማዋል እያሰቡ መሆኑንም መጽሄቱ ገልጿል። በሶማሊ ክልል በኤሚ ወረዳ የሸበሌ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ 700 …

ጥቅምት ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቅዳሜ ጥቅምት 13 2007 ዓም በተካሄደው በዚህ ዝግጅት ላይ ነዋሪነታቸው በኪዊንስላንድ ግዛት የሆኑ የሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የታደሙበት ሲሆን ለንደን ከሚገኘው የኢሳት ማሰራጫ ጣቢያ ጋዜጠኛ መታሰቢያ ቀጸላ ተገኝታ ከነዋሪዎቹ ጋር ውይይት ተካሂዷል። ዝግጅቱን በቡራኬ የከፈቱት በብሪዝበን የደብረ ጸሃይ ቅዱስ ጊዎርጊስ ቤ/ክ አስተዳዳሪ ቀሲስ መንግስቱ ሃይሉ ሲሆን እሳቸውም …

የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ከሕግ ውጪ፣ በቃል በሚሰጥ ትዕዛዝ ብቻ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ወጭ በማድረግ ግዥ እየፈጸመ መሆኑ ታወቀ፡፡

የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ጥቆማ ደርሶት ምርመራ በመጀመር መረጃዎችን እያጠናቀረ መሆኑ ታውቋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የግዥ መመርያ ከ500 ሺሕ ብር በላይ ወጪ የሚደረግ ከሆነ፣ በውስን ጨረታ ግዥ መፈጸም ይከለክላል፡፡ ነገር ግን የአገር ውስጥ አምራቾችን ለማበረታታት ሲባል፣ የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ውስን ጨረታዎችን እያወጣ በቢሊዮን በሚቆጠር ገንዘብ ግዥ ሲፈጽም መቆየቱ ታውቋል፡፡

ይህ ሕግን ያልተከተለ ግዥ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ትኩረት የሳበ በመሆኑ፣ ኮሚሽኑ የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ የፈጸማቸውን የተለያዩ ግዥዎች ለመመርመር መረጃ ጠይቆ ወስዷል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ለሚመራው ኮማንድ ፖስት ተጠሪ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በከንቲባ ድሪባ ኩማ የሚመራው የቤቶች ግንባታ ሥራ አመራር ቦርድ፣ የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱን ሥራ በቅርብ እየተከታተለ መመርያ ይሰጣል፡፡

ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተካሄደ አንድ ስብሰባ ላይ የአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይድነቃቸው ዋለልኝ፣ በቃል በሚሰጥ ትዕዛዝ ብቻ ግዥ እየፈጸሙ መሆናቸውን በግልጽ ተናግረዋል፡፡

አቶ ይድነቃቸው እንዳሉት፣ የበላይ አመራሮች በቃል በሚሰጡት ትዕዛዝ ብቻ ከሕግ ውጪ ግዥ እየተፈጸመ ነው፡፡ በተጨማሪም የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት እየተመራ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚመራው ኮማንድ ፖስት፣ በምክትል ከንቲባውና ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ መሆኑን ገልጸው፣ በአብዛኛው በጽሑፍ ሳይሆን በቃል ትዕዛዝ መመርያ እንደሚሰጣቸው ጠቁመዋል፡፡ ‹‹የሕግ ማዕቀፍ እንዲስተካከል ወይም ሰርኩላር እንዲሰጠን በተደጋጋሚ ጠይቀናል፣ እስካሁን ምላሽ አላገኘንም፤›› ያሉት አቶ ይድነቃቸው፣ ‹‹የፀረ ሙስና ኮሚሽን ግዥ ስንፈጽም የቆየንባቸውን መረጃዎች ወስዷል፤›› ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 6.3 ቢሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ለግንባታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ግዥ ፈጽሟል፡፡ ‹‹ያለምንም የጽሑፍ ትዕዛዝ አመራሮቻችንን አምነን በ1.6 ቢሊዮን ብር የአርማታ ብረት ግዥ አከናውነናል፤›› በማለት ጉዳዩ እንዳሳሰባቸው አቶ ይድነቃቸው ሳይሸሽጉ ተናግረዋል፡፡ ‹‹እኛ ይህንን ገንዘብ እያንቀሳቀስን የአዲስ አበባ የግዥ መመርያ ውስን ጨረታ ከ500 ሺሕ ብር በታች ነው ይላል፤›› በማለት የሕግ ማዕቀፉ ሊሻሻል እንደሚገባም አቶ ይድነቃቸው አሳስበዋል፡፡ 

ነገር ግን የቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ግዥዎቹን ለመፈጸሙ በጽሑፍ ሰርኩላር እንዲወርድለት ቢጠይቅም፣ እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል የፀረ ሙስና ኮሚሽን የተለያዩ ሰነዶችን በመውሰድ በግዥ አፈጻጸሙ ላይ ምርመራ ማካሄዱን ቀጥሏል፡፡

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ

–    ተከሳሾቹ እሳቸው የማይቀርቡ ከሆነ ብይን ይሰጠን አሉ

 በተደጋጋሚ ለሦስት ጊዜያት በተጠሩበት የመከላከያ ምስክርነት ያልቀረቡበትን ምክንያት ለጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓም. እንዲያቀርብ የታዘዘው የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት በላከው ደብዳቤ አስታወቀ፡፡

በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ የተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ፣ አቶ ደህናሁን ቤዛ፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁንና አቶ አንሙት የኔዋስ፣ አቶ አንዳርጋቸውን በመከላከያ ምስክርነት እንደሚፈልጓቸው ለፍርድ ቤት አመልክተው ነበር፡፡ ከየመን በኢትዮጵያ የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው መምጣታቸውን በመጠቆም፣ ዋናው ክሳቸው በኤርትራ ከእሳቸው ጋር በመገናኘት መመርያና ትዕዛዝ ስለመቀበላቸው መሆኑን አስታውሰው እንዲያስረዱላቸው መጠየቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ሆኖም ግን ዓቃቤ ሕግ አቶ አንዳርጋቸው የዕድሜ ልክ እስራትና ሞት የተፈረደባቸው በመሆኑ፣ ቀርበው ሊመሰክሩ አይገባም በማለት ተቃውሞ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱም የዓቃቤ ሕግን ተቃውሞ ውድቅ በማድረግ ጥያቄውን ተቀብሎ ለማረሚያ ቤቱ ትዕዛዝ አስተላልፎ ነበር፡፡

ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. አቶ አንዳርጋቸው ይቀርባሉ ተብሎ የነበረ ቢሆንም፣ ማረሚያ ቤቱ በላከው ደብዳቤ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት አለመኖራቸውን በመግለጹ ተከሳሾቹ ብሶታቸውን ገልጸዋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ቀደም ያሉት ትዕዛዞች በትክክለኛ አድራሻ እንዳልተጻፉለት በመግለጽ ሲያመላልሳቸው ከርሞ፣ መጨረሻ ላይ እንደሌሉ መግለጹ ተገቢ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ ክሳቸውን መከላከል ከጀመሩ ከአንድ ዓመት በላይ ማስቆጠራቸውንና በማረሚያ ቤት በደል እየደረሰባቸው ከመሆኑ አንፃር የአስተዳደሩ መልስ የማይታመን መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የዕድሜ ልክና የሞት ፍርደኛ ከማረሚያ ቤት ውጪ ሊታሰር እንደማይችል የገለጹት ተከሳሾቹ፣ አቶ አንዳርጋቸው ከየመን ተይዘው እንደመጡ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይልና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቴሌቪዥን መናገራቸውን በመጥቀስ በወቅቱ ለሁለቱም አካላት ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ለፍርድ ቤቱ ማመልከታቸውን አስታውሰዋል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው በመከላከያ ምስክርነት እንዳይሰሙ ማረሚያ ቤት ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም የእሳቸው ምስክርነት ቀርቶ ብይን እንዲጣቸው ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

ተከሳሽ ምንዳዬ ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ግን፣ ‹‹ከአቶ አንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተህ መመርያ ተቀብለሀል ስለተባልኩ ቀርበው መመስከር አለባቸው፤›› በማለት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን አቤቱታ ካዳመጠ በኋላ አቶ አንዳርጋቸው ይገኙበታል ለተባለው ተቋም ትዕዛዝ ለመስጠት፣ ለጥቅምት 23 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

–    በክሱ ባልና ሚስት ተካተዋል

የሙስና ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠሩት የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ከፍተኛ ኃላፊዎችን ጨምሮ 15 ሠራተኞች ላይ፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. ክስ መሠረተባቸው፡፡

በፌዴራል በከፍተኛ ፍርድ ቤት 18ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሠረተባቸው ተጠርጣሪዎች፣ አቶ ማስረሻ ምትኩ ፈንቴ የድርጅቱ የሰው ኃይል ልማትና ማኔጅመንት ዳይሬክተር፣ አቶ አስቻለው አወቀ የስትራቴጂክ ፕላኒንግና ፋይናንስ ዳይሬክተር፣ አቶ ፍቅረ ማርያም አያሌው የሰው ኃይል አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ፣ አቶ ጌታቸው ደበበ የፋይናንስ ኦፊሰር፣ የአቶ ጌታቸው ባለቤት ወ/ሮ ስሜነሽ ጌታቸው አበጋዝ (የግል ሠራተኛ)፣ መቅደላዊት ባንቱ የወ/ሮ ስሜነሽ ወንድም ሚስት፣ ወ/ሮ ገነት አረጋ የአቶ ጌታቸው እናት፣ አቶ ሚካኤል አበበ የድርጅቱ የፋይናንስ አገልግሎት የክፍያና የሒሳብ ማጠቃለያ ማስተባበሪያ ኃላፊ፣ አቶ ንጉሤ ካህሳይ የፋይናንስ ኦፊሰር፣ እፀገነት ብርሃኑ ከፍተኛ የሒሳብ ሠራተኛ፣ ሔለን ብርሃነ የከፍተኛ ጥቅማ ጥቅምና መረጃ ኦፊሰር፣ አቶ መላኩ ወርቅነህ የፋይናንስ አገልግሎት ኃላፊ፣ እሌኒ ኤልያስ የፋሲሊቲዎች ዳይሬክቶሬት ኦፊስ ኢንጂነር የነበረች፣ አቶ ዘነበ ወሰኔ የራንዌይ ቴክኒሻን የነበረና አቶ መልካሙ አበበ በቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት አስተዳደር ጀማሪ የፋይናንስ ኦፊሰር ናቸው፡፡

ባልና ሚስት የሆኑት አቶ ጌታቸውና ወ/ሮ ስሜነሽ በመመሳጠር ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ያለውን የሠራተኞች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ክፍያዎች አገልግሎት ውልን በመጠቀም፣ ሠራተኞች ባልሆኑ 189 ሰዎች ስም በድምሩ 3,335,950 ብር ወደ ግል አካውንታቸው ማስገባታቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡

ተከሳሾቹ የሐምሌና የነሐሴ ወር ደመወዝ ፔሮል በመሥራትና በተለያዩ ደረጃዎች ያሉ ኃላፊዎችን በማስፀደቅ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኤርፖርቶች ቅርንጫፍ ከድርጅቱ ገንዘብ ላይ ተቀናሽ በማድረግ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጀሞ ቅርንጫፍ በወ/ሮ ስሜነሽ ስም በተከፈተ አካውንት ውስጥ ማስገባታቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ በግለሰቧ ስም ብቻ የተከፈተውን አካውንት (Joint and/or Account) በጥምረት በማድረግ ወደ አቢሲኒያ ባንክ ጀሞ ቅርንጫፍ ማዛወራቸውንም ክሱ ይተነትናል፡፡

አቶ ጌታቸው በድርጅቱ የሚከፈላቸው የተጣራ ደመወዝ 1,173 ብር የነበረ ቢሆንም ደመወዛቸውን ወደ 9,816 ብር ከፍ በማድረግ፣ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ያላግባብ በመጠቀም በመንግሥትና በድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ ያስረዳል፡፡

እሌኒ ኤልያስ የተባለች ተከሳሽ ድርጅቱን ከየካቲት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በራሷ ፈቃድ የለቀቀች መሆኗ እየታወቀ፣ አቶ ጌታቸው ከየካቲት እስከ ነሐሴ 2007 ዓ.ም. ድረስ በፔሮል ውስጥ በማካተት በወር 3,420 ብር በድምሩ 23,943 ብር እንዲከፈላት ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ አቶ ዘነበ ወሰኔ የተባለው ተከሳሽም ከአቶ ጌታቸው ጋር በመመሳጠር፣ ከታኅሳስ 1 እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ በወር 1,562 ብር በድምሩ 14,058 ብር እንዲከፈለው መደረጉም በክሱ ተጠቅሷል፡፡ አቶ ጌታቸው ለአቶ መልካሙ አበበ 13,178 ብር በባንክ ሒሳባቸው እንዲገባላቸው ማድረጋቸውንም ክሱ ያብራራል፡፡

አቶ ጌታቸውና ወ/ሮ ስሜነሽ ከድርጅቱ በተጭበረበረ መንገድ ወስደዋል የተባለውን ገንዘብ፣ በዘመዶቻቸውና በራሳቸው የተለያየ መጠን በማድረግ በባንክ በማስገባት፣ በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስለው ማቅረባቸውን፣ እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29(2ሀናመ) ሥር የተደነገገውን መተላለፋቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡

አቶ ፍቅረ ማርያም፣ ማስረሻ፣ ሚካኤልና ንጉሤ የተባሉት ተከሳሾች ደግሞ በደመወዝ መክፈያ ፔሮልና መሸኛ ደብዳቤው ላይ የተገለጸው ደመወዝ ቀድሞ ከነበረው ጋር ሲነፃፀር ልዩነቱ ፍፁም የተጋነነ ሆኖ እያለ፣ የሰነዱን ትክክለኛነት ሳያረጋግጡና ሳይፈትሹ በፊርማቸው በማፅደቃቸው በድርጅቱና በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን ክሱ ይዘረዝራል፡፡ እፀገነት ብርሃኑ፣ ሔለን ብርሃነ፣ አስቻለው አወቀና መላኩ ወርቅነህ የተባሉት ተከሳሾች ደግሞ፣ እሌኒ ኤልያስ የተባለችው ተከሳሽ ከድርጀቱ ከየካቲት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በራሷ ፈቃድ ሥራዋን መልቀቋን የካቲት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ለሰው ሀብት ልማትና ማኔጅመንት በደብዳቤ ካሳወቀች በኋላ፣ ያልሠራችበት ጊዜ ደመወዝ ተመላሽ እንዲሆን ማድረግ ሲገባቸው ሳያደርጉ በመቅረታቸው፣ ግለሰቧ 23,943 ብር ያላግባብ እንዲከፈላት በማድረጋቸውና ግዴታቸውን በአግባቡ አለመወጣታቸውን ገልጿል፡፡

በአጠቃላይ ተጠርጣሪ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን ያላግባብ ሥልጣን መጠቀም፣ የመንግሥትን ወይም የሕዝባዊ ድርጅት ሥራን በማያመች አኳኋን መምራት፣ በሙስና ወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ  የሚሉ አምስት የሙስና የወንጀል ክሶች ቀርበውባቸዋል፡፡

ክሱን የሚመረምረው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 18ኛ ወንጀል ችሎት ክሱን ካሰማ በኋላ፣ ተከሳሾቹ ዋስትና እንዲከበርላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የአቶ ጌታቸው፣ ወ/ሮ ስሜነሽ፣ ወ/ሮ መቅደላዊትና ወ/ሮ ገነት አረጋን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፣ ሌሎቹ ተከሳሾች ከ8,000 ብር እስከ 15,000 ብር በሚደርስ ዋስ እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ በክሱ ላይ መቃወሚያ ካላቸው እንዲያቀርቡ ለኅዳር 28 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጥሯል፡፡   

ወደ ደቡብ አፍሪቃ ለመዝለቅ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ማላዊ የገቡ ናቸው የተባሉ ኢትዮጵያውያን፣ በተለያዩ የማላዊ እስር ቤቶች ይገኛሉ። ይሁንና የቅጣት ጊዜያቸውን ጨርሰው ነገር ግን ከእስር ያልተፈቱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በርካታ ነው።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

በኢትዮጵያ በእሥር ላይ የሚገኘውን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጤንነት በተመለከተ ባለፈው ሳምንት መዘገባችን ይታወሳል። ዛሬ ባገኘነው መረጃ መሠረት፥ ጋዜጠኛው ያለበት ሁኔታ የእኛን ያሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ ጨምሮ በሌሎችም መገናኛ ብዙሃን ከተገለጸ በኋላ፥ ተመስገን በቤተሰብ እንዳይጎበኝና ስንቅ እንዳይገባለት ተከልክሏል።

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ (ከቤቱ)

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ ከእናቱ ወ/ሮ ዘነበች ይመኑ ጋር፡፡


እቤቴ ከገባሁ ጀምሮ ወዳጅ ዘመዶቻችን ሁሉ ‹‹እንኳን ለቤትህ አበቃህ›› እያሉኝ ነው፡፡ የ‹እንኳን ለቤትህ አበቃህ› መልዕክቶቹ ግን ብዙውን ጊዜ በተጨማሪ ምክሮች ይታጀባሉ፡፡ በነገራችን ላይ፣ በተለይ እንደኔ በዕድሜ የገፉ ወላጆች ላሉት ሰው መታሰር የሚከፋው የእነርሱ እንግልት ባሰበ ጊዜ ነው፡፡ እኔ ትልቅ ፈተና ገጥሞኛል ካልኩ፣ የእነርሱ፣ በተለይም በየሳምንቱ ‹‹አልቀርም›› እያለች የምትመላለሰው እናቴ ነገር ነው፡፡ እናም ‹እንኳን ተፈታህ› ባዮች ሁሉ የማይዘነጓት የእስር ቤት ሕመሜን፣ እናቴን ነው፡፡ ‹‹እባክህን፣ ለእናትህ ስትል እንዲህ ዓይነቱ ነገር ይቅርብህ›› ይሉኛል፡፡ 

እናቴ፣ የተወለደችው እና እስከ ዐሥራምናምን ዕድሜዋ ድረስ የኖረችው ሰሜን ሸዋ (መንዝ አካባቢ) ነው፡፡ በአካባቢው ባሕል መሠረት (አሁንም ድረስ) ሴቶችን ያለዕድሜያቸው በቤተሰብ ፈቃድ መዳር የተለመደ ነገር ነው፡፡ እናቴም ከዚህ ዓይነቱ ወግ ማምለጥ የምትችልበት ዕድል አልነበራትም፡፡ ወላጆቿ ገና በጨቅላነቷ ዳሯት፡፡ እናቴ፣ ዕኩያዋ ያልሆነውን ባሏን አልወደደችውም ነበር፡፡ በአካባቢው ባሕልና ወግ መሠረት አለመውደድ ደግሞ አይፈቀድላትም ነበር፡፡ ስለዚህ የወላጆቿን ፈቃድ ሽራ የራሷን ዕጣ ፈንታ በራሷ ለመወሰን ወሰነች፡፡ ይህ ውሳኔዋ ወላጆቿን የሚያስከፋ ብቻ ሳይሆን፣ ጭራሹኑ ተቀባይነት የማያገኝ ውሳኔ እንደሆነ አልጠፋትም፡፡ ስለዚህ በጣም አስፈሪ ዕቅድ አውጥታ ተገበረችው፡፡ የልጅነት ስሟ ገበያነሽ ነበር፡፡ በመጀመሪያ ያደረገችው ስሟን ወደ ዘነበች መቀየር ነው (በነገራችን ላይ በእኔና በአባቴ ስም መሐል የምጽፋትን ‹ዘ› የወሰድኩት ከሷ ስም ነው)፡፡

ከዚያም አገሯን ጥላ ኮበለለች፡፡ የኮበለለችው ደግሞ ምንም፣ ማንንም ወደማታውቅባት፣ ማንም ወደማያውቃት አዲስ አበባ ነው፡፡ ዝርዝሩ የማያልቅ ፈተና ያለበት ውጣ ውረድ ነው፡፡ የሆነ፣ ሆኖ ነፍሷን አትርፋ ራሷን አዲስ አበባ ላይ ማደላደል ቻለች፡፡ በዚሁ አጋጣሚ ነበር ከአባቴ ጋር የተገናኙት፣ የተዋደዱት፣ የተጋቡት እና ልጆች ያፈሩት፡፡ ወላጆቿ በወቅቱ አዝነውባት ይሆናል፤ ነገር ግን ተጨንቀው እሷን ፍለጋ ብዙ ሲንከራተቱ እና ሲንገላቱ እንደነበርም በታሪክ ስትናገር አውቃለሁ፡፡ ሲያገኟትም ከአባቴ ትዳር ይዛ የመጀመሪያ ልጇን ወልዳ ነበር፡፡ ከመደሰት ውጪ አማራጭ አልነበራቸውም፡፡ ለእናቴም የእራሷን ሕይወት ለመምራት፣ እነርሱን ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የሚያስከፋ እና የሚያስጨንቅ ውሳኔ መወሰን ነበረባት፤ መጨረሻውም አስደሳች ሆኗል፡፡ መጨረሻው ምንም ሆነ ምን እናቴ የማትፈልገውን ሕይወት ‹‹እምቢ አልኖረውም›› ብላ መጀመሯ ተገቢ ነበር፡፡

እኔም የወላጆቼ ልጅ ነኝ፤ ታሪካቸውን በተለያየ ቀለም በተደጋጋሚ እየሰማሁ ነው ያደግኩት፡፡ የተሠራሁትም ከነርሱ ታሪክ እና ከሌሎችም ብዙ የሕይወት ልምዶች ነው፡፡ የናቴን እምቢተኝነት፣ የማይፈልጉትን ላለመሆን አደጋ መጋፈጥ፣ ይመጥነኛል የሚሉትን ሕይወት እስከሚገኝበት አጥናፍ ድረስ መፈለግ ተፈልፍዬ የተቀረፅኩበት ‹ሳይኮአናሊቲካዊ› ሥረ-መሠረቴ ነው፡፡ እናቴ፣ ወላጆቿን ታከብራለች፣ ትወዳለች፤ ሕይወቷን ግን ስለነርሱ አልኖረችም፡፡ እኔም በሕይወቴ የምወስዳቸውን እርምጃዎች የምረዳቸው በዚሁ ቋንቋ ነው፡፡ እናቴን እወዳታለሁ፤ ነገር ግን ‹የሱን ሕይወት ትቶ የኔን ድርሻ ይኑርልኝ› ትለኛለች ብዬ አልገምትም፡፡ ማረሚያ ቤት እያመላለስኩ ባስቸገርኳት ግዜም ይሁን ሰዎች በወቀሱኝ ጊዜ ለራሴ የምሰጠው ምክንያት ይኸው ነው፡፡ እኔ የናቴ ልጅ ነኝ፤ እራሴን የምሆነውም ከርሷ በወረስኩት ባሕሪዬ ነው፡፡

(ይህንን ጽሑፍ የጻፍኩት እናቴን አስፈቅጄ ነው፡፡)

ድርቁ ከ4.6 ሚ. በላይ ህጻናትን የረሃብ ተጠቂ ሊያደርግ ይችላል ተባለ

ተመድና ኦክስፋም የተረጂዎች ቁጥር 15 ሚ. ይደርሳል ሲሉ፣ መንግስት 8.5 ሚ. ብቻ ናቸው ብሏል
ፖለቲከኞችና ባለሙያዎች ፖለቲካዊ ጥቅምን ትተን ችግሩን ለመፍታት እንረባረብ አሉ

በኤልኒኖ ሳቢያ በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ፣ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ከ4 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ህጻናትን የርሃብ ተጠቂ ሊያደርግ ይችላል ሲል ሴቭ ዘ ችልድረን የተባለው አለማቀፍ ተቋም አስጠነቀቀ፡፡350 ሺህ ያህል የአገሪቱ ህጻናት የከፋ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ችግር ተጠቂ ሆነዋል ያለው ተቋሙ፣ ችግሩ ተገቢው መፍትሄ ካልተሰጠው  በህጻናቱ ዕድገት ላይ የመቀጨጭ፣ የአካላዊና አእምሮአዊ ዝግመት ሊያስከትል ብሎም ለህልፈተ ህይወት ሊዳርግ ይችላል ብሏል፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ኦክስፋም ሰሞኑን ባወጡት ሪፖርት፣ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር እስከ 15 ሚሊዮን ሊደርስ እንደሚችል የገለፁ ሲሆን፣ መንግስት በበኩሉ፤ የተረጂዎቹ ቁጥር 8.5 ሚሊዮን ብቻ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ታዋቂ የአገሪቱ ፖለቲከኞችና የኢኮኖሚ ባለሙያዎች በበኩላቸው፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወት አደጋ ላይ በሚገኝበት በዚህ አሳሳቢ ወቅት፣ ለፖለቲካዊ ጥቅም መሯሯጡን ትተን ድርቁ ያስከተለውን የርሃብና የምግብ እጥረት ችግር ለመፍታት በጋራ መረባረብ አለብን ብለዋል፡፡

“ዴርቶጋዳ” በተሰኘው የመጀመሪያ ረዥም ልብወለዱ ዕውቅና ያተረፈው ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ፤ በአይናለም የመጽሐፍት መደብር ባለቤት፣ በአቶ አይናለም መዋ የ330 ሺህ ብር  ክስ እንደቀረበበት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ከክስ መዝገቡ ላይ ለመረዳት እንደተቻለው፤ ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ “ዴርቶጋዳ” እና “ዣንቶዣራ” የተሰኙ መጽሐፎቹን በራሱ ማተሚያ ቤት አሳትሞ ለአይናለም መዋ ለመስጠት ከተዋዋለ በኋላ፣ ውሉን አፍርሶ ከሌላ ሰው ጋር ተዋውሏል፡፡ አይናለም የመፅሀፎቹን ዋጋ አስቀድሞ መክፈሉም በክሱ ተጠቅሷል፡፡ ደራሲው መጽሐፎቹን አትሞ ለመስጠት የተዋዋለው እስከ ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ የነበረ ቢሆንም “ዴርቶጋዳ” የተሰኘውን መጽሐፍ 5ሺህ ኮፒ አሳትሞ ለመስጠት ተዋውሎ 2ሺህ ኮፒ ብቻ ለውል ሰጪው በማድረስ ቀሪውን 3ሺህ ኮፒ ለሌላ ሰው ከውል ውጪ ማስተላለፉ በክሱ ላይ ተገልጿል፡፡ ክሱ የቀረበለት ፍ/ቤትም፤ ተከሣሽ ቀርቦ ምላሽ እንዲሰጥ ለፊታችን ሰኞ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ደራሲና አሣታሚ ይስማዕከ ወርቁ በበኩሉ፤ ስለክሱ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ለአዲስ አድማስ በስልክ በሰጠው ምላሽ ገልጿል፡፡ አስራ አንደኛ መፅሀፉን ለማውጣት በማስተዋወቅ ላይ የሚገኘው ዝነኛው ደራሲ ይስማዕከ፤ “ዴርቶጋዳ” የተሰኘ የመጀመሪያ ልብወለዱ ከ200ሺ በላይ ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይታወቃል፡፡ የሙሉ ጊዜ ደራሲ የሆነው ይስማዕከ፤ በአዋሳ የህክምና ትምህርቱን አጠናቋል፡፡  

በቤተ ክርስቲያን ስም በሚዲያዎች ስለሚተላለፉ ‘ትምህርቶች’ ይወስናል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉዳይ ከመነጋገርያ አጀንዳዎቹ ተካቷል እነየማነ ዘመንፈስ ቅዱስ፣ በአዳራሹ መግቢያና በአባቶች ቤት ደጅ እየጠኑ ነው በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ድንጋጌ መሠረት፣ ትላንት ጥቅምት 12 ቀን በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የመክፈቻ ንግግር የተጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ፤ ዘመኑን የዋጁ እና ወቅቱን የተመለከቱ የመነጋገርያ …

ከኣዲስ ኣበባ ተነስቶ በአየርላንድ በኩል ወደ አሜሪካ በመብረር ላይ የነበረ የኢትዮጵያ ኣየር መንገድ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላን በሞተሩ ላይ በተፈጠረ እክል ምክንያት ተመልሶ ወደ ደብሊን ለማረፍ መገደዱ ተገለጸ።

መሠረታዊ ችግር ሊኾን የሚችለው ክፍተት ለምን ተፈጠረ የሚለው ሳይኾን ክፍተት መኖሩ እየታወቀ ዝም ብሎ መኖሩ ነው ሕዝበ ክርስቲያኑ ቤተ ክርስቲያኑን ለመደገፍና ለማልማት የሚያደርገው ቀና ትብብር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ተሰፋ ሰጪ ኾኖ ይታያል ሐዋርያዊ ተልእኮን ለማስፋፋት በተደረገው እንቅስቃሴ ከምዕራብ አሜሪካ እስከ ጃፓን፤ ከአየርላንድ እስከ አውስትራልያ ቤተ ክርስቲያናችን ክንፎቿዋን የዘረጋችበት ኹኔታ በመፈጠሩ ዓለም አቀፋዊት ወደ መኾን አድጋለች …

ጥቅምት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ ጌትነት ደርሶ ” ‹‹ሽብር ተፈፅሞብኛል እንጅ አሸባሪ አይደለሁም››፣ ‹‹ፍትህ ቢኖር ኖሮ እኔ ሳልሆን ወያኔና ግብረ አበሮቹ ነበሩ እዚህ መቆም የነበረባቸው›› ሲል፣ አቶ ዘመነ ምህረት ደግሞ ” ‹‹የተከሰስኩት ድርቡሽ እንኳ ያልደፈረውን የጎንደር ጥምቀት ላይ ፈንጅ ልታፈነዳ ነበር ተብዬ ነው፡፡ ምርመራ ላይ ግን ለምን የመኢአድ አባል …

ጥቅምት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሳውድ አረቢያ በጸሎት ስነስርአት ላይ በነበሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ከፍተኛ አደጋ ተከትሎ መንግስት የሃዘን መግለጫ ባለመውጣቱና ሰንደቅ አላማም ዝቅ ብሎ ባለመውለብለቡ የሃይማኖቱ አባቶች ቅሬታቸውን እየገለጹ ባለበት ወቅት፣ የእስልምና ምክር ቤቱ ሟቾቹን ለመዘከር የጸሎት ስነስርዓት አድርጓል። በአብዛኛው ሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው መጅሊሱ፣ ያካሄደውን የጸሎት …

ጥቅምት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሰው በእስር ላይ የሚገኙት ፓስተር ኦሞት አግዋ ፡ አሽኔ አስቲንና ጀማል ኡመር ትናንት ፍርድ ቤት ቀርበው በድጋሜ ለጥቅምት 25 ተቀጥረዋል። ቀጠሮ የተሰጠው ሁለተኛው ተከሳሽ አቶ አሽኔ አስቲን የምክር ቤት አባል በመሆናቸው፣ ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ በመታሰራቸው ፣ ጉዳዩን ለማየት ነው። እነፓስተር ኦሞት የታሰሩት የውጭ …

ጥቅምት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሶስት መቶ መንገደኞችን ጭኖ ከአዲስ አበባ ተነስቶ በደብሊን አድርጎ ወደ አሜሪካ ሲጓዝ የነበረው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነው ድሪምላይን 787-8 አውሮፕላን ዛሬ ማለዳ ላይ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር በድንገት አንድ ሞተሩ አየር ላይ ቢጠፋም በአየርላንድ ዋና ከተማ ደብሊን በሰላም ማረፍ ችሏል። መንገደኞቹ ከጀርመን ፍራንክፈርት በተላከ ተቀያሪ …

ጥቅምት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በደቡባዊ ግብጽ ሉዞር ላይ በባቡር አድርገው በህገወጥ መንገድ የግብጽን ድንበር ተሻግረው የገቡ አስራ አንድ ሶማሊያዊያን እና አስር ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን መያዛቸውን የአገሪቱ የጸጥታ ሃይሎች ምንጭ ጠቅሶ ዮም ሰበን ዘግቧል። በህገወጥ መንገድ በግብጽ አድርገው ወደ ሊቢያ የሚገቡ ስደተኞች በቅርብ ጊዜያት ውስጥ እየበዙ መሆናቸውንና ከ2 ሺ 215 በላይ …

ሃምሣ ሺህ የሚሆኑ ሰዎችን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ለማስገባት የሚያስችል የዲቪ (Diversity Visa) ዕጣ መርሃ ግብር በአውሮፓ የዘመን አቆጣጠር ለ2017 ዓ.ም መዘጋጀቱን አዲስ አበባ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ገለፀ።

ካለፈው አመት የፈረንጆቹ ሰኔ ወር መባቻ ላይ ወደ ኤርትራ ሲጓዙ የመን(ሰነኣ ) አለም አቀፍ አወሮፕላን ጣቢያ ላይ ታፈነው ለ አዲስ አበባ መንግስት ተላለፈው የተሰጡት እና ቀደም ሲልም በሌሉበት ኢትዮጵያ ውስጥ በ 2009 አኤአ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው የግንቦት 7ቱ ዋና ጸሃፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እጣ ፈንታ ያሳሰበው አንድ ታዋቂ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የእንግሊዝ መንግስት “ለጥቅሙ […]

ሲኖዶስ ማለት፡- ሲኖዶስ፣ ቃሉም ሥራውም የምሥራቃውያን ነው ቃሉ ግሪክኛ ኾኖ የአንድነት ስብሰባ ማለት ነው የእኛ ቤተ ክርስቲያን ከምሥራቃውያን አንዷ ነች ቤተ ክርስቲያናችን ሐዋርያዊትና ሲኖዶሳዊት ነች የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ፡- የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ እንደ ማንኛውም ጉባኤ አይደለም፤ የቤተ ክርስቲያን የበላይ መሪዎች ስብሰባ ነው፤ በመንፈስ ቅዱስ ስለሚመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ተብሎ ነው የሚጠራው፤ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል እንደተባለው፤ …