ማክሰኞ ህዳር 23/07 ዓ.ም ወደዚያች ንዳድ ወደሆነችው ዝዋይ ከተማ ስንደርስ ከረፋዱ 3፡00 ነበር፡፡ ያንን መከረኛ መንገድ እንደዋዛ አልፈን ወደ ግዞት ቤቱ ስንገባ በመመላለስ የተግባባናቸው ጠባቂዎች በፈገግታ ተቀበሉን፡፡ ሙሉ አድራሻችንን አስመዝግበን ያመጣነውን ስንቅ በማስፈተሽ ጠያቂና እስረኛ የሚገናኝበት ቦታ ላይ ስፍራችንን ያዝን፡፡ የዛሬው ቀን ግን ከሌላው ሳይለይ አይቀርም፡፡ ከተቀመጥን ደቂቃዎች ቢያልፉም ስለታሰረ ብቻም ሳይሆን አብረውት ቢያወሩ የሚናፍቁት ተመስገን አልመጣም፡፡ ከእንቅልፍ አልነቃ ይሆን? እንደምንመጣ ስለሚያውቅ ግን ይሄ ሊሆን አይችልም፡፡ ተመስገንን እንዲጠራልን የላክነው እስረኛ መልዕክቱን እንዳስተላለፈ ነግሮን አለፈ፡፡ ይህ ልጅ ታማኝ ከሚባሉት እስረኞች መካከል የሚጠቀስ ነው፡፡ እነዚህ ታማኝ እስረኞች ከመታመናቸው የተነሳ ከጊቢውም ወደ እየወጡ እንደሚመለሱ የከተማው ነዋሪ የሹክሹክታ ወሬ ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ መቼም ከተማ የሚወጡት ከዝዋይ ሀይቅ አሳ ሊያጠምዱ እንዳልሆን ግልፅ ነው፡፡ የወታደሮቹ ሀላፊ መጥቶ ገርመም አድርጎን አለፈ፡፡ እሱን ተከትሎ ሌሎች ሁለት ወታደሮች በተመሳሳይ ሁኔታ አይተውን ተመለሱ፡፡ ነገረ ስራቸው አላማረንም፡፡ ይሄን መታገስ አልቻልንም፤ ድምፃችንን ከፍ አድርገን መናገር ጀመርን፡፡ ‹ተመስገን ሳይመጣ 40 ደቂቃ አለፈው፤ ኸረ የተመስገን ያለህ› ብንልም ሰሚ ግን አልነበረም፡፡ በቦታው ከተገኘን ከ55 ደቂቃ በኋላ ታማኙ እስረኛ ተመስገን ሲጠቀምባቸውን የነበረውን እቃዎች ወረቀት ከያዙ ወታደሮች ጋር ይዞ ሲመጣ የማደርገውን ነገር እስካጣ ድረስ ድንጋጤ ወረረኝ፡፡ እንዳልናገር ምላሴ ተያያዘ፤ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ለማ፡፡ ከፊታችን ሊደርሱ ጥቂት የቀራቸውን ወታደሮች ‹‹ተመስገንስ? ተሜስ›› አልኳቸው፡፡ እነሱ ግድም አልሰጣቸው፡፡ የመጣሁትን ስንቅ ዕየደባበሱ ‹‹ተመስገን ትላንት አዲስ አበባ ሄዷል››፤ ‹‹የምን አዲስ አበባ ነው? መቼም ወደቤት አይሄድም?››፡፡ ወደ ቃሊቲ በለሊት መሄዱን አረዱን፡፡ አሁን ተናድድኩ፡፡ ‹‹ትላንት ከሰዓት ጠይቀነዋል፤ አንደሚሄድ እሱም አያወቅም ነበር፤ ለኛም አልንገራችሁን ሌላው ቢቀር ደውላችሁ ብትነግሩን ምን ነበረበት?›› መልስ ሳይሰጡን የራሳቸውን ወሬ ማውራት ጀመሩ፡፡ ያመጣሁት ምግብና ቡና እናታችን ዕረፍት አጥታ የሰራቸው ነው፡፡ ድካሟን ሳስበው አዘንኩላት፡፡ ምን ማድረግ ይቻላል? ምንም፡፡

ያመጣሁትን ምግብ ለክንፈሚካኤል (አበበ ቀስቶ) እንድሰጥ እንዲጠሩልኝ ብጠይቅም አልሆነም፤ ግን እናድርስላቹሁ የሚል ሀሳብ ከወታደሮቹ መጣ፡፡ አማራጭ ስለሌለን ቡናና ምግቡን ሰጥተን ተመሰገን ሲጠቀምባቸው የነበሩትን እቃዎች ይዘን ተመለስን፡፡ ተልዕኮአችን ሳይሳካ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ፡፡

ቃሊቲ ዞን 3
እንግዲህ ተመስገን ለሚወዳት ሀገሩ ሲል ከቂሊንጦ ዝዋይ፤ ከዝዋይ ደግሞ ቃሊቲ መንከራተቱን ተያይዞታል፡፡ መከራውን የሚያብሰው ደግሞ ከቃሊቲ እስር ቤት እጅግ አስከፊ ወደሆነው ቦታ መዘዋወሩ ነው፡፡ ዞን 3 ይባላል፡፡ ዞኑ ምን እንደሚመስል ዛሬ ከሰማሁት ጥቂት ላካፍላችሁ፡፡ መግቢያው ላይ ‹በከፍተኛ ጥበቃ ስር የሚገኝ› ይላል፡፡ በዞን 3 የሚገኙት እስረኞች በጠቅላላ ማለት ይቻላል በተደጋገመ ስርቆት፣ ማጭበርበርና አስገዳጅ የሌብነት ወንጀል ሲፈፅሙ ተገኝተዋል የተባሉ እስረኞች የሚታጎሩበት ዞን ነው፡፡ ታዲያ ተመስገን ይህ ቦታ እንዲገባው የተፈረደበት ስለምንድን ነው? እኛ ሳናውቅ የዘረፈው ነገር ይኖር? ህዝብ ሳይሰማ በሌብነት ንብረት አካብቶ ይሆን? ሰብዕናው ይህ እንዳልሆነ ለመመስከር ከኔ በላይ የከሳሾቹም ልብ ያውቀዋል፡፡ የዕሰረኞቹ ማደሪያ መጋዘን በቆርቆሮ የተሰራና ጠባብ ሲሆን በውስጡ ሙሉ ቃሊቲ እንኳን የማይችላቸው 300 እስረኞች ታሽገውበታል፡፡ ዛሬ ተመስገን 301ኛ በመሆን ነባሮቹን ተቀላቅሏቸዋል፡፡ የእነዚህ እስረኞች የመኝታ ሁኔታ የአንዱ ራስ ከስር ያንዱ እግር ከላይ ሲሆን በተለምዶ አስመራ ድርድር የሚባለውን መልክ ይወክላል፡፡ በርግጥ ይህ ለተሜ ትንሹ መስዋዕትነት ነው፡፡ መንፈሱን ለማድቀቅ፣ ጥንካሬውን ለማራከስ የታሰበ ቢሆንም የታመነለትን ምክኒያት ሊሸርፉት እንደማይችሉ ግን ነብሴ ትመሰክራለች፡፡ የሐዋሪያው ጴጥሮስ ተዘቅዝቆ መሰቀል ላመነበትስ አይደል! ለእነዚህ 300 እስረኞች ያለው የሻዎር አቅርቦት 1 ብቻ መሆኑ ደግሞ ሌላው ትንግርት ነው፡፡ አንድ ሰው በሳምንትም የመታጠብ እድል ላይኖረውም ይችላል፡፡ የመጋዘኑ መታፈን ለተባዮች ምቹ መኖሪያ ሆኗቸዋል፡፡ ተሜ ከከፋ ግፍ ወደ ከፋ ሰቆቃ ቢዘዋወርም ‹‹ለሀገሬ ስል ጉዞዬ እስከ ቀራኒዮ ድረስ ነው›› ያለውን እያደረገ እንደሆነ ስመለከት በፅናቱና በብርታቱ እደነቃለሁ፡፡

(በአማን ነጸረ) ሁለት ጽንፍ የያዙ ኃይላት ያገሪቱን የፖለቲካ መድረክ ተቆጣጠረዋል–ያንድነት ኃይላት ነን ባዮችና ብሔረሰባውያን!! 2ቱም የየራሳቸው በጎ ጎን እና ለሀሳባቸው አሳማኝ ምክንያቶች እንዳላቸው እረዳለሁ፡፡ሆኖም በጎ በጎውን ላቆየውና የሚያሥከፋኝን ልናገር፡፡ያደፋፈረኝ የልሂቃኑን የብሔር መነሻ ከአመለካከታቸው ለማስተሳሰር የደፈረው የዶ/ር መረራ መጽሐፍ ነው፡፡ 1– ትናንት የተፈጸሙ በደሎችን ሽምጥጥ አድርገው ይክዳሉ ወይም ያለባብሳሉ፡፡ “እኔ አልጨቆንኩህም ሥርዓቱ ነው” ማለት አንድ ነገር ነው፡፡ነገር ግን ተጨቆንኩ ብሎ ያመነን ማኅበረሰብ–ያውም ስለጭቆናው ከአያት ቅድመ – አያቱ ብቻ ሳይሆን ከበዙ የአማርኛ ምሳሌያዊ አነጋገሮች ሊረዳ የሚችልን ፊደል የቆጠረ ትውልድ ስለ አንተ አለመጨቆን ታሪክ እጽፍልሀለሁ ማለት ግብዝነት ነው!! “ነገሥታቱ እናንተን ብቻ ሳይሆን እኛንም ጨቁነዋል” የሚለው መከራከሪያ እኔ ራሴ ብዙ ጊዜ ብጠቀምበትም በኢ/ያ የጭቆና ትረካ አቀራረቡ ትክክል አልሆንልህ ይለኛል፡፡ምክንያቱም የአንድ ብሔር የራስ በተባለ ሰው (ብሔር) መንገላታትና ከራስ ውጭ ባለ ሰው(ብሔር) መንገላታት ያለው ትርጉም ይለያያል፡፡ለምሳሌ፡- የአጼ ቴዎድሮስ የሸዋን መሳፍንት እጅ መቁረጥ እና የአጼ ምኒልክ የኤርትራውያንን ምርኮኞች እጅና እግር መቁረጥ ታሪኩን እንደሚዳኘው ሰው የብሔር ማንነት ትርጉሙ ሊለያይ እንደሚችል መረዳት አለብን፡፡የምኒልክ ንጉሥ ተ/ሃይማኖትን እምባቦ ላይ መውጋት ራሱን እንደ ምኒልክ ልጅ ለሚቆጥረው የዛሬ ዘመን የጎጃም ልሂቅ ምንም ላይመስለው ይችላል፤ለወላይታው ልሂቅ ግን የምኒልክ ጦናን መውጋት የአባት ተግባር ሳይሆን በማንነት ላይ የተቃጣ የጎረቤት ትንኮሳ ተደርጎ ነው የሚታየው፡፡የምኒልክ የደቡብ ሕዝቦችን የማስገበር ሂደት አፈጻጸሙ ታይቶ “ባልተወለደ አንጀቱ…” ቢባል አይግረመን፡፡ “እኔ ስላልተሰማኝ ለምን ይሰማችኋል??” አንበል!!በቃ!! የተሰማው የተሰማውን በተሰማው መጠን ይናገር!!ድርጊቱን እስካመንን ድረስ ቢያንስ […]

ዮሃንስ ደሳለኝ (በርሊን -ጀርመኒ)

Ethiopia Zare ሐሙስ ኅዳር 24 ቀን 2007 ዓም December 4, 2014  ከደች ባንክ ብድር ለመጠየቅ ረቡዕ ለታ ከጀርመኗ ቻንስለር መርከል ጋር ውይይት ለማድረግ ወደ ስፍራው ያቀኑት ጠ/ሚር ኃይለማርያም ደሳለኝን በመቃወም በርካታ ኢትዮጵያዊያን በቦታው በመገኘት ተቃውሟቸውን ማስማታቸው ታወቀ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም :- በነጻነት ለሀገሬ

ባለፈው ሳምንት በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን/ት ቤተሰቦች ከዘመዶቻቸው እና ከጓደኞቻቸው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ታሪክ በመጥፎ ገጽታው ሲታወስ የሚኖረውን እ.ኤ.አ ኖቬምበር 14/1974 በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመውን የእልቂት ሰለባዎች ለማስታወስ በአንድ ላይ ተሰባስበው የጸሎት ስርዓት አድርገዋል፡፡ በዚያ የጥላቻ ዕለት የወታደራዊው አምባገነን ስብስብ ተራ ስብሰባ በማድረግ 60 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኖችን፣ የመንግስት ሰራተኞችን፣ አርበኞች ከፍተኛ ማዕረግ ያላቸውን ወታደራዊ መኮንኖችን፣ የተማሩ ወታደራዊ ባለስልጣናትን እና የግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ስላሴን ልዩ የጥበቃ አባላት ያካተተ የግድያ እልቂት ለመፈጸም ተራ እና አስደንጋጭ ውሳኔን አሳለፈ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

አሰፋ ጫቦ

 

እንዲያው ዘው ተብሎ አይገባ ነገር! ” ቤቶች!” ተብሎ” ደጆች!” ተብሎ “ይግቡ/ግባ!” ተብሎ ነው እንጅ። ጠፍቼ ስነበትኩ።ከርምኩ ሳይሻል አይቀርም።”ለመሆኑ አስፋ ጫቦ የት ገባ” ብለው በአደባባይ ከጠየቁት ወሰንሰገድ ገ/ኪዳንንና እንዳለ ጌታ ከበደን ሌሎች እዚህ በስም ያልጠቀስኳቸዉን ሁሉ አመስግናለሁ።ለክፉም ለደጉም ጠያቂ አያሳጣችህ! እኔማ ሌላ ምን እላለሁ ! የቤት ክህነት አባቶች እንደሚሉት ሱባዔ ገብቼ ነበር።ከዚያው ከቤተክህነት ተውሸ፤(ነበርኩብትምና) “ዘኀሀለፈ ሥርየት ወለዘይመጽዕ እቅበት” እላለሁ። ነጠላ ትርጉሙ “ያለፈው ይሰረዝ ይደለዝ ለመጭው መታቀብን/መቆጠብን  ስጠኝ/ስጠን!” እንደማለት ነው።በምወደው መጽሐፍ Gone with Wind   ስካርሌት ኦሐራ (Scarlet O’Hara) Tomorrow is Another Day ትላለች።። “ነገም ሌላ ቀን ነዉ” ብሎታል ተርጏሚው ነብይ መኮንን።እኔም እንድያ እንዳልኩ ይቆጠርልኝ!

ሙሉውን አስነብበኝ …


 ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
የውጪ ደራሲያን የጻፏቸውን መጻሕፍት ወደ አማርኛ መተርጎሙን ማን እንደጀመረው በትክክል አላውቅም፡፡ ሆኖም የዶ/ር ሳሙኤል ጆንሰን ድርሰት የሆነው “ራሴላስ” በአማርኛ የተተረጎመ የመጀመሪያው የውጪ መጽሐፍ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡ ከዚያም ክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል የትርጉም ስራዎችን በስፋት ተያይዘውት ነበር፡፡ ለምሳሌ ከበደ ሚካኤል የሼክስፒርን ሮሚዮና ጁሌት በ1940ዎቹ ተርጉመውት ነበር፡፡ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም በርካታ የሼክስፒር ስራዎችን በ1960ዎቹ ተርጉመዋል፡፡
  
  የአማርኛ የትርጉም ስራዎች እንደ አሸን የፈሉት ግን “ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት” በ1970ዎቹ ከተቋቋመ በኋላ ነው፡፡ በዚያ ዘመን በተለይም ዘመን አይሽሬ የሚባሉ ታላላቅ የስነ-ጽሑፍ ስራዎች በብዛት ወደ አማርኛ ተመልሰዋል፡፡ ኢ-ልቦለድ ከሆኑትም መካከል የካርል ማርክስን “ዳስ ካፒታል”ን ጨምሮ በርከት ያሉ መጻሕፍት ተተርጉመዋል፡፡
በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ ደግሞ የትርጉም ስራው የዳኒኤላ ስቴልን፣ የሲድኒ ሸልደንንና የአርቪንግ ዋላስን ስራዎች ወደ አማርኛ በመመለሱ ላይ ነበር ያተኮረው፡፡ እስከ 1990ዎቹ መጀመሪያ ድረስ በብዛት ሲተረጎሙ የነበሩት ደግሞ የጃኪ ኮሊንስ ድርሰቶች ናቸው፡፡ አሁን ግን የትርጉም ስራው ቀዝቅዟል፡፡
   ለመሆኑ እስከ ዛሬ ድረስ በአማርኛ የተተረጎሙ ታላላቅ የስነ-ጽሑፍ በረከቶች የትኞቹ ናቸው? ይህንን ጥያቄ መመለስ ይከብዳል፡፡ ቢሆንም የቻልኩትን ያህል ለመዘርዘር እሞክራለሁ፡፡ ታዲያ በዚህ ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት በመላው ዓለም ዝነኛ ለመሆን የበቁ ስራዎች ብቻ ናቸው፡፡ ለምሳሌ የነ ዳንኤላ ስቴል፣ ሲድኒ ሸልደንና ጃኪ ኮሊንስ ስራዎች በሀገራችን በብዛት ቢተረጎሙም በዓለም ዙሪያ ያላቸው ተነባቢነት እምብዛም ነው፡፡
    መጻሕፍቱን የምጠራቸው በአማርኛው ርዕሳቸው ነው፡፡ የዋናውን ደራሲ ስም እና የተርጓሚውንም ስም እጠቅሳለሁ፡፡ በአንዳንድ የተርጓሚዎችን ማንነት ለማወቅ ስቸገር ግን ዝም ብዬ አልፌአቸዋለሁ፡፡
(ማስታወሻ፡ ይህ ዝርዝር የሃይማኖት መጻሕፍትን አይመለከትም)፡፡
==== ዘመን አይሽሬ የልብወለድ መጻሕፍት (Classical Fictions)===
1.      “ነገም ሌላ ቀን ነው”፣ ደራሲ ማርጋሬት ሚሼል፣ ተርጓሚ ነቢይ መኮንን
2.     “መከረኞች”፣ ደራሲ ቪክቶር ሁጎ፣ ተርጓሚ ሳህለ ሥላሤ ብርሃነማሪያም (በህይወቴ ያነበብኩት ምርጥ የአማርኛ ትርጉም ስራ ይህኛው ነው)፡፡
3.     “የሁለት ከተሞች ወግ”፣ ደራሲ ቻርለስ ዲከንስ፣ ተርጓሚ ሳህለ ሥላሤ ብርሃነማሪያም
4.     “የአገር ልጅ”፣ ደራሲ ሪቻርድ ራይት፣ ተርጓሚ ሳህለሥላሤ ብርሃነማሪያም
5.     “ዶን ኪኾቴ”፣ ደራሲ ሚጉኤል ሰርቫንቴስ፣ ተርጓሚ ዳምጤ አሰማኽኝ (ሌላ ሰው ይህንኑ መጽሐፍ “ዶን ኪሾት” በሚል ርዕስ ተርጉሞት ነበር፤ ይሁን እንጂ ያኛው ትርጉም ብዙም አይጥምም)
6.     “ሳቤላ”፣ ደራሲ ሄንሪ ውድ፣ ተርጓሚ ሀይለ ሥላሤ መሓሪ
7.     “እናት”፣ ደራሲ ማክሲም ጎርኪ
8.     “ዩኒቨርሲቲዎቼ”፣ ደራሲ ማክሲም ጎርኪ
9.     “አጎቴ ቫኒያ”፣ አንቶን ቼኾቭ
10.    “ሼርሎክ ሆምዝ”፣ ደራሲ ሰር አርተር ኮናን ዶይል፣ ተርጓሚ ዳኛቸው ተፈራ
11.     “ውቢት”፣ ደራሲ አልቤርቶ ሞራቪያ፣ ትርጉም ሺፈራው ጂሶ
12.    የካፒቴኑ ሴት ልጅ፡ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪን
13.    “ካፖርቱ”፣ ደራሲ ኒኮላይ ጎጎል
14.    እንደ ሰው በምድር እንደ አሳ በባህር፡ ደራሲ ኒኮላይ ጎጎል
15.    “ወንጀልና ቅጣት”፣ ደራሲ ፊዮዶር ዶስቶየቪስኪ፣ ተርጓሚ ካሳ ገብረህይወት እና ፋንቱ ሳህሌ
16.    “እንዲህ ሆነላችሁ”፣ ደራሲ ሩድያርድ ኪፕሊንግ፣ ተርጓሚ አረፈዐይኔ ሐጎስ
17.    “አሳረኛው”፣ ደራሲ ነጂብ ማህፉዝ፣ ተርጓሚ አማረ ማሞ
18.    ሌባውና ውሾቹ፣ ደራሲ ነጂብ ማሕፉዝ፤
19.    “እፎይታ”፣ ደራሲ አሌክሳንደር ዱማስ ፔሬ፣
20.   “ጃኩሊን”፣ ደራሲ አጋታ ክሪስቲ
21.    “የደም ጎጆ”፣ ደራሲ አጋታ ክሪስቲ፣ ተርጓሚ ሌ/ኮሎኔል ጌታቸው መኮንን ሐሰን
22.   “አና ካሬኒና”፣ ደራሲ ሊዮ ቶልስቶይ፣
23.    “ሽማግሌውና ባህሩ”፣ ደራሲ አርነስት ሄሚንግዌይ፣
24.    “እሪ በይ አገሬ”፣ ደራሲ አላን ፒተን፣ ተርጓሚ አማረ ማሞ
25.    “የስዕሉ ሚስጢር”፣ ደራሲ ኦስካር ዋይልድ፣ ተርጓሚ ፋሲል ተካልኝ አደሬ
26.   “ጠልፎ በኪሴ”፣ ደራሲ ተውፊቅ አልሃኪም፣ ተርጓሚ መንግሥቱ ለማ
27.   “የእንስሳት እድር”፣ ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል፣ ተርጓሚ ለማ ፈይሳ
===ዓለም አቀፍ የተረት መጻሕፍት===
1.       “ተረበኛው ነስሩዲን”፣ ደራሲ ኢድሪስ ሻህ፣ ተርጓሚ አማረ ማሞ
2.     “አንድ ሺህ አንድ ሌሊት”፣ ወደ እንግሊዝኛ ተርጓሚ ሪቻርድ በርተን፣ ወደ አማርኛ ተርጓሚ ተፈሪ ገዳሙ
3.     “ጥንቸሉ ጴጥሮስ፣ ደራሲ ቤትሪክስ ፖተር፣
4.     “የኤዞፕ ተረቶች”፣ ደራሲ ኤዞፕ፣ ተርጓሚ አማረ ማሞ
5.     “የግሪም ተረቶች”፣ ደራሲ የግሪም ወንድማማቾች፣ ተርጓሚ ዓለም እሸቱ
====ዘመን አይሽሬ የግጥም ስብስቦች====
1.      “ነቢዩ”፣ ገጣሚ ካህሊል ጂብራን
2.     የአሌክሳንደር ፑሽኪን ግጥሞች፣ ተርጓሚ አያልነህ ሙላቱ
3.     የዑመር ኸያም ሩባያቶች፣ ወደ እንግሊዝኛ ትርጉም በኤድዋርድ ፊዝጂራልድ፣ ወደ አማርኛ ተርጓሚ ተስፋዬ ገሠሠ
4.     ኢሊያድ እና ኦዲሴይ፣ ገጣሚ ሆሜር፣ ተርጓሚ ታደለ ገድሌ
==== ወቅታዊ የሽያጭ ሪከርድ ያስመዘገቡ መጻሕፍት (Best Sellers)====
1.      “የጡት አባት”፣ ደራሲ ማሪዮ ፑዞ
2.     “የሚስጢሩ ቁልፍ”፣ ደራሲ ኬን ፎሌት፣ ተርጓሚ ኤፍሬም እንዳለ
3.     “የዳቪንቺ ኮድ”፣ ደራሲ ዳን ብራውን፣
4.     “ሃሪ ፖተር እና የፈላስፋው ጠጠር”፣ ደራሲ ጄ.ኬ. ሬውሊንግስ፣
5.      “ሳዳም ሑሴን እና የባህረ ሰላጤው ቀውስ”፣ ደራሲ ባሪ ሩቢን፣
6.     “ሞገድ”፣ ደራሲ አርቪንግ ዋላስ፣
7.     “የኦዴሳ ፋይል”፣ ደራሲ ፍሬድሪክ ፎርስይዝ፣ ተርጓሚ ማሞ ውድነህ
8.     “ዘጠና ደቂቃ በኢንቴቤ”፣ ተርጓሚ ማሞ ውድነህ
9.     አስራ አንዱ ውልዶች፣ ደራሲ ጄፍሪ አርቸር፤
=== ዓለም አቀፍ ተጽእኖን የፈጠሩ የፖለቲካና የፍልስፍና መጻሕፍት===
1.      “ካፒታል”፣ ደራሲ ካርል ማርክስ፣ (በቡድን ነው የተተረጎመው፡፡ የጓድ መንግሥቱ ኃይለማሪያም አስተርጓሚ የነበሩት አቶ ግርማ በሻህ እና ደራሲ ስብሐት ገብረ እግዚአብሄር በተርጓሚዎቹ ውስጥ ይገኛሉ)፡፡
2.     “የኮሚኒስት ፓርቲ ማኒፌስቶ”፣ ደራሲ ካርል ማርክስና ፍሬድሪክ ኤንግልስ፣ ተርጓሚ “ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት”
3.     “የሌኒን ምርጥ ስራዎች”፣ ደራሲ ቪላድሚር ሌኒን፣ ተርጓሚ “ኩራዝ”
=== ታዋቂ ግለ-ታሪኮችና የታሪክ ማስታወሻዎች===
4.     “ትንሿ መሬት”፣ ደራሲ ሊዮኒድ ብሬዥኔቭ፣ ተርጓሚ “ፕሮግሬስ የመጻሕፍት ማዘጋጃ ድርጅት”
5.     “የኦሽዊትዝ ሚስጥር”
6.     የአና ማስታወሻ፤ ደራሲ “አና ፍራንክ”፣ ተርጓሚ “አዶኒስ”
7.     “ፓፒዮ”፣ ደራሲ ሄንሪ ቻሬሬ
8.     “በረመዳን ዋዜማ”፣ ደራሲ ሙሐመድ ሀይከል፣ ተርጓሚ ማሞ ውድነህ
9.     “የጽናት አብነት”፣ ሄለን ከለር
=== ሌሎች ኢ-ልብወለድ መጻሕፍት===
1.      “ጠብታ ማር”፣ ደራሲ ዴል ካርኒጌ፣ ተርጓሚ ባሴ ሀብቴና ደምሴ ጽጌ

ኀዳር ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ባዘጋጀው የ2006 የጸጥታ የደህንነት ግምገማ ላይ የተገኙ የተለያዩ ክልሎች የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊዎች ባቀረቡት ሪፖርት በአዲስ አበባ የሃይማኖት አባቶች የተሰጣቸውን የደህንነት ተልእኮ በፈቃደኝነት አምነው ሲፈጽሙ በትግራይና ፣ በአማራ ክልሎች ግን የሃይማኖት አባቶች ተልእኮዋቸውን በአግባቡ ሳይወጡ ቀርተዋል። የትግራይ ጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ እንደተናገሩት በክልሉ አብዛኛው ህዝብ የኦሮቶዶክስ …

ኀዳር ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲዎቹ ጥሪውን ያስተላለፉት ህዳር 27 እና 28 የሚካሄደውን የ24 ሰአት የተቃውሞ ሰልፍ በማስመልከት ባወጡት መግለጫ ነው ገዥው ፓርቲ ወደ ስልጣን ከመጣ ጊዜ ጀምሮ በህገ መንግስቱ ካስቀመጠውና በየ መድረኩ ከሚናገረው በተቃራኒ የእምነት ተቋም መሪዎችን ካድሬዎቹ በማድረግ ህዝብን ለመያዝ እየጣረ እንደሚገኝ የሚያትተው መረጃው፣   የገዥውን ፓርቲ አካሄድ የተቃወሙ ምዕመናን በአሸባሪነት፣ …

ኀዳር ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየአመቱ ህዳር 29 የሚከበረው የብሄር ብሄረሰቦች በአል አምና በጅጅጋ ሲከበር ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ሲያስወጣ ዘንድሮ ደግሞ በአሶሳ በሚከበረው እስከ 300 ሚሊዮን ብር ያስወጣል። ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች እንደሚሉት የብሄር ብሄረሰቦችንም ሆኑ  የባንዲራ፣ የመከላከያና ሌሎች አገር አቀፍ በአላትን በብቸኝነት ለማዘጋጀት የተፈቀደለት ወዛም ኮሚኒኬሽን የተባለው ድርጅት ለህወሃት ባለስልጣናት …

ኀዳር ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰሜን ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ ወረዳ የጸጥታ አስተዳደር ሰራተኞች እርስ በርስ ሲገማገሙ ከቆዩ በሁዋላ ፖሊሶቹ የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊውንና አቶ ባዩ ማሩንና ሌላ የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊውን በጥይት ደብድበው ገለዋል። አቶ አባይ ማሩ በጃናሞራ ወረዳ መካነ ብርሃን ከተማ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ህዳር 3 ቀን ተቀብረዋል። በተራ ፖሊስ አባላት የተወሰደው …

ኀዳር ፳፭(ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ  ህዳር 25/2007 ዓም የመከላከያ ምስክርነቱን የሰጠ ሲሆን  ጥር 11/2004 በታላቁ አወሊያ መስጂድ ቅጥር ጊቢ ተገኝቶ  የሙስሊም መሪዎች በነጻ ምርጫ መመረጣቸውን ተናግሯል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሃምሌ 9/2004 የህግ አዋቂውን ኡስታዝ ካሚል ሸምሱን፣ ኡስታዝ አቡበክር አህመድን፣ ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋን፣  ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ማናገሩን ገልጿል።  የመንግስት ባለስልጣን …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የተለያየ እምነት ተከታይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በአገር ላይ የመጣን ችግር በጋራ ሲከላከሉ ዘመናትን አስቆጥረዋል፡፡ የተቀያየሩት መንግስታት ሳይወስኗቸው፣ እምነታቸው ሳይለያያቸው በጋራ ችግሮቻቸውን ሲፈቱ ቆይተዋል፡፡ በእየ እምነቶቻችን ያሉት ጥልቅ ስነ ምግባሮች ጥቃቅን ልዩነቶቻችንን ተሻግረው አብሮ ለመኖራችን ዋነኛ ሚስጥሮች ናቸው፡፡ በዚህ በኩል እምነቶቻችን ኢትዮጵያውያን ለተሳሰርንበት ድር ትልቅ ሚና እንዳላቸው መናገር ይቻላል፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያውያን ይህን ታሪካዊ መስተጋብር ሲያደርጉ እምነታቸውን በነጻነት ያራምዱ ነበር ማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ጊዜያት እምነታቸውን በነጻነት እንዳይከተሉ የተለያዩ በደሎች ደርሰውባቸዋል፡፡ የእምነት ነጻነታቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ትግልም ከፍተኛ ዋጋ ከፍለዋል፡፡
Image
ህወሓት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜም ጀምሮ እንደሚያከብር ቃል ከገባቸውና በህገ መንግስቱም ካሰፈራቸው ጉዳዮች መካከል የእምነት ነጻነት አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ ሆኖም ይህን መብት በየ መድረኩ ለፕሮፖጋንዳነት ከመጠቀምና የወረቀት ጌጥ ከመሆን አልፎ መሬት ላይ ሲተገበር አልታየም፡፡ ገዥው ፓርቲ ወደ ስልጣን ከመጣ ጊዜ ጀምሮ በህገ መንግስቱ ካስቀመጠውና በየ መድረኩ ከሚናገረው በተቃራኒ የእምነት ተቋም መሪዎችን ካድሬዎቹ በማድረግ ህዝብን ለመያዝ እየጣረ ይገኛል፡፡ ይህን የገዥው ፓርቲ አካሄድ የተቃወሙ ምዕመናን በአሸባሪነት፣ በጸረ ሰላም ኃይልነት፣ በአፍራሽነት…እና በሌሎችም ስርዓቱ በመፈረጃነት በሚጠቀምባቸው ስሞች ሲከስ፣ ሲያስርና እርምጃ ሲወስድ ኖሯል፡፡ ለአብነት ያህልም የሙስሊምና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን ስርዓቱ ከሚፈልገው ውጭ እምነታቸውን እንዳይከተሉ እያደረገ እንደሚገኝ መጥቀስ በቂ ነው፡፡

በኢህአዴግ አገዛዝ እምነቱን በነጻነት እንዳይከተል በደል ሲደርስበት ከቆዩት መካከል የሙስሊሙ ማህበረሰብ አንዱ ነው፡፡ ኢህአዴግ በአንድ በኩል የእምነት ነጻነትን እንደሚያከብር እየተናገረ በእውኑ ግን የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን መሪዎች እምነቱ ከሚፈቅደው ውጭ በቀበሌ እስከመምረጥ ደርሷል፡፡ እምነታቸው ባስቀመጠው መሰረት መሪዎቻቸውን መምረጥ እንዳለባቸው ድምጻቸውን ያሰሙ የእምነቱ ተከታዮች በስርዓቱ ከፍተኛ በደል ደርሶባቸዋል፡፡ ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈረው መብታቸው እንዲከበር በመጠየቃቸው ብቻ ጸረ ኢትዮጵያ፣ አሸባሪ፣ አክራሪና ሌሎች ስሞች ተለጥፎባቸዋል፡፡ በርካቶች በዘግናኝ እስር ቤቶች ታጉረዋል፣ በቅዱሱ የረመዳን እለት ሳይቀር በስርዓቱ ታጣቂዎች በጭካኔ ተደብድበዋል፤ የእስልምና እምነት ስርዓት ከሚፈቅደው ውጪ መስጊዶቻቸው ተደፍረዋል፡፡ በተለይ ባለፉት 3 አመታት መብታቸው እንዲከበር በሰላማዊ መንገድ የጠየቁት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ የሚገኘው ታሪካዊ በደል ስርዓቱ የእምነት ነፃነትን በማታለያነት ከመጠቀም ውጭ በህገ መንግስቱ ያሰፈረውን መብት እንደማያከበር፣ ከዚህም አልፎ ጸረ እምነት ስለመሆኑ ቋሚ ማሳያ ነው፡፡

ስርዓቱ የተጠናወተው እምነትን በመሳሪያነት የመጠቀም፣ የእምነት መሪዎችን ካድሬ የማድረግና ህዝብን የመሸበብ መጥፎ አባዜ በክርስትና እምነት ተከታዮች ላይም በግልጽ ሲንፀባረቅ ቆይቷል፡፡ ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ ክርስትና እምነትን ከቆዩ ስርዓቶች ጋር በማዛመድ በጠላትነት ፈርጆታል፡፡ የእምነቱ መሪዎችንም መሳሪያ ለማድረግ የሚቻለውን ያህል ደክሟል፡፡ ከዚህ አለፍ ሲል ደግሞ ኢትዮጵያውያንን በእምነታቸው ለመከፋፈልና ለማጋጨት ጥረት እንዳደረገ በርካታ መረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡ ልክ እንደ ሙስሊሙ ማህበረሰብ፤ የክርስትና በተለይም የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች የስርዓቱ መጥፎ አባዜ ገፈት ቀማሽ ሆነዋል፡፡

ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ባለፉት 24 አመታት ኦርቶዶክስ ተከታዮችን ከሌሎች የእምነት ተከታይ ኢትዮጵያን ጋር ለማጋጨት ከመጣር ባለፈ ካድሬዎች በቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እንዲወስኑ ትልቅ ስራ ሰርቷል፡፡ ይህ ጥረቱ በልማት ስም በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ እጅግ የሚከበሩ ገዳማትን እስከ ማፍረስ ደርሷል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ስር የተቋቋሙና ከእሱ ካድሬያዊ መስመር ጋር ለመሄድ ያልፈቀዱ ተቋማትንና ግለሰቦችን ማጥቃቱንም ቀጥሏል፡፡ በማህበረ ቅዱሳን ላይ ሊወስድ ይችላል የሚባለው እርምጃ እንደምሳሌ ማቅረብ ይቻላል፡፡ በሌሎች አማኞች ላይም ተመሳሳይ በደል እንደሚፈጸም ይታወቃል፡፡

ህወሓት/አህአዴግ የእምነት መሪዎችን ካድሬዎቹ ማድረግ የሚፈልገው የእሱ መሰረታዊ የፖለቲካ አቋም ስለ እውነት፣ ስለ አንድነት፣ ስለ ሰላም ከሚያስተምሩት የእምነት መርሆች ጋር ፍጹም ተቃራኒ በመሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን በእምነታቸው መሰረት ስለ አንድንት ሲሰበኩ የኢህአዴግ የመግዢያ መሳሪያ የሆነው ከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው ዋጋ አልባ እንደሚሆን ግልፅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን በየ እምነቶቻቸው ስለ ሰላም ሲሰበኩ ከኢህአዴግ የጦረኝነት ባህሪ ጋር ቢጋጩ የሚገርም አይሆንም፡፡ በእየ እምነቶቻቸው ስለ እውነት የሚሰበኩት ኢትዮጵያውያን መሰረቱን በሙስና፣ በሀሰትና በፈጠራ የተመሰረተ ስርዓት የሚጠብቃቸው እርምጃ አሁን ኢህአዴግ የሚወስደውን አይነት ቢሆን ሊገርም አይችልም፡፡ በመሆኑም በኢህአዴግና በምዕመናን መካከል የሚታየው ተቃርኖ በነጻነት እምነትን የመከተልና የጸረ እምነትነት ነጭና ጥቁር ተቃርኖ ነው፡፡

እንዲህም ሆኖ ግን በርካታ ኢትዮጵያውያን በእምነታቸው ለመጽናት ከፍተኛ መስዋዕትነት እየከፈሉ ይገኛሉ፡፡ ለዚህም በእስር ላይ የሚገኙት፣ እንዲሁም ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ በጁምዓ እለትና ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ በጽናት ትግላቸውን የቀጠሉት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ትልቅ አርዕያ ናቸው፡፡ ስርዓቱ በጥይትና በቆመጥ ሊገታው ያልቻለው ይህ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹም ተምሳሌት የሚሆንና ሊደነቅ የሚገባም ነው፡፡ በተመሳሳይ በየ ገዳሙና በሌሎችም ተቋማት የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች ኢህአዴግ ከሌሎች ጋር ለማጋጨት ሲጥር፣ በእምነታቸው ጣልቃ ሲገባና መሪዎቻቸውን ሊመርጥ ሲሞክር በመቃወም ትግላቸውን ቀጥለዋል፡፡

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ይህን ገዥው ፓርቲ በኢትዮጵያውያን ምዕመናን ላይ የሚፈጽመውን በደል እና ምዕመናኑ የእምነት ነጻነትን ለማስከበር የሚያደርጉትን ትግል ከልብ ይደግፋል፡፡ ይህን ሲያደርግ ሀይማኖት ኢትዮጵያውያንን ያስተሳሰረ ትልቅ ድር እንደሆነ፣ ትውልዱን በመልካም መንገድ ለመቅረጽ ካለው ትልቅ ሚና አንጻር እና ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያውያን የእምነት ነጻነት ሊከበርላቸው የሚገባ መሰረታዊ መብት በመሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም ስርዓቱ እየፈጸመው የሚገኘውን ታሪካዊ ስህተት የትኛውም ኢትዮጵያዊ ሊቃወመው የሚገባ እንደሆነ እናምናለን፡፡

ትብብሩ የአንድ ወር መርሃ ግብር አውጥቶ ሲንቀሳቀስ የመርሃ ግብሩ አንድ አካል ካደረጋቸው መካከል አማኞች በየፊናቸው ለአገራቸው እንዲጸልዩ የጠየቀበት ይገኝበታል፡፡ ይህን ስናደርግ ኢትዮጵያውያን አማኞች በአገራቸው ላይ የሚመጣን አደጋ፣ በራሳቸውና በሌሎች ላይ የሚፈጸምን በደል በጋራ በመከላከል ያላቸውን ተሞክሮ፣ አቅምና ታሪካዊ ግዴታም ግምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ መርሃ ግብሩን ይፋ ካደረግንበት ጊዜ ጀምሮ ለጥሪው አመርቂ መልስ ማግኘታችን ምዕመናን ለለውጥ ያላቸውን ፍላጎት አረጋግጦልናል፡፡ ወደፊትም ከገጠመን መከራ እንድንወጣ ኢትዮጵያውያን ምዕመናን በእምነታቸው ላይ ከሚደርስባቸው በደል ሳይበግራቸው ከጎናችን እንደሚሆኑ ጥርጥር የለንም፡፡

ትብብሩ ህዳር 27/28 ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል የ24 ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ ያደርጋል፡፡ ይህ መርሃ ግብር ለኢትዮጵያውያን ምቹ ስርዓት ለመመስረት የሚያስችል የትግል ጉዞ እንደሚሆንም እናምናለን፡፡ በመሆኑም ፀረ እምነት በሆነው የገዥው ፓርቲ አካሄድ እምነታቸው እየተረገጠ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእምነት ነጻነታቸውን ለማረጋገጥ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የአዳር ሰልፉን ቅስቀሳ እንዲደግፉና በሰልፉም በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ታሪካዊ ግዴታችን በመወጣት የእምነት ነጻነታችንን እናረጋግጥ!

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

የፍርድ ቤት ሙሉና የተጣራ ዘገባ በቂሊንጦ ልሳን

የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የፋክት መፅሄት ዓምደኛ እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ኡስታዝ ያሲን ኑሩ ለኮሚቴዎቻችን አስደናቂና አስደማሚ ምስክርነታቸውን ሰጡ።
⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄
★የቂሊንጦ ልሳን
(የኢትዬጲያዊያን ሙስሊሞች ድምፅ)

⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄⇄

ህዳር 25/2007 ዕለተ ሃሙስ

በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ታስረው ጉዳያቸውን CMC ከዲቦራ ት/ቤት አጠገብ በሚገኝው በፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት እየተከታተሉ የሚገኙት የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎቻችንና ወንድሞቻችን በዛሬው እለት እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን አቅርበው አስደናቂ የመከላከያ ምስክርነት ቃሉን እንደሰጠ ተገለፀ።

እንደሚታወሰው ትላንት ህዳር 24/2007 ዕለተ ረቡዕ በዋለው ችሎት የቲሞች አባት የሆኑትና በነኡስታዝ አቡበክር አህመድ የክስ መዝገብ 12ተኛ ተከሳሽ የሆኑት ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ ለ9ኛ ተከሳሽ ለሆኑት ለኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ ሲሆን በተለይም በጭብጡ ላይ ማዕከላዊ ተብሎ በሚጠራው እስር ቤት የደረሰባቸውን የህግ ጥሰትና ኢ-ሰብዓዊ ድብደባና እንግልቶችን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። በማያያዝም ቃሉን በሃይል እንደሰጠና አካላዊ ድብደባው አሁን ድረስ ምልክቱ እንደሚታይ ገልፀዋል።

በፍርድ ቤቱ ቀነ ቀጠሮ መሰረትም መሪዎቻችንና የሰላም አምባሳደሮቻችን በችሎት የቀረቡ ሲሆን ለተከታታይ ጊዜያት ዳኞች እንዲቀርብ ትዕዛዝ ቢሰጡም በማረሚያ ቤቱ ያረባ ምክንያት የተነሳ ያልቀረበው፥ ህዳር 17/2007 ለመጨረሻ ጊዜ ዛሬ እንዲቀርብ በታዘዘው መሰረት ትላንት አመሻሹ ላይ ከታሰረበት ከዝዋይ ማረሚያ ቤት ወደቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የመጣው የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የፋክት መፅሄት ዓምደኛ እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አስደናቂና አስደማሚ የመከላከያ ምስክርነቱን ለኮሚቴዎቻቻንና ለወንድሞቻችን ሰጥቷል።

እንደሚታወቀው የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና የፋክት መፅሄት ዓምደኛ እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 9ኛ ወንጀል ችሎት፣ ጥቅምት17 ቀን 2007 በህገ መንግስቱ የተፈቀደውን የመፃፍና የመናገር መብት በመጣስ የፌደራሉ አቃቤ ህግ ካቀረባቸው 3ት ክሶች ውስጥ የወንጀል ህግ 257(ሀ)ን በመተላለፍ የተመለከተውን “በፍትህ ጋዜጣ ላይ አመፅ የሚቀሰቅሱ ጽሑፎችን በራሱና በሌሎች አመንጭነት እንዲታተሙ ማድረግ” በሚለው በአንዱ ክስ ብቻ የ3ት አመት ፅኑ እስራት እንደፈረደበት ይታወቃል።

ዛሬ ህዳር 25/2007 ዕለተ ሃሙስ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በማረሚያ ቤት የፖሊስ አባላት ታጅቦ በፍርድ ቤት ቀርቦ የመከላከያ ምስክርነቱን የሰጠ ሲሆን ያስረዳውም ጥር 11/2004 በታላቁ አወሊያ መስጂድ ቅጥር ጊቢ እንደተገኝ በመግለፅ ሶስቱን ጥያቄዎች ህዝቡ እንደጠየቀ፣ ምርጫው ፍፁም ሰላማዊ ና ህዝባዊ እንደነበር፣ የጥያቄው መነሻ ህዝበ ሙስሊሙ እንደሆነ፣ ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ ለህዝቡ ጥያቆዎቻችሁን አቅርቡ ብሎ በመድረኩ ተናግሮ ህዝቡም በወረቀት እየፃፈ እንደሰጠ፣ በአጠቀላይ ምርጫው ፍትሃዊ እንደነበረና ኮሚቴዎቹም በህዝብ እንደተመረጡ አስረድቷል።

በመቀጠልም ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥር 11/2004 ላይ ጥር 18/2004 እንገናኝ ብለው ቀጠሮ በሰጡት መሰረት በአወሊያ እንደነበር በመግለፅ በውቅቱም ከህዝቡ የመጡትን ጥያቄዎች ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጠቢያ እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዳደረሱ በመድረክ መግለፃቸውን አስረድቷል። የሙስሊሙን ማህበረሰብ ጥያቄዎችና የኮሚቴውን ሂደትም በሚያዘጋጀው ጋዜጣ ላይ እንዳወጣውምገልፆዓል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሃምሌ 9/2004 የህግ አዋቂውን ኡስታዝ ካሚል ሸምሱን፣ ኡስታዝ አቡበክር አህመድን፣ ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋን፣ የታሪክ ሙሁሩን ኡስታዝ አህመዲን ጀበልን ቃለ መጠይቅ ማድረጉን በመግለፅ በቃላ መጠይቁ ላይም በዋናነት የሚያጠነጥነው ጥያቄዎቻቸው እንዳልተመለሱና ጥያቄውም እስኪመለስ ድረስ ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንደሚቀጥሉ እንደሆነ ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል።

ተመስገን ደሳለኝ አያይዞም የመንግስት ባለስልጣን የሆኑት አ/ቶ ሪድዋን ሁሴን በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ በመቅረብ “ኮሚቴው አላማው ኢስላማዊ መንግስት ማቋቋም ነው” ብለው መግለጫ ሲሰጡ ማየቱንና ኡስታዝ አቡበክርን ስለሁኔታው ጠይቆት በጭራሽ አላማቸው እንዳልሆነ መግለፁን አስረድቷል፤ ተመስገን ጨምሮም በወርሃ መስከረም የተካሄደው የመጅሊስ ምርጫ መንግስት በቀበሌ ይሁን ያለው ” መንግስት ለ23 ዓመታት ሙስሊሙን ማህበረሰብ በቀበሌ ምርጫ እያካሄደ ጨፍልቋል፥ አሁንም ለመጨፍለቅ ነው፥ ከጨፍላቂዎቹ አንዱ ደግሞ አ/ቶ ሪደዋን ሁሴን ናቸው” ብሎ አስደማሚ ንግግር አርግቷል።�

በቀጣይም ኡስታዝ ያሲን ኑሩ በነአቡበክር አህመድ መዝገብ ለተካተቱት ለኡስታዝ ሙራድ ሽኩር የመሰከሩ ሲሆን በተለይም ማዕከላዊ እስር ቤት በተለምዶ ሳይቤሪያ ተብሎ በሚጠራው ክፍል ውስጥ አብረው እንደነበሩ በመግለፅ የተፈፀመበትን የመብት ጥሰትና ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ አጋልጠዋል።

ኡስታዝ ሙራድ ሽኩር ኮሚቴው ኢስላማዊ መንግስት ሊያቋቁም አቅዷል፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቶቹ ከአልቃዒዳ ጋር ግንኙነት አላቸው…ወዘተ እያሉ እየደበደቡና መስክር እያሉት እንደነበር ኡስታ ያሲን ገልፆዓል።

በማያያዝም ለኡስታዝ ሙራድ ሽኩር “ያሲን ጋር አብረን አንድ ክፍል ውስጥ ለምን እንዳረግንህ ታውቃለህ? አይተከዋል አይደል እንዴት ጨርቅ እንዳረግነው? ከእሱ እንድትማር ነው አንድ ክፍል ላይ ያስገባንህ” ይሉት እንደነበር ለፍርድ ቤቱ ገልፆዓል።

እውቁ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ኡስታዝ ያሲን ኑሩ የመከላከያ ምስክርነታቸውን ከሰጡ በሁዋላ በፌደራሉ አቃቤ ህግ የቀረበላቸውን መስቀለኛ ጥያቄዎች በአስደናቂ ሁኔታ መልሰው ችሎቱ ተጠናቋል።
Image
የፍርድ ሂደቱ ነገም ይቀጥላል።

ፍትህ ለኮሚቴዎቻችን!
ፍትህ ፍትህን ለተነፈጉ!
ሰላምና መረጋጋት ለኢትዮጲያ ህዝብ!

የጊዜ፣ የገንዘብ፣ የዕውቀት…መስዋዕትነት ተከፍሎባቸው የሚሰሩ ዘገባዎችን ሼር እና ኮፒ በማድረግ እንዲሁም በየሰሌዳን፣ በየጉረፑ፣ በየፔጁ በመለጠፍ መረጃውን ለሰፊው ማህበረሰባችን በማሰራጨት ኢስላማዊ ግዴታዎን ይወጡ!!!! ይጠቀማሉ!!! ኢንሻ አላህ

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በአፅህሮቱ (IOM) ታንዛንያ ዉስጥ ታስረዉ የነበሩ 253 የኢትዮጵያ ስደተኞችን ባለፈዉ ሳምንት ወደ ሃገራቸዉ መልሶአል። ድርጅቱ እንዳስታወቀዉ ከታንዛንያ እስር ቤት ተለቀዉ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱት ስደተኞች መካከል 39 ኙ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ናቸዉ።

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት በአፅህሮቱ (IOM) ታንዛንያ ዉስጥ ታስረዉ የነበሩ 253 የኢትዮጵያ ስደተኞችን ባለፈዉ ሳምንት ወደ ሃገራቸዉ መልሶአል። ድርጅቱ እንዳስታወቀዉ ከታንዛንያ እስር ቤት ተለቀዉ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱት ስደተኞች መካከል 39 ኙ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ናቸዉ።

ራሳቸዉን ቤተ- እሥራኤላዉያን እያሉ የሚጠሩ የኢትዮጳያ አይሁዶች ባለፈዉ ሰሞን በየዓመቱ የሚያከብሩትን የሥግድ በዓል እያሩሳሌም ላይ በከፍተኛ ድምቀት አክብረዋል። የሥግድ በዓል በቤተ እሥራኤላዉያን ዘንድ እንዴት እና ለምን ይከበራል? በለቱ ዝግጅታችን ቤተ-እሥራኤላዉያን ስለሚያከብሩት የሥግድ በዓል ምንነት እንመለከታለን።

ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀሎኞች መዳኛ ፍርድ ቤት (አይ ሲ ሲ )በኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ላይ የቀረበው ክስ በአንድ ሳምንት ውስጥ እንዲጠናቀቅ አለያም ክሱ እንዲሰረዝ ወሰነ ።የፕሬዝዳንቱን ጉዳይ የያዙት አቃቤ ህጎች መረጃ ለማሰባሰብ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸዉ ያቀረቡትን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ዉድቅ አድርጎቷል።

* ስለ ሰራተኞች መብት ጥበቃ መነሳቱ አልተዘገበም * በተወያይ ኤጀንሲዎች በኩል ግን ረቂቁ ውዝግብ አስነስቷል * ከዚህ ቀደም ያለ በኮንትራት ለተበተኑትስ ዜጎችስ ምን ታስቧል ? አዲሱን መረጃ ያገኘሁት ሃገር ቤት ከሚታተመው ከአድማስ ጋዜጣ ላይ ነው ፣ እንዲህ ይላል ” ወደ አረብ አገራት የሚሄዱ ሰራተኞች ላይ የሚደርሰውን ችግርና እንግልት ለማስቀረት በሚል ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የቆየውን […]

Journalist Tesfalem Woldeyes

 #FreeZone9bloggers  #FreeEdom  #FreeTesfalem  #FreeAsemamaw  #Ethiopia

የዞን 9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች “የተሻሻለ ክስ” ተሰማ ፡፡  ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በልደት በአሉ የደረሱትን የንኳን አደረሰህ መልእክቶች በፈገግታ ሲቀበል አርፍዷል፡፡

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ 10 ተከሳሾችን የፍርድ ሂደት የሚያየው  የልደታው ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጠዋት ተሰይሞ ተሻሻለ የተባለውን የአቃቤ ህግ ክስ በቃል አዳምጧል፡፡ ክሱ አንዲሻሻል የታዘዘበትን ብይን ግልባጭ ማግኘት አልቻልንም ያሉት የተከሳሾች ጠበቆች ክሱ መቅረብ አንደማይገባው ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ጠበቆች ክሱ ላይ አስተያየታቸውን አንዲሰጡ እድል አንደሚሰጥ በመጥቀስ ተሻሻለ የተባለው ክስ በንባብ ተሰምቷል፡፡

የተሻሻለው ክስ አንደቀደመው ሁሉ ዞን 9 የሚል ምንም አይነት ቃል ያልተጠቀመ ሲሆን በተለያየ ቦታ የተጠቀሰው የሽብር ቡድን ግንቦት ሰባት እንደሆነ እንድምታ ባለው ሁኔታ በተደጋጋሚ የግንቦት ሰባት ስም ተጠቅሷል፡፡ ተቀጣጣይ ቦንብ አጠቃቀምና የሽብር ተግባር ተከታታይ ስልጠናም ከግንቦት ሰባት አንደተሰጠ በደፈናው ጠቅሷል፡፡ በክሱ ውስጥ ስልጠናው በማን እና መቼ እነደተሰጠ የስልጠናው ዝርዝር ተሳትፎና ቦታ ያልተጠቀሰ ሲሆን ሊከናወን የነበረው የሽብር ተግባርም ምን አንደሆነ አሁንም አልታወቀም፡፡ ክሱ የግንቦት ሰባት ልሳን ለሆነው ኢሳት መረጃ ማቀበልንም የሰሩት የሽብር ተግባር ነው ሲል አካቶታል፡፡ 

ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ተቀበለ የተባለው 48000 ብር አሁንም በድጋሚ የተጠቀሰ ሲሆን ብሩ ከማን አና ለምን ተግባር አንደተላከ በዝርዝር ያልተገለጸ ሲሆን በደፈናው ግን ለሽብር ተግባር ተብሎ በድጋሚ ተጠቅሷል፡፡ የተከሳሾችን የስራ ዝርዝር በግልጽ ለማቅረብ የሞከረው ክሱ ጦማሪት ሶልያና ሽመልስን የቡድኑ ዋና አስተባባሪ ጦማሪ በፍቀዱን ሃይሉን ጸሃፌ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀን የአገር ውስጥ አስተባባሪ የሚል የሽብር ስራ ድርሻ የሰጣቸው ሲሆን ሌሎቹን ተከሰሾች መስራችና አባል ናቸው ሲል አስቀምጧል፡፡ ኦነግን ከክሱ ውስጥ ከማውጣት ውጪ መሰረታዊ ለውጥ ያላሳየው የተሻሻለው ክስ ፣ የስልጠናዎቸን ዝርዝር በማን እና የት አንደተሰጡ፣ ተቀበሉ የተባሉትን የሽብር ስትራቴጂ ፣ እነዲሁም ሊሰሩት የነበረውን ሽብር ተግባር ሳያስቀምጥ አልፏል፡፡
የተከሳሽ ጠበቆች ክሱ አንዲሻሻል የታዘዘበትን ብይን ከፍርድ ቤቱ ተቀብለው ፣ አስተያየታቸውን ይዘው አንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በዛሬው ቀጠሮ ጦማርያን እና ጋዜጠኞቹ  በጠንካራ መንፈስ እና ፈገግታ የታዩት ሲሆን ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ልደት ቀኑን በማስመልከት የቀረበለትን የእንኳን አደረሰህ መልእክት በልባዊ አጸፋ ሲመልስ ታይቷል፡፡ የዞን9 ጦማርያንም ለጓደኛቸን ተስፋለም ወልደየስ መልካም ልደት ለመመኘት አንወዳለን፡፡

ማስታወሻ
ዞን9 ጦማርያን አና ጋዜጠኞች ምንም አይነት ህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው አንደማያውቁና ክሱም ፓለቲካዊ አንደሆነ እያስታወስን ፍርድ ቤቱ የጀመረውን መንገድ በማጠናከር ለአገራቸው የሚያገባቸው ወጣት ጦማርያንን በነጻ በማሰናበት የፍትህ ስርአቱ የሚታማበትን ወገንተኛነት የመለወጥ እድሉን አንዲጠቀም ለማስታወስ አንወዳለን ፡፡

አሁንም ስለሚያገባን አንጦምራለን!
ዞን 9

Journalist Asmamaw, Blogger Atnaf and Natnael at Lideta Court Today

ኀዳር ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፋይናንሻል ታይምስ የተባለው አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ከአለማቀፍ የግል ባንኮች ለመበደር የወሰነው የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት ለግል አበዳሪ ተቋማት ባላሃብቶች የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች አስተያየቶችን እየሰጡ ነው። ፋይናንሻል ታይምስ 1 ቢሊዮን ዶላር ለመበደር ጫፍ ላይ የደረሰው መንግስት ለውጭ ባለሀብቶች የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ያልተለመደ ወይም እስከዛሬ ያልታየ ነው ብሎታል። …

ኀዳር ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ትብበሩ የንግዱ ማህበረሰብ ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም በሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ከመሳተፍ ጀምሮ በገንዘብና በሌሎችም መንገዶች ድጋፉን እንዲገልጽ ጠይቋል። ኢህአዴግ ወደ ስልጣን በመጣበት ጊዜ ጀምሮ ነጻ ገበያን እንደሚከተል በመግለጹ የንግዱ ማህበረሰብ በነጻ ገበያ መርህ ተወዳድሮ ራሱንም አገሩንም ይጠቅማል የሚል ተስፋ የነበረ ቢሆንም ይህ ተስፋ እውን ሳይሆን …

ኀዳር ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-9ነኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል የሚያስተናግደው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል  ዝግጅት ማጠናቀቁን ቢገልጽም፣ በአካባቢው መንግስትን  የሚቃወሙ ኃይሎች በተለያየ ጊዜያት በደፈጣ ውጊያ ጥቃት  ማድረሳቸው ያሰጋው መንግስት በአካባቢው ከፍተና ወታደራዊ ሃይል አሰማርቷል። ህዳር 29 ከሚካሄደውን በዓል ጋር ተያይዞ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል ብዙዎች የሚሰጉ ሲሆን፣  ጥቂት የማይባሉ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች …

ኀዳር ፳፬(ሃያ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጀርመንን ለመጎብኘት መገኘታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያውያኑ መንግስትን የሚያወግዝ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል። ጠ/ሚንስተሩ ከጀርመን መሪ አንግላ መርከል ጋር ተገናኝተዋል። ታዋቂው የጀርመን ባንክ ለኢትዮጵያ መንግስት በድር ለመስጠት ከተዘጋጁት ባንኮች መካከል ቀዳሚው ነው። ጉብኝቱም ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን መዘገባችን ይታወቃል።  

በጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሚመሩ የኢትዮጵያ መንግሥት ልዑካን ፤ ከጀርመን መራኂተ መንግሥት ወ/ሮ አንጌላ ሜርክልና ሌሎችም ባለሥልጣናት ጋር በጋራና በአፍሪቃ ቀንድ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸው ተገልጿል። የሁለቱ ሃገራት ባለሥልጣናት ሕንጻ ውስጥ

የ NATO አባል ሃገራት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ፣ ትናንት ባራሰልስ ውስጥ፤ ባደረጉት ስብሰባ፤ የመከላከያው ጉድኝት ኃይል በሚደራጅበትና በሚመደብበት ሁኔታ የተስማሙ ሲሆን፤ ከመጪው ወር 2015 አዲሱ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት መግቢያ አንስቶ ጊዜያዊ ፈጥኖ ደራሽ

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ላቲን አሜሪካዊቷ ሀገር ፔሩ ፣ ከትናንት በስቲያ አንስቶ ለ 12 ቀናት የዓለምን የአየር ንብረት ጉባዔ ስታስተናግድ ትሰነብታለች። የ 195 አገሮች ተወካዮች ናቸው በዚህ ዐቢይ ጉባዔ የሚመክሩት። ለተፈጥሮ አካባቢ ፤ ለየብስ ባህርና ከባቢ አየር

በትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የዘንድሮው ዓመት የሙስና ሠንዘረዥ መሰረት ዴንማርክ እንደ አምናው ከሙስና ነፃ ከሚባሉት ሀገራት ተርታ በቀደምትነት ስትሰለፍ ሶማልያ ደግሞ በሙስና ከተዘፈቁት ሀገራት ከመጨረሻ 1ኛ ሆናለች። ኢትዮጵያና ሌሎች ሀገራትስ?

«ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል» በመባል የሚታወቀው፣ በዓለም ዙሪያ ለነባር ህዝቦች ኅልውና የሚታገለው ድርጅት የጀርመን መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ስለኦሞ ሸለቆ ጉዳይ እንዲያነሱ አሳሰበ። ድርጅቱ በኦሞ ሸለቆ «የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተከሰተ ነው፤ ጀርመንም ሆነች ሌሎች የአውሮጳ ሃገራት የመብት ጥሰቱን አይተው እንዳላዩ ሆነዋል» ብሏል።

ህዳር 27 እና 28 2007 ዓ.ም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የሚያደርጉት የአዳር (24 ሰዓት) ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃ ላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ እስካሁን ሰው በሰውና ቲሸርት በመልበስ ቅስቀሳ ሲደረግ እንደቆየና በተለይ ዛሬ ህዳር 24/ 2007 ዓ.ም ከሰዓት ጀምሮ በአዲስ ከተማ፣ ጉለሌ፣ አራዳ፣ የካ፣ ንፋስ ስልክ፣ ኮልፌና ሌሎች የአዲስ አበባ ክፍለ ከተማዎች ወረቀት በመበተን የተሳካ ቅስቀሳ መደረጉን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል አራዳ ክፍለ ከተማ ፒያሳ አካባቢ ለአዳር ሰልፉ ሲቀሰቅሱ ከነበሩት መካከል የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑት ሜሮን አለማየሁ፣ ወይንሸት ንጉሴ፣ ባህረን እሸቱ፣ ማቲያስ መኩሪያ እንዲሁም ጉለሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሲቀሰቅስ የነበረው ሲሳይ በፖሊስ ተይዘው መታሰራቸው ተግልጾአል፡፡

ከአሁን ቀደም ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ቅስቀሳ ላይ ሲያደርጉ በርካታ የፓርቲው አመራሮችና አባላት መታሰራቸውን ያስታወሱት አቶ ዮናታን ‹‹ይህ የገዥው ፓርቲ የተለመደ እርምጃ ነው፡፡ በቀጣይነትም ሌሎች አባላትንና አመራሮች መታሰራቸው አይቀረም፡፡ ትግሉ መስዋዕትነት የሚያስከፍል እንደመሆኑ በእስሩ ሳንገታ ትግሉን እንቀጥላለን፡፡›› ሲሉ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡ የዛሬው ቅስቀሳ 12 ሰዓት ላይ የተጠናቀቀ ሲሆን ነገ ጠዋት ጀምሮ በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
Image

Image

ከሰሞኑን በአንዳንድ ድረ ገጾችና በሶሻል ሚዲያው የታቦተ ጽዮን መሰረቅ/መጥፋት አሳዛኝ ዜናን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ን መሪ የሆኑት በፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በይፋ መግለጻቸውን እየተቀባበሉ ሲያስነብቡን ሰንብተዋል፡፡ የሶሻል ሚዲያው ተከታታይ በኾኑት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ዘንድም ይህ ዜና ምናልባትም መርዶ ብሎ መግለጹ የተሻለ ሣይሆን አይቀርም ለጊዜውም ቢሆን ብዙዎችን ያደናገጠና ያስቆጨ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የዜናውን […]

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለንግዱ ማህበረሰብ ጥሪ ቀረበ ::

ጥሪው እንደሚከተለው ነው::
የንግድ ማህበረሰብ ለአንድ አገር ምሰሶ ነው፡፡ በዴሞክራሲ በበለጸጉ አገራት የንግዱ ማህበረሰብ ለራሱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ያለውን ፈርጣማ የኢኮኖሚያዊ አቅምና ኢኮኖሚያዊ አቅሙ የሚፈጥርለትን የተሻለ ንቃተ ህሊና በመጠቀም ለጭቁኖች መከታ ሲሆን ታይቷል፡፡ ለዚህም ነው የንግዱ ማህበረሰብ ዴሞክራሲን በመገንባት ትልቅ ሚና እንዳለው የሚነገርለት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን ባለው ሁኔታ የንግዱ ማህበረሰብ በነጻነት ሰርቶ የሚበለጽግበት፣ ወገኑንና አገሩን በተለያየ መንገድ የሚያግዝበት መንገድ በመዘጋቱ የሚገባውን ያህል አስተዋጽኦ አበርክቷል ለማለት ይከብዳል፡፡

ኢህአዴግ ወደ ስልጣን በመጣበት ጊዜ ነጻ ገበያን እንደሚከተል በመግለጹ የንግዱ ማህበረሰብ በነጻ ገበያ መርህ ተወዳድሮ ራሱንም አገሩንም ይጠቅማል የሚል ተስፋ የነበረ ቢሆንም ይህ ተስፋ እውን ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ይልቁንም ገዥው ፓርቲ የራሱን የኢኮኖሚ ኢምፓየር በመመስረት የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ስርዓት አበላሽቶታል፡፡ በራሳቸው ነግደው የሚያድሩ ኢትዮጵያውያን መካከል ግልጽነት በጎደለው መንገድ የአገሪቱን አንጡራ ሀብት እየተጠቀሙ ከሚገኙት የገዥው ፓርቲ ግዙፍ ኩባንያዎች ጋር መወዳደር አቅቷቸው የከሰሩት በርካቶች ናቸው፡፡ በተለያየ መንገድ አሁንም ድረስ የቀጠሉትም ቢሆን ከገዥው ፓርቲ ተቋማት ጋር መወዳደር ተስኗቸው ለራሳቸውም ሆነ ለአገራቸው ማበርከት የነበረባቸውን አስተዋጽኦ እንዳያበረክቱ ተደርገዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለገዥው ፓርቲ ባለማደራቸው ምክንያት አግባብ ያልሆነ ቀረጥና ሌሎች ጫናዎች እየተጣሉባቸው አንድም ከገበያ ወጥተዋል፡፡ አሊያም የሚገባቸውን ጥቅም ማግኘትና አገራቸውን መጥቀስ ሳይችሉ ቀርተዋል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ለገዥው ፓርቲ መዋጮ እንዲከፍሉ ከመጠየቃቸውም በላይ ስርዓቱ ባነገሰው ሙስና ምክንያት እጅ ተወርች ተይዘው ራሳቸውን፣ ህዝባቸውንና ለአገራችን ዴሞክራሲ ግንባታ ያበረክቱትን የነበረው አስተዋጽኦም ተገድቧል፡፡
በሌላ በኩል በገበያው ላይ የሚቆየው ለስርዓቱ ያደረ ብቻ በመሆኑ በርካቶች ለአገር ከመስራት ይልቅ ለገዥው ፓርቲ ማደር መርጠዋል፡፡ በዚህም አንድ የንግድ ማህበረሰብ ለአገሩ ያበረክት የነበረውን አስተዋጽኦ ረስተው የተሳሳተ መንገድ ይዘዋል ብለን እናምናለን፡፡ ራሳቸውን ለገዥው ፓርቲ አሳልፈው በመስጠታቸውም ታሪካዊ ግዴታቸውን ሳይወጡ ቀርተዋል፡፡ ይህን ስንል ግን ከገዥው ፓርቲ ተጠግተው ከሚያገኙት ጥቅም ይልቅ ከህዝብ ጋር ቆመውና ግዴታቸውን እየተወጡ መስዋዕትነት የሚከፍሉ የሉም ማለት አይደለም፡፡ ሆኖም በአሁኑ ወቅት የንግዱ ማህበረሰብ የሚጠበቅበትን ያህል እየሰራ እንዳልሆነ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡

የንግዱ ማህበረሰብ ስርዓቱ በራሱም ሆነ በአገሩ ላይ የሚፈጽመውን ህገወጥነት በየግሉ ከመቃወምም ባሻገር ትግሉን በማገዙ ወደፊት ለራሱም ሆነ ለአገሩ የሚያሰራ ስርዓት መፍጠር ይችላል ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም ስርዓቱ በራሱና በአገራችን ላይ የሚፈጽመውን በደል በመቃወም ላይ የሚገኙትን ተቃዋሚዎች ትግል በሞራል፣ በገንዘብና በሌሎችም ድጋፎች በማገዝና ትግሉን በመቀላቀል ለንግዱ ማህበረሰብና ለኢትዮጵያ የሚያዋጣትን ስርዓት እንድንመሰርት ጥሪ እናደርጋለን፡፡

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለንግዱ ማህበረሰብና በአጠቃላይም ለኢትዮጵያ የሚመች ስርዓት ለመፍጠር በጋራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከዚህም መካከል ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጾ በመንቀሳቀስ ላይ ሲሆን ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ያደርጋል፡፡ ይህ ሰላማዊ ሰልፍ ኢትዮጵያውያን መብታቸው ተከብሮ የሚኖሩባት ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ጮራ የሚፈነጥቅ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም የራሱንም መብት በማስከበርና የአገሩን ዴሞክራሲ በመገንባት ታሪካዊ ሚና ያለው የንግዱ ማህበረሰብ ትግላችን በመቀላቀል፣ በገንዘብና በሞራል በመደገፍ የዚህ ታሪካዊ ትግል አካል እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

ታሪካዊ ግዴታችን በመወጣት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንገንባ!

ግንቦት ሰባት የተሰኘው ፣ መሰረቱን አስመራ ያደረገው ድርጅት፣ በአገር ቤት ላሉ ተማሪዎች፣ መምህራን ጥሪ አቅርቧል። «የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የትምህርት ኃላፊዎችና ፕሬዚዳንቶች ሆይ! ለገዛ ራሳችሁ ክብር፣ ለአካዳሚ ነፃነት፣ ለትውልድ ስትሉ በዚህ መመሪያ ላይ አምጹ! “እንቢ፣ አሻፈረን፣ በዚህ መመሪያ አንገዛም” በሉ! የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጎናችሁ ይቆማል» ሲል ነው፣ ግንቦት ሰባት ጥሪ ያስተላለፈው። ይህ የግንቦት ስባት መግለጫ […]

የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ማሩ ንግግር ተከትሎ የቆርጦ ቀጥል የፍረጃ ፖለቲካ አራማጆች እና ከሩቅ ሆኖ ድጋይ ለማቀበል የሚፈልጉ ኃይሎች ቁንፅል ነገር ይዘው በየአቅጣጫው በዱምዱም ጥፍራቸው አንድነት ፓርቲንም ደምረው መቧጠጥ ጀምረዋል ፡፡ ሆኖም አቶ ግርማ አሉ የተባሉትንና የመለሱትን ምላሽ እንዲሁም ከተቃወሟቸው ሰዎች መሃል ጥቂቱን ሰምቼአለሁ አንብቤያለሁ ፡፡ አልገባንም ምን ለማለት ተፈልጎ ነው ይብራራልን ማለት የአባት ሆኖ […]

የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደተለመደው በጸረ ሰላም እና በጸረ ሕዝብነት በጥብቅ ይፈረጃሉ::
Minilik Salsawi

የወያኔው ጁንታ ስልጣኑን እንዳያጣ እየተፈረካከሰ ባለበት በዚህ ወቅት መጪው ምርጫ ከመድረሱ በፊት አስፈላጊውን ከለላ ለማግኘት ለመከላከያ ለፖሊስ እና ለደህንነት ክፍሉ ምርጫውን ተገን በማድረግ እና በማሳበብ የስልጠና ሰነድ ይዞ በየክፍሉ ካድሬዎችን በማሰራጨት የፓርቲውን አስተሳሰብ ለመጫን ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል::

ስልጠናው ዋናው ነጥብ በመጭው ምርጫ ህዝባዊ አመጾች የነጻነት እና ይመብት ጥያቄዎች እንዳይይፈነዱ ስጋት ያለብት ወያኔ በሰራዊቱ እና ደህንነቱ ላይ ያለውን ጥርጣሬ ለመቅረፍ እና ለማሳመን ያዘጋጀው ሰነድ እንዲሁን በግሩፕ እየለየ ጠላቱን ለመልቀም ያመቸው ዘንድ ያዘጋጀው መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::

ምንጮቹ የስልጠናውን ሰነድ ጠቅሰው እንደተናገሩት በዋናነት በተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ላይ ያነጣጠረ ጥላቻ የተዘጋጀ ሲሆን እንደተለመደው በጸረ ሰላም እና በጸረ ህዝብነት ይፈረጃሉ::ድርጅቶቹ ለሃገር አደጋ እንደሆኑ እና ሰራዊቱን ሊበትኑ የተዘጋጁ እንደሆነ ታውቋል:: ምንጮቹ አክለው እንደተናገሩ በሃገር ቤት የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ሰራዊቱን ና የደህንነት ክፍሉን በመረጃ በዝርዝር ማስተማር አለባቸው:: ያሉ ሲሆን የሚያጉረመርሙ የሰራዊቱ እና ደህንነቱ ክፍሎች የለውጡ አካል እንዲሆኑ ከፖለቲካ ድርጅቶቹ ትልቅ ስራ ይጠበቃል ብለዋል::ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሰኝ አቀርባለሁ::

በምርጫ አለመሳተፍ መብት ነው !በኢትዮጵያ ያለው ጭላንጭል የፖለቲካ ምኅዳር ሲታይ፣ይህ ውሳኔ የሕግ፣የፖለቲካ እና የሞራል ድጋፍ አለው፡፡ሆኖም ግን በምርጫ ያለመሳተፍ መብት በራሱ-የራሱ የሆነ ተግዳሮቶች አሉትና፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የትርፍ-ኪሳራ ሥሌት የግላቸው ነው የሚሆነው፡፡
Yidnekachew Kebede
ይህ ጹሑፍ በምርጫ አለመሳተፍ መብት መሆኑን ከህግ አንፃር ለማየት እንጂ፣ የሚጪው አገረ አቀፍ ምርጫን አስመልክቶ “ኢሕአዴግ ለመርጫ አልተዘጋጀም !” እና “የ24 ሰዓት ተቃውሞ በአዲስ አበባ !” በሚል ዕርሶች ከዚህ በፌት በፃፍኳቸው ፁሑፍ የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ፣ ገዥው መንግስት ለነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ እራሱን አዘጋጅቶ፣ ውጤታማ ምርጫ ማካሄድ እንደማይቻል የግል እምነቴን ገልጫለው፡፡
ወደተነሳሁበት ዕርስ ስገባ፡- ማንኛውም ሰው በፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ እንዲሳተፉ አይገደድም፣ባለመሳተፉ ግን ተቃውሞን የመግለፅ እና ደግፋ የመስጠት መብት ይነፈጋል ማለት አይደለም ፡፡ይህም በመሆኑ የትኛውም የዲሞክራሲ ሥርዓት የተሟላ ተሳትፎ በህብረተሰብ ካልተደረገበት ውጤታማነቱ ደካማ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡የዲሞክራሲ ሥርዓት ማሳያ መስታዎት ከሆኑት ውስጥ አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃነት መንቀሳቀስ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ያለምንም ፍርሃት በፈለገው ወይም በፈለገችው ፓርቲ ውስጥ አባል የመሆን ዕድልና አማራጭ ማግኘት የግለሰብ መብት ነው፡፡ግለሰቦች በፈለጉት የፖለቲካ ፓርቲ የመደራጀት እና የመሳተፍ ነፃነት ሲኖራቸው ለዲሞክራሲ መሠረት ይሆናል፡፡
ይህ አይነቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት በአገራችን ምን ያኸል ተፈፃሚ ነው ? ተብሎ ቢጠየቅ ምላሹን ለማወቅ ብዙም አድካሚ አይደለም፡፡ውጤቱ አሉታዊ ነው፡፡እርግጥ ነው በሕገ መንግስት አንቀፅ 31 ማንኛውም ሰው ለማንኛውም ዓለማ በህግ “የመደራጀት” መብት እንዳለው በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ይሄን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ እና በክልል ደረጃ የተቋቋሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው የሚታወቅ ነው፡፡የእነዚህ ፓርቲዎች መብት እና ግዴታ እንዲሁም ሊከተሏቸው የሚገባ መርህዎች፣ በሕገ መንግስቱ፣በፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ አዋጁች እዲሁም በመተዳደሪያ ደንብቻው ብቻ ነው፡፡
በዚህም መሠረት ተቋቁመው እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአገራችን ቁጥራቸው በርካታ ቢሆንም፣ ቢሚፈለገው ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ግን በቁጥር አነስተኛ ፓርቲዎች ሲሆን፣ የተቀሩት የምርጫ መጣ ወይም የመግለጫ አሯሯጮች pacemaker መሆናቸው በግልፅ የሚታወቅ ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ዋንኛ ዓላማ በመርጫ ተወዳድረው በማሸነፍ የፓለቲካ ሥልጣን በመያዝ የቆሙለት ዓላማ በስልጣን ዘመን ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡
ምርጫ በዲሞክራሳዊ አካሄድ ለሚወከል መንግስት የጥንካሬ መለኪያ ነው፡፡ይህን ለማለት የሚያስችለው ተመራጮች መብታቸው እና ግዴታቸውን ሙሉ በሙሉ ከመራጩ ሕዝብ ስለሚያገኙት ነው፡፡እንዲ አይነቱ በሕዝብ ተሳትፎ ሥልጣን የሚቀየርበት ዋናው መንገድ ነፃና ሚዛናዊ የሆነ ምርጫ ሲደረግ ብቻ ነው፡፡ በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ በኢሕአዲግ/ በህወሐት መንግሰት የ24 ዓመት የስልጣን ዘመን በተደረጉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለመሆን አልቻለም፡፡ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በዋነኛነት የሥርዓቱ አስከፊ ድርጊት ቢሆንም፣ በተጨማሪ ጠንካራ የሆኑ በመላው ኢትዮጵያ የሕዝብ ድጋፍ ያለው የተቃዋሚ ፓርቲ አለመኖሩም ጭምር ነው፡፡ እርግጥ ነው በ1997 ዓ.ም በቅንጅት የታየው የተቃዋሚ ፓርቲዎች መነቃቃት፣ በአገራችን የዲሞክራሲ በዓል አንድ እርምጃ ወደፊት ከነበረበት ያንቀሳቀሰው ቢሆንም፣ በገዥው ሥርዓት ቀጥተኛ ተፅኖ፣ እንዲሁም በቅንጅት ፓርቲ ውስጥ በታየው ድክመት እና የስልጣን ሽኩቻ የለውጥ እንቅስቃሴውን ገትቶታል፡፡
አሁን ላይ በአገራችን የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ከበፊቱ “በቆምክበት እርገጥ” አይነት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተላቀው ምን ያህል “ወደፊት” እየሄዱ ነው የሚለውን ምላሽ ይህን ጹሑፍ ለሚያነቡ እና ለጉዳዩ ቅርብ ነኝ ለሚሉ ወገኖች የምተወው ሃሳብ ነው፡፡ ሆኖም ግን በአገር ውስጥ የሚንቀሣቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከ6 ወር በኋላ አገር አቀፍ ምርጫ ይጠብቃቸዋል፡፡ፓርቲዎች የምርጫ ፓርቲ ቢሆኑም ፣በምርጫ አለመሳተፍ መብታቸው በሕግ የተጠበቀ መሆኑን አውቀው ግራ ቀኛቸውን ቢመለከቱ፣ዝም ብሎ ገዥውን ፓርቲ በምርጫ ከማጀብ ይላቀቃሉ፤አሊያም በእኩል ተሳትፎ ወደ ምርጫው የሚገቡበትን መንገድ ተገዳድረው ማመቻቸት ይቻላል፡፡
የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ ቁ .573/2000 አንቀፅ 39 ቁ.2 ሐ.“ የፖለቲካ ፓርቲ ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን የጠቅላላ ወይም የአካባቢ ምርጫ ወድድርን ሳይሳተፍ የቀረ እንደሆነ ” ምርጫ ቦርድ በአዋጁ መሠረት ውሳኔ በማስተላለፍ ከመዝገብ ሊሰርዝ ይችላል፡፡የሚል የህግ ድንጋጌ አለ፣ይህን ድንጋጌ ከተነሳንበት ዓላማ ጋር በማገናኘት ምክንያት እና ውጤቱን መመልከት ተገቢ ነው፡፡
በመሠረቱ የፓርቲ ነፃነት በእንዲ መልኩ መገደብ አጠቃላይ የአዋጁ ችግር ዋንኛ ማሳያ ነው፡፡የትኛውም ፓርቲ በምርጫ የመሳተፍ ወይም ያለመሳተፍ መብት ካለጊዜ ገደብ ለራሱ ለፓርቲ የሚተው ስራ እንጂ ፣በህግ ገደብ የተጣለበት መሆን የለበትም፡፡ይህን ለማለት የሚያስደፍረው የግል እንዲሁም የጋራ መብት የሚጋፋ በመሆኑ ነው፡፡ለዚህም ማሳያ የመምረጥ እና ያለመምረጥ መብት የተጠበቀ ነው፡፡ ለምሳሌ እኔ በመጪው ምርጫ አልመርጥም ፣አልመረጥም ይህ በህግ ክልከላ ተደርጎብኝ ሳይሆን የእኔ መብት በመሆኑ ነው፡፡ልክ እንደኔ የግል መብት ያላቸው ሰዎች ተሰባበስበን የጋራ መብታችን ለማቋቋም በምንቀሳቀስበት ወቅት በግሌ ማድረግ የምችለውን በጋራ እንደማጣት ይቆጠራል፡፡ከዚህ አንፃር ይህ ድንጋጌ በእኔ እይታ ተገቢ መስሎ አይታየኝም፡፡
አሁን ባለው ነባራዊ ሃቅ በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የሚተዳደሩት በዚህ አዋጅ ነው፡፡በመሆኑም አዋጆን መሠረት በማድገረግ በምርጫ አለመሳተፍ ገደብ ቢኖረውም ለፓርቲዎች የተሰጠ መብት አለ፡፡ ማንኛው ፓርቲ ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን ሳይሳተፍ የቀረ እንደሆነ ይሰረዛል፡-ይህ ማላት፣በ2002 አገር አቀፍ ምርጫ በማንኛውም ምክንያት በምርጫ ያልተሳተፈ “ሀ” የተባለ ፓርቲ በ2007 የማይሳተፍ ከሆነ ይሰረዛል ማለት ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ይሄ “ሀ” የተባለው ፓርቲ በ1997 ምርጫ አልተሳተፈም ብንል ፣በ2002 ተሳትፏል ካልን በ2007 ምርጫ አለመሳተፍ የ”ሀ”ፓርቲ መብት ነው፡፡ይህም በማድረጉ ከምርጫ ቦርድ ምን አይነት ጥያቄ ለዚህ ፓርቲ አይቀርብም፡፡በዚህ መሠረት ፓርቲዎች ለሁለት ተከታታይ የምርጫ ዘመን በምርጫ ካተሳተፉ የመሰረዝ እጣቸው በእጃቸው ነው፡፡ሆኖም ግን የምርጫ ዘሙኑ ተከታታይነት ሳይኖረው በምርጫ አለመሳተፍ በአዋጁ መሠረት የሚያስከትለው ውጤት አይኖረውም፡፡
ይህ ከላይ የቀረበው ማሣያ፣ ለአገር አቀፍ እንዲሁም ለአካባቢ ምርጫ የሚያገለግል ነው፡፡በአሁን ወቅት ሁለቱ ምርጫዎች በተመሳሳይ የምርጫ ዘምን ባለመካሄዳቸው እረሳቸውን ችለው የሚቆጠሩ የምርጫ ዘመን ነው፡፡በኢትዮጵያ አሁን ባለው የምርጫ ስርዓት ፣የአንድ የምርጫ ዘመን አምስት ዓመት ነው፡፡ስለዚህም በአገር አቀፍ እና በአካባቢ የምርጫ ዘመን የ2 ዓመት ልዩነት አለ ማለት ነው፡፡በመሆኑም በዘንድሮ የአገር አቀፍ ምርጫ ዘመን ከባለፈው ሁለት ዓመት ከተካሄደው የአካባቢ ምርጫ ዘመን ፈፅሞ የሚገኛኝ አይደለም፡፡
በሕገ መንግሥት አንቀፅ 38 ቁ.1 ሐ.“ በማናቸውም ደረጃ በሚካሄዱ ምርጫ፣የመምረጥ እና የመመረጥ ፣ምርጫው ሁሉ አቀፍ፣በእኩልነት ላይ የተመሰረት እና መራጩ ፈቃዱን በነጻነት የሚገልፅበት ዋስትና የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡”በማለት የህጎች ሁሉ የበላይ ሕግ በሆነው ሕገ መንግሰት በግልፅ ተቀምጧል፡፡
ሆኖም በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ሕገ መንግስቱን መሰረት ያደረገ ምርጫ ስለመካሄዱ አጠራጣሪለው የሚል ፓርቲ፣እንዲሁም ምርጫው ከመካሄዱ በፌት በምርጫው ሄደት ላይ ቅደመ ሁኔታ እስካልሟላለት ድረስ የታሰበው ምርጫ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ አይደለም በማለት ከበቂ ምክንያቶች ጋር በማዛመድ ከላይ በተገለፀው የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ መሰረት፣ በምርጫ ያለመሳተፍ መብት በሕግ ድጋፍ ያላው መብት ነው፡፡
ይህ መብት ከሕገ መንግሰቱ እና ከላይ በተገለፀው አዋጅ የመነጨ ሲሆን፣ ከዚህ ውጪ ያሉ ማናቸውም አሰራሮች፣ልማዳች እንዲሁም መመሪያ ይህን መብት የሚጋፉ መሆን እንደሌለባቸው የታወቀ ነው፡፡እናም ፓርቲዎች ሁሌም የፖለቲካ ምኅዳሩ ተዘግቷል፣ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ አልቻልንም፣መሰብሰቢያ አዳራሽ ተከለከልን……..ወዘተ እያሉ ከሚናገሩ፣ምኅዳሩ እንዲሰፋ ከገዥው ፓርቲ ጋር በመነጋገር ማስተካከል ካልተቻለ፣በጊዜ ከምርጫው ታቅበው ገዥው ፓርቲ እራሱ ደግሶ እራሱ ለብቻው ይስተናገድበት ዘንድ በመተው እውነታውን ለህዝብና ለዓለም ቁልጭ አድርጎ ማሳየት ነው፡፡እስከ መቼ በምርጫ መጭበርበር !
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !