የ«ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል» ወቀሳ

«ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል» በመባል የሚታወቀው፣ በዓለም ዙሪያ ለነባር ህዝቦች ኅልውና የሚታገለው ድርጅት የጀርመን መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ስለኦሞ ሸለቆ ጉዳይ እንዲያነሱ አሳሰበ። ድርጅቱ በኦሞ ሸለቆ «የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተከሰተ ነው፤ ጀርመንም ሆነች ሌሎች የአውሮጳ ሃገራት የመብት ጥሰቱን አይተው እንዳላዩ ሆነዋል» ብሏል።