መስታወት ራሱን አያይም ! ቀልዶ-አደር ክበበው ገዳና
ሜሮን ጌትነት ፤
አበበ ተካ ፤

ይህን ፅሁፍ እንድፅፍ ያነሳሳኝ በቅርቡ በሁሉም ዌብ- ሳይቶች ላይ ማለት ይቻላል ፣ የወጣ አንድ የአድናቆት ፅሁፍ ነው ። ጽሁፉ አንዲት ገጣሚትን ለማድነቅ የተፃፈ ነው ። የፅሁፉ ርእስ “ሐገሬ ፤ ሕዝቤ ፤ ክብሬ ” የሚል ሲሆን በእንግሊዝኛ እንዲህ ተተርጉሟል ፤ “My Country, My People, My Honor” :: ይህ የአድናቆት ፅሁፍ የሚያጠነጥነው ፤ ሚሮን ጌትነት በምትባል ኢትዮጵያዊት ዘመናዊ የፊልም ተዋናይ ችሎታና
በግጥሙ ታክኮ ለሃገሯ ያላት ልዩ ፍቅር ላይ ነው ።
ፅሁፉ ገና ሲጀምር ነው “The poet-artist with an “unconquerable soul?” በማለት ተዋናዩዋን ማንቆለጳጰስ የሚጀምረው ። ፀሃፊዋና አድናቂዋ ደግሞ በእንግሊዝኛ መፃፍ የሚቀናቸው አል ማርያም ናቸው ። እናም አል ማርያም ናቸው ከላይ እንደጠቀስኩት በሁሉም ዌብ ሳይቶች ላይ አድናቆታቸውን የናኙት ። የግል አድናቆታቸውን ትክክል ነው አይደለም የሚል ክርክር ወስጥ አልገባም ። ከዚህ በፊትም ይህቺው ሜሮን ጌትነት የተባለች ተዋናይ የተሳተፈችበትን “ድፍረት” የሚል ፊልምን ክሊፕ አይቼ በጣም ተደነቅኩባት ብለው አሞካሽተዋት ነበር ። ካለፈው ሙገሳቸው ላይ እንዲህ ሲሉ በመጨረሻ ባወጡት ፅሁፍ ላይም ቀንጭበው አስቀምጠዋል ፡፤

“… The beautiful young actress Meron Getnet sat stunned and speechless. She is visibly shocked and confused. She looked around in total disbelief trying to get someone to tell her what she has just heard is not true… In her seat, Meron clasps her palms in the traditional praying position as if to implore God’s intervention to save her and her country from such cruel public humiliation. An unidentified interviewer asks her how she feels. (How does one really feel when one’s heart is yanked out before the entire world!?) Meron is visibly brokenhearted. But she puts on a calm and brave face. She is struggling to hide her outrage and fury. She is fighting tears; but she does not breakdown though she is manifestly broken-hearted…”

እንዲህ ይተረጎማል ።

“…..ውቢቱ ወጣት ተዋናይ ሜሮን ጌትነት ፍዝዝ ብላ በዝምታ ተቀምጣለች ፤ እንደሚታየው ደንግጣለች ግራ ተጋብታለችም ። የሰማችውን ነገር ማመን ስላቃታት ዙሪያዋን እየቃኘች እውነት አይደለም የሚላት ሰው ፈለገች…… እንደተቀመጠች ሜሮን የእጆቿን መዳፎች በተለመደው የፀሎት አይነት ገጥማ፤ እግዚአብሄር እሷንና አገሯን ከህዝባዊ ውርደት እንዲያድናቸው ጣልቃ ገብነቱን እንዲያሳያት ተመኘች ። ያልታወቀ ቃለ መጠይቅ አድራጊ ምን እንደሚሰማት ጠየቃት ። (አንድ ሰው በመላው አለም ፊት ልቡ ቡጥርቅ ብሎ ሲወጣ ምን ሊሰማው ይችላል ? ) ሜሮን ልቧ እንደተሰበረ ይታያል ። ሆኖም ግን መረጋጋትና ጀግንነት ይታይባታል ። ብስጭትና ንዴቷን ለመደበቅ ትታገላለች። እንቧዋ ይተናነቃታል ፤ ግን እንባዋ አልወረደም ይሁንና ልቧ የተሰበረ መሆኑ በግልፅ ይታይባታል…….”
የትርጉሙ መጨረሻ ።

አል ማርያም ይህን ከላይ የሰጡትን ሙገሳ ያደረጉት የፊልሙን ቅንጫቢ ብቻ አይተው ነው። ሙሉውን ገና አላዩትም ከፅሁፍዎ እንደተረዳሁት ። እንዴት ነው በቅንጫቢው ብቻ ይህን ያህል ሙገሳ ያፈሰሱላት ። በፊልሙ ውስጥስ ከሷ ሌላ ተዋናዮች አልነበሩም ፤ የነሱስ ሚና ምን ነበር ? ብየ ልጠይቅ እገደዳለሁ ፤ መቼም አንድ እጅ ብቻውን አያጨበጭብ ። እንደተመልካችና እንደ ውበቷ አድናቂ ቀደምብየ እንዳልኩት የተዋናይዋ የግል አድናቂዋ ከሆኑ የግል አመለካከትዎ ነውና ነውር የለበትም ። ፍቅር እንደ አፍቃሪው አይን ነው እንደሚባለው ፤ አድናቂም እንደዚያው ነው ። አድናቂና አፍቃሪ አለምንና ህይወትን እንደሚያይበት መነፅርም ይለያያል ።
“ድፍረት” የሚለውን ፊልም ወያኔ/ኢሕዲጎች እንዳይታይ ከለከሉ ። ይህ ዘረኛ አገዛዝ ይህን አደረገ ያን አደረገ ሲሉ የተቹት ግን አልገባኝም ። ፊልሙ ለመጀመሪያ ጊዜ ሊታይ ከነበረበት ቦታ በፖሊሶች መከልከሉ እሙን ነው ። የፊልሙ ዳይሬክተር ዘረሰናይ መሃሪ እንደተናገረው በፍርድ ቤት ፊልሙ ክስ አለበት ተብለን ነው እንዳይታይ የተደረገው ሲል በጊዜው ለገባው ታዳሚ ገልጿል ። ዘረሰናይን ለሚያውቀው ደሞ ከማንም በላይ ለወያኔው ስርአት የተሻለ ቀረቤታ አለው ። እኔ እዚህ ላይ አል ማርያም ወያኒያዊውን አገዛዝ አይተቹ አይንቀፉ የሚል ፍላጎት የለኝም ።
“ድፍረት” ፊልም ግን በታገደ ጥቂት ቀናት ውስጥ እንዲታይ ተፈቅዶ እየተየ ነው ። የፊልሙ ይዘትም ከወያኔ ስርአት ጋር ፖለቲካዊም ሆነ ማህበራዊ ተቃርኖ የለውም ። ወያኔ ለምን ሲል ያግደዋል ? የጠለፋ ጋብቻ ከወያኔያዊው ስርአት በፊትም ነበረ ፤ አሁንም አልፎ አልፎ ይኖራል ብዬ እገምታለሁ ። ይህው ሰሞኑን የሰማነው በታዳጊዋ በሃና ላላንጎ ላይ የተፈፀመ የደቦ አስገድዶ ድፍረት አንዱ ማሳያ ነው ። “ድፍረት” የሚለው ፊልም በራሱ እንዲያውም አገራችን ኢትዮጵያን በማስተዋወቅ ረገድ በጎ አስተወኦ አለው ብዬ አላምንም ። ይህ ራሱን የቻለ ሌላ ርእስ ስለሆነ በሌላ ጊዜ ልመለስበት እችላለሁ ።

አሁን ተመልሰን ወደ ተዋናይቷ ሜሮን ጌትነት እንምጣ ። የተዋናይነት ብቃቷንም ሆነ ገጣሚነቷ ላይ ዛሬ ልተች አልፈልግም ፤ የራሴ አስተያየት ቢኖረኝም ። አል ማርያም ሆይ የሚያደንቋትን የሜሮንን ግጥም እንደገና ያዳምጡና ወደራስዎ እንዲመለከቱ በዚህ አጋጣሚ ጋብዤዎታለሁ ።
“….መቼም የአሳ ዝላይ መልሶ ከውሃው ነው እመጣለሁ ዞሬ ፣ ስሜን ቀያይሬ ፣
ያኔ ይቀበለኛል ፤ ፍቅር ያጠግበኛል ህዝቤ ፤ አገሬ ፤ ክብሬ ፤”.. ….. ይላል አንዱ የገጣሚዋ ስንኝ ። አቶ አለማየሁ ገ/ማርያም የሚለው ስምዎን አል ማርያም ካሉት ጋር አይገጥም ይሆን ይህ ስንኝ ።
በተረፈ ሜሮን ጌትነት በወያኔው ቴሌቪዥን ላይ የወያኒው የልማት ፕሮግራም ውድድር አዘጋጅነቷንና አቅራቢነቷን ነው እኛ የምናውቀው ። “The poet-artist with an “unconquerable soul”? የሚለው ሙገሳዎ አለቦታው የገባ ነው ብየ እከራከርዎታለሁ ፤ የሜሮን ጌትነት ነፍሷ በወያኔ/ኢሓዲጎችconquer ከተደረገ ከረመ። እንዲያውም ሰሞኑን አሶሳ ወስጥ እየተደረገ ባለው የወያኔ ብሄር ብሄረሰቦች በአል ላይ ይመልከቷት፤ የህገ/መንግስቱ አወዳሽና ቀዳሽ አስተዋዋቂ ናት ። ይህ ከልክ ያለፈ ሙገሳዎ፤ ይህን እያወቁ ከሆነ እታዘብዎታለሁ ፤ ካላወቁ ደግሞ ይቅርታ አደርጋለሁ ። ወይም የፅሁፍዎ አቢይ አላማ ሜሮን ጌትነትን የማስተዋወቅ የPR ስራ ከሆነ ደግሞ ከጋራ አገራችን ፍቅርና ደህንነትና ጋር አይለውሱብኝ ። ኢትዮጵያንና ሚሮንን አንድ ላይ ሳይለውሱ ኢትዮጵያን ለቀቅ አድርገው ሜሮንን ጠበቅ ያድርጉ ። እዚህ ላይ እንዲታውቅልኝ የምፈልገው ነገር አለ ። ሜሮን ከወያኔ/ኢሕአዲግ ጋር ሰራች አልሰራች የራሷ ምርጫ ነው ፤ ስሪ ወይም አትስሪ ብዬ ልጫናት መብቱም ሆነ አቅሙ የለኝም ። አል ማርያም ሆይ ፤ እኔ የምመክረዎ ፤ መስታወት ራሱን አያይምና ዘውር ብለው እንደገና ያሞገሱላትን ግጥም “….ህዝቤ ፤ አገሬ ፤ ክብሬ …” የሚለውን ከራስዎ ጋር አያይዘው እንዲመለከቱ ነው ። ለዛሬው በሜሮን ጌትነት ላይ በዚሁ አበቃለሁ ። አስፈላጊ ሆኖ ካገኘሁት ደግሞ በግጥሙም ሆነ በተዋናይነት ብቃቷ ላይ እመለስበታለሁ ። ከዚያው ከሜሮን ጌትነት የግጥም ንባብ ላይ ለወደፊቱ ፅሁፌ ታግዘኝ ዘንድ አንድ ስንኝ ጥዬ ልለፍ ።

“……እድሜህን ቀርጥፈህ ብትሆን ባለ ዲግሪ ፣ ማስትሬት ዶክትሬት ብትደክም ብትለፋ ፤
እውነቱን ልንገርህ በሃገሬ ሂሳብ ፤ ከውጪ የመጣ የሶስት ወር ኮርስ ነው ሚዛን የሚደፋ ፡…….”

…………………………………………………….

ውድ አንባቢዬ ሆይ እንግዲህ ይህን አጋጣሚ አግኝቻለሁና አንዳንድ ተዋንያንና ድምፃውያን ላይ በየዌብ-ሳይቱ ተለጥፈው ካገኘኋቸው ዜናዎችና እኒም ከታዘብኳቸው ውስጥ ጥቂቶቹን ላጋራችሁ ።
ከጥቂት ወራት በፊት ነው አበበ ተካ የሚባል ነዋሪነቱን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገ ድምፃዊ ላይ “አበበ ተካ ለሴት ሲል አገሩን የከዳ ” በሚል ርእስ አንድ ዜና በተወሰኑ ዌብ-ሳይቶች ላይ ተሰራጭቶ ያየሁት ። ይህ አበበ ተካ የሚባል ድምፃዊ የምን አገር ዜጋ አግብቶ ነው ሙዚቃ ያስተወችው ? የሚል ጥርጣሬ ነው በውስጤ ያደረው ። ምክንያቱም በአበበ ተካና በአገሩ መካከል ያለውን ግንኙነት ፤( በአድናቂዎቹና በሱ መካከል እንዳለ ግንኙነት አድርጌ በመገመት) አበበ ተካም ሆነ ባለቤቱ ትዳራቸውን የሚወዱ ባልና ሚስት አድርጌ ገምቼም ነበር ። ለሚወዳት ባለቤቱ ሲል አንድ ያለችውን ሙያ ትቶ በፍቅር ተሰብስቦ የሚኖር ግለሰብ አድርጌ ገምቼውም ነበር ። ህይ ዜና በወጣ በጥቂት ወራት ውስጥ አበበ ተካን ባለቤቱ አስገድዶ ደፈረኝ ብላ ከሰሰችው የሚል ሌላ ዜና ደግሞ በነዚሁ ዌብ-ሳይቶች ላይ ብቅ አለ ። ምንድነው ነገሩ ! ያቺ ስሙ የጠፋላት ሚስቱ ነች ወይስ ስለሌላ አበበ ተካነው የምሰማው እያልኩ ሳስብ ፡ የአስገድዶ ደፈረኝ ክስ ተነስቶለት ልጆቹን የማየት እድል እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቀ ተባለ ። ከፍርድ ቤት ሲወጣ ፤ በዩ-ቲዩብ ላይ አጥር ያለች ቃለ መጠይቅ ቢጤ ሰጥቶ ስለነበር ያችኑ ሳዳምጥ አበበ ከባለቤቱ ጋር የነበረው አለመግባባት ስር የሰደደ እንደነበር በግልፅ ይታይ ነበር ፤ የወራት ሳይሆን አመታት የተቆጠሩበት አለመግባባትም ነበር ። ስለዚህ ከወራት በፊት አገሩን የከዳ ሲል የተጻፈው ዜና ከንቱና ባዶ ፈጠራ ሆኖ አገኘሁት ። እንግዲህ ጉዳዩ የቤተስብ ቢሆንም አንዴ አደባባይ ወጥቷል ፤ በዚህ ላይ አበበ ተካ Public Figure ታዋቂ ግለ-ሰብ ስለሆነ ነው እንጂ ብዙ አበሻ እሱን ከገጠመው በባሰ ሁኔታ ትዳሩ ተፈቷል ፤ መፋታት አዲስ አይደለም ለማለት ነው ። ይህንና ግን ባለቤቱ እንዲህ አደረገችው እንዲህ በደለችው እየተባለ ነው ወሬው የሚናፈሰው ።ስለዚህ የአንድ ወገን የአበበ ተካን ብሶት ብቻ ከመስማት የባለቤቱን ብሶትም መጠየቅ ተገቢ ነው። አለዚያ ለፍርድ አይመችም ።

……………………………………..

ሌላው ትዝብቴ ደግሞ ቀልዶ-አደሩን ክበበው ገዳን ይመለከታል ። ክበበው ገዳ ከኢትዮጵያ ቀልዶ-አደሮች ውስጥ ቁንጮ ነው ብየ ብናገር ማጋነን አይሆንም ። የቀልድ ስራዎቹ ላይ እንደማንኛው ሰው ችግሮች ሊታዩበት ይችላሉ ።
ተመልካችም በቀልደኛው ንግግር እየሳቀ ሲሰደብ እንኳን መሰደቡ አይገባውም ። ወይም እየገባው ያው የአበሻ ባህሪይ ሆኖበት ዝም ብሎ ያልፈዋል ። የአበሻ ባህሪይ ያልኩት አንድ የምናደንቀው ሰው ላይ ዛሬ የምናየውን ስህተት በይሉኝታ ፤ ወይም ይቅርታ እንድናደርግ ሳንጠየቅ በይቅርታ ፤ እናሳልፈውና ነገ በላያችን ላይ ሲጨፍርብን ፀጉራችንን መነጨት መጀመራችንን ነው ።
ዛሬ በሰለጠነው ዘመን ማንኛውም ሙያ በትምህርት ሲደገፍ ጥቀሜታ አለው ። ሁሉም የቁም ቀልዶ-አደር Stand-Up Comedian በአሜሪካም ቢሆን እንኳ ፤ የመድረክ ላይ ትምህርት አለው ማለት አይደለም ፤ ሆኖም ግን በሙያው የሰለጠኑ ባለሙያዎች ያማክሩታል ፤ ቀልዶቹን ይመርጡለታል ፡ቃላቱን ይቀርፁለተል ፤ መድረኩን ይመሩለታል ፤ ሰአቱን ያቅቡለታል ። በኛ ሃገር ግን ከፈረንጆቹ በተለይ ከአሜሪካ ሁሉንም ነገር እየኮረጅን መሟላት ከሚገባቸው ሁነታዎች አንዱን እንኳ ሳናሟላ የምንገባበት ሙያ ላይ ብዙ ስህተቶች ሲፈጠሩ እንመለከታለን ። ከነዚህ ሙያዎች ውስጥ የቁም-ቀልድ Stand-up comedy ሙያ አንዱ ነው ።

ሌላ ሌላውን እንተወውና ከአስኮራጃችን አሜሪካን ሃገር አንድ የቁም ቀልዶ-አደር ፤ ቢያንስ ፕሮግራሙን የሚመራለት ዳይሬክተር ብሎም አማካሪ ይፈልጋል ። እንደፈለገና አፉ እንዳመጣለት ያሻውን አይዘላብድም ። በተለይ ለተመልካቹ ያለው ክብር ከፍተኛ ነው ። ምክንያቱም ኑሮው የተመሰረተው እንጀራው የሚጋገረው በተመልካቹ ላይ ነውና ። ኒውዮርክ ሾው ላይ የነበረውን ተመልካቹን አትላንታ ሄዶ አይቀልድበትም ። በሌሎቹ የአውሮፓ አገሮችም እንደዚሁ ነው ።
ቀልዶ-አደር ክበበው ገዳ የታዳሚውን የልብ ትርታ ማዳመጥና አድናቂዎቹ መኖሪያቸው ኢትዮጵያም ይሁን አሜሪካ ፤ ካናዳም ይሁን ቻይና ማክበር ይገባዋል ። እንደ አለቅላቂ ሴት አንዱ አገር ሲሄድ ቀደም ብሎ የሄደበትን ከተማ ማንቋሸሽ ወይም መዝለፍ አይገባውም ። ይህን እንድል ያነሳሳኝ ክበበው ገዳ ከተወሰኑ አመታት በፊት ወደ ኮሎምበስ ኦሃዮ ብቅ ብሎ ነበር ። ከተመልካቹ መሃል ቀልዱ ያላስደሰተው አንድ ግለ-ሰብ ጋርም መጣላቱን ሰምቻለሁ ። ከዚያ ወደዋሽንግቶን ዲሲ ሲመለስ መድረክ ላይ ወጥቶ “ ኢትዮጵያ እያለሁ አገሬ መራቧን እሰማ ነበር ። አሁን ግን ኦሃዮ ደርሼ ከመጣሁ በኋላ አገሬ ለምን እንደተራበች ገባኝ ፤ ለካ ገበሬው ሁሉ ተሰብስቦ ኦሃዮ ገብቶ ነው ሲል ቀለደ ።” ዋሺንግቶን ዲሲም ኦሃዮ በብዛት የወልቃይት ፀገዴ ተወላጆች እንደሚኖሩበት በማውቅ ለቀልዶ-አደሩ ክበበው ገዳ ሳቀለት አስካካለት ።
የአንተን የቀልዶ-አደሩን ሆድ ለመሙላት ውልቃይት ፀገዴ ማረስ ነበረበት ? ቀልዶ-አደሩ ወንድሜ አገራችን ረሃብተኛ መባሏን ከሰማህና ገበሬው ሁሉ ኦሃዮ መመጣቱን ከተገነዘብክ ለምን ራስህ ገብተህ አታርስም ነበር ። በዚህ አጋጣሚ አገር የምትለማው በአርሶ አደሮች እንጂ በቀልዶ አደሮች እንዳልሆነ ልገልፅልህ እወዳለሁ ። ታዲያ ይህን አባባልህን ሳትወቀስበት በዋሽንግተን ተስቆልህ አለፍክ ።
ውድ አንባቢዬ ፤ አሁን በቅርቡ ደግሞ ይባስ ብሎ አውሮፓ አንድ የፋሽን ትርኢት ላይ እንደሟሟያ ሆኖ ቀርቦ ነበር ክበበው ገዳ ። የአዲስ አበባ ጆክ ነው ብሎ አንድ ቀልድ አወራ ። “ጎስቋላዎቹና ማዲያታሞቹ ሴቶች ሁሉ አሜሪካና ካናዳ ነው ያሉት” ሲል ቀለደ ። ጆኩ እንደጆክ ተወርቶ በዚያ ቢያበቃ መልካም ነበር ። “ለነገሩ እውነት ነው እኔ ዘወር ዘውር ብየ አይቻለሁ” ማንከሽከሻ ብቻ ናቸው ሲል አሾፈ ። ይህን አባባሉን ለመመልከት የሚቀጥለውን ሊንክ ይመልከቱhttps://www.youtube.com/watch?v=t0-qU60ik3E ።ወይም ክበበው ገዳ ብለው ጉግል ያድርጉና “ ቆንጆዋን እንካ ግን አትንካ ” የሚለውን ርዕስ ይጫኑ ።
ቀደም ብየ እንዳልኩት እንደ አለቅላቂ የመንደር ሴት የኦሃዮን ዲሲ የአሜሪካና ካናዳን አውሮፓ እየወሰደ ያለቀልቃል ። ቀልዶ አደሩ ወንድሜ ክበበው! እነዚህ ማንከሽከሻ ፤ ጎስቋላ፤ ያልካቸው የአሜሪካና የካናዳ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ሚስቶቻችንና እናቶቻችን ናቸው ። አዎ ማዲያታም ሊሆኑን ይችላሉ ሊጎሳቆሉም ይችላሉ ። አንተ ኢትዮጵያ ወስጥ ያውም አዲስ አበባ ብቻ እንደምታውቃቸው ፤ ምሽት-አደር ሴቶች ላይቆነጁ ይችላሉ ። ሰርተው ጥረው ግረው በላባቸው በወዛቸው የሚያድሩ ናቸውና ። በዚህ በፈጣኑ አለም ውስጥ ልጆች አሳድገው አስተምረው ትዳራቸውን ጠብቀው ከዚያም አልፈው ኢትዮጵያ ወስጥ ቤተ-ሰብና ዘመድ ረድተው የሚኖሩ ሴቶች ናቸው ፤ ቢጎሳቆሉ ይነሳቸው ፤ ማዲያት ቢወጣባቸው ይብዛባቸው ።
የአንተ የአዲስ አበባ ቆነጃጅት ሴቶች ለፀጉራቸው ሶስት ሰአት ፤ ለጥፍራቸው ሁለት ሰአት ለቅንድባቸው ሌላ ሁለት ሰአት ለማጥፋት በቂ ጊዜ ያላቸው ናቸው ፤ ምነው አይቆነጁ ። ስለዚህ ስትቀልድም የምትናገረውን እወቅ ። በአንድ አካባቢ በሚኖሩ ሰዎች ላይ ስትቀልድም እዚያው እፊታቸው ላይ ቀልድ ። አንዱን ካንዱ አታምታታ ። አንድ እውነታ ግን ልንገርህ ። ኦሃዮም ካናዳም ሆነ አሜሪካ አንተ መጣህባቸው እንጂ እነሱ አንተን ብለው አልመጡብህም ። ኦሃዮም ካናዳም አሜሪካም ያላንተ ኖረዋል መኖርም ይችላሉ ። አስር አመት ቀልደህ ከአዲስ አበባ ቆነጃጅት ሴቶች የማታገኘውን ገንዘብም በአንድ ትርኢት የምታገኘው ከነዚህ ማንከሽከሻዎች ፤ ማዲያታሞችና ባሎቻቸው ነው ። ዘወር ዘወር ብየ አለምን አይቻለሁ ብለሀናልና እግርህ ተፍታቶ ክንፍ አውጥተህ ዘወር ዘወር ያልከው ከነዚሁ ከማዲታሞቹ በተገኘ ገንዘብ እንደሆነ ልትረዳው ይገባል ። ይህ እውነት አይደለም እንዴ ወንድሜ? መቼም ቀልደኛ ነህና ፤ አይደለም ከአባቴ በወረስኩት ገንዘብ ነው ብለህ እንዳታስቀኝ ።

ውድ አንባቢየ ለዛሬው በዚሁ ላብቃ !

ከአንበሳው ይብራ

እ.ኤ.አ ዲሴምበር 2 2014


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
እነሆ ከተሚማ ጋር የጂማን ምድር “ሽርርርር” ልንልበት ነው፡፡ ሆኖም “ተሚማ” የትናንትናው ሙገሳ አንሶኛል ብላለች፡፡ “የነየታችሁት ሐጃ ሞልቶላችሁ በደስታ እንድትፍለቀለቁ ካሻችሁ ሙገሳውን ጨመርመር አድርጉልኝ” ትላለች፡፡ ታዲያ እኛም አላንገራገርንም፡፡ “ምን ገዶን! አንቺ ሰኚ ሞቲ! ሙገሳ በየዓይነቱ ይኸውልሽ” ብለን በድጋሚ መወድሳችንን ልንደረድርላት ተዘጋጅተናል፡፡ እንዲያውም ሙገሳችንን የምንጀምረው እሸትነቷን በማወደስ ነው፡፡ ለመወድሳችን የመረጥነውም የሟቹን የዮሴፍ ገመቹን ዜማ ነው፡፡ አዝማቹ እንዲህ ይሄዳል፡፡
Naale naale naalen irgixiidhaa
Maddiin furnoo hidhiin buskutiidha.
በአማርኛ ሲተረጎም እንዲህ ይሆናል (አማርኛው አዛማጅ ትርጉም በመሆኑ የኦሮምኛውን ያህል አስደሳች ላይሆን ይችላል)፡፡
ናሌ ናሌ ናሌ እርግጥ ነው፡፡
ጉንጯ ፉርኖ ከንፈሯም ብስኩት ነው፡፡
ፈገግ ያሰኛል አይደል? (ቂቂቂቂቂ….)፡፡ አዎን! በኦሮምኛ እንዲህ እያሉ መግጠምም ይቻላል፡፡ መወድሱ ከወገብ በታች ያለውን የሰውነት ክፍል አይንካ እንጂ ከወገብ በላይ ያለውን ውበት በሚያውቁት መንገድ ማወደስ ይቻላል፡፡ ከወገብ በታች ካለው የሰውነት ክፍልም ተረከዝን ማሞገስ ይቻላል፡፡ ከዚያ በላይ ያለውን ክፍል ግን መጥቀስ አይፈቀድም፡፡
ዮሴፍ በግጥሙ ውስጥ “ናሌ ናሌ..” የሚል ሐረግ ደጋግሟል አይደል? ቃሉ እንዲህ ሲደጋገም ትርኪ ምርኪ ሊመስል ይችላል፡፡ ነገር ግን ያለቦታው የገባ አይምሰላችሁ፡፡ ትናንትና የጠቀስነው “አህለን አህላ” ነው ተቀይሮ እንዲህ የሆነው፡፡ ዘፋኙ ዘፈኑን የሚጀምረው በዚህ ሐረግ ነው፡፡ ከዚያም እርሱ የዘፈኑን ግጥሞች እያከታተለ ሲጠራ ተቀባዮቹ “ናሌ ናሌ…” እያሉ ጨዋታውን ያደምቁለታል፡፡
*****
አሁን ደግሞ የአማርኛ ተናጋሪዎችን በመወከል ተሚማን እናሞግሳታለን፡፡ ለሙገሳችን የመረጥነውም የነዋይ ደበበን “ከጊቤ ባሻገር”ን ነው፡፡
ከጊቤ ባሻገር አለችኧረ አንዲት ሰው
በፍቅር በናፍቆትልቤን የምትወዘውዘው
አቦል ጀባብላኝ ቡናዋን ብቀምሰው፣
እግሬ ወደጅማ ሱስ አመላለሰው
እንግባ አይመሽምወይ
ቤትሽ ጅማ ነውወይ ?
ነዋይ እውነታውን ነው ቁጭ ያደረገው፡፡ “ተሚማ” ቄጤማ ጎዝጉዛ፣ ቡናውን አፍልታ ሐድራውን ሞቅ ሞቅ ስታደርገው ፍቅር የምትፈትል ነው የምትመስለው፡፡ ከሐድራው የሚፈልቀው ሙሐባ የቡና ሱስ ብቻ ሳይሆን የፍቅር ሱስን ያስይዛል፡፡
ደግሞ አንድ ነገር!! በሌሎች አካባቢዎች እንግዳን በእቅፍ አበባ ነው የሚቀበሉት አይደል?… የጅማዋ ተሚማ ደግሞ ለዚያራ የመጣውን ሰው በቡና ቀንበጥ ነው የምትቀበለው፡፡ እንዲህ ያለች ጥበበኛ አርቲስት ናት ተሚማ!
*****
ኧረ ለመሆኑ እኛ እንዲህ ያሞገስናት “ተሚማ” በርግጥ ፍቅርን ታውቀዋለች?… ምንም አትጠራጠሩ!! ተሚማ ፍቅርን ከማወቅም አልፋ ለፍቅር የምትንበረከክ ልበ-ንጹህ ናት፡፡ ከልቧ ለምታፈቅረው ሰው ፍቅሯን የምትገልጸው ደግሞ በጣም ኪነታዊ በሆነ መንገድ ነው፡፡ ይህም “ሂዲ ደርቡ” (Hiddii darbuu) ይባላል:: “ሂዲ ደርቡ” የኦሮሞ ሴቶች ለፍቅር መረታታቸውን የሚገልጹበት ወግ ነው፡፡ ይህም በአማርኛ “ሎሚ መወርወር” ከምንለው ወግ ጋር ይቀራረባል፡፡ ልዩነቱ ግን ተሚማ ፍቅሯን በምትገልጽበት ጊዜ የምትወረውረው ነገር “ሎሚ” ሳይሆን “እምቧይ” ነው፡፡ ሁለተኛው ልዩነት ደግሞ “ሂዲ ደርቡ” እንደ “ሎሚ መወርወር” በጥምቀት ብቻ የሚፈጸም አለመሆኑ ነው፡፡ ሶስተኛው ልዩነት ተሚማ እምቧዩን ሌሎች ሰዎች እያዩዋት የምትወረውር አለመሆኑ ነው፡፡ Safuu የሚባለው የኦሮሞ የስነ-ምግባር ደንብ ይህንን እንዳታደርግ ያግዳታል፡፡ በመሆኑም ተሚማ የወደደችውን ሰው በእምቧይ የምትመታው ሰው በሌለበት ስፍራ ነው (በነገራችን ላይ አንዲት ሴት ወንዱን መውደዷን የምትገልጽበት ይህ የ“ሂዲ ደርቡ” ወግ በሀረርጌና በአርሲም ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በአርሲና በሀረርጌ “ሂዲ ደርቡ” አይባልም፡፡ እዚያ ዘንድ “አሴና” ወይንም “አሼና” እየተባለ ነው የሚጠራው፤ በተጨማሪም የሀረርጌና የአርሲ ኮረዶች ፍቅራቸውን የሚገልጹት በብዙ እምቧዮች ነው፤ ወንድዬው ጠዋት ከቤቱ ሊወጣ ሲል ሴቲቷ በአጥር ላይ ተንጠልጥላ ብዙ እምቧዮችን ከፊቱ ትበትንና ወደ ቤቷ ትነጉዳለች፤ ወንድዬውምም ጉዳዩን ለወላጆቹ ይነግርና ልጅቷን ያገባታል)፡፡

በ“ሂዲ ደርቡ” እና “በሎሚ መወርወር” መካከል ያለው ትልቁ ልዩነት ግን ከላይ ከተገለጹት ውስጥ የለም፡፡ ትልቁ ልዩነት ወዲህ ነው ያለው፡፡ እንደሚታወቀው “ሎሚ መወርወር” በወንድ የሚፈጸም ወግ ነው፡፡ ሴቲቷ ሎሚውን አትወርውርም (ምንም እንኳ ያቺ ጭራ ቀረሽ የሚሏት ዘነበች ታደሰ “ሎሚ ብወረውር” እያለች ብትዘፍንም ሴቶች ሎሚ ሲወረውሩ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም)፡፡ የጅማዋ ተሚማ የምትፈጽመው “ሂዲ ደርቡ” ግን በራሷ የሚፈጸም እንጂ በወንድ የሚፈጸምላት አይደለም፡፡ ወንድዬው ፍቅሩን የሚገልጸው ነጠላ ገዝቶ በማልበስ ነው እንጂ እምቧይ በመወርወር አይደለም፡፡
ታዲያ ተሚማ የምትወደውን ሰው በእምቧይ የመምታቷን ጀብድ ስትገለጸው ሰምታችኋት ታውቃላችሁ?… ካላወቃችሁ “ፌይሩዝ” የተባለች ወጣት ያዜመችውን በትንሹ ቀንጨብ አድርገን እናሳያችሁ (ከፌይሩዝ የተዋስነው አባባል ለተሚማም ይሆናል)፡፡
Akkasumaan hiddii darbannaanii (ለዚያው ነው እምቧይ መወርወሬ)
Sijaaladhe giddiin naqbnaanii (ግድ ብሎኝ ነው አንተን አፍቅሬ)
ተሚማ! ጉብሊቷ ወጣት የጅማ!! ስትወደን እንዲህ ነው የምትለን፡፡ ለፍቅር መረታቷን እንዲህ ነው የምታስረግጠው፡፡ ፍቅሯ ሲባባስባት ደግሞ በጣፋጭ አንደበቷ እየዘማመረች ልባችንን ልታፈርሰው ትችላለች፡፡ እንዲያውም ታዋቂዋ የጅማ ተወላጅ አርቲስት ሲቲና አባዱላ “ቡርቱካኒ” ብላ ያዜመችው ዝነኛ ዘፈን ተሚማ በፍቅር በምትጨነቅበት ጊዜ የምትቀኘውን እንጉርጉሮ ሊወክል ይችላል፡፡ እስቲ ደግሞ የሲቲናን ዘፈን እንዋስና የተሚማን የፍቅር ብሶት እንግለጽ፡፡
Burtukaani mitii hadhaadha miti hadahaadha (ብርቱካን አይደለም ይህስ መራራ ነው)
Kun jaalalaa miti maraachaadha (ፍቅርስ አይደለም ይህስ እብደት ነው)
እጥር ምጥን ቅልብጭ ያለች ግጥም፡፡ የፍቅር ፍላጻ ልቧን ወግቶ ህመሙ በሚያስጨንቃት ጊዜ ነው እንዲህ ብላ የምታዜመው ተሚማ! ያቺ ውብ ቄጤማ! የአባጅፋር ልጅ የጅማ!!
*****
ብራቮ! ብራቮ! ተሚማ ሙገሳችንንና መወድሳችን ከልብ የፈለቀ መሆኑ ስለገባት በጅማ ምድር ልታንሸራሽረን የገባችውን ቃል በድጋሚ አድሳለች፡፡ በመሆኑም ጅማን ልናስሳት ነው፡፡ በአሰሳችን ድብርት ቢገጥመን ተሚማ በጣፋጭ አንደበቷ “Hin mukaayinaa” እያለች  ታባርረዋለች (Hin mukaayinaa ብዬ ስጽፍ ሳቅኩኝ….ቂቂቂቂቂቂ… ቢሆንም በጣም ደስ እያለኝ ነው የምስቀው… እንደ ሐላዋ በሚጣፍጥ አባባል ድብርትን ማባረር ይሏል ይሄ ነው… Hin mukaayinaa)
“Hin mukaayinaa” ምን ዐይነት ትርጉም እንዳለው አውቃችኋልን?…. “እንጨት አትሁኑ” ማለት እኮ ነው፡፡ ከሩቅ ሀገር ሊገበኘን የመጣ ሰው እንግድነት እንዳይሰማው ለማድረግ ከፈለግን “አትቦዝን” እንለዋን አይደል?… አዎን! በፈረንጅኛውም “Just feel at home” ለማለት ይቻላል፡፡ የጅማዋ ተሚማ ግን “Hin mukaayin” ማለትም “እንጨት አትሁን” ነው የምትለው፡፡ ተሚማ የምትጠቀምበት Hin mukaayinaa ውስጠ ወይራ ፍቺን ያዘለ ሐረግ ነው፡፡ “ማዕና”ውም እንዲህ ሊሆን ይችላል፡፡
   እንግድነት የሚሰማው ሰው ዝምታ ያበዛል፡፡ ከሰዎች መሃል የወጣ ይመስለዋል፡፡ ይህም በመንገድ ላይ ለብቻው ከቆመ ዛፍ ወይንም የኤሌክትሪክ እንጨት ጋር ያመሳስለዋል፡፡ እርሱን የተጫጫነው ስሜትም በኛ ላይ የድብርት መአት ሊጠራብን ይችላል፡፡ እንግዲህ ሰውዬው እንግድነት ተሰምቶት እንደ እንጨት ድርቅ ብሎ ድብርት እንዳይጠራብን ለማድረግ በሚል ነው ተሚማ Hin mukaayin” የምትለው፡፡ ደስ ሲል!!
Hin mukaayinaa” እንዳለችው ተሚማ እኛም “ሂንሙካይና ጋ ማሎ” እንላችኋለን!!
(ይቀጥላል)
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 22/2007
ሀረር… ምስራቅ ኢትዮጵያ
—–
The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of ethnography and history with special focus on Eastern Ethiopia.  You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.

ዛሬ ከስዓት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀብታሙ አያሌውን ቂሊንጦ ወደሚገኘው ወህኒ ቤት ሄጄ ለማየት ከባለቤቱ ቤቲ ጋር ቂሊንጡ ተገኝቼ ነበር፡፡ እግረ መንገዴንም ባለፈው ተመስገን ደሳለኝን ለመጠየቅ ሄጄ የጠፋብኝን ስዓት ካገኘሁት የሚል ተሰፋ ነበር፡፡ የሰዓቱ ነገር … ውሃ የበላው መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ አርድቻችሁ ልለፍ ብዬ ነው፡፡ ነገሩ ትልቅ ጉዳይ ሆኖ ሳይሆን የተረሳ ንብረትም ሆነ በፖሊስ እጅ ድንገት […]

ምንም እንኳን የፖለቲካ ምህዳሩ የጠበበ ብቻ ሳይሆን የተዘጋ ቢሆንም፣ የአንድነት ፓርቲ በምርጫ 2007 እንደሚወዳደር በይፋ ለሕዝብ ማሳወቁ ይታወቃል። አንዳንድ ወገኖች “አንድነት እንዴት ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ ምርጫ ይገባል ?” የሚል ጥያቄ ያቀርባሉ። እነዚህ ወገኖች ይሄን ጥያቄ ለምን እንዳቀረቡ ግልጽ ቢሆንም፣ ወድ ምርጫው አለመግባቱ ደግሞ ሊያስከትል የሚችለው የራሱ ጉዳት እንደሚኖር የመረዳት ችግር ያለ ይመስላል። በተለይም በፖለኢትካው […]

የአንድነት ለፍትህና ዲሞክራሲ (አንድነት) አባል ወጣት ሽሻይ አዘናው ለ24 ቀን መሰወሩ ተያይዞ በ26/02/2007ዓ.ም ከሚሰራበት የስራ ቦታው ታፍኖ በመቐለ ኮሙሽን ፖሊስ ክልል ትግራይ ልዩና ፅኑ እስርቤት ታስሮ ህገ መንግስታዊን መብቱ በመከልከል ጠበቃ እንዳያአማክረው ምግብ እንዳይገባለት ፡ ዘሞዶቹና ጓደኞቹ እንዳያዩት ተነፍጎት 12 ቀን ያህል በህቡእ ታሰሮበት ከነበረበት ተሰውሮ እስከ 18/03/2007ዓ.ም በጠቅላላ ለ24 ቀን በመሰወሩ መጀመርያ ከሰራ ቦታው […]

ኀዳር ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል መንግስቱ የ2006 የጸጥታ አጠባበቅ ግምገማ በሚያደርግበት ስብሰባ ላይ እንደተገለጸው በአዲስ አበባ 7ቱም የሃይማኖት ተቋማት ከመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ጋር በጋራ በመቀናጀት የደህንነት ስራ እየሰሩ ነው። አጠቃላይ ውይይቱን በተመለከተ ለኢሳት የደረሰው ሚስጥራዊ የድምጽ መረጃ እንደሚያስረዳው በአዲስ አበባ በተቋቋመው መዋቅር ውስጥ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች የሚገኙበት ሲሆን፣ መንግስት መኪና፣ ኮምፒዩተር፣ …

ኀዳር ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ትብብሩ ህዳር 27 እና 28 በመስቀል አደባባይ ለሚደረገው የአንድ ቀንና ሌሊት የተቃውሞ ሰልፍ ህዝቡ የተጀመረውን የሰው በሰው ቅስቀሳ እንዲደግፍ፣ የገንዘብ የሞራልና ቁሳቁስ ድጋፎችን እንዲያደርግ እንዲሁም ለትግሉ ይጠቅማል ያሉትን ሁሉ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቋል። ህዝቡ በዝግጅቱ ከሚያደርገው ድጋፍ ባሻገር በመስቀል አደባባይ በሚኖረው ቆይታ የሚያስልጉት ቁሳቁሶች በተለይም ደረቅ ምግብና ውሃ …

ኀዳር ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ2003 ዓ.ም ወዲህ በተከሰተ አደጋ በክልሉ 18ሺ 994 የመኪና አደጋዎች ተከሰተዋል፡፡ በትራፊክ ሳምንት ውይይት ላይ እንደተገለፀው በአጠቃላይ በአምስት አመታት በተከሰተው አደጋ 6ሺ 668 ሰዎች ህይዋታቸውን አጠዋል፡፡ 6ሺህ 581 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ፤ 11 ሺ 781 ሰዎች ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ሲደርስባቸው  994 ሚልዮን 626 ሺህ 866 …

ኀዳር ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ አገሪቱ ከግል የገንዘብ ተቋማት ለመበደር መወሰኑዋን ተከትሎ የኢትዮጵያን ብድር በበላይነት በሚያስተባብረው በጀርመን ትልቁ ባንክ አማካኝነት በተዘጋጀ ዝግጅት ላይ ይገኛሉ ተብሎአል። ኢትዮጵያ ከአለማቀፍ ገንዘብ ተቋማት ለመበደር መወሰኑዋ ብዙ ኢኮኖሚስቶችን እያነጋገረ ነው። ጠ/ሚኒስትሩ ከጀርመን ቻንስለር አንግላ መርክል ጋር እንደሚነጋገሩም ታውቋል። አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ማዳበሪያ ከሚያቀርብ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም የሚመራዉ ቡድን የጀርመንኗን መራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክልን ጨምሮ የተለያዩ የጀርመን ባለሥልጣናትንና ባለሐብቶችን ለማነጋገር ቀጠሮ አለዉ።ጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን፤ የኢትዮጵያ ወዳጆችና የሠብአዊ መብት ተሟጋቾች ባንፃሩ እዚያዉ በርሊን ዉስጥ ተቃዉሞ ሠልፍ ለማድረግ አቅደዋል።

በቱርክ የሶስት ቀናት ጉብኝትን ያደረጉት የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ርእሰ ሊቃነ-ጳጳሳት ፍራንሲስ በጉብኝታቸዉ ማጠቃለያ በተደረገዉ የመሰናበቻ ዝግጅት ከኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ በርተለሜዎስ ጋር የሐዋርያዉን ቅዱስ አንድርያስ ዕለተ ሞት በልዩ መንፈሳዊ ሥነ-ስርዓት አስበዋል።

በሶስት የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት የተዛመተዉ ኢቦላ 6000 ገደማ ሰው ገልዋል። ወደ 16 ሺህ ህዝብ ደሞ በተውሓሲው ተለክፎአል። የኢቦላ ወረርሺኝ ያደረሰዉ ቀዉስ ከቁጥጥር ዉጭ የሚወጣበት ደረጃ መድረሱ እየተነገረ ነዉ። የኤቦላ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገዉ ጥረትና ትብብር ጀርመን የምታደርገዉ ርዳታ ሳይዘገይ እየተነገረ ነዉ።

የዱሮ ወዳጄ ሰላምታዬ ይድረሽ። እንደምታውቂው ከተያየን ከሁለት አስርት አመታት በላይ ሆኗል። እኔም ካገሬ ከወጣሁ 21 ዓመት አለፈኝ። በጤናና በምቾት እንደምትኖሪ እሰማለሁ። እግዚአብሄርም መንግስትም ጥሩውን ነገር ሁሉ አብዝቶ እንዲሰጥሽ ምኞቴ ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጓደኝነት ከምቀርባቸውና ከማከብራቸው ስዎች ውስጥ አንቺ አንዷ እንደነበርሽ ራስሽም ብዙ ሰዎችም ያውቃሉ። ከጊዜ ብዛትና በስልጣንም ርቀት ምክንያት ጓደኝነቴን ብትረሽውም አልፈርድብሽም። እኔ ግን […]

የሶማልያዉ አክራሪ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን የአሸባብ ታጣቂዎች ኬንያ ዉስጥ ሰላሳ ስድስት ድንጋይ አዉጪዎችን ገደሉ። ታጣቂዎቹ በሰሜናዊ ምስራቅ ኬንያ ማንዴራ ከተማ አጠገብ ዛሬ ሲነጋጋ በከፈቱት ጥቃት የገደሏቸዉ አብዛኞቹ ሰዎች የቀን ሰራተኞችን ነበሩ።

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የኮምቦልቻ ከተማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በ07 ቀበሌ ልዩ ስሙ ትዩ አምባ የሚኖሩ አርሶ አደሮች ላይ በቱርካውያን የባቡር መስመር ዝርጋታ ካምፓኒ የደረሰውን የአዝእርት ጭፍጨፋ በአካል በመሄድ የመስክ ግምገማና ምልከታ እንዲሁም ከአርሶ አደሮች ጋር ውይይት ማካሄዱን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ ፡፡ ለዝግጅት ክፍላችን በደረሰው መረጃ መሰረት ህዳር 21 ቀን […]

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ ዕለታዊ መግለጫ

ዝግጅታችን ተጠናክሮ ቀጥሏል! እርስዎም ይዘጋጁ!
‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል የአንድ ወር መርሃ ግብር ከጀመርንበት ጊዜ አንስቶ ስርዓቱ መርሃግብሮቻችን በማጨናገፍ ለነጻነት የምናደርገውን የትግል ጉዞ ለማደናቀፍ ሌት ተቀን እየሰራ ይገኛል፡፡ ሆኖም የነጻነት ትግሉ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚያስከፍል መሆኑን የተረዳው ትብብሩ ለገዥው ፓርቲ አፈና ሳይንበረከክ ስራውን ቀጥሏል፡፡ በተለይ ከመርሃ ግብሮቻችን መካከል ስርዓቱን ያስፈራውን የ24 ሰዓት የአደር ሰልፍ ለማድረግ ዝግጅታችን አጠናክረን ቀጥለናል፡፡ ለዚህ የአዳር ሰልፍ የትብብሩ አባል ፓርቲዎች ሰው በሰው በመቀስቀስ፣ ወረቀት በመበተን እንዲሁም በየ ፓርቲዎቻችን ስም የታተሙ ቲሸርቶችን በመልበስ ህዝቡን እያነቃቃን እንገኛለን፡፡ ሰልፉ እስከሚደረግበት ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም ድረስም ዝግጅታችን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡

ይህን መርሃ ግብር ስንነድፍ ለነጻነት የሚከፈለው መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተንና የቀድሞ አባቶቻችን ካሳዩት ቆራጥነት ተምረን ነው፡፡ በዚህ ለቀጣይ የትግል ጉዞአችን ጭላንጭል ለምናይበት መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎናችን እንዲቆም ጥሪ እናደርጋለን፡፡ በውጭም ሆነ አገር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለነጻነት ለምናደርገው ጉዞ የጀመርነውን የሰው በሰው ቅስቀሳ በመደገፍ፣ በገንዘብ፣ በሞራልና በሌሎች ለመርሃ ግብሩና ለአጠቃላይ ትግሉ ይጠቅማል ባሉት መንገድ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ መርሃ ግብሩ ከጀመረ ጊዜ አንስቶ በሞራልና በተለያየ መንገድ መልዕክቶቻችን ለህዝብ እንዲደርሱ ድጋፍ ያደረጋችሁልን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ልባዊ ምስጋናችን ማቅረብ እንፈልጋለን፡፡ አሁንም ድጋፋችሁን አጠናክራችሁ በመቀጠል ታሪካዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን፡፡

በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በኩል ለሰላማዊ ሰልፉ የሚያስፈልገው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ህዝቡ በዝግጅቱ ከሚያደርገው ድጋፍ ባሻገር በመስቀል አደባባይ በሚኖረን ቆይታ የሚያስልጉት ቁሳቁሶች በተለይም ደረቅ ምግብና ውሃ ከአሁኑ እንዲያዘጋጅ ማስታወስ እንፈልጋለን፡፡ ህዳር 27/28 2007 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚደረገው የ24 (አዳር) ሰልፍ ኢትዮጵያውያን ላይ የተጫነውን የፍርሃት ድባብ በመስበር ለነጻነት የምናደርገው ወሳኝ ጉዞ ጅማሬ በመሆኑ በሁሉም የማህረሰብ ክፍል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ራሳቸውንና አገራቸውን ነጻ ለማውጣት የትግሉ አካል እንዲሆኑ ጥሪያችን እያቀርባለን፡፡

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

ህዳር 23/2007 ዓ.ም

አዲስ አበባ


እኔና ባለቤቴ ልክ እንዳንቺ ሆነን ነበር፡፡ ነገራችን ሁሉ ችኮ ሆኖ፡፡ ያ ድሮ እንደ መልካም ሙዚቃ ጆሮሽን አዘንብለሽ የምትሰሚው የባልሽ ድምጽ ፍሬን እንደያዘ መኪና ድምጽ ሲሆንብሽ ይሰማሻል፡፡ ይናፍቅሽ የነበረው ድምጽ ሲደውል ሐሳብ ውስጥ ይጥልሻል፡፡ ደግሞ ምን ሊል ይሆን? ትያለሽ፡፡ ስልክ ከማንሳት ይልቅ ስልኩን ለመዝጋት ትቸኩያለሽ፡፡ ለመሆኑ ባል ማለት ምንድን ነው? ለእኔ ከባልሽ ጋር ብቻ የምታደርጊያቸው ነገሮች ስላሉ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር ብቻ የምትቀልጃቸው፣ ከእርሱ ጋር ብቻ የምታወሪያቸው፣ ከእርሱ ጋር ብቻ የምትሠሪያቸው፣ ከእርሱ ጋር ብቻ የምትወስኛቸው፣ ከእርሱ ጋር ብቻ የምትባልጊያቸው፣ ከእርሱ ጋር ብቻ የምታኮርፊያቸው፡፡

ለአንቺ ብቻ የሚቀጸሉ፣ለአንቺ ብቻ የሚውሉ፣ ለአንቺ ብቻ የሚነገሩ፣ ለአንቺ ብቻ የሚገለጡ፣ ለአንቺ ብቻ የሚደረጉ፣ ለአንቺ ብቻ የሚሰሙ የተለዩ ነገሮች ከሌሉ ምኑን ሚስት ሆንሺው፡፡ ባልሽ ደግ፣ ሩኅሩኅ፣ ትዕግሥተኛ፣ የማይሰክር፣ ገንዘብ የማያባክን፣ ታማኝ፣ መልከ ቀና  ቢሆን እጅግ የታደልሽ ትባያለሽ፡፡ ይኼ ሁሉ ግን መልካም ሰውነቱን እንጂ መልካም ባልነቱን አያሳይም፡፡ ደግ ሰው፣ ቆንጆ ሰው፣ ትጉኅ ሰው፣ ፍጹም ሰው ያሰኘዋል እንጂ ብቻውን መልካም ባል አያሰኘውም፡፡
መልካም ባል ለመሆን በመልካም ሰውነት ላይ ሊጨመሩ የሚገባቸው ሌሎች የባልነት ነገሮች አሉ፡፡ በመልካም ባል ውስጥ ሚስትነት፣ በመልካም ሚስት ውስጥ ደግሞ ባልነት መኖር አለባቸው፡፡ መልካም ባል ማለት ሚስት መሆን ማለት ምን ማለት እንደሆነ የሚረዳ፣ ሚስትነት በውስጡ ያለው ባል ማለት ነው፡፡ መልካም ሚስትም እንዲሁ፡፡ መልካም ባል ማለት የሚስትን ስሜት፣ ልብና ኩላሊት ለማወቅ የሚችል ማለት ሳይሆን ሊረዳውና ሊሰማው የሚችል ማለት ነው፡፡
እንዲህ ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቼ ሳስበው ለካ እኛ ቤት ውስጥ የነበሩት ባልና ሚስት ጠፍተው አንድ ወንድና አንዲት ሴት ቀርተዋል፡፡ አብረው የሚኖሩ፣ አብረው የሚሠሩ፣ አብረው የሚያድሩ፣ አብረው የሚበሉ፣ አብረው ልጅ የሚያሳድጉ ሁለት ወንድና ሴት፡፡ ባለ ትዳሮቹ ጠፍተው ትዳሩ ቀርቷል፡፡ አንድ ነገር የሚመሠረተው፣ ለመመሥረቱ በሚኖረው ቀዳሚ ምክንያት ነው፡፡ ያ ምክንያት ነው ለዚያ ነገር የህልውናው ሞተር፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን ምክንያቱ ይጠፋና ነገሩ ብቻውን ይኖራል፡፡ የምክንያቱ ሳይሆን ምክንያቱ የፈጠረው ተቋም ወይም ቡድን አባል ትሆኛለሽ፡፡
ከዚያ በኋላ የምትኖሪው ወይም የምትንቀሳቀሽው ለምክንያቱ ሳይሆን በምክንያቱ የተነሣ ለተፈጠረው ተቋም ወይም ቡድን ይሆናል፡፡ ያ ተቋም የተመሠረተበትን ምክንያት ለመፈጸም ሲል የፈጠራቸው ሕጎች፣ ሥርዓቶች፣ ደንቦች፣ ባሕሎች፣ ልማዶች፣ ወጎች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ነገሮች በሰው ውስጥ ሰርጸው የመኖር ዐቅም ስላላቸው፤ አንቺም ለእነዚህ እየተገዛሽ መኖር ትቀጥያለሽ፡፡ ያን ጊዜ ሕይወት አዙሪት ይሆንብሻል፡፡ ሥራ ስላለሽ ከቤት ትወጫለሽ፣ ቤት ስላለሽ ብቻ ተመልሰሽ ትመጫለሽ፤ ልጆች ስለወለድሽ ለእነርሱ ስትዪ ትዳርሽን ትቀጥዪዋለሽ፣ ባል ስላለሽ ብቻ አብረሽ ትተኛለሽ፤ የጋራ ጉዳይ ስላለሽ ብቻ ተነጋገሪያለሽ፤ እያለ ይቀጥላል፡፡
እኔ እንዳየሁት አንቺ በትዳር ውስጥ ስትሆኚና ትዳሩ አንቺ ውስጥ ሲሆን ይለያያል፡፡ አንቺ በትዳር ውስጥ ስትሆኚ፣ በውስጥሽ ምንም ስሜት ሳይኖርሽ፣ ነፍስሽ ምንም ሳይሰማት እንዴው ማድረግ ስላለብሽ ብቻ ስታደርጊው ነው፡፡ ምግብን ሆድሽ ብቻ ሲበላውና ኅሊናሽ ጭምር ሲበላው አይለያይም? ለመኖር መብላት ስላለብሽ ብቻ ስትበዪና ደስ ብሎሽ፣ ኅሊናሽ ረክቶ፣ ዘና ብለሽ ስትበዪ ማለቴ ነው፡፡ አንቺ በትዳር ውስጥ ስትሆኚ ለመኖር ብቻ ሲባል ምግብ እንደመብላት ነው፡፡ ትዳር በአንቺ ውስጥ ሲሆን ግን ሌላ ነው፡፡ ስትሄጂ፣ ስትሠሪ፣ ስትተኚ፣ ሲደክምሽና ስትበረቺ እንኳን ትዳርሽን ባሰብሽ ቁጥር አንዳች ልዩ የሆነ የደስታና የእርካታ ስሜት ሲሰማሽ፤ ገብተሸ ስትዋኚበት፣ ያወራችሁትን፣ ያደረጋችሁትን፣ የሆናችሁትን፣ ሌላው፤ ቀርቶ የተኳረፋችሁትን እንኳን እንደ ቤት እንስሳ መልሰሽ ስታመነዥኪው እንደ መልካም ጠጅ በኅሊናሽ ኩልል ብሎ ሲንቆረቆር፤ ከቤትሽ ስትወጭ ለመመለስ ስትቸኩዪ፤ ከባልሽ ስትለዪ ለመገናኘት ስትጣደፊ፤ ባልሽን፣ ልጆችሺን፣ ቤትሽን ይዘሺው ስትሄጂ – ያ ነው – ትዳር በአንቺ ውስጥ ሲኖር ማለት፡፡
ትዳር ስንጀምር ትዳር ውስጣችን ገብቶ ነበር፡፡ ስንቆይ ግን እኛ እንገባና እርሱ ይወጣል፡፡ ያኔ ነው ‹መነጋገር› መነጋገር ብቻ የሚሆነው፡፡ መነጋገር የፍቅር መግለጫ፣ በነፍስ የመዛመድ ምልክት፣ በሐሳብ የመገናዘብ ማሳያ መሆኑ ይቀርና መነጋገር መነጋገር ብቻ ይሆናል፡፡ እኔም እንዲህ ሆኖብኝ ብዙ ጊዜ ተቸገርኩ፡፡ ስነጫነጭ፣ ስብሰከሰክ፣ ስማረርና ስቆርጥ ስቀጥል ኖርኩ፡፡ አንድ ቀን እንደ ድንገት ጋብቻን ስለማደስ የተጻፈ መጽሐፍ አገኘሁ፡፡ በፈረንጆቹ ባሕል ጋብቻን ማደስ (marriage renewal) የተለመደ ባሕል ነው፡፡ ለምን ወደ እኛ አንቀይረውም ብዬ አሰብኩ፡፡
በዚያ መጽሐፍ ላይ አንድ ቁም ነገር አየሁ፡፡ ከትዳር ልምድ ያገኘሺውን ነገር ተጠቅመሽ አዲስ የቃል ኪዳን ሰነድ አዘጋጂ ይላል፡፡ ለባለቤቴ ወሰድኩና አሳየሁት፡፡ ሲያነበው ወደደው፡፡ ያ ነገር ምክንያት ሆነንና ስለትዳር ማደስ አወራን፡፡ እኔም የራሴን እርሱም የራሱን ሰነድ አዘጋጀ፡፡ በቃል ኪዳን ሰነዱ ሞዴል ላይ ያለፈውን የትዳር ዘመን፣ ባለፈው ዘመን በክፉም በደጉም ለቆየንባቸው ዘመናት ለፈጣሪ ምስጋና፣ ለፈጠርናቸው ስሕተቶች ይቅርታ፣ ከዚያ ደግሞ ለወደፊቱ በትዳራችን እንድናደርግ የምንፈልገውን ነገር ይዘረዝራል፡፡ እኔ የርሱን እርሱም የእኔን ልናዘጋጅ ተስማማን፡፡ ባሌ ምን ቢሆንልኝ እንደምፈልግ ለብዙ ጊዜ አሰብኩበት፤ እርሱም አስቦበታል፡፡
ያዘጋጀነው ሰነድ ከትዳራችን ምን እንደምንፈልግና፣ ምን እንደማንፈልግ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነበር፡፡ ትዳራችንን የፈተሽንብት መልካም አጋጣሚ ሆነልን፡፡ ሁለታችንም በተዘጋጀልን ሰነድ ላይ መጠነኛ ማሻሻያ ከማድረግ ያለፈ አልተጓዝንም፡፡ አሁን በስለናል፤ ከልምድ ብዙ ነገር አግኝተናል፤ በፊት በትዳር ውስጥ እናስባቸው ያልነበሩ ነገሮችን ማሰብ ጀምረናል፤ ተፈታትነናል፤ ተዋውቀናልም፡፡ አንዳችን የሌላችንን በማዘጋጀታችን የተነሣ ነገሮች በዝርዝር ቀርበው ነበር፡፡ አናደርግም የምንለው፣ እናደርጋለን የምንለው ቁልጭ ብሎ ቀርቧል፡፡
በጣም የሚገርምሽ ነገር ችግር የማይመስሉን ነገሮች ሁሉ በሌላችን ተነቅሰው ሲመጡ ችግር መሆናቸውን ለመረዳት አስችሎናል፡፡ ቀላል የሚመስሉ፣ እንደዋዛ የምንዘላቸው፣ ነገር ግን ሌላችንን የሚያናድዱና የሚያሳዝኑ ነገሮች ሁሉ መጡ፡፡  በፈጣሪ ፊት ቆምንና ሁለታችንም እንደገና ቃል ገባን፡፡ እንደገናም ተጋባን፤ ለትዳራችን አዲስ እሴት ጨመርንለት፣ እንደገና የመኖሪያ ምክንያታችንን አደስነው፤ እርሱ ወደ እኔ፣ እኔም ወደ እርሱ ውስጥ ገባን፡፡ ትዳራችንም ወደ እኛ ገባ፡፡ ያንን ሰነድ በየጊዜው እያየሁ ራሴን አረጋግጥ ነበር፡፡ ቃሌን እየጠበቅኩ ነውን? እል ነበር፡፡ እንደ አዲስ ተጋቢ ነበር የሚሰማኝ፡፡
እንዳየሁት ከሆነ ትዳርና አትክልት በየጊዜው ካልተከታተሉት አረም ይበቅልበታል፡፡ ሲብስም አትክልቱ ይጠፋና አረሙ መታየት ይጀምራል፡፡ ያኔ ነው እንጨት እንጨት የሚለው፡፡ ጎበዝ ሰው ቶሎ ብሎ ያርምና አትክልቱ እንዲያብብ ያደርገዋል፡፡ እንደገና መኮትኮት፣ እንደገና ማዳበሪያ ማድረግ፣ እንደገና አፈር መከለስ፣ እንደገና ውኃ ማጠጣት፣ እንደገና አጥር ማጠር ይጠይቅ ይሆናል፡፡ ድሮ አፈር አድርጌ ነበር፣ ማዳበሪያ ነበረው፣ አጠጥቼው ነበር፣ ኮትኩቼው ነበር አይሠራም ወዳጄ፡፡ አንዳንዴም እርሻው ብቻ ቀርቶ ተክሉ ሊጠፋ ይችላል፡፡
እና እስኪ ቆም ብለሽ ተመልከቺው፤ እንደገና መጋባት፣ ጋብቻውን እንደገና ማደስ፣ ለአዲሱ ሰብእናሽ አዲስ ሐሳብ መፈለግ፣ አሁን ለደረስሽበት ነገር አዲስ ቃል ኪዳን መግባት ያስፈልጋችሁ ይሆናል፡፡ ትዳርሽ አርጅቶ ይሆናል፡፡ ትዳር ይፀነሳል፣ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ያረጃል፣ ዝም ካሉትም ይሞታል፡፡ ጀግኖች ደግሞ እንዳያረጅና እንዳይሞት እንደ አዲስ ያድሱታል፡፡ አንቺም ትዳርሽ እንደ ንሥር አድሽው፤ ያለበለዚያ መጀመሪያ ያረጃል፤ ከዚያም ከባሰ ይሞታል፡፡ እሳትን እንጨት ላይ እያለ መልሶ ማቀጣጠል መልካም ነው፤በእንጨትነቱ ካልተደረሰም እንጨቱ ከሰል ሲሆን ቶሎ መድረስ ነው፤ ከሰሉ አመድ ከሆነ በኋላ ግን እንደገና ማቀጣጠል አስቸጋሪ ነው፡፡ ›› ነበር ያለቺኝ፡፡
አሁን  ሳስበው እርሷ ያለቺኝ ሳይሻል አይቀርም፡፡
‹እውነትሽ ነው› አለቺ ጓደኛዋ ‹‹ሁላችንም ብንሞክረው ሳይሻል አይቀርም››
ዑራኤል የኤሌክትሪክ ሱቆች ጋር ደርሼ ተለየኋቸው፡፡ እነርሱ ግን ቀጠሉ፡፡
ፍራንክፈርት አውሮፕላን ጣቢያ

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አምስተኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሠረተባቸው ተጠርጣሪዎቹ ዋና ኢንስፔክተር ጐይቶም አረጋዊ ኪዳነ ማርያም፣ ረዳት ኢንስፔክተር አንተነህ አስናቀ ተፈራና ኮንስታብል ዘሪሁን ሲሳይ ሲሆኑ፣ ሁሉም በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪ መሆናቸውን የክስ ቻርጁ ያስረዳል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ለሕግ ተቃራኒ በሆነ መንገድ በማስገደድና ከሕግ ውጪ የግል ተበዳይ ናቸው የተባሉትን አቶ አህመድ ኑርን ይይዟቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከሶማሌ ክልል ወደ አዲስ አበባ በመምጣት፣ ተበዳዩን የያዟቸው ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ጐተራ አካባቢ መሆኑን ክሱ ይገልጻል፡፡ የግል ተበዳይ ናቸው የተባሉት አቶ አህመድን ከነበሩበት ተሽከርካሪ ላይ ጐትተው በማውረድ፣ በሽጉጥ በማስፈራራት፣ በቦክስ ፊታቸውንና የተለያዩ የሰውነት ክፍላቸውን በመምታት ራሳቸውን ሲስቱ፣ ተጠርጣሪዎቹ በያዙት ተሽከርካሪ ወደ ቦሌ ክፍለ ከተማ መድኃኔዓለም አካባቢ እንደወሰዷቸውም ተገልጿል፡፡

ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ በሚገኘውና ‹‹የሶማሌ ክልል ዳያስፖራ ቢሮ›› በመባል በሚታወቀው ጊቢ በሚገኝ ሰርቪስ ቤት ውስጥ በማስገባት፣ ለሦስት ሰዓታት እንዳቆዩአቸውም ክሱ ያብራራል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከሦስት ሰዓታት በኋላ የሰሌዳ ቁጥሩ 0071 በሆነ የሶማሌ ክልል ፖሊስ ፒክአፕ ተሽከርካሪ ጭነው፣ ወደ ጅግጅጋ ያመራሉ፡፡ አዋሽ፣ ልዩ ቦታው አዋሽ ድልድይ ኬላ ላይ የሚጠብቁ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል አባላት በቁጥጥር ሥር እንዳዋሏቸውና ሰውን ከሕግ ውጪ ይዞ ማስቀመጥ ወንጀል መከሰሳቸውን የክስ ቻርጁ ያስረዳል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ዋስትና የጠየቁ ቢሆንም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አምስተኛ ወንጀል ችሎት ኅዳር 19 ቀን 2007 ዓ.ም. ውድቅ አድርጐ በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከራከሩ ብይን ሰጥቷል፡፡
Source: Reporter Amharic


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
 በለምለሚቷ ምድራችን ላይ እየተሽከረከረ ዚያራ ማድረግ ወጉ የሆነው የኢትኖግራፊ ፈረሳችን ታሪካዊቷን ጅማንና ህዝቧን መጎብኘት አሰኘው፡፡ እኛም “አበጀህ! ጥሩ ሀገር መርጠሃል” በማለት መረቅነው፡፡ ፈረሳችንም የደቡብ ምዕራብ አቅጣጫን ይዞ ገሰገሰ፡፡ ከጊቤ ዉሃ ከተጎነጨ በኋላም ወደ ታሪካዊቷ ቀበሌ ሰተት ብሎ ገባ፡፡
The palace of Abba Jifar, Jimma,
ጅማ! የአባጅፋር ሀገር! የአባ ፎጊ ሀገር! የአባ ቦጊቦ ሀገር! የአባ ጎመል ሀገር! ዝንተ-ዓለም አይረሴ የሆኑ ነገሥታት ታሪክ ሰርተውባት ለታሪክ ያኖሯት ውብ መንደር!!
ጂማ! የሰቃ ጨቆርሳ ሀገር! የጌራ ሀገር! የጉማ ሀገር! የጎማ ሀገር! የሊሙ ሂናሪያ ሀገር! አምስቱ የጊቤ መንግሥታት የለመለሙባት ምድር!!
ጅማ! የአባ ሚዛን ሀገር! የአባ ቆሮ ሀገር! የአባ ገንዳ ሀገር! የአባ ዱላ ሀገር! በኦሮሞ ምድር የዘመናዊ ቢሮክራሲ ጥንስስ የተጀመረባት ሰፈር!
ጅማ! የአቦል ሀገር! የበረካ ሀገር! የቃህዋ ጀባ ሀገር! ለስምንት መቶ ዓመታት ተወዳጅነቱ ሳይቀንስ የዘለቀውን “ቡና”ን ለዓለም ያበረከተች የሙሐባ መንበር!!
ጅማ! የተሚማ ሀገር! የገሜቲ ሀገር! የአያንቱ ሀገር! የአስሊያ ሀገር! የበድሪያ ሀገር! የፈይሩዝ ሀገር! ውብ ልዕልታትና ወይዛዝርት የወጡባት ምድር!!
*****
ተሚማ ነው ያልኩት! ይገርማል!! ገና የፈረሳችን ኮቴ መሬቱን ከመርገጡ ተሚማ በፈገግታ ታጅባ ልትቀበለን መጣች፡፡ ተወዳጅዋ የጅማ ጉብል!
ወይ አፈጣጠር!! “ቁርጥ ባለቤቴን” አለ ሰውዬው፡፡ በእውነት ይህቺ የጅማ ጉብል ናት ወይስ በሀረርጌ የምናውቃት ቀሽቲ?… እንዲያው ሁለመናዋ ከኛዋ ቀሽቲ ጋር አንድ ነው እኮ!!
ይህቺን “ኑረል ዐይን” የምትመስል ጉብል በተራ ሰላምታ ማነጋገር ተገቢ መስሎ አልታየንም፡፡ በመሆኑም ድሮ የ“ሐፈዝናቸውን” ሙገሳዎችና በቅርብ ጊዜያት የሰማናቸውን “ወለሎ”ዎች ተራ በተራ እየደረደርን ዐጃኢብ እስክትል ድረስ እንዘምርላታለን፡፡
*****
እውነቴን ነው!! ለጂማዋ ጉብል ማን ያልዘመረ አለ?… ብዙ ተዘፍኖላታል፡፡ ብዙ ተብሎላታል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ለርሷ የተደረደረው ሙገሳ በጣም ያንሳታል፡፡ እልፍ አዕላፍ “ቀሲዳ”፣ “ሩባኢያት”፣ “ወለሎ”፣ “ቅኔ”፣ “ገዛል”፣ ወዘተ… ይገባታል፡፡ የኛም ዚያራች ያማረ ይሆንልን ዘንድ ወደ ሌሎች ወጎች ከማለፋችን በፊት ለርሷ ክብር የተዜሙትን ዜማዎች አንዴ በጀመዓ ብንከልሳቸው መልካም ይመስለኛል (በአጸፌታው የጂማዋ  ጉብል  ደረጃውን የጠበቀ መስተንግዶ አድርጋልን ዚያራችንን ልታደምቀው ተሰናድታለች)፡፡
ለጅማዋ ጉብል የተዜመው የመጀመሪያው ዜማ የትኛው እንደሆነ በትክክል አናውቅም (አንቺ ተሚማ! ያ ገሜቲ ጂማ!! ያ በሬዱ ነማ!! እኛ “እኛ” መሆናችንን ታውቂዋለሽ አይደል?…. አዎን!  “እኛ” እያልን የምንጽፈው ከሀረርጌ በመሆናችን ነው)፡፡ እስካሁን ድረስ ባለን መረጃ መሰረት ግን የጥላሁን ገሠሠ “ሰላመካ ያ ገንኔ ሰላመካ” ለጅማዋ ጉብል የተዘፈነ የመጀመሪያው ዜማ ይመስለኛል፡፡ የግጥሙ ደራሲ ተገኑ ባልከው ይባላል (“አሸም ያ ማተቤ”ንም የጻፈው እርሱ ነው)፡፡ ጥላሁን ለጅማዋ ጉብል ሲዘፍን እንዲህ ነበር ያለው፡፡
Salaama kaa yaa gannee salaama kaa
Harka fuune yaa immeetee salaamka.
Dubbiin Tamiima dubbiin mucayyoo magaala
Ija koo qabee gurra koo qabee na raasa
Gandan dhagayee dhiisi naan jenaani
Ittin dhiise yaadden na qabnaani.
ጥላሁን በዘፈኑ ውስጥ የጅማን ስም አልጠቀሰም፡፡ ነገር ግን በግጥሙ ውስጥ የተጠቀማቸውን ቃላት እና የሙዚቃውን ምት (rhythm) በአንክሮ ስናያቸው ዘፈኑ “ለጅማዋ ተሚማ” እንደተዘፈነ በቀላሉ መረዳት እንችላለን፡፡ ለምሳሌ ከበርካታ የኦሮምኛ ዘዬዎች መካከል “ሰላመ-ካ” እያሉ ሰላምታ መስጠት የሚቻለው በጅማው ዘዬ ነው፡፡ “ሰላመት” ከዐረብኛ ወደ ኦሮምኛ የገባ ቃል መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ቃሉ በኦሮምኛ ውስጥ የሚያገለግልበት ስልት እንደየአካባቢው ይለያያል፡፡ በሀረር ኦሮምኛ አንድን ሰው ስንገናኝ “ሰላም ጄኔ” (ሰላም ብለናል) ለማለት እንችላለን፡፡ በጅማው ዘዬ ደግሞ “ሰላመ-ካ” እንላለን (ሌሎች ስልቶችን ከወደታች እንመጣባቸዋለን)፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ጥላሁን ልጅቷን “ተሚማ” እያለ ነበር የጠራት፡፡ ይህም ዘፈኑ ለጅማ ጉብል የተዜመ መሆኑን ያሳብቃል፡፡ የጅማ ሴቶች ከሚጠሩባቸው ስሞች መካከል በጣም ዝነኛ የሆነው እርሱ ነው፡፡ ሌሎች አርቲስቶችም የጅማን ኮረዳ ለመጥራት ሲፈልጉ በዚህ ስም ነው የሚጠቀሙት (ጥላሁን “ፋጡማ” ወይንም “አዒሻ” ቢል ኖሮ ለሀረር ቆንጆ ነው ያዜመው ብለን እንጠረጥር ነበር)፡፡
*****
ከጥቂት ዓመታት በፊት ነው፡፡ “ሃጫሉ ሁንዴሳ” (Haacaaluu Hundeessaa) የሚባል የኦሮምኛ ዘፋኝ መጀመሪያ ካሴቱ በሙዚቃ አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቶ ነበር፡፡ በካሴቱ ውስጥ ከተካተቱት ዜማዎች መካከል በጣም ተወዳጅ ሆኖ የወጣው ደግሞ ለጅማዋ ጉብል የተገጠመው ነው፡፡ ሃጫሉ ከጅማ ጉብል የያዘውን ፍቅር ሲገልጽ እንዲህ ነበር ያለው፡፡
Galaanni Gibee guutus daaktuuf bidiruutu nama ceesisaa
Garaan jaalatte hin rafuu halkuu jilbibbii nama deemsisaa
Ani sossodaadhe barana qalbii kootii
Gibee gaman jaaladhe sanyii mootii.
ሃጫሉ የዘፈነውን ወደ አማርኛ ስንተረጎመው እንደሚከተለው ይሆናል፡፡
“የጊቤ ወንዝ የሞላበት ሰው በዋናተኛና በታንኳ ይሻገራል
ያፈቀረ ሆድ ግን አያስተኛም፤ ሌሊቱን በሙሉ በዳዴ ያስኬዳል፡፡
አረ ዘንድሮስ ፈራሁኝ እንዳይታመም ይሄ ቀልቤ
ከጊቤ ወዲያ ያለችውን የንጉሥ ዘር አፍቅሬ ከልቤ፡፡
ሃጫሉ የወደዳት ልጅ “ጉብል” ብቻ ሳትሆን “የንጉሥ ዘር” እንደሆነች ነግሮናል፡፡ የዚህን አባባል “ተፍሲር” ወደፊት ስለምንመጣበት በአዕምሮአችሁ ውስጥ መዝግባችሁት ቆዩ፡፡
*****
ከላይ እንደገለጽኩት ለ“ጅማ ጉብል” የተዜመው የመጀመሪያ ዜማ የጥላሁን ገሠሠ “ሰላመካ” ነው፡፡ ነገር ግን ጥላሁን “ጉብሊቷ”ን በስም አልጠቀሳትም፡፡ ታዲያ “የጅማ ጉብል” የሚለውን ሐረግ በግጥሙ ውስጥ በግልፅ (explicitly) በማሳየት ማዜሙን የጀመረው ማን እንደሆነ ታውቃላችሁን?
  ነፍሱን ይማረውና አሁን በህይወት የለም፡፡ አብደላ መሐመድ ነው፡፡ አብደላ የፖሊስ ኦርኬስትራ አባል ነበረ፡፡ በኦርኬስትራው ውስጥ በነበረው ቆይታ “አሪፍ” ጣዕመ ዜማዎችን አስመዝግቦ አልፏል፡፡ ከነርሱ ውስጥ በመጀመሪያ ደረጃ ተጠቃሽ የሆነው ደግሞ “መጋለ ቀሎ ያ በሬዱ ጅማ” የተሰኘው ዘፈን ነው፡፡ አስታወሳችሁት አይደል?… አዎን!! አብደላ ያዜመው ዜማ በጣም ተወዳጅ ከመሆኑ የተነሳ በአንድ ሰሞን የህዝብ ዘፈን እስከመሆን ደርሷል፡፡ በተለይም በቀድሞው ጊዜ የኢትዮጵያ ሬድዮ የኦሮምኛ ፕሮግራም የአብደላን ዘፈን እየደጋገመ ያጫውተው የነበረ መሆኑ ኦሮምኛ የማይሰሙ ሰዎችም ጭምር የዘፈኑን ግጥሞች እንዲሸመድዱ አስችሎአቸው ነበር፡፡ እነሆ አዝማቹን ላስታውሳችሁ ነው፡፡
Jenneen ashamaan ashamaa jenneen ashamaa
Magaala qalloo yaa bareedduu Jimmaa
የአብደላ ዘፈን መልዕክቱ እንዲህ ሊሆን ይችላል፡፡
“እንዴት ነሽ… ሰላም ነሽ ወይ” አልናት፡፡
ያቺን ጠይም ጉብል የጅማ ወጣት፡፡
አብደላ በዚህ ዘፈኑ የጅማዋን ጉብል በማወደሱ ብቻ አይደለም የሚለየው፡፡ በዘፈኑ ውስጥ የጅማ ሰዎች መታወቂያ የሆነውን  የኦሮምኛ ቃል በመጠቀም ግጥሙን ያቀናበረ በመሆኑም ጭምር ነው የሚታወሰው፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡
በርግጥም የጅማ ሰዎች ሰላምታ ሲሰጣጡ ከላይ በጠቀስኩት “ሰላመ-ካ” የተሰኘ ቃል ይገለገላሉ፡፡ ሆኖም ጅማዎች ሰላምታውን በመጠይቃዊ ዘዴ ሲያቀርቡልን ብዙሃኑ የኦሮምኛ ተናጋሪዎች በሚናገሩበት ስልት “አከም” (Akkam) አይሉም፡፡ ከዚህ በተለየ ስልት “አሸም” (Asham) ወይንም “አሸማ” (Ashamaa) ነው የሚሉት፡፡ አንድ ኦሮሞ የትም ሆኖ “አሸም” ብሎ ሰላምታ ካቀረበላችሁ ትውልዱ ከወደ ጅማ እንደሆነ ልብ በሉ፡፡(በነገራችን ላይ ለየት ያለ መጠይቃዊ የሰላምታ ማቅረቢያ ቃል የምናገኝበት ሌላው የኦሮምኛ ዘዬ በኢሉባቦር የሚነገረው ነው፤ የኢሉባቦር ሰዎች “አከም” ለማለት ሲሹ “አተም” ነው የሚሉት፡፡ የወለጋና የምዕራብ ሸዋ ኦሮሞዎችም  “አተም”ን ያውቁታል፡፡ ነገር ግን ወለጋዎችና ሸዋዎች በአብዛኛው “አከም”ን ነው የሚጠቀሙት)፡፡
የጅማ ሰዎች በሚያዜሟቸው ዘፈኖች ላይ በብዛት የሚጠቀሙት ሌላ ቃል አለ፡፡ እንዲያውም ያ ቃል ከቋንቋነትም አልፎ የጅማን ዘፈን የምንለይበት ምልክት (mark) እስከመሆንም ደርሷል፡፡ ለምሳሌ አንድ አርቲስት በዘፈኑ ውስጥ “አራዳ… አራዳ ሆዬ” የሚል ሐረግ ከደጋገመ ዘፋኙ ስለአዲስ አበባ እየዜመ መሆኑን በቀላሉ መረዳት እንችላለን፡፡ “እሪኩም” እና “መጋሎ” የተሰኙ ቃላትን የሚያበዛ ዘፋኝም ስለወሎ የሚያዜም ነው፡፡ ስለጅማ የሚያዜም ሰው ደግሞ ብዙ ጊዜ “አህላን አህላ” እያለ ነው ዘፈኑን የሚጀምረው፡፡
አዎን! በኦሮምኛ ጨዋታዎች ውስጥ “አህላን አህለ” ከተባለ ዘፈኑ የጅማ መሆኑ ምንም አያከራክርም፡፡ “አህለን” በመሰረቱ የዐረብኛ ቃል ነው፡፡ በዐረብኛ “አህለን ወሳህለን” ከተባለ “ጤና ይስጥልኝ” እንደማለት ነው (አገባቡ ሰፋ ሲል ደግሞ “እንኳን ደህና መጡ” እንደማለትም ይሆናል)፡፡ በሃይማኖታቸው ሙስሊሞች የሆኑት የጅማ ሰዎች “አህለን”ን ከዐረብኛ ወርሰው ነው ቤተኛ ያደረጉት፡፡
*****
ጅማዎች “አህለ”ን የሚሉት ከልብ የመነጨ ስሜታቸውን ለመግለጽ ነው፡፡ እኛ ጅማ ስንገባ የፈረሳችንን ልጓም ይዛ የጅማን መሬት እንድንረግጥ የረዳችን “ተሚማ”ም ከፈገግታ ጋር “አህለን” በማለት ተቀብላናለች፡፡ እንግዲህ በርሷ አስጎብኚነት “አህለን አህለን” አያልን በጅማ መሬት መንሸራሸራችንን ልንጀምር ነው፡፡
አህለን አህላ… ሸጌ አህለን አህላ
አህለን.. አህላ.. ጊፍቲ አህለን አህላ
(ይቀጥላል)
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 22/2007
ሀረር… ምስራቅ ኢትዮጵያ
—–
The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of ethnography and history with special focus on Eastern Ethiopia.  You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click the following link to go to his page.

ኀዳር ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሃገሪቱ ህገ መንግስት አንቀጽ 31 መሰረት በህጋዊ መልኩ ተመዝግበው ሰላማዊ የፖለቲካ እንቃስቃሴ የሚያደርጉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን በሽብርተኝነት እና ጽንፈኝነት በመፈረጅ የጥቃት ኢላማ ለማድረግ መታሰቡን ኢሳት የፌደራል መንግስት የጸጥታ ጉዳዮች ሰሞኑን ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር  ካካሄደው ውይይት ለመረዳት ተችሎአል፡፡ የትግራይ፣ቤንሻንጉል ጉሙዝና አማራ ክልል ሃላፊዎች ሰማያዊ ፣አንድነትና መኢአድ ፓርቲዎች ጽንፈኞች በመሆናቸው …

ኀዳር ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሺን፣ ፓርቲዎቹ ይህን አስታወቁት ባወጡት መግለጫ ነው። ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው ደብዳቤ ለመቀበል አሻፈረን ሲል የነበረው መስተዳድሩ በፖስታ የተላከለትን ደብዳቤ ከተቀበለ በሁዋላ ከህገመንግስቱና ከአዋጁ ቁጥር 3/1983 ተቃራኒ የሆኑ ምክንያቶችን በመደርደር ለሠላማዊ ሠልፉ ዕውቅና አልሰጠሁም ሲል ህዳር 22 ቀን  ድብዳቤ መጻፉን አስታውቀዋል፡፡ “በመሠረቱ መስተዳድሩ ጊዜና ቦታ እንዲቀየር አስተያየት …

ኀዳር ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከወራት በፊት 111 በመቶ የደሞዝ ጭማሪ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሺን፣ በአማራ እና በኦሮምያ ክልል በተከታታይ ተገቢ የሆነ የደሞዝ ማስተካካያ አላደረገም በሚል ጥያቄ ሲቀርብብት ቆይቷል። ሰሞኑን የካቢኔ አባላት ተሰብስበው   የአማራ ክልል ጋዜጠኞች ከግንቦት ሰባት እና አርበኞች ግንባር እንዲሁም  የኦሮምያ ክልል ጋዜጠኞች ከኦነግ ጋር የሚሰሩትና ለኢሳት መረጃ በማቅረብ በክልሎች …

ኀዳር ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወኪላችን እንዳለው በዋና ከተማዋ ጁባ አንድ ወንድና አንድ ሴት ሲገደሉ ሁለት ሴቶች ግን በጠና ቆስለው ወደ ኢትዮጵያ ተወስደዋል። የሁለቱም ሟቾች አስከሬንም በኢትዮጵያውያን እርዳታ ወደ ኢትዮጵያ መሄዱ ታውቆል:: ሰዎቹ በምን ሁኔታ እንደተገደሉና እንደቆሰሉ እንዲሁም ጥቃቱን ያደረሱትን ወገኖች ዝርዝር ለማወቅ አልተቻለም። በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በኢትዮጵያውያን የሚደረገውን ግፍና …

ኑ- ለነጻነታችንና ክብራችን ድምጻችንን በጋራ እናሰማ!

ከባርነትና ውርደት ለመላቀቅ ነውና በፍጹም አይቀርም፣ አይቀርም!

የ9ኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ ››በሚል መርህ የመጀመሪያ ዙር ዕቅዱን ለህዳር ወር አዘጋጅቶ ወደ እንቅስቃሴ ከገባ ሦስት ሣምንታትን አሳልፏል፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባራትና የተጓዝንበትን መንገድ ለጉዳዩ ቀዳሚ ባለቤትና ለባለ ድርሻ አካላት ስናሳውቅ የነበረ በመሆኑ ያጋጠሙንን ችግሮች በመደጋገም ማሰልቸት አንሻም፡፡

ስለሆነም የዛሬው መግለጫችን በቀጣይ ለቀሩን ተግባራት የደረስንበትን ድምዳሜና ያወጣነው ዕቅድ በሚመለከት ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በእስከዛሬው እንቅስቃሴያችን ይዘን የተነሳነው ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› የሚለው መርህ ትክክልና ወቅታዊ፣ ያነሳናቸው ጥያቄዎችም አግባብ መሆናቸውን ያረጋገጥንበትና ገዢው ፓርቲ መድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ማለት ፍጻሜዬ ነው በሚል ከገባበት ከፍተኛ የፍርኃት ስሜትና ሥጋት ለተቃውሞ ጎራው እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ማለት በሚያስችል ሁኔታ በሩን ለመዝጋት የተዘጋጀ መሆኑን አገር ለ23 ዓመታት በላይ ካስተዳደረ መንግስታዊ ሥርዓት የማይጠበቅ መረን የለቀቀ የውንብድና ተግባራት ያረጋገጥንበት ነው፡፡ በመሆኑም ጥያቄዎቻችንን በህገ መንግስቱና በአገሪቱ ህጎች መሠረት ለመመለስ ቀርቶ ለመስማትና ለማንበብ ፍቃደኝነቱና የኃላፊነት ስሜቱ እየተሟጠጠ በመሆኑ የአፈናና ማስፈራራት መንገድን ብቸኛ አማራጭ አድርጎታል፡፡ ይህ በመሆኑም የራሱን መንግሥታዊ መዋቅር አሰራር ሥርዓት እንኳ በአደባባይ ለመቀበል እምቢተኛ መሆኑን በአደባባይ አረጋግጧል፡፡ ባለሥልጣናቱ በግንባር ያቀረብነውን ደብዳቤ ካለመቀበል አልፈው በመንግሥታዊው ፖስታ ቤት የተላከ ደብዳቤ ያለመቀበላቸው የሚያመለክተው ይህንና የደረስንበትን የመልካም አስተዳደር አዘቅት ነው፡፡

በተቃራኒው አበረታችና መልካም ዜናም አለ፡፡ ይህም ይህን የአፈናና ማስፈራትት አካሄድ አንቀበልም ያሉ ለነጻነታቸውና ክብራቸው፣የራሳቸው ብቻ ሣይሆን የመንግሥት መዋቅሮችና ባለሥልጣናትም ነጻነት መረጋገጥ አለበት ብለው የቱንም መስዋዕትነት ለመክፈል በቁርጠኝነት የተዘጋጁ በትብብሩ የታቀፉ ፓርቲዎች፣ አመራርና አባላት መኖራቸውና በትግሉ ለመቀጠል መወሰናቸው ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ትብብሩ ለመጀመሪያ ዙር ዕቅዱ ማጠቃለያ የህዳር 27/28 የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ደብዳቤ አመራሩ በግንባር ቢያቀርቡም አሻፈረኝ አንቀበልም ያሉት አሰራርና ባለሥልጣናት ከፖስታ ቤት እንዲቀበሉ ተደርጓል፡፡ለዚሁ ደብዳቤ መስተዳድሩ ከህገመንግስቱና ከአዋጁ (ቁጥር 3/1983) ተቃራኒ የሆኑ ምክንያቶችን በመደርደር ለሠላማዊ ሠልፉ ዕውቅና አልሰጠሁም ሲል በዛሬው ቀን (22/03/07) መልስ አድርሶናል፡፡ በመሠረቱ መስተዳድሩ ጊዜና ቦታ እንዲቀየር አስተያየት ከማቅረብ ያለፈ ዕውቅና የመንፈግ መብት የሌለው በመሆኑ ትብብሩ የደብዳቤውን መልዕክት ያልተቀበለ መሆኑንና ሠልፉም በታቀደው ጊዜና ቦታ እንደሚደረግ ወስኖ የመልስ ደብዳቤ አስገብቷል፡፡ በመሆኑም ለተግባራዊነቱ ዝግጅቱን በሙሉ አቅም ጀምሯል፤ ለዚህም የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ከአገር ውስጥና ከውጪ አጋርነታቸውን ገልጸዋል፤ አበረታተውናል፡፡ ይህም የያዝነው የትብብር የጋራ ዓላማችን ተቀባይነት፤ የኅብረትና አንድነትን ዋጋ አመላካች፣ ለማይቀረው ሠላማዊ ትግላችን ሥንቅ ነውና በታላቅ አክብሮት ተቀብለነዋል፡፡

ስለሆነም ይህ መግለጫ ትግላችን ነጻነታችንና ክብራችን የማስመለስ መንገዱም ፍጹም ሠላማዊ፣ ህጋዊና ህገ- መንግሥታዊ ስለሆነ የህዳር 27/28 ሠላማዊ ሰልፍ የማይቀርና የማይቀርበት መሆኑን ለመግለጽና ነጻነትና ክብርን ወዳድ ኢትዮጵዊያንና የፖለቲካ ኃይሎች በሙሉ ለዚህ ታሪካዊ ዕለትና ሠላማዊ ትግል ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ነጻነታችንና ክብራችን ለማስመለስ ዋጋ ለመክፈል እንዘጋጅ፣ ያለመስዋዕትነት ድል የለምና!!
Image

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስና የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያን አንድነት ፓትሪያርክ በርጦሎሜዎስ ቀዳማዊ ፣ ክርስቲያኖች ከመካከለኛው ምሥራቅ እንዲጠፉ የመላው ዓለም ፍላጎት አይደለም አሉ።

በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ ቸልሲ ፈጣን ግስጋሴው ገታ ብሏል፥ የአምናው ባለዋንጫ ማንቸስተር ሲቲ እግር በእግር መከተሉን አላቋረጠም። በጀርመን ቡንደስ ሊጋ ኃያሉ ባየር ሙንሽን እንደልማዱ ሊጋው ከመጠናቀቁ ቀደም ብሎ ዋንጫውን ለመጨበጥ ተቃርቧል፤ የቀድሞው ብርቱ ተፎካካሪ ቦሩስያ ዶርትሙንድ አቅም አንሶት በወራጅ ቃጣናው ጠርዝ ላይ እያጣጣረ ነው።

ኢትዮጵያም -በአብዮትና ፀረ-አብዮት ግብግብ ትናወጥ ነበር።የሶማሊያ ጦርም ገሚስ ኢትዮጵያን ለመያዝ ምሥራቅና ደቡባዊ ኢትዮጵያን ተቆጣጠረ።የአብዮቱ ትርምስ፤ የኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት፤ የዩናይትድ ስቴት መንግሥት ፀረ-ኢትዮጵያ አቋም መያዝ፤ ለቤገን ዕቅድና ቃላቸዉን ገቢር ለማድረግ ጥሩ አጋጣሚ ነበር።

የገዳዩን የኤቦላ ተሐዋሲ የመዛመት ዜናን ተከትሎ ሰናይ ዜናን መሰማቱ ያልተለመደ ነበር። በቅርቡ ግን ተሐዋሲዉን ለመከላከል ያስችል ይሆናል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ የተጣለበት የክትባት መድሃኒት፤ ሰዎች ላይ ተሞክሮ ተስፋ ሰጭ ዉጤትን አስገኝቶአል። ። በሌላ በኩል ክትባቱ አሉታዊ ገፆች እንዳሉትም ነዉ የተነገረዉ።

ምንም እንኳን በግብፅ በኩል አድርገው በህገ ወጥ መንገድ ወደ እስራኤል የሚገቡት ስደተኞች ቁጥር፣ ባለው ጥብቅ ቁጥጥር የተነሳ ቢቀንስም፣ አሁን ድረስ በእስራኤል 48 000 የአፍሪቃ ስደተኞች እንደሚገኙ ይታመናል።

በአለፈው ዓመት በ­22.11. 2013 የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ፣ በእስራኤል ለሚገኘው የወያኔ ሚዲያ ለ­“IETV” ያመጣው የክስ መዘዝ፣ቀጥሎ ለውሳኔ መቀጠሩ የክሊክ ሃበሻ ዘገባ አመልክቷል::የዛሬ ዓመት ኖቨምበር 22 ቀን 2013 ነበር፤ ቴል አቪቭ ከሚገኘው ኢትዮጵያ ኤምባሲ ጽ/ቤት ፊት ለፊት ኢትዮ­ይሁዳያንና ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ዓረቢያ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ግፍና መከራ፣ ሞተና የሴቶች መደፈር፣ ሰቃይና ሰቆቃ የወያኔ/ኅውሃት ገዥውና እምባገነኑ መንግሥት ችላ ብሎታል ብሎ በመቆርቆርና በመበሳጨት የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደው እንደነበር የሚታወስ ነው። http://www.clickhabesh.com/?p=105083

Image
ከሰላማዊ ሰልፈኞቹ መካከል አብዛኛዎቹ በልጅነት እድሜ የመጡና ከዚህ የተወለዱ ወጣት የኢተዮጵያ ይሁዳውያን የተሳትፉበት ከመሆኑም ባሻገር፤በዚህ መልኩ በኢምባሲው ጽ/ቤት ፊት ለፊት ወጣት ኢትዮ ይሁዳውያንን አልገብግቦ እንደዚህ ዓይነት የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በእሥራኤል ሲካሄድ በዓይነቱ የመጀምሪያ ነበር ቢባል ማገነን አይሆንም። ምክንያቱም ቴል አቪቭ የሚገኘው አምባሳደር ኽላዊ ዮሴፍ የወጣት ኢትዮ ይሁዳውያን በሰልፉ መሳተፋቸው አስደንግጦት፣ እዚሁ እሥራኤል በሚገኘው የአማረኛ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ቀርቦ ከተናገረው፣ በእሥራኤል መንግሥት ሙሉ በሙሉ በሚተዳደረ የአማረኛው ሬዲዮ ጣቢያ የተናገርውን አዳምጡ የሬዲዮውን ቃለ ምልልስ አዳምጡና ንባቡን ቀጥሉ፦

ልብ በሉ፦ በዲሞክራሲና በነጻው ሚዲያ ሃገረ እሥራኤል ውስጥ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ “የአንድን ወገን ብቻ አቅርቦ” በተደጋጋሚ ማለትም አምባሳደሩንና ደጋፊዎቹን ቃለመጠይቅ ሲያደርግ፣ ቴሌቪዥኑም ሆን ሬዲዮው ከሙያው ህግ ውጭ በመሆን አንድም ቀን የተቃዋሚውን ወገን በጋራም ሆነ በተናጠል ቃለ መጠይቅ አካሂዶ አያውቅም። ህዝቡ በነጻውሚዲያ ሃገር የሁለቱንም ሃሳብ ሳያዳምጥ አንድ ወገን ብቻ ይዞ እንዲጓዝ መደረጉ ያበሳጫቸው ከዚህ ህዝብ አብራክ የወጡ በተናጠል ትግል የጋራ ትግል በማለት ተደራጅተው፣ “መሬት ­

ኢትዮ ­እሥራኤል የሰብዓዊና ነጻነት ድምጽ ምክር ቤት” ብለው ያቋቋሙት የመጅመሪያ ትግላቸው ማተኰር ያለበት በዲሞክራሲና በነጻ ሚዲያ ሃገር የህዝብ ድምጽ የታፈነውን መብተማስጠበቅ መሆኑን እጠቁማለሁ። ይህ የአምባሳደሩ መግለጫ አንዳንድ የዋህ አዛውንቶችን የኢትዮጵያን ህዝብ እያስራበ በሚያስመጣው “ጤፍ” በማታለል ለማሳመን መሞከሩ ነበር። ምክንያቱም የሚያስበው እሥራኤል የሚገኘው ኢትዮ ቤተ እሥራኤላውያን እኛ እንዳዘዝነው ነው ብሎ ያስብ ስለነበር ሳያስበው የደረሰበት የውርደት ካባ የተከናነበበት በመሆኑ ለማስተባበል መሞከሩ ነበር።ስለጤፍ ከአንድ ስብሰባ ላይ የተናገረውን ተመልከቱ፦ይህን ያህል ለመንደርደሪያ ካልኩ ዘንዳ፣ ወደ ዋናው ሃሳብ ልንደርደር።

ምንም እንኳ ዓርብ ቀን ድምጻውያን እንድሚሉት “….ዓርብ ዓርብ ይሸበራል እየሩሳሌም!” ያለ ምክንያት አይደለም። ዓርብ ህዝበ እሥራኤላውያን ለ 26 ስዓታት ሰንበትን የሚቀበሉበት ቀን ስለሆነ፤ ሁሉም ነገር ከመዘጋጋቱ በፊት ማልደው በመገዛዛት ሲያበስሉና ቤታቸውን ሁሉ ሲያጸዱ ከዋሉ በኋላ ሁሉም ቤተሰብ ሰውነቱን ታጥቦ ጽዓዳ በመልበስ ወደ ጸሎት ቤት ሄደው ሲመለሱ፣ ሰንበት ከመግባቱ በፊት ያበሳስሥሰሉትን፣ መላው ቤተሰብ በአንድ የጠረጴ ዙሪያ በመቀመጥ እየበሉና ወይናቸውን እየተጡ አምላካቸውን የሚያመሰግኑብት ቀን ሲሆን፤ የህዝብ ማመላለሻዎች፤ ሱቆች፤ መ/ቤቶች፤ ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ማንኛውም በሙሉ ዓርብ ከስዓት በኋላ ከቀኑ 14፡00 ማለት 02፡00ስዓት (በኢትዮጵያ ስዓት አቆጣጠር ከቀኑ 08፡00 መሆኑ ነው) ይዘጋል።

ሆኖም ግን በዚህ ቀን የቤተሰብ ኃላፊነት ያላቸው ሌሎች በእድሜ ትንሽ ከፍ ያሉ ቢኖሩም፤ አንዲት ወጣት ቤተ እሥራኤል ከገጠሪቱ ኢትዮጵያወደ እሥራኤል በ­8 ዓመት ዕድሜዋ፤ ኅውሃት አዲስ አበባን ከመቆጣጠሩ ከሁለት ቀን በፊት “ዘመቻ ሰሎሞን” (Operation Solomon) በተባለውየመጣች፤ አሁን የ 31 ዓመት ወጣት፤ በፌስ ቡክ ያተላለፈውን በሳዑዲ ዓረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን መከራና ሥቃይ ችግርና ስቆቃ ተመልክታ “ለወገን ደራሽ ወገን ነው!” ብላ፤ ልጆቿን ዛሬ የ­7 እና የ­የ­5 ዓመት ዕድሜ፡(ባለፈው ዓመት የ­6 እና የ­4 ዓመት) ከወላጆቿ አስጠግታ፤ ከምትኖርበት ከተማከተወሰኑ ጓደኞቿ ጋር በባቡር ተሳፍራ በስዓቱ ከተባለው ቦታ ቴል አቪቭ በመድረስ ከሌሎች ከሰላማዊ ሰልፈኛው ጋር በመሆን፤ በሳዑዲ ዓረብያ ጭካኔ የተጐዱትንና የሞቱትን ኢትዮጵያኖች ፎቶ በማንገብ፤ የኢትዮጵያው መንግሥት ለዜጐቹ ግድ ሳይሰጠው ዝም ማለቱ በጣም ስለአንገበገባት፣ የዲሞክራሲ መብቷን በመጠቀም በጉዳት ላይ ላሉት ወገኖቿ ስትጮህላቸውና ድምጿን ስታሰማ ዋለች፡፡

ታዲያ ከሰላማዊ ሰልፉ አንድ ሳምንት በኋላ (በሳምንቱ ዓርብ) “IETV” በተባለው ቴሌቪዥን ይህችን ወጣት ያልተናገረችወን በኤዲቲንግ የተቀነባበረ ፕሮግራም ቀረበ። (የኢዲቲንግ ዕውቀቱ ወይም ሙያው ያለው አቆራረጡንና አቀጣጠሉን ይረዳል)ይህን ፓርት/ክፍል ተመልከቱ፤ፊልሙ ተጀምሮ እስኪያልቅ “ሰባት” (7 ጊዜ)ይህ ቃል በፕሮግራሙ ተደጋግሟል። ለምን? ተደጋገመ የሚለውን የፍርዱ ሁኔታ ሲያበቃ ከህግ ጠበቃዋና ከወጣቷ ጋር ፈቃደኛ ከሆኑ በቃለ መጠየቅ ከአንደበታቸው እንሰማለን የሚል እምነት አለኝ። እንደ ባለመያ እስኪ የራሴን አስተያየት ጠቆም አድርጌ ልለፍ፤

1ኛ) እንደዚህ ዓይነት ነገር ልጅቱ ከተናገረች፣ መሆን ያለበት ሙሉ ንግግሯን ከነመልኳ ማቅረብግዴታ ነው፤ ከዚያ በኋላ ቋንቋ ልማይረዱ ትክክለኛ ትርጉሙን ማቅረብ የሙያ ግዴታ ነው፣

2ኛ) በጋዜጠኛ ህግናደንብ መሰረት “Sling” ወይም “የመንገድ ቋንቋ” ብሎ ነገር የለም። ለህዝብ መቅረብ ያለበት “እውነተኛና ሃቅ ብቻ እና ሃቁ ብቻ ነው”፤ ምክንያቱምሚዲያ የአንድ ሃገር ህዝብ ጠበቃ ማለት ነው፣ወደ ታሪኩ ልመልሳቸሁ፣ ይህን የተላለፈ ፕሮግራም ያዩ ዘመድ አዝማድና ቤተሰቦቿ ”እንዴት ፋሲል ይገደል ትያለሽ?” “ለምን ልጆችሽን ዝም ብለሽ አታሳድጊም?” እያሉ
ሲያዋክቧት በመደናገጥ በጣም ተረብሻ ወዲያውኑ የሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊ የነበሩትን ስታማክር፤ በመጀመሪያ እንድትረጋጋ ከመከሯት በኋላ፡
ፕሮግራሙን በኢንተርኔት በማየት በፍጹም ቃላት የተለቃቀመበት የተቀጣጠለ ስለሆነ፤ ቴሌቪዥኑንና አቅራቢውን “በስም ማጥፋት” የሚያስወነጅል እንደሆነ ገለጹላት። ይህች የ­31 ዓመት ወጣት የኢኮኖሚ ችግር እንዳለባትና ልጆችዋን ብቻዋን እንደምታሳድግ ስታማክር፤ የተወሰኑ ከተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉ የተሳተፉ በመመካከር ወደ­5 የሚሆኑ ገንዘብ በማዋጣት ከፍለውላት“ፒኒ ጌልዓድ” የተባለ የሀግ ጠበቃ እንድትይዝ ሆነ።

በተላለፈው ፕሮግራም ላይ እንዳያችሁት፦የሀግ ጠበቃዋ በህጉ መሰረት ክሱን ጀመረ፣ “IETV” ወዲያውኑ ከኢንተርኔትና ከፌስ ቡክ ላይ ሙሉ ፕሮግራሙን አወረደው፤ ነገር ግን እንደዚህ ዓይነት ፕሮግራሞችን እያወረደ የሚያስቀምጥ የተጠናከረ የወጣቶች ቡድን ቀድሞ ቀድቶ አስቀምጦታል።ክሱ ተጀመረ ብያለሁ፤ እናስ ማለታችሁ አይቀርም፤ እናማ የቴል አቪቭ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ የከሳሽና ተከሳሽን የህግ ጠበቆችን ቃል ከሰማ በኋላ፤ እንደ እሥራኤል ህግና ደንብ መሰረት የሚቻል ከሆነ ሁለቱ የከሳሽ የህግ ጠበቃና የተከሳሽ የሀግ ጠበቃ በጋራ ተስማምተው እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ገለልተኛ ለሆነ የሀግ ጠበቃ ሁኔታውን በመካከላቸው ሁና ከህግ አንጻር እንድታሸማግል “Court Mediators” ዘንድ ተላኩ። እዚያ መስማማት ባለመቻላቸውም በአለፈው ኦጐስት/ነሃሴ 2014 ወረዳው ፍ/ቤት ቀርብው ነበር።

ታዲያማ የተከሳሽ ጠበቃ ለዳኛው በ”ይፋ” ከሳሾችና ተከሳሾች በተገኙበት(በ”ይፋ” የሚለው ይሰመርበት) በመከራከሪያነት የተጠቀመው (የ“IETV” የህግ ጠበቃ በሂብሪው የተናገረውን ቃል በሂብሪውና በእንግሊዝኛ ላስቀምጠው) በሂብሩ የተጠቀመው ቃል “להבהיר” (Apologize) ከማለቱም በተጨማሪ፤ ከሳሿ ፈቃደኛ ከሆነች በዚያው ቃለ መጠይቅ ልናደርግላት እንችላለን ሲል የመከላከያ መልሱን አቅርቧል። የወጣቷ የህግ ጠበቃ ግን በወጣቷ ማህበራዊ ህይዎትም ሆነ የሥነ ልቦና ላይ ከፍተኛ መረበሽና አለመረጋጋትን ስላስከተለባት፤ ሆን ተብሎ በወጣቷ ላይ የተክናወነ የስም ማጥፋት ዘመቻ ስለተካሄደ፤ ለድርጊቱ “IETV” ይቅርታ ከመጠየቅም ባሻገር የሥነ ልቦና ጉዳት ካሳና የህግ ጠበቃዋን ወጭ ሊከፍል ይገባዋል ሲል መልስ ሰጥቷል።

ዳኛውም ወጣቷን ተከሳሾቹ በሚሉት ትስማማ አትስማማ እንደሆን ተጠይቃ፤ በ­“IETV” ምን ዓይነት ቃለ ምልልስ እንደማትሰጥና፣ ይህ ቴሌዥን በህይወቴ ላይ ከፍተኛ የሆነ መጥፎ አሻራ ያጣለባት መሆኑንና፤ የተለያዩ ዛቻና ማስፈራሪያዎች ከተለያዩ ክፍሎች የደረሳት መሆኑንም ለፍ/ቤቱ አስረድታለች። ፍ/ቤቱም ለ­19.01.2015 ቀጥሯል። ችሎቱ ክፍት ስለሆነ ማንም ሰው የዲሞክራሲ መብቱን ተጠቅሞ መገኘት ይችላል። ቦታው ቴል አቪቭ ወረዳ ፍ/ቤት ነው፤ “ቫይጽማን ጎዳና 1 ­ ቴል አቪቭ“ ትክክለኛውን ስዓትና ቀን ቀኑ ሲቃረብ እናሳውቃለን። ለወገን ደራሽ ወገን ነው ብላ ድምጿን ለማሰማት ወጥታ ሥነ ልቦናዊ ድቀት ለደረሰባት ወጣት እህታችን፤ ፍትህና ዲሞክራሲ ያለበት ሃገር ያለሽ በመሆንሽ ሁላችንም መልካሙን ሁሉ እንመኝልሻለን!!
ሐና መከተ – ጋዜጠኛ እሥራኤል

የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ሊያደርገው ላቀደው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግለት፣ ህዳር 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ መጠየቁ የሚታወስ ቢሆንም አስተዳደሩ በቁጥር አ.አ/ከፅ/10/30.4/55 ህዳር 19 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው የመልስ ደብዳቤ ለሰላማዊ ሰልፉ እውቅና አለመስጠቱን አስታውቋል፡፡

ትብብሩ ለሰልፉ የመረጠው ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን፣ አስተዳደሩ በበኩሉ የ24 ሰዓቱን ሰልፍ ላለማወቁ ምክንያት ነው ያለውን ሲያስቀምጥ፣ ‹‹የተጠየቀው ቦታ በልማት ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅና ትላልቅ የመንግስት ተቋማት እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ያሉበት ስለሆን ጥያቄውን ተቀብለን ለማስተናገድ የምንቸገር መሆኑን እየገለጽን፣ የአደባባይ ስብሰባውም ሆነ ሰላማዊ ሰልፉ እውቅና ያልተሰጠው መሆኑን እናስታውቃለን›› በማለት አስፍሯል፡፡

የትብብሩን ሰልፍ እያስተባበሩ ያሉት ፓርቲዎች አመራሮች ዛሬ ለአስተዳደሩ በጻፉት ደብዳቤ እንደጠቀሱት ደግሞ፣ የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 3/1983 አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 2 “የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት በዚህ አዋጅ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 1 የተመለከቱትን ሁኔታዎች በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ሥፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለው ምክንያቱን በመግለፅ ይህንኑ ጥያቄው በደረሰው በ12 ሰዓት ውስጥ በጽሁፍ ለአዘጋጁ የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ጊዜም ወይም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም” በማለት አስተዳደሩ እውቅና የመንፈግ ስልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
Image
በመሆኑም፡-
‹‹1ኛ. እውቅና እንዲሰጥ የተጠየቀ ማንኛውም አካል ከላይ የተደነገገውን በማገናዘብ ለሌላ ጊዜና በሌላ ቦታ እንዲደረግ ሃሳብ ከማቅረብ ውጭ ሰላማዊ ሰልፉ ምን ጊዜም ወይም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ለማለት ለመስሪያ ቤታችሁ ስልጣን ያልተሰጠ በመሆኑ፤
2ኛ. ሰላማዊ ሰልፉና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የሚከናወኑት በመሰረታዊነት ለትላልቅ የመንግስትና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ለማሳወቅ በመሆኑ በእነዚህ አካባቢ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ማድረግ በአዋጁ ያልተከለከለ በመሆኑ፤

ለጥያቄያችን የተሰጠን መልስ ከምክንያታዊነትና ህጋዊነት ውጭ ሰልፉ እንዳይካሄድ ለመከልከል ስለሆነ እንዲህ ዓይነቱን ኢ-ህጋዊ የሆነ ውሳኔና አሰራር ፈፅሞ የማንቀበል በመሆኑ አስቀድመን ባሳወቅነው መሰረት ሰላማዊ ሰልፉን በተጠቀሰው ቀን፣ ሰዓትና ቦታ የምናካሂድ መሆኑን እያሳወቅን በጽ/ቤታችሁ በኩል አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግልን በድጋሚ እናስታውቃለን›› ብሏል ትብብሩ ዛሬ ለአስተዳደሩ በጻፈው ደብዳቤ፡፡

ሰዎች በማንኛውም መንገድ ሸብረክ ሸብረክ የሚሉ ከሆነ መርህ አልባ መሆናቸውን ከማሳየት ውጭ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ ባለፈው ሳምነት ፍኖተ ነፃነት ላይ ወጣቱ ፀሃፊ ኢዮኤል ፍስሃ ዳምጤ ለምን እንደምንፈራ ቁልጭ አድርጎ አሳይቶን ነበር፡፡ የገዢዎቻችን በትር የበረታብን በእነርሱ ጥንካሬ ሳይሆን ከፍርሃት በመጣ ዝምታችን እንደሆነ አስምሮበታል፡፡ መፍትሔውም ከፍርሃት መላቀቅና ዝምታውን ማፍረስ ነው፡፡ በዛሬው ፅሁፌ ማንሳት የፈለኩት ደግሞ ለምን […]

በእርግጥም “ እንዲህ እንደዋዛ ሲጠሩት ቀላል ይመስላል ቃሉ፤ እረ ሁላችሁም፤ አገር አገር በሉ፤ አገር አገር በሉ”። የምትለዋ ስንኝ በጋራ ስንላት ንዝረቷ ለጉድ ነበር። ተመኩሮዬን ያኔ ቆርጦ ሰልፉ ላይ የነበረ በቅርብ ፅፎ አስታወሰኝ። “ተርቲብ” የምትለዋን ቃል ትርጉም እስካሁን ስለማላውቅ ሙሉ መልክቱን በእርግጥ በትክክል አልረዳውም። ያም ሆኖ “ተርቲብ፤ አላህ ዋአክበር”። በጋራ ስትሉት ሲያምር። ምጥን ያለና ጉልበታም ነበር። […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
——
የልጅ እያሱ ሞት ይፋ የወጣው በህዳር ወር 1928 ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ወደ ማይጨው ከመዝመታቸው ሶስት ቀን አስቀድሞ ነው። በአሟሟታቸው ዙሪያ ከሚነገሩት መካከል
·        ልጅ እያሱ የተገደሉት ሀረር ውስጥ ነው::
·        ልጅ እያሱ የተገደሉት አዲስ አበባ ገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ውስጥ ሲሆን የተቀበሩትም ከቤተ መንግሥቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ከሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ክልል ነው::
·        ልጅ እያሱ የቀብራቸው ስነ-ስርዓት የተከናወነው ደብረ ሊባኖስ ነው::
·        ልጅ እያሱ የተቀበሩት ሰንዳፋ ውስጥ ነው የሚሉት ይገኙባቸዋል።
የልጅ እያሱን አሟሟት አውቃለሁ በማለት እማኝነታቸውን ከሰጡ ግለሰቦች መካከል አገልጋያቸው የነበሩ አዛውንት ኢጣሊያኖች አቤቶ እያሱን ከጋራሙለታ እስር ቤት ለማስወጣት ሙከራ አድርገው እንደነበር በመግለጽ እንዲህ ይላሉ።
 
 “የኢጣሊያ ወኪሎች አባጤናን ከግራዋ እስር ቤት ለማስወጣት ከሞከሩ ጀምሮ ልዑልነታቸው በእስር ቤቱ ክልል እየተከዙ ወዲያ ወዲህ ይንጎራደዱ ነበር። አንድ ቀን ምሽት አንዲት አውቶሞቢል ወደ እስር ቤቱ መጣች። እርሳቸውም ይፈሩት የነበረው ሰው መኖር አለመኖሩን ጠየቁ። በቀጣዩ ቀን “የመጡት አባ ሐና ብቻ ናቸው” አልኳቸው። ነገር ግን ጥቂት ዘግይቶ ሁለተኛዋ አውቶሞቢል ሁለት ሰዎችን አሳፍራ መጣች። ከሁለቱ አንዱ ፊታውራሪ ነበር። እስኪጨልም ቆይተው እያደቡ ወደ እስር ቤቱ ተጠጉ። መዝጊያው ሰፋፊ ስንጥቆች ያሉት በመሆኑ ልዑልነታቸው በስንጥቆቹ ውስጥ አዘውትረው ምራቃቸውን ጢቅ ይሉ ስለነበር ሲያነጣጥሩባቸው ሳያዩአቸው አልቀረም። በተኮሱባቸው ጊዜ የመስኮቱን መቃኖች ጨምድደው ጨበጡ። ኃይለኛ ስለነበሩ ቤቱን በሙሉ ያናጉትና የሚናድ መስሎኝ ፈርቼ ነበር። ተንገዳግደው ወለሉ ላይ ሲወድቁ ሰማሁ። ሬሳቸው በባቡር ተጭኖ ወደ አዲስ አበባ ከመወሰዱ በፊት ሁለቱ ነፍስ ገዳዮች እንደ ባላዛር ሬሳቸው ላይ ተጎንብሰው አጓሩ። ሬሳቸው አዲስ አበባ እንደደረሰ ከፍተኛ ባለስልጣን ለባላምባራስ አበበ አረጋይ አስረከቡ። እንግዲህ ሬሳቸው ለዘላለም ያረፈበትን ቦታ የሚያውቁት ባላምባራስ አበበ አረጋይ ብቻ ናቸው። ይሁንና እኒሁ ሰው ደግሞ በ1953 በተሞከረው የመንግሥት ግልበጣ ጊዜ የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው ነበርና በአረንጓዴው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ታዛ ወለል ላይ ደማቸው ፈስሶ ሞቱ። አባ ሃና ጂማም ተመሳሳይ እጣ ገጠማቸው”።
    እንደ አዛውንቱ ምስክርነት ከሆነ አባ ሐና ጅማም ሆነ አበበ አረጋይ የልጅ እያሱን አስከሬን በተረካከቡበት ቦታ ላይ ስለተገደሉ ምስጢሩ አብሮ ሞቷል ማለት ነው።
ሌላኛዋ ለቤተ መንግሥቱ ቅርበት ያላቸው ሴት ደግሞ ለጎበዜ ጣፈጠ እንዲህ ብለው ነበር የተናገሩት (“አባ ጤና እያሱ” ከተሰኘው የጎበዜ ጣፈጠ ድርሰት የተወሰደ ነው)።
    “ዕለቱን አላስታውስም። ቢሆንም ልጅ እያሱ አርፈዋልና ቤተ መንግሥት እንድትመጡ የሚል መልዕክት ተላለፈ። እኛም ማልደን ወደ ቤተ መንግሥቱ ሄድን። አዲስ አበባ ውስጥ የምንገኝ ወይዛዝርትና መኳንንት ተሰብስበን ስንላቀስ ዋልን። ሬሳ ግን አልነበረም። እቴጌ መነን በጣም አዝነውና ተክዘው እንባቸውን ያፈሱ ነበር።  ጃንሆይ በርኖሳቸውን ገልብጠው ደርበው ወንድሜ ወንድሜ በማለት ያለቅሱ ነበር።”
ልጅ እያሱን በታሸገ ባቡር አሳፍሬ ወደ አዲስ አበባ ልኬአቸኋለሁ በማለት እማኝነታቸውን የሚሰጡት ብላቴን ጌታ ዶ/ር ሎሬንዞ ታዕዛዝ በበኩላቸው የቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ቄስ የነበሩ ገ/መድህን የተባሉ ግለሰብ እንዲህ በማለት ነግረውኛል ይላሉ።
“በቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ትይዩ የዱክ ቤት ይባል በነበረው ህንጻ ሰገነት ላይ አንድ እጆቹን በሰንሰለት የታበተ ሰው ከቀትር በኋላ ዘወትር ሲመላለስ እናየው ነበር። ነገር ግን ጃንሆይ ወደ ጦርነቱ ከመዝመታቸው በፊት ሌሊቱን ጸሎተ ፍትሐት እንድናደርግ ታዘዝን። ሆኖም የሟቹን ሰው የክርስትና ስም የሚነግረን አልነበረም። ከዚያ በኋላ ያ ሰውዬ ይመላለስበት ከነበረው ሰገነት ላይ አልታየም። እኛም የሞቱት ልጅ እያሱ እንደሆኑ ተረዳን።
(ምንጭ፡- ጎህ መጽሄት፣ ቅጽ 1 ቁጥር 5፣ ጥቅምት 1993፣ ገጽ 6/22)
—————–
ለዚሁ መጽሄት ቃለ-ምልልስ የሰጡት የልጅ እያሱ የልጅ ልጅ ፕሮፌሰር ግርማ ዮሐንስ እያሱ ቄስ ገ/መድሕን የተባሉት ሰው ከሰጡት ምስክርነት ጋር የሚጣጣም ቃል አሰምተዋል። ፕሮፌሰር ግርማ እንዳሉት ልጅ እያሱ በስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ባለው የዱክ ቤት (አሁን Law Faculty ዋና ህንጻ የሆነው) መታሰራቸው እውነት ነው። “አጼ ኃይለ ስላሴ ወደ ማይጨው ሀሙስ ከመዝመታቸው በፊት ማክሰኞ ሌሊት ልጅ እያሱ ተገድለው አሁን የዩኒቨርሲቲው የእግር ኳስ ሜዳ ከሆነውና ያኔ የቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን አጸድ ከነበረው ስፍራ ተቀብረዋል” ይላሉ ፕሮፌሰር ግርማ።
—————
አፈንዲ ሙተቂ
ሰኔ 22/2005
ሀረር- ምስራቅ ኢትዮጵያ

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

1- ሁለቱም በፈጣሪ አያምኑም ( የራሴ የሚሉት እምነት የላቸውም)
2- የጦር አዛዦቻቸው::ሂትለር በራሱ ግዜ ሮሚዮን ማርሻል አድርጎታል –መለስ ሳሞራን < ጀነራል> አድርጎታል
3-ሂትለር ሁለት ልጅ ነበረው::መለስም ሁለት ልጆች አሉት
4-ሁለቱም በጅምላ ህዝቦችን ጨርሰዋል (የዘር ማጥፋት ፈጽመዋል)
5-ሁለቱም insomnia ይሰቃዩ ነበር :; ( የመተኛት ችግር ከተኙም ቶሎ አለመንቃት)
6-ሁለቱም የሶሻሊዝም issue ነበራቸው:;ለዚህም ማሌሊትን ልብ ይልዋል
7- በዘር እና በጎሳ ላይ የተመሰረተ ፓርቲ በመፍጠርም ይታወቃሉ ::
8-ሂትለር ታላቅዋን ጀርመን ለመመስረት እቅድ የነበረው ሲሆን መለስ ደግሞ ታላቅዋን ትግራይን ..
9-E -ዲሞክራሲ ናቸው
10-ራሳቸውን በራሳቸው የፓርቲ እና የአገር መሪ አድርገው ሾመዋል Dagem Ahunem

Image

Eyasped Tesfaye…….(የግል ዕይታ)
‹‹……ሪቮሉሽን የአዳራሽ ዙሪያ አመፅ አይደለም፤ የሰፊው ህዝብ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ሰፊው ህዝብ ካልተሳተፈበት፣ ካልደገፈው፣ አይሆንም፤ አይፀናምም፡፡ የጥቂቶች አመፅ በሌሎች ጥቂቶች አመፅ ይገለበጣል፡፡ መሰረታዊ ለውጥ፣ በሰፊው ህዝብና በጨቋኝ መደቦች መካከል የሚካሄደው የትግል ፍሬ ነው፡፡….››ዴሞክራሲያ ቅፅ1 ቁ15
የኢትዮጲያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በ1993 ያሳተመው አማርኛ መዝገበ ቃላት አብዮት የሚለውን ቃል ‹‹በአንድ ነገር ክስተት ወይም ሂደት ውስጥ ያሉ ቅራኔዎች ተካረው ከፍተኛ ደረጃ ላይ ሲደርሱ የሚፈጠር መሰረታዊ ለውጥ፤ አዲስ ከፍተኛና የተሻለ ነገር፤ ክስተትና ሂደት ወይም አስተሳሰብና እውቀት የሚከሰትበት፡፡›› የሚል ትርጓሜ ይሰጠዋል፡፡
አብዮት በተለያየ የታሪክ ወቅት እንዲሁም በተለያየ ቦታ ተከስቷል፣ እየተከሰተ ነው፤ ወደፊትም ይከሰታል፡፡ ከፈረንሳይ አብዮት እስከ ሩሲያው አቢዮት፤ ከላቲን አሜሪካ ሀገሮች እስከ ሩቅ ምስራቅ እስያ ብሎም እስከ አረቡ አብዮት፤ የአብዮት ንፋስ ያልነፈሰበት የአለማችን ክፍል የለም፡፡ በተለያዩ ቦታዎች የተካሄዱ አብዮቶች እንደወቅቱ እና እንደቦታው የራሳቸው የሆኑ መለያዎች ያሏቸው ይሁን እንጂ ሁሉም የሚጋሯቸው የወል የሆኑ ባህርያትም አሏቸው፡፡ ይኸውም ሁሉም አብዮቶች በጭቆና ማህፀን ውስጥ ተፀንሰው መወለዳቸው ነው፡፡
አብዮቶች ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ አሊያም ኢኮኖሚያዊ መነሾ ምክንያቶች ሊኖሯቸው ይችላል፡፡ ለምሳሌ ታሪካዊውን የፈረንሳይ አብዮት ያየን እንደሆነ ሶስቱም መነሾ ምክንያቶች እንደነበሩት እንረዳለን፡፡ የፈረንሳይ ህዝብ በፈላጭ ቆራጭ ንጉሳዊ አስተዳደር ስር ሆኖ መብቶቹን መገፈፉ የአብዮቱ ፖለቲካዊ መነሾ ሲሆን፤ በፈረንሳይ ህዝብ መካከል የነበረው የመደብ ልዩነት በተለይም አብዛኛው የፈረንሳይ የህብረተሰብ ክፍል በድህነት የሚማቅቅበት እና መብቱን የተነፈገበት ሶተኛው መደብ ውስጥ መካተቱ የአብዮቱ ማህበራዊ መነሾ ሆኗል፡፡ እንዲሁም ደግሞ በወቅቱ ፈረንሳይ በከፍተኛ የኢኮኖሚ ድቀት ውስጥ መገኘቷ እና በዜጎች ላይም ያለው የግብር ጫና ከፍተኛ መሆኑ የአብዮቱ ኢኮኖሚያዊ መነሾ ሆኗል፡፡
አብዮቶች አብዛኛውን ጊዜ በገዢው መደብ በኩል ሳይጠበቅ የሚከሰት ክስተት ነው፡፡ ለዚህም ነው የሩቁ የፈረንሳይ አብዮትም ሆነ የቅርብ ግዜው የአረቡ አለም አብዮት አለምን ያስደነቀው፡፡ አንዳንድ አብዮቶችን ትልልቅ የስለላ ተቋማት(ሲ.አይ.ኤ፤ ኬጂቢ) ሳይቀር ያልጠበቁት ክስተት እንደነበር ታሪክ ያስገነዝበናል(መሀመድ ሬዛን ያስወገደውን የኢራኑን አብዮት ልብ ይሏል)፡፡ ይህ የሚሆንበትን ምክንያት ቲሙር ኩራን የተሰኘው ፀሀፊ ‹‹sparks and praire fires: a theory of unanticipated political revolution›› በተሰኘው ፅሁፉ ላይ በአለማችን ላይ የተከሰቱትን ሶስት ዋና ዋና አብዮቶችን እንደምሳሌ በማንሳት ህዝብ የተቃውሞው ወገን እስኪጠናከር ድረስ በገዢው ወገን ላይ ያለውን ጥላቻ በውስጡ ደብቆ መያዙ አብዛኛውን ግዜ ገዚዎችን እንዲዘናጉ እንደሚያደርጋቸው ገልፆ አብዮቱ አንድ ግዜ ከፈነዳ በኋላ ለማስቆም አስቸጋሪ የሚያደርገውም በህዝብ ዘንድ ስር የሰደደ እና የቆየ ጥላች እና ቅራኔ መኖሩ እንደሆነ ያስረዳል፡፡
ለአብዮት መነሳት ምክንያቱ ከላይ የዘረዘርናቸው ቅራኔዎች(ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ) ቢሆኑም ከእነዚህ ሁሉ ቀድሞ የሚመጣው ግን የህብረተሰቡ የንቃተ ህሊና(enlightenment) ጉዳይ ነው፡፡ በላቲን አሜሪካ የተካሄዱት አብዮቶች ላይ ጥናት ያካሄዱት እንደ ዴቪድ ክሎስ ያሉ ምሁራኖች ለአብዮቱ መነሳት ዋና ምክንያት አድርገው የሚያቀርቡት የህብረተሰቡ ንቃተ ህሊና መዳበሩን እና በሌሎች ሀገራት የተካሄዱትን አብዮቶች ከራሱ ሀገር ነባራዊ ሁኔታ ጋር ማስተያየት እና ማገናዘብ መቻሉ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
በሀገራችን በኢትዮጲያም ተከስቶ የነበረውን የ66ቱን አብዮት ያየን እንደሆነ በአለም ዙሪያ የነበረው ሁኔታ በወቅቱ የነበሩትን ወጣቶች ላይ ተፅእኖ ማሳደር መቻሉ እና የወጣቱ ንቃተ ህሊና የዳበረ መሆኑ ከነበረው ጭቆና ባሻገር ለአብዮቱ መነሳት አበይት ምክንያት ነበር፡፡
እነዚህን ከላይ የዘረዘርናቸውን የአብዮት መነሾዎች ይዘን የሀገራችን ነባራዊ ሁናቴ ካጤንን በኢኮኖሚው በፖለቲካውም ሆነ በማህበራዊው ዘርፍ ያለው ከፍተኛ የሆነ ምስቅልቅል እና ብሶት ለአብዮቱ መነሳት በቂ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ነገር ግን መረጃ የማግኘት መብቱን የተነፈገው ሰፊው የህብረተሰብ ክፍል መብቱን በማስከበር ዙሪያ ላይ ያለው የንቃተ ህሊና መዳበር በጥያቄ ውስጥ ያለ ጉዳይ ይመስለኛል፡፡
የቡርኪና ፋሶው የአብዮት ንፋስ በፍጥነት ወደ ቶጎ እና ጋቦን ተዛምቶ አምባገነን መንግስታትን ሲያንቀጠቅጥ ይህንን ጀብዱ የሰማው የኢትዮጲያ ህዝብ ምን ያህል ነው; ሰምቶስ ወስጡን የኮረኮረው እና መንፈሳዊ ቅናት ያደረበት ስንቱ ነው; የሚለው ጉዳይ ያሳስበኛል፡፡
በእኛ ሀገር አብዮት እንዲነሳ ካስፈለገ አብዮቱ መሪ ያሻዋል፡፡ በቡርኪና ፋሶም ሆነ አሁን በቶጎ እና በጋቦን የተነሳው ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ናቸው እየመሩት ያሉት፡፡ በእኛም ሀገር ባለው ተጨባጭ ሁናቴ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አስተባባሪነት ውጪ በአሁኑ ሰዓት በራሱ የሚፈነዳ አብዮት ይኖራል ብሎ መገመት አስቸጋሪ ነው፡፡ ነገር ግን ተቃዋሚዎች
1ኛ፡- ለህዝብ ወቅታዊ መረጃዎችን በማቀበል እና በመተንተን የህዝብን ንቃተ ህሊና የሚያሳድጉበትን መንገድ መቀየስ ይኖርባቸዋል፡፡
2ኛ፡- በህዝብ ዘንድ ያላቸውን ቅቡልነት በማሳደግ የሚሞትላቸው ድርጅቶች መሆናቸውን ማረጋገጥ አለባቸው፡፡
Image

በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን ወሲባዊ ጥቃት አሳሳቢ ነው ተባለ። በ17 ዓመቷ ታዳጊ ሐና ላላንጎ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈጽሞባት ህይወቷ ካለፈ በኋላ ድርጊቱ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ቁጣን ቀስቅሷል።

Image

ሠማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች የአንድነት መድረክ በመፍጠር ሰላማዊ ሰልፍ ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ/ም ለማድረግ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልፀው የሐገሪቱ ህዝብ በቦታው በመገኘት ድምፁን እንዲያሠማ ባሳወቁት መሠረት የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሠማ ጊዜያዊ ኮሚቴ እና የማህበሩ አባላት በሠላማዊ ሠልፉ ላይ ከሌላው የሐገራችን ህዝብ ጋር በመሆን ድምፃችንን እንደምናሠማ እየገለፅን ለሠላማዊ ሠልፉ መሣካት የበኩላችንን ደርሻም ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን ስንገልጽ በዚህ በጨለማ ዘመን ኃላፊነት ወስደው ይህንን ታላቅ ሠለማዊ ሠልፍ ላዘጋጁት የሠለማዊ ሠልፉ አዘጋጆች ምስጋናችንን በማቅረብ ነው፡፡
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያን እያስተዳደሩ ሳይሆን እየገዙ ያሉት ብዙሀኑ ባለስልጣናት ከትምህርት አለም እርቀው ወደ ትግል የገቡ እና አሁንም ቢሆን በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እና የተሻለ ንቃተ ህሊና ያለው ሰው እንዳይፈጠር ትግል ላይ ናቸው በተለይ ለመምህራንና ባጠቃላይ ለትምህርት ስርአቱ ያላቸው ጥላቻ ላቅ ያለ ነው ይህንን እንኳን ስላልተማሩ ነው ብለን እንዳናልፈው የስርአቱ አመራሮች እና አጃቢዎች አለማወቃቸውንም ሊደብቁ ፍቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ሟቹ መለስ ዜናዊ በህይወት ያለው ተፈራ ዋልዋ መምህራኑን ለማሰደብ አፋቸውን ከፍተው ባዶነታቸውን በነጻ ሲያስኮሞኩሙን ኖረዋል፡
እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ መምህር እንደሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ ጥርስ ውስጥ ከገቡት መካከል ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል፡፡ ገዢው የወያኔ ቡድን ጠንካራውን የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር በማፍረስ ተለጣፊ ማህበር ከማቋቋም አልፎ ታላላቅ የማህበራችንን አመራሮች ከአሰፋ ማሩ ጀምሮ በመግደል በተለያዩ ጊዜያት ከኢትዮጵያዊው መምህር ሊነሱ የሚችሉ ተቃውሞችን ለማፈን ጥረት ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል በ2004 እንኳን የደመወዝ ጭማሪን ተከትሎ በተነሳው የመምህራን ጥያቄ መብታችን ይከበር ያሉ የማህበራችንን አባላት ከስራ ማባረር ጀምሮ ለእስር መዳረጉ የሚታወስ ሲሆን ይህም ሳያንስ በወቅቱ ከአንድ የሐገር መሪ ነኝ ከሚል ግለሠብ የማይጠበቅ ንግግር ከቀድሞው የሐገራችን አምባገነን ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ በሐገራችን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መስማታችን ይታወሳል ይህ በወያኔ አመራች ዘንድ ያለውን ከፍተኛ ንቀት እና ፍርሐት የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ውስጣዊ ፍርሀት የተነሳ በርካታ መስራት የሚችሉ እና ሀገሪቱን ሊቀይሩ ምሁራንን እንዲሰደዱ በማድረግ ያልተሰደዱትን ደግሞ በማሰር እና በማንገላታት የመምህርነትን ሙያን እንደማሰሪያ ብሎም አነስተኛ ደመወዝ በመክፈል የመምህራኑ አእምሮ በማጀት ወሬ እንዲጨናነቅ ማድረጉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡
ከሰሞኑም ይህንን ውስጣዊ ፍራቻውን ለካድሬዎቹ በመመሪያ መልክ በመስጠት በየት/ቤቱ የሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባላት ያልሆኑ መምህራንን ስማቸውን ከተለያዩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በማያያዝ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ሲያቀርብባቸው ሰንብቷል በተለይ የግንቦት ሰባት እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቹህ በማለት በየእለቱ ዛቻ የሚደርስባቸው መምህራን ቁጥር እጅግ ከፍተኛ ነው በተለይ ከሰሞኑ የአባይ መዋጮ እንደአዲስ ለማስከፈል የሚደረገውን ጥረት ተከትሎ በተነሳው የመምህራን ጥያቄ በመምህራን ላይ የሚደርሰው መከራ እና ግፍ መጠኑ ጨምሯል፡፡
ስለሆነም የዚህ የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ለትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩን ቢያሳውቅም እልባት ሊያገኝ አልቻለም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴሩም ለጉዳዩ እልባት ከመስጠት ይልቅ የአባዬን ወደእምዬ እንዲሉ በኮሚቴው አባላት ላይ ወቀሳ እና ማስፈራሪያ አቅርቧል ይኸውም ወትሮውም በትምህርት ሚኒስቴር ላይ አመኔታ ያልነበረውን ኮሚቴ ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ከሚታገሉ ሌሎች የሙያ ማህበራት እና ፓርቲዎች ጎን እንዲሠለፍ አድርጎታል በዚህም የተነሳ የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ኮሚቴ አባላት በሰልፉ ላይ እንደምንገኝ ቃል እየገባን ሌላው የሀገራችን መምህርም ከጎናችን በመሆን በሠላማዊ ሠልፉ ላይ ይገኝ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የኢትዮጵያ መምህራን ድምጽ ይሠማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
ህዳር 21/2007
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ማስታወሻ፡ ይህች ጽሁፍ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከተከሰሰባቸው ሁለት መጣጥፎች አንደኛዋ ናት። በመጭው ወር በአሶሳ የሚደረገውን የብሄር ቀን ድራማ እሳቤ በማድረግ – በርካታ አንባብያን በጠየቁት መሰረት እነሆ በድጋሚ ለንባብ አቅርበናል። – ክንፉ አሰፋ – “እኛ ጭቁን ብሄረሰቦች ከዚህ ቀደም በየሰው ቤት ተቀጥረን የምንሰራ፣ አሽከሮች እየተባልን ነበር የኖርነው። አሁን ግን ይኸውና ህገ-መንግስታችን መብታችንን ሰጥቶናል… ኑሯችንም ተሻሽሎ ዛሬ […]