የደቡብ ሱዳን የተራዘመ ጦርነት በሀገሪቱ እና በአጎራባች ሃገራት ላይ የሚያስከትለዉን የኤኮኖሚ ወጪ የመዘነ ዘገባ ቀረበ። እንደዘገባዉ የደቡብ ሱዳን የእርስ በርስ ግጭት በዚህ ይዞታ ከአንድ እስከ አምስት ዓመታት ከቀጠለ ከ22,3 እስከ 28 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር አዲሲቱን ሀገር ያሳጣታል።

በነገረ ኢትዮጵያ • ፖሊሶች የደረጃ እድገት እንደሚደረግላቸው ቃል ተገብቶላቸዋል የአማራ ክልል መስተዳደር በግንቦት 2007 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀውን አምስተኛው አገራዊ ምርጫ ተከትሎ አመጽ ከተከሰተ ለመቆጣጠር ያስችላል ያለውን ስልጠና ለክልሉ ፖሊስ፣ ለማረሚያ ቤት ፖሊስ፣ ለሚሊሻና ለመከላከያ ሰራዊት አባላት እየሰጠ መሆኑን ሰልጣኞቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ስልጠናውም፤ ለፖሊሶች በዞን እንዲሁም ለሚሊሻና ለፀጥታ ጉዳይ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌዎች እየተሰጠ […]

Image
• ፖሊሶች የደረጃ እድገት እንደሚደረግላቸው ቃል ተገብቶላቸዋል
የአማራ ክልል መስተዳደር በግንቦት 2007 ዓ.ም ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀውን አምስተኛው አገራዊ ምርጫ ተከትሎ አመጽ ከተከሰተ ለመቆጣጠር ያስችላል ያለውን ስልጠና ለክልሉ ፖሊስ፣ ለማረሚያ ቤት ፖሊስ፣ ለሚሊሻና ለመከላከያ ሰራዊት አባላት እየሰጠ መሆኑን ሰልጣኞቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ስልጠናውም፤ ለፖሊሶች በዞን እንዲሁም ለሚሊሻና ለፀጥታ ጉዳይ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌዎች እየተሰጠ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

የስልጠናው ዋና አላማ በቀጣዩ ምርጫ ሊከሰት ይችላል ተብሎ የሚፈራውን አመጽ መቆጣጠር እንደሆነ የገለጹት የፖሊስ ምንጮች በተለይ ፖሊስና ፀጥታ ጉዳይ ከ‹‹ማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ›› ጋር በመተባበር የደፈጣ ውጊያን ለመከላከል ‹‹የደፈጣ ውጊያ ስምሪት›› በሚል አጭር ስልጣና እየወሰዱ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ይህም አገር ውስጥ አመጽ ያነሳል ተብሎ ከሚፈራው ህዝብ በተጨማሪ መሳሪያ ያነሱ ተቃዋሚዎች በምርጫው ወቅት ጦርነት ይከፍታሉ የሚል ስጋት በመኖሩ ነው ሲሉ ሰልጣኞቹ ገልጸዋል፡፡ በደብረማርቆስ ውስጥ ስልጠናውን የሚወስዱት ሰልጣኞች ማታ ማታ የተኩስ ልምምድ እንደሚያደርጉ አንድ የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል ምርጫውን ተከትሎ ይከሰታል ከተባለው አመጽና ታጣቂ ቡድኖች ያደርሱታል ተብሎ ከሚፈራው ጥቃት በተጨማሪ የጥምቀት በዓል ላይ አመጽ እንዳይነሳ መከላከል፣ ከተነሳም መቆጠጠር የስልጠናው የአጭር ጊዜ ግብ ነው ተብሏል፡፡

በስልጠናው ወቅት በተለይ ፖሊሶች ‹‹ልዩ ኃይልና ፌደራል ፖሊስ በስራችን ጣልቃ ስለሚገቡ ነጻነት የለንም፣ ፖሊስ የህዝብ ነው እየተባለ ህዝብ ግን ይጠላናል፣ በህገ መንግስቱ መሰረት የህዝብን ሰላም ማስጠበቅ ሲገባን እርምጃ እንድንወስድ ከበላይ አካል እንታዘዛለን፣ ከፖለቲካው ገለልተኛ አይደለንም›› የሚሉና ሌሎች ቅሬታዎችንና ጥያቄዎችንም አንስተዋል ተብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ፖሊሶች በቂ ደመወዝና ዩኒፎርም አይቀርብልንም የሚል ቅሬታ እንዳቀረቡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በስልጠናው ወቅትም በተለይ ፖሊሶች ጠንካራ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን መሰንዘራቸው ተከትሎ ሁሉም የክልሉ የፖሊስ አባላት አንድ የደረጃ እድገት እንደሚሰጣቸው ቃል ተገብቶላቸዋል ተብሏል፡፡ ጥር 12007 ዓ.ም የጀመረው የ‹‹ፀጥታ ኃይሎች›› ስልጠና ቅዳሜ ጥር 9/2007 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከጥር 7/- ጥር 11/2007 ዓ.ም ለሚሊሻዎች አመራሮች ተጨማሪ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገልጾአል፡፡

በታህሳስ ወር የታቦት ማደሪያው ለባለሀብት መሰጠት የለበትም በሚል የባህርዳር ከተማ የክርስትና እምነት ተከታዮች አደባባይ ወጥተው ተቃውሞ ማሰማታቸው እንዲሁም በደብረማርቆስና በሌሎች የክልሉ ከተሞች ስልጠና ላይ የነበሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ስልጠናውን በመቃወም ሰልፍ መውጣታቸው በ‹‹ፀጥታ ኃይሎች› ስልጠና ወቅት መወያያ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን ሁለቱ ክስተቶች የአማራ ክልል አስተዳደር በዚህ አመት አመጽ ይነሳል የሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዲገባ ምክንያት ሆነዋል ተብሏል፡፡

በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ተነሥቶ የነበረው እሳት በደቅ ደሴት ሕዝብ፣ በገዳማውያኑና በፖሊስ ትብብር መጥፋቱ ተነገረ፡፡ እሳቱ ቁጥቋጦዎችን ከማጥፋት በቀር ደኑን እንዳላወደመው ተነግሯል፡፤ የደቅ ደሴት ሕዝብ ላደረገው አስቸኳይ ርብርብ ገዳማውያኑ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የክልሉ መንግሥትም ሄሊኮፕተር ለመላክ እስከመዘጋጀት ድረስ ያሳየውን ትብብር ገዳማውያኑና ሕዝቡ አድንቀዋል፡፡

Addis Admas

የ25 ዓመቷ አሜሪካዊት ጄድ ሲልቪስተር፤ በእርግዝና ወቅት በተፈጠረባት አምሮት መላቀቅ ዳገት ለሆነባት ክፉ ልማድ እንደተጋለጠች ትናገራለች፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ነፍሰጡር ሳለች የጀመረችው የመፀዳጃ ቤት ወረቀት (ሶፍት) የመብላት ልማድ ከወለደችም በኋላ ሊላቀቃት አልቻለም፡፡ ዛሬ ያ አምሮት ወደ ሱስ ያደገ ይመስላል፡፡ በየቀኑ አንድ ጥቅል ሶፍት…

በምድራችን ላይ የሚገኘው ሀብት ውስን (አላቂ) መሆን እና በአንፃሩ የሰው ልጅ ፍላጎት ገደብ አልባነት፣ ማንኛውም ሰው የፈለገውን ነገር በፈለገበት ሰአት እና ቀን እንዳያገኝ ምክንያት ከመሆኑም በላይ ለየትኛውም ግለሰብም ሆነ ሀገር ትልቁ ፈተና ከእጥረት ጋር የተያያዘ እንዲሆን አድርጓል፡፡ በሌላ በኩልም አንድ ሰው የፈለገውን ነገር በፈለገበት ሰአት እና ቀን አለማግኘቱ የተገደበ (ውስን የሆነውን) ገቢውን፣ ሰአቱን እና ሀብቱን ቅድሚያ ለሚሰጣቸው መሰረታዊ ነገሮቹ እንዲያውል ይገደዳል፡፡ ከላይ እንደጠቀስኩት እንደ ሀገር ትልቁ የኢኮኖሚ ዳራ በዋነኛነት ከእጥረት ጋር የተገናኘ ቢሆንም፤ በአለም ላይ ያሉ ሀገራት የየራሳቸውን ባህል፣ ሀብት (ቁሳዊም ሆነ ሰዋዊ)፣ ታሪክ ወዘተ ያገናዘበ የኢኮኖሚ ስርአት በመከተል፤ ከእጥረት ጋር የተገናኘውን ኢኮኖሚያዊ ዳራ ለመወጣት እንደሞከሩ እና እንደሚሞክሩ የኢኮኖሚ ታሪክ ላይ ትኩረት ያደረጉ ኢኮኖሚስቶች ይናገራሉ፡፡ ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ ኢኮኖሚስቶች አራት አይነት (ባህላዊ፣ የእዝ፣ የገበያ መር እና ድብልቅ) የኢኮኖሚ ስርአት እንዳለ ስምምነት ላይ ቢደርሱም፣ ከእጥረት ጋር በተገናኘ ያለውን የኢኮኖሚ ዳራ ከመፍታት እና ከመቀነስ አኳያ የትኛው የተሻለው ነው የሚለው ላይ አንድ አይነት አቋምም ሆነ ስምምነት የላቸውም፡፡ መንግስታት የህዝብን ኑሮ ለማሻሻል በሚል የሚያደርጉት እንቅስቃሴ፣ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት ሊመጣ የሚችለው የሚፈሰው ሀገራዊ ሀብት በአንድ በኩል ከወቅታዊው የሀገሪቷ ህዝብ ችግር አኳያ፣ ከዘለቄታዊ ጥቅሙ አኳያ በሌላ በኩል ለመጪው ትውልድ ከሚያስረክበው ተራፊ ሀገራዊ ሀብት አኳያ ከተገናዘበ ነው፡፡ በዚህ መንገድ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት የመምጣቱ ዋስትና በመንግስታዊ ስርአት ባህሪ ላይ የተንጠለጠለ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህም በእኔ እምነት ኢህአዴግ የሚለፍፍለትን የኢኮኖሚ እድገት በአንድ በኩል የኢኮኖሚ እድገቱ ማሳያ ተብለው የሚቀርቡትን የልማት እንቅስቃሴዎች እንደ ህዝብ ካለብን ድህነት እና የምግብ ዋስትና ማጣት አንፃር፣ ድህነታችንን በመቅረፍ የምግብ አንፃር ያላቸውን ፋይዳ፣ ዘለቄታዊ ጥቅማቸውን የሚፈስባቸውን ሀገራዊ ሀብት ማእከል ባደረገ መልኩ፤ ኢህአዲጋዊውን የልማታዊ መንግስት ስርአት መፈተሸ የሚቻል ይመስለኛል፡፡

በልማታዊ መንግስት ስርአት ውስጥ የህዝብ ሚና እስኬት ድረስ ነው?

የልማታዊ መንግስት ንድፈ ሀሳብ፣ በዋነኛነት ማእከል የሚያደርገው መንግስት በኢኮኖሚ ስርአቱ ላይ ባለው የቁጥጥር እና የተሳታፊነት ስፋት መጠን ላይ ብቻ ነው፡፡ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ማብቃት በኋላ የጃፓን እና የምስራቅ ኤሽያ ሀገራት መንግስታት በሀገራቸው ኢንደስትሪን ለማስፋፋት ኢኮኖሚ ስርአቱን ተከላካይ በሆነ መልኩ በመምራትም ሆነ በኢኮኖሚ ስርአቱ ላይ ተሳታፊ በመሆን የአንበሳውን ድርሻ ወስደዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1980 ዓ.ም የላቲን አሜሪካ ሀገራት የብድር ቀውስ እና ከ1997 ዓ.ም የምስራቅ ኤሽያ ሀገራት የገንዘብ ቀውስ፣

ከአለም- አቀፋዊነት መስፋፋት እንዲሁም ኢኮኖሚን ከማረጋጋት፣ ትምህርት፣ ጤና እና መሰረተ-ልማቶችን ከማስፋፋት አንፃር መንግስት የሚኖረውን ሚና በተመለከተ በዋሽንግተኑ መግባቢያ ሰነድ ላይ የርዕዮት አለም ልዩነት ከመፈጠሩ ጋር በተያያዘ የልማታዊ መንግስት ስርአት በ20ኛው ክፍለ ዘመን እውቅና አግኝቷል፡፡ በሌላ በኩል ከልማታዊ መንግስት ጋር አንድ አይነት የሆነ ስርአት፣ ሆላንድን የመሳሰሉ የአውሮፓ ሀገራት በ 17ኛው እና በ18ኛው ክፍለ-ዘመን ስለመተግበራቸው የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡ ይህም የሚያሳየው ልማታዊ መንግስት በሀያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረ፣ አንዳንዶች እንደሚሉት እና እንደሚያምኑት የልማታዊ መንግስትን ንድፈ ሀሳብ ኢህአዴግ የፈጠረው አለመሆኑን ነው፡፡ ‘እከሌ የሚባለው ሀገር በልማታዊ መንግስት መርህ ነው ያደገው፣ እከሌ ኒዮ-ሊበራሊስት ነው እከሌ ልማታዊ ነው’ የሚለውን የአላዋቂ ክርክር ወደጎን ትተን፣ በልማታዊ መንግስት መርህ ኢኮኖሚያቸውን በጠንካራ መሰረት ላይ በመገንባት ህዝባቸውን ከድህነት ያወጡ ሀገራትን ታሪክ እነዚህ አገራት ባህላቸውን፣ ታሪካቸውን፣ ሀብታቸውን መነሻ በማድረግ እና የፖለቲካ ልዩነትን ወደጎን በመተው አሳታፊ የሆነ ፖሊሲ በመቅረጽ ስለተንቀሳቀሱ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በዋነኝነት ግን ህዝባዊ ቅቡልነት ስለነበረው መሆኑ አይካድም፡፡

የአለም ሀገራት የኢኮኖሚ ታሪክ እንደሚያሳየን መንግስታዊ ስርአቱ አንባገነን መንግስት በኢኮኖሚው ላይ የሚያደርገው ጣልቃ-ገብነት፣ ውስን በሆነው ሀገራዊ ሀብት የሚከናወኑ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉት የመንግስቱን ባለሟሎች እና ከመንግስታዊው ስርአት ጋር ተለጣፊ የሆኑትን የግል ባለሀብቶችን ብቻ ይሆናል፡፡ የአንባገነኑ ሙጋቤን ሀገር ዚምባቡዌ እና የአንባገነኑ ፒኖቼ ሀገር ቺሊ (በፒኖቼ አመራር ስር በነበረችበት ወቅት) ተመክሮ ለዚህ በቂ ማሳያ ይመስለኛል፡፡ መንግስት፣ በኢኮኖሚው ውስጥ በሚሣተፍበት የልማታዊ መንግስት ስርዓት ስኬት እና ውድቀት፣ ልማታዊ መንግስቱ ለመድብለ ፓርቲ ስርዓትም ሆነ ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሁም ነፃና ገለልተኛ ተቋማት እንዲኖሩ ከሚያበረክተው አስተዋፅኦ ጋር የተገናኘ ነው፡፡ የፖለቲካ ስርአቱን ለኢኮኖሚ እድገት አጋዥ ለማድረግ፣ ለመድብለ ፖርቲም ሆነ ለዲሞክራሲያዊ ስርአት፤ እንዲሁም ለነፃ እና ለገለልተኛ ተቋማት መኖር ከፍተኛ አስተዋፅዖ የሚያደርግ የልማታዊ መንግስት ስርአት፤ በአስተማማኝ የኢኮኖሚ እድገት የህዝቡን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ በፖለቲካ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያግዛል፡፡ የልማታዊ መንግስትን መርህ በሚከተሉ ፖርቲዎች አማካይነት አሁን ላሉበት የኢኮኖሚ ደረጃ የበቁትን የሆላንድን እና የጃፓንን ታሪክ በማሳያነት ማቅረብ ይቻላል፡፡

ኢህአዴግአዊው ልማታዊ መንግስትስ ?

ኢሕአዴጋዊው ልማታዊ መንግስት፣ ድህነትን ለመቅረፍ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ረጅም የስልጣን ዘመን የግድ ነው የሚለውን ሀሳብ ከአብዮታዊ ዴሞክራሲ የፖለቲካ ስርዓት ጋር በመግመድ ብልፅግናን አመጣለሁ የሚል ስርዓት ነው፡፡ በእንደእኛ አይነቱ ደሀ ሀገር ከላይ በጠቀስኩት መልኩ ልማታዊ መንግስትነትን ለአንድ ፖርቲ ብቻ ተለቆ ቢቀጥል የሚቀነሰው የህዝቡ ድህነት ነው ወይስ የባለስልጣኖቹ እና ሸሪኮቻቸው ድህነት ነው? የሚል ጥያቄ በማንሳት ማየት ተገቢ ነው፡፡

አፍሪካ በኒዮ-ሊበራሊዝም አስተሳሰብ ኢኮኖሚዋ ከማደግ ይልቅ አዙሪት ውስጥ መግባቱን በመተንተን ከዚህ አዙሪት ለመውጣት አፍሪካ የኒዮሊበራሊዝም አስተሳሰብን አሽቀንጥራ በመጣል፣ የልማታዊ መንግስን ስርአት መከተል እንዳለባት፣ ልማታዊ መንግስት ህዝቦችን ከድህነት በማውጣት እና በማነቃቃት ድህነት ቀራፊ ፖሊሲ የሚነድፍ እና የሚተገብር፣ ለረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ የሚቆይ ፓርቲ አስፈላጊ ስለመሆኑ በመግለፅ ይህ ለረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ የሚቆየው ፓርቲ ረዥም ጊዜ በስልጣን ላይ ለመቆየት ዋስትናው በሀገሪቷ በየጊዜው የሚያስመዘግበው የኢኮኖሚ እድገት መሆኑን የኢህአዴግ ጭንቅላት የነበሩት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ “African Development the dead ends and the new beginning” በሚለው የዶክትሬት ዲግሪ ሟሟያ ጥናታዊ ፅሁፋቸው ላይ ያትታሉ፡፡ አቶ መለስ፣ ኢህአዴግ ለሚከተላቸው የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ዋነኛው ነዳፊ እንደመሆናቸው መጠን ከላይ የጠቀስኩት ጥናታቸው የስርዓቱን የልማታዊ መንግስት ትርጓሜና አፈፃፀም በግልጽ ያሣያል፡፡

እውቁን ኢኮኖሚስት ፕሮፌሰር ማርክ ኦንልሰን፣ አንባገነን መንግስታት ለልማት በሚል የሚያፈሱት ሀገራዊ ሀብት ቅድሚያ ስሌቱ የህዝቡን ኑሮ ማሻሻል ሳይሆን ለስርአቱ ከሚያስገኘው ገቢ እና ለህልውናው ካለው ፋይዳ (ወተትን ለማግኘት እንጂ ለላሚቷ በማሰብ ሳር ከማይሰጣት ግለሰብ ጋር በተመሳሰለ መልኩ) አንፃር በመሆኑ አንባገነን መንግስታት የብዙሀኑን ህዝብ ኑሮ የሚያሻሽል አስተማማኝ የኢኮኖሚ እድገት ሊያመጡ አይችሉም’ ይላል፡፡ ይህን የኦንልሰን ንድፈ ሀሳብ መነሻ በማድረግ የሀገራችን ግብርና ዘርፍ ልማታዊ ነኝ የሚለው ኢህአዴግ፤ ከሀያ ሶስት አመት በሁአላም በሀገራችን ዋነኛ የግብርና ምርታማነት ግብአት የሆነው ማዳበሪያ ብቸኛ አቅራቢ እራሱ መሆኑ፣ ለግብርና ቴክኖሎጂዎች መስፋፋት የሚመድበው በጀት ሲታይ፣ የሚከተለው የመሬት ፖሊሲ ከገበሬው ይልቅ ሹመኞችን መጥቀሙ ወዘተ የኢህአዴግ ልማታዊ መንግስትነት ፋይዳው ለማን እንደሆነ የሚያመላክት ይመስለኛል፡፡
ኢህአዴግ፤ ‘ልማታዊ መንግስትነኝ’ ከማለቱ ጋር በተገናኘ ልማት በሚል የዳቦ ስም ሀገሪቷ ላይ የሚፈሰው የሀገሪቷ ሀብት፣ ከሀገሪቷ ህዝብ ወቅታዊም ችግርም ሆነ ከዘለቄታዊ ጥቅም አኳያ የህዝብ የምግብ ዋስትና በመሆኑ፣ ለግብርና ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ ኢህአዴግ ለግብርና ትኩረት አለመስጠቱ ከላይ ከጠቀስኩት የግብርናችን ተግዳሮት በተጨማሪ የግብርና ምርቶች የዋጋ ንረት ማሳያ ይመስለኛል፡፡ ኢህአዴግ በሚመራዊ ኢኮኖሚ ስርአት ውስጥ የሚታየውን ፖሊሲ ከመሸጥ (ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለግለሰቦች ማሳወቅ) እስከ ፖሊሲን ለሸሪኮች ማመቻቸት፤ ኢኮኖሚያዊ ስርአቱን ለፓርቲው ሰዎች ብቻ ምቹ ማድረግን እንዲሁም መንግስታዊ ሌብነትን መነሻ በማድረግ ከግብርና ውጪ ባሉ የኢኮኖሚ ክፍሎች ላይም የሚፈሰውን ሀገራዊ ሀብት ለህዝቡ ከሚያስገኘው ዘለቄታዊ ጥቅም አንፃር ሲታይ መንግስት በኢኮኖሚያዊ እድገት የብዙሀኑን ህዝብ ኑሮ ከማሻሻል ይልቅ የሀገሪቷ ሀብት በጥቂት ግለሰቦች እና ቡድኖች የሚዘውሩት የኢኮኖሚ ኢምፖየር እንዲገነባ አድርጓል፡፡

የሃገራችን ማህበረ-ፖለቲካዊ አውድ ከድሮ እስከ ዘንድሮ፣ ከግለሰባዊነት ይልቅ ማህበራዊነት ያጠላበት ነው፡፡ ብዙዎቻችን ስንወድ ስንጠላ፣ ስንደግፍ ስንቃወም የጀማውን አዝማሚያ አይተን ነው፡፡ በግላችን የምናቀርበው ክርክር በጀማው ዘንድ ተቀባይነት ካጣ፣ በግል እምነታችን ከመፅናት ይልቅ ተሸማቀን የምናፈገፍግበት ጊዜ ይበዛል፡፡ ትክክለኛነታችንን የምንለካው፣ በተከተለን መንጋ ብዛት እንጂ በአመክንዮአችን ጥንካሬ አይደለም፡፡

ይህ አንደህዝብ የምንጋራው በጎ ያልሆነ እሴታችን ነው፡፡ መንግስት ደግሞ የህዝብ ነፀብራቅ ነውና በተለያየ ወቅት ሃገራችንን የመሩ መንግስታትም ከዚህ የተዋጁ አይደሉም፡፡ ገዥዎቻችን፣ ብዙሃኑ ህዝብ ሰጥ ለጥ ብሎ እየተገዛላቸው፣ ጥቂት የተለየ ሃሳብ ያነሱ ዜጎችን ከምድር በታች ካላደረጉ እንቅልፍግ የማይወስዳቸው ለዚህ ነው፡፡ ሁሉም ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ሃገሬው “ስዩመ እግዚአብሄር” እያለ ይሰግድላቸው የነበሩት አፄ ኃ/ስላሴ፣ ገርማሜ ነዋይን የመሰለ ባለ አእምሮ የገመድ ራት ያደረጉት በዚህ አግባብ ነው፡፡ የነ ልጅ እያሱ፣ በላይ ዘለቀ፣ ጥላሁን ግዛው አሳዛኝ ፍፃሜ የዚሁ የንጉሱ በደቦ የመግዛት ፍላጎት ክፉ ውጤት ነው፡፡ ዱላ ተቀባዩ ወታደራዊው መንግስትም ኢትዮጵያ ትቅደም፣ የኢትዮጵያ ሶሻሊዝም፣ የእድገት በህብረት የእውቀት እና የስራ ዘመቻ፣ ሁሉም ነገር ወደጦር ግምባር፣ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ ወዘተ እያለ በየጊዜው የሚያመጣቸው ግን ደግሞ እርሱ እራሱ በቅጡ ያልተረዳቸውን ፍልስፍናዎች በደቦ ያልደገፈውን ሁሉ ደም ከማፍሰስ ወደኋላ አይልም ነበር፡፡ የዚህ አካሄዱ ማጀቢያም “ከእኛ ጋር ያልሆነ ከጠላታችን ጋር ነው” የሚል የደመ-ነፍስ መርህ ነበር፡፡

ተተኪው ኢህአዴግም መውደድ መጥላቱን፣ አድናቆት ውግዘቱን ከዘጠና ሚሊዮኑም የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በደቦ ማድረግ ይፈልጋል፡፡ ከዚህ ያፈነገጠን ሁሉ የዲያቢሎስ አምሳያ የሃገር ጠላት አድርጎ ያብጠለጥላል፡፡ ይህን የደቦ አባዜውን፣ ከሃገሬው ህዝብ አልፎ እስከ ባህርማዶ የምዕራባዊያን ግለሰቦች እና ተቋማት ድረስ ያዘልቀዋል፡፡ ከሚያስተዳድረው ህዝብ አልፎ ባዕዳንም በደቦ የወደደውን እንዲወዱ የጠላውን እንዲያወግዙ ይፈልጋል፡፡

የፍቅር ደቦ -1

በ1977 ዓ.ም በሃገራችን ተከስቶ በነበረው ረሃብ ሰበብ፣ የምዕራባዊኑን ዶላር ጣዕም የቀመሰው ህወሃት የምዕራባዊያኑ ንዋይ የህይወት መስመሩን የሚያረዝም መሆኑን የተረዳው ገና ጫካ እያለ ነበር፡፡ ሸማቂው ቡድን፣ “ቆምኩለት” በሚለው ድሃው የትግራይ ህዝብ ስም የመጣውን የእርዳታ ገንዘብ አያሌ ድርሻ፤ በአቶ መለስ ፊታውራሪነት ለማሌሊት መመስረቻ እና ማጠናከሪያ እንዲውል እንደተደረገ፣ አልፎ ተርፎም ሱዳን ላይ ለድርጅቱ ትላልቅ የእርሻ መሬት ተገዝቶ ሰሊጥ እያመረቱ ይቸበችቡ እንደነበር በወቅቱ የድርጅቱ በጅሮንድ የነበሩት አቶ ገ/መድህን አርአያ፤ በአንድ ወቅት ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ተናግረዋል፡፡ይህ ተግባር አሳፋሪ ቢሆንም፣ በዚሁ መንገድ የመጣው ረብጣ ገንዘብ ሕወሓትን በወቅቱ ከነበሩ ሃብታም ሸማቂዎች መካከል እንዲመደብ አድርጎታል፡፡ ነገሩ ድርጅቱን ከምዕራባዊያኑ ጋር ከአንጀት ባይሆንም ከአንገት በላይ በሆነ ፍቅር እንዲወድቅ አድርጎታል፡፡ በመሆኑም የሸማቂነቱ ዘመን አብቅቶ መንግስት ሲሆን የምዕራባዊያኑን ፖለቲካዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፈለግ እንደሚከተል ይገልፅ ጀመር፡፡ በፖለቲካው ረገድ፣ በምዕራባዊያኑ ዲሞክራሲ ስም በመማል በመገዘት፣ በኢኮኖሚው በኩል ደግሞ “የምከተለው ነጭ ካፒታሊዝምን ነው” ሲል ያመሽ ያነጋ ነበር፡፡ ዓለም-አቀፍ የሰብዐዊ መብት አንቀፆችን የህገ-መንግስቱ አካል በማድረግ፣ ለምዕራባዊያኑ ሊብራሊዝም ፅንሰ-ሃሳብ እና አጠቃላይ ርዕዮተ-ዓለም ያለውን ታማኝነት ለማስመስከር ሞክሯል፡፡ የጣለውን የደርግ ስርዓት ያብጠለጥል የነበረውም የዜጎችን ሰብዐዊ መብት በመርገጥ እና ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን ለማስፈን ባለመቻሉ ያጠፋቸውን ጥፋቶች በማነሳሳት ነበር፡፡ በዚህ ወቅት የምዕራባዊያኑ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ፈለግ፣ በኢሕአዴግ ዘንድ ብቸኛ የድኅነት መንገድ ተደርጎ ይወሰድ ነበርና ከዚህ ሃሳብ መለየት ለማንም አልተፈቀደም ነበር፡፡ የተለየ ሃሳብ አለኝ የሚል ቢገኝ እንኳ መጠሪያው የደርግ ርዥራዥ፣ “የዲሞክራሲ ጠላት” የሚል ይሆናል፡፡

የፍቅር ደቦ -2

ሕወሓት ከውልደቱ ጀምሮ በሻዕብያ ፍቅር ክፉኛ የተመታ ነበር፡፡ ይህ ጣራ የነካ ፍቅር በሚገርም ሁኔታ እናት ሃገርን ቅኝ ገዥ አድርጎ እስከማሰብ እና ቀኝ ተገዥዎችን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት እናት ሃገርን እስከ መውጋት አድርሶታል፡፡ ህወሃት፤ ከሻዕብያ ጋር የወደቀበት ሃያል ፍቅር፣ ወዳጅ ጠላቱን ለመለየት ሳይቀር ዋና መለኪያው፣ ያ ወገን የኤርትራን ጉዳይ የሚረዳበትን መንገድ እስከ ማድረግ ደርሶ ነበር፡፡ ለምሳሌ ህወሃትን ከኢህአፓ ጋር ያቃቃረው፣ ኢህአፓ የኤርትራን ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው ለማለት ባለመድፈሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም የህወሃት ፍቅር፣ ከራሳቸው ከኤርትራዊያኑ ታጋዮች የበለጠ ለኤርትራ ያገባኛል እንደማለት ስለሚሞክረው ለወሬ የማይመች የሚሆንበት ጊዜም ነበር፡፡ አቶ መለስ፣ ጫካ በነበሩበት ወቅት የትክክለኛ ኤርትራዊነትን መስፈርቶች እስከማውጣት ደርሰው እንደነበር የአስራት አብረሃም “ከሃገር በስተጀርባ” መፅሃፍ ያስረዳል፡፡ አቶ መለስ፣ በዚሁ መስፈርታቸው በኢትዮጵያዊነት ስር ሆኖ የኤርትራ ጥያቄ ይመለስ የሚሉ፣ ኢትዮጵያ የኤርትራ እናት ሃገር ነችና መገንጠሏን አንቀበልም የሚሉ፣ ከደርግ ጋር ተደራድረው ኤርትራን ለመገንጠል የሚደረገውን ትግል ለማስቆም የሚከጅሉ ኤርትራዊያን፤ ከኤርትራዊነት የጎደሉ እንደሆኑ አምርረው ይናገሩና ይፅፉ ነበር፡፡ በአቶ መለስ መስፈርቶች ከተሰፈሩ፣ አንድ ሁለት ጊዜ ከደርግ ጋር ለመደራደር መለስ ቀለስ ብለው የነበሩት ኢሳይያስ አፈወርቂ ራሳቸው ኤርትራዊነት የሚጎድላቸው ይሆናሉ ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነታቸውን የሚወዱት እውቁ ኤርትራዊ ምሁር ፕ/ር ተስፋፅዮን መዳኔ፣ ከኤርትራዊነት ፀዳል የጎደሉ እንደሆኑ አቶ መለስ “የኤርትራ ህዝብ ትግል የቁልቁሊት አይደፋም” የሚል መፅሃፍ እስከመፃፍ በደረሰ ሙግት ሲያስረዱ ነበር፡፡
ይህ ከጠዋቱ ህወሃትን የተጣባው የሻዕብያ ፍቅር፣ ሸማቂ ቡድኑ አድጎ ኢህአዴግ በሚል ሰፊ ድርጅታዊ ማዕቀፍ ውስጥ ገብቶም፣ የመንግስትነት ሰገነት ላይ ወጥቶም የሚብስ እንጅ የሚበርድ አልሆነም፡፡ ሸማቂ ቡድኑ፣ ወደ አዲስ አበባ በሚያደርገው ግስጋሴ ሁሉ ቆምኩለት ከሚለው ኢትዮጵያ ህዝብ ጥቅም እና ፍላጎት ይልቅ የሻዕብያ አመራሮችን ፍላጎት ያስቀድም ነበር፡፡ አዲስ አበባ ገብቶ የታላቋን ሃገር የኢትዮጵያን እጣ-ፋንታ አንድ ደረጃ ሳያደርስ፣ የኤርትራን መገንጠል በአስተማማኝ ሁኔታ ለማሳካት የተባበሩት መንግስታትን ሹማምንት እረፍት በነሳ ውትወታ ተጠምዶ ነበር፡፡ የመገንጠሉ ሂደት ሚጢጢዋን ኤርትራን ያለ አግባብ ባለ ሁለት ወደብ ሲያደርግ ኢህአዴግ ታገልኩላት የሚላትን ታላቋን ሃገራችንን ወደብ አልባ ማድረጉ፣ በኤርትራ ፍቅር አይነ-ልቦናው ለታወረው ህወሃት ነገሬ የሚባል ጉዳይ አልነበረም፡፡

ይህ ምንጩን ለማወቅ የሚያስቸግር ህወሃት የወደቀበት ሃያል ፍቅር፣ ወደ ሁሉም ኢትዮጵዊ በደቦ ሰርጎ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የኤርትራን ጉዳይ ቀዳሚ እንዲያደርግ የመፈለጉ ዝንባሌ ራሱ ከወደቀበት ፍቅር ብርታት የበለጠ የሚገርም ነበር፡፡በወቅቱ አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ህወሃት የፈለገውን ያህል በኤርትራ ፍቅር ሊወድቅ ቀርቶ፣ የኤርትራን ሃገርነት ለመቀበልም እንኳ ዝግጁ አልነበረም፡፡ በተቃራኒው ህዝቡ ኤርትራ የተገነጠለችበትን ሪፈረንደም አግባብነት እና የኢትዮጵያ ሁለት ወደብ አስረክቦ ወደብ አልባ መሆን እያስቆጨው ነበር፡፡ ይህ የአብዛኛው ዜጋ እምነት ታዲያ ለህወሃት መሪዎች የደርግ ቅሪት፣ የነፍጠኛው ስርዓት ርዝራዥ፣ የነፃነት ጥያቄ የማይገባው ትምክህተኛ፣ የተስፋፊነት አባዜ የተጠናወተው፣ የጎረቤት ሃገር ሉአላዊነት የማይዋጥለት ጦረኛ …. የሚል መጠሪያ ይሰጠው ነበር፡፡ “ስለ ኤርትራ አንዳች ክፉ የሚናገር ቀድሞ የሚጣላው ከእኛ ጋር ነው” የሚለው የህወሃት አባባል፤ ሽርክናው ወደ መሸካከር ተቀይሮ፣ በሁለቱ ሃገራት መሃከል ከፍተኛ ደም መፋሰስ ከሆነ በኋላም የቀጠለ ነው፡፡

‘የኤርትራ መገንጠል የነፃነት ምልክት ነው ከተባለ ይሁንና የኤርትራ አካል ያልሆነው የአሰብ ወደብ እንኳን ለሃገራችን ይትረፍ’ ማለትም በህወሃት መንደር የሚያስቀስፍ ሃጢያት ነበር፡፡ የወደብ እጦቱ ድህነቱን ያባባሰበት የኢትዮጵያ ህዝብም የአሰብን ወደብ ያለአግባብ ለኤርትራ መሰጠቱን በደቦ እንዲቀበል አልፎ ተርፎም ህገ-መንግስቱ ያመጣው የነፃነት ትሩፋት ነው ብሎ እንዲያምን ይጠበቅበታል፡፡ ህወሃት፣ ኤርትራን በተመለከተ የያዘውን አስገራሚ አቋም እንዲይዝ ባደረገው ፍቅር የተለከፈበት በሚናገረውም ሆነ በማይናገረው የራሱ ምክንያት ሆኖ ሳለ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ያለ ምክንያት ተገቢ ያልሆነውን የሚቀበልበት እና ከህወሃት ጋር የፍቅር ደቦ ገብቶ ‘ከኤርትራ ያስቀድመኝ’ የሚልበት ምንም ምክንያት የለውም፡፡ ሆኖም ደቦ ወዳዱ ህወሃት፣ እርሱ በወደቀበት የኤርትራ ፍቅር የኢትዮጵያም ህዝብ እንዲወድቅ ይጠብቃልና የወደቡ አንሶ ቡናው፣ ጤፉ፣ ገብሱ፣ ስንዴው …. ወደ ኤርትራ ሲጋዝ ከልቡ ደስ እንዲለው ሲፈርድበት ኖሯል፡፡

የፍቅር ደቦ-3

የመገንጠል መብትን የህገ-መንግስቱ አካል ያደረገው ኢህአዴግ፣ ህገ-መንግስቱ በፀደቀ ማግስት የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ በደቦ በመገንጠል ፍቅር እንዲወድቅ፣ የመለያየት መዝሙር እንዲዘምር፣ ከሃገራዊነት ይልቅ ወንዘኝነቱን እንዲያጠብቅ፣ መገንጠልን የነፃነት ቁንጮ አድርጎ እንዲያስብ መፈለጉ አልቀረም፡፡ በሌላ በኩል በዘውዳዊው ስርዓትም ሆነ በወታደራዊው መንግስት ዘመን ለተቆጠሩ ረዥም አመታት በጋብቻ፣ በጉርብትና እና መሰል ማህበራዊ መስተጋብሮች አንድነቱ ሲያጠብቅ ለኖረው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ደግሞ ይህ በቀላሉ የሚዋጥ አልነበረም፡፡ ሆኖም ኢህአዴግ ከጠዋቱ የሃገር አንድነትን በነፍጠኛ አማሮች ብቻ የሚቀነቀን ክፉ አባዜ አድርጎ ይቆጥር ነበርና እርሱ በወደቀበት የመነጣጠል ፍቅር ያለመመታት፣ የትምክህተኝነት ምልክት ተደርጎ ይወገዛል፡፡ የሚገርመው ይህን የሚለው ኢህአዴግ መገንጠልን አልመው የሚንቀሳቀሱ የብሄር ፓርቲዎችንም በጠባብነት ይከሳል፡፡ በህወሃት/ኢህአዴግ አተያይ፣ የመገንጠል ጥያቄ የነፃነት ትግል የሚሆነውም የሚሳካውም ሻዕብያ ሲያነሳው ብቻ ነው፡፡ በተረፈ ስለመገንጠል ቀርቶ ስለአንድ ብሄር መብት ጥያቄ ማንሣት የጥበት ምልክት ነው፡፡ ይህን ግራ የተጋባ የገዥው ፓርቲ አቋም፣ በደቦ መከተል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ግዴታ ነው፤ ካልሆነ የተለመደው ውግዘት ይከተለዋል፡፡

የፍቅር ደቦ – 4

ከ1997 ዓ.ም ወዲህ ‘ዲሞክራሲያዊነቱን ትቼ ልማታዊ ሆኛለሁ’ ያለው ኢህአዴግ፣ ይህን ሲል ወደስልጣን ከመጣ ጀምሮ እስከ 1997 ዓ.ም ድረስ ሲዘምርለት የኖረውን የምዕራባዊያን ዲሞክራሲ በልማታዊ መንግስት ርዕዮት ተክቶ ነው፡፡ “ሩቅ አሳቢ” ሲል የጠራውን የልማታዊ መንግስት እሳቤ፣ ‘የእስያን ሃገሮች ኢኮኖሚ እንደ ነብር እንዲፈተለክ ያደረገ ብቸኛ መድህን ነው’ ሲል አወዳድሶ፤ ቀድሞ ሲያሞካሸው የነበረውን የምዕራባዊያኑን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ የርዕዮት አለም ዘይቤ ደግሞ፡- “በአሸናፊነት መንፈስ አለቅጥ የሰከረ፣ ለአፍሪካ ፈፅሞ የማይበጅ” ሲል አጣጥሎ ነው፡፡ የኒዮ ሊብራል ቀሳውስት ዶግማ የሚለውን የምዕራባዊያን የኢኮኖሚ ዘይቤ በተለይ “የዘበኛ መንግስት የመመስረት ህልም ያለው” ሲል ያራክሰዋል፡፡

በዚህ ቅፅበትም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሲዘምርለት የኖረውን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ህልም ወዲያው ረስቶ፣ ከኢህአዴግ ጋር በቻይና ፖለቲካዊ ርዕዮት ፍቅር እንዲወድቅ፣ ስለሱው እንዲዘምር፣ በአንድ አውራ ፓርቲ ስር መሆንን ፀዳል ድንቅነት እንደያወድስ፣ ስለሰብዐዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶቹ አያያዝ ሁኔታ ትንፍሽ ሳይል ስለቁሳዊ እድገት እና እንዲሁ በደቦ የልማታዊ መንግስትን መስመር ተከትሎ ስለሱው ትሩፋቶች ብቻ እንዲነጋገር ይጠበቅበታል፡፡ ከዚህ የደቦ አስተሳሰብ የሚያፈነግጥ የልማት አደናቃፊ፣ የህዝብ ጠላት የሚሉ ተቀፅላዎች ይንጠለጠሉበትና ጉዞው ወደቃሊቲ ይሆናል፡፡

ከላይ ለማሳያነት የቀረቡት የኢህአዴግ የደቦ ጉዞ ፍላጎቶች፣ በምክንያታዊነት ለሚያምን እና የራሱ አተያይ ላለው ዜጋ ክፉ ፈተና የሚደቅን ነው፡፡ ሌላው የዚህ ከመንግስት በኩል የሚፈለገው የደቦ ጉዞ ችግር፣ ራሱ ለደቦ የሚጋብዝበትን ሃሳብ ይዞ የመሰንበት ዝንባሌው አናሳ መሆን ነው፡፡ ከላይ በመጠኑ ለማሳየት እንደተሞከረው ገዥው ፓርቲ ትናንት በፍቅር ወድቆለት ሌት ተቀን ሲያነሳሳው ህዝቡንም ለደቦ አድናቆት ሲጋብዝበት የነበረውን ርዕዮተ አለምም ሆነ መመሪያ፣ ከመቅፅበት ቀይሮት ጠላት ሲያደርገው ይስተዋላል፡፡ የምዕራባዊያኑ የዲሞክራሲ እና የሰብአዊ መብቶች አያያዝ እሳቤ፣ ከኤርትራ ጋር የነበረው ወዳጅነት፣ የመገንጠል ጥያቄን የሚያስተናግድበት ሁኔታ ወ.ዘ.ተ ለዚህ አባባል በማሣያነት ሊቀርቡ የሚችሉ አብነቶች ናቸው፡፡ በዚህ የተነሳ የደቦ ጉዞውን ለመቀበል ለተዘጋጀ ሰውም ቢሆን የኢህአዴግ አካሄድ አስቸጋሪ እና ግራ አጋቢ መሆኑ አይቀርም፡፡ በዚህ ሁኔታ ለመያዝ ለመጨበጥ አስቸጋሪ የሆነው የኢህአዴግ አካሄድ አስቸጋሪ ሆኖ ሳለ፣ መንግስት ለፍቅሩ ብቻ ሳይሆን ለጠቡም ደቦ የመፈለጉ አካሄድ ደግሞ ሌላው ከባድ እና ግራ አጋቢ ጉዳይ ነው፡፡

የኢህአዴግ የፍቅርም ሆነ የጠብ ደቦ ፍለጋ፣ የዜጎችን እጣፈንታ የሚወስን እየሆነ መምጣቱ ይብስ አሳሳቢው ጉዳይ ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ ኢህአዴግ የወደደውን መውደድ የጠላውን መጥላት ብቻ ሳይሆን አብሮ ማውገዝ ከሁሉም በመንግስቱ ጥላ ስር የሚኖር ዜጋ ግዴታ ወደመምሰሉ እየሄደ መጥቷል፡፡ በዚህ የማይስማማ እጣ-ፈንታው ሁለት ነው ወይ ቃሊቲ መውረድ ወይ መሰደድ፡፡ እለት እለት እየጨመረ የመጣው የተሰዳጅ እና የታሳሪ ቁጥርም በአመዛኙ ከዚሁ ከኢህአዴግ የልብ ሃሳብ ጋር የመመሳሰል እና ያለመመሳሰል ጉዳይ ነው፡፡ ለፍቅርም ሆነ ለጠብ ከመንግስት ጋር እኩል ማሰብ ደግሞ ተፈጥሯዊም አይደለምና ለዜጎች ትልቅ ፈተና ነው፡፡ የፈተናውን ክብደት የሚያሳዩ የኢህአዴግ የጠብ ደቦ ፍላጎቶችን ለማሳየት ሳምንት እመለሳለሁ፡፡

ቃጠሎው ለአትክልት ልማት ከተደረገ ምንጣሮ ጋራ የተያያዘ መኾኑ ተጠቁሟል በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ደን ውስጥ ዛሬ፣ ጥር ፮ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ከረፋዱ 4፡30 ላይ የተቀሰቀሰው እሳት በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገለጸ፡፡ ቃጠሎው በቁጥጥር ሥር የዋለው ከቤተ ክርስቲያኑ በግምት ከመቶ ሜትር ባነሰ ርቀት ላይ በደረሰበት ኹኔታ ነው ብለዋል – እሳቱን በማጥፋት የተራዱ የዐይን እማኞች፡፡ …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

አመቺ፤ በውጪም፤ ቀለል በሚለው የፀሐይ ኃይል ላይ ያተኮሩ አገሮች ቁጥር በሚያስደንቅ ፍጥነት በማደግ ላይ ይገኛል። እ ጎ አ በ 2014 ዓ ም ብቻ፤ በ 20 ከመቶ ነው ያሻቀበው። ይኸው ታዳሽ የኃይል ምንጭ፣ የወደፊቱ ዋንኛ የሥነ ቴክኒክ ፀጋ ያህል

ቦኩ ሐራም ልጃገረዶችን ለእጥፍቶ ጠፊነት ማዝመቱን መንታ ድል እንደሚያስገኝለት ሥልት ነዉ የሚቆጥረዉ።አንደኛ «ሴቶችም ይዋጋሉ» እያለ ወጣቶች ዓላማዉን እንዲቀበሉ መቀስቀሻ ያደረገዋል።ሁለተኛ ቡድኑን ይበልጥ ተፈሪ ያደርገዋል።

በጀርመኗ ቢለፌልድ ከተማ ዛሬ ማምሻዉን የኢትዮጵያ የባህል የሙዚቃ ድግስ ይካሄዳል። የሙዚቃ ድግሱ WDR በተሰኘዉ የጀርመን ራዲዮ በሀገሩ አቆጣጠር ከምሽቱ ሁለት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት በቀጥታ የሙዚቃ ድግሱ ከሚካሄድበት አዳራሽ ይሰራጫል።

*የደም ናሙናው ለተጨማሪ ማረጋገጫ ወደ አሜሪካ በዛሬው ዕለት ተልኳል፡፡ በትናንትናው ዕለት አንድ ከሴራሊዮን የመጣ ግለሰብ በኢቦላ ሕመም ተጠርጥሮ ምርመራ ቢደረግለትም ከቫይረሱ ነፃ መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ አስታወቁ፡፡ ታማሚው በሴራሊዮን በአንድ የአለም አቀፍ የበጎ አድራጎት ድርጀት በኩል ተቀጥሮ የአካባቢ ቁጥጥር ባለሙያ በመሆን  ይሠራ የነበረ  ሲሆን፥ ከሴራሊዮን ከተመለሰ በ15ኛ ቀኑ በትኩሣት ራሱን በመሳቱ በተደረገለት የደም ምርመራ ፋልሲፓረም የተባለ የወባ በሽታ የተገኘበት በመሆኑ ለዚሁ አገልግሎት ባዘጋጀችው ላብራቶሪ ለኢባላ የደም ምርመራ ተደርጎለት ውጤቱ ከበሽታው ነፃ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በላብራቶሪ ውጤቱ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ብንሆንም ታካሚው ሴራሊዮን ደርሶ ከመመለሱ አንፃር የደም ናሙናው ለተጨማሪ ማረጋገጫ ወደ አሜሪካ በዛሬው ዕለት መላኩንና ከ48 እስከ 72 ሰዓታት ውስጥ ውጤቱ እንደሚታወቅ ነው የተመለከተው። በውጤቱ ላይ ለውጥ የሚኖር ከሆነ በቀጣይ ሚኒስቴሩ እንደሚያሳውቅ ዶክተር ከሰተብርሃን ገልጸዋል፡፡ ታካሚው በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ረፋድ ላይ ሕይወቱ ማለፉንም ነው ያስታወቁት፡፡ የተላከው ናሙና ውጤት እስከሚመጣ ድረስ ከተጠርጣሪው ጋር ቀጥታ ግንኙነት የነበራቸው ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ላይ የባለሙያ ክትትል በመደረግ ላይ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ኢቦላን ለመከላከል የምታደርገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ አረጋግጠዋል፡፡ ******** ምንጭ፡- ፋና – ጥር 6፣ 2007 More from Horn Affairs Amharicበአሶሳ ምንነቱ ያልታወቀ በሽታ ተከሰተ – ክልሉ ኢቦላ አይደለም ይላልየኬሚካል ክምችትና የአደጋ ስጋት በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶችዓለማየሁ አቶምሳ – ኪራይ ሰብሳቢነትን አምርሮ የታገለና ያታገለኢትዮ-ቴሌኮም በ75 የአዲስ አበባ አካባቢዎች የኔትወርክ ችግር ፈታሁ […]

አምስተኛው ጠቅላላ ምርጫ የፊታችን ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ጽሕፈት ቤት ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህ ፕሮግራም መሠረትም የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ እንቅስቃሴ ገብተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በቦርዱ በዘንድሮው ጠቅላላ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ካለፈው ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ቦርዱ ይፋ ካደረገውና እየተገበረው ካለው የምርጫ […]


እሳቱ ከደኑ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳያልፍ መነኮሳቱ፣ ፖሊስና ሕዝቡ ቆርጠውታል፡፤ በአፈር ከተር በመሥራት የእሳቱን ተሻጋሪነት ቀንሰውታል፡፡ አሁን እሳቱን ለማጥፋት እየተረባረቡ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ፣ ዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ መሀል የተደረገውን ውህደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በዛሬው ዕለት፣ ጥር 2 ቀን 2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የግንቦት 7፣ ለፍትህ ለዴሞክራሲና የነጻነት፣ ንቅናቄ፣ ድርጅቶች፣ ተዋህደን “አርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ዴሞክራሲ፣ ንቅናቄ”፣ በሚባል ሥም መጠራት መጀመራችንን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስናበስር፣ እጅግ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል። የኢትዮጵያ […]

መግቢያ፤ ኢትዮጵያንና አርሚኒያን ከሚያመሳስሏቸው ጉዳዮች አንደኛው የአንድ ዓይነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የእምነት መሠረት (ዶግማ) ተከታዮች ያሉባቸው ሐገሮች መሆናቸው ነው። በዚህ ጽሑፍ የማተኩርበት ተመሳሳይነት ግን ሁለቱም ሐገሮች በከባድ የጦር ወንጀሎች ተጠቅተው እያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተጨፈጨፈባቸው መሆኑ ነው። ሌላም እጅግ አስጸያፊ ግፍ የተፈጸመባቸው ሐገሮች ናቸው። በተጨማሪም፤ ሁለቱን ሐገሮች ያቀራረባቸው ሌላው ጉዳይ በኦቶማን ዘመነ መንግሥት፤ ከቱርኮች ግፍ […]

* መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል …! አርአያነታቸው ፋና ወጊ ሆኖ እያለ ብዙ ያል ተነገረላቸውን ዶር በርናርድ ብሬድሊ አንደር ሰንን ባዘከርኩበት የማለዳ ወጌ የጠቢቡን ህይዎት ከጃማይካ እሰከ አሜሪካ ለመቃኘት መሞከሬ እውነት ነው ። ዛሬም የምቀጥለው ከዚያ ለጥቆ ያለውን የዶር በርናርድን አፍሪካና ኢትዮጵያ ያደረሰውን መንገድ ሲሆን እንደ መግቢያ በአንድ የጥምቀት ዋዜማ ጎንደር ከዶር በርናርድና ከባለቤታቸው ከሲስተር […]

በጣና ሐይቅ ውስጥ በሚገኘው የዳጋ እስጢፋኖስ እሳት መነሣቱን የገዳሙ ምንጮች ተናግረዋል፡፤ እሳቱ የተነሣው ከደኑ አካባቢ ሲሆን ወደ ገዳሙ ገና አልደረሰም፡፡ የክልሉ ፖሊስ ወደ ቦታው በፍጥነት መድረሱ ተሰምቷል፡፡ አባቶች እሳቱን ቆርጦ ለመከላከል እየሞከሩ ነው፡፡ በሰው ኃይል ለመከላከል የማይቻል ከሆነ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ክልሉ ገልጦላቸዋል፡፡

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርስ የነበረው ጣይቱ ሆቴል በእሳት ወደመ:: ከዚሁ ጋር ተያይዞ ታዲያ “አቃጠሉት” እና “አቃጠሉበት” የሚሉት ድምጾች በርክተዋል:: “አቃጠሉበት” የሚለውን የጨዋታ ክር መምዘዝ ከጀመርን; የቤቱ ባለቤት ፍጹምዘአብ ጋር ያደርሰናል:: ፍጹምዘአብ የትግራይ ተወላጅ ነው:: ግን ደግሞ የትግራይ ተወላጅ ስለሆነ ከስልጣን ዙፋን ላይ አልተቀመጠም:: ይልቁንም በዘመነ ኢህአዴግ ከአምስት አመታት በላይ የወያኔን እስር ቤትን ቀምሶ የወጣ ሰው ነው:: አሁን በተቃጠለው […]

ብዙ ሰዎች ፍቅርን እና ሰላምን ለያይተውት ማወቅ አይችሉም።የመፅሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ግን በሙሉ ከመንፈሳዊ ትምህርትነታቸው በላይ በተአማኒነት የሚታወቁት በአፈ-ታሪካዊነታቸው ሳይሆን፣የፍቅርን እና የሰላምን ትርጉም እንደባሕር ጥልቀት በዕውነተኛነት መረጃ በማስተማራቸው ነው። አይደለም የሰው ልጅ፣እንደምድረ-በዳዎች ሁሉ በውስጡ የጦርነት ሕይወት የሚ ኖ ርበት ባሕር እንኳ ሰላማዊ ነው ይባላል፤ዕውነቱ ግን በረሐዎችም ሆኑ ውቅያኖሶች መቼም ጊዜ ሰላማዊ ሊሆኑ አይችሉም።በሕዝባዊ መረጃነት የመፅሐፍ ቅዱስ […]

ህዳር 27 እና 28/2007 ዓ.ም በ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ተዘጋጅቶ በነበረው የአዳር ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ የቅስቀሳ በራሪ ወረቅት ሲበትን ለእስር የተዳረገው የሰማያዊ ፓርቲ አባል ሲሳይ ዘርፉ በፌደራል አቃቤ ህግ ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታዬ ሲሆን በነገው ዕለት (ጥር 7/2007 ዓ.ም) የሰማያዊ እና የኦህዴህ ሊቃነ-መናብርት ለተከሳሽ ተከላካይ ምስክር ሆነው እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡ ተከሳሹ አቶ ሲሳይ ዘርፉ ‹‹…‹ነጻነት […]

ላለፉት አንድ መቶ ዘጠኝ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የኖረው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሆቴል እቴጌ ጣይቱ ሰሞኑን ባጋጠመው ቃጠሎ ከደረሰበት ጉዳት ለማደስ ጥረቶች እንደሚጀመሩ የሆቴሉ አስተዳደር አስታውቋል።

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩም የተቃጠለውን ሆቴል ጎብኝተዋል።

በሌላ በኩል የእሳት አደጋ ሠራተኞች የሆቴሉን ጉዳት ለመቀነስ ተገቢውን ጥረትና መነሳሳት አላሳዩም ሲል የሆቴሉ አስተዳደር ወቅሷል።

ወቀሳውን ያልተቀበሉ የአዲስ አበባ የእሳት አደጋ መከላከያና መቆጣጠሪያ ባለሥልጣን “የእኛን አሠራር ካለማወቅ የተሰጠ ወቀሳ ነው” ብለዋል።

እስክንድር ፍሬው ዝርዝሩን ልኳል።

ጥር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፍኖተ ነጻነት የፓርቲውን የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ አቶ ተክሌ በቀለን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ታህሳስ 25 ቀን 2007 ኣመተ ምህረት ባደረገው ስብሰባ መጪውን ምርጫና ከምርጫው ጋር ተያይዘው ስለሚመጡ ጉዳዮች፤ እንዲሁም ከምርጫው በሁዋላ ፓርቲዎች ሊኖራቸው ስለሚገባው ትብብርና ውህደት የሚያመቻች ኮሚቴ ተቋቁሟል። በስብሰባው፣ ፓርቲዎች በትብብርና በውህደት […]

ጥር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፍኖተ ነጻነት የፓርቲውን የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ አቶ ተክሌ በቀለን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ታህሳስ 25 ቀን 2007 ኣመተ ምህረት ባደረገው ስብሰባ መጪውን ምርጫና ከምርጫው ጋር ተያይዘው ስለሚመጡ ጉዳዮች፤ እንዲሁም ከምርጫው በሁዋላ ፓርቲዎች ሊኖራቸው ስለሚገባው ትብብርና ውህደት የሚያመቻች ኮሚቴ ተቋቁሟል። በስብሰባው፣ ፓርቲዎች በትብብርና በውህደት […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ( አንድነት ) እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ ) የውስጥ ችግራቸውን መፍታት አልቻሉም በሚል በዛሬው ዕለት ውሳኔ እሰጣለሁ ብሎ የነበረው ምርጫ ቦርድ ሁለቱ ፓርቲዎች በሁለት ሳምንት ውስጥ የውስጥ ችግራቸውን ፈትተው ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ የመጨረሻ ጊዜ ሰጥቻቸዋለሁ ሲል ገልጾአል ፡፡ ቦርዱ ዛሬ ከሰዓት በሰጠው መግለጫ በአንድነትና መኢአድ ስም የተለያዩ […]

ጥር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፎርቹን ሳምንታዊ ጋዜጣ እንደዘገበው፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ -የአእምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤትን በጀነራል ዳይሬክተርነት እረየመሩ ያሉትን አቶ ብርሀኑ ያዴሎን   ካለፈው ታህሳስ 27 ቀን ጀምሮ ከስልጣን አንስተዋቸዋል። ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የተጻፈ ደብዳቤ  ከዚያው እለት ጀምሮ በአስቸኳይ አቶ ብርሀኑ ያዴሎ ከስልጣናቸው መነሳታቸውንና በምትካቸው በቢሮው የፓተንት ዳይሬክተር የሆኑት  አቶ ግርማ በጅጋ መተካታቸውን …

ጥር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሶስት ዓመት ህጻንን ጨምሮ ከሶስት ህጻናት ልጆች ጋር ለእህቷ ስርግ ወደ ኢትዮጰያ አቅንታ የነበረችውና ላለፉት 20 ቀናት በአዲስ አበባ የቆየችው ወይዘሮ አበባ፤ ከነ ልጆቿ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ታስራ እንድታድር ከተደረገች በሁዋላ ነው ከሀገር የተባረረችው። በእህቷ ሰርግ ላይ በርካታ ደህንነቶች ሲከታተሏት እንደነበረ የገለጸችው ወይዘሮ አበባ፤ በማግስቱ በቤተሰቦቿ ቤት ሳለች  …

ጥር ፭(አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግብጽ የመስኖ ሚኒስትር -በኢትዮጰያ እየተሰራ ያለው ግድብ የሚይዘው የውሀ መጠን በግብጽ  የውሀ ድርሻ ላይ ጉዳት ስለሚያስከትል  እንደሚቃወመው አስታወቀ። አህራም  ኦንላይን “ሜና”የተሰኘውን የ አገሪቱን የዜና አገልግሎት ጠቅሶ  እንደዘገበው በመስኖ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ  የአባይ ግድብ ቃል አቀባይ የሆኑትን ሚስተር አላን ያሲን  በአሁኑ ወቅት ኢየተሰራ ያለውና 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ …