ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሰሜኑ የአገሪቱ ክፍሎች የታፈኑ  የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡ በሰሜን ጎንደር ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አግባው ሰጠኝ ፣ የምእራብ አርማጭሆ  የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ  ሰብሳቢ አቶ አንጋው ተገኝ  ትናንት  ወደ ማዕከላዊ መወሰዳቸውን ጋዜጣው ዘግቧል። ሌሎች የተቃዋሚ አመራሮች ወደ ማእከላዊ ይወሰዱ አይወሰዱ …

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ገልፍ ኒውስ ባወጣው ዘገባ 4 ወንዶች አንዲት ኢትዮጵያዊትን አአስገድደው መኪና ላይ ከጫኑዋት በሁዋላ በየተራ ደጋግመው በመድፈርና በመኪናቸው ገጭተው በመግደል በላዩ ላይ ድንጋይ በማስቀመጥ ለማምለጥ ሞክረዋል። ግለሰቦቹ ተይዘው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በሁዋላ የጄራጂ ፍርድ ቤት በግለሰቦቹ ላይ የሞት ፍርድ ለማስተላለፍ በሂደት ላይ ነበር። ይሁን እንጅ ዳኛ አብዱላህ የሱፍ …

አባቶቻችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ግለሰባዊ ዓምባገነንነትን አልፈቀዱም የቤተ ክርስቲያን አሠራርና አመራር ማኅበራዊና ጉባኤያዊ ነው፡፡ ግለሰባዊ አመራር÷ ክሕደትንና ኑፋቄን ለማስገባት፣ ለሌሎች አካላት ቁጥጥር እና ዘመን የፈቀደለት ኹሉ ልቡ የወደደውን በቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲጭን ያመቻል፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንደ መኪና መሪውን የያዘ መኪናውን ወደ ፈለገው ሊወስደው የሚችልባት ቦታ ብትኾን ኖሮ ዘመነ ሱስንዮስን መሻገር ባልቻለች ነበር፡፡ *             *             * …

( …. መርዝን በመርዝነት ስለመርዝ መመረዝ :
የመርዙን ለመርዙ በመርዙ ማስመረዝ …. )
(መርዝ ……. ::) #Ethiopia #EPRP #EthiopiaTeachers #MinilikSalsawi
iframe
የታላቁ ገጣሚ እና ባለቅኔ ሃይሉ ገብረዮሃንስ (ገሞራው) አጭር የሕይወት ታሪክ http://www.debteraw.com/gemoraw/ = ድምጽ ላጣው ሕብረተሰብ ድምጽ ሆኖ በማስተጋባቱ በሶስት መንግስታት ስቃይ ያየ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሃይሉ ገሞራው – ቨድዮውን ይመልከቱት

phpBB [video]

Image

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም  ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ ጭራቁ ህዳር 2005! እ.ኤ.አ በ2005 ኢትጵያውያን/ት ለመናገር የሚዘገንን እጅግ በጣም የሚያስፈራ ድርጊትን አስተናግደዋል፡፡ በዚያኑ ዓመት በግንቦት ወር የተካሄደውን ፓርላሜንታዊ ምርጫ ተከትሎ የህዝብ ድምጽ በአደባባይ በጠራራ ጸሐይ በመዘረፉ ምክንያት ታቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ ለመግለጽ ወደ አደባባይ …

ኢትዮጵያ በ2014፡ ሁልጊዜ በህዳር አስታውሳለሁ Read more »

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።
Image

ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ አንጎላዊ ጋዜጠኛ ነው። በሙያው በሃገሩ አንጎላ በርካታ ክስ እና እስር እንደገጠመው ይነገራል። ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ ዊትስ በተካሄደው የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥሰት በመፈጸም ከአፍሪካ ህብረት ህልም በተቃራኒ ቆማለች በማለት ተችቷል። ”የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በቀዳሚነት የመላ አፍሪካውያንን ህልም ይወክላል። የሰው ልጅ ክብር እና የሰብዓዊ መብት ክብር ደግሞ የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ህልም ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የሰዎችን ሰብዓዊ መብት በመጣስ በተቃራኒው መንገድ እየተጓዘች ነው። ይህ ደግሞ የአፍሪካውያንን ህልም አይወክልም። የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በመፍታት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትን እንዲያከብር እና ዜጎች እና ጋዜጠኞች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በተግባር እንዲያውሉ እንዲፈቅድ የአፍሪካ ህብረት ጫና ማድረግ ይኖርበታል። ”

ራፋኤል በጉባኤው የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን እስር እና ክስ እንዲሁም የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን የሶስት አመት ብያኔ በማሳያነት አንስቷል። አፍሪካውያን ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቸልታ አልፈዋል ሲልም ተችቷል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ማክበር ካልቻለች የአፍሪካ ህብረት ከአዲስ አበባ መነሳት ይኖርበታል ብሎ ያምናል።

”የተወሰኑ ጋዜጠኞችን አውቃለሁ። በ2005 ተኩስ ሲጀመር እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ በአዲስ አበባ ነበርኩ። አሁን በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ በቂ ግንዛቤ አለኝ። ከኢትዮጵያውያን ምሁራን እና አሁን ባለው መንግስት የተለያየ ጫና የደረሰባቸውን ሰዎች አገኛለሁ። የአፍሪካ ህብረትን ለመወከል በመጀመሪያ ሰብዓዊ መብትን የሚያከብር ሃገር እንፈልጋለን። ኢትዮጵያ ይህንን ማድረግ ካልቻለች እንደ አፍሪካዊነታችን የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ዜጎች ራሳቸውን የመግለጽ እና ሰብዓዊ መብት ወደ ተከበረበት ሃገር እንዲዛወር መጠየቅ ይኖርብናል። ምክንያቱም ግለሰቦች የሚከበሩባት መንግስታት የህዝብ አገልጋይ እንጂ ከህግ በላይ ያልሆኑባት አጋርነት የጠነከረባት አፍሪካን እንሻለን። ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ወቅት ይህን እያደረገች አይደለም። ””

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት ብቻ በኢትዮጵያ ስድስት የህትመት ውጤቶች ሲዘጉ ከ ሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች መሰደዳቸውን ይፋ አድርጓል። በምህጻሩ ሲፒጄ ተብሎ በሚጠራው የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ተቋም መሰረት ደግሞ ቢያንስ 17 ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ በእስር ላይ ይገኛሉ። ራፋኤል ማርኩዌዝ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ አፍሪካውያን ሊተባበሩ ይገባል ሲል ይናገራል።

”አፍሪካውያን በሙሉ በተለይም ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በትብብር ከሰራን የኢትዮጵያ መንግስት ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንችላለን። አላማችን ኢትዮጵያን ማግለል አይደለም። አላማችን ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እንድታከብር ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩትንም እንድትፈታ ነው።”

http://www.dw.de/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1% … a-18051929

ፎቶ – ሐራ ተዋሕዶ

ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ በተመለከተ አሠረ ሐዋርያትን የተከተለ ሆኖ እንዲጸድቅ አድርጓል፡፡ አባቶቻችን በቤተ ክርስቲያን ላይ ግለሰባዊ አምባገነንነትን አልፈቀዱም፡፡ ጸሎተ ሃይማኖቱም ‹ነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት›› በማት ቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ዘሐዋርያት መሆንዋን ያመለክታል፡፡ በ50/51 ዓም በኢየሩሳሌም የተሰበሰበችው ሲኖዶስም ‹እኛና መንፈስ ቅዱስ› አለች እንጂ  ‹እኔ› የሚል ግለሰባዊ ድምጽ አልተሰማባትም፡፡
ኢትዮጵያውያን አበው የቅዱስ ሲኖዶስን ሥርዓት ብቻ ሳይሆን ሌሎችን የቤተ ክርስቲያን የአመራር ሥርዓቶች ከግለሰብ አምባገነንነት ለማውጣት መልካም የሆነ ሥርዓት ሠርተዋል፡፡ ቅዳሴው በአምስት ልዑካን እንዲሆን፣ አጥቢያው በሰበካ ጉባኤ እንዲመራ፣ ገዳማት በምርፋቅ (ጉባኤ አበው) ወይም በማኅበር እንዲመሩ፣ ጵጵስናን አንድ ጳጳስ (ፓትርያርክ እንኳን ቢሆን) ብቻውን እንዳይሰጥ፣ ቢያንስ ሦስት አበው ሊኖሩ እንደሚገባ፤ አንድ አባት ብቻውን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዳይለውጥ፤ አድርገው የሠሩበት አንዱ ምክንያት ግለሰባዊ አምባገነንነትን ለመቋቋም እንዲቻል ነው፡፡
ይህንን ማኅበራዊና ጉባኤያዊ የሆነ የቤተ ክርስቲያን አሠራርና አመራር ለማስወገድ በየዘመናቱ ጥረት ተደርጓል፡፡ የዚህም ምክያቱ ግልጽ ነው፡፡ ግለሰባዊ የሆነ አመራር ለሦስት ነገሮች የተጋለጠ ነውና፡፡ የመጀመሪያው ክህደትንና ኑፋቄን ለማስገባት ይመቻል፡፡ አንዱ ወሳኝ ሌላው ‹ኦሆ በሃሊ› ስለሚሆን እርሱ ትክክል ነው ያለው ትክክል፣ ስሕተት ነው ያለው ደግሞ ስሕተት ይሆናል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤያዊት በመሆንዋ አንዳንድ ግለሰቦች በየዘመናቱ ያመጡትን ክህደት በጉባኤ ተመልክታ በጉባኤ ለማውገዝ ጠቅሟታል፡፡ ደገኛ ትምርትና ድርሰት ሲገኝ ደግሞ እንዲሁ በጉባኤ ተመልክታ ለመቀበል ረድቷታል፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መጽሐፈ ምሥጢርን ጽፎ በጨረሰ ጊዜ ጉባ ሊቃውንቱ ተመልክተው ‹አማንኬ ዮሐንስ አፈወርቅ ወቄርሎስ አፈ በረከት ተንሥኡ በመዋዕሊነ፡፤ ኢትዮጵያ ተመሰለት በቁስጥንጥንያ፤ ወተአረየታ ላዕለ እስክንድርያ – በእውነት ዮሐንስ አፈወርቅና አፈ በረከት የሆነው ቄርሎስ በዘመናችን ተነሥተዋ፡፡ ኢትዮጵያም ቁስጥንጥንያን መስላለች፤ ከእስክንድርያም ልቃ ከፍ ከፍ ብላለች›› ብለው ምስክርነታቸውን ሰጥተው ነበር፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ለሌሎች አካላት ቁጥጥር ስለሚመች ነው፡፡ ጌታችን አስቀድሞ ኃይለኛውን ማሠር እንዳለው መሪውን የያዘ ቤተ ክርስቲያኒቱን አን ልቡ ለመዘወር ይመቸዋል፡፡

ይኼ ነገር በዘመነ ሱስንዮስ ጊዜ ታይቷል፡፡ ሮማውያን ግብጻዊውን ጳጳስ በሮማዊ ጳጳስ በመተካት ቤተ ክርስቲያኒቱን በሮማዊ ጳጳስ ለማስመራትና ለመቆጣጠር ፈልገው ነበር፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጠባይ ማኅበራዊና ጉባኤያዊ በመሆኑ ጉባኤ ሊቃውንቱ ከግብጹ ጳጳስ ጋር ሆኖ ተቃወማቸው፡፡ ጳጳሱና ሊቃውንቱም እስከ ደም ማፍሰስ ድረስ መሥዋዕት ሆኑ፡፡ ጥቅምት 19 ቀን 1621 ዓም በምዕራብ ጎጃም በምትገኘው ደብረ መዊዕ የተሰበሰቡት የቤተ ክርስቲያን ማኅበርተኞች ለዚህ ማስረጃ ናቸው፡፡ በዚህ የደብረ መዊዕ ጉባኤ እስከ 7000 የሚደርሱ ምእመናን፣ ካህናት፣ መነኮሳትና ሊቃውንት ተሰባስበው ነበር፡፡ የጉባኤው መሪዎችም እነ አባ ተስፋ ኢየሱስ፣ አባ ዘጊዮርጊስ ዘዋሸራ፣ አባ እንጦንዮስ፣ አባ ግርማ ሥሉስ ዘውይት ነበሩ፡፡ የጉባኤው አፈ ጉባኤ ደግሞ አባ ግርማ ሥሉስ ነበሩ፡፡በዚህ ጉባኤ የተገኙት ሁሉ ንጉሡንና አዲሶቹን ሮማውያን የሃይማኖት መሪዎች ተቃውመው እንደ አንድ ልብ መክረው እንደ አንድ ቃል ተናግረው በተዋሕዶ ጸኑ፡፡ የንጉሥ ሱስንዮስም ጦር ጥቅምት 19 ቀን ከብቦ ፈጃቸው፡፡ 
እነዚህ ጽኑአን ጉባኤተኞች ነበሩ በኋላ ዐፄ ሱስንዮስ ሐሳባቸውን እንዲቀይሩና ‹ፋሲል ይንገሥ፣ ሃይማኖት ይመለስ› እንዲሉ ያደረጋቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንደ መኪና መሪውን የያዘ መኪናውን ወደ ፈለገው ሊወስደው የሚችልባት ቦታ ብትሆን ኖሮ ዘመነ ሱስንዮስን መሻገር ባልቻለች ነበር፡፡ 
ሦስተኛው ምክንያት ደግሞ ዘመን የፈቀደለት ሁሉ ልቡ የወደደውን በቤተ ክርስቲያን ላይ እንዳይጭን ነው፡፡ በተለያዩ ዘመናት የተነሡ መንግሥታት ለራሳቸው የሚመቻቸው መሪ በቤተ ክርስቲያን ላይ ለማስቀመጥ ሞክረው ነበር፡፡ የቤተ ከርስቲያን አሠራር፣ ሕግና ሥርዓት ግን በአንድ ሰው የሚዘወር ባለመሆኑ ገመዱን ከመበጣጠስ ያለፈ ጀነሬተሩን ማቋረጥ አልተቻላቸውም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ውሳኔዎችም በጉባኤ እንጂ በአንድ ሰው ኅሊና ብቻ የሚወሰኑ ባለመሆናቸው አስተዳደራዊ ጥቅም ከማግኘትና በደል ከማድረስ ባለፈ አጥንቷን ለመስበር ዐቅም አላገኙም፡፡ 
ይህንን ታሪካዊና ቤተ ክርስቲያናዊ ሐሳብ ጠንቅቆ በመረዳት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያኒቱን ወደ ግለሰባዊ አምባገነንነት የሚወስደውን  መንገድ በማረም የቤተ ክርስቲያኒቱ ራስ ክርስቶስ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱም የበላይ ወሳኝ አካል ቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን በሕገ ቤተ ክርስቲያን አጽንቶታል፡፡ 
የሀገራችን ሰው ሲተርት ‹የማያለቅስ ልጅ በእናቱ ጀርባ ይሞታል› ይላል፡፡ ይራበው አይራበው፣ ይታፈን አይታፈን፣ ይመመው አይመመው፣ ይመቸው አይመቸው አይታወቅምና፡፡ ምናልባትም ዝምታው እንደ ጨዋነት ታስቦለት ዘወር ብሎ የሚያየው ላይኖርም ይችላል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በቤተ ክርስቲያን ላይ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ላይና በሊቃነ ጳጳሳት መብት ላይ፣ ቤተ ክርስቲያንን ሊያገለግሉ በተነሡ ማኅበራትና ወጣቶች ላይ፣ በየገጠሩ በተሠማሩና የመከራ ገፈት በሚቀምሱ ካህናትና ምእመናን ላይ የሚደርሰውን በደልና ጫና እየሰሙና እያዩ ዝም ቢሉ በእናታቸው ጀርባ ላይ ሆነው መሞታቸው የማይቀር ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱን መብት ለማስከበር ደግሞ አስቀድሞ የቅዱስ ሲኖዶሱ መብት መከበር አለበት፡፡ ያልቆመ አንገት ራስን አይሸከምም እንዲሉ፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አንድ ሆነው የቅዱስ ሲኖዶሱን መብት እንዳስጠበቁትና ቤተ ክርስቲያኒቱንም ከግለሰብ አገዛዝ እንደታደጓት ሁሉ በአጠቃላይ የሰበካ ጉባኤውና በቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤ የቀረቡትን በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሱ ያሉ ችግሮችን አንድ ሆነው ለመፍታት በቀጣይ  መነሣት አለባቸው፡፡    

Image
“ኤፈርት-መር ካፒታሊዝም” ብዙዎችን እያደኸየ ጥቂት የወያኔ ጎጠኞ ገዢዎችን ግን በሃብት
እያንበሻበሸ በመገስገስ ላይ ነው። ለመሆኑ ኤፈርት ምንድነው? የማነው?
ኤፈርት /በትግርኛው ምህፃር “ትእምት” ወያኔ በረሃ እያለ ባንኮችን፣ የመንግሥት መኪናዎችን እና የግለሰቦችን ንብረት
በመዝረፍ ያቋቋመው ህገ-ወጥ የዘራፊዎች ድርጅት ነው፡፡ ወያኔ የሚኒሊክ ቤተመንግስትን ከተቆጣጠረ ወዲህም
ኤፈርት ራሱን በአስራ ሶስት ግዙፍ ኩባንያዎች አደራጅቶ በሁሉም አቅጣጫ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመቦጥቦጥ የወያኔ
ሹማምንትን ኪስ እንዲያደልብ አደራ የተጣለበት ተቋም ነው።
በዚህም መሠረት መሶበ የኮንስትራክሽን ግብዓት ማምረቻ፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ አዲስ የመድሃኒት
ማምረቻ፣ ኢዛና የማዕድን ልማት፣ ጉና የንግድ ድርጅት፣ ሕይወት የግብርና ሜካናይዜሽን፣ ሳባ እብነ በረድ ማምረቻ፣
ሼባ የቆርቆሮ ፋብሪካ፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ አልሜዳ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ ኤክስፕረስ የትራንዚት አገልግሎት፣
ኢትዮጵያን እንወቅ አስጎብኚ ድርጅት እና ትራንስ ኢትዮጵያ የጭነት ማመላለሻ አገልግሎት የተሰኙ ግዛዙፍ
ኩባንያዎችን አቋቁሞ እንደ ተባይ ድሆች ኢትዮጵያንን የሚመጥ “ካፒታሊዝም” ኢትዮጵያ ውስጥ ለማንሰራፋት
ተንቀሳቀሰ። ከጥቂት ዓመታት ሥራ በኋላ የቁጥጥር አድማሱን በማስፋት ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ፣ ማይጨው
ፓርቲክል ቦርድ ፋብሪካ፣ ዲማ የማር ማጣሪያ፣ አላጌ ደንና የደን ውጤቶች፣ ናሽናል ጂኦ-ቴክስታይል እና አበርደሌ
የእንስሳት ማድለቢያና ኢክስፖርት ድርጅት የተባሉ ስድስት ኩባንያዎች የያዘው ደጀና ኢንዳውመንት ተጨመረለት።
ይህ በአደባባይ የሚታወቀው ኤፈርት ነው። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በቅርበት የሚከታተሉ እንደሚያውቁት ሁሉ ኤፈርት
በኮንትሮባንድ ንግድ ጭምር የገባ “ወንበዴ ድርጅት” ነው። ኤፈርት ያሻውን ያህል ተበድሮ ያለመክፈል ልዩ ፈቃድ
ያለው ቅምጥል ድርጅት ነው፡፡ እስካሁን ከሶስት ቢሊዮን በላይ የባንክ እዳ እንደተሰረዘለት ይወራል፡፡ የህወሓት
ማዕከላዊ ኮሚቴ በተሰበሰ ቁጥር ከማይቀሩ አጀንዳች አንዱ ትዕምት (ኤፈርት) ነው። ለኤፈርት የቦርድ አባላትንም ሥራ
አስኪያጆችንም የሚሾምለት ህወሓት ነው። የአገሪቱ የፓርቲዎች ህግ ፓርቲዎች እንዳይነግዱ ይከለክላል። ህጉ ሕወሓት
ላይ አይሠራም። እርግጥ ኤፈርት ዘራፊ እንጂ ነጋዴ ስላልሆነ አዋጁ አይመለከተውም።
የኤፈርት ኢትዮጵያን የመዝረፍ ሕልም ትልቅ ነው። “በግል” ባንኮችም የአንበሳ ድርሻ አክሲዮን በመያዝ የፋይናንስ
ሴክተሩን ሊቆጣጠረው ደርሷል። በአገሪቱ ያሉ ያሉ ዋና ዋና የቢዝነስ ኮንትራቶችን የሚወስደው ኤፈርት ነው። ለሕዳሴ
ግድብ ግንባታም ዋና እቃ አቅራቢ ነው። የአገሪቱን 40 በመቶ የፒቪሲ (ፕላስቲክ ነክ ምርቶች) ገበያ ለመቆጣጠር
የሚያስችለውን ማምረቻ እየገነባ ነው። ኤፈርት የድሀውን ገንዘብ እየሰበሰ ለወያኔ ጄኔራሎችና ሹማምንት የሚያድል
አገርን ለማጥፋት የተቋቋመ ተቋም ነው። “የሙስና መርከብ” የኤፈርት የቤት ስሙ የሆነው ያለምክንያት አይደለም።

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም – በነጻነት ለሀገሬ)

 

.. 1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ (ክፍል 2)

ባለፈው ሳምንት ባቀረብኩት ትችቴ (እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፡ ክፍል1)፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት ረኃብን በማስመልከት ሳቀርባቸው በነበሩት ትችቶች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እና አሁን በህይወት የሌለው መሪው መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት ረኃብ የለም በማለት ሙልጭ አድርገው በመካድ ሲያደርጉት የነበረውን ተራ ቅጥፈት በማጋለጥ በተጨባጭ መረጃዎች ላይ በመመስረት ስሞግት የቆየሁባቸውን ዋና ዋና ጭብጦች በማካተት ክለሳ ማድረጌ ይታወሳል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

‹‹ኢህአዴግ በጭቆና ውስጥ ጸጥ ብሎ የተቀመጠን ሕዝብ እየቆሰቆሰ ነው››

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ከቃሊቲ እስር ቤት

(በኤሊያስ ገብሩ – ጋዜጠኛ)
ትናንት፣ በዕለተ ዓርብ እኔ እና የዕንቁ መጽሄት ማኔጂንግ ዳይሬክተር ከሆነው ፍቃዱ ማህተመወርቅ (ባሪያው) ጋር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና ፖለቲከኛን አቶ አንዷለም አራጌን በቃሊቲ ተገኝተን ጠይቀናቸው ነበር፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተላለፈ አገራዊ የጸሎት ጥሪ

በኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር

አገራችን የክርስትናና እስልምና ኃይማኖቶችን በመቀበል ቀደምት በመሆኗ ብቻ ሳይሆን የኃይማኖቶቹ ተቋማት፣አባቶችና ምዕመናን በመከባበርና መቻቻል አብረው በሠላም በመኖር ለዓለም ህዝብ ተምሳሌት መሆናችን የምንኮራበት ነው፡፡ ለዚህም የቤተ እምነቶቹ አባቶች ለምዕመናኑ ያስተማሩት የሞራልና ሥነ-ምግባር እሴቶችና በአብሮነት ላይ የቆመ የአገር ፍቅር ስሜት፣ እነዚህንም እንዲጠብቋቸውና እንዲያከብሯቸው አርዓያ በመሆን ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡

አገራችንና ህዝቧ በተፈጥሮ ሚዛን መዛባት በሚከሰትም ሆነ በአገዛዝ ሥርዓቶች ምክንያት በችግር ውስጥ በሚወድቁበት ጊዜ ሁሉ የእነዚህ ኃይማኖቶች ተቋማትና ምዕመናን መዓቱ እንዲርቅና ምህረቱ እንዲወርድ ፈጣሪያቸውን በጾምና በጸሎት በመለመን/ በመማጸን፣ በሃይማኖታዊ የሞራልና ሥነ ምግባር እሴቶቻቸው መሠረት በመተዛዘን ፣ በመረዳዳትና በመተጋገዝ የተገኘውን በመካፈል በአብሮነት ስሜት በርካታ ክፉ ጊዜያትን መሻገራቸው በታሪክ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡

ዛሬ ላይ እነዚህ የሞራልና ሥነ-ምግባር እሴቶች እየተናዱ በመሄዳቸው ዜጎች ለማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ምስቅልቅል ተጋልጠዋል፣ የአገር ፍቅር ስሜት በጥያቄ ውስጥ ወድቋል፡፡ በዚህም በመቻቻል ፋንታ ግጭትና መፈናቀል በአራቱም አቅጣጫ ህዝብን ለሥቃይና ሥጋት ዳርጓል፣ የህግ ‹‹አምላክ›› ክብር እያጣ ፍትህ እየተዛባ ነው፣ ወህኒ ቤቶች በታሳሪዎች ተጨናንቀዋል፣ የምግብ ተረጂውና የጎዳና ላይ ተዳዳሪው ዜጋ ቁጥር ተበራክቷል፣… በአጠቃላይ የህዝባችን ኑሮና ህይወት፣ የአገራችን ሠላምና መረጋጋት ፈታኝና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ናቸው፤ የዜጎች ተስፋ በመናመኑ የህይወት ዋጋ በሚጠይቅ ሁኔታ ውስጥ እየተሰደዱ በባዕድ አገር ለአደጋ እየተጋለጡ ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በአገራችን ያሉ የተፎካካሪ ፓርቲዎች/ገዢው ፓርቲና ተቃዋሚዎች/ ተጨባጩን ሁኔታ የሚመለከቱበትና የሚረዱበት መንገድ በሁለት ጫፍ ላይ በመወጠሩ የጋራ መፍትሄ ለማምጣት ያለው ዕድል በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በመሆኑ ችግሮቹን እያባባሰ ይገኛል፡፡ ስለዚህ፡-
በአገራችን ውስጥ በተለያየ ምክንያት በሁለት ጠርዝ ላይ የቆሙ ኃይሎች ወደ ብሄራዊ መግባባትና ዕርቅ እንዲመጡ፣ በህዝብ ውስጥ የሚታየው የሞራልና ሥነምግባር ጉድለት እንዲቃናና የመቻቻልና መተሳሰብ ስሜት እንዲያንሰራራ፣ የዜጎች ሥቃይና ሥጋት ተወግዶ በተስፋ እንዲሞላ፣….፤

በአገራችን መረጋጋትና ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን፣ ቀጣይና ዘላቂ ልማት እውን እንዲሆን፣ አብሮነታችንና አንድነታችን እንዲጠናከር፣ የአገር ፍቅር ስሜት እንዲለመልምና ለሉዓላዊነታችን ያለን ቀናዒነት እንዲጠናከር፣….፤

በሰንበትና የጁምኣ ቀናት በጋራ እንዲሁም በየግል የዘወትር ጸሎት ፈጣሪ አምላክን በመለመን ለተያያዝነው አገራዊ ዓላማና የጋራ ጥረት ድጋፋችሁን እንድታደርጉ ለየቤተ እምነት ኃላፊዎች /ቤተ ክርስቲያናትና መስጂዶች/ እና ለምዕመናን በሙሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ፈጣሪ አምላክ አገራችንንና ህዝቧን ከጥፋት ይታደግ ዘንድ በጸሎት እንትጋ!!

ኅዳር 01 ቀን በ2007 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘዉን መኢአድን የተመለከተ የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት :: ======================================= – “መኢአድን ለማዳን እንረባረብ::” የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ – ከድርጅቱ የተባረሩ የወያኔ ቅጥረኞች በእርቅ ስም ወደ ድርጅቱ ተመልሰዋል::(አባላት) – ጠቅላላ ጉባዬው የተካሄደው ፍጹም አምባገነንነት በሞላበት ሁኔታ ነው:: በኢትዮጵያ በአንጋፈነቱ የሚታወቀው እና በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ […]

የኢትዮጵያ አትሌቶች በተለያዩ አለምአቀፍ የማራቶን ሩጫ ውድድሮች ድል ተቀዳጅተዋል። ፍቃዱ ግርማና ሙሉሀብት ጸጋ በቤይሩት፥ ሹሜ ሀይሉ በፈረንሳይ አሸንፈዋል። ጊዜአቸውም የፍቃዱ 2 – 12 – 26 እና 2- 29 – 15 ተመዝግቧል። በፈረንሳዩ የአልፕስ ማራቶን ደግሞ የወንዶቹን ሹሜ ሃይሉ በአንደኝነት አጠናቋል።

በሕገ ወጥ መንገድ የቴሌኮምዩኒኬሽን መሳሪዎችን በማስገባት የተጠረጠሩ ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተዘገበ። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የውጭ አገር ዜጎች እንደሚገኙባቸው ተገልጿል።

ድርጊቱ አገሪቱን በብዙ ሚሊዮን ዶላር እንዳሳጣትም ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ››በሚል መርህ ትብብር  የመሰረቱት 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች ቀደም ብለው ባሳወቁት የአንድ ወር መርሃ ግብር መሰረት የጀመሪያውን ጥሪ ለሃይማኖት ተቋማት አድርገዋል። ፓርቲዎቹ አገራችንና ህዝቧ በተፈጥሮ ሚዛን መዛባት በሚከሰትበትም ጊዜ ሆነ በአገዛዝ ሥርዓቶች ምክንያት በችግር ውስጥ በሚወድቁበት ጊዜ የኃይማኖት  ተቋማትና ምዕመናን ሚና ከፍተኛ እንደነበር አውስተው፣ ዛሬ ላይ እነዚህ …

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹በተለይ ባሳለፍነው አንድ ሳምንት ጊዜያት ውስጥ መቆራረጡ በወሳኝ ሰዓታት ጭምር ማለትም በምሽት እና በጠዋቱ ጊዜያት ተጠናክሮ መቀጠሉን የገለጹት ነዋሪዎች በዚህ ምክንያት ለከፍተኛ ኪሳራና ወጪ እየተዳረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ባለስልጣናት «የኃይል እጥረት የለም፣ እንዲያውም ተርፎን ለጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት እያደረግን ነው» በሚሉበት በዚህ ወቅት በተለይ የአፍሪካ ርዕሰ መዲና መሆንዋ በሚነገርላት አዲስአበባ …

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-‹በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት ከገቢያቸው ጋር በማይመጣጠን የግብር  እዳ እየተሰቃዩ  ነው። የገዢው ፓርቲ ባለስልጣኖች አድሎአዊ በሆነ መልኩ በሚጥሉት ግብር ነጋዴዎች ድርጅታቸውን እየዘጉ ነው። በእነብሴ ሳር ምድር   ወረዳ አሰፋ ሁነኛው፣ ኢሳየ ቸኮል፣ የንጉስ ዋለና  መሰሉ የሚባሉት ነጋዲዎች በጋራ ለቤት መስሪያ በባንክ ከስያዙት  ገንዘብ ላይ ያለፍላጎተቻው …

ጥቅምት ፴(ሠላሳ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ታማኝ የሆኑ የደህንነቶች ሰራተኞች ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የጦር መሳሪያ እና ሌሎች እቃዎችን ጭነው ሲጓዙ የነበሩ 4 መኪኖችን አስቁመዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቃል አቀባይ ስቴቨን ዱጃሪክ እንደገለጹት የደህንነት ሰራተኞች መሳሪያዎቹ ለአንድ ተቃዋሚ ሃይል ሊሰጥ ነው በሚል እንደያዙትና በሹፌሮቹ ላይ ጉዳት እንዳደረሱባቸው ገልጸዋል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት …

– “መኢአድን ለማዳን እንረባረብ::” የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ
– ከድርጅቱ የተባረሩ የወያኔ ቅጥረኞች በእርቅ ስም ወደ ድርጅቱ ተመልሰዋል::(አባላት)
– ጠቅላላ ጉባዬው የተካሄደው ፍጹም አምባገነንነት በሞላበት ሁኔታ ነው::

Minilik Salsawi

በኢትዮጵያ በአንጋፈነቱ የሚታወቀው እና በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የተመሰረተው መአሕድን የተካው በኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ሲመራ ቆይቶ አቶ አበባው መሃሪ የተረከቡት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ (መኢአድ)ከባድ የመፈረካከስ አደጋ ከፊቱ ተደቅኗል ሲሉ የድርጅቱ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ በላኩት መረጃ ገልጸዋል::

መኢአድ ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚያደርገውን ውህደት ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከድርጅቱ የተባረሩትን እነ አቶ ማሙሸት እና ኮሎኔል ታምሩን አደራጅቶ ውህደቱን በመበጥበጥ በመኢአድ ቢሮ ውስጥ ከዚህ ቀደም በተደረገ ስብሰባ ላይ ደህንነቶችን እና ፖሊሶችን አስከትሎ በመምጣት ከፍተኛ የሆነ ብጥብጥ አንስተው የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸው ቀርቷል::

ውህደቱ የጉሮሮ ላይ አጥንት የሆነበት የወያኔው መንግስት ምርጫ ቦርድን ተገን በማድረግ መኢአድን በማጉላላት ውህደቱ እንዳይፈጸም ከፍተኛ ደባ ከቅጥረኞቹ ከነማሙሸት ጋር በመሆን ሲፈጽም ቆይቶ በስተመጨረሻ ኢንጂነር ሃይሉን በማስገደድ የተባረሩ አባላትን አቶ አበባው መልሶ እንዲያስገባ ካላስገባ ስልጣኑን እንዲለቅ በሚል ጫና የበላይ ጠባቂነታቸውን ተገን በማድረግ የወያኔ ስራ አስፈጻሚዎች ወደ ድርጅቱ ሰርገው በመግባት ድርጅቱ አደጋ ውስጥ መሆኑን የድርጅቱ አባላት በምሬት ተናግረዋል::

ኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ከዚህ ቀደም ከወያኔ ጋር ከድርጅቱ እውቅና ውጪ በራሳቸው ፍቃድ ከሟቹ መለስ ዜናዊ ጋር የምርጫ ደንብ የሚል ስምምነት ተፈራርመው ድርጅቱ እንዲዳከም እና ለወያኔዎች በሩን እንዲከፍት ያደረጉ ሰው ቢሆንም ቀደም ብለው ለትግሉ የከፈሉት አስታውጾ ታይቶ የድርጅቱ የበላይ ጠባቂ እና አማካሪ ቢደረጉም በድርጅቱ ማህተም የተባረሩ ቅጥረኞች ወደ ድርጅቱ እንዲመለሱ አድርገዋል ሲሉ አባሎቹ ተናግረዋል::ኢ/ር ሀይሉ ሻውል በፍጹም አምባገነንነት ጉባኤተኛውን አፍነው እርሳቸው በሚፈልጉት መልኩ በእርቅ ጭምብል አንዱን አስወጥተው አንዱን አስገቡ፡፡ ሲሉ የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ ተናግረዋል::

ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘዉን መኢአድን የተመለከተ የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት ::
viewtopic.php?f=2&t=89291

ጎርቫቾቭን ታቸር ከለንደን ሬገን ከዋሽግተን እየተቀባበሉ ሲያንቆለጳጵሷቸዉ፤ መራሔ መንግሥት ሔልሙት ኮል የቀዳሚዎቻቸዉንም፤ የራሳቸዉንም የሕዝባቸዉንም ሕልም ምኞት እዉን ለማድረግ ሞስኮዎችን እንደ ጥሩ ወዳጅ ቀረቧቸዉ።አግባባቡ አባበሉ።

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።

የአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ፣ እንዲሁም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዚሁ ማጣሪያ ውድድር የጀመረው ዝግጅት፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ያደረጉበት የቤሩት፣ ሊባኖስ እና የኒስ፣ ፈረንሳይ አትሌቲክስ ውድድር፣ የሳምንቱ

የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት ::
መግቢያ –
——-
“የቱ ይቀድማል?:- በዲክራሲያዊ መርህ ላይ የቆመ ሀገር ወይስ ዲሞክራሲን ሊሸከም የሚችል ባህል ላይ የቆመ ማህበረሰብ ?” በሚለዉ ጽሁፌ የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን የዉይይትና የክርክር ባህል አለመዳበርን በማስመልከት የተወሰኑ ፓርቲዎችን እያነሳሁ ወቅሼአቸዉ ነበር:: ፓርቲዎች ዉስጥ በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ የሀሳብ ክፍፍል ሲነሳ ፓርቲዎች በሀሳብ የመሸናነፍ ባህል እንዳላዳበሩ ምሳሌ አድርጌ ካቀረብኩት ፓርቲ አንዱ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ነበር:: እንዲህም ስል ፓርቲዉን በሀሳብ ሸንቆጥ አድርጌዉ ነበር:-

“መኢአድ ዉስጥ ችግር ከተፈጠረ አራት አመታት አለፉ:: በርካታ የእርቅ ጥረቶች እንደተደረጉ የኢትዮጵያ ሰዉ አስተዉሏል :: በልዬ ልዩ ሚዲያዎችም ላይ ተደምጧል:: ሆኖም በሃሳብ የተለያዩት ሰዎች አንድም ቀን ቁጭ ብለዉ ተደማምጠዉ በሀሳብ ተፋጭተዉ እና ልዩነታቸዉን አቻችለዉ መፍትሄ ላይ ሲደርሱ አልታዬም:: አንዱ ሌላዉን ይወነጅላል:: አንዱ አንዱን ሰርጎ ገብ ነዉ : ባንዳ ነዉ ሲል ስሙን ያጠፋል:: ደግሞ አንዱ እሱ ብቸኛ የድርጅቱ ተጠሪ ይሆንና ሌላዉን ለማግለል ዳዉላ ሙሉ ከዚያም ዘሎ ከቶንም ስፍር የበለጠ ሀሰትና ዉሸት ይደረድራል:: እናም መደማመጥና መነጋገር ብሎም በሀሳብ መፋጨትና ወደ መቻቻል መድረስ ቦታም አላገኙም:: አስቂኙ ነገር ታዲያ መኢአድ ዉስጥ ተከፋፍለዉ ያሉ ብድኖች ሳያፍሩ ስለ ብሄራዊ እርቅ ጉዳይ ሲናገሩ መስማት የተለመደ ነገር መሆኑ ነዉ:: እራሱን ከራሱ ጋር በሀሳብ ተከራክሮና ተወያይቶ ለማስታረቅ ያልቻለ ቡድን ስለብሄራዊ እርቅ ሲያወራ መስማት እጅግ አስቂኝ ነገር ነዉ::”

ይሄን ወቀሳ ያወረድኩበት በመኢአድ ላይ ብቻ አይደለም ነበር:: ሌሎችም የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎችንም አጣቅሸ ነበር:: ሆኖም ዛሬ ትኩረቴን መኢአድ ላይ አድርጌአለሁ:: ምክንያቱም ዛሬ መኢአድ ማንም ኢትዮጵያዊ ያላሰበዉን እና ያልጠበቀዉ የዲሞክራሲ ማማ ላይ ተፈንጥሮ ወጥቶ ተገኝቷልና::

ለራሱ ሀሳብና ህሊና ብቻ ተገዥ የሆነዉ ደፋሩ : እዉቁና ወጣቱ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ባንድ ወቅት የመኢአድ ሰዎች እርስ በርስ ንክሻ እና አለመግባባት ብቻ ሳይሆን በፕሮፌሰር አስራት የሙት አመት ላይ እንኳን ሲጣሉ ቢያስተዉል ” ዛሬ የፕሮፌሰር አስራት ሙት አመት ብቻ ሳይሆን የመኢአድም ሙት አመት ነዉ” ሲል መጻፉን አስታዉሳለሁ::

እኔም ሆንኩ ተመስገን ደሳለኝ በመኢአድ ላይ ትችቶችን ያወረድንበት ወደን ሳይሆን በሚጠበቅበት ስፍርና ቁመት ልክ ሆኖ አልገኝ ስላለን ነበር:: መኢአድ ከ2003 ዓም እስከ አሁኑ ጥቅምት 30/ 2007 ዓም ድረስ ለአራት አመታታ ያሳለፈዉ ዉጣ ዉረድ እና አባላቱም በአምስት ቡድን ተከፋፍለዉ ያደረጉት ሽኩቻ ጉድ የሚያስብል ብቻ ሳይሆን ወይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚያሰኝ ነበር:: አንድ ፓርቲ አምስት ቡድን ተከፋፍሎ መልሶ ሊድን የሚችለዉ እንዴት ነዉ?

የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ወደ ዲሞክራሲ የከፍታ ጉዞ ?
========================================

ለአራት አመታት በአምስት ቡድኖች ተከፋፍለዉ የማያቋርጥ አሉባልታ: ስድብ ወቀሳና ክስ ላይ ተጠምደዉ የነበሩ ሀይሎችን ወደ አንድ ማምጣትና በዉይይት ችግራቸዉን ፈትተዉ እርቅ ወርዶ አንድ የፖለቲካ ሀይል ሆነዉ እንዲቀጥሉ ማድረግ ይቻላል? ለአራት አመታት ያስተዋልነዉ ነገር አይቻልም የሚል ፍጹም አስተማማኝ ድምዳሜ ላይ መድረስ ነበር:: ለዚህም ነዉ ከንግዲህ የመኢአድ ነገር አከተመለት የተባለዉ ነበር::

የሆኖ ሆኖ በጠንካራ ሽማግሌዎች እረዳትነት እያንዳንዱን አምስት የተለያዬ ቡድን በማነጋገር : በተለያዬ ወቅት አመራር በመሆን የተመረጡትን ሀይሎች ሁሉ በማካተት እንዲሁም አንድንም ወገንን ያላገለለ : ከገጠር እስከ ከተማ ያለዉን አመራር በማካተት ጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ አስገራሚ ዉጤት ላይ የደረሰ ፓርቲ ሆኖ ወጥቷል:: ዉጤቱን አስገራሚ ያደረገዉም የጠቅላላ ጉባዔዉ ሂደት እጅግ ጠንካራ: በበርካታ ሙግቶች : ክርክሮች : ፊት ለፊት በሚነሱ የተፋጠጥ አካሄዶች እዲሁም አንድም እዉነት ሳይቀር እዚችዉ እህዝብ ፊት ትፋት የሚል አካሄድ የታጀበ መሆኑ ነበር::

እያንዳንዱ ቅሬታ አለኝ የሚል ቡድን ከስድስት መቶ ተሰብሳቢ በላይ ባለበት እዉነት ስትሞግተዉ ወይ ያቀረቅራል ወይም እዉነትን ተርትሮ ለተሰብሳቢዉ ያስረዳል;: ተሰብሳቢዉ ያደምጣል: አፋጣጭ ጥያቄን ይጠይቃል ብሎም ደግሞ ብይንን ይበይናል:: መሸወድ አይቻልም:: ብዙሃን እዉነትን እሰዉ ፊት ላይ ያነባታል: ብዙሃን እዉነትን ከሰዉ ኪስ ዉስጥ በርብሮ ያወጣታል:: አሉባልታ ተናግሮ ማምለጥ አይቻልም:: ፊት ለፊት ላሉባልታዉ መልስ የሚሰጥ ወገን አለና:: ከሁሉም በላይ ደግሞ አይኑን እና ጆሮዉን አንቅቶ የሚያስተዉል ከስድስት መቶ በላይ ህዝብ አለና:: የትም መደበቅ አይቻልም:: የዲሞክራሲ ዉበቱ ህዝብ ፊት እራቁትን ስለሚያስቆም ነዉ::

እናም እያንዳንዱ ቡድን ከጥቅምት 28 እስከ ጥቅምት 30/2007 ዓም በተደረገዉ እልህ አስጨራሽ ግን ደግሞ የዲሞክራሲ የከፍታ ማማ ላይ የረገጠ ሊባል በሚችል የጠቅላላ ጉባዔ ሂደት ዉስጥ ያለዉ አማራጭ ወደ አንድ መምጣትና በጋራ ለዲሞክራሲ መታገል መሆኑን በደንብ የተማረበት: እያንዳንዱንም ለሌላው ወገን ያስተማረበት ወቅት ሆኖ አልፏል:: ለሶስት ቀናት በዘለቀዉ የስብሰባ ሂደት ዉስጥ እስከ ለሊቱ ስድስት ሰዓት ድረስ በማምሸት የተደረገዉ የዲሞክራሲ ከፍታ ላይ የደረሰ የሀሳብ ፍጭት: ክርክር: እና ዉይይት እጅግ ገንቢና ለወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ጥሩ ልምድ ጥሎ ያለፈ አስተምህሮት ይመስላል:: እዚህች ጋ በተለያዩ ፓርቲዎች ስር የታቀፉ ፖለቲከኞቻችን ፈገግ ሲሉ ይታዩኛል:: እኛማ የዲሞክራሲዋን ቁልፍ ጨብጠናታል ሲሉ ፈገግ ማለታቸዉ አንዱ የዲሞክራሲ ድቀት መገለጫ መሆኑን እናጣቅስና እንለፈዉ::

ሀይሉ ሻዉል ከ28-30/3007 ዓም ባሉት መጨረሻ የፖለቲካ ቀኖቻቸዉ ዉስጥ የሰጡት አመራርም ብዙዎቹን አስገርሟል:: “ከንግዲህ እኔ ከማንም ጋር ጸብ የለኝም:: እያንዳንዳችሁም እርስ በርሳችሁ መታረቅና በመሃከላችሁ ያለዉን ጸብ ንዳችሁ አብራችሁ መስራት አለባችሁ::” ይሄን አቋማቸዉን የተፈታተኑ አንዳንድ ወገኖች ቢኖሩም የብዙሃኑም ተሰብሳቢ ዋና ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሂደትን ማዬት እንጅ ብጥብጥ ስላልነበረ ነገሮች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቅ ችለዋል:: በዉነቱ ሂደቱ እጅግ አስጨናቂ እንደነበረ ከ20 በላይ ተሰብሳቢዎችን አንድ ባንድ ቃለ መጠይቅ በማድረግ ተረድቻለሁ:: ብዙዎች እንዳሉትም በመጀመሪያ አካባቢ ሂደቱ ከመክበዱ የተነሳ አንድ አጀንዳ ላይ አንድ ቀን የመዋል አካሄድ እንደነበርም አብራርተዉልኛል::

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት
=================================================
ማሙሸት አማረ የመኢአድ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆኖ በከፍተኛ ድምጽ ተመርጧል:: ማሙሸት አማረ ገና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲት የአንደኛ አመት ተማሪ ሆኖ ዩኒቨርስቲ እንደ ገባ ወገን ሀገርህ አይደለም ተብሎ ካባቶቹ ሀገር ሲባረርና ገደል ሲገፈተር የምን ትምህርት ነዉ ሲል ከፕሮፈሴር አስራት ጋር የፖለቲካ የትግል አዉድማ በወጣት እድሜዉ የተቀላቀለ ሰዉ ነዉ:: አቶ ማሙሸት በፖለቲካ ሂወት ዉስጥ እየተመላለሰም በርካታ የትምህርት ዘርፎችን በማጥናት እራሱን ለአመራር ብቁ ያደረገ ሰዉ ነዉ :: በማርኬቲን ዲፕሎማ: በሊደርሽፕ/አመራር/ ዲፕሎማ እንዲሁም በማኔጅመንት ዲግሪዉን አጠናቋል:: በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በፖለቲካ ሳይንስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የቀጠለ ብርቱ የሰላማዊ ትግል መሪ ነዉ::

ለአስራ ሁለት አመታት የታሰረ ሰዉ ቢሆንም በኢትዮጵያ ፖለቲካ የማይማረር : በዲሞክራሲ ሂደት የሚያምን እና የሚያምንበትን ሀሳብ ፊት ለፊት የሚያራምድ ፖለቲከኛ ነዉ:: በቅርበት የሚያቁትም እንደሚገልጹት ለሚያምንበት ነገር ብቻ የሚኖር ሰዉ ሲሉ ይገልጹታል::

ማሙሸት በሀሳብ ልዩነት ያምናል:: በክርክር ያምናል:: ሰዉ አክባሪ እንደሆነ የሚነገርለት ማሙሸት ተናግሮ የማሳመን አቅሙን አብረዉት የሰሩ ሁሉ ይመሰክሩለታል:: ከ28-30/2007 ዓም በተደረገዉ ጠቅላላ ጉባዔ ላይም ይሄንኑ ተናግሮ የማሳመን ችሎታዉን እንዳስመሰከረ ብዙዎች ተስማምተዉለታል:: ሆኖም ማሙሸት አንድ ነገር አይሆንለትም:: ይሄዉም እዉሸትና መስሎ ማደር:: ይሄ ነገር ለፖለቲካ ሂወቱ ዋናዉ ተግዳሮትም አዎንታዊ ገጽታም ሆኖ ከፊቱ የተደነቀረ ይመስላል::

ለአራት አመታት ከማሙሸት አማረ ጋር በሀሳብ ተለያይተዉ የከረሙትና በማሙሸት ላይ ክፉኛ ቂም ይዘዉ የነበሩት ኢ/ር ሀይሉ ሻዉል ከማሙሸት ጋር ሲታረቁ ማሙሸት ለአቶ ሀይሉ በሽማግሌዎች ፊት ያቀረበላቸዉ አንዱ ጥያቄ “ለመሆኑ እኔ እርስዎን ሰድቤዎታለሁ?” የሚል ጥያቄ ነበር:: ሀይሉም ” እረ በፍጹም” ሲሉ መለሱ:: ማሙሸትም በማስከተል ” ታዲያ ሚዲያዉ ሁሉ ማሙሸት አማረ አቶ ሀይሉን ሰደባቸዉ እያለ ሲያናፍስ እርስዎ ዝምታን የመረጡት ለምን ነበር?” ሲል ጠየቀ:: ሀይሉም መለሱ “እኔ ለያንዳንዱ ሚዲያ ያሉባልታ ወሬ ምላሽ ልሰጥ የምችልበት እድሜ ላይ አይደለሁም” ሲሉ መለሱ::

“እኔና አንተ የተጣላንዉ አንተ ለእኔ አልታዘዝም ስላልክ ብቻ ነዉ” ሲሉ አስከትለዉ ሀይሉ ተናገሩ:: ማሙሸትም ለአቶ ሀይሉ ሲመልስ ” እኔ ለእርስዎም ሆነ ለማንም ህገወጥ በሆነ መንገድ የምታዘዝ ሰዉ አይደለሁም:: ከእርስዎም የተጣላንዉ እርስዎ የድርጅቱን ህገ ደንብ ጥሰዉ ያለስልጣንዎት የማይገቡ ዉሳኔዎችን ስለወሰኑ ነዉ::አሁንም ሆነ ወደፊት የድርጅትን ህገ ደንብ የሚጥስ መሪ አምባገነን መሪ ነዉ:: የተጣላንዉም እርስዎ ህግ ስለጣሱ ነዉ:: አሁን ያለዉን አምባ ገነን ስርዓት እየታገልን በተቃዋሚ ፓርቲዎች ዉስጥ ደግሞ የፓርቲ አምባ ገነንነትን አናበረታታም:: ማንኛዉንም አይነት አንባገነንነትን እንታገለዋለን እንጅ:: ” ሲል ቁርጥ ያለ መልስ መለሰ::

ማሙሸት በማስከተል እንዲህ አለ “አባቴ ገና ዩኒቨርስቲ አንደኛ አመት ተማሪ እያለሁ ጠርቶ “ወገን እያለቀ ዝም የምትሉት ምንድን ነዉ? ከፕሮፌሰር አስራት ጋር ተነስታችሁ ታገሉ:: ለእዉነት ሙት” ሲል ለእዉነት ብቻ እንድኖር መመሪያ ሰጥቶኛል:: እዉነትን ማንም ከጣሳት ከዚያ ሀይል ጋር በሀሳብ ሙግት መግጠሜ አይቀርም:: ከርስዎም ጋር የሆነዉ ይሄዉ ነዉ::” ሲል አስገራሚዉን ያባቱን ታሪክ ተናገረ:: ግን በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት አባቶች አሉ እንዴ የሚያስብል ነገር ነዉ::

እናም ሀይሉ ሻዉል ጠቅላላ ጉባዔዉ በተደረገበት ቀን አንድ አስገራሚ ነገር ተናገሩ ” እናንተ ይሄን ማሙሸትን አታቁትም:: እሱ የሚለዉ እዉነት ብቻ ትዉጣ ነዉ:: እንደ ፖለቲከኛ የሚያድበሰብሰዉ ነገር የለም:: የሚፈልገዉ እዉነቷን ብቻ ነዉ:: በአንደበቱ ሁለት ወይም አንድ ነገር አይናገርም:: አንድ ነገር ብቻ ይናገራል:: እሱም እዉነት ብቻ::”

የጠቅላላ ጉባዔዉ ተሰብሳቢ በአቶ ሀይሉ ንግግር እየተገረመ እያለ ድርጅቱን ለተወሰነ ጊዜ በፕሬዝዳንትነት የመሩት አቶ አበባዉ ደግሞ (ከማሙሸት ጋር ጸብ የነበሩ ናቸዉ) ብድግ ብለዉ ” አቶ ማሙሸት ድርጅትን በመክዳት ወይም በገንዘብ ወይም በሌላ በምንም መጥፎ ባህሪ አይታማም :: የሱ ችግር ሀይለኝነት ብቻ ነዉ:: ተጋፋጭ ነዉ:: እልህኛ ነዉ” ሲሉ ስለ ማሙሸት አማረ ያላቸዉን አመለካከት አካፈሉ::

እንግዲህ እነዚህና ከሌሎችም በርካታ ምንጮች የሰበሰብኋቸዉ መረጃዎችን ስተነትናቸዉ ማሙሸት አማረ አሁን በተረከበዉ የፕሬዝዳንትነት ሀላፊነት ቦታ ላይ የሚያሳካቸዉ በርካታ አዎንታዊ ጉዳዮች እንደሚኖሩ መገመት ይቻላል:: እንዲሁም የሚገጥሙት ተግዳሮቶች ቀላል የሚሆኑ አይመስለኝም::

እነዚህ አሉታዊና አዎንታዊ ፈተናዎች ከኢትዮጵያ ባህላዊ ጽንፍ ዉስጥ መንጭተዉ የሚዎጡ ጭብጦች ናቸዉ:: በኢትዮጵያ እዉነት ወዳዱ ሰዉ ፍጹም እዉነት ወዳድ ነዉ:: ሸፍጠኛዉ ደግሞ ጽንፈኛ ሸፍጠኛ ነዉ:: ፕሮፌሰር ሰባስኪ የተባለ የጣሊያን ፕሮፌሰር የኢትዮጵያ ታሪክ በፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት በሚለዉ መጽሀፉ (እምሻዉ አለማዬሁ ወደ አማርኛ ተርጉሞታል ) አንድ አስገራሚ መረጃን አካፍሎናል:: ጣሊያኖች ስለ ሀበሻ ስነ ልቦና ጥናት አደረጉ:: በርግጥ ጥናቱ ወታደራዊ ጥናት ስለነበረ ያተኮረዉ የሀበሻን ሰዉ ስነልቦና ከወታደራዊ ጭብጥ አንጽር የመተንተን ስራ ላይ ነበር::

እናም የጥናቱ ዉጤት አስገራሚ ነበር:: አጭር የጥናቱ ድምዳሜም ሀበሻ ጀግና ከሆነ ፍጹም ጀግና ነዉ:: ከአፍሪካ ምድር የጀርመንን ጦር ጠራርገህ ለማስወጣት ከፈለግህ ጀግኖቹን የሀብሻ ወታደሮችን መልምል:: ሆኖም ደግሞ አበሻ ፈሪ ከሆነም ፍጹም ፈሪና አድር ባይ ነዉ:: ስለዚህ ምልመላችን ለመለዬት ከባድ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል የሚል ነበር::

ልክ እንደ ጣሊያኖቹ ጥናት ሁሉ ኢትዮጵያ ባህል ዉስጥ እዉነተኛ ሰዎች ሁለት አይነት ጽንፈ ላይ የተንጠለጠለ ቦታ አላቸዉ:: አንድኛዉ ማማቸዉ የጀግናና የተወዳጅነት ማማ ሲሆን ሁለተኛዉ ማማ ደግሞ የተጠላ ማማ ነዉ:: ገትጋታ ተብለዉ የመጠላታቸዉ እድልም የዚያኑ ያህል ሰፊ ነዉ::

ለዚህ እንግዲህ ብቸኛዉ መፍትሄ ሁል አቀፍ የሆነ የጋራ አመራር እንዲኖር ማድረግ እንዲሁም የተለያዩ ሀሳቦች የሚያንጸባርቁ ቡድኖችን ማበረታታት ወሳኝ ነዉ:: ማሙሸት አማረ ትልቁ የቤት ስራዉ የሚሆነዉም ይሄዉ ነዉ:: እርግጥ ነዉ ባዋቀረዉ ካቤኔ ዉስጥ አካታች ስራን እንደሰራ ብዙዎች መስክረዉለታል:: በተለያዩ ጎራ ተከፋፍለዉ የነበሩትን ልዩ ልዩ አመራሮች ሁሉ ጥሩ አድርጎ በካቢኔዉ ዉስጥ ማካተቱም ለወደፊት ሰፊ የሀሳብ ምንጭ ያለዉ አመራርን በድርጅቱ ዉስጥ እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንዳሰበ እንዲሁም ሁሉም አካላት በትክክል እንዲታቀፉ መፈለጉን አመላካች ነዉ:: የሆነ ሆኖ ግን ወደፊትም ሰፊ መሰረት ላይ የቆመ ሰፊ ማህበረሰብን የሚያካትት የአመራር ሀይል የመመስረት ጠንካራ ጥረት የሚጠበቅበት ይመስለኛል::

ከዚህ በተጨማሪም ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በትብብር የመስራት እና የላቀ ሀገራዊ የዲሞክራሲ እሴት ላይ መስራት ሌላዉ ትልቁ የቤት ስራዉ የሚሆን ጉዳይ ይሆናል:: በተለይም የኢትዮጵያ ሰዉ እፊት ጀምሮ ፓርቲዎች ወይ ተባበሩ አለዚያ ተሰባበሩ የሚለዉ አቋሙ ወደፊት እየጠነከረ እንደሚመጣ ይጠበቃል:: እናም መኢአድ ለዚህ የህዝብ የልብ ትርታ የሚሰጠዉ ምላሽ የማሙሸት አማረ ያመራር ብቃትን ከሚፈትኑ ጥቂት ጉዳዮች ዉስጥ አንዱ የሚሆን ይመስላል::

ሌሎች ፓርቲዎች ከመኢአድ ተሞክሮ ምን ሊቀስሙ ይገባል?
==============================
መኢአድ ለአራት አመታት በተለያዩ ቡድኖች ተከፋፍሎ የዳከረዉን መዳከር ከቶ እንዳይደገም ደግሞም እንዳይታሰብ ብለዉ ሌሎች ፓርቲዎች ተሞክሮ ሊሆናቸዉ የሚችል አስተምህሮት መርምረዉ ማዉጣት ያለባቸዉ ይመስለኛል:: እኛ ሀገር የፖለቲካ ትንታኔ ማድረግ: ከአንድ ሂደት ምን ተማርን ብሎ መወያዬት : ሀሳብ ለሀሳስብ ለመለዋወጥ መነሳሰት ፈጽሞ ባህላችን አይደለም:: በተለያዩ ፓርቲዎች ጥላ ስር ታቅፈዉ ያሉ ሀይሎች በተለይም አሁን በተለያዩ ብድኖች ተከፋፍለዉ ያሉ ሀይሎች ቁጭ ብለዉ ትንታኔ መስሪያ ግዜአቸዉ ይመስለኛል::

ህጋዊ መፈንቅለ ስልጣን ተደረገ ብሎ አንዱ ወገን ሲጮ አንድኛዉ ወገን አትንጫጫ ብሎ አፍ ለማሲያዝ ከመሄድ የመኢአድ ተሞክሮ ምን ይመስላል ብሎ መጠዬቅና መወያዬት ብልህነት ይመስለኛል:: ጠንካራ ዉይይትና ክርክር ሁሉንም የሀሳብ ልዩነቶች ባይፈታቸዉም ዲሞክራሲያዊ ከፍታ ላይ መዉጣት ግን ያስችላል:: ዲሞክራሲ ከፍታ ላይ የወጣ ሀይል ደግሞ ሀሳቦችን ዲሞክራሲያዊ በሆነ አካሄድ ወደ ጋራ ስምምነት ያመጣቸዋል:: ከመኢአድ መማር የሚቻለዉ ይሄን ነዉ::

በዚህ አጋጣሚ እግዚአብሄር በሰጠን ጥቂት የጽሁፍ ጸጋ ሀሳባችንን የምናካፍል ሁሉ በኢትዮጵያ ያለዉ የፖለቲካ ባህላዊ እሴት ያብብ ዘንድ እያንዳንዱ ወገን ወደ ዲሞክራሲ ከፍታ ይራመድ ዘንድ የምንጽፈዉ ጽሁፍ : የምንሰነዝረዉ ሀሳብ ዋጋ ያገኝ ዘንድ ለሚመለከተዉ ሁሉ እናሳስባን:: ሆኖም ማንንም አንማጸንም::

Image

-በሰሞኑ የሰራዊቱ ግምገማ የወያኔው መከላከያ ሰራዊቱ እንደ ደርግ ሰራዊት ሊበተን ይችላል ተባለ::
-በአዲስ አበባ የለውጥ ሃይሎች በመተባበር የሕዝባዊ እንቢተኝነት ጥሪዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ ናቸው::
-በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል::
Minilik Salsawi

ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ የቀውስ ማእበል ያስከተሉት ሕዝቦቻቸን ለስደት እና ለእስር እንዲሁም ለሞት የዳረጉት የገደሉት የሻእቢያ እና ወያኔ መንግስታት እስከዛሬ ድረስ ተደጋግፈው እዚህ የደረሱ ቢሆንም ከአሁን በኋላ ያላቸው ሃይል እየተሟጠጠ ህዝባዊ እምቢተኝነት እና አመጽ እየተፈጠረባቸው በውስጣቸውም እየተቦጠቦጡ በመፍረክረክ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል::

የሻእቢያ እና ወያኔ ባለስልጣናት በመጭው ጊዜ ማድረግ የሚገባቸውን ጉዳይ እየተገናኙ እንደሚወያዩ እና በመደጋገፍ ቀሪውን ጊዜያት በስልጣን ለመቀጠል የሚያደርጉት ሙከራ የለውጥ ሃይሎች ህዝቡን በማስተማር እያከሸፉባቸው መሆኑ ተሰምቷል::በዚህም መሰረት በአስመራ ሐርነተ አርቢ ወይንም የአርብ ነጻነት የተባለ የለውጥ ንቅናቄ የተጀመረ ሲሆን ከኤርትራውያን ዲያስፖራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ንቅናቄው ትልቅ ዉጤት አምጥቶ በአስመራ ከተማ ኢሳያስን የሚቃወም ወረቀት በብዛት ሲበተን የደህንነት አባላትና ፖሊሶችም ወረቀቶችን ሳይሰበስቡ ጥሪው ሕዝቡ ዘንድ እንዲደርስ መተባበራቸው ታውቋል። እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚገኙ ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትንንሽ ፓርቲዎችን በትብብር በማቀፍ እንዲሁም በተናጠል በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች ታላላቅ ሰልፎችን እና ተቃውሞዎችን በማድረግ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲፈጠር ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ የለውጥ ግብረሃይልም ከባዱን ሚና በመጫወት ትግሉ እንዲፋፋም አስታውጾ እያበረከተ ነው::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህን ሰሞን በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ እየተደረገ ባለ ግምገማ ላይ የመከላከያ ሰራዊቱ የአሸባሪ ሃይሎችን መቆጣጠር ካልቻለ እጣው እንደ ደርግ ሰራዊት መበተን ነው ሲሉ የግምገማው መሪዎች መናገራቸው ታውቋል:: በምድር ጦር መምሪያ ስር ባሉ የሰራዊት ክፍሎች በተደረገ ግምገማ በሁሉም አደራሾች ይህ አይነት የመበታተን አደጋ እንዳለ በይፋ ተገልጿል::የአሸባሪ ሃይሎች የተባሉት በሃገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የዲያስፖራ ጽንፈኞች እንደሆኑ የተገለጸ ሲሆን የዲያስፖራ ጽንፈኞች በሃገር ቤት የሚገኙሃይሎችን በመርዳት አመጽ ሊቀሰቅሱ ሕገመንግስቱን ሊያፈርሱ ምናምን የሚል ዛቻ እና ሃይል የተቀላቀለበት መመሪያ ሲሰጥ የነበረ ሲሆን ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የብሄራቸው ስም እየተጠራ እና እየተለየ ሲተቹ እና ሲገመገሙ እንደነበር ታውቋል::

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይላት ከድርጊታቸው ካልተቆጠቡ የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ-መንግስታት ባለሥልጣን በምህጻሩ ኢጋድ እንደሚቀጣቸው በድጋሚ አስጠነቀቀ። አስፈላጊ ከሆነም ኢጋድ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ጣልቃ ሊገባ እንደሚችል ዝቷል። የደቡብ ሱዳን አማፂያን በበኩላቸው የደቡብ ሱዳን መንግስት ስምምነቱን ጥሶ ውጊያ ከፍቶብናል ሲሉ ከሰዋል።

ሺሻይ አዘናው፣ የቀድሞ የአረና አሁን ደግሞ አንድነት ፓርቲ አባል፣ መቀሌ በሚገኝ ፍርድ ቤት ቀርቦ “ሽብርተኛ ነህ” በሚል ክስል ተመስርትበታል። በሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ማስተርሱን ይማር የነበረው ሺሻይ፣ በትግራይ ድምጻቸዉን ከሚያሰሙ ደፋርና አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኞች መካከል አንዱ ነበር። ኢትዮሜዲያ የሚከተለዉን ዘግቧል፡ http://www.ethiomedia.com/15store/4251.html

ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም መኢአድ እና አንድነት ዉህደት ይፈጽማሉ ተብሎ ተጠብቆ እንደነበረና የሕወሃት ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ አመራር እውቅና አልሰጥም በሚል ዉህደቱን ማጨናገፉ ይታወቃል። ከሁለት አመታት በላይ በአቶ አበባው መሐሪ ከሚመራው መኢአድ ጋር ደብዳቤዎች ሲጻጻፍ የነበረው ምርጫ ቦርድ ፣ አንድም ጊዜ በአመራሩ ላይ ጥያቄ አንስቶ ሳያውቅ፣ ዉህደት ሊደረግ ሲል፣ ሸንካላ ምክንያት በመፍጠር ሆን ብሎ ዉህደቱን ማጨናገፉ፣ ምርጫ ቦርዱ በሕወሃት አመራር ታዞ ያደረገዉ እና ምንም አይነት ገለልተኝነት እንደሌለው ያሳየበት እንደሆነ ብዙዎች ያናግራሉ።

የምርጫ ቦርድን ሕገ ወጥ ጥይቄ ለማሟላት መኢአድ ቅዳሜ ጥቅምት 29 እና እሁድ ጥቅምት 30 ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ የነበረ ሲሆን፣ ጠቅላላ ጉባኤው ባለመስማማት እንደተጠናቀቀ ለማወቅ ችለናል።

አርብ ጥቅምት 28 ቀን፣ የመኢአድ ላእላይ ምክር ቤት ተሰብስቦ የመኢአድ አመራር የነበሩና በተለያዩ ችግር የተገለሉ ፣ አቶ ማሙሸት አማረን ያካተተ ፣ 14 ሰዎችን ጉዳይ፣ ጠቅላላ ጉባኤው በነገታው ዉሳኔ እንዲያሳልፍ ስምምነት የተደረሰ ሲሆን፣ ምንም እንኳን ከአንድንት ጋር ሊደረግ የነበረዉን ዉህደቱ ምርጫ ቦርድ ቢያጨናግፈውም፣ የምርጫ ዘመቻውን ከአንድነት ጋር በተቀናጀ መልኩ ለማድረግ በጠቅላላ ጉባኤው ዉሳኔ ለማስወሰን ታስቦም እንደነበረ ለማወቅ ችለናል።

ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን ጠቅላላ ጉባኤው በአቶ ሃይሉ ሻዉል መሪነት የተከፈተ ሲሆን፣ ከ335 በላይ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ተገኝተዉም ነበር። እነ አቶ ማሙሸት በርካታ ሰዎች በስብሰባው እንዲገኙ ማድረጋቸዉንም ለማረጋገጥ ችለናል።

በስብሰባው ወቅት በአቶ ኃይሉ ሻዉልና በአቶ አበባው መሐሪ መካከል ጠንካራ ልዩነቶችና አለመስማማቶች የነበሩ ሲሆን ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ እንዳልተጠናቀቀም ለማውቅ ችለናል። አቶ አበባው፣ ከሁለቱ በስተቀር የሥራ አስፈጻሚ አባላት በሙሉ ለደህንነታቸው ፈርተናል በሚል ስብሰባዉ ጥለው እንደወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከስብሰባው ከወጡት መካከል የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ ተስፋሁን አለምነህም ይገኙበታል።

ስብሰባው እሁድ ጥቅምት 30 በቀሩት በአብዛኛው እነ አቶ ማሙሸት የሰበሰቧቸው ተወካዮች ባሉበት አቶ ማሙሸት አማረን የመኢአድ ፕሬዘዳንት አድርገው መርጠዋል።

ጠቅላላ ጉባኤው ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን የተደረገ እለት የምርጫ ቦርድ ተወካይ እንዳልነበረም የደረሰን ዘገባ ሲያመለክት፣ የምርጫ ቦርድ ተወካይ በሌለበት፣ አብዛኛው የጠቅላላ ጉባኤ ተወካዮች አልተገኙም በተባለበት የተደረገ ምርጫ ምን ያህል ሕጋዊ ሊሆን እንደሚችል ግልጽ የሆነ ነገር እንደሌለ ከመኢአድ አባላት የሚደርሱ ዘገባዎች ይገልጻሉ።

ከአራት አመታት በላይ ያልታዩት ኢንጂነር ኃይሉ ሻዉል፣ በዚህ መልኩ ስብሰባው በሰላም እንዲጠናቀቅ አለማድረጋቸው እንዳልተደሰቱ የሚገልጹት አንድ ያነጋገርናቸው የመኢአድ አባል ለመኢአድ አሁን ያለበት ደረጃ በዋናነት ተጠያቂው አቶ ኃይሉ ሻወል እንደሆኑ ይናገራሉ።
በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ሊደረግ ታስቦ የነበረ አብሮ የመስራት ዉሳኔ በነበረው አለመስማምምት አልመሳካቱ ጥሩ እንዳልነበረ የተናገሩት እኝሁ የመኢ፤አድ አባል፣ “አብዛኛው የመኢአድ አባል ከአንድነቶች ጋር እየታሰረ፣ እየተደበደበ፣ እየተገደለ ነው። በተግባር የመኢአድ እና የአንድነት አባላት አንድ ናቸው” ሲሉ በአመራሮች ዘንድ አለመስማማቶች ቢፈጠሩም በሜዳ በየዞኑና በየወረዳው ያለው የመኢአድ ታግይ እንኳን እርስ በርሱ እንደ አንድነቶ ካሉ ሌሎች የትግል አጋሮቹ ጋር አንድ ሆነ እየሰራ እንደሆነም ይገልጻሉ።
በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው ከበርካታ ተወካዮች ጋር ስብሰባዉን ለቀው የወጡት አንድ የመኢአድ ከፍተኛ አመራርር አባል፣ በማንም ድርጅት አለመስማማቶች እንደሚፈጠሩ ገልጸው፣ ብሶት ለመናገር ወደ ኢቲቪ እንደማይሮጡ ገልጸዋል።

በአቶ አማረ ማሙሽት የሚመራው መኢአድ ጽ/ቤቱን ተቆጣጥሮ አዲስ ካቢኔም እንዳዋቀረ ለማወቅ ችለናል። በዚሁ መሰረት አዲስ ካቢኔ የሚከተሉት አባላትን አካቷል፡

1: አቶ ማሙሸት አማረ (ፕሬዝዳንት)
2: ዶ/ር ታዲዎስ ቦጋለ (ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት)
3: አቶ እንድርያስ ኤሮ (ምክትል ፕሬዝዳንት)
4: አቶ ተስፋየ መላኩ (ዋና ፅሃፊ)
5: አቶ ሰማሀኝ አብርሃም (የድርጂት ጉዳይ)
6: ኮኔሌር ትርሶት ጉልላት(የህዝብ ግንኙነት)
ገ: ወ/ሮ አለማየሁ ሞገድ (የሴቶች ጉዳይ)
8: አቶ አብርሀም ጌጡ (የውጭ ጉዳይ)
9: አቶ ሀብተማርያም ያንተ(ፋይናንስና አስተዳድር)
10: አቶ ታጠቅ አሰፋ (የወጣቶች ጉዳይ)
11:አቶ ሀይለየሱስ ሚናስ (የምርጫ ጉዳይ)
13:አቶ ተስፋሁን አለምነህ (ትምህርትና ስልጠና አላፊ)
14 : መ/አ አየለ አለ(የህግና ዲስፕሊን አላፊ)
15: አቶ ወርቁ ከበደ (የምሃል ቀጠና ሃላፊ)
16: አቶ አዳነ ጥላሁን(የሰሜን ቀጠና ሃላፊ)
17: አቶ ብሩ ደሲሳ( የምራብ ቀጠና ሃላፊ)
18: አቶ ገለቱ ደጀርሳ (የደቡብ ቀጠና ሃላፊ)
19: አቶ ተፈራ መንግስቴ (የምስራቅ ቀጠና ሃላፊ)\

ጄ/ል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ለመውጣት ሲሉ ከቦሌ አየር ማረፊያ በደህንነቶች እንዳይወጡ መደረጋቸውን ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል። ከመከላከያ የጦር አዛዥነታቸው በጄ/ል ሳሞራ የኑስ እንዲነሱ የተደረጉት ጄ/ል አበባው ከአገር እንዳይወጡ የተደረገበት ምክንያት ግልፅ እንዳልሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ የተለያዩ ጥያቄዎች እንዳሉ በመግለፅ ለኢታማጆር ሹሙ ጄ/ል ሳሞራ ከረር ያለ ሪፖርት ያቀረቡት ጄ/ል ሰዓረ፣ ጄ/ል ሞላና ጄ/ል […]

በሰሞኑ የሰራዊቱ ግምገማ የወያኔው መከላከያ ሰራዊቱ እንደ ደርግ ሰራዊት ሊበተን ይችላል ተባለ:: -በአዲስ አበባ የለውጥ ሃይሎች በመተባበር የሕዝባዊ እንቢተኝነት ጥሪዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ ናቸው:: -በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል:: ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ የቀውስ ማእበል ያስከተሉት ሕዝቦቻቸን ለስደት እና ለእስር እንዲሁም ለሞት […]

ፍኖት ታትማ ወጥታለች ኢቲቪ (ወይም አዲሱ ስማችውው ኢቢሢ)፣ የኢትዮጵያ ሬድዮ፣ አዲስ ዘመን ጋዜጣ በመንግስት ገንዘብ የሚተዳደሩ የመገናኛ ብዙሃን ናቸው። የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 29 ንኡስ አንቀጽ 5 “በመንግስት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም በመንግስት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማስተናግገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል።” እንደሚለው የተለያዩ አስትያየቶችን ፣ በአገሪቷም ያሉ በሕግ የተመዘገቡ ሲቪክና የፖለቲካ ድርጅቶችን ከኢሕአዴግ […]

ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም መኢአድ እና አንድነት ዉህደት ይፈጽማሉ ተብሎ ተጠብቆ እንደነበረና የሕወሃት ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ አመራር እውቅና አልሰጥም በሚል ዉህደቱን ማጨናገፉ ይታወቃል። ከሁለት አመታት በላይ በአቶ አበባው መሐሪ ከሚመራው መኢአድ ጋር ደብዳቤዎች ሲጻጻፍ የነበረው ምርጫ ቦርድ ፣ አንድም ጊዜ በአመራሩ ላይ ጥያቄ አንስቶ ሳያውቅ፣ ዉህደት ሊደረግ ሲል፣ ሸንካላ ምክንያት በመፍጠር ሆን ብሎ ዉህደቱን ማጨናገፉ፣ […]

ኢትዮጵያና ጀርመን ዘመናት የተሻገረ የሁለትዮሽ ግንኙነት በመካከላቸዉ የመሠረቱ ሃገራት መሆናቸዉ በመረጃዎች የተመዘገበ ነዉ። ሁለቱ ሃገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ዉል ከተፈራረሙም 105 ዓመታት ተቆጥረዋል።


 ከታሳሪ ዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች
 
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስታችንን ያክብሩ!
ሠላም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!? እንዴት ነዎት? ያስታውሱ ከሆነ የዛሬ ሁለት ዓመት አካባቢ ከፊሉ የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች ‘ግልፅ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ’ በሚል ርዕስ:
“ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እባክዎትን የተለያዩ የመንግስት አካላት የሕገ መንግስታችንን ድንጋጌዎች እየጣሱ ነውና እርስዎም በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 74/13/ መሠረት ሕገ መንስቱን የማስከበርና የማክበር ግዴታ ስላለብዎት ሕገ መንግስቱን ያክብሩ” በማለት አንዲት አጭር ደብዳቤ ፅፈንልዎት ነበር፡፡
ድንገት በተለያዩ ምክንያቶች የጻፍንልዎትን ደብዳቤ ካላነበቡት ወይም ማስታወስ ካልቻሉ ዛሬ ይሄን ማስታወሻ ስለምንፅፍልዎት ግለሰቦች አንድ ሌላ ማስታወሻ እንስጥዎ፡ ከ6ወራት በፊት /በሚያዚያ 2006 ዓ.ም/ ሶስት  ጋዜጠኞችንና ስድስት ጦማሪያንን ‘ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ በመሞከር ወንጀል ጠርጥሬያችኋለሁ’ በማለት መንግስትዎ ልማታዊ ርምጃ (አብዮታዊ ርምጃ እንደሚባለው) ወስዶ ነበር፡፡
እኛም የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች የዚህ ‘ልማታዊ ርምጃ’ ሰለባ የሆንን ግለሰቦች ነን፡፡ በርግጥ ከሁለት ዓመታት በፊት ‘ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሕገ መንግስቱን’ ያስከብሩልን በማለት ጥያቄ ያቀረብንልዎት ግለሰቦች ‘ከ6ወራት በፊት ሕገ መንግስቱን ለመናድ  ሞክራችኋል’ በማለት መንግስትዎ ሲያስረን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር ጠይቀን ሕገ መንግስቱን ለመናድ በመሞከር ወንጀል ተጠርጥረን ስንታሰር እስሩ በጣም ግራ አጋብቶን ነበር፡፡ በዚህ ያልቆመው መንግስትዎ ክሱን ‘ሕብረተሰቡንና ሀገሪቱን ለማሸበር አቅዳችኋል ሞክራችኋል አሲራችኋል…’ በማለት ወደ ‘ሽብርተኝነት’ ያሳደገው ሲሆን እርስዎም ከዚህ ጋር በተያያዘ ሃሳብዎትን ሲሰጡ ስለተመለከትንዎ ትንሽ ቅሬታ ይዘን መጣን፡፡
በቅድሚያ አሁን ያለንበትን ሁኔታ በትንሹ ብናስረዳዎት ቅሬታችንን ለመረዳት ያስችልዎታልና አንዳንድ ጉዳዮችን እንንገርዎት፡፡
ይሄን ማስታወሻ በምንፅፍልዎት ወቅት ከታሰርን ከ 200 ቀናት የተቆጠሩ ሲሆን፣ነገር ግን ጉዳያችን ገና በቅድመ ክስ (Pre Trial) የክርክር ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ይሄ የሆነበት ዋነኛ ምክንያትም መንግስትዎ እንኳን ለእኛ ለተከሳሾች ለከሳሽ አካልም ግልፅ ያልሆነ ክስ በማቅረቡ ነው፡፡ ይሄንንም ስንል ልትፈፅሙት ነበር የተባለው ‘የሽብርተኝነት ድርጊት’ ሳይጠቀስ ‘በቃ የሽብርተኝነት ድርጊት ልትፈፅሙ ነበር’ በማለት በጨበጣ ስለመጣብን ነው፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እንግዲህ የብዙ ድብደባ፣ ዛቻ እና ስድብ ሰለባዎች ከሆንን በኋላም የቀረበው ይሄ  ክስ ነው ከ6 ወራት በኋላም ተከሳሾች ከሳሾቻችንም ሳንረዳው በየቀጠሮው እየታሸ ነው የሚገኘው፡፡ ‘የተፋጠነ ፍትህ’ ሕገ መንግስትዊ መብት ነውና የተፋጠነ ፍትህ ይሰጠን፣ እርስዎም ይሄን ሕገ መንግስታዊ መብት ያክብሩ እያልንዎት አይደለም ‘ሕገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ሕገ መንግስቱ ይከበር በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ’ በማለት ‘ጥፋት የሚያሳምን’ ( አንዱ የዚህ ደብዳቤ ጸሃፌ ጦማሪ ጥፋት ብሎ አንዲፈርም የተገደደው ህገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ህገመንግስቱ ይከበር ማለቴ ጥፋት ነው ብሎ መሆኑ መንግስትዎን መልክ ግልጽ አድርጎ ያሳያል) መንግስት አለዎትና ይህ ጥያቄ አንደሚበዛብዎት እናውቃለን፡፡
ይልቁንም ቀላልና ግልፅ ቅሬታን ነው ይዘን የመጣነው፡፡ ይሄውም የኢፌድሪ ሕገ መንግስት በአንቀፅ 20/3/ ላይ
‘የተከሠሡ ሰዎች[…]  በፍርድ ሂደት ባሉበት ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደ ጥፋተኛ ያለመቆጠር […]መብት አላቸው::’
በማለት የደነገገ ሲሆን፣ ይሄንን ሕገ መንግስታዊ መብትም ማንኛውም የመንግስት አካል እንዲሁም ግለሰብ የማክበር ግዴታ አለበት፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር እርስዎና መንግስትዎም በተደጋጋሚ ‘ሕገ መንግስቱ ሳይሸራረፍ እናስከብራለን’ ይላሉና ይሄን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ የምታውቁት ይመስለናል፡፡ ነገር ግን ከታሰርን ወዲህ ስለእኛ የእስር ጉዳይ በተጠየቁባቸው ጊዜያት ይሄን ሕገ መንግስታዊ ድንጋጌ በመጣስ ‘ፍርድዎትን’ በተደጋጋሚ ሲሰጡ ታዝበናል፡፡ እናስረዳዎ፡- ሐምሌ 12/2006 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣሚ መግለጫ ላይ ስለእኛ እስር ጉዳይ ለቀረበልዎት ጥያቄ ሲመልሱ፡-
‘ከአስመራ እስከ ሞቃዲሾ የተዘረጋው የሽብር ሰንሰለት ውስጥ አንዴ ከገቡ በኋላ ብሎገር ነኝ፣ ጋዜጠኛ ነኝ ማለት ዋጋ የለውም’
በማለት ብዙ ነገሮችን ተናገሩ፡፡ ይሔውልዎት ስህተትዎ፡-
  1.   የክሳችን ዋነኛ ጭብጥ በሃገር ውስጥ ‘የሽብርተኛ ድርጅት በማቋቋም ‘የሽብርተኝነት’ ተግባራትን ለመፈጸም አሲረዋል፡ አቅደዋል… የሚል እንጂ፣ እርስዎም እንደሚሉት ‘ሰንሰለት’ ምናምን አይደለም፣ 
  2.      እሺ አሸባሪዎችም ይበሉን፣ ነገር ግን ሕገ መንግስቱ እንደሚደነግገው በፍርድ ቤት ‘ጥፋተኝነታችን’ እስሚረጋገጥ ቢጠብቁስ ምናለበት? ይህ የሚያመለክተው እርስዎም እነደማእከላዊ መርማሪዎች ነፃ ሆኖ የመገመት (presumption of innocence) መብታችንን እያከበሩልን እንዳይደለ ነው፡፡
ይሄ ነገር የሆነው በድንገት ሊሆን ይችላል ብለን ዝም ብንልም እርስዎ ግን በድጋሚ ጥቅምት 6/2007 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ከምክር ቤቱ አባል ለቀረበልዎ ጥያቄ ሲመልሱ፡-
“የብሎገር ጭምብል አጥልቆና በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ ተሸሽጎ ከተከሳሽነት ማምለጥ አይቻልም፡፡ ሽብርተኝነትን መዋጋታችን ይቀጥላል…” እያሉ እርስዎ ያሉትን የብሎገር ጭምብል አውልቀውና ተሸሸጉበት ያሉትን የጋዜጠኝነት ሙያ መሸሸጊያ አፍርሰው ባንዴ ‘የአሸባሪነት’ ካባ ደረቡልን፡፡
ክቡር ጥቅላይ ሚኒስቴር፣ እያልን ያለነው የአንድ ሰው ‘አሸባሪነት/ወንጀለኝነት’ የሚረጋገጠው በፍርድ ቤት እንደሆነ ሕገ መንግስቱ ደንግጎ እያለ፣ እርስዎ ግን ነፃ ሆኖ የመገመት መብታችን ወደ ጎን ብለው እንደ ከሳሽም እንደ ፈራጅም በመሆን ‘አሸባሪዎች’… እያሉን ይገኛሉ ነው፡፡
ምናልባት ‘ስራ አስፈጻሚው ከሳሽ ነውና እኔም የስራ አስፈጻሚው አካል መሪ ስለሆንኩ የፈለኩትን አስተያየት የመስጠት መብት አለኝ’ ብለው ከሆነ፣ ሕገ መንግስቱን የማክበር ጉዳይ ‘ርስዎን ጨምሮ ሁሉም ዜጎች ላይ የተጣለ ግዴታ ነው፡፡ እርስዎ ‘L’e’tat, c’est moi’ ይሉት አይነት የራስ ግምት ውስጥዎ ከሌለ በስተቀር እንዲህ በግልፅ እየጠየቅንዎት ‘ሕገ መንግስትቱን  አላከብርም’ በማለት ገና ዋነኛ ክርክሩ እንኳን ያልተጀመረ ክስን (ዋነኛ ክርክር ካለው) መሠረት በማድረግ ከዚህ በኋላ እኛን ‘አሸባሪዎች’ አይሉንም ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ይህን ተመሳሳይ ምላሽ “በእርግጠኝነት አሸባሪ ናቸው” በሚል ቃና ለቢቢሲ ለኢንቢሲ ለመሳሰሉት አለም አቀፍ ሚዲያ  ተቋማትም መስጠትዎን ሰምተናል፡፡
ሌላው ልናስታውስዎ የምንፈልገው ጉዳይ እንደኛ አይነት የተራገበ( በሰፊው በታወቀ የአደባባይ) የፍርድ ጉዳይ ([un] popular case) ላይ የመንግስት አካላት አስተያየት (say) ያለውን ተፅእኖ እንዲያስቡት ነው፡፡ እርስዎ በምክር ቤት ቀርበው የአሸባሪነት ፍርድ ከበየኑብን (አሁን እያደረጉት እንዳሉት) ፍርድ ቤትም ሆነ ሌሎች የመንግስትዎ አካላት ምን ሊያስቡ እንደሚችሉ አስተውለውታልን?!
ይሄን ሁሉ ስንልዎ እንዲያው ሕጉን ያክብሩልን ለማለት ያክል ነው እንጅ፣ ከሽብርተኝነት ጋር የሚያገናኘን ቅንጣት ያክል እውነት /A segment of fact/ እንደሌለና የሰው ልጆች መልካምና ደስተኛ ሕይወት እንዲኖራቸው ከመመኘትና ለአገራችን ያገባናል ከማለት ያለፈ ሕይወትም ፍላጎትም እንደሌለን እኛም እናውቀዋለን እርስዎና መንግስትዎም ያውቁታል፡፡ ነገር ግን ካለፉት ስድስት ወራት አንስቶ ጨዋታውን በግድ ካልተጫወታችሁ ተብለናልና እየተጫወትን ነው፡፡ የአሁኑ ጥያቄያችን ግን በጣም ቀላል ነው፣ ጨዋታው ገና በደንብ እንኳን ሳይጀመር ውጤቱን እይወስኑት ነው፡፡
እርስዎ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት የስልጣን ደረጃ በወጡ ሰሞን አብዛኞች የዚህ ማስታወሻ ፀሃፊዎች መጠነኛ ለውጥና ማሻሻዎች ያደርጋሉ የሚል ተስፋ ሰንቀን “The First 100 Days” ወዘተ እያልን ብዙ ጠብቀንዎት ነበር፡፡ ከሁለት ዓመት በሚበልጥ ግዜ እንደተመለከትንዎ ግን ተስፋችን ፍሬ ሊያፈራልን አልቻለም፡፡ አሁንም አዲስ ተስፋ ሰንቀን ግን ፡- “ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር እባክዎትን ሕገ መንግስቱን ያክብሩ! የእኛንም መብት ያክብሩልን” እንላለን፡፡
‘’የብሎገር ካልሲ አድርጎ፣ የጋዜጠኝነት ጫማ ተጫምቶ የሽብረተኝነት ሰንሰለት ውስጥ ከገቡ በኋላ ሕገ መንግስቱን ያክብሩልኝ ማለት ዋጋ የለውም!’’ በማለት ተስፋችን ዋጋ እንደማያሳጡት ተስፋ አለን፡፡
ከአክብሮት ጋር
  ጦማርያን                    ጋዜጠኞች
 ዘላለም ክብረት                  ኤዶም ካሳዬ 
 ናትናኤል ፈለቀ                  ተስፋለው ወ/የስ
 በፍቃዱ ሃይሉ                   አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ
 አጥናፍ ብርሃኔ                       
 አቤል ዋበላ
 ማህሌት ፋንታሁን
 

የዞን ፱ ጦማርያንና የጋዜጠኞችን የ200 ቀናት እስር አስመልክቶ በማኅሌት ሰለሞን የተዘጋጀ

                                     
                       


                                     
                       

Image
Eritrean refugees in North Ethiopia

በአውሮፓና በአሜሪካ፣ በአፍሪካና መካከለኛው ምሥራቅ፣ በሩቅ ምስራቅና በአውስትራልያ ሳይቀር እያደር
ኤርትራና ስደት ተወራራሽ ቃላት (synonymous) እየሆኑ መጥተዋል። እገሌ/ እገሊት እኮ ኤርትራዊ
ነው/ነች ሲባል ስደተኛ ነው/ነች እንዴ? – ብሎ መጠየቅ የተለመደ አነጋገር ሆኗል። እዚህ አገር ስደተኞች
በዝተዋል ሲባል ሱማሌና ኤርትራውያን በዝተዋል የሚል – ድምዳሜ ላይ ይደረሳል። ኢትዮጵያውኖችም
በዝተዋል ሊባል ትንሽ ቀርቷል።
በቅርብ ዘመናት የነበሩት የኢትዮጵያ ነገስታት ከአውሮጵውያኖች ዘመናዊ መሳርያና ጥቅማጥቅሞችን
ይፈልጉ ነበርና ከባህረ ነጋሹ መሬት (ቦገስ፣ሠሃጢን) ቆንጠር እያደረጉ ለባእዳኑ ኃይላት እንደ መወዳጃነት
ይሰጡ ነበር። የስዊዝ ቦይ ሲከፈት ታድያ የቀይ ባህር ቀጠናነቱ እየጎላ በመሄዱ የአውሮጳ ቅኝ ገዝዎችን
ቀልብ እየሳበ መጣ። በመሆኑም እንግሊዝ ግብጽን – ነጭ አባይን ራሷ መቆጣጠር ፈልጋ ለጥቁር አባይ
ቃፊር በመፈለጓ ይህንኑ ኃላፊነት ኢጣልያ ላይ ወረወረች። ኢጣልያ ይህንኑ ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ
ስትቅበዘበዝ የአድዋው ጦርነት ተከስቶ የውርደት ሸማ ተከናነበች። ይሁንና ግን በወቅቱ በነበረው
አስቸጋሪ ነባራዊ ሁኔታ ኢጣልያ ከመረብ ወድያ ያለውን የኢትዮጵያ መሬት በቁጥጥሯ ሥር አደረገች።
በመሆኑም ባህረ ነጋሽን – ኤርትራ የሚል መጠርያ ሰጥተዋት ከእናት ሀገርዋ ነጠሏት።
ኤርትራውያን ከስድሣ ዓመታት በላይ በእጣልያ አገዛዝ በነበሩበት ወቅት የኢጣልያን ስልጣኔ እጅግ
ቀስመዋል። በእጃቸው ከመብላት ይልቅ ሹካና ማንኪያን መጠቀምን ለምደዋል። የቤት ቁሳቁሶችን
አጠቃቀምና በንጽህና አያያዝን ያውቁበታል። አለባበሳቸው ይማርካል። አነጋገራቸውና ዘበናይነታቸው ደስ
ያሰኛል። ጓደኝነታቸው በወረት አይደለም፣ በችግርም ይሁን በደስታ ጊዜ ከወደዱት አይለዩም።
ኤርትራውያን በክልልላቸው ጉዳይ ላይ ድብቅ ቢሆኑም እንኳን በተለያዩ ቁምነገሮች ላይ ለወዳጆቻቸው
ግልጽ ናቸው። ብዙውን ጊዜ ከሸጋዋ ኤርትራዊ ቆንጆ ጋር የተፈጸመ ትዳር እንደ አበባ የፈካ ነው።
ከትዳር አክባሪዋ ኤርትራዊ ጋር የሚመሰረት ጋብቻ ጽናትን ይወልዳል።
ኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን “ኤርትራን” እንደማትታየዋ “ሠማያዊዋ ሀገራቸው” ሲያመልኳት
ሌሎቹን የአለም አሕጉራት ደግሞ እንደ “ምድራዊ ሀገራቸው” ይቆጥራሉ። ብዙዎች ኤርትራን በሩቅ ሆነው
እንደ መካና መዲና ያከብሯታል፣ ይጨፍሩላታል፣ የጀግኖች ሀገር እያሉ ያወድሷታል እንጂ ጎጇቸውን
ከእሷ ዘንድ መቀለሱን አይመርጡም። በእድሚአቸው የገፉት እንኳን ሳይቀሩ ሀገራቸውን ትተው በውጭ
ሀገር መኖር አይከብዳቸውም። መሰደዱ አላንገሸገሻቸውም። ይህን አስመልክቶ አቶ መለስ
“ኤርትራውያን እግር እንጂ ሀገር የላቸው” – አሉ እየተባለ ይቀለዳል።
ኤርትራውያን አስመራን ንጹሂቷ ትንሿ ሮማ ይሏታል። ሥዕሏ እንደ መላዓከ ሚካኤል ሥዕል ከቢታቸው
ግድግዳ ተለጥፋለች። ነግደው ያተረፉባትን – ተምረው የከበሩባትን አዲስ አበባ ግን ቆሻሻ ይበዛባታል ሲሉ
ያንቋሽሿታል። አፋቤትን፣ ምጽዋን፣ ከረንን፣ ደቀመሀሪን ያንቆላጵሷቸዋል – ረብጣ ነዋይ የዛቁባቸውን
ድሬዳዋን፣ ናዝሬትን፣ አዋሳንና ጅማን አያስታውሷቸውም።
የኤርትራና ስደት መወደጃጀት እክልላቸው መኖር ካለመፈለግ ምክንያት የመነጨ ይመስላል። ስደት
ይቀናቸዋል – ያሳምራቸዋልም። ስለ መሪያቸው አቶ ኢሳይያስ አንዳች ክፉ ነገር ለመናገር የማይፈልጉት
እነዚሁ ኤርትራውያን ይልቁንም በሳቸው ፈላጭ ቆራጭ ባላባታዊ አገዛዝ ምክንያት የመሰደዱ በር ዳግም
ክፍት ስለሆነላቸው በውስጣቸው ያከብሯቸዋል። አቶ ኢሳያስም ቢሆን በበረኸኝነት እልሃቸው ፈረንጆቹን
መናቃቸውና ፊት መንሳታቸው በሌላ በኩል ለኤርትራውያኑ የምዕራቡ ሀገር የመግቢያ ቪዛ መገኛ ስልት
ሆነ።
የኤርትራ የነጻነት ትግል – “ሕዝቡን ነጻ የማውጣት ትግል” – ወይንስ – “መሬቱን ነጻ አውጥቶ ለአቶ
ኢሳይያስ መሸለም”? – የሚለው ጥያቄ አዲስ የማህበራዊ ሳይንስ ንድፈ ሃሳብን ፈንጥቋል። ብዙ ሰዎች
ምትክ የሌላት ሕይወታቸውን ሰውተውላቸው፣ በመድፍና በታንክ እየተታኮሱላቸው የትልቅ ጋሻ መሬት
ብቸኛ ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ – ባለርስቱ ፕሬሲደንት ኢሳያስ በጣት ከሚቆጠሩት የዓለም ሰዎች
አንዱ ናቸው። ግናስ ሕዝቡ አካባቢውን እንደ ኒውክለር ራድየሽን ብክለት እየፈራ የሚፈረጥጠው ለምን
ይሆን? ይህም ጥያቄ አዲስ የማህበራዊ ሳይንስ ምርምርን መፈንጠቁ አልቀረም።
በቅርቡ ሃያ አንድ ዓመት የነጻነታቸውን በዓል ያከበሩት ኤርትራውያን ታሪክ በቅጡ የመዘገበው የግማሽ
ምዕት ዓመት የጦርነትና የስደት ታሪክ አላቸው። ከሃያ አንድ ዓመት በፊት የተጎናጸፉት ነጻነት በየሀገሩ
በስደት የወጡትን ዜጎች ሊመልስ አልቻለም። ይህ ከናቅፋ የተተኮሰው የፋኖ መራዒው የነጻነት ጥይት –
“የመንፈሱን ነጻነት” – ማምጣት አልቻለም። ይልቁንም ከነጻነቱ ማግስት ጀምሮ የሚሰደደውን ሕዝብ
ብዛት ባለፈው ሰላሳ ዓመት ከተሰደደው በመብለጥ ኤርትራውያን ከሶማሌያ ቀጥሎ ምዕራቡን ዓለም
ኢትዮጵያን ጨምሮ እንዲያጨናንቁ አድርጓል። ከባለእርስቱ አቶ ኢሳይያስ ጋር የውስኪ ብርጭቆ
የሚያነሱት የግል አውሮፕላን ነጂዎቻቸው ሳይቀሩ በቅርቡ አውሮፕላኑን ሰርቀው ወደ ሳውዲ
መኮብላላቸው ራሱ አቶ ኢሳይያስ ወዳጅ አልባ መሆናቸውን ያስመሰክራል።
ኤርትራውያኖችን የስደቱ ሰለባ ያደረገው የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ አስመልክቶ ንድፈሀሳባዊ ግንዛቤን
ለማግኘት የማርክስንና ኤንግልስን ሥራዎች በጥሞናና ስነምግባራዊ በሆነ መንገድ መረዳትን ይጠይቃል።
በተጨማሪም የራሽያ የጥቅምቱ አብዮት ክስተትንና ተያይዞ የመጣውን የብሔር ጥያቄ ጽንሶችን በጽሞና
መመርመርም ከውዥንብር ያድናል። በእርግጥ የብሔር ብሔረሰብ ጥያቄ አቀንቃኞች ማርክስና ኤንግልስክ
ብቻ ሳይሆኑ ቦልሸቪኮች፣ ሮዛ ሉክሰምበርግና ካርል ካውትስኪም ተጠቃሾች ናቸው።
ማርክስ እ/ኤ/አ በ 1848 ዓ/ም ወደ ተሻለ ማህበራዊ ብልጽግና ደረጃ የሚያሸጋግሩት የምርት ኃይሎች
እድገት (productive forces) ወሳኝ እንደሆኑ አትቶ ይኸው ሂደት በተለያዩ የብሔር ጥያቄዎች ላይ
እንኳን ቢሆን ተጽዕኖ እንደሚያሳርፍ ገልጿል። በመሆኑም በሰራተኛው መደብ (working class) ትግል
ውስጥ የብሔር ጥያቄ የሞተ ነው ሲል ማርክስ ጨምሮ አብራርቷል። የሰራተኛው ትግል መደቦችንና
(classes) ብሔሮችን (nationalities) ስለሚያጠፋ የብሔሮች ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ቦታ
አያገኝም ብሎ ነበር። የማርክስ ዋነኛ መፈክር የዓለም ሠራተኞች ሁሉ ተባበሩ ነበር። (workers of all
countries unite)
ማርክስና ኤንግልስክ ከ እ/ኤ/አ 1850 በፊት ስለ ብሔር ጥያቄ በቂ ንድፈሃሳቦችን ያልቀረጹ ቢሆንም ቅሉ
እ/ኤ/አ – በ 1863 በተከሰተው የፖላንድ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ብሔራዊ ጥያቄ ላይ
አስተሳሰባቸውን በመለወጥ አየርላንድ ከእንግሊዝ ተገንጥላ ራሷን ማስተዳደር ትችላለች የሚል ጠበቅ
ያላለ፣ ብዥታዊ መደምደምያ ላይ ሊደርሱ ቻሉ። ሌኒንም በተመሳሳይ በሠራተኛው መደብ ልዕልና ላይ
በማተኮር የአርመንያኑ ሶሻል ደሞክራሲ የመገንጠልን ጥያቄ በሠራተኛው መደብ ነጻ መውጣት ይፈታል
ቢልም ቅሉ ሀሳቡን በመለወጥ የተጨቆነ ብሒረ እስከ መገንጠል ሊያደርስ የሚችል መብት አለው ሲል
ድንብርብር ያለ ጽሁፍ ሞነጫጭሯል። በሌላ በኩል ደግሞ ስታሊን – ሌኒንን መሠረት በማድረግ አንድ
ሕዝብ ተመሳሳይ ቋንቋ ከተናገር፣ ባንድ አካባቢ ሳይነጣጠሉ የሚኖሩ ከሆኑ፣ አካባቢአቸው ድንበር
ሊበጅለት የሚችል ከሆነ፣ ሕዝቡ በቂ የምጣኔ ኃብት ክምችት ካለው፣ ተመሳሳይ ስነልቦናዊ አመለካከት
እንዲሁም ተመሳሳይ ባህላዊ ትስስር ካለው ብሔር ሊባል የሚያስችለውን መስፈርት ስለሚያሟላ
የመገንጠል ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል የሚል መደምደምያ ሰጠ። ሆኖም ግን ስታሊን ከነዚህ ስድስቱ
መስፈሮቶች አንድ እንኳን ለተጓደለ ብሔር ስለማይባል መገንጠል እንደማይቻል አስጠንቅቋል።
ይህ ከላይ የተመለከትነው የፈረንጆቹ አኳኋን፣ ፖለቲካ፣ ፍልስፍና፣ ርዕዮተ ዓለም፣ ብዥታ፣ አመለካከትና
ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ ትምህርት ወደ ኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ ዘልቆ በመግባት –
“የብሔረሰቦች ስታሊናዊ ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል” – በሚል አጉል ሀሳብ ተቀሽሮ ቀረበ።
ሻዕቢያ ከዚህ ንድፈሃሳብ በመነሳት – “አረብ ነኝ” – የሚለውን ጀብሃ ካስወገደ በኋዋላ በመገንጠሉ ጥያቄ
ጸንቶ ሲያበቃ ኦነግን በራሱ አምሳያ በመፍጠር መከረኛይቱን ኢትዮጵያ በእርስ በእርስ ጦርነት አናውጦ
ሲያበቃ ተገነጠለ።
ሻዕቢያ አስቀድሞም ቢሆን ኤርትራን ለመገንጠል ያመቸው ዘንድ በንጉሡ ዘመን የተሰነዘሩትን
የኢትዮጵያን ጭቁን ሕዝብ ጥያቄዎች በራሳቸው ስውር ዓላማ ሥር ሸሽገው ላይ ላዩን ኢትዮጵያዊ
ተቆርቋሪዎች መስለው በደጋፊዎቻቸው በመታገዝ በጥንቃቄ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል። ከቀዝቃዛው ጦርነት
ማክተም በኋላ የማርክሲዝም ሌኒኒዝም ሃሳቦች በሚካኤል ጎርባቾቭ ፔሪስትሮይካና ግላስኖስት ተሀድሶ
አዲስ መልክ ቢይዝም ቅሉ ሻዕቢያ፣ ሕወሀትና ኦነግ በመገንጠሉ ርዕዮት ላይ ጽናታቸውን አሳዩ።
ሻዕቢያ በገሀድ፣ ሕወሀት በዘዴ ኦነግ በተቀጽላነት። እንዴት?
የኃይለሥላሴ ንጉሳዊ መንግስት በድንገት መገርሰሱ “ለማርኪሲዝም ሌኒኒዝም” ርዕዮተ ዓለም መስፋፋት
ጥርጊያ መንገድ እንዳዘጋጀ ሁሉ፣ የደርግ በራሱ የውስጡ ቅራኔ ምክንያት መፈረካከሱ ደግሞ
ለብሔረሰቦቹ “የራስን በራስ መወሰን እስከመገንጠል” ዓላማ ተግባራዊነት እጅግ ምቹ ሆነ። ድንገት
ሳይታሰብ የሚኒልክ ቤተ መንግስቱን የተቆጣጠሩት በሕወሀቱ ውስጥ የነበሩት ታጋዮች – “የታላቋ ትግራይ”
– ምስረታን መርሀ ግብር ለጊዜው ወደ ጎን ቢተዉም ቅሉ በወቅቱ ለተከሰተው ድንገተኛና አስቸጋሪ ነባራዊ
ሁኔታ ተጋለጡ። ኢሕአዲጎቹ አባቱ ሻዕቢያን ተከትሎ ኦሮምያን ለማስገንጠል ያሰፈሰፈውን ኦነግ
ለማዘናጋት እንዲሁም አዲስ አበባ ድረስ አብሯቸው የመጣውን የጦር አጋራቸውን ሻዕቢያ ላለማስቀየም
መላ በመዘየድ የብሔረሰቦች ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል የሚለውን የማርክሲዝም ሌኒኒዝም
ጽንሰሃሳብ አንቀጽ 39 በህገመንግስቱ ውስጥ ለማካተት ተገደዱ። ቀስ በቀስ ግን ኢሕአዲግ የኦነግን
ሠራዊት ከቦ ከማረከና መሪዎቹን ከምክር ቤቱ ሲያስወግድ ” አንቀጽ 39″ ለይስሙላ የተቀመጠች አንቀጽ
መሆኗ ገሀድ ወጣ። የሕወሃቶቹ ትግራይዋዎቹ፣ ከተወሰኑ ዓመታት ቆይታ በኋላ፣ ኤርትራውያን ቀድሞ
ያካበቱት ሃብት ንብረታቸው ተቀምቶ ባዷቸውን እንዲባረሩ ሲያደርጉ መገንጠል ፋይዳ ቢስ የእልኸኞች
ፖለቲካ መሆኑን በማሳየት ከመቶ ሃምሳ ዓመት በፊት ማርክስና ኤንግልስን ውዥንብር ውስጥ ከቶ
የነበረውን የብሄረሰቦች እስከመገንጠል ጥያቄን ውጤት አልባነትን በተግባር በማሳየት ለሲሪላንካ ታሚል
ተገንጣዮች አዲስ ትምሕርት አስገኙ። ኢሕአዲግ በሌላ በኩል ደግሞ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ
ግንባርን (ኦብነግ) በመፋለም ላይ ሲገኝ የመገንጠሉ ጥያቄ ከስታሊን ጋር አብሮ ለመቀበሩ ገለጻ ለማድረግ
ናይሮቢ ውስጥ ስብሰባ ጠርተዋቸዋል።
በመሆኑም ከስታሊናዊው – “የብሔር ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመንገንጠል” – ጽንስ የተወለደችዋ
ኤርትራ ውርዴ ስትሆን አንቀጽ 39 የእንግዴው ልጅ ነው። በዚህም በዚያም ሰበብ ግን ገናናዋና ጥንታዊዋ
ኢትዮጵያ ወደብ አልባ ሀገር እንድትሆን ክፉ ደባ ተሸረበባት።
የመገንጠሉ ሰለባ የሆነው የኤርትራ ሀገር ሕዝብ እንደ ግለሰብ እጅግ መልካሞች ናቸው። ከሚወዷት
እናት ሀገራቸው የነጠላቸው ዘመናዊው የፈረንጆቹ ፖለቲካ ነው። ይኸው የትዕቢትና የማናህሎኝነት
ማኦኢስት ፖለቲካዊ አስተሳሰብ በተማሪዎች ንቅናቄ ዘመን ከነበሩት ተማሪዎችና የዛሬው መሪዎች
አዕምሮ ውስጥ ፈጽሞ እስካልተነቀለ ድረስ ሕዝቡ በራሱ ፈቃድ መኖር አይችልም። ፖለቲካ በማስተዋል
ካልታገዘ መከራን ይወልዳል። ፖለቲካ በጥበብ፣ በትዕግስት፣ በሥነምግባርና በጨዋነት ካልተመራ ሕዝብን
ያሸብራል። ከንቱ እልህና ጀብደኝነት ደሀውን ያሰቃያል። በምስኪኑ ሕዝብ ስቃይ የሚደሰቱ ደግሞ የኋላ
ኋላ የመከራውን ጽዋ ይጨልጡታል። የእቴጌ ጣይቱ ፍርሀት እውን ሆኖ ኢትዮጵያ ራሷ ዘመናዊ
ትምህርት ያስጨበጠቻቸው ልጆችዋ ተረከዛቸውን አነሱባት። በእርግጥ እግዚአብሔር ታሪክ ሠሪ ነው።
ኢትዮጵያን እየጠበቀ ዘመን ከዘመን አሻግሯታል። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ፈጽሞ አይተዋትም።
የሻዕቢያው ባለሥልጣናትና በርከት ያሉ ኤርትራውያን ደጋፊዎቻቸው ኤርትራ ከእናት ሀገርዋ ኢትዮጵያ
መሬት ጋር ዳግም እንድትዋሀድ አይፈልጉም። ኤርትራን የጀግንነት ምሳሌአቸው፣ የስልጣኔ ምንጫቸውና
የቀይ ባህር በራቸው አድርገው ይቆጥሯታል። ማንም እንዲነካባቸው አይፈልጉም። የሕወሀቶቹ
ኤርትራውያኖቹም ቢሆን ባለርስቱ ፕሬዚደንት ኢሳይያስን ማስቀየም አይፈልጉም። ከዚህ ቀደም ሥልጣን
ላይ በነበሩት የሕወሀቱ ትግራዋዮች የተፈጸመውን ኤርትራን የኢትዮጵያ ኤኮኖምያዊ ድጋፍ ያሳጣውን
ርምጃ ለመካስ በሚቻለው ይሞክራሉ። ላንዳንዶቹ ንግዳቸውንና ቤታቸውን እየመለሱላቸው ነው።
አንዳንዶቹም የተጀጋጀውን ቅጽ እየሞሉ ኢትዮጵያው ውስጥ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ፈቅደውላቸዋል።
“ጠርጥር ከገንፎም አይጠፋ ስንጥር” – ያሉ ደግሞ ነገ ምን እንደሚፈጠር ስለማይታወቅ መጠንቀቁ
ይበጃል በሚል አርፈው እተሰደዱበት ሀገር ሆነው አድፍጠዋል።
የሻዕቢያውም ሆነ የሕወሀቱ ቀን የሰጣቸው ኤርትራውያኖች በክፉም በደጉም ጊዜ አብረውት የኖሩትን
የየዋሁን ኢትዮጵያ ሕዝብ ስነልቦናዊ አመለካከት ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ማናከሱን፣ ማከፋፈሉንና
ማጠላለፉን እንደ በቀል ዱላ ይጠቀሙበታል። የግፍ ሥራዎችንም የሥልጣን ዘመናቸው ማራዘምያ
ምትሀት አድርገው ሊጠቀሙበት ይሞክራሉ። “የቤት ሥራ” – የሚሏቸውን እነዚህኑ የርኩስ መንፈስ
ሕዋሳት በየፖለቲካ ማህበሮች፣ ትምህርት ቤቶች፤ ሕዝባዊ ስብስቦችና በየመዝናኛ ቦታዎቹ ሳይቀር እንደ
አንደ አንደ መተት እያሰሩ የዋሁን ኢትዮጵያዊ ያደነዝዛሉ። ታድያ ይህን እያወቁ አንዳንድ ተቃዋሚዎች
ከሻዕቢያ ጋር የመሞዳሞዳቸው ጥፋት – “የፖለቲካ ቂልነት” ወይም “የፖለቲካ ንዝህላልነት” – ተብሎ ብቻ
ሊታለፍ የሚችል አይደለም። ማን ይሙት ማን ሻዕቢያ የወያኔን መውደቅ ይሻል? ወያኔም ቢሆን ልብን
በፕሮፖጋንዳ እያደረቀ እግዚአብሄር በቃ እስከሚለው ቀን ድረስ ያሾፋል እንጂ ከኤርትራ ጫፍ እንኳንስ
ጦር ሣር እንደማይመዘዝ ያውቃል።
እግዚአብሄር በቃ ሲል ኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን በበጎና በንጹህ ፍላጎት ወደ እናት ሀገራቸው
ጉያ ይመጣሉ። ተንኮል – ተንኮልን መውለዱን ያቆማል። መሠሪነት፣ ሸርና ደባ ወደ ጥልቁ ይወረወራሉ።
ጊዜው ይቅረብም ይራቅም እግዚአብሔር ይህንንም መስራት አይሳነውም።
ኢትዮጵያ ስትበደል እግዚአብሔር ዝም አይልም። ሰላምና ብልጽግና – ፍቅርና አንድነት ለመላው ሕዝብ
ይሁን።
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች። አሜን
ከሀበሻ አበበ (ኖርዌ)

እ ጎ አ ከነሐሴ ወር 1961 ዓ ም አንስቶ በርሊንን ከ ሁለት በመክፈል 28 ዓመታት የዘለቀው 15 ኪሎሜትር ርዝማኔ የነበረው የግንብ አጥር የፈረሰበት 25ኛ ዓመት ዛሬ በደመቀ ሥነ ሥርዓት ሲከበር ውሏል። ከበርሊን ውጭ ፤ በአጠቃላይ 155 ኪሎሜትር

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ኢትዮጵያና ጀርመን ዘመናት የተሻገረ የሁለትዮሽ ግንኙነት በመካከላቸዉ የመሠረቱ ሃገራት መሆናቸዉ በመረጃዎች የተመዘገበ ነዉ። ሁለቱ ሃገራት ይፋዊ የዲፕሎማሲ ዉል ከተፈራረሙም 105 ዓመታት ተቆጥተዋል።

ከአርአያ ተስፋማሪያም ጄ/ል አበባው ታደሰ ወደ ውጭ ለመውጣት ሲሉ ከቦሌ አየር ማረፊያ በደህንነቶች እንዳይወጡ መደረጋቸውን ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል። ከመከላከያ የጦር አዛዥነታቸው በጄ/ል ሳሞራ የኑስ እንዲነሱ የተደረጉት ጄ/ል አበባው ከአገር እንዳይወጡ የተደረገበት ምክንያት ግልፅ እንዳልሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ …

ጄ/ል አበባው ታደሰና ፍጥጫው Read more »

”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” ለሚለው ለአቶ አንተነህ መርዕድ ጽሁፍ መልስ፣ ቁ. 1 ዛሬ ኦክቶበር 8/2014 ምሳ ሰዓት ላይ አንድ ጓደኛዬ ደውሎ ”ፕሮፌሰር መስፍንን ለቀቅ” የሚለውን ጽሁፍ አንብቤው እንደሆን ጠየቀኝ። ይህ ሰው በፕሮፌሰር መስፍን ማንነት ላይ ይቅርታ ጠይቄው ስለነበር ”ቢጤህ የጻፈውን እየው” ለማልት ማሾፉ ነበር። ለፕሮፌሰር መስፍን ከወጣትነት በተለይም የትግራይ ብሄረተኞች ስልጣን ላይ ሊመጡ አጥቢያ ጀምሮ በየአደባባዩ […]

በገዥው ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ክንፍ የደ.ህ.ዴ.ን ፖለቲካ ፖርቲ አባላት ወዳጆቸ ባደረጉልኝ ግብዣ መሰረት በደ.ህ.ዴ.ንን 22ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ተገኝቸ ነበር ። እንደ ዛሬው የደ.ህ.ዴ.ን በዓል ፍሪዳ ተጥሎ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ድርጅቶች የልደት በዓላቸውን ሲያከብሩ እግር ጥሎኝ ስገኝ በምባረርበት የጅዳ ቆንስል ግቢ በሚገኘው የኮሚኒቲ አዳራሽ ተገኝቸም ኬክ እስኪቆረስና ሙዚቃው እስኪጀመር ያለውን ፕሮግራም ተከታትያለሁ። በልደት ፕሮግራሙ በቀረበው የድርጅቱ የትግልጉዞ “የስምጥ […]

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡