ኤፈርት – የሙስና መርከብ – አገርን ለማጥፋት የተቋቋመ ተቋም

“ኤፈርት-መር ካፒታሊዝም” ብዙዎችን እያደኸየ ጥቂት የወያኔ ጎጠኞ ገዢዎችን ግን በሃብት
እያንበሻበሸ በመገስገስ ላይ ነው። ለመሆኑ ኤፈርት ምንድነው? የማነው?
ኤፈርት /በትግርኛው ምህፃር “ትእምት” ወያኔ በረሃ እያለ ባንኮችን፣ የመንግሥት መኪናዎችን እና የግለሰቦችን ንብረት
በመዝረፍ ያቋቋመው ህገ-ወጥ የዘራፊዎች ድርጅት ነው፡፡ ወያኔ የሚኒሊክ ቤተመንግስትን ከተቆጣጠረ ወዲህም
ኤፈርት ራሱን በአስራ ሶስት ግዙፍ ኩባንያዎች አደራጅቶ በሁሉም አቅጣጫ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመቦጥቦጥ የወያኔ
ሹማምንትን ኪስ እንዲያደልብ አደራ የተጣለበት ተቋም ነው።
በዚህም መሠረት መሶበ የኮንስትራክሽን ግብዓት ማምረቻ፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ አዲስ የመድሃኒት
ማምረቻ፣ ኢዛና የማዕድን ልማት፣ ጉና የንግድ ድርጅት፣ ሕይወት የግብርና ሜካናይዜሽን፣ ሳባ እብነ በረድ ማምረቻ፣
ሼባ የቆርቆሮ ፋብሪካ፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ አልሜዳ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ፣ ኤክስፕረስ የትራንዚት አገልግሎት፣
ኢትዮጵያን እንወቅ አስጎብኚ ድርጅት እና ትራንስ ኢትዮጵያ የጭነት ማመላለሻ አገልግሎት የተሰኙ ግዛዙፍ
ኩባንያዎችን አቋቁሞ እንደ ተባይ ድሆች ኢትዮጵያንን የሚመጥ “ካፒታሊዝም” ኢትዮጵያ ውስጥ ለማንሰራፋት
ተንቀሳቀሰ። ከጥቂት ዓመታት ሥራ በኋላ የቁጥጥር አድማሱን በማስፋት ብሩህ ተስፋ ፕላስቲክ ፋብሪካ፣ ማይጨው
ፓርቲክል ቦርድ ፋብሪካ፣ ዲማ የማር ማጣሪያ፣ አላጌ ደንና የደን ውጤቶች፣ ናሽናል ጂኦ-ቴክስታይል እና አበርደሌ
የእንስሳት ማድለቢያና ኢክስፖርት ድርጅት የተባሉ ስድስት ኩባንያዎች የያዘው ደጀና ኢንዳውመንት ተጨመረለት።
ይህ በአደባባይ የሚታወቀው ኤፈርት ነው። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በቅርበት የሚከታተሉ እንደሚያውቁት ሁሉ ኤፈርት
በኮንትሮባንድ ንግድ ጭምር የገባ “ወንበዴ ድርጅት” ነው። ኤፈርት ያሻውን ያህል ተበድሮ ያለመክፈል ልዩ ፈቃድ
ያለው ቅምጥል ድርጅት ነው፡፡ እስካሁን ከሶስት ቢሊዮን በላይ የባንክ እዳ እንደተሰረዘለት ይወራል፡፡ የህወሓት
ማዕከላዊ ኮሚቴ በተሰበሰ ቁጥር ከማይቀሩ አጀንዳች አንዱ ትዕምት (ኤፈርት) ነው። ለኤፈርት የቦርድ አባላትንም ሥራ
አስኪያጆችንም የሚሾምለት ህወሓት ነው። የአገሪቱ የፓርቲዎች ህግ ፓርቲዎች እንዳይነግዱ ይከለክላል። ህጉ ሕወሓት
ላይ አይሠራም። እርግጥ ኤፈርት ዘራፊ እንጂ ነጋዴ ስላልሆነ አዋጁ አይመለከተውም።
የኤፈርት ኢትዮጵያን የመዝረፍ ሕልም ትልቅ ነው። “በግል” ባንኮችም የአንበሳ ድርሻ አክሲዮን በመያዝ የፋይናንስ
ሴክተሩን ሊቆጣጠረው ደርሷል። በአገሪቱ ያሉ ያሉ ዋና ዋና የቢዝነስ ኮንትራቶችን የሚወስደው ኤፈርት ነው። ለሕዳሴ
ግድብ ግንባታም ዋና እቃ አቅራቢ ነው። የአገሪቱን 40 በመቶ የፒቪሲ (ፕላስቲክ ነክ ምርቶች) ገበያ ለመቆጣጠር
የሚያስችለውን ማምረቻ እየገነባ ነው። ኤፈርት የድሀውን ገንዘብ እየሰበሰ ለወያኔ ጄኔራሎችና ሹማምንት የሚያድል
አገርን ለማጥፋት የተቋቋመ ተቋም ነው። “የሙስና መርከብ” የኤፈርት የቤት ስሙ የሆነው ያለምክንያት አይደለም።