ሚኒሊክ ሳልሳዊ – በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል

በሰሞኑ የሰራዊቱ ግምገማ የወያኔው መከላከያ ሰራዊቱ እንደ ደርግ ሰራዊት ሊበተን ይችላል ተባለ::
-በአዲስ አበባ የለውጥ ሃይሎች በመተባበር የሕዝባዊ እንቢተኝነት ጥሪዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ ናቸው::
-በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል::

ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ የቀውስ ማእበል ያስከተሉት ሕዝቦቻቸን ለስደት እና ለእስር እንዲሁም ለሞት የዳረጉት የገደሉት የሻእቢያ እና ወያኔ መንግስታት እስከዛሬ ድረስ ተደጋግፈው እዚህ የደረሱ ቢሆንም ከአሁን በኋላ ያላቸው ሃይል እየተሟጠጠ ህዝባዊ እምቢተኝነት እና አመጽ እየተፈጠረባቸው በውስጣቸውም እየተቦጠቦጡ በመፍረክረክ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል::

የሻእቢያ እና ወያኔ ባለስልጣናት በመጭው ጊዜ ማድረግ የሚገባቸውን ጉዳይ እየተገናኙ እንደሚወያዩ እና በመደጋገፍ ቀሪውን ጊዜያት በስልጣን ለመቀጠል የሚያደርጉት ሙከራ የለውጥ ሃይሎች ህዝቡን በማስተማር እያከሸፉባቸው መሆኑ ተሰምቷል::በዚህም መሰረት በአስመራ ሐርነተ አርቢ ወይንም የአርብ ነጻነት የተባለ የለውጥ ንቅናቄ የተጀመረ ሲሆን ከኤርትራውያን ዲያስፖራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ንቅናቄው ትልቅ ዉጤት አምጥቶ በአስመራ ከተማ ኢሳያስን የሚቃወም ወረቀት በብዛት ሲበተን የደህንነት አባላትና ፖሊሶችም ወረቀቶችን ሳይሰበስቡ ጥሪው ሕዝቡ ዘንድ እንዲደርስ መተባበራቸው ታውቋል። እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚገኙ ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትንንሽ ፓርቲዎችን በትብብር በማቀፍ እንዲሁም በተናጠል በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች ታላላቅ ሰልፎችን እና ተቃውሞዎችን በማድረግ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲፈጠር ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ የለውጥ ግብረሃይልም ከባዱን ሚና በመጫወት ትግሉ እንዲፋፋም አስታውጾ እያበረከተ ነው::