በአሁኑ ወቅት በአገራችን በከተሞችና በገጠሮች እየታዩ ያሉ ምልክቶችን በጥንቃቄ የመረመረ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መታዘቡ አይቀርም።

በአንድ በኩል፣ ወያኔ የተወገደባት፣ ፍትህ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየት ተስፋችን እየለመለመ ነው። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም ዓመታት በሕዝብ ላይ ሰፍኖ የነበረው የፍርሀት ደመና እየገለጠ በመሆኑ ተዘግተው የቆዩ አንደበቶች መናገርና “ይኸ ሁሉ ግፍ ለምን?” ብለው መጠየቅ ጀምረዋል። ይህንን መነቃቃት በአስተሳሰብም፣ በተግባርም፣ በኪነጥበብም እያየነው ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጥ በአገራችን ሊመጣ እንደሚችል ከማመን አልፎ ራሳቸውን በለውጥ አምጭ ኃይልነት መመልከት ጀምረዋል። በርካታ ወጣቶች ወያኔን በትጥቅ ለመገዳደር የወሰኑ ወገኖቻችንን እየተቀላቀሉ በዚህም ምክንያት ጉልበታቸውን እያፈረጠሙ ነው። የለውጡ እርሾ ከሲቪሉ አልፎ በመከላከያ ሠራዊቱ እና በኢሕአዴግ ድርጅቶች ውስጥም እየተብሰለሰለ ነው። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፣ ህወሓት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የሚጠቀምበት ኃይል መሆኑ እያበቃ በአንፃሩ የትግሉ አጋር የሚሆንባቸው ሁኔታዎች እየታዩ ነው። በሁሉም የሠራዊቱ ክፍሎች ጉምጉምታው ወደ ጩኸት እየተቀየረ በመሆኑ ሠራዊቱ በአለቆቹ ላይ የሚነሳበት ጊዜ እሩቅ አይደለም። በተለያዩ ምክንያቶች ህወሓትን ወይም ህወሓት የፈጠራቸውን ድርጅቶች የተጠጉ በአጠቃላይ ኢሕአዴግ በሚባለው ስብስብ ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንም “ለመሆኑ ማንን ነው እያገለገልን ያለነው?” ብለው በመጠየቅ ላይ ናቸው። በዚህም ምክንያት ወያኔ ውስጡ እየተረበሸ ነው። ከኢትዮጵያም ውጭ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ ዘንድ ያለው ቁጣና ዝግጁነት ከወትሮው እጅግ የላቀ ነው። በአጭሩ፣ በሁሉም አቅጣጫ፣ ደረጃ በደረጃ የሕዝባዊ እምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች ተጀምረዋል።

በአንፃሩ ደግሞ፣ የጨለማ ንጉሥ የሆነው ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብን ወደ ፍርሀት ቆፈን ለመመለስ እስሩን ከመቸውም በላይ ያጧጧፈበት ጊዜ ነው። በትግራይ፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በአፋር በሶማሊ … በመላው ኢትዮጵያ ብሩህ ራዕይ የሰነቁ ወጣቶችና አዛውንት ታድነው እየታሰሩ ናቸው። የወያኔ እስር ቤቶች በአርቆ አስተዋይ ዜጎቻችን ተሞልተዋል። ወትሮም ከፍተኛ የነበረው ስደት ብሶበታል፤ ለእውነት በጽናት የቆሙ ጋዜጠኞች ወይ ታስረው፣ አልያም ተሰደው አልቀዋል። የወያኔ የግዴታ ስልጠና አገሩን እያመሰው ነው። የኢትዮጵያዊያን ኑሮ በእጦቶች የታጀበ ሆኗል። የነፃነት እጦት፣ የፍትህ እጦት፣ የመብራት እጦት፣ የስኳር እጦት፣ የዘይት እጦት፣ የታክሲ እጦት፣ የመኖሪያ ቤት እጦት፣ እጦት፣ …. እጦት።

እነዚህ ሁለት ተፃራሪ እውነታዎች ሁለት ተፃራሪ ኃይሎች ለወሳኝ ፍልሚያ ፊት ለፊት መፋጠጣቸዉን በግልጽ ያሳያሉ። ዛሬ አገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃነትና ባርነት፣ ፍትህና ጭቆና፣ ደስታና ሀዘን፣ ተስፋና ተስፋ መቁረጥ፣ ብልጽግናና ድህነት፣ እውቀትና ድንቁርና፣ ብርሃንና ጨለማ፣ ለወሳኝ ግጥሚያ ተፋጠዋል። ይህ ፍጥጫ የኢትዮጵያን የወደፊት እጣ ፈንታን በመወሰን ረገድ አቢይ ሚና የሚኖረው ወሳኙ ግጥሚያ – ሕዝባዊ እምቢተኝነት – መጀመሩን አብሳሪ ነው። የነፃነት፣ የፍትህ፣ የተስፋ፣ የብልጽግና፣ የእውቀትና የብርሃን ወገኖች ነን የምንል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ይህንን ፍልሚያ በድል መወጣት ግዴታችን ነው።

ወያኔ ታጋዮችን ቢያስር ትግሉን አያስርም። በእጦት ኑሮዓችን በማመሰቃቀል በድህነት ሊያንበረክከን ቢሻም፣ በፍጹም አንበረከክለትም። በተዘረፈ የድሆች ድካም ህንፃዎችን ቢገነቡም የራስ ባልሆነ ጌጥ አንኮራም። የወያኔ የሆነ የኛ አይደለም፤ የእነሱ መክበር የኛ መክበር አይደለም። ወያኔ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ገዢና ተገዢ፤ በዳይና ተበዳይ፣ ገፊና ተገፊ ናቸው።

ተበዳይና ተገፊ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በዘረኞች፣ ሙሰኞችና ከፋፋዮች የህወሓት ባለሥልጣኖቻቸውና ሎሌዎቻቸው ላይ ይነሳሉ። የተጀመረው ሕዝባዊ እምቢተኝነት አመቺ በሆኑ መንገዶች ሁሉ ይጧጧፋል።

የወያኔ ትዕዛዛትን መሻር፤ በሥራ ላይ መለገም፤ ግብር አለመክፈል፤ አድማ መምታት፤ የወያኔ ካድሬዎችን ማግለልና ማዋረድ፤ የነፃነት ኃይሎችን መደገፍ፤ የፓሊስና የጦር ሠራዊት አባላትን ማቅረብ እና በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ እነሱም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ማበረታታት፤ ህሊና ያላቸው የኢሕአዴግ አባላት የሕዝቡን ትግል እንዲያግዙ ማበረታታት … – እነዚህንና እነዚህን የመሳሰሉ በርካታ የትግል ስልቶች ከአሁን ጀምሮ በተከታታይ በሥራ ላይ መዋል ይኖርባቸዋል። የወያኔን የጭቆና ምሽግ ከውስጥ መሸርሸር፤ ከውጭ መደርመስ ይኖርበታል። የመሸርሸርና የመደርመስ ሥራዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ ማድረግ ይገባል። ጊዜው የእምቢተኝነት ነው።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የዲሞክራሲና የነፃነት ንቅናቄ የኢትዮጵያ ሕዝብ አጠገቡ ባሉት መሪዎቹ አስተባባሪነት በአንድነት እንዲነሳ ጥሪ ያቀርባል፤ በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚደረገው ሁለገብ ትግል በጽናት እንዲደግፉ ያሳስባል። ይህንን ትግል በድል መወጣት ግዴታችን ነው፤ እንወጣዋለንም!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Hailu Gebreyohannes Gemoraw ደራሲ፣ ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) “… እንደ ኪሩብ ሁሉ – ክንፍ አካል ቢኖረኝ፣
መች እጠበስ ነበር – በዚህ ዓለም በቃኝ፣
ስላጣሁ ብቻ ነው – መሸሻ መድረሻ፣
በዚች በሽት ዓለም – የኖርኩ እንደውሻ …፣”
“… በሥጋዬ ብቻ ውጪ – ሀገር እስካለሁ፣
እወቁልኝ በርግጥ – አልኖርኩም ሞቻለሁ! …
ኃይሉ (ገሞራው)
Ethiopia Zare (ረቡዕ ኅዳር 3 ቀን 2007 ዓ.ም. November 12, 2014):- በኢትዮጵያ የሥነ-ጽሑፍ ታዋቂ የነበረው ደራሲ፣ ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ባለፈው እሁድ ጥቅምት 30 ቀን 2007 ዓ.ም. (ኖቨምበር 9፣ 2014) በስደት በሚኖርባት ስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በ79 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ተለየ። ሥርዓተ ቀብሩ በስዊድን እንደሚፈፀም ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢወጋን – በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ መልእከቶችን ለህዝብ እይታ አብቅቷል። ‪#‎VIDEO https://www.youtube.com/watch?v=F2jq9pNgmzg የአትዮጵያ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (ኢወጋን)አባላት በአዲስ አበባ ዋና ዋና የህዝብ መገናኛ ቦታዎች እና የአውቶብስ መጠበቂያ የገበያ ቦታዎች ላይ የወያኔን ስርአት የሚያወግዙ እና ስርአቱን ለማውረድ ህዝቡ በጋራ እንዲነሳ የሚያደርጉ ጥሪዎችን ያነገኡ መፈክሮችን በመለጠፍ እንዲሁም ለፖሊስ እና ጦር ሰራዊቱ የሚገባውን የአንድነት እና […]

ትናንት ማክሰኞ በመላው ዩናይትድ ስቴይትስ የአርበኞች ቀን Veteran’s Day ተከብሯል። የመጀመሪያው ዓለም ጦርነት ያበቃበት 100ኛ ዓመት ከዚህ በዓል ጋር ኩታ በመግጠሙ፤ ፈንጠዝያውና የማስታዎሻ ስነስርዓቱን በእጅጉ አድምቆታል። ትናንት ማምሻውን ታዋቂ አሜሪካዊያን ሙዚቀኞች በዋሽንግተን ዲሲ ታላቅ የሙዚቃ ዝግጅት አቅርበዋል። በዚህ ትእይንት የዩናይትድ ስቴይትስ ጦርን ያገለገሉ ወንዶችና ሴቶች ከነቤተሰቦቻቸው ተገኝተዋል። ዘገባው የArash Arabasadi – ሔኖክ ሰማእግዜር ያቀርበዋል።

ሱማልያ ውስጥ እንደገና የተፈጠረው የፖለቲካ ውጥረት የሃገሪቱን የወደፊት ጉዞ ሊገታ ወይም አሁን ከደረሰችበት የመረጋጋት ጎዳና ሊያፈናቅላት እንደሚችል ተሰግቷል።

ፊሌ ተብላ የተሰየመች ንብረትነቷ የአውሮፓ የጠፈር ኤጀንሲ የሆነ መንኩራኩር ሕዋ ውስጥ ከምትገኝ አንዲት ቀደም ብላ ከተላከች የአውሮፓ ኅብረት ማምጠቂያ መደብ ተወንጭፋ በልማድ “ጅራታም ኮከብ” እየተባሉ ከሚጠሩ የተፈጥሮ የሰማይ አካላት ወይም ኮሜቶች በአንዷ ላይ አረፈች፡፡

ዩናይትድ ስቴትስና ቻይና ወደ ከባቢ አየር የሚለቅቋቸውን በካይና ሙቀት አማቂ ጋዞችን መጠን ለመቀነስ ያስችላል የተባለ አዲስ ዕቅድ ይፋ አደረጉ፡፡

ባለፈዉ ዕሁድ በስደት በሚኖርበት ስዊድን ሐገር ያረፈዉ የኢትዮጵያዊው ባለቅኔ የኃይሉ ገብረዮሐንስ‬ (ገሞራው) የቀብር ሥነ-ሥርዓት ሰሞኑን እንደሚፈጸም ወዳጆቹ አስታወቁ።ኃይሉ በኢትዮጵያ ዘመናይ ሥነ-ፅሁፍ ሥመ ጥር ከነበሩ ደራሲዎች አንዱ ነበር።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 11 በለሚ አካባቢ የምትገኘው ማሪያም ቤተከርስቲያን በህገወጥ መንገድ ተሰርታለች በሚል ፖሊሶች ለማፍረስ ሲሄዱ ህዝቡ ባሰማው ተቃውሞ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ ታውቋል። ድርጊቱን የተቃወሙ ምእመናን “ቤተክርስቲያኑዋን ማፍረስ አትችሉም” ማለት ሲጀምሩ ፖሊሶች መደብደብ የጀመሩ ሲሆን፣ ህዝቡም በአጸፋው በፖሊሶችና በወረዳው አስተዳዳሪ ላይ ድንጋይ በመወርወር የተወሰኑ ፖሊሶችን አቁስሏል። የወረዳው …

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ትምህርት ሚኒስቴር ” የከፍተኛ ትምህርት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጃት ማንዋል፣ ለምርጫ 2007 የተሻሻለ” በሚል ርእስ ያዘጋጀውና ለኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣኖች የቀረበው ሰነድ እንደሚለው በአገሪቱ ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዚዳንቶች ውጤታቸው የሚሞላላቸው በምርጫው ለኢህአዴግ በሚያዘጋጁት የተማሪዎች የድጋፍ ሃይል መጠን ነው። ሰነዱ የትምህርት ልማት ሰራዊትን በዩኒቨርስቲዎች ለማስፋፋት የተደረገው ስራ …

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስአበባ ከተማ በርካታ አካባቢዎች የ24 ሰዓታት የውሃ አቅርቦት ማግኘት ካለመቻሉ ጋር ተያይዞ ነዋሪዎች ሥራቸውን በመተው ውሃ ለማግኘት ከሰፈር ሰፈር እንዲንከራተቱና ለተጨማሪ ወጪ እየተዳረጉ መሆኑን ዘጋቢያችን ተዘዋውሮ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በአዲስአበባ በየትኛውም አካባቢ የመጠጥ ውሃ ችግር ተባብሶ መቀጠሉን የጠቆሙት  ነዋሪዎች አስተዳደሩ በየጊዜው ተስፋ ከመስጠት ባለፈ በተጨባች …

ኀዳር ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ግሎባል ፋይንሻል ኢንተግሪቲ ባወጣው ዘገባ በዚህ ሳምንት የቡድን 20 አገራት በአውስትራሊያ በሚያደርጉት ስብሰባ በህገወጥ መንገድ ገንዘብ በሚያዘዋውሩ ኩባንያዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል። ተቀማጭነቱ አሜሪካ የሆነው ድርጅት በዋጣው ዘገባ፣ ኩባንያዎች ሽያጮቻቸውን፣ ታክሶቻቸውን፣ ትርፋቸውና ኪሳራቻውን ግልጽ እንዲያደርጉ መመሪያ ሊወጣላቸው ይገባል ብሎአል። ታዳጊ አገሮች በእነዚህ ኩባንያዎች የተነሳ በእየአመቱ 1 ትርሊዮን …

በሙያ የአፈርና ቋጥኝ እንዲሁም የእሳተ- ገሞራ ተማራማሪ ነው– «ጂዎፊዚስት»፤ ጠፈርተኛ ፣ አሌክሳንደር ጌርስት! ካለፈው ዓመት ግንቦት 20 ቀን 2006 ዓ ም አንስቶ ግን፣ እስካለፈው እሁድ፣ ከምድር አናት ላይ ሆኖ ፣ ማለት 418ኪሎሜትር ከፍ ብሎ ነበረ ምርምሩን ሲያካሂድ የቆየው።

የአውሮፓ ፍርድ ቤት ትናንት ሉክስምቡርግ ላይ ባስቻለው ችሎት የጀርመን መንግሥት ፣ ኤልሳቤት ዳኖቭ ለምትባለው ሩሜኔያዊት የስራ አጥ ድጎማ መከልከሉ አግባብነት ያለውና በሕግም የተመሠረተ ነው ሲል ውሳኔ አሳለፈ።

በደቡብ ኢትዮጵያ በጌዴዖ አካባቢ የይርጋ ጨፌ ወረዳ ኑዋሪዎች የሆኑ ወደ 400 የሚጠጉ አባዎራዎች፤ ከመሬታችን የመፈናቀል ብርቱ ሥጋት አድሮብናል አሉ። አርሶ አደሮቹ፤ ለጠ/ሚንስትር ጽ/ቤት ባቀረቡት የአቤቱታ ማመልከቻና ለ DW በሰጡት መግለጫ፣

ባለፉት ዓመታት ዮርዳኖስ ከአካባቢዉ ሃገራት ወደ ሃገርዋ የሚገቡትን በርካታ ስደተኞች ስትቀበል ቆይታለች። ወደ ዮርዳኖስ የሚገቡት ስደተኞች በመጀመርያ ከፍልስጤም ከዝያ ከኢራቅ ነበር አሁን ደግሞ ከሶርያ በርካታ ስደተኞች በመፍለስ ላይ ናቸዉ። ይህች በንጉሳዊ አስተዳደር የምትመራ ትንሽ ሀገር የስደተኛ ጉዳይ ከባድ ፈተና ሆኖባታል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለሚያደርገው የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብር የአደባባይ ስብሰባ የተላከውን ደብዳቤ ተቀበለ፡፡ የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በአንድ ወር ውስጥ ከሚያደርጋቸው መርሃ ግብሮች መካከል እሁድ ህዳር 72007 ዓ.ም አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ሜዳ ወይንም ቤልኤር ሜዳ ላይ የሚደረገውን የመጀመሪያውን የአደባባይ ስብሰባ ሰማያዊ ፓርቲ እንዲያስተባብር ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን የማሳወቂያ ክፍሉ ደብዳቤውን በዛሬው ዕለት ተቀብሏል፡፡
ትብብሩ እሁድ ህዳር 7 የሚያደርገው የአደባባይ ስብሰባ ፍትሃዊ ምርጫ ስለሚደረግበት ሁኔታ አባላቱንና ደጋፊዎቹን የሚያስተምርበት መሆኑን ለአስተዳደሩ ያስገባው ደብዳቤ ላይ ጠቅሷል፡፡ በስብሰባውም ከ3000 በላይ ህዝብ እንደሚገኝ የስብሰባው አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡
የአደባባይ ስብሰባው አስተባባሪዎች ከአሁን ቀደም በተደጋጋሚ ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ ያቀኑ ቢሆንም የክፍሉ ሰራተኞች በተደጋጋሚ ‹‹የሉም›› እየተባሉ ሳያገኟቸው ይመለሱ እንደነበር ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ትብብሩ በአንድ ወር ውስጥ የሚያደርጋቸውን ሌሎች መርሃ ግብሮች ሰማያዊና ሌሎቹም ፓርቲዎች በየተራ እንደሚያስተባብሯቸው ይጠበቃል፡፡

Image
የፌደራል አቃቢ ህግ በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በጦማርያኑና በጋዜጠኞቹ ላይ የመሰረተውን የሽብር ክስ እንዲያሻሽል የልደታ ከፍተኛ ችሎት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

ፍርድ ቤቱ ዛሬ ህዳር 3/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት ቀደም ብሎ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን በመስጠት በንባብ አሰምቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በክስ መቃወሚያው ላይ የቀረቡትን ዝርዝር ነጥቦች መርምሮ በተወሰኑ ነጥቦች ላይ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ትዕዛዝ ሲሰጥ፣ በሁለተኛነት ቀርቦ የነበረው የክስ ይዘት በአንደኛው የክስ ይዘት ላይ መጠቃለል ስለሚችል ሁለተኛውን የክስ ይዘት ፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡

በክስ ዝርዝሩ ላይ ተከሳሾቹ ‹‹ለአመጽ ማነሳሳትና መምራት›› የሚያስችል ስልጠና ወስደዋል በሚል በተጠቀሰው ላይ ስልጠናው መቼ፣ በማን እና በምን ጉዳዮች ላይ ተሰጠ የሚለው ግልጽ ስላልሆነ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም ተከሳሾቹ አመጽ ለመምራት የስራ ክፍፍል አድርገዋል በሚል የተጠቀሰባቸው የክሱ ይዘት ‹‹ምን አይነት የስራ ክፍፍል፣ ማን ምን እንዲሰራ ክፍፍሉ ተደረገ›› የሚለውን ስለማያመለክት ይህንንም መሻሻል እንዳለበት ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡

በተጨማሪም በክሱ ዝርዝር ላይ ‹‹ቡድን›› እና ‹‹ድርጅት›› በሚል (ግንቦት 7፣ ኦነግ ወይስ ሌላ የሚለውን ስለማይገልጽ) በደፈናው የቀረቡት ነጥቦች ላይ በዝርዝር መቀመጥ ስላለባቸው አቃቢ ህግ ማሻሻያ እንዲያደርግ ታዝዟል፡፡

በሌላ በኩል የተከሳሽ ጠበቆች ‹‹በኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን መረጃ በመስጠት›› በሚል ተከሳሾች ላይ የቀረበው የክስ ይዘት ሆን ተብሎ ወደ ሌላ አካል (ግንቦት 7) ጋር ለማገናኘት ነው በሚል ያቀረቡትን መቃወሚያ፣ ‹‹በኢሳትና በግንቦት 7 መካከል ያለው ግንኙነት ወደፊት በማስረጃ የሚታይ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎታል፡፡

ከተከሳሽ ጠበቆች መካከል የሆኑት አቶ አምሃ መኮንን ከችሎቱ በኋላ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ጠበቆች ላይ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ ጊዜ ወስዶ መርምሮ ውሳኔ እንዳሳለፈ ጠቅሰዋል፡፡ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ላይ ጥያቄ የተነሳላቸው አቶ አምሃ የውሳኔው ዝርዝር በጽሑፍ ገና እንዳልደረሳቸው ጠቅሰው፣ ‹‹አቃቢ ህግ በታዘዘው መሰረት ክሱን የማያሻሽል ከሆነ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ውድቅ የሚሆኑበት አሰራር አለ›› ብለዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ክሱ ተሻሽሎ መቅረብ አለመቅረቡን ለማየት ለህዳር 24/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Image
ኢወጋን – በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ መልእከቶችን ለህዝብ እይታ አብቅቷል።
የአትዮጵያ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (ኢወጋን)አባላት በአዲስ አበባ ዋና ዋና የህዝብ መገናኛ ቦታዎች እና የአውቶብስ መጠበቂያ የገበያ ቦታዎች ላይ የወያኔን ስርአት የሚያወግዙ እና ስርአቱን ለማውረድ ህዝቡ በጋራ እንዲነሳ የሚያደርጉ ጥሪዎችን ያነገኡ መፈክሮችን በመለጠፍ እንዲሁም ለፖሊስ እና ጦር ሰራዊቱ የሚገባውን የአንድነት እና የህዝብህን አድን ጥሪ በማስተላለፍ የተሳካ ስራ መስራታቸውን ከአዲስ አበባ ኢወጋን የደረሰን መረጃ ያመለክታል::በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ መልእከቶችን ለህዝብ እይታ አብቅቷል።
መላው ኢትዮጵያዊ ወጣት ከኢወጋን ጎን እንዲሰለፍ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል።
በቭድዮ የተደገፈ ዝርዝር ዜናውን በኢትዮጱያ ወጣቶች ድምጽ በኩል ይፋ እናደርጋለን።
ያለ መስዋዕትነት ድል የለም !!! – የኢትዮጵያ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (ኢወጋን)አዲስ አበባ

phpBB [video]

Image

ዛሬ ማክሰኞ እንደአውሮፓውያን የዘመን ኣቆጣጠር ህዳር አስራ አንድ ቀን በየዓመቱ ሀገራቸውን በውትድርና ያገለገሉ እና መስዋዕትነት የከፈሉላት ወንዶችና ሴቶች የሚከበሩበት ዕለት ነው።

ታዲያ ዩናይትድ ስቴትስን በውትድርና ያገለገሉዋት አርበኞችዋ ዜጎችዋ ብቻ ኣይደሉም። .

በጦር ሃይሎች አገልግሎቱ ለመግባት የአሜሪካ ዜጋ ባይሆኑም ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ግሪን ካርድ በሚባለው ማመልከት እንዲቻል ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ተፈቅዱዋል።

በዩናይትድ ስቴትስ የመከላከያ ሚኒስቴር መዝገብ መሰረት ጦር ሃይሎችዋ ውስጥ ግዳጅ ላይ ያሉ ከስድሳ ኣምስት ሺህ በላይ እና የውጭ ሃገር ተወላጆች አሉ።

የቪኦኤዋ Deborah Block በዋሽንግተን ኣካባቢ የሚኖሩ ኣንድ የሶማሊያ ኣንድ የፊሊፒንስ ተወላጅ ኣነጋግራ “ኣሜሪካ ጦር ሰራዊት ውስጥ ገብታችሁ ህይወታችሁን ለኣደጋ ማጋለጥን…

ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡

======================

“ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” ይህ ፁሑፍ የተወሰደው ከአምባገነን አገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ ከሚለው ከ ጄን ሻርፕ መፃሐፍ ነው፡፡ በዙህ አጋጣሚ ይህ መፃፍ እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው፣በተለይ በአገር ውስጥ ለሚንቀሳቁ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያደርጉት አመፅ አልብ ትግል ብዙ አመላካች መረጃዎችን የሚሰጥ ነው፡፡ ዜጎች በሰላማዊ መንገድ የመሰብሰብና የመንግስትን የፖሊሲ ውሳኔዎች እና አሰራሮች የመቃወም መብታቸው የተጠበቀ ነው፣በሰላማዊ ሰልፍ፣በተቃውሞ የፊርማ ሰነድ ፣ለመንግስት ጥሪ ባለመተባበር፣በሥራ ማቆም አድማና በመሳሰሉት ዘዴዎች ተቃውሞ መግለፅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የዲሞክራሲ መብት ነው፡፡ በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች የሚከተሉትን ብሏል ‹‹ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብአዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፤በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡ ››የሚል ሲሆን ፡፡የኢፌዴሪ ህገ መንስት አንቀፅ 30 ንዑስ አንቀፅ 1 ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዞ በሰላም የመሰብሰብ ፣ሰላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነፃነት እና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ በማለት በህገመንግስቱ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ይህ መብት ምን ያህል በአገራችን ተፈፃሚ ነው ብሎ መጠየቅ እና ምላሹን ማወቅ ብዙ እርቀት መሄድን የማይጠይቅ አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደም በተለያየ ወቅት እና ቦታ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ የተደረጉ አመፅ አልባ የአደባባይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ምን ያህል ፈተኛ እንደነበሩ ለአብዛኞቻችን ግልፅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሂደቶ የገዥው መንግስት ፍላጎት ከማስጠበቅ አንፃር እንጂ በየትኛውም ሕግ ድጋፍ ሣይኖረው አብዛኛው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ውጤት አልባ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ይህ ማለት ግን የተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ውጤት አልነበራቸውም ማለት አይደለም፡፡ መንግሰት የሕግ ድጋፍ ሣይኖረው በራሱ ፍላጎትና ፍራቻ ብቻ የህዝቡን ቅሬታዎች ሁሉ ጫና በመፍጠር አፍኖን እንገኛለን፡፡ እንዲህ አይነቱን ሕገ-ወጥ መንግስታዊ ሥራ፣ አልቀበለም ማለት የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግዴታም ነው፡፡ይህን ደግሞ የማሳውቅ እና የማንቃት ኃላፊነት ስለ-አገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ የሚመለከተው ሲሆን ፣በተለይ ፓርቲዎች የቀን-በቀን ሥራቸው መሆን አለበት፡፡ይሄንን ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የተረዱ፣ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ትብብር የመሰረቱት ዘጠኝ ፓርቲዎች “ ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የሕዝባዊ ትግል ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር እንቅስቃሴ ይፋ አድርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተቃወሞ እንቅስቃሴ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር የተጠራ አመፅ አልባ የ24 ሰዓት የአዳር የአደባባይ የተቃውሞ ትይንት በታሪክ የመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡እንዲህ አይነቱ የሞራል የበላይነት እና ጥልቀት ያለው ሃሳብን የሚጠይቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጥሪ ላስተላለፉት ፓርቲዎች በሙሉ አድናቆትን በሙሉ ልብ የሚያሰጥ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሌሎች እውነተኛ የተቃዋሚ የፓርቲዎች በትብብሩ ያልታቀፉ፣ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋው በተለያየ ምክንያት የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረሙ፣ የተቃውሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ ብትቀላቀሉ ውጤቱ የበለጠ ያማረ ይሆናል፡፡በመሆኑም ከሕግ አግባብ ውጪ በማን-አልብኝ እና ትምክተኝነት የተነጠቅነው “የአደባባይ ተቃውሞ” የምናስመልስበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው፡፡ ይዚህ ጽሑፍ አቅራቢ፣ ከዚህ ቀደም “ኢህአዴግ ለምርጫ አልተዘጋጅም” በሚል ርዕስ፡፡ “ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡” ሲል ግንዛቤውን አቅርቧል፡፡ ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ፣ የተዘጋውን በር ለማስከፈት ይቻል ዘንድ በ9 ፓርቲዎች ትብበር ትግሉን የ ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል የፕሮግራም መርህ የመጀመሪያውን ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ የአንድ ወር ዕቅድ አዘጋጅቷል፡፡ በዕቅዳቸው መሠረት ዝግጅቱ የፕሮግራሙ የአፈጻጸም ስልት ፣የጊዜ ሰሌዳ፣ የቦታ ሽፋን፣የፋይናንስ ምንጭ፣ ዓላማዎች፣ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮችና መንግስታዊና የህዝብ ክፍሎች፣ዋና ዋና ተግባራት ፣በተጨማሪም በታሳቢነት በአፈጻጸም ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች/ደንቃራዎችና ሥጋቶች እንዲሁም ለፕሮግራሙን ስኬት አጋዥ ሁኔታዎች እንዲካተቱ አድርገዋል፡፡ይህ ደግሞ ከላይ እንደተገለፀው የፓርቲዎቹ ጥንቃቄ የታከለበት ዕቅድ መንደፋቸው የሚያመላክት ነው ፡፡ዘጠኙ የትብብር ፓርቲዎች በህዳር ወር የሚያተኩሩባቸው የተቃወሞ ተግባራትን እንደሚከተለው ይፋ አድረገዋል፡- 1.በየቤተ እምነቱ ጸሎት ፕሮግራም እንዲደረግ ጥሪ ማድረግና አባላት እንደየእምነታቸው ተሳትፎ ማድረግ፤ 2. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግ፤ 3. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ፤ 4. ለመንግሥታዊ ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት፤ 5. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት፤ 6. የህዝብ ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ፤ ናቸው፡፡ የነዚህ እንቅስቃሴዎች ማጠቃለያ ሕዳር 27 ተጀምሮ ሕዳር 28 የሚያበቃ የ24 ሰዓት የአዳር “የአደባባይ ተቃወሞ” ነው፡፡ በዚህ ፁሑፍ መግቢያ ላይ እንደተገለፀው “ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” እንደተባለው ሁሉ በዘጠኙ የተቃወሚ ፓርቲዎች የተጠራው የሕዳር ወር የተቃውሞ እንቅስቃሴ በስልት የተሞላ ስለሆነ ሂደቱ እና ውጤቱ ታሪካዊ እንደሚሆን ተስፋ የሚጣልበት ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ እንዲህ አይነት ገፍቶ የመጣ ሕዝባዊ ጥያቂ ዕድል በመስጠት ፣ለሚጠየቁ ሕጋዊና ሰላማዊ ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ይህ ደግሞ መንግሰት ደግ ስለሆነ የሚያደርገው ሣይሆን ግዴታውም ጭምር ስለሆነ ነው፡፡ሆኖም ግን ከዚህ በተቃራኒ በጦር መሣሪያ ኃይልና በደህንነት አቅም በመመካት የሕዝብን ጥያቄ ለማፈን በተለመደው መልኩ መሄድ ከባድ ቀውሶች እንዲፈጠሩ መመኘት ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ አይነቱ አሉታዊ ነገር መንግስት እንዲፈጠር ቢፈለግ እንኳን፣ ሕዝብ ከፓርቲዎቹ በሚሰጠው መመሪያ ሥነ-ሥርዓታዊና ደፋር እርምጃ ፣ብልህነት የተሞላበት አካሄድ በመከትል ፤አደባባይ ይዞ የወጣውን ጥያቄ ምላሽ አሰጥቶ፣ ሁሉም ነገር በሠላም እንደሚያበቃ የለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፍላጎት ነው፡፡ በዚህም መሠረት የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፎ ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ መሸጋገራቸውን በተጨባጭ ማስረጃ አረጋግጠዋል፡፡እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችሁንም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሕዝብ አሳውቀዋል፤ሕዝቡ ደግሞ ወትሮም ቢሆን በአገራችን እየተካሄዱ ባሉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ እምነት የለውም፡፡ይህ ደግሞ “ሰኔ እና ሰኞ” እንደሚባለው ነው፡፡ አሁን ላይ የእምነት ነጻነት ጠያቂዎች፣ጋዜጠኞች፣ጦማሪያን፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና አባላት፣ ከገዢው ፓርቲ የተለየ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በአፋኝ ህጎች፣ በፈጠራ ወንጀል ተከሰው አንድም በወህኒ ወይም በስደት ይገኛሉ፡፡በአገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት የለም፣የኑሮ ውድነት የአብዛኛ ኢትዮጵያዊ ትከሻ ያጎበጠ ነው፣ዜጎች በአገራችን ኢትዮጵያ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ የመንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት እንዲሁም የመኖር መብት እየተነፈገ ነው፣ሥራ-አጥነት፣ስደት ፣በአገር ላይ ተስፋ መቁረጥ እና ሌሎች መሰል ችግሮች በመንግሰት አስተዳደር ድክመቶች አማካኝነት የተከሰቱ ናቸው፡፡ ስለዚህም እንዲ አይነቱ ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡ በመጨረሻም ለዚህ ጽሑፍ ማጠቃለይ እንዲሆን ሙሉ በሙሉ ከዘጠኙ የፓርቲዎች ትብብር ከሰጡት ጋዜጣዊ መግላጭ ሃሳብ በመዋስ ነው፣የዚህም ፁሑፍ አቅራቢ ከዚህ የተለይ እምነት የለውምና፡፡ “ ገዢው ፓርቲ በጉዳይ ፈጻሚው የምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ በምርጫ ሥም ለመሥራት የተያያዘውን ቧልት ራቁቱን በማስቀረት ለ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል በሠላማዊ ትግል አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ በእኛ በኩል አስፈላጊውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈልና እስከ መጨረሻው በጽናት መቆም ” በማለት ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል ፡፡ይበል !!!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !
Image

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

በግብፅ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) ምዝገባ ቀነ-ገደብ ሰኞ ኅዳር 1 ቀን፣ 2007 ዓም ተጠናቋል። የመያዶች አዲስ ሕግ መነሻ በቀድሞው የግብፅ ፕሬዚዳንት ሆስኒ ሞባረክ ወቅት እጅግ አፋኝ እንደነበረ የሚጠቀስለት ሕግ እንደሆነ ተነግሯል። በርካታ መያዶች የመወረስ አለያም የመዘጋት ዕጣ እንደተጋረጠባቸው በስጋት ተውጠው ገልጠዋል።

Image
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ ተጠይቆበት ወደ ማረፍያ ክፍል መግባቱ ታወቀ፡፡
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የጅማ ዩኒቨርሲቲ ባቀረበበት ክስ የፕሬስ ህጉን በሚፃረር መልኩ ለአራት ቀናት በማዕከላዊ ታስሮ የተለቀቀው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ክሱ እንደ አዲስ እንዲቀሰቀስበት ከተደረገ በኋላ ዛሬ በተለምዶ ገዳም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ሁለተኛ የወንጀል ችሎት ከእንቁ መፅሔት አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን ጋር እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝም ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ እና የእንቁ አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን እያንዳንዳቸው የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ እንዲያቀርቡ እስከዛውም ወደ ማረፊያ እንዲሄዱ አዟል፡፡ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን በአሁኑ ሰዓት ችሎት መድኃኔዓለም አካባቢ በሚገኘው ወረዳ 8 ጣቢያ እንደሚገኝም ታውቋል፡፡

በቅርቡ ይፋ የሆነ ሠነድ እንዳመለከተዉ በአሁኑ ወቅት በዓለማችን 382 የስኳር ሕሙማን አሉ። በዚያ ላይም 316 ሚሊዮን ሕዝብ 2ኛዉ ደረጃ (ታይፕ 2 ) ለሚባለዉ የስኳር ሕመም የመጋለጥ እድሉ ሰፊ እንደሆነ መረጃዉ ይጠቁሟል።

ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የዛምቢያ ፕሬዚደንት ማይክል ሳታ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ በመዲናይቱ ሉሳካ ተፈፀመ። የፕሬዚደንት ሳታ ይፋ የቀብር ሥነ ሥርዓት ከ50,000 የሚበልጡ የሀገሪቱ ዜጎች እና በርካታ የአፍሪቃ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በአርበኞች ስቴድየም ውስጥ ነበር የተከናወነው።

የጀርመን ፌደራል መንግሥት የኤቦላ ጉዳይ ተጠሪ ቫልተር ሊንድነር የጀርመንን ተሳትፎ ሲያወድሱ ሌሎች የርዳታ ድርጅቶች የጀርመን ድጋፍ የተጓተተ ነው በማለት ይተቻሉ። በዛሬው የአውሮፓ እና ጀርመን ዝግጅት የምናነሳው ርዕስ ነው ።

ኢብቲህል አብደልላጢፍ በቀድሞው የቱኒዚያ አምባገነን ገዢ በዚን አል- አብዲን ቤን አሊ የቱኒዚያ ስርዓት ስር በደል የደረሰባቸውን ሰዎች ጉዳይ ይከታተላሉ። ወይዘርዋ ቀደም ሲል በአንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ፣ አሁን ደግሞ በሀገሪቱ የሀቅ አጣሪ ኮሚሽን ውስጥ ያገለግላሉ።

የኢትዮጵያ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መንግሥት በፓርቲዉ አመራርና አባላት ላይ የሚሰነዝረዉን ማዋከብ ከምንጊዜዉም በላይ አጠናክሮ ቀጥሎአል ሲል ከሰሰ።

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል የልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል ለምርጫ 2007″ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ሰነድ በጥቅምት ወር በአዋሳ እንዲቀርብ ተብሎ የተዘጋጀ ቢሆንም፣  የሰነዱ ጥራት የወረደና በሰነዱ የተካተቱት ነጥቦች ከልማት ሰራዊቱ ኢህአዴግ ሙሉ በሙሉ መጠቀሙን  አያረጋግጥም በሚል  በኢህአዴግ ጽ/ቤት በመተቸቱ እንዲሻሻል ከተደረገ በሁዋላ እንደገና ህዳር 1 …

ኀዳር ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአማራ ክልል የአስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሴ አሰሜ እንደተናገሩት በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ፤ ሰሜን እና ደቡብ አቸፈር ስራ አጥ ወጣቶች በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ግንቦት ሰባት እና አርበኞች ግንባር እየተቀላቀሉ ነው። የወረዳው ወጣቶችን ያወያዩት ሃላፊው ወጣት አርሶ አደሩ ተምሮ ስራ ካላገኘ ፤ ወይ የሚያርሰው …