«ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት ) እና የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ጭቁን ህዝቦች ጋር በመሆን ያካሄዱትን የትጥቅ ትግል በድል ያጠናቀቁት የውጭና የሌሎች ድጋፍ አግኝተው ሳይሆን የጠራ ህዝባዊ መስመር በመያዛቸው ነው» ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር አስታወቁ። ህወሓት የትጥቅ ትግል የጀመረበትን የደደቢት በረሃና ሌሎች ታሪካዊ ስፍራዎች በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገቡ ጥረት እንደ ሚያደርጉ ታሪካዊ ስፍራዎችን የጎበኙ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ገልጸዋል። የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በመጪው የካቲት የሚከበረውን የህወሓት 40ኛው ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በክልሉ የትጥቅ ትግል የተካሄደባቸውን ስፍራዎችና የማዘዣ ጣቢያዎችን ለአንድ ሳምንት ያህል ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የህወሓት ሊቀመንበር አቶ ዓባይ ወልዱ የጉብኝቱን መርሐ ግብር መጠናቀቅ አስመልክቶ ትናንት ማምሻውን በመቀሌ በተዘጋጀው የማጠቃለያ ፕሮግራም ላይ እንደገለጹት፤ ህወሓትና የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ጭቁን ህዝቦች ጋር በመሆን የትጥቅ ትግሉን በአሸናፊነት ሊወጡ የቻሉት የጠራ ህዝባዊ መስመር በመያዛቸው ነው። የክልሉ ህዝብ ቀደም ሲሉ በነበሩትና በደርግ ሥርዓቶች ሲደርስበት የቆየውን ብሔራዊ ጭቆና ለማስወገድ ህወሓት የትጥቅ ትግሉ መጀመሩን ገልጸው፤ በወቅቱ የተሳሳተ ዓላማ ያነገቡ ኃይሎች ትግሉን ገና ከጅምሩ በእንጭ ጩ ለማኮላሸት ተንቀሳቅሰው እንደነበር አስታ ውሰዋል። «ህወሓት የያዘውን ህዝባዊ ዓለማና ትክክለኛ መስመር የሚደግፉ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎችን ከጎኑ እያሰለፈ ህዝቡን የትግሉ ባለቤት ማድረጉ ትግሉን በአሸናፊነት እንዲወጣ አስችሎታል» ብለዋል። ሊቀመንበሩ እንዳሉት ህወሓት በወቅቱ ሲያጋጥሙት የነበሩትን በርካታ ተግዳሮቶችና እንቅፋቶችን ተቋቋሞ ትግሉን በአሸናፊነት ሊወጣ የቻለው የጠራ ህዝባዊ መስመር በመያዙና ባለው የዓላማ ፅናት ነው። ህወሓትና የትግራይ ህዝብ የትጥቅ ትግሉን ያካሄዱት ይደርስባቸው የነበረውን […]

Image
ጌታቸው ሽፈራው
ያች ስለ መገንጠል የተዶለተባት ደደቢት በዓለም ቅርስነት ትመዝገብ እየተባለ ነው አሉ፡፡ አሜሪካኖች እርስ በእርስ ተዋግተው አገር ገንብተዋል፡፡ ጣሊያንና ጀርመኖች ደም ተፋስሰው አገር አቁመዋል፡፡ ምን አልባት እነዚህ አገራት ለአገር ግንባታ (አንድነት) ደም የፈሰሰባቸው ቦታዎች በራሳቸው ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ይሰጧቸው ይሆናል፡፡ እንጅ ዩኒስኮን መዝግብልን ብለው የተጃጃሉ አይመስለኝም፡፡ ኧረ እንዲያው ቢጠይቁስ ስለ አንድነት አጀንዳ የተነሳበት ቦታ (የግድ ከሆነ) ቅርስስ ቢሆን ምን አለበት?

ደደቢት የጠባብ ‹‹ብሄርተኝነት›› እንጅ የአገር ግንባታ መነሻ አይደለችም፡፡ የዓለም ህዝብ ከህወሓት አላማ ምን ሊማርበት ነው ደደቢትን ዓለም በቅርስነት የሚሸከመው? ከዚህ በተቃራኒ ቢቻል በዓለም አቀፍ ደረጃ ካልተቻለ ደግሞ በአፍሪካ ደረጃ አድዋ የሚከበርና የሚታወስ ቦታ ማድረግ ይቻል ነበር፡፡ ምክንያቱም የአፍሪካ የነጻነት ትግልም የሚፈነጥቀው ከዚህ ታሪካዊ ቦታ ነውና! ግን ይህ ኢትዮጵያና አፍሪካውያን እንጅ ህወሓት እንደ ቡድን ጥቅም አያገኝበትም፡፡ ከአላማው ጋርም ፍጹም የተለያዩ ናቸው፡፡

አሊያም ህወሓት ራሱ ተዋናይ የሆነበትን የሀውዜን ጭፍጨፋ በዓለም ከተደረጉ አስከፊ ጭፍጨፋዎች መዝገብ የሚባል ነገር ካለ ቢገባ ምክንያታዊ ይሆናል፡፡ ወይንም ደግሞ ከደርግ ጋር የተደረገውና በሁለቱም ወገን በርካታ ኢትዮጵያውያንን የጨረሰው የእርስ በእርስ ጦርነትን አስከፊነት ዓለም እንዲማርበት ቢደረግ ችግር ላይኖረው ይችላል፡፡ ቢያንስ ኢትዮጵያውያንም ሌላው ዓለምም ይማርበት ይሆናል፡፡

ደደቢት ምን ባይ ነች በዓለም ቅርስነት የምትመዘገበው? እንዲያው ፈረንጆቹን ‹‹ደደቢትን በዓለም ቅርስነት መዝግቡልን!›› ሲባሉ ምንድን ነው የሚሰማቸው? መቼስ ፈርዶብን በእነሱ ምክንያት ኢትዮጵያውያን ጅሎች ናቸው አይደለም የምንባለው? ሌላውን ነገር ለብቻቸው፤ ስድቡን ግን አብረን እንጋተዋለን፡፡ አይ አገር የመጋራት እዳው! ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር አይደለም የሚባለው?

እነዚህ ሰዎች በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ መለስ ዜናዊ የተቀመጡበት ባርጩማ፣ አልኮል የጠጡበት መለኪያ፣ የለበሱት ፒጃማ….በዚህ ከቀጠለም ሚስታቸው (አዜብ) ሳይቀሩ በዓለም ቅርስነት ይመዝገቡልን ብለው ወደ ዩኒስኮ መንከራተታቸው የሚቀር አይመስለኝም፡፡ ጋሻጃግሬም ይመዝገብ የሚል ድርጅታዊ ውሳኔ ከተላለፈ ደግሞ ለሰውዬው ቀኝ እጅ ሆነው ህዝብ ሲያስበዘብዙ የኖሩት እነ በረከት፣ አባዱላ፣ ሽፈራው ሽጉጡ….በቁማቸው የፖለቲካ ሉሲዎች መሆናቸው ነው፡፡ አይጣልኮነው!

እኔ በበኩሌ ከደደቢት ይልቅ ራሱ ህወሓት በ‹‹ቅርስነት›› ባይሆን ባንዳች አስገራሚ መዝገብ ላይ ቢሰፍር ምክንያታዊ ነው ባይ ነኝ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በዓለም ገዥ ሆኖ ገንጣይነቱን አንጠልጥሎ የሚዞር አስገራሚ ቡድን ህወሓት ብቻ በመሆኑ ነው፡፡ ገዥ ሆኖ ተገንጣይ ዓለም አይታ አታውቅም ነበር፡፡ አሁን ግን ጉዱ ህወሓት አለላት፡፡ በመሆኑም አንድ ቀን ትውልድ አፉን ይዞ ይስቅበት ዘንድ በአንዳች አስገራሚ መዝገብ ጎላ ብሎ ቢጻፍ ክፋት የለውም፡፡

እስከዛው ግን እነ አዜብ የስራ ሂደት ባለቤት ተቋቁሞላቸው በዓለም ቅርስነት የሚመዘገቡበት ሁኔታ እንዲመቻች አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እየጠየቅን ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ያለ አንዳች ተቃውሞ! ያለ አንዳች ድምጽ ታቅቦ! በቃ የባለራዩ ሚስት አዜብ መስፍን በቅርስነት ይመዝገቡ! ከተጃጃሉና ካሰደቡን አይቀር እስከዚህ ድረስ ነው እንጅ!

Image
ወያኔው የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የተከሰተውን አለመተማመን ለመቆጣጠር በድጋሚ እንቅስቃሴ ተጀመረ::
የወያኔ ተባባሪ ባለስልጣናት በውሳኔ ሰጭነት ጉዳዮች ላይ አንሳተፍም ሲሉ አማረሩ ::(ምንሊክ ሳልሳዊ)
የደህንነት አባላት ለጸረ ሰላም ሃይሎች እና ለጠላቶቻችን መረጃ እየሸጡ ነው ሲሉ በሃላፊው ተወንጅለዋል::

የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊቱ ከሃገሪቱ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በማበር አደጋ ሊፈጥር ይችላል ሲል መፈራቱ እንዲሁም ሰራዊቱን እየከዱ የሚሄዱ መበራከታቸው አለመተማመኑን ከማስፋቱም በላይ በሕወሓት የጦር እና ደህንነት ክፍሎች ውስጥ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል ሲሉ ውስጥ አውቂዎች ይናገራሉ::ክዚህ ቀደም ተሞክሮ እንዳልተሳካ እና አሁንም ከባለፈው አካሄድ እና ግምገማ በተሻለ መልኩ በወያኔ መከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ አዳዲስ የሆኑ ውስጣዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በተጠናከረ መልኩ በሰራዊቱ መካከል እየተከሰተ ያለውን አለመተማመን ለመቆጣጠር የሚረዱ ግምግናዎች እና የማጣሪያ ስብሰባዎች በስፋት መካሄድ የጀመሩ ሲሆን በፖሊስ ክፍሉ ውስጥ በተለይ በቡድን የሚያሴሩ ሰዎች አሉ እየተባለ ስለሚነገር የወያኔ አንድ ብሄር ሰዎችን በስፋት በመመደብ እንዲሁም ከዚህ ቀደም እንደተደረገው የቢሮ ሰራተኛውን ከደህንነት ቢሮ በሚመደቡ የሕወሓት ደህንነቶች ለመተካት የታቀደ ሲሆን ቀሪውን ከቢሮ ውጭ የሚሰራውን የፖሊስ አካል ለመቆጣጠር አዲስ ሃይል እንደሚመደብ ታውቋል።

የወያኔ ተባባሪ ባለስልጣናት በውሳኔ ሰጭነት ጉዳዮች ባለመሳተፋቸው ማማረራቸው ተሰምቷል በሃገሪቱ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መንግስት እንቅስቃሴ ውስጥ ከወያኔ ባለስልጣናት ውጪ ለበታች ተከታይ ባለስልጣናት ምንም አይነት መረጃ መስጠት እንደቆመ ሲታወቅ ማንኛውም ሃገራዊ ጉዳይ አልቆ እና በአፈጻጸም ደረጃ ላይ ሆኖ እንደማንኛውም ሰራተኛ እንደሚሰሙ ባለስልጣኖቹ በመናገር ላይ መሆናቸው ታውቋል ። በደህንነት ቢሮ ውስጥ በተደረገ ግምገማ የደህንነት አባላት መረጃዎችን በግል ጥቅም በመለወጥ አሳልፋቹ እየሸጣችሁ ናቸው በሚል መገምገማቸውን የውስጥ ምንጮች ተናግረዋል።እንደ ምንጮቹ ከሆነ መረጃን ያለምንም ርሕራሔ መረጃው በአምስት ደቂቃ ውስጥ ጠላት እጅ ገብቶ ያገኘነው ነው ሲሉ አንድ የደህንነት ሹም ተናግረዋል።በዚህ ግምገማ የተከፉት የደህንነት አባላት በመንግስት ባለስልጣናቱ እየተናጡ ቢወረፉም ዝምታን መርጠዋል።

ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን ወደ እውነት ያመጡ ህጎች በኢትዮጵያ አሉ የሚለው ወያኔ ህዝቦች ግን በተግባር ተጠቃሚ ሲሆኑ አላየንም::ህጎቹ በተግባር ይዋሉ ይህንን ህጎች በመመሪያ በደብዳቤ እና በስልክ የሚቀይሩ የሚደፈጥጡ በጥቅም የሚሸጡ የሚረጋግጡ የሚለውጡ ከየወንበራቸው ተሽቀንጥረው ይጣሉ:: የቀን ተቀን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ሂደት ውስጥ እጃቸውን እያጠለቁ ፍትህን የሚያዛቡ አስተዳደራዊ በደሎችን የሚፈጽሙ ባለስልጣናት የህዝብን ማህበራዊ ህይወቶች ከማፋለሳቸውም በላይ ከቀድሞው በባሰ መልኩ ፖለቲካው እንዲጭበረበር ኢኮኖሚው እንዲደቅ ሃገር በብድር እንድትዘፈቅ ህዝብ እንዲደኽይ ከባዱን ሚና እየተጫወቱ ነው::

ለዘላቂ ልማት እንሰራለን በሚል ስርኣት ውስጥ የመሰረታዊ የዲሞክራሲ መብቶች በጊዜያዊነት መኖር እና እንደመነገጃ መጠቀም ህዝብን አገለግላለሁ ሳይሆን አጭበረብራለሁ እንደማለት ይቆጠራል:: የወያኔ ስርኣት ባለስልጣናት በፍርሃት ተውጠው በጠበንጃ ሃይል በሚኖሩባት በዚች ኢትዮጵያችን የፍትህ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ አሁንም እጅግ መልስ የሚያሻቸው ጉዳዮች ናቸው::ዜጎች በሃገራቸው እንዳይኮሩ በመኖር ደህንነታቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲያሳድሩ እየተደረገ ስለሆነ ይህ ደሞ ወያኔ የያዘውን ስልጣን ላለመነጠቅ የሚሰራው ፖለቲካዊ ደባ ውጤት መሆኑ እሙን ነው::

ህዝቦች ህግ እየጸደ ህግ እየተሽሞነሞነ እና እየተብለጨለጨ ቢቀመጥ ምንም የሚጠቅማቸው ነገር እንደሌለ መታወቅ ያለበት ሲሆ አንድ ህዝብ ባላረቀቀ ባልተወያየበት እና ባላጸደቀው ህግ እየተገዛ ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን እንዴት ማስፈን ይቻላል??? መተማመን እና የዜግነት ኩራቱን በሚሰብሩ ባለስልጣናት እየተሰበረበት ያለ ህዝብ ፍትህን እና አስተዳደራዊ እንዲሁም አገልግሎቶችን በተግባል ለማየት እና ለመጨበጥ አልቻለም:: ለተበደለና ፍትሕ ላጣ ዜጋ፣ መልካም አስተዳደር አጥቶ ለሚንገላታ ዜጋ ፍትሕና መልካም አስተዳደር እንዲኖር በአንቀጽ ተደንግጓል እያልን ብናወራ ዋጋ የለውም::

ህዝብ ባለው ስርኣት ላይ እምነት የለውም:; ይህ ደግሞ ራሱ ስርኣቱ ያረጋገጠው ነገር ነው የስርኣቱ ታጣቂ ሃይሎች በሌሎች ወገኖቻቸው ላይ የሚያደርሱትን የሰብኣዊ መብት ጥሰት እያዩ በሃገሪቱ ህግ የለም እኔም ነገ እደበደባለሁ እታሰራለሁ ንብረቴን እነጠቃለሁ መብቴን እነፍርጋለሁ እጠቃልሁ እገደዳለሁ እሰደዳለሁ እገደላለሁ በሚል በስርኣቱ ላይ ያላቸው እምነት የተሟጠጠ ከመሆኑም በላይ ከትንሽ እስከ ትልቅ ከሃገር የመውጣት ንብረትን እና ሃብትን የማሸሽ ተግባር ላይ በመሰማራት በዜግነት አለመተማመን እንዲፈጠር በሩን በርግዶ ከፍቷል ይህ ደሞ ህጎች በተግባር ህዝብን አለማገልገላቸው እና በባለስልጣናት የመደፍጠጣቸው ውጤት ነው::

በተግባር ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት የተነሳ ማንም የለም::ስርኣቱም በጥቅመኞች የሚመራ ህዝቡም ላላወጣው ህግ በዝምታ ደንታቢስነቱን እየገለጸ ነው; ፍትህን እና መልካም አስተዳደርን የሚጥስና የሚያደናቅፍ የስርኣቱ ባለሥልጣን፣ ዜጋም ሆነ ግለሰብ፣ በማስረጃ ሲታይና ሲረጋገጥ ዕርምጃ ለመውሰድ ሕግ ፊት ለማቅረብ ምንም አይነት የተሰራ ስራ ካለመኖሩም በላይ በባሰ መልኩ በይፋ ህጎች ሲደፈጠጡ እያየን ነው:: ባለሥልጣንም ሆነ ባለ ሀብት፣ ታዋቂም ይሁን ተራ ዜጋ፣ ከፈለገው ብሔር ብሔረሰብ ይምጣ፣ የፈለገውን ሃይማኖት የሚከተል ይሁን፣ የጾታና የዕድሜ ልዩነት ሳይኖር ተቃዋሚም ይሁን ደጋፊ ሁሉም ሕግ ፊት፣ ፍትሕ ፊት፣ መልካም አስተዳደር ፊት እኩል መሆኑን አምነን በተግባር ለማዋል ቁርጠኝነት በፍጹም የለም:: ፍትህ እና መልካም አስተዳደር እንዴት ሊረጋገጡ ይችላሉ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እየተጓዝን ነው ጥያቄያችን ;ስለዚህ ህዝብ ለውጥ ይፈልጋል::የወደደ ይውደድ የጠላ ይጥላ እትዮጵያ ውስጥ ወያኔን ጨምሮ ሁሉም የፖለቲካ ጎራ ጥያቄው የስልጣን እና የአገዛዝ ሩጫ ነው::የእኛ የዜጎች ጥያቄ ግን ፍትህ መልካም አስተዳደር የአገልግሎት አቅርቦት እና ሰላም ነው::ይህንን ለማግኘት በጃችን ያለውን ነጻነት ለመቀዳጀት ከትግሉ ያልተቀላቀላችሁ እንድትቀላቀሉ ያስፈልጋል።

ሕያው የሆነው የኢትዮጽያ ታሪክ በተገቢው መንገድ እንዳስቀመጠው የአማራው ሕብረተሰብ ለአያሌ ሺህ ዘመናት የኢትዮጽያን ሉዓላዊነት ከውጭ ተስፋፊዎች በመከላከል ሃገራችን ክብሯን እንደጠበቀች በነጻነት ደምቃ በአንድነቷ ኮርታ ከጥቁርዓለም ውስጥ ብቸኛ ልዋላዊ የግዛት አንድነት ያላት የራሷ ቋንቋና ፊደላት ባለቤት የሆነች ታላቅ ሃገር ትሆን ዘንድ የአማራው ተወላጅ ከሌሎች ወገኖቹ ጋር በመሆን መስፈሪያ የሌለው ዋጋ ከፍሎ ሃገሩን በነጻነት ቢያኖርም በየጊዜው አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ያባረራቸው ቅኝ ገዠ ወራሪዎችና የአድህሮት ሃይላት ሃገር በቀል የእናት ጡት ነካሽ ባንዳ ተላላኪዎችን በማደራጀትና በማስታጠቅ ታፍሮና ተከብሮ የኖረውን ሉዓላዊ ነፃነቷን ሊፈነጩበትና ነባር
አንድነቷን አላልተው ሕልውናዋን ሙሉ በሙሉ በደላሎቻቸው ቁጥጥር ስር ለማድረግና ነባር ሆኖ የቆየውን ሃገራዊ ማንንነት ለመበረዝና ለማውደም የሚያደርጉትን የተቀነባበረ ሴራ በአስተማማኝ መንገድ ለማሳካት ኢትዮጽያዊነትን አንቆ አሻፈረኝ ያለውን የአማራውን ሕዝብ ስልታዊ በሆነ መንገድ አዳክሞ ለማጥፋት ላለፉት 100 አመታት ሲደረግ የነበረው ሴራ በዘመነ ወያኔ ተሳክቶ አማራው ከስልጣንና ከወታደራዊ አመራር ሙሉ በሙሉ በማግለል ከምሁር እስከ ቀን ሰራተኛው ከነጋዴ እስከ ገበሬው ሁሉን ባደረሰ መልኩ የበቀል ሰይፍ ተመዞበት በጅምላ ኢኮኖሚያዊ ሃይሉም ተመቶ ጥገኛና ስደተኛ የማድረጉ ወያኔያዊ ስልት ተግባራዊ ከሆነበት ባለፉት 22 አመታት ውስጥ በአማራው ህዝብ ላይ የተካሄደው ጥቃት ከማንም የተሰወረ አይደለም። የህወሐት ወያኔ የጥቃት ሠይፍ ከተመዘዘበት ከደደቢት እስከ ምንሊክ ቤተ መንግስት የተቀላው የአማራው ተወላጅ አንገት ቤቱ ይቁጠረው። በጥላቻ ተወልዶ በበቀል ያደገው ይህው እኩይ የዘረኛ መንጋ ከመነሻው ይዞ የተነሳውን የጸረ አማራነት ፖሊሲ ለማሳካት በቀጥታና በተዘዋዋሪ ሲያካሂድ የኖረውን የዘር ማጽዳት ተግባር ስልታዊና ዝግመታዊ በሆነ መልኩ በመለወጥ በአማራው ህዝብ ላይ ፈረንጆች (Systematic Genocide) እንደሚሉት የአማራውን ሕዝብ ከሚኖርበት የተለያዩ ክልሎች በማፈናቀል ሐብትና ንብረቱን በማሳጣት ቤተሰቡን በትኖ በረሀብ እርዛት በድንቁርና በጎዳና አዳሪነት ኑሮው እንዲገፋ በማድረግ ከማንነቱ እስከ ወዲያኛው ተቆራርጦ እንዲኖር ለማድረግ በቅርቡ በደቡብ ክልል ጉራፈርዳና በቤኒሻንጉል እንዲሁም ሰሞኑን በምዕራብ ሸዋ በሚኖሩ የአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮች ላይ የተፈጸመውን አሳዛኝ ድርጊት እንዲገታ በአማራነታችን ተሰባስበን ትግሉን ለማገዝ ቁርጠኛ አቋም ላይ ለመድረስ እንድንችል አብይ ምክንያት በመሆኑ ይህን ንቅናቄ ለመመስረት ሳንወድ በግድ ተገፍተን በማንነታችን ዙሪያ ለመሰባሰብ አስገድዶናል።
ይህ በአማራው ሕዝብ ላይ በተከታታይ በመፈጸም ላይ ያለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ በአንድ ቦታ መግታትና መቆም ካልቻለ አሁን በያዘው የበቀል ፍጥነት ከቀጠለ ውጤቱ አስከፊና ሊገመት ከሚችለው በላይ ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል፤ ስለሆነም ሕወሐት/ወያኔ የአማራውን ሕዝብ ለማጥፋት የመዘዘው የጥፋት ሰይፍ ያለ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በተዓምር ወደ አፎቱ ስለማይመለስ በዐማራው ትግዕስትና ሆደ mሰፊነት ወያኔ ያቀደው የዘር ማጥፋት ሊገታ እንደማይችል በመረዳት የአማራው ነገድ ወጣቶች በመሰባሰብ በማንነታችንና በእናት ሃገራችን ላይ የተቃጣውን አደጋ ባለን አቅም ለመከላከል ባለብን ትውልዳዊና ሃገራዊ ግዴታ በንቅናቄያችን ዙሪያ ወጣቱ በመሰባሰብ ትግሉን በማገዝ ታሪካዊ ሃለፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን።
የአማራ ወጣቶች ንቅናቄ የትኩረት አቅጣጫው በሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ፕሮግራም የሠፈረውን በግፍ ሀብት ንብረታቸውን ተነጥቀው ለተፈናቀሉ የዐማራ ነገድ ተወላጆች ዕርዳታ ማሰባሰብ፣ድምፅ አልባ እና ባገሩ ባይተዋር ለሆነው የዐማራ ነገድ ድምፅ መሆን የዐማራውን ሁለንተናዊ ዐቅም በመገንባት ዐማራው በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ሕይዎት ውስጥ ተገቢ ቦታውን እንዲይዝ ለማድርግ ሞረሽ ወገኔ የዐማራው ድርጅት በሚያደርገው ሁሉአቀፍ እንቅስቃሴ የዐማራው ወጣት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የበኩሉን ድርሻ ከመወጣት ባሻገር የዐማራውን ወጣት በዘመኑ የብዙኃን መገናኛዎች በመድረስ ትውልድና አገር አድን ሚናውን እንዲወጣ የማደራጀትና የማንቃት
ሥራዎችን መሥራት ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለመላው የዐማራ ነገድ ተወላጆች የምናስተላልፈው መልዕክት፣ አባቶቻችን ያቆዩንን ነፃነት፣አንድነትና
ሰላም ማረጋገጥ የሚቻለው ዐማራው ተደራጅቶ በአውራ ጠላትነት ፈርጀው ፣ፈጽሞ ሊያጠፉት ከተሰለፉት ኃይሎች በአቻነት ሲቆም ብቻ ነው፡፡ ድር ሲያብር አንበሣ እንደሚያስር ሁሉ፣ የእኛም መደራጀት በማንነታችን ላይ የተከፈተውን የዘር ማጽዳትና የዘር ማጥፋት ተግባር ፈጽሞ በማስቆም የኢትዮጵያን ትንሣዔ የሚያረጋግጥ ስለሆነ የዐማራው ወጣት ይህን ንቅናቄ በመቀላቀል ትውልዳዊ ኃላፊነታችን በክብር እንድንወጣ የድረሱልን ጥሪ በሚያሰማው የዐማራ ነገድ ስም ጥሪአችን እናቀርባለን፡፡ እኛም እንደ አባቶቻችን ታሪክ ሠሪ እንሁን!
አማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደግ!
ሞረሽ የአማራ ወጣቶች ንቅናቄ ግንቦት ፳፰፤ ፪ሺ፭ ዓ/ም

ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ የጀመርነው የጋራ ትግል ተጠናክሮ ይቀጥላል!!

በ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› የሁለተኛ ዙር ፕሮግራም ከ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የተሠጠ መግለጫ፤

ትብብራችን ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ያወጣውን የመጀመሪያ ዙር ፕሮግራም አጠናቆ ወደ ሁለተኛው ዙር ሲሸጋገር ከሁሉ በማስቀደም የአንደኛው ዙር ዕቅዳችን ተግባራት ክንዋኔ ከዓላማችን ጎን ቆማችሁ በተለያየ መንገድ ለደገፋችሁን በአገር ቤትና በውጪ አገር ለምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋናችንን፣ በአንጻሩ ዕቅዳችን ከዳር እንዳይደርስ ህገመንግስታዊ መብታችንን በመጨፍለቅ ጉዞኣችንን ለማደናቀፍ የተቻላችሁን ህገወጥ የቢሮክራሲ መሰናክልና ለኢትዮጵያዊ ሠላማዊ ዜጋ ቀርቶ ለጠላት የማይገባ ኃይል በመጠቀም የመብት አፈና ለፈጸማችሁ የመንግሥት አካላት ሁሉ ወደ ኅሊናችሁ እንድትመለሱ ጥሪ በማቅረብ ነው፡፡ በተጨማሪ ለሁሉም ወገን የያዝነው ትግል የአገርና የህዝብ፣ተጠቃሚውም ሁላችንም/ሁሉም ዜጎች/ና የሁላችንም የጋራ አገራችን፣ለጉዞኣችን የመረጥነው መንገድ ሠላማዊና ህገመንግሥታዊ ብቻና ብቻ፣መጓጓዣችን ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ መድረሻችን መድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ እንዲሁም በጉዞኣችን ላይ የቱንም ያህል አረመኔያዊ የኃይል እርምጃ ይወሰድብን፣ ትግሉ የቱንም ዓይነት ዋጋና መስዋዕትነት ይጠይቅ ከጅምሩ ያለመስዋዕትነት ድል የለም ብለን ተነስተናልና ከያዝነው ዓላማ ኢንች የማናፈገፍግና ለቃላችን በጽናት የምንቆም መሆኑን ዳግም በማረጋገጥ ነው፡፡

ትብብራችን የመግባቢያ ሰነዳችንና የጥናት ሪፖርታችንን እንዲሁም ከመጀመሪያው ዙር ያገኘውን ተሞክሮ በሠረት በማድረግ ይህን የሁለተኛ ዙር የሁለት ወር ዕቅድ (ከታህሳስ 16 እስከ የካቲት 15 /2007) አውጥቶ በቀዳሚነት ለዋነኛ ባለቤቶቹና ፈጻሚዎቹ ኢትዮጵያዊያን ሲያቀርብ እንደመጀመሪያው ዙር ከጎኑ እንደሚቆሙ ሙሉ እምነት በማሳደር፣በእኛ በኩል ከፊት ቆመን ትግሉን ለመምራት ያለንን ዝግጁነትና ቁርጠኝነት ለዚህም የገባነውን ቃል በማደስ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ‹‹በየትም የዓለማችን ክፍል አምባገነንነት የህዝቦችን የተባበረ የዲሞክራሲ ጥያቄ በኃይል አፍኖ በጨቋኝነት የዘለቀበት ታሪክ አልተመዘገበም›› ማለታችንን በማስታወስ ነው፡፡

ይህ ዕቅድ የመጀመሪያው ዙር ቀጣይ እንደመሆኑ ዓላማችንም የምርጫ ሁኔታዎች ባልተሟሉበትና የመራጩ ህዝብ ነጻነት በሌለበት ስለምርጫ መናገር አስቸጋሪ ነው፣ እነዚህ በሌሉበት አማራጭ የምርጫ ኃሳቦች በህዝብ ውስጥ ሊንሸራሸሩም ሆነ አማራጭ ኃሳባችንን ከህዝብ ማድረስ አይቻልም፣ሚናችንም የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አማራጭ ሆኖ መቅረብ ሣይሆን የህወኃት/ኢህአዴግ አጃቢነትና የሀገር ሃብት በአላስፈላጊ መንገድ የማባከን ሥራ ተባባሪነት የዘለለ አይሆንም ከሚል የመነጨ ነው፡፡ ደጋግመን እንደገለጽነው ነጻነት በሌለበት ያለንበት ተጨባጭ ሁኔታ ምርጫ ቧልት ነው፡፡

በመሆኑም የዚህ ዙር ዓላማችንም ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የጀመርነውን እንቅስቃሴ አጠናክሮና አስፍቶ በመቀጠል ለነጻ ፣ፍትሃዊ፣ተኣማኒ፣አሳታፊ….በአጠቃላይም ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ ለህዝብ ተደራሽ በመሆን በህዝብ (የተለያዩ የህዝብ ክፍሎችን፣ አደረጃጀቶችንና ዜጎችን በማካተት) የነቃ ተሳትፎ ተጽዕኖ በማሳረፍ በምርጫ ሂደቱና አተገባበሩ ላይ ያነሳናቸው ጥያቄዎች እንዲመለሱ ማድረግና ከዚህ ጎን ለጎን በቀጣዩ ምርጫ (2007) ተቃውሞ ጎራው በአጠቃላይ የትብብሩ አባላት በተለይ ድምጽ እንዳይሻሙ /የመራጩ ህዝብ ድምጽ እንዳይከፋፈል/ የሚያስችል ስልት በመቀየስ ከመራጩ ህዝብ ማድረስ ነው፡፡

በዚህ ላይ በመመስረት ትብብሩ በዚህ ሁለተኛ ዙር ፕሮግራም ዕቅዱ እንደባለፈው ተደጋጋፊ፣ ተመጋጋቢና ተከታታይ ሦስት ዋና ዋና ተግባራትና በሥራቸው አስራ አራት ዝርዝር ተግባራት አካቷል፡፡ እነዚህ በትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ጥልቅና ዝርዝር ውይይት ተደርጎባቸው የጸደቁ ዋና ዋና ተግባራትም፡-
1. የአባላትና የትብብሩ አቅም ግንባታ፡- የትብብሩን አባላት አብሮነት ማጠናከርና የጋራ ዓላማውን የማስፈጸም አቅም ማጎልበት፤
2. የህዝብ ግንኙነት ተግባራት፡- የህዝብ ተደራሽነት ማስፋትና ዓላማ ማስተዋወቅ፣
3. የህዝብ ንቅናቄ መድረኮች ማመቻቸት፡- በአዲስ አበባና የተመረጡ ከተሞች አራት የአዳራሽ/አደባባይ የህዝብ ውይይት ፤በአዲስ አበባና በተመረጡ አስራ አምስት የክልል ከተሞች በተመሳሳይ ቀንና ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ፤ የሚያጠቃልሉ ናቸው፡፡
4.
አስተባባሪ ኮሚቴው ተግባራቱን በጊዜ ሠለዳ በማስቀመጥ ለነዚህ ተግባራት ማስፈጸሚያ የብር 1,215, 000.00 (አንድ ሚሊየን ሁለት መቶ አስራ አምስት ሺህ ) በጀት አጽድቋል፡፡

እዚህ ላይ ይህን ዕቅድ ስናወጣ መንግሥት/ጠቅላይ ሚ/ሩ/ ከቅርብ ቀን በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ‹‹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መንግሥትን መገዳደር አይችሉም›› የሚል ኃሳብ ያዘለ መልዕክት ማስተላለፋቸውን ማድመጣችንን፤ይህ መልዕክት የማደናገሪያና ማደናበሪያ ፕሮፖጋንዳ ስልትም ይሁን የተቃዋሚዎችን ዓላማና የመኖር ትርጉም የመጨፍለቅ ግልጽ መልዕክት ቢሆን እኛ የተያያዝነው ህገመንግሥታዊ መብታችንና የዜግነት ክብራችንን የማስከበር ሠላማዊና ህጋዊ ትግል በመሆኑ ማስፈራሪያውም ሆነ ማስጠንቀቂያው ህገመንግሥታዊ አይደለምና ህገወጥ ነው አይመለከተንም፤በሚል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡

በመጨረሻም ለተያያዝነው ሠላማዊና ህገመንግሥታዊ የመድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ትግል፡-
1ኛ/ የጉዳዩ ቀዳሚና ዋነኛ ባለቤት የሆናችሁ ኢትዮጵያዊያን ይህን አምባገነናዊ ሥርዓት በሠላማዊ ትግል አስገድደን ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ ራሱን እንዲያዘጋጅ የነቃ ተሳትፎ በማድረግና ሁለንተናዊ ድጋፍ በማቅረብ ከጎናችን እንድትቆሙ፣ በተለይ በውጪ አገር የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን ትብብሩ ለትግሉ ተገቢውን አቅም እንዲገነባ በጀቱን ለመሸፈን ወቅታዊ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታደርጉ፤
2ኛ/ በአገራችን የሚደረጉ ምርጫዎች ዲሞክራሲያዊ እንዲሆኑና ከማንኛውም ፓርቲ ተጽዕኖ ነጻ ሆኖ ለማስፈጸም በህገ መንግሥቱ ሥልጣኑ የተሠጣችሁ፣ ኃላፊነቱ የተጣለባችሁ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አመራርና አስፈጻሚ ባለሥልጣናት ከገዢው ፓርቲ ወገኝተኝነት እንድትላቀቁና እንደ ተቋሙ መሪና ዜጋ ራሳችሁን ከትውልድ ባለዕዳነትና ከታሪክ ተጠያቂነትና ተወቃሽነት ነጻ እንድታወጡ፤
3ኛ/ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለይም የመግባቢ ሰነዱና የጥናቱ ሪፖርት ባለቤቶች የአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ የሚጠይቀውና የተያያዝነው ትግል ከፓርቲ መሪዎች የግል ፍላጎትና ከፓርቲ ጥቅም በእጅጉ የላቀ በመሆኑ ለአገርና ህዝብ ቅድሚያ በመስጠት ተቃዋሚ ጎራው ባለፉት ምርጫዎች ሁሉ በመከፋፈልና የህዝብን ድምጽ በመበታተን ሚናው ከምርጫ አጃቢነት ያላለፈ በመሆኑ ይህን ‹‹በቃ›› የማለት ወቅቱ ነገ ሳይሆን ዛሬ ስለሆነ ከ‹‹እናቴ መቀነት ጠለፈኝ›› ምክንያት ወጥታችሁ ለዚህ ዓላማ በጋራ ለመቆም ትብብሩን ያለቅድመ ሁኔታ እንዲቀላቀሉ፤
4ኛ/ገዢው ፓርቲ/መንግሥት ከተያያዘው በአፈና ‹‹ለብቻ በመሮጥ›› አሸናፊ ነኝ በሚል ሥላጣን የማስጠበቅ ኢህገመንግሥታዊ አካሄድ ታርሞ የአገርና ህዝብ ጉዳይ ከሥልጣን ማስጠበቅ በላይና የኃይል እርምጃና አፈና ሥልጣን የማራዘም እንጂ የህዝብን የለውጥ ፍላጎትም ሆነ ለውጥን የማስቀረት አቅምና ኃይል የሌለው መሆኑን ከዓለም ታሪክና ከቅርብ ጊዜ የጎረቤት አገሮች ተሞክሮ እንዲማርና ራሱን ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲያዘጋጅ፤ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ያለመስዋዕትነት ድል የለም፤ የጋራ ትግላችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!!

ታህሳስ 17/2007 ዓ.ም! አበባ!

የፌድራል ጉዳዪች ሚኒስትር ከነሰራተኞቹ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሊሰማሩ ነው፡፡ የዶ.ር ሽፈራውን ድምጽ ይዘናል

http://goo.gl/kYqE7x
http://goo.gl/kYqE7x

በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ (ድምጽ ጥራቱ ዝቅተኛ)
http://goo.gl/AslZyM
http://goo.gl/AslZyM

Image

ከድሬዳዋ ተነስተው ኤርትራ ቀይ ባህር ዳርቻያረፉት የኢትዮጵያ ሄሊኮፕተሮች ጉዳይ ለወያኔ ራስ ምታት ሆኖበት ሰንብቶአል። ሄሊኮፕተር ይዘው ኤርትራ የገቡት ኢትዮጵያውያን የአየር ሃይል አብራሪዎች ማንነት እና በወያኔ ላይ ያላቸው ተቃውሞ ምን እንደሆነ ገና አልታወቀም። በተያያዘ የኢትዮጵያ አየር ሃይል ከማንኛውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ሽባ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ። አማራ እና ኦሮሞ የጦር አይሮፕላን አብራሪዎች ከስራ ውጭ ተደርገዋል። የትግራይ አብራሪዎችና ቴክኒሻኖች ደ’ሞ በጣት የሚቆጠሩ በመሆናቸው አየር ሃይልን በትግራይ ሰዎች ብቻ ለማንቀሳቀስ አልተቻለም። በተለይም ክኒሻኖች በአብዛኛው አማራና ኦሮሞዎች በመሆናቸው ወያኔ ችግር ውስጥ ወድቆአል። የፌክ ፌደራሊዝም ውጤት ይኸው ነው።

ከቀጣዩ ምርጫ ጋር በተያያዘ ወያኔ ብዙ ፈተናዎች ከፊቱ ተደቅነውበታል። ህወሃትና ብአዴን የስልጣን ሽኩቻ ላይ መሆናቸው ሰሙነኛ ወግ ነበር። ኦህዴድ ከጨዋታ ውጭ ሆኖአል። ድቡብ ህዝቦች፤ አልነበሩም – የሉምም። ኦህዴድን ያልያዘ የኢህአዴግንሊቀመንበርነት (ጠቅላይ ሚኒስትርነትን ጭምር) መያዝ እንደማይችል ግልፅ ነው።ስለዚህ ህወሃትና ብአዴን የኦህዴድ አባላትን በግለሰብ ደረጃ በመቀራመት የራሳቸው ለማድረግ ውስጥ ውስጡን ይሻኮቱ ይዘዋል። ኦህዴድ ለራሱ እንዳያስብ ተደርጎ ስለተሽመደመደ ከፊቱ የተደቀነው ጥያቄ፣ “ማንን ላንግስ?” የሚለው ብቻሆኖአል። ርግጥ ነው፤ የኦህዴድ አባላትን በቅርብ እንደማውቃቸው አማራ ወደ ስልጣን ከሚመጣ ህወሃት ስልጣን ላይ ቢቆይ ይመርጣሉ። ግን ደግሞ በዚህ ወቅት የአካባቢያችን ዋነኛ ጠላት ወያኔ እንጂ የአማራ ፖቲከኞች እንዳልሆኑ የሚያጡት አይመስለኝም። ወያኔ ቢወድቅ ደመራው ወዴት እንደሚወድቅ አለመታወቁ ለማናቸውም ቢሆን አሳሳቢ ነው። ሁኔታዎች ተወሳስበዋል።የኦህዴድ አመራር መግባባት ችሎ ቢደራጅ ህወሃትና ብአዴንላይ ተፅእኖ ማድረግ ይቻለው ነበር። ለአብነት ከኢህአዴግ አባል ድርጅትነት ቢወጡ ጠንካራ ተደራዳሪ መሆን በቻሉ። ከፓርላማው ራሳቸውን ቢያገልሉ ወያኔ የኦሮሞን ህዝብ ማክበር በጀመረ ነበር። በርግጥ እንዲህ ያለ ወግ፣ “እንጀራ የለም እንጂ – ወጥ ቢኖር ኖሮ” እንዲሉ ሊሆን ይችላል።

የወያኔ አመራር አባላትም መስቀለኛ መንገድ ላይ ናቸው። አማራ ወደ ስልጣን ከሚመጣ ኢትዮጵያ ብትፈራርስ እንደሚመርጡ ግልፅ ነው።የአቦይ ስብሃት ነባር አቋምይታወቃል። ሃይለማርያምና ደመቀ (አገውና ወላይታ – ፕሮቴስታንትና ሙስሊም) ወደ ስልጣን ሲመጡ፣ “የኢትዮጵያን ስልጣን ከአማራና ከኦርቶዶክስ አፅድተነዋል” ብሎ በሬድዮ ሲናገርተሰምቶአል። ለነገሩ የተሳሳተ አይመስለኝም። ኮሎኔል መንግስቱ በማፈራረስ የጀመረውን የኦርቶ – አማራ ቢሮክራሲ ወያኔ በተሳካ ሁኔታ አጠናቆታል። ስለዚህ ብአዴን (አማራ ነው ከተባለ) የፈለገውን ያህል ቢፍጨረጨር የጋረዳለቲን በተመንግስት እንዲቆጣጠር ሌሎች አይፈቅዱለትም። ህወሃት ደብረፅዮንን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሊያመጣ ማሰቡ ሲናፈስ የሰነበተው ወሬ ልክ አይመስለኝም። ደብረፅዮን የቴክኒክ ሰው ነው። የኢትዮጵያን ፖለቲካ ለማሽከርከር የሚቻለው ፖለቲከኛ አይደለም። በዚህ ወቅት ህወሃት ወደ ስልጣን ሊያመጣው የሚችለው ብቸኛ ተቀባይነት ያለው ሰው ቢኖር ቴዎድሮስ ነው። ትውልዱ ከአድዋ የሚመዘዘውን፣ አስመራ ተወልዶ ማደጉ የሚነገርለትን ቴዎድሮስ አድሃኖምን በመለስ ዜናዊ ወንበር ላይ ማስቀመጥም ቢሆን ግን ለህወሃት አስቸጋሪ ነው። ቴዎድሮስ አድሃኖም የሚናከስ ጥርስ የለውም ተብሎ ይታማል። ኢትዮጵያን ለመምራት ደግሞ የሚናከስ ብቻ ሳይሆን፣ የሚቦጭቅና የሚያኝክ ጥርስ ያስፈልጋል። ህወሃት ቴዎድሮስ አድሃኖምን ወደ ስልጣን ማምጣት ይመኙ ይሆናል። ቴዎድሮስ ስልጣኑን ቢይዝ ለህወሃት ጥቅም ነው። አደገኛ ጉዳትም ግን አለው። ጫጫታውን አይችሉትም። ከውስጥም ከውጭም የሚወረወርባቸውን የተቃውሞ ፕሮፓጋንዳ መሸከም ስለመቻላቸው ርግጠኛ አይደሉም። ስለዚህ ሃይለማርያምን ወይም እሱን የመሰለ ታዛዥ ሰው እየለዋወጡ፣ ከጀርባ እየተቆጣጠሩ ድምፃቸውን አጥፍተው ስልጣን ላይ መቆየቱን ይመርጡ ይሆናል።

ሃይለማርያም በህወሃትና በብአዴን ተከቦ ስራውን ሲሰራ ሰንብቶአል። መከላከያ፣ ደህንነትና ውጭ ጉዳይን ማዘዝ አይችልም። መንግስትን መንግስት ሊያሰኙ የሚችሉት እነዚህ ሶስቱ ቁልፍ ቦታዎች ደግሞ በህወሃት የተያዙ ናቸው። በጌታቸው አሰፋ፣ በሳሞራ የኑስ እና በቴዎድሮስ አድሃኖም መዳፍ ስር ናቸው። ስለዚህ ሃይሌ ቴክሱ ስልጣን አልባ ሆኖ (በጌታ ፈቃድ) የታዘዘውን ሲሰራ ቆይቶአል። ያም ሆኖ ሃይለማርያም በተቀረው የአስተዳደር ቦታ የተቻለውን ያህል የደቡብ ሰዎችን ለመሰግሰግ መሞከሩ አልቀረም። ይህ ሁኔታ እንግዲህ ለረጅም ጊዜ በአማራ ተይዞ የቆየውን የማእከላዊ መንግስት የአስተደዳር ቦታዎች እያዳከመ ስለሚሄድ፣ የአዲሳባን ቢሮክራሲ የሰው ሃይል ሚዛን ስለሚያመጣጥነው ወያኔዎችም አይጠሉትም። ከዚህ ባለፈ ሃይለማርያም ሊያደርግ የሚችለው የለም። “ሃይሌ ጥርስ አብቅሎ እነ አባይ ፀሃዬን አልታዘዝም ማለት ጀምሮአል” የሚለውን ሹክሹክታ ለጊዜው ለማመን እቸገራለሁ። መጠበቅ ይሻላል።

ኦቦ ሌንጮ ለታ ለቀጣዩ ምርጫ ወደ ፊንፊኔ ያቀናል ሲባል ተሰንብቶ ነበር። እምን እንደደረሰ አልተከታተልኩትም። ሌንጮ ጠቅልሎ ቢገባ ግን ወያኔ የሚጎዳ እንጂ የሚጠቀም አይመስለኝም። እንኳን ሌንጮ ገብቶ መረራ ጉዲና እንኳ እያዋዛ ፈተና ውስጥ ጨምሯቸዋል። በቀጣዩ ምርጫ በመጠኑም ቢሆን ወያኔን ሊፈታተን የሚችለው መረራ ጉዲና ነው። ስልጣን ይገለብጣል ተብሎ ባይታመንም ጥቂት የፓርላማ ወንበሮችን ያገኝ ይሆናል። ሌንጮ ተሳክቶለት ፊንፊኔ ገብቶ አስማተኛውን የኦነግ ባንዴራ ማውለብለብ ቢችል የምርጫ ሜዳውን ሞቅ ደመቅ ባደረገው። ወያኔም ቢጫ ወባ በሽታው በተቀሰቀሰበት ነበር። በነገራችን ላይ “ODF” የሚለው ምህፃረ ቃል Oromia Defence Force መስሎ ይሰማኛል።

አሜሪካኖች ህወሃትን እየደገፉ መሆኑ አይካድም። ህወሃትም ቢሆን ለአሜሪካ ብብቱን ከፍቶ ሰጥቶአቸዋል። አሜሪካኖች በህወሃት አመራር ባገኙት ጥቅም ደስተኛ ቢሆኑም፤የወያኔ ስርአት በስልጣን እንዲቆይ ይፈልጋሉ ማለት ግን አይደለም። “አናሳ ብሄረሰብ በስልጣን ላይ ሊቆይ ከሚችለው በላይ ገዝታችሁዋል። ከዚህ በላይ መሄድ አትችሉም። ችግር ሳይገጥማችሁ ቦታውን ብትለቁ ይሻላል።” ብለው ደጋግመው መክረዋቸዋል። ወያኔ የህዝብ ድጋፍ ስለሌለው አገሪቱን ገፍቶ ገፍቶ ገደል ይጨምራታል ብለው ሊሰጉ ይችላሉ። አሜሪካኖች እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ያሉትን ከጀርባ ደጋግፈው ወደ ስልጣን ለማምጣት እንደሚፈልጉ ይታወቃል። ስለ ኦሮምያ ነፃነት የሚያስቡ ወጣቶችን ግን አሜሪካኖች በጣም ይፈሯቸዋል። “በኢትዮጵያ አንድነት” የሚያምን፣ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ሊኖረው የሚችል ወጣት ኦሮሞ ለማግኘት መከራቸውን ሲያዩ ሰንብተዋል ይባላል። የሚሳካላቸው አይደለም። በርግጥ በመጪው ዘመን የኦሮሞን ህዝብ በትክክል የሚወክል ሃይል ወደ ስልጣን ካልመጣ የኢትዮጵያ አንድነት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ምእራባውያኑ አስጠንተው ደርሰውበታል። ያም ሆኖ ኦሮሞዎች ካላቸው አቅም አንድ አስረኛውን እንኳ እንዳልተጠቀሙ ይታመናል።

የአንድነት ሃይሎች የፖለቲካ አካሄድ ቀልድ ይመስለኛል። አንዳርጋቸው ፅጌ፣ “ነፃነትን የማያውቅ ነፃአውጪ” ብሎ ነበር። “አንድነትን የማያውቁ አንድነቶች” ከፕሮፓጋንዳ ባሻገር የትም መሄድ አልቻሉም። ኢትዮጵያዊነት ባለቤት አጥቶአል። ህይወቱን ቀርቶ እንቅልፉን የሚሰዋለት እያጣ ነው።ጠጋ ብሎ ላያቸው “አንድነቶች” በጎንደርና በጎጃም፤ በወሎና በመንዝ ተከፋፍለው ሲሻኮቱ ይገኛሉ። የጎንደር – ሸዋ ሽኩቻቸውን ሳይፈቱ ኦጋዴን ኢትዮጵያዊነትን እንዲዘምር ይመኛሉ። ብዙውን ጊዜ የአማራ ፖለቲከኞች፣ “ኦሮሞ ወንድሞቻችን” ማለት ያበዛሉ። በአማራ ፖለቲከኞች ዘንድ፣ “ግማሽ ኦሮሞ ነኝ” ማለት ፋሽን ሆኖአል። በአንፃሩ የኦሮሞ ፖለቲከኞች፣ “አማራወንድሞቻችን” የሚል አባባል ሲጠቀሙ ሰምቼ አላውቅም። አንደኛው ተለማማጭ የመሰለበት ምክንያቱ ምንድነው? ከልብ ስላልሆነ ይመስለኛል። “ወንድሞቻችን” የሚለው አባባል የለበጣ ነው።የኦሮሞን ህዝብ ስነልቦና “የቡርቃ ዝምታ” በተባለው መፅሃፌ ጥሩ አድርጌ በመግለፄ እኔ የአማራ ህዝብ ባለውለታ እንደሆንኩ ይሰማኛል። አሁንም አማራ ፖለቲከኛ ወንድሞቼን በግልፅ መምከር እፈልጋለሁ። ጊዜ እያመለጠ ነው። የአማራ ፖለቲከኞች ከሽማግሌ ኦሮሞዎች ጋር ዛሬውኑ ተግባብተው ለመስራት ካልሞከሩ በርግጥም ጊዜ እያመለጣቸው ነው። ሽማግሌዎቹ ቢያንስ በኢትዮጵያዊነት ስር ኖረዋል። ወደውም ሆነ ተገደው ለባንዴራው ዘምረዋል። አዲሱ የኦሮሞ ትውልድ ግን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለሙን ባንዴራ አጥብቆ ይጠላዋል። አማርኛን ይጠየፋል። ‘ኢትዮጵያዊ ነኝ’ ማለት አይፈልግም። የአንድነት ሃይሎች ዛሬውኑ መባነን አለባቸው። ዮሃንስ መጥምቁ፣ “ከኔ በሁዋላ የሚመጣው በእሳት ያጠምቃችሁዋል!” እንዳለው እየመጣ ያለው የኦሮሚያ አዲሱ ትውልድ ከአበሻ ጋር ቁጭ ብሎ መነጋገር ስለመቻሉ እጠራጠራለሁ። መልካም አዲስ አመት፤ መልካም የገና በአል ይሁንልን። አላህ ይርዳን። አሜን!

በአስመራ የመሸጉ ተቃዋሚዎች እና የሻእቢያ ግፍ
Image

አንደኛ – በሻእቢያና በወያኔ ልዩነት የለም ፤ ጠባቸው በራሡ ሻቢያ ወያኔን አንስቶ በሌላ ትግሬ መተካት ይፈልጋል እንጅ ከወንድሞቹ “ትግራዋይ” ጋር ምንም ፀብ የለውም ደምህት የሚባለው የትግሬ ድርጅት ባጭር ጊዜ የት እንደደረሰ ማየት ይቻላል፤ ወያኔም እንደዛው ምንሊክ ነው ከወንድሞቻችን የለየን እያሉ እየነገሩን ነ።

ሁለተኛ ፦ ከደምሕት በአራት አመት ቀደም ብሎ የነበረው አርበኞች ግንባር አመራሮቹ ታስረዋል እንደውም ኮለኔል ታደሰን ሻብያ ገድሏቸዋል ።በርካታ የአርበኞች ግንባር አባላት ታስረዋል ትግሉን ጥለው ተሰደዋል:: በቅርቡ የአማራ ንቅናቄ የሚባሉት በኤርትራ ያለው ትግል የውሸት ነው በሻእቢያ ቤት ሆኖ ነጻነት የለም መውጣት አለብን ብለው ስላሉ አምስት አባሎቼን ሻቢያ አፈነብኝ ሲል ተሰምቷል፤ ልብ በሉ እንኳን መደራጅት በቃን ብለው ከኤርትራ መውጣት አልቻሉም ።

ሶስትኛ :- ግንቦት ሰባቶች ግልጽ የሆነ አድር ባይነት እያሣዩን ነው ፤ እነሱ የሚሉት እዛ የታሰሩት ከኢሳያስ ጋር ችግር ስላለባቸው ነው ይሉናል ። የምን ችግር ብለን አማራ ፎርስ የሚባሉትን ስንጠይቅ ሻእቢያ እንደህጻን ልጅ “ሁን” የሚልህን ከመሆን ውጭ እንዲህ አደርጋለሁ ማለት ፈጽሞ አይታለምም ይሉናል ። እውነት ነውም ። ግንቦቴዎች ግን ይህን ተቀብለው እየሰሩ ነው ። ልብ አድርጉ ኤልያስ ክፍሌ አስመራ የኢትዮጵያን ሪቪው ቅርንጫፍ ሊከፍት ከሻብያ ጋር ተስማምቶ ነበር ፤ የኮለኔል ታደሰን መታፈን እንደሚቃወም ስለጻፈ ብቻ ከሻእብያ ጋር ተጣልቷል ፤ ኢሳት ኤርትራ ውስጥ ስለሚደርሰው ሰቆቃ ሲዘግብ ሰምታችሁ ታቃላችሁ ? አይችልም ። አንዱ የሚረዳው ሻእቢያ እንደሆነ የዶክተር ብርሀኑን ድምጻቸውን ሰምተናል (የሚረዳው ሲባል ለድርጅቶች የሚገባው ገንዘብ መጀመሪያ ሻእብያ ላይ ነው ፣ ያኑ ገንዘብ ነው የሚስጣቸው እሱ የፈቀደውን እና እንዴት ነው ኢሳትስ አለቃየ ሻእብያ ይሄን በደል ሰራ ብሎ የሚናገረው ?)

ልብ ያለው ልብ ይበል ሻእብያ ወያኔ ቢጠላ ኢትዮጵያን ወደደ ማለት አይደለም ። ወያኔም እንደዛው ። ሻእብያ ትናንት ኢትዮጵያን የመቶ አመት የቤት ስራ ስጠሓት ብሎናል ። መቸም ቢሆን ኢትዮጵያን አይወድም ። አትልፉ ። ለምን አርበኞችና ግንቦት ሰባት አልታጠቁም ደምሒት ባጭር ጊዜ ካሥር ሺ በላይ ሰራዊት አለው ። ሁለቱ 500 የሚሆን ታጣዊ አላቸውን ? ይሄ ሆን ተብሎ በሳይካተሪስቶች የኢትዬጵያን ህዝብ ለዛላለሙ ልቡን ለመሥበር የተቀየሰ መንገድ ነው ። እንዴት እንደሚሆን ወደፊት የምናየው ነው ።

ባሁኑ ስዐት ሻእቢያ ሀገር ያለው ነገር ፡ ወያኔ ኦሕዴድና ብአዴን ብሎ እንዳስቀመጣቸው ያሉ በደምሕት ስር ቅጥረኛ ሆነው ሊገቡ ያሰፈሰፉ ናቸው ። እነሱ የሚሉት ወያኔ ይውደቅ እንጅ ነው ፤ እውነታው ወታደራዊ መንግስት ሆኖ ነው የሚመጣው ከዚያ ቡሃላ ትግራይና ኤርትሬ “ፒስ” በሚል ቅኝ ግዛት ውስጥ ለዘላለሙ ትወድቃለህ ።

ግንቦቴዎችን ለመቃወም ምንም አልፈራም ምክኒያቱም አሥመራ የሚያሥገርፉት ኢትዮጵያውያንን ነው በተለይ አማራውን ፤ ድርጅቱ ለይሥሙላ ያማራ ነው ተብሏል ። ግንቦት ሰባት NAIVE ነው ፤ ዋለልኝ ከግንቦት ሰባት በጣም በጣም ላማራዎች ይሻላቸዋል ብየ እላላሁ ።ግንቦት ሰባት ከማንም ድርጅት ሲነጋገር ተሰምቶ አይታወቅም ከ FIRST OROMOዎች ጋር ብቻ እንጅ ። ከሌሎች ጋር መነጋገር የማይችሉበት ምክኒያት መሰረት ሥለሌላቸው ብቻቸውን በሜድያ ህዝብ አታለው መያዝ ስለሚፈልጉ ብቻ ነው ።ግንቦቴዎች የትም እንደማይደርሱ እስረግጬ ስነግራችሁ ህብረትሰቡን ግን ላንዴና ለመጨርሻ ጊዜ ኢትዮጵያዊ የሚባል ድርጅትን እርግፍ አድርጎ ተስፋ እንዲቆርጥ ያደርገዋል ።የሻእብያን ግንቦቴዎች ማሸነፍ የምንችለው ሜድያ ሲኖረንና አስመራ የሚሰራውን ግፍ ማጋለጥ ስንችል ብቻ ነው ።

Image
በ15 ከተሞች በተመሳሳይ ሰዓት ሰልፎች ይደረጋሉ :: የ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ያወጣውን ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩን ዛሬ ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓ.ም ይፋ አድርጓል፡፡ ትብብሩ የመጀመሪያ ዙር መርሃ ግብሩን በህዳር ወር በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ማከናወኑ የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለተኛ ዙር መርሃ ግብሩ ደግሞ ለ2 ወራት የሚቆይ እንደሚሆን ተገልጹዋል፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የትብብሩ አመራሮች በሰማያዊ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት በሁለተኛ ዙር የትብብሩ መርሃ ግብር መሰረት የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት በ15 የሀገሪቱ ትላልቅ ከተሞች ላይ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፎች ይደረጋሉ፤ በአዲስ አበባ፣ በሀዋሳ፣ በባህር ዳርና በአዳማ ደግሞ ህዝባዊ ስብሰባዎች እንደሚደረጉ የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነት (ኢ/ር) በመግለጫው ወቅት ተናግረዋል፡፡

‹‹የመግባቢያ ሰነዳችንና የጥናት ሪፖርታችንን እንዲሁም ከመጀመሪያው ዙር ያገኘውን ተሞክሮ በሠረት በማድረግ ይህን የሁለተኛ ዙር የሁለት ወር ዕቅድ (ከታህሳስ 16 እስከ የካቲት 15 /2007) አውጥቶ በቀዳሚነት ለዋነኛ ባለቤቶቹና ፈጻሚዎቹ ኢትዮጵያዊያን ሲያቀርብ እንደመጀመሪያው ዙር ከጎኑ እንደሚቆሙ ሙሉ እምነት በማሳደር ነው›› ያለው መግለጫው፣ በትብብሩ በኩል በአመራር ከፊት ቆመው ትግሉን ለመምራት ዝግጁነትና ቁርጠኝነት መኖሩን አስረድተዋል፡፡

‹‹የያዝነው የትግል መንገድ ሠላማዊና ህገ-መንግሥታዊ ብቻና ብቻ፣ መጓጓዣችን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ መድረሻችን መድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ እንዲሁም በጉዞኣችን ላይ የቱንም ያህል አረመኔያዊ የኃይል እርምጃ ይወሰድብን፣ ትግሉ የቱንም ዓይነት ዋጋና መስዋዕትነት ይጠይቅ ከጅምሩ ያለመስዋዕትነት ድል የለም ብለን ተነስተናልና ከያዝነው ዓላማ ኢንች የማናፈገፍግና ለቃላችን በጽናት የምንቆም መሆኑን ዳግም እናረጋግጣለን›› ብሏል ትብብሩ በመግለጫው፡፡

እቅዱ የመጀመሪያው ዙር ቀጣይ መሆኑን ያተተው የትብብሩ መግለጫ፣ ‹‹ዓላማችን የምርጫ ሁኔታዎች ባልተሟሉበትና የመራጩ ህዝብ ነጻነት በሌለበት ስለምርጫ መናገር አስቸጋሪ ነው፣ እነዚህ በሌሉበት አማራጭ የምርጫ ኃሳቦች በህዝብ ውስጥ ሊንሸራሸሩም ሆነ አማራጭ ኃሳባችንን ከህዝብ ማድረስ አይቻልም፣ ሚናችንም የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው አማራጭ ሆኖ መቅረብ ሣይሆን የህወኃት/ኢህአዴግ አጃቢነትና የሀገር ሃብት በአላስፈላጊ መንገድ የማባከን ሥራ ተባባሪነት የዘለለ አይሆንም ከሚል የመነጨ ነው›› ሲል አቋሙን አሳውቋል፡፡ ነጻነት በሌለበት ተጨባጭ ሁኔታ ምርጫ ቧልት ነው ሲልም አክሏል መግለጫው፡፡

ሁለተኛ ዙር ፕሮግራም ዕቅዱ እንደባለፈው ተደጋጋፊ፣ ተመጋጋቢና ተከታታይ ሦስት ዋና ዋና ተግባራትና በሥራቸው አስራ አራት ዝርዝር ተግባራት ማካተቱም ተመልክቷል፡፡ እነዚህ በትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ጥልቅና ዝርዝር ውይይት ተደርጎባቸው የጸደቁ ዋና ዋና ተግባራትም፡-
1. የአባላትና የትብብሩ አቅም ግንባታ፡- የትብብሩን አባላት አብሮነት ማጠናከርና የጋራ ዓላማውን የማስፈጸም አቅም ማጎልበት፤
2. የህዝብ ግንኙነት ተግባራት፡- የህዝብ ተደራሽነት ማስፋትና ዓላማ ማስተዋወቅ፣
3. የህዝብ ንቅናቄ መድረኮች ማመቻቸት፡- በአዲስ አበባና የተመረጡ ከተሞች አራት የአዳራሽ/አደባባይ የህዝብ ውይይት፤ በአዲስ አበባና በተመረጡ አስራ አምስት የክልል ከተሞች በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን፤ የሚያጠቃልሉ ናቸው፡፡

የትብብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ተግባራቱን በጊዜ ሠሌዳ በማስቀመጥ ለነዚህ ተግባራት ማስፈጸሚያ የብር 1,215, 000.00 (አንድ ሚሊየን ሁለት መቶ አስራ አምስት ሺህ ) በጀት ማጽደቁንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ትብብሩ ለያዘው ሠላማዊና ህገ-መንግሥታዊ የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ትግል በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ ሌሎች ትብብሩን ያልተቀላቀሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ትብብሩን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡

የተቃዋሚዎች አዳዲስ የትግል ስትራቴጂ የኢሕአዴግ ስጋት ሆኗል::

– ዲያስፖራውን በድሪቶ ወሬዎች መጥለፍ ስራችን ሊሆን ይገባል::ብለዋል – በደቡብ ሱዳን አሶሳን አስታኮ እየተፈጠረ ያለ ችግር መኖሩን አንስተው ተወያይተዋል:: – በአሶሳ የኦነግ ሰራዊት ነኝ ያለ ቡድን ካለቶክስ እጁን ሰቷል ሲሉ ተደምጠዋል:: – በድርጅታችን ቢዝነሶች ላይ የሚጠሩ ባይኮቶችን የሚያደናቅፉ የተቃዋሚ ዲያስፖራዎችን ከበፊቱ በበለጠ መልኩ መተባበር እና አስፈላጊውን እርዳታ ማድረግ እንዳለባቸው ተወያይተዋል::

Minilik Salsawi
ከፍተኛ የወያኔው ቱባ ባለስልጣናት እና የደህንነት ሃላፊዎች በመጪው የአገዛዝ ሂደታቸው ላይ ተገናኝተው መወያየታቸው ከውስጥ አዋቂ ምንጮች የተገኘ ዘገባ ጠቁሟል:: በአፍሪካ ጎዳና ቦሌ መስመር ከሚገኝ ለባለስልጣናት ብቻ ክፍት ከሆነ የጎልፍ መጫወቻ ክለብ ውስጥ ተጠራርተው የተሰበሰቡት ባለስልጣናቱ የተቃዋሚዎች አዳዲስ እና ስልታዊ ስትራቴጂ እንዳሳሰባቸው እና የትግል ስልቱ ስጋት እንደሆናቸው በውይይታቸው አስቀምጠዋል::

በኤርትራ በኩል ያለውን እንቅስቃሴ መምታት ያስፈልጋል አያስፈልግም በሚለው ዙሪያ የተነጋገሩ ቢሆንም ለጊዜው እሱ ይቆይ እና በአሁን ሰአት ስጋት የሆነው የተቃዋሚዎች አዳዲስ የትግል ስልት እና የዲያስፖራው ከስልቱ ጋር መቀናጀት ስለሆነ ይህንን በፍጥነት በፕሮፓጋዳ እና በተግባር እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል ሲሉ ተደምጠዋል::በድርጅታን ውስጥ የተሰገሰጉትን ተመሳስለው መረጃ የሚያቀብሉ እና የተቃዋሚውን እንቅስቃሴ የሚያበረታቱት የሚተረጠሩ ሁሉ ክትትል እየተደረገባቸው እንዲያዙ በሚለው የተስማሙ ሲሆን ከምርጫው በፊት እንደሁኔታው ታይቶ በሙስና እና የሃገርን ሰነድ በማባከን እንዲከሰሱ እንዲሁም አሸባሪ እየተባሉ የሚከሰሱ ሰዎች እንዲቀንሱ እና በሌላ የወንጀል ህግ አንቀጽ እንዲከሰሱ ያሉ ሲሆን አሸባሪ እያሉ መክሰስ ተቃውሞ እንዳበረከተ እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ የአሸባሪነት ክስ እንዲቀርብ ተነጋግረዋል::የሃገሪት ፖሊስ በተለይ ፌዴራል ፖሊስ ከበፊቱ በተሻለ መልኩ ጥቅማጥቅም እና መብቶች እንዲሰጡት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ላይ እንዳይላላ ያደርገዋል ሲሉ ተደምጠዋል::

በደቡብ ሱዳን በኩል አንዳንድ ሃይሎች እየተፈጠሩ ስለሆነ ከመበራከታቸው እና ከመጠናከራቸው በፊት በአከባቢው ጥብቅ ቁጥጥር መደረግ እንዳለበት እና ባለፉት ወራቶች በቆረጣ እና በመረጃ ስብስብ የታገዘ እርምጃ በኦነግ ታጣቂዎች ላይ እንደተወሰደ ሳይጠቅሱ አላለፉም::የኤርትራ ፓስፖርት ይዘው በኡጋንዳ በማድርግ ወደ ደቡብ ሱዳን ዘልቀው በመግባት አሶሳ መስመር ላይ ስለላ ሲያካሂዱ የነበሩ ግለሰቦች የተያዙ ሲሆን ወርቁ የተባለ የኦነግ አባል የሆነ እና የዐኦ ዳውድ የቀድሞ ሹፌር ሊያመልጥ እንደቻለ ታውቋል::እጁን የሰጠው ቡድን ከኤርትራ ተደራጅቶ ይምጣ አሊያም እዛው ደቡብ ሱዳን ውስጥ ይደራጅ ጉዳዩ እየተጣራ መሆኑን የደህንነት ሃላፊዎቹ አስረድተዋል::

ዲያስፖራው አሁንም የኢሕአዴግ የእግር እሳት እንደሆነ በሚያስታውቅ ሁኔታ ጥልቅ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ዲያስፖራው በብዛት የድህረገጽ ተጠዋሚ ስለሆነ በድሪቶ ወሬዎች መጥለፍ ዋና ስራ እንዲሁም በውጪ የሚገኙ የተቃዋሚ አባላትን በተለያየ ጥቅማ ጥቅም በመደለል አስፈላጊ መረጃ ማሰባሰብ ሲሉ ውጪ አግር በሚገኙ የድርጅታችን የንግድ ስራዎች ላይ እንከን እንዳይፈጠር ባይኮት እንዳይጠራ አስታውጾ እያደረጉ እና ለሚተባበሩን የተቃዋሚ ዲያስፖራዎች አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ ማድረግ አለብን ሲሉ ተደምጠዋል::በማለት የውስጥ አዋቂ ምንጮች መረጃቸውን አድርሰውኛል::

(ቢልልኝ ሀብታሙ አባቡ) አንድ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሆነ ሔሊኮፕተር ተጠልፎ በኤርትራ ምድር ማረፉ በዚህ ሳምንት ተሰምቷል፡፡ የጠለፋውን አጠቃላይ አገራዊና አለም አቀፋዊ እንድምታ ለማየት ድርጊቱ ከግለሰቡ ስሜት የሚመነጭ ተራ የዜጋ ክህደት ነው ወይስ በአገራቱ መካከል በተፈጠረ መሻከር የተነሳ የፖለቲካ ትግላቸው አንድ አካል የሚለውን ለይቶ ማስቀመጥ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት በቅድሚያ የድርጊቱ ምንጭ ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን ጥያቄ መመለሱ ጠቃሚ ነው፡፡ የድርጊቱን መነሻ ለማወቅ ፓይለቱ ለድርጊቱ ያነሳሳው የራሱ የግለሰቡ ተራ የሆነ የግለሰብ ስሜት ነው ወይስ ከጀርባው የተለየ ተልዕኮ አለ የሚሉትን ሁለት መነሻዎች ለይቶ ማጥናት ያስፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት ከሁለቱ አንዱን መምረጥ የሚያስችሉ የአሳብ መነሻዎችን ማየት ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ለዚህ ዋናው መነሻ ግለሰቡ ከሌሎች አገሮች ኤርትራን ለመድረሻ የመረጠበት ምክንያት እና ግለሰቡ የኤርትራን ድንበር አቋርጦ ሲሄድ በሰላም መስተናገዱ ምንአልባት ግለሰቡ በጉዳዩ ዙሪያ ከኤርትራ መንግስት ጋር ረዘም ላለ ጊዜ በድብቅ ሲሰራ እንደቆየ ሊያመላክት ይችላል፡፡ የኤርትራ መንግስት እንደጠላት ከሚያያት አገር የጦር ሄሊኮፍተር ድንበሩን አቋርጦ ሲገባ የአፀፋ ምላሽ አለመስጠቱ አስመራው አስተዳደር ድርጊቱ እንደሚፈጸም ቀደም ብሎ ያውቅ እንደነበረ ሊያመላክት ይችላል፡፡ እነደዚህ ከሆነ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት ጠላት ያለው በራሱ ጉያ እንጂ በሚሊየን ኪሎሜትር ርቀት ላይ እንዳልሆነ ያመላክታል፡፡ የተጠናከረውን የኢትዮጵያ መንግስት ደህንነት አልፎ ተልዕኮውን ማሳካቱ የኤርትራ መንግስት በጉዳዩ ላይ ለረጅም ጊዜ ሲሰራበት የቆየ ተልዕኮ እንዳልቀረ ያመላክታል፡፡ የኢትጵያ መንግስት ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል? በዋናነት ውድ ዋጋ ያለው ሀብት በመወሰዱ ሳይሆን በሁለቱ አገራት […]

ልማታዊው ቀልድ
————————
–ኢትዮጵያ ውስጥ አንዲት ሴት … አንዱን
ወንድ “3500 ብር
ሰረቀኝ ” ብላ ትከሰዋልች :: ተከሳሹም
ፍርድ ቤት ቀርቦ የተባለውን ገንዘብ መስረቁን
ያምናል ::
የሰረቀበትን ምክንያትም ሲያስረዳ ደግሞ
“3500ቱ ብር ላይ ከራሴ 1500 ብር
ጨምሬበት … የአባይ
ግድብ ቦንድ ገዛሁበት ” ብሎ ያስረዳል ::
የህንን የሰሙት ‘”ልማታዊ ” ዳኛ …አንተ
“ልማታዊ ሌባ “
ስለሆንክ … በነጻ ተለቀሀል … ከሳሽህ
ደግሞ “የልማት አደናቃፊ ” ስለሆነች
እንድትታሰር ወስነናል ‘
ብለው “ልማታዊ ” ውሳኔአቸውን አሰሙ::

አስደንጋጭ መረጃከአስገደ ገ/ስላሴ
35 ሺ ኢትዮዽያውያን እስረኞች በኢርትራ ሳህል በረሃ ዘመኑ ያለፈው የባርያ አገዛዝ እየተፈፀመባቸው ይገኛሉ::
የሻዕብያ የሽፍታ መንግስት በ1983 ዓ/ም ከደርግ ጋር በነበረ ጦርነት የተማረኩ ወጣት ወታደሮች ስቪል የመንግስት ሰራኞች በዛን ጊዜ ኢርትራ ላይ ይኖሩ የነበሩ ወጣት ዜጎች በሙያ የተካኑና ለስራው ያስፈልጉኛል ብሎ በመለየት ከ 36 ሺ በላይ በሳህል በረሃዎች በዓፍዓበት በናቅፋ በሰሜን መሰራቅ ሳህል ወስዶ በሃይልና ከባድ ስራ ያሰራቸው ነበር::
በኢትዮ ኢርትትራ ጦርነት ዋዜማ በሁሉም የኢርትራ ከተሞች የነበሩ ስቪል ሕብረተሰብና በሙያቸው ጦርነቱ ከተጀመረ እስከ ሻዕብያ የተሸነፈበት የማረካቸው ወታደሮችና ምልሻዎች ከኢርትራ ዘልቆ ወደ ትግራይ እየገባ ከ1990 እስከ 2007 ዓ/ም ለ17 ዓመት ያህል በብዙ ሺ የሚቆጠሩ የትግራይ የጎንደር ወጣቶች አፍሶ የወሰዳቸው::
በስራ አጥነት በድህነት በመልካም አስተዳደርና ነፃነት እጦት ወደ ሱዳን ስራ ፍለጋ ብሎም ወደ ሌላ ሃገር ለመሸጋገር የኦሮሞ የአማራ የትግራይ የጋንቤላ ወዘተ ሱዳን የገቡ የሻዕብያ ልዩ ሰላዮች ወደ ሱዳን ሰርገው በመግባት ከሚሰሩበት በረሃና ከተሞች በመጥለፍና በማፈን ወደ ወገኖቻቸው ሳህል አገቡዋቸው:: እነዚህ ግፍ ይፈፀምባቸው ያሉ ዜጎች ከ1983 ዓም እስከ ዛሬ በእሱር መልክ ተይዘው በሁሉም የሻዕቢያ አካባቢዎች በከባድ ስራ ተሰማርው ይሰሩ የነበሩ እስከ 60ሺ ይገመቱ እንደነበሩ የመረጃው ምንጮች ይናገራሉ:: አሁን ግን በሳሀል በረሃዎች በተጨባጭ የሚኖሩ 36ሺ ናቸው ይባላል ከዛም ሊበልጡ ይችላሉ የቀሩ ተገድለዋል፡፡
እነዚህ ዜጎች የሚሰሩትን ስራ በሳዋ በባርካ በሰሜን ምስራቅ ሳህል በዓፍዓበት በማይሕመት በአልጌን በናቅፋ በግዝግዝያ በከረን አካባቢና በሰሜን ባህር በፍልፍል ዓራቶ የሚባሉ ቦታዎችና በሌሎች ቦታዎች በተለያዩ ከባድ ስራዎች ያሰሩዋቸው ነበሩ በሚሰሩበት ጊዜ በከባድ ጥበቃ ነው:: ለሚደርሰው ግፍ የመቃወም ምልከት ያሳዩ ወገኖች በእሰረኞች ፊት ይረሸናሉ::
ሌላ አስገራሚ ነገር ደግሞ በኢትዮዽያ ሰላማዊ ትግል አይቻልም ኢህአደግ እሱ በመጣበት መንገድ በነፍጥ ነው የሚወገድ ብለው ከሻዕብያ ጋር ተጠግተው ከህወሓት ለሻዕብያ ከሞት ለማዳን ያደረገው ሎሌነት እነዚም ከህወሓት በባሰ መንገድ ሎሌ ሆኖው የኢሳያስ ቤተ መንገሰት የሚጠብቁ ኢሳያስ ተኩሱ ሲላቸው የሚተኩሱ ደፈጣ ተዋጊዎች በመቃወም ኢትዮዽያዊ ጥያቄ ያነሱ ሻዕብያ የሚጠረጥራቸው ኢርተራውያን ወደ ሱዳን በስደት የገቡ የቻድ የናይጀርያ ዜጎች ሳይቀሩ ከ35ሺ እሰረኞች ቀላቅለው የባርያ አገዛዝ ተቋዳሽ ናቸው:: የዚህ ሁሉ ሚስጢር ያወጡ ያሉ ከእሰረኞቹ አምለጠው ወደ ዓረብ ሃገር የገቡ ሰዎች ናቸው:: እስረኞቹ ከ 10 ዓመት በፊት መላው የኢርተራ የሻዕብያ ተቋማት የእረሻና የግድበ ስራዎች እሰከ ምሸግ መስራት የሚሰሩ ነበሩ:: ማምለጥ በመጀመራቸው ግን ወደ ሳህል አካባቢ እንዲሰበሰቡ ተደረጉ::
የሚሰሩት ስራ ሻዕብያ 30 ዓመት የተቀመጠበት የቀበሮ ጉድጓድ 180 ኪሎሚትር ርዘመት ያለው ምሸግ ማደስ ለቱሪዝም ተብሎ በአፍዓበት በናቅፋ ቤቶች መስራትና ማደስ በሰሜን ምሰራቅ ሳህል የሚገኙ ትላልቅና አነስተኛ ተፋሰሶች መገደብ የእረሻ ስራ መስራት በሳህል የሚገኘው የነ ኢሳያስ የመሬት ውሰጥ ቤተመንገስተ ማደስ:: ሻዕብያ ይጠቀምባቸው የነበረ መንገዶች ማደስ ስራ ይሰማራሉ::
በዜጎቻችን የሚፈፀም ግፍ ቀን ተሊት በጥበቃ ስር ናቸው:: በቂ መገብ ህከመና የላቸውም የማምለጥ አዝማሚያ ያሳዩ ዜጎች በሆነ መንገድ ይረሸናሉ:: ሆን ተብሎ የተመሳሳይ ፆታ ወሲብ እርሰ በራሳቸው እንዲፈፅሙ ይደረጋል:: በቂ ልበስ የላቸውም በከባድ ስራ በህመም በርሃብ ተመጣጣኝ ምገብ ባለማግኘታቸው የወደቁ እንደልገመኞች ተቆጥረው ይረሸናሉ::
በአጠቃላይ በጨለማ የሚኖሩ ተስፋ የቆረጡ መሆናቸው ይገለጣል:: ታድያ የኢህአደግ መንገሰተና የሱ መዋቅሮች የሃገር መከላከያ ሚኒስቴር የደህንነት ጀነራሎች የደህንነት ባለስልጣናትና ሰላየቹ ምን እያደጉ ናቸው:: ከ35ሺ በላይ ዜጎቹ በበረሃ በአንድ ሽፈታ ስርዓት ሲሰቃዩ 23 ዓመት ሙሉ ምን እያደረጉ ናቸው:: እንደእሰራኤል ያሉ መንገሰታት እኮ ዜጎቿ በሓማስ ታጋዮች ሲጠለፉ ከባድ ጦርነት ተካሄደ ነገር ግን ኢስራኤል ወታደር ጂልዓድ ሸሊም ነፃ ለማውጣት ኋላ ግን በኢስራኤልና ከሓማስ በተደረው ስምምነት ኢስራኤል 3ሺ የፈለስጢም እስረኞች እንድትፈታና በጂልዓድ ሸሊም በዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል አማካይነት የእሰረኞች ልውውጥ ተደርጎ ነው ነገሩ የተፈታው::
የኢህአደግ መሪዎች ግን በአስር ሺ የሚቆጠሩ ዜጎቹ የባርያ አገዛዝ እየተፈፀመባቸው ደሮ የታፈነችባቸው አይመስሉም:: በቀላሉ እንኳ በምሽግ ያለው የሻዕብያ ሰራዊት በመተራመስ በ10ሺ የሚቆጠር ወታደር ማርኮ ተደራድሮ ማስወገድ ነበረበት:: በዚሁ የሻዕብያ ሽፍታ መንግስት ግፍ የኢርትራ ህዝብም ደስተኛ አይደለም::
ሌላ ይህ የሻዕብያ የሽፍታ መንግስት የሚፈፅመው ያለ ግፍ በዓለም መንግስታት በሰብአዊ መብት ተሟጓቾች ኢህአደግ ተፅኖ ለማድረግ ይችል ነበር:: ነገር ግን ምኑም አይደለም የትግራይ ክልል መሪዎች በወልቃይት ወርቅ ሲለቅሙ ከ280 በላይ ወጣቶች ታፍሰው ሳህል ሲገቡ እያወቀ ስለእነሱ ሲጠየቅ ውሸት ነው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ያስፋፉት ወሬ ነው አሉ::
ሌላ በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስለእነዚህ ዜጎች እንደአጀንዳ ይዘው አያነሱትም:: በመጨረሻ መላው የሃገራችን ህዝብ ሙሁራኖች ተማሪዎች በውጭ የምትገኙ ዜጎች ይህ በሻዕብያ የዜጎቻችን ይፈፅመው ያለው ግፍና የህወሓትት ኢህአደግ መሪዎች ለዜጎቻቸው አለመቆርቆር ተቃውሞ በማስነሳት ተፅእኖ ሊታደርጉ ዘንድ ጥሪ አቀርባለሁ:: በተጨማሪም ለተባበሩ መንግስታት ለሰብአዊ መብት ተሟጓቾች በዲፕሎማሲ ፅኖ በማድረግ ስለዜጎች እንስራ ሚስጢሩም መላው ዓለም ይወቀው::

(ቃለየሱስ በቀለ) የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡ ከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡ አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡  ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን […]

የአማራ ክልል ባለስልጣናት የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ በባህርዳሩ ግዮን ሆቴል ላይ ያለውን የባለቤትነት መብት እስካሁን ማስከበር አልቻሉም፡፡

ታኀሳስ ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፌደራል ፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ተረክቦ ቦታውን ለልማት ለማዋል ዝግጅት የጀመረው የክልሉ የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ ሆቴሉን ነጻ ለማድረግ ከህዳር 15 ቀን ጀምሮ አገልግሎቱን እንዲያቋርጥ እና በውስጡ ያሉትን የግለሰብ ንብረቶች ለማስወጣት ያደረገው እንቅስቃሴ ለአንድ ወር ያህል አለመሳካቱን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ኤጀንሲው በቁጥር ኮቤልኤ-ዋሥ/32/1108 በቀን 16/ 03/07ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ በግቢው ውስጥ የሚገኙትን የግለሰብ ንብረቶች ከ15/03/07 ዓ.ም ጀምሮ በህጋዊ መንገድ እንዲያወጡ በመጠየቅ፣ ንብረቱ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ የማያወጡ ከሆነ በቤቱና በግቢው ውስጥ ለቆዩበት ጊዜ ሁሉ በቀን ሃያ ሽህ ብር እና ሌሎች ኪሳራዎችን የቤቱ ባለቤት የሆነው የክልሉ መንግስት ተወካይ የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ የሚያስከፍል መሆኑን በመግለጽ ንብረቱ እንዲነሳ በመጠየቅ ሆቴሉን አሽጎ ሰራተኞችን መበተኑ ታውቋል፡፡

ለአስራ አምስት ቀናት ቢጠብቅም ምንም ውጤት ያላየው ኤጀንሲ በ01/04/07 ዓ.ም ባወጣው ድጋሚ ደብዳቤ « መንግስት በቦታው ላይ ያቀደውን የልማት ስራ እርስዎ ንብረትዎትን ባለማውጣትዎ ምክንያት ሊያቆም ስለማይገባ በግቢው ውስጥ ያለውን ንብረት ወደ አንድ ቦታ በማሰባሰብ የልማት ስራውን ለማስቀጠል ስላስፈለገ እቃው በሚሰባሰብበት ወቅት በእርስዎ በኩል በታዛቢነት የሚኖር ሰው ሰኞ ታህሳስ 8ቀን 2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ሆቴሉ መግቢያ በር እንዲገኝ እያሳሰብን የእርስዎ ተወካይ ወይም ታዛቢ ባይገኝ ሌሎች ታዛቢዎች በተገኙበት በግቢው ውስጥ ያለውን ዕቃ ወደ አንድ ክፍል የሚያሰባሰብ መሆኑን እየገልጽን መንግስት ይህንን እና ሌሎች ለስራው የሚያስፈልጉ ወጭዎችን ቀደም ሲል በተሰጠዎ ማስጠንቀቂያ መሰረት ከእርስዎ እንደሚጠበቅ አንዲያውቁት እናሳስባለን፡፡” ብሎአል።

በባህርዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት የአቶ መለስ ዜናዊ የቅርብ ዘመድ አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከ900 መቶ ሺህ ብር በላይ እንዳያገኝ ያደረገ ታክሰ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ወልዱና ቤተሰቡ ኃላፊነት የተወሰነ የግል ማህበር በእስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የምዕራብ ጎጃም ዞን የባህርዳር ምድብ ችሎት ውሳኔ ማስተላለፉን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የውሳኔ መዛግብት ዋቢ በማድረግ መዘገባችን ይታወሳል።

የምዕራብ ጎጃም ፍርድ ቤት ባህርዳር ምድብ ችሎት ወልዱና ቤተሰቡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ እና አቶ ብስራት ወልዱ ወልዳረጋይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብስቦ ያለማሳወቅና ያለመክፈል እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ባልሆነ ደረሰኝ ግብይት በማካሔድ ወንጀል በአመት ስድስት ነጥብ ሶስት ሚልዩን ብር መሰብሰባቸው መጠቀሱንና ከዚህም ለመንግስት መግባት የነበረበት ከስድስት መቶ ሺ ብር በላይ ለግል ጥቀማቸው አውለዋል በማለት ተከሳሽ ወልዱ ወልዳረጋይ በ7 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ አንደኛ ተከሳሽ ወልዱና ቤተሰቡ ሀላፊነቱ የግል ማህበርን በተመለከተ በህገ-ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በመሆኑ በወንጀል ህግ አንቀፅ 90/3 መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብስቦ ያለማሳወቅ፣ ያለመክፈል ወንጀልና ግብር ለመንግስት ያለመክፈል ወንጀል ክሶች እያንዳንዳቸው የብር 10 ሽህ መነሻ ቅጣት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ባልሆነ የደረሰኝ ግብይት ማካሔድ ወንጀል ክስ ደግሞ ብር 5 ሺህ ባጠቃላይ 25 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጫ እንዲከፍሉ ውሳኔ መተላለፉን ዘግበናል፡የባህርዳር ነዋሪዎች በድርጅቱና በልጅቻው ላይ የተሰጠውን ውሳኔ ቀልድ ነው ማለታቸውም ይታወሳል ፡፡

ከ10 ቀን በፊት ከባህር ዳር ማረሚያ ቤት ከገዢው መንግስት ባለስልጣናት በተሰጠ ቀጭን ትዕዛዝ የእስር ጊዜያቸውን ሳያጠናቅቁ ሳይሆን ሳይጀምሩ የተፈቱት አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ ፣ ኤጀንሲው በሰጠው ማስጠንቀቂያ መሰረት ንብረታቸውን ያላነሱ ሲሆን በኤጀንሲው ውሳኔ መሰረት ንብረታቸውን ላላነሱበትና ልማቱን ላደናቀፉበት 30 ቀናት ከ600 ሽህ ብር በላይ እንደሚጠበቅባቸው ምንጮች ገልጸዋል፡፡፡የባህርዳሩ ግዮን ሆቴልን ለረዢም አመታት በአምስት ሽህ ብር የክራይ ዋጋ ሲጠቀሙበት የነበሩት አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ ኤጀንሲው እንዲከፍሉ የወሰነባቸውን ገንዘብ መክፈል ሳይሆን በሌሉበት እና በህግ ጥላ ስር እያሉ በማናለብኝነት ሆቴሉ በመዘጋቱና ሰራተኞችንም በመበተኑ ላደረሰባቸው ኪሳራ የክልሉን የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲን በህግ ለመጠየቅ ከጠበቆቻቸው ጋር እየተመካከሩ መሆኑን እማኞች ለዘጋቢያችን ገልጸዋል፡፡

አቶ ወልዱ ግዮን ሆቴልን የሚያክል ድርጅት የአቶ መለስ ዜናዊ ዘመድ በመሆናቸውና በትጥቅ ትግሉ ወቅት መረጃ በማቀበል ላገለገሉበት እንደውለታ ተቆርጦላቸው እጅግ እርካሽ በሆነ መንገድ በሆቴሉ ከ20 አመታት በላይ ሲጠቀሙበት መቆየታቸው በክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ቅሬታ ያስነሳ ጉዳይ ሆኖ ቆይቷል። አሁንም ባለስልጣናት ደፍረው የፍርድ ቤት ትእዛዝ ለማስፈጸም እንዳልቻሉ ታውቋል።

ሰዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብት አላቸው::የህዝቦችን ነጻነት መጋፋት ጋዜጠኛ አያሰኝም::
ጥፋተኛው የኢሳት ኢዲቶሪያል ሳይሆን የጥቂት ግለሰቦች የማናለብኝነት እና በስሜት የመነዳት ፖለቲካ ነው:: አዎን ምናልባት አንዳንዶች በልቅ የፖለቲካ ስድነት ያሸበረቁ ግለሰቦች ስማቸውን የቀያየሩ ሰውን በየድህረገጹ የሚዘልፉ የኢሳት ጋዜጠኞች ይህ ጽሁፍ ላይመቻቸው ይችላል::

ኢሳት ገና ከጅምሩ ሲመሰረት ህዝባዊ አላማ አንግቦ እና ህዝባዊ ስራዎችን ለመስራት እንደተቋቋመ የማይካድ ሃቅ ነው::ኢሳት የሰራቸው በጎ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው እጅግ ሊሻሻሉ እና ሊታረሙ የሚገባቸው ጥፋቶችም በገሃድ አይተናል እያየን ነው::አብዛኛው ጥፋቶች የሚከሰቱት ዲሲ ከሚገኘው እና የግንቦት ሰባት አመራሮች በስሜት ፖለቲካቸው ከሚነዱት ስቱዲዮ መሆኑን ስንመለከት ደሞ ራሳችንን እንድንጠይቅ አድርጎናል::

ለኢሳት ስኬት አስፈላጊውን አስታውጾ እና ድጋፍ እስካደረኩ ድረስ የኢሳት ጉዳይ ያገባኛል ይመለከተኛል:: አንዳንድ ኢሳት የነሱ ብቻ የሚመስላቸው አዋቃጭ ግለሰቦች በደመነብስ የሚናገሩትን አልባሌ ቦለቲካቸውን ወደ ጎን በመተው ኢሳት ሊጠናከር የሚችለው ያለበትን ሲያርም እና በውስጡ የተወሸቁ ስሜታዊ እና ልቅ ጋዜተኞችን ሃይ ማለት ሲችል ብቻ ነው::አንድ ሳው አስተያየት በሰጠ ሰአት ሁሉ እየተነሱ የኒዛለፉ እና የሚሳደቡ ባለጌ ጋዜጠኞች እና አዋቃጭ ተባባሪዎቻቸውን ሊያርማቸው ይገባል::ጥላቻን ማራመድ በቀረበት በዚህ ስልጡን ዘመን ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያውያን ላይ ጥላቻ እንዲያራምዱ የሃገር ጉዳይ ተረስቶ ግለሰቦች እንዲዘረጠጡ በተራ አሉባልታ እና የስድብ ናዳ ጊዜ እንዲጠፋ የሚያደርጉ ሰዎችን ታቅፎ መጓዝ ከተጠያቂነት አያድንም::

የኢሳት ጋዜጠኞች በሃገር ውስጥ እና በውጪ ሃገር የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶችን ወደ አንድነት እና የጋራ አጀንዳ እንዲመጡ መስራት ሲገባቸው እየከፋፈሉ የህዝብ የለውጥ ጥያቄ እና የነጻነት ጥማት እንዲዘገይ አድርገዋል::በሃገር ቤት የሚገኙ ፓርቲዎችን አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ በማደረግ በየፕሮግራሞቻቸው እኩልነትን ባላስተናገደ መልኩ በመዝለፍ እጅግ አሳፋሪ የሆነ የጋዜጠኝነት ስራ ስውርተዋል::በስሜት የሚነዱ ጥቂቶች የህዝብ ቤት ይሆናል የተባለውን ኢሳትን የራሳቸው የስሜት ሃሳብ መጋለቢያ አድርገውታል::በውጪ ሃገር የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶችን በማግለል የአንድ የፖለቲካ ድርጅት ስም ገኖ እንዲወጣ ተግተው ሲሰሩ በተግባር እያየን ነው::ስለዚህ ኢሳት የኔ ነው እስካልን ድረስ የኢሳት ጉዳይ ይመለከተናል እንዲታረምም ሂስ የመስጠት መብታችን የተጠብቀ ነው::ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ብዙ ማለት ይቻል ነበር ግን የኢሳት ቦርድ ሁኔታውን አይቶ ሊያስተካክል ይገባል::
Image

መታሰር ክፉ ነው፡፡ የታሰረ ሰው ተስፋው ሁሉ ውጪ በቀረው ታጋይ ላይ ነው፡፡ የሀብታሙ አያሌው እና የየሺዋስ አሰፋ ልብ የሚነካ ተማፅኖ አእምሮዬን ሁሉ ተቆጣጥሮታል፡፡ ‹‹እባካችሁ ተባበሩ›› ‹‹እስቲ ቀረብ ብላችሁ ተነጋገሩ›› በየንግግራቸው መሀል እየደጋገሙ የሚያስተላልፉት መልዕክት ነው፡፡ ‹‹እኛ እኮ ከዛሬ ነገ ለውጥ መጥቶ ኑ ውጡ እንባላለን ብለን ነው የምንጠብቀው……በተናጠል ድርጅቶች ያላቸውን አቅም የምናውቀው ነው….እባካችሁ ተባበሩ›› ሀብታሙ አያሌው፡፡
አንድነት እና ሰማያዊ በትብብሩ ውስጥ አብረው መስራት ለምን አይችሉም???
አብረው መስራት የማይችሉበት ምንም ምክንያት ፈልጌ ላገኝ አልቻልኩም፡፡ ከሁለቱም በኩል በቀና እና ለውጥ ፈላጊ ልቦና ተቀራርቦ መነጋገር ከተቻለ የሚያግዳቸው ምንም ነገር አይኖርም፡፡ ሀብታሙ አያሌው እና የሺዋስ አሰፋ ቂሊንጦ ሲገቡ ተግባብተዋል፡፡ እኛም ነገ ቂሊንጦ ከገባን መግባባታችን አይቀርም፡፡ ከዛም እንደ የሺዋስ እና ሀብታሙ ውጪ ያለውን ሰው ተባበሩ እያልን እንመክራለን፡፡ በተስፋ ምግብም መንፈሳችንን በሂወት ለማቆየት እንጥራለን…..ከንቱ ልፋት፡፡
ወህኒ ሳንወርድ አሁን ላይ መግባባት ስለምን ይሳነናል???
አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ አንድነት እና ሰማያዊ በትግል ስልታቸው ላይ መጠነኛ ልዩነት ያላቸው ይመስላል፡፡ ነገር ግን እንዲህ አይነት መጠነኛ ልዩነት አይደልም በሁለት ፓርቲ መሀል ይቅርና በአንድ ፓርቲ ውስጥም ባሉ ግለሰቦች መሀል የሚከሰት ነው፡፡ አንድነት ያለምንም ቅድመ ሁናቴ ምርጫ ውስጥ እገባለሁ ብሏል፤ ሰማያዊ ደግሞ ቅድመሁናቴ አስቀጧል፡፡ ነገር ግን ከምርጫ ሂደት ውስጥ ወጥቻለሁ ያለ የለም፡፡ በመሆኑም ምርጫውን ያለቅድመ ሁናቴ የሚሳተፈውና ቅድመሁናቴ ያስቀመጠው አካል የምርጫ ምህዳሩን ለማስፋት፤ ምርጫው አልሆን ካለ ደግሞ ለህዝባዊ እምቢተኝነት ተባብረው የማይሰሩበት ምክንያት አይታየኝም፡፡
አንድነት ወደ ትብብሩ ያልመጣበት ምክንያት ከመድረክ ከወጣሁ በኋላ እንደገና ያለጥናት በፍጥነት ወደ ሌላ ትብብር ውስጥ መግባት የለብኝም የሚል ነው፡፡ ነገር ግን አንድነት ፓርቲ ውህደት ከሆነ በማንኛውም ጊዜ ዝግጁ ነኝ ይላል፡፡ ለመዋሀድ ዝግጁ የሆነ አካል ደግሞ ለመተባበር ይከብደዋል ብዬ ማሰብ ያቅተኛል፡፡ በመሆኑም ለመተባበር ዛሬ ነገ ሳይል ቢወስን ደስ ይለኛል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ትብብሩ ውስጥ ያሉት ፓርቲዎች ግማሽ መንገድ ሄደው አንድነትን መቀበል አለባቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ አንድነት ካለው ድርጅታዊ አቅም አንፃር ታይቶ የትብብሩ ምክር ቤት አባል ብቻ ሳይሆን የትብብሩ ስራ አስፈፃሚም ውስጥ ተወካዩን እንዲያስገባ ሊፈቅዱለት ይገባል እላለሁ፡፡ ይህ ደግሞ ለአረናም ሆነ ለኦፌኮ የሚሰራ ይመስለኛል፡፡
በዚህ መልኩ ተባብረው የሚሰሩ ከሆኑ ምናልባትም አሁንም ቢሆን ጊዜው አረፈደም እና ሁሉም ፓርቲዎች በስምምነት በአንዱ ፓርቲ የምርጫ ምልክት ሊወዳደሩ ይችላሉ፡፡ ይህ እንኳን ባይሆን በእጩ አቀራረብ ላይ እየተመካከሩ ድምፅ የማይነጣጠቁበትን መንገድ መፈለግ ይችላሉ፡፡ ምርጫው ነፃ እስካልሆነ ድረስ አላስፈላጊ ነው ብለው ካሰቡም በጋራ ህዝቡን ለህዝባዊ እምቢተኝነት የሚያነቁበትን እና የሚያደራጁበትን መንገድ መፈለግ ይችላሉ፡፡
በቅርቡ አንድነት ፓርቲ በተለያዩ ክፍለሀገሮች ሰልፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ትብብሩም ሁለተኛ ዙር መርሀግብሩን አውጥቷል፡፡ እነዚህን ሁለት እንቅስቃሴዎች ማቀናጀት አስፈላጊ ነው፡፡ ለዚህም ከእንቅስቃሴዎቹ በፊት ፓርቲዎቹ አንዳች ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው፡፡
የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እኔም ሆንኩ ሌሎች ጓዶች መታሰራችን እንደማይቀር አውቀዋለሁ፡፡ እስር ቤት ከገባሁ በኋላ ግን ውጪ ያለውን አካል እንዲተባበር መለመንን አልሻም፡፡ ‹‹ቀን ሳለ ሩጥ›› እንዲሉ ዛሬ ውጪ እያለሁ ፓርቲዎቹ እንዲተባበሩ ሙሉ ጊዜየን ሰጥቼ እሰራለሁ፡፡ ሌሎችም እንዲሰሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
Image

ኢሳት የሚድያ ተቋም በበርካታ ሽህ ማይሎች ርቀት ላይ የሚገኝ ላገር ያስባል ተብሎ የተቋቋመ ድርጅት ነዉ፡፡እንደሚለዉ የኢትዮጵያዉያን አይንና ጀሮ ይሆናል ብለንም አስበን ነበር፡፡የኢድቶርያል ቦርዱን ፖሊሲ ብናዉቀዉ ደስ ባለን፡፡መስራቾች ብዙ ለፍተዉና ሩቅ አልመዉ እንዳቆሙት ይታመናል፡፡አንድነትን በፖሊሲ ደረጃ እየታገሉት ከሆነ ያሳዝናል፡፡የሁለትና ሶስት ጋዜጠኞች የግል ፍላጎትና ጨዋታ ከሆነም እናያለን፡፡
Image
እንዳለመታደል የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ሁሉ ባለብዙ ሚድያ፤ባለ ሙሉ ጦርና(ፌደራል ፖሊስ) ያገር ሃብት ይዞ ለሚያፍነን ፀረ ዲሞክራሲና አንደነት የሆነዉን ስረኣት እየታገልን ለዚህ ድርጊት የምንሸበር አንሆንም፡፡እነዚህ ጋዜጠኞች ግን የአንድነትን አወንታዊ የሰላማዊ ትግሉን እንቅስቃሴ፤የተመዘገበዉን ዉጤት ሳይሆን የእስርና እንግልት እንደሚያጎሉት እናዉቃለን፡፡ እኛ የጣልነዉን ወይ የወደቀብንን በማንሳት የኢቲቪን ስራ ሲደግሙብንም እንታዘባለን፡፡ይህንንም ከዚህ በፊት በሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት ግዜ በግብረሃይሉ ተገምግሞኣል፡፡

ብሶታችንን ብቻ ሳይሆን ያሉንን አማራጮች፤ስልተና እስትራተጂክ ግባችንን እንድናብራራ ቅርብ ያለዉ ሲዘጋብን እነሱዉ ቢከፍቱልን መላካም ነበር፡፡የሚፈልጉን ለብሶት ከሆነ ህዝቡ በቅርብ ስለሚያዉቀዉ ብዙም አያምሩንም፡፡ህዝቡ እንዲደራጅና ህገ መንግስታዊ መብቱን እንዲጠቀም ጉልበት እንዲኖረዉ ቢያስተምሩ በጎ ነበር፤እንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራርና የፓርላማ አባል ከሌላ ፓርቲ የፓርላማ አባልና የግዜዉ ባለስልጣን ተጨባበጠ ብሎ ክስ ግን ያስገምታል፡፡አንድነት የተከበሩ ዶ/ር ነጋሶን አምጥቶ መሪ፤እነ ሃብታሙ አያሌዉን ከፍተኛ አመራር… ያደረገበትን አገራዊ ፋይዳ የዘነጉት ይመስለኛል፡፡ዛሬም የአንድነት በር ወንጀለኛ ላልሆነ የኢህአዴግ አባልና ኢትዮጵያዊ ሁሉ በሩ ክፍት ነዉ፤ለዉይይትም ለትግልም፡፡

ሚድያ ናቸዉና ከሰራን ይዘግባሉ፡፡አንድነቶች በያለንበት ወደ ስራ!!! ሰላማዊ ለዉጥ እንዲመጣ የበኩላችሁን ገንቢ አስተዋፅኦ ለምታደርጉ የየትኛዉም ሚዲያ አይነት አካለት ግን በግሌ ክብር እሰጣለሁ፡፡ኢሳትና አንድነት ባላንጣም፤ወዳጆችም ሊሆኑ አይችሉም፡፡
ለለዉጥ እንደራጅ!!

Image

የባህር ዳሩ ገዳይ ካለምንም ጥያቄ በቀጥታ ለፖሊስ እጁን ሰቷል:: Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ካሳንቺስ ከቀድሞ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ጀርባ ከሚገኘው ድብቅ የደህንነት እስር ቤት ውስጥ በመገኘት በከፍተኛ የሴኩሪቲ ጥበቃ የነጻነት ታጋይ የሆነውን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር Greg Dorey እንዳነጋገሩ ሲታወቅ ከአንዳርጋቸው ጋር ያደረጉትን ቆይታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ባይገኝም በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሲገልጹ የኤምባሲው ምንጮች እንዳሉት ስለ አንዳርጋቸው መረጃ ያላቸው ለስርአቱ ቅርብ የሆኑ ክፍተኛ የደህንነት አባላት እና የአንድ ብሄር ተወላጅ የሆኑ አንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች እንደሆኑ ገልጸዋል::እንዲሁም አመነስቲ ኢንተርናሽናል አንዳርጋቸውን በተመለከተ ከታፍነ 6 ወር መሆኑን ገልጾ ሁኔታው አሳሳቢ ነው ሲል ለእንግሊዝ መንግስት አቤት ያለበተን መግለጫ ባሳለፍነው ሳምንት መግለጫ አውጥቶ ነበር::

ይህ በ እንዲህ እንዳለ በባህር ዳር ከተማ ውስጥ ድብ አንበሳ እየተባለ በሚጠራው ሆቴል አካባቢ አንድ አርሶ አድር ታጣቂ ሚሊሻ በሚመስል ጸጉረ ልውጥ ሰው የእንግሊዝ ዜግነት ያለው ቱሪስት መገደሉ ታውቋል::የአምባሰደሩ የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉብኝት ተከትሎ የእንግሊዛዊ ቱሪስት መገደል ድንጋጤ ፈጥሯል::ገዳዩ ለግድያው እንደተዘጋጀበት በሚያስታውቅ መልኩ በአከባቢው አድብቶ ሲጠባበቅ የነበረ እና ወዲያው እንግሊዛዊውን እንደገደለው ለፖሊስ ያለምንም ጥያቄ እጁን ሰቷል::በአከባቢዉም የታተቁ ፖሊሶች የነበሩ ሲሆን ግድያው ሲፈጸም ምንም ያደረጉት መከላከል አልነበረም::ግድያው የተቀነባበረ ነው ሲል የባህር ዳር ህዝብ እየተናገረ ነው::

Image
በባህር ዳር ከተማ አንድ ኢንግሊዛዊ ቱሪስት ከአንድ ግለሰብ በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አለፈ::በባህር ዳር ከተማ አንድ ኢንግሊዛዊ ቱሪስት ከአንድ ግለሰብ በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አለፈ።ድርጊቱ የተፈፀመው ዛሬ ረፋድ 4 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ነው።በግድያው የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ የወንጀል ድርጊቱ እየተጣራ ነው ። የሟቹም አስክሬን በሆስፒታል እንደሚገኝ ተመልክቷል።

ሻምበል ሳሙኤል መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ሪፖርተር :?:

” አብራሪዎቹ ከፖለቲካ ራሳቸውን ገለልተኛ ያደረጉት ባለው መንግስት ላይ ያላቸውን ጥላቻ እና ቂም ያመለክታል::በአንድ ሃገር የደህንነት ህዝባዊ ጥበቃ ስራ ላይ የተሰማራ ወታደር ከአምባገነኖች ፖለቲካ ራሱን ማግለሉ ህዝባዊ ተቆርቋሪነቱን ያሳያል:: ” Minilik Salsawi

ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው ነበረ::
የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ ::
ሪፖርተር :- የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡

ከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡

አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡

ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን ፀጋ ብርሃን ግደይ ጋር በኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር የዘወትር የልምምድ በረራ ለማድረግ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ድሬዳዋ ከሚገኘው የአየር ኃይል ቤዝ እንደተነሱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዋና አብራሪው ከአጭር ጊዜ በረራ በኋላ የበረራ ከፍታውን በመቀነስ ወደ ኤርትራ በማቅናት ሔሊኮፕተሩን አሰብ ማሳረፉን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

መከላከያ ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ ተዋጊ ሔሊኮፕተሩን ዋና አብራሪው ይዞ ወደ ኤርትራ መኮብለሉን አምኗል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው ዋና አብራሪው ቴክኒሺያኑንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን አስታውቋል፡፡

ሔሊኮፕተሩ ባለፈው ዓርብ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ጀምሮ በመደበኛ የሥልጠና ልምምድ ላይ እንደነበር ጠቅሶ፣ ሔሊኮፕተሩ ከግንኙነት ውጪ በመሆኑ ሠራዊቱ በአካባቢው ማኅበረሰብና አጋሮች ለተከታታይ ቀናት ፍለጋ ሲደረግለት መቆየቱን አትቷል፡፡ ‹‹ሆኖም ሔሊኮፕተሩ በከሀዲው ዋና አብራሪ አማካይነት ቴክኒሻንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፤›› ብሏል፡፡ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች ዋና አብራሪው የሔሊኮፕተሩ አዛዥ በመሆኑ የትም ወስዶ ሊያሳርፈው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡

‹‹ረዳት አብራሪው ጀማሪ ነው፡፡ የበረራ ቴክኒሺያኑ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን መከታተል ነው፡፡ ዋና አብራሪው ረዳት አብራሪውና ቴክኒሺያኑ እያወቁም ወይም ያለነሱ ዕውቅና የፈለገበት ወስዶ ሊያሳርፍ ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው መክረማቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር መትረየስና ተወንጫፊ ሮኬቶች የተገጠሙለት ዘመናዊ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ነው፡፡ ከኋላው ስምንት ወታደሮችን ወይም ሁለት የቁስለኛ አልጋዎችን መያዝ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኤምአይ 17 እና ኤምአይ 8 የትራንስፖርት ሔሊኮፕተሮች ሲኖሩት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸው በደርግ ጊዜ የተገዙ ኤምአይ 24 ሔሊኮፕተሮችን ነበር፡፡ በግንቦት 1990 ዓ.ም. የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲጀመር አሥር ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተሮች የተገዙ ሲሆን፣ በጦርነቱ ወቅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡

የ1997 ዓ.ም. ሦስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተነሳውን ግርግር ተከትሎ ሁለት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች (ሻምበል አብዮት እና ሻምበል በኃይሉ) አንድ ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ይዘው ወደ ጐረቤት አገር ጂቡቲ መኮብለላቸው ይታወሳል፡፡ ብዙም ሳይቆይ የጂቡቲ መንግሥት አብራሪዎቹን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግሥት የሰጠ ሲሆን ሔሊኮፕተሩንም መልሷል፡፡ አብራሪዎቹ የጦር ፍርድ ቤት ቀርበው በአሁኑ ወቅት በእስር እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ወቅት በቤላሩስ በሥልጠና ላይ የነበሩ ሰባት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የኤስዩ 27 ተዋጊ ጀት አብራሪዎች ከድተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ አብራሪዎቹ በተለያዩ የምዕራብ አገሮች ጥገኝነት ማግኘታቸው ይነገራል፡፡

ቀደም ሲል ሻምበል ተሾመ ተንኮሉ የተባለ የአየር ኃይል ባልደረባ በ1995 ዓ.ም. ኤል 39 የተሰኘ የመለማመጃና ቀላል የውጊያ አውሮፕላን ለልምምድ በረራ ከመቀሌ ቤዝ ይዞ እንደተነሳ ወደ ኤርትራ ኮብልሎ ነበር፡፡

እስከ ማክሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ምሽት ድረስ የኤርትራ መንግሥት ስለተጠለፈው ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጠም፡፡
source Reporter ሪፖርተር
Image

ከአርአያ ተስፋማሪያም

ፍቅረኞቹ አሁን የሚኖሩት አሜሪካ ነው። ተማሪ እያሉ ሳያስቡት ልጅ አፈሩ። የሁለቱን ፍቅርና መዋደድ እንዴት እነደነበረ የሚያውቋቸው ምስክር ናቸው። 6 አመት በመዋደድ የዘለቀው ፍቅራቸው በድንገት እሷ ከአገር በመውጣቷ ለጊዜው ተቋረጠ። የምትፅፋቸው ደብዳቤዎች ውብና አስደናቂ ነበሩ። ልክ እንደውጫዊና ውስጣዊ ውበቷ አይነት ነበሩ። በተለይ «..ውድ ፍቅሬ ቅድሚያ ግን እወቅልኝ፤ ዛሬም ልቤ አንድ! ፍቅሬም ዘላለማዊ ወረት የሌለበት እንደሆነ! ..ብቸኝነት ጅራፍ ነው! የእሳት ጅራፍ!…የዚህ አለም ኑሮ አክትሞልኝ ፅዋዬን እስክጐነጭ ፣ ተራ ደርሶኝ አንደበቴ ተሸብቦ እጅና እግሬ እስከሚታሰር ለአንተ ያለኝን ጥልቅ ፍቅርና መውደድ ከመግለፅና ከመተግበር ወደኋላ አልልም። አንተ ከማጣ (ልብ ተነጥቆ መኖር ከተባለ) ሞቴን እመርጣለሁ..» የሚለው አስደማሚ ደብዳቤዋ ይጠቀሳል። ከ4 አመት በኋላ ስትመጣ ግን እሱ በማያውቀውና ባላደረገው ነገር ቤተሰብ በጠነሰሰው ሴራ ለመለያየት በቁ። በተደጋጋሚ ቀርቦ ሊያስረዳት ቢሞክርም ለማዳመጥ እንኳ ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። ልጃቸው ልታስታርቅ ብዙ ጥራለች፤ ግን አልሆነም ..ሌላ ሰው አፍቅራ አሜሪካ ገባች። እሱም ልጁን ይዞ ሄደ። ልጇን ለማየት እሱ ወዳለበት ከተማ ስትመጣ ሁሉንም ነገር አስረዳት። ታማኝ ሆኖ ለ4 አመት እንደጠበቃት አስረዳት። በጣም ተፀፀተች።..ጊዜው ግን አልፎ ነበር። ..በቅርቡ ልጅ መውለዷን ሲሰማ ሆስፒታል ድረስ በመሄድ ጠየቃት። የልጇን ግንባር ስሞ « እንኳን በሰላም ተገላገልሽ..ደስ ይበልሽ!» አላት። አንገቷን እንዳቀረቀረች ነበር። …እሱ አንድ እመነት አለው፤ ያፈቀርከውን ሰው ስትለያየው መጥፎውን የምትመኝ ከሆነ..መጀመሪያውኑ ፍቅር አልነበረህም ማለት ነው!..ይላል።..ደግሞም ምንም ክፋት የማታውቅ መልካም ሴት መሆኗን ይመስክርላታል።….ይህ እውነተኛ ታሪክ የእኔ ነው፤….ባለቷሪኳ ደግሞ የኢየሩስ እናት…

«..ለአይኔ ማመን ያቃተኝ ታላቅ ነገር ዛሬ ተከሰተ – ደብዳቤህ። ተመስገን አምላኬ!

በስራ የዛለ ሠውነቴ ከእረፍት አስበልጦ ከአንተ ሊያወጋ የተወሰኑ ረድፎችን መጓዙን አይኖቼ አስተዋሉ። ስቀጥል፥ ከምንም በላይ በሀገርህ ላይ ሠላምህን፣ በቤትህ ውስጥ የሠከነ ሕይወትን፣ ከሰዎች ጋር መልካም ግንኙነትን፣ ለፈጣሪህ ቅን ልቦናን፣ ለቤተሰብህ መታዘዝን፣ እምነት ማተብህን ማጥበቅን፣ ለሰውነትህ ምቾትን፣ ለአይምሮህ መረጋጋትን፣ በስራህ አስተዋይነትን፣ በማህበራዊ ህይወትህ ጥሩ ግንኙነትን፣ በሰዎች ዘንድ ተወዳጅነትን፣ እንዲያድልህ ፥ ለፈጣሪዬ – ለፈጣሪህ፣ ለአምላኬ – ለአምላክህ፣ ፃድቅም ባልሆን ለሃጢያተኞች ሲል መከራን ለተቀበለ፣ በበደሉት መጠን ቂም ለማይዝ፣ በጠሩት ጊዜ ለሚሰማ ለሕያው አምላክ – በልኡል መንበሩ ተቀምጦ አዳርህን – አዳሬን፣ ውሎህን – ውሎዬን፣ ለሚቃኝ ለሚመለከት፣ እውነተኛ ሚዛንና ፍርድን በእጁ ለያዘ ፈጣሪ አምላክ የእጁን በረከት እንዲዘረጋልህ የዘወትር ፀሎቴ ነው!!

ውድ ፍቅሬ፥ ቅድሚያ ግን እወቅልኝ፤ ዛሬም ልቤ አንድ፣ ፍቅሬም ዘላለማዊ ወረት የሌለበት እንደሆነ!! በቀዘቀዘና በሰከነ አነጋገር ክንድህን ተንተርሼ….ጠረንህን እያሸተትኩ ..አ. ፈ..ቅ..ር..ሀ..ለ..ሁ…የምልህን! በቀን የሰው አይን፣ በጠፍ ጨረቃ ጋኔን ሳልፈራ ..አንተን እያልኩ ድፍን ሰፈርህን እያሰስኩ « ፍቅሬን.. ውለዱ» እያልኩ ሳስሥህ የምከርመውን፤ ይህን ስፅፍልህም ወደኋላ በትዝታ እየተቃጠልኩ ትርሃስ ላይ ተደፍቼ እያነባሁ መሆኑን ብታየኝ.. “አዝንልሻለሁ” ከምትለኝ በላይ ዛሬ ታዝንልኝ ነበር። የሚያባብለኝ የለ፤ የሚያፅናናኝ። ብቻዬን ልብህን እያሰብኩና እየፈለኩ፣ እንዲያጫውተኝ እየዳሠስኩ – ፍቅርን ከትርሃስ ጋር በእንባ ሌሊቱን በመገላበጥ አነጋለሁ፤ ናፈቅከኝ!!…በካፊያ ዝናብ ከአንተ ጋር መሆን ምን ያህል እንደሚያስደስተኝ አንተም ታውቃለህ፤ ምን ብዬ ልንገርህ!?…ቢያንስ ያንተ ይሻላል- ቤተሰብን አይቶ መፅናናት ቀላል ነገር እንዳይመስልህ!! ብቸኝነት ጅራፍ ነው፤ የእሳት ጅራፍ!!!..ከስራ መልስ አረፍ ባልኩ ቁጥር ቀልቤ አዲስ አበባ….ሰፈር ልቤ ከአንተ ጋር በምናብ ሲጨዋወት ያመሻል።

« …የምወድህ ፍቅሬ፥ አጀማመራችን እኮ ብንተማመን – ልንፋቀር፣ ብንዋደድ ልንዛለቅ፣ ብንተሳሰብ ልንስማማ፣ ብንከባበር ላንናቆር፣ ብንቀያየም ላንለያይ ነበር። ታዲያ ዛሬ ማዶና ማዶ ሆነን እየተሰቃየን ተግባብተን ላንስማማ በየራሳችን ሃሳብ እየተጓዝን የፍቅራችንን መንገድ አጣመምነው። ሃላፊነቱን በእኔ ላይ ብቻ እንደማትጥልብኝ አምናለሁ፤ እንዲሁም የጥፋተኝነትን ፅዋ። ካጠፋሁ ይቅርታ! ግን ጥፋቴ ምን እንደሆነ አልታየኝም። እዚህ ያለሁበትን አጣብቂኝና ፈተና፣ ስቃይ፣ ችግር፣ መከራ ብትመለከት እንኳን ቅያሞት ሃዘን ይገልህ ነበር። እኔ አንተን የማልቀየምህ ለምን መሰለህ?..ሁሉን ነገር ስለማታየው፣ የስደትን ኑሮ በሰው ሃገር ስላልተረዳህልኝ፣ እኔም ኢትዮጲያ እያለሁ እዚህ ችግር ያለ ስለማይመስለኝ፣ አንተም ከእኔ የተለየ አስተሳሰብ ስለሌለህ፥ ለዚህ ነው ብዙም ያላመረርኩብህ። ተስፋ ነበረኝ ከአንድ ከ8 ወራቶች በኋላ አይንህን የማየት፤ ሁሉን ነገር ተወያይተን አምላካችንን በመሃከላችን አኑረን ቃሌን ልሰጥህ፣ ቃልህን ልቀበልህ!! በቃ ተስፋዬ ተሟጠጠ፤ የጓጓሁለትም የመምጫዬ ጊዜ አጠራጠረኝ። ገላዬ እኮ ከምንም በላይ ይናፍቅሃል! እውነተኛ ፍቅር በልቤ ስለመኖሩ መሀላና ምስክር የምትሻ አይመስለኝም። እወድሃለው እኮ! አልተለወጥኩም! ኑሮ አስመርሮኝ፣ ጤና ማጣት ማንነቴን እየተፈታተነ መኖር ስላስጠላኝ እንጂ በአንተም የጨከነ አንጀት ኖሮኝ አይደለም። አንተን ከማጣ ፍቅርህን በልቤ እንደሰነቅኩ ወደ መቃብሬ መውረድን እመርጣለሁ!!..የማይካድ እውነታ ተለያይተን ላንረሳሳ ትልቅ ምሰሶ የብረት ማገር በመካከላችን ጋርደን (ቃልን) በትዝታ እየተንገላታን ማዶና ማዶ ሆነን <ነበረን> መጨዋወት ከጀመርን ሁለት አመታት ተቆጠሩ። ወደ ኋላ ትንሽ ልመልስህ፥ በአብሮነት የፍቅር ጊዜያችን በአንተ ያለወጥኩት ፍጥረት አልነበረም፤ ቢኖር እንኳ አንድ እናቴ ብቻ ነች። ከተጣላኸው ተጣልቼ፣ ከተቀየምከው ተቀይሜ፣ የወደድከውን ወድጄ፣ ያቀረብከውን አቅርቤ፣ አንተን መስዬ ሣይሆን ሆኜህ አብሬህ ዘልቄ ነበር ፍፃሚያችን ያምር መስሎኝ – በተስፋ ጓጉቼ!! ከሁሉ ጋር እንደ ሺህ ዘመን የርስት ባላጋራ የጐሪጥ ስተያይ ኖሬያለሁ። የፍቅር ሃይማኖተኛ ባህታዊ መሆኔና መገዛቴ ጥሩ ባሪያ ተብዬ ያስመሰግነኛል እንጂ አያስንቀኝም! በጥሩ አፍቃሪነቴም እኮራለሁ እንጂ አላፍርም! አንተም ብትሆን እንደማትጠላኝ አውቃለሁ!..»

« .. ውድ የሆንከው ፍቅሬ ሆይ፥ የዚህ አለም ኑሮ አክትሞልኝ ፅዋዬን እስክጎነጭ፣ ተራ ደርሶኝ አንደበቴ ተሸብቦ እጅና እግሬ እስከሚታሰር፣እስትንፋሴ እስከቆመበት፣ በድኔ ወደከርሰ መቃብር ወርዶ የዘላለም እረፍቱን እስካገኘበት እለት የመጨረሻ ደቂቃና ሰኮንድ ድረስ አንተን ከማድነቅና የሕይወቴ እስትንፋስ መሆንህን ከመናገር ወደኋላ አልልም!! እወድሃለሁ! አፈቅርሃለሁና የሚደርስብኝን ችግር፣ የሚገጥመኝን ፈተና አንተን በማስታወስ ፍቅር ትዕግስቱን ሰጥቶኝ በደስታ ለማሳለፍ የቆረጥኩት ዛሬ አይደለም። ወደኋላ ሳስብ “አንተን አፍቅሬ የተሰቃየሁበት፣ በቤተሰቤ የደረሰብኝ የስድብ ናዳ …ሁሉም ትዝታ ሆኖ፥ እንዳያልፍ የለም አለፈ። ያንተ ፍቅር ግን ምንግዜም በልቤ ውስጥ የማይቀልጥ የዘላለም ሻማውን እንዳበራ ይኖራል። መቼም ቢሆን የማይለወጥ ቃል ኪዳኔ ነው!! ከአምላኬ በታች ያመለኩህ አንተን ብቻ ነው!! ብትጠላኝ ላልጠላህ፣ ብትክደኝ ላልከዳህ፣ ብትርቀኝ ላልርቅህ፣ ብትሰድበኝ ብትንቀኝና ብታዋርደኝ፣ ላልሰድብህ ላልንቅህ ላላዋርድህ፣ ከትእዛዝህ ውጭ ላልወጣ “እሺ” ከማለት በቀር መጥፎ ቃላት ላልሰነዝር..ፍቅር ሸብቦ የያዘኝ የአንተው ምርኮኝ ነኝ!! ልቤ ፍቅርህን ከማሽበልበል ውጭ መርዝ አይተፋም። አንደበቴ ፍቅርህን( አንተነትህን) ከማድነቅ በቀር ሬት አይተፋም!! ፍቅርህ ጣፋጭ ነው!! ቁጣህ አስደንጋጭ – ንግግርህ አስፈሪ፣ ቁልምጫህ አጥጋቢ – ፀብህ መራራ፣ ልብህ የዋህ – አስተሳሰብህ ጠንካራ (አስተዋይ)፣ ተክለቁመናህ ማራኪ – ቁም ነገር አዋቂ፣ አላማህ ተወዳጅ – ለችግር ፈጥኖ ደራሽ፣ በአጠቃላይ አምላክ ሲፈጥርህ ከሁሉም ነገር አድሎሃል። እወድሃለሁ! ልቤ ንፁህ ነው፤ ያንተን ፍቅር ብቻ የሚያስተናግድ!! አንደበቴ ቁጥብ ነው፥ አንተን ብቻ የሚያደንቅ!! ለእኔ ምንጊዜም ቢሆን ውድ ነህ!! ከማንም – ከምንም በላይ አፈቅርሃለሁ፤ እወድሃለሁ!! ”አፈቅርሃለሁ” ለሚለው ቃል መተኪያ ባገኝለትና የልቤን ብገልፅልህ ምንኛ ደስ ይለኝ ነበር መሰለህ!?..

ፍቅሬ ሆይ፥ ሁልጊዜ እሰጋለሁ፣ እጨነቃለሁ። አንተ ከእኔ ጋር የመኖር አላማ የሌለህ ስለሚመስለኝ ኑሮዬ የስጋት፣የጭንቀት፣ የብስጭት ይሆናል። ሌላ ምንም አያሳስበኝም። ደግሞም ከአንተ ተለይቼ ከምኖር (ልብ ተነጥቆ መኖር ከተባለ) ሞቴን እመርጣለሁና አደራ የገደል ላይ ሳር የሆነውን ሕይወቴን ነፍስ ዝራበት፤ በደመነፍስ የሚመራ ሕይወቴን፣ አላማቢስ የሆነብኝን ጭንቅላቴን፣ በጭንቀት የሚሸማቀቅ አካላቴን፣ አዝናናው፣ አበረታታው፣ ደባብሰው፣ ነፍሴ በአንተ ትለምልም፤ ካለአንተ ማን አለኝ፤!? አገር ቤት እያለሁ የሰራህልኝን ውለታ እስከ እለተ ሞቴ የማልረሳው ትልቅ ሸክም ነው። < ሸክም ነው ያለኩህ> ከፍዬ ስለማልጨርሰው ነው!! የእኔ ፍቅር አንድ ነገር ልንገርህ?፤ እኔን የአሜሪካ ኑሮ የሚያስደስተኝ፣ እዚህ ያለው ብልጭልጭ ነገር የሚያዘናጋኝ አይደለም። …አንድ ነገር ልብ በል፤ እየፃፍኩልህ ያለሁት ከሌሊቱ 7፡30 በኢትዮ.ሰዓት አቆጣጠር እንደሆነ እወቅ። ከእንቅልፌ ሠአት ላይ ቆጥቤ ነው በድቅድቅ ሌሊት የምፅፍልህ፤ እንጂ ቀንማ ትንፋሽም የለኝ። ምን ያክል ስለፋ እንደዋልኩ ፈጣሪ አይቷል!! የድካሙ ነገር አይነሳ.. እስቲ ተከድኖ ይቀመጥ፤ ስደትን ያየ ይፍረደኝ!?….ግን ዛሬ ደግሞ ደስ ያለኝ ነገር አንተ ማንንም እንዳልተላመድክ ገለፅክልኝ፤ ጥሩ ጌታ ያፅናህ! እኔስ ፀንቻለሁ በአካልም፣ በልብም፣ በመንፈስም። አምንሃለሁ! ባላምንህ ኖሮ መልስ አልፅፍልህም ነበር። አንተስ ታምነኛለህ?..እንደድሮው?..

ውድ ፍቅሬ፥ መኝታዬ ክፍል ጥግ ላይ ተቀምጬ እንባዎቼ በጉንጬ ላይ እየተሽኳለሉ ዱብ.. ዱብ..ዱብ ይላሉ። ፎቶዎችህን አስተውላቸዋለሁ፤ ድብዳቤዎችህን መላልሼ አነባቸዋለሁ፤ ደግሞ እፅፋለሁ። ልቤ ግን ድም -ድልቅታውን አያቋርጥም፤ የመገናኘት ምኞቴን በደውሉ ያስተጋባልኛል!! ያሳለፍነው እኮ እንኳን በነዚህ አመታት ቀርቶ መቼም የሚረሳ አይደለም፤ አይረሳም። አንተ ትረሳለህ ወይ?..ሰሞኑንማ ከመስሪያ ቤትህ ጀምሮ አዘውትረን እናድርበት የነበረው ..ሆቴል ድረስ ጣፋጩ ትዝታ በአእምሮዬ ይመላለሳል። ትዝ ይልህ እንደሆነ በዛ ሰሞን ፍቅር በዝቶ ቅብጥብጥ ሲያደርገን « ውዴ ፍቅር በዛ፤ ልንለያይ ነው መሰለኝ » ስትለኝ እኔም < እባክህ ፍቅሬ እንደዚህ አትበለኝ?> ብዬ አንገትህ ስር ሽጉጥ የምለው፣ በደረትህ የምንፈላሰሰው፣ አትዩብኝ የምለው አይንህ፣ አትንኩብኝ የምለው እጅህ…አረ ስንቱን…ስንቱን ልዘርዝረው!?…ውድ ነህ፣ እንቁ ነህ!

ውድ ፍቅሬ ሆይ፥ ግን አንድ ነገር የማልደብቅህና ከዚህ በፊት ደግሜ ደጋግሜ የፃፍኩልህ፣ በህልሜም ተደጋጋሚ ነገር ስላየሁ ሰጋሁ። አንተን በርግጥ ልመንህ?..እንዴት ነው ልቤ ያምንሃል፤ ህልሜ ግን አስፈራኝ። ስለዚህም ጉዳይ ገልፀህ ፃፍልኝ። ኩርት ያልክ ሁንልኝ!! ልክ እንደቀድሞህ። እንዲያ ከሆንክ ስመጣ አይኔን ለማየት አታፍርም። ከምንም በላይ ደግሞ ሕሊናህ ነፃ ይሆናል!! ካልሆነ ግን ከእኔ ይበልጥ እራስህን ሰላም ታሳጣለህና ጠንቀቅ፣ ሰቅጠጥ በል!! “ምነው ይህቺ ልጅ ጨቀጨቀችኝ” እንደማትለኝ ነው!?..ፍቅር የወለደው የስጋት ጭንቀት ነውና አትፍረድብኝ። ..ቦሌ ላይ ስትሸኘኝ አንድ ጥያቄ ጠይቀኸኝ ነበር፤ < አንቺ ግን ቃልሽን ጠብቀሽ፣ አስችሎች ሌላ ሳትላመጂ እንገናኛለን? > ስትለኝ እኔም “ራሴን የምፈትንበት ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል፤” ብዬህ ነበር። አዎ! አንተን ካላሰብኩ በቀር ገላዬ ፈተናውን በቅጡ ተወጥቷል። በፈጣሪ እርዳታ!! …በብዙ ፈተና ተፈትኜ አለፍኩ፤ ማለፍ ያቃተኝ ግን የልቤን ፈተና ነው። ጊዜ ይፈታዋል!!…አሁን ላበቃ ጥቂት መስመሮች ቀርተውኛል። የደስታ ብስራት ላቋድስህ፤ ከ6 ወራት በኋላ ልመጣ ነው..» አበቃ።…..ይህ እውነተኛ ታሪክ ሲሆን የፍቅር ሴረኞች ለያዩዋቸው። ባለታሪኮቹ….

በነ ሀብታሙ አያሌው የክስ ጉዳይ የተሰየመው ችሎት ‹አስገራሚ› ውሎ

∙ተከሳሾቹ ‹‹ዘረፋ›› ተፈጽሞብናል ብለዋል ∙‹‹ለማን አቤት ይባላል?›› ሀብታሙ አያሌው

በላይ ማናዬ : ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች ተሟልተው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል፡፡

ችሎቱ የተሰየመው ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ወቅት ተከሳሾች በቀረበባቸው የሽብር ክስ ላይ የሰጡትን መልስ በተመለከተ 7ኛ ተከሳሽ መልስ በዕለቱ ባለማቅረባቸው አሟልተው እንዲቀርቡ ነበር፡፡ በተጨማሪም ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ስለነበር ይህን በተመለከተ ማረሚያ ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ በታዘዘው መሰረት ማብራሪያውን ለመስማት ነበር፡፡
Image
የተከሳሾች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በጥየቃ ወቅት በተለየ መዝገብ ይመዘገባሉ የተባለውን አቤቱታ በተመለከተ፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በደብዳቤ መልስ መስጠቱ የተገለጸ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ‹‹ማረሚያ ቤቱ በሰጠው መልስ እስረኞች ከሌሎች በተለየ የደረሰባቸው ችግር የለም›› ማለቱን ገልጾ ይህንኑ መልስ ሙሉ ለሙሉ መቀበሉን አስታውቋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በዛሬው የችሎቱ ውሎ ላይ ተከሳሾች ለየት ያለ አቤቱታ በጠበቆቻቸው በኩል አቅርበዋል፡፡ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ለችሎቱ እንዳስረዱት ደንበኞቻቸው ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ በደል እየተፈጸመባቸው ነው፡፡ አቶ ተማም አባቡልጉ በታህሳስ 12 ለ13 ቀን 2007 ዓ.ም አጥቢያ ሌሊት ስምንት ሰዓት ጀምሮ ደንበኞቻቸው ላይ ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጎ የግል ማስታወሻዎቻቸው፣ ገንዘብ እና በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ እያዘጋጁት የነበረው መቃወሚያና መከራከሪያ ተወስዶባቸዋል ብለዋል፡፡

‹‹ደንበኞቼ ላይ እየተደረገ ያለው ጉዳይ ለህይወታቸውም የሚያሰጋቸው ነው፡፡ በማረሚያ ቤቱ በሌሊት ፍተሻ ያደረጉባቸው ሰዎች ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ‹ህገ-ወጥ› ተግባራት ሲፈጽሙባቸው የነበሩ የፌደራል ፖሊስና የደህንነት አባላት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ሰዎች ደንበኞቼ ያውቋቸዋል፡፡ ስለሆነም ፍተሻው የተከናወነው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አልነበረም ማለት ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው የተለየ የስም ዝርዝር ተይዞ ከሌሎች በተለየ መልኩ ነው፡፡ ለአብነት ደንበኞቼ አቶ አብርሃ ደስታና በሌላ የክስ መዝገብ የተከሰሰው አብዱራዛቅ አክመድ ላይ የሆነው ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ነው፡፡ ፍተሻው ስለት ነገር አልያም ሌላ ህገ-ወጥ ቁሳቁስ ለመያዝ የተደረገ አለመሆኑን ከተወሰዱት ንብረቶች ማየት ይቻላል›› ሲሉ አቶ ተማም ለፍርድ ቤቱ በደንበኞቻቸው ላይ የተፈጸመውን ድርጊት አስረድተዋል፡፡

ይህን በተመለከተ አስተያየት የሰጡት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ በበኩላቸው፣ ‹‹ማረሚያ ቤቱ መንግስት ዜጎች ታንጸው እንዲወጡ ያሰራው ነው፡፡ ይህን አሰራር ለመጠበቅም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የተለያዩ ስራዎችን ሊሰራ ይችላል፡፡ እየቀረበ ያለው አቤቱታም ከዚህ አኳያ መታየት ያለበት ነው›› ብለዋል፡፡

ጠበቃ ተማም የደንበኞቻቸውን አቤቱታ ከህግ አንጻር ያስረዱ ሲሆን፣ ‹‹በመሰረቱ ፍተሻ ሊካሄድ መቻሉ ላይ አይደለም አቤቱታው፡፡ የተካሄደው ፍተሻ ግን ህገ-ወጥ ነው፤ ምክንያቱም ፍተሻው የተከናወነበት ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ባለው ጊዜ ሳይሆን ሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ነው፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ፍተሻው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አይደለም የተከናወነው፡፡ በደህንነቶችና የፌደራል ፖሊሶች ነው ፍተሻው የተደረገው፡፡ ይህም ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎቱም ሆነ ብቃቱ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ ይህን መሰል ድርጊት የፈጸሙት አካላትና በማን ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ምርመራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን›› ብለዋል፡፡

ጠበቃ ተማም በተጨማሪ ከደንበኞቻቸው ላይ በፍተሻው ወቅት የተወሰዱባቸው ንብረቶችና ማስታወሻዎች እንዲመለሱላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው አመልክተዋል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ‹‹የተለየ ከፍተኛ በደል ደርሶብኛል›› በሚል ለፍርድ ቤቱ እንዲያስረዱ ዕድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው የነበሩት 3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺ የጠየቁት የመናገር እድል ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡

በጠበቆቹ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታን በተመለከተ ችሎቱ አስተያየት የሰጠ ሲሆን በተለይ ጠበቃ ተማም አቤቱታውን ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎትም ብቃትም የለውም›› ያሉት አገላለጽ ተገቢ ስላልሆነ እንዲታረሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በቃል የገለጹት የመሐል ዳኛው፣ ‹‹እንዲህ አይነት አገላለጽ ማረሚያ ቤቱ የበቀል እርምጃ እንዲወስድ የሚገፋፋ እንዳይሆን…›› በማለት ሌላ አስገራሚ መነጋገሪያ ከፍተዋል፡፡

ይህን የዳኛውን ንግግር ተከትሎ 2ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌው የመናገር እድል ከተደጋጋሚ ጥያቄ በኋላ ለአጭር ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡ እናም፣ ‹‹እርስዎ እያሉት ያለው ነገር ተገቢ አይደለም፡፡ በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ ይህንን ስጋቴን ለችሎት እያስረዳሁ ነው፡፡ ግን እርስዎ ‹የበቀል እርምጃ› እንዲወሰድብን ማሳሰቢያ እየሰጡ ነው፡፡ ይህ ተገቢ አይደለም፡፡ በእርግጥ አሁንም የበቀል እርምጃ እንደማይወሰድብን ማረጋገጫ የለንም፡፡ እሺ ለማን አቤት ይባላል? የደረሰብንን በደል ለፍርድ ቤት ከማስረዳት ውጭ ለማን አቤት እንላለን….አሁን እኮ ፍርድ ቤቱ ከማረሚያ ቤቱ ጋር መወገኑን ነው እያየን ያለነው፡፡ ፍርድ ቤቱ የእኛን አቤቱታ እየሰማ አይደለም፡፡ ከፍርድ ቤት ውጭ ለማን አቤት እንበል?›› ሲል አቤቱታውን በስሜት ውስጥ ሆኖ አስረድቷል፡፡

የሀብታሙን ንግግር አዳምጠው አንደኛ ዳኛ ‹‹እኛ ሳንሆን ህጉ ነው ይህን እንድንል የሚያደርገን›› በማለት አጭር መልስ ሰጥተዋል፡፡

በዚህ መልኩ ቀጥሎ የዋለው ችሎት በተከሳሾች በኩል የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ የማየት ስልጣን አለው ወይስ የለውም በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት፣ እና መደበኛ ክሱን ለማየት ለታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተጥቷል፡፡
‪#‎NegereEthiopia‬

Image
– የድሬደዋ አየር ሃይል መምሪያ በግምገማ ታመሰ::
– መጭውን ውህደት የሚያሳፈጽሙ የአርበኞች ግንባር አባላት ከአውሮፓ እና አውስትራሊያ ተወከሉ::
http://ireport.cnn.com/docs/DOC-1200173
አርብ እለት ከድሬዳዋ ተነስተው በደቡባዊ ኤርትራ አሰብ ዘልቀው የገቡት የወያኔው አየር ሃይል አብራሪዎች እና ቴክኒሺያኖች በደህና ሁኔታ ውስጥ ሲገኙ በኤርትራ የአየር ክልል የተቀበላቸው እና በ1987 አመተምህረት በወያኔ እና የደርግ መኮንኖች የሰለጠነው የሻእቢያ ኮማንዶ ጦር አጅቧቸው ወደ አስመራ ቤተመንግስት ከገቡ በኋላ በቤተ መንግስቱ ውስጥ ለሁለት ቀን በእንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ ቆይተው ወደ ሆቴል መዘዋወራቸውን ከአስመራ የተገኙ ምንጮች ጠቁመዋል::

በቤተ መንግስት ቆይታቸው አስፈላጊ ጥያቄዎች እና ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ከደምህት ጦር ጋር በመቀላቀል እየተገነባ ባለው ዘመናዊ አየር ሃይል ውስጥ አገልግሎት እንዲሰጡ የተጠየቁ መሆኑን ምንጮቹ ሲናገሩ አብራሪዎቹ ግን ወደ አውሮፓ ለመጓዝ ፍላጎቱ እንዳላቸው እና አውሮፓ ሆነው ትግሉን መርዳት እንደሚችሉ ሲናገሩ ተደምጠዋል::አብራሪዎቹ እጃቸውን የሰጡትም ሆነ የተቀላቀሉት ከኤርትራ መንግስት ጋር እንጂ ከሌላ አካል ጋር እንዳልሆነ ምንጮቹ አረጋግጠዋል::

ከደብረዘይት አየር ሃይል አከባቢ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በድሬዳዋ ያለው የአየር ሃይል ካምፕ ሃላፊዎች ላይ ከፍተኛ ግምገማ ተደርጓል::በዚህም መሰረት የሃገሪት የአየር ክልል ሳይቀር ከራዳር ውጪ ነው የሚል ጉዳይ ተነስቶ መነጋገሪያ እና መገማገሚያ ሆንዋል::እርስ በርስ መወነጃጀል እንኳን ባልተደፈረበት ግምገማ ላይ እያንዳንዱ መኮንን ሃላፊነቱን ወስዶ ዋጋ ሊከፊል ዪገባዋል ሲሉ ከፍተኛ አዛዦች በቁጣ ተናግረዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በመጪዎቹ ሳምንት በሚካሄደው የግንቦት ሰባት እና የአርበኞች ግንባር ውህደት ላይ እስካሁን ወኪል ያላከው የአርበኞች ግንባር አንድ ሰው ከአውሮፓ አንድ ሰው ከአውስትራሊያ በመምረጥ ለእህደት ስብሰባው ማስትላለፉን ምንጮቹ ተናግረዋል::የተመረጡት አስመራ እንደደረሱ በውህደቱ ዙሪያ ንግግር እንደሚጀመር እና የፊርማው ውህደት እንደሚጸድቅ ኮሎኔል ፍጹምን ዋቢ ያደረጉ ምንጮች ጠቁመዋል::

Image

“ካልመለሱልኝ በውጊያ አስመልሰዋለሁ::” የደነገጠው ወያኔ
(ምንሊክ ሳልሳዊ)
ስርአቱን ከዱ የተባሉት አብራሪዎች ከድሬዳዋ ተነስተው በጅቡቲ ድንበር አስታከው በአሰብ ዘልቀው ኤርትራ ያሳረፉት ሄሊኮፕተር በሱዳን በኩል እንዲመለስለት ሻእቢያን መጠየቁን የሱዳን ዲፕሎማቶች ጠቆሙ::

ወያኔ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚያደርገውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እና በአየር ሃይሉ ውስጥ የሚፈጸመውን ደባ በመቃወም ከድተዋል የተባሉት 2 ፓይለቶች(ካፒቴን ሳሙኤል እና ቢሊሊኝ )እና አንድ ቴክኒሽያን(ጸጋ ብርሃን)ለኤርትራ መንግስት እጃቸውን የሰጡ ሲሆን ይህንንም የወያኔው ቴሌቭዥን ጣቢያ እማኝነቱን ሰቷል:: http://andargachewtsige.com/?p=383 ) አብራሪዎቹ ይዘውት የሄዱትን ሄሊኮፕተር እንዲመለስለት ወያኔ የሱዳን ዲፕሎማቶችን የላከ ሲሆን ሻእቢያ የማይመልስ ከሆነ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ከባድ አጸፋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አንድ ለስርአቱ ቅርብ የሆነ ድህረገጽ ጽፏል::

በሃገር ውስጥ እና በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ፖለቲካ ድል ሲቆጥሩት አንዳንዶቹ ወያኔ የሻእቢያን አየር ሃይል በሰው ሃይል እየገነባ ሊሆን ይችላል ከጀርባ ሌላ ደባዎች በወያኔ እና ሻእቢያ ሊሰራ ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አልጠፉም::የወያኔ መክላከያ ሰራዊት አጸፋዊ እርምጃ ይወስዳል የሚል ስጋት ቢያይልም;ሃገር ወዳዶች ግን ምንም እርምጃ አይወስድም የፍርሃት ዛቻ ነው ሲሉ ተደምጠዋል::

ከመከላከያ ሰራዊት እንዲባረሩ የታሰቡ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች ለስርአቱ ደህንነት ሲባል በቦታቸው እንዲቆዩ መደረጉ ታወቀ::

ክምርጫ መረጋጋት በኋላ በርካታ መኮንኖች ሊባረሩ ይችላሉ::
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

በከፍተኛ የመከላከያ ሰራዊት አመራር ውስጥ በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰራ የነበረው ሌተናል ጄነራል አበባው ታደሰ ባለፈው አመት ከቦታው መባረሩ ተከትሎ መባረር አለባቸው ተብለው ውስጥ ለውስጥ የተጨረሰላቸው በርካታ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች ቢኖሩም፤ ከኋላ ሊነሳ የሚችለውን ችግር ግምት ውስጥ በማስገባት በተደረገው ግምገማ ላይ በማስጠንቀቅያ ብቻ እንዲታለፉ መደረጉን ታውቋል::

መባረር አለባቸው ተብለው ከተቀመጡት ከፍተኛ መኮነኖች አብዛኛዎቹ የሌተናል ኮረኔል ማእረግ ያላቸው እንደሆኑ የገለፀው መረጃው የጄኔራል አበባው ተከታዮች ስለሆኑና እንቅፋት ስለሚፈጥሩብን ተብለው እንዲባረሩ የተወሰነባቸው ቢሆንም፤ በመጪው ምርጫ ታሳቢ በማድረግ በህዝቡ መሃል ገብተው ኢህአዴግን ለመጣል ሊያነሳሱ ስለሚችሉ ግምገማ በማድረግ በማሰጠንቀቂያ እንዲታለፉ መደረጋቸውን መረጃዎች አምልክተዋል::መረጃዉም አያይዞ እንደጠቀሰው ክምርጫ መረጋጋት በኋላ በርካታ መኮንኖች ሊባረሩ ይችላሉ::

Image

በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰዉን በድልና ጭቆናን በመቃወምና የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮችአስመልክቶ በዋሽግተን ዲሲ የሚገኘዉ ፈርስት ሒጅራህ ፋዉዴሽን የ አቋም መግለጫ አወጣ
ባለስድስት ነጥብ የሆነዉ የ አቋም መግለጫ የ ኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮች ያጠቃለለ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግስት በዜጎቹ ላይ የሚያደርሰዉን በደልና ጭቆና ለመታደግ ፈርስት ሒጅራህ ፋዉዴሽን አገራዊ ሐላፊነቱን ለመወጣት የሚጠበቅበትን ሁሉ እደሚያደርግ የ አመራር አካላቱ ለ ቢቢኤን ገልጸዋል። የአቋም መግለጫዉም እንደሚከተለዉ ይነበባል፦

• ሆን ተብሎ ሙስሊሙ ህብረተሰብ ላይ መንግስት ሲፈፅም የቆየዉን ኢሰብአዊ ድርጊት ባዲስና በከፋ መልኩ የጀመረዉን እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን

• ሙስሊም እህቶቻችንን የእምነት ነፃነት በመንፈግ ባአዲስ አበባ ዩኒፈርሲቲና በሌሎች የትምህርት እንዲሁም በመንግስት መስሪያ ቤቶች ሂጃባቸዉን እንዲያወልቁ የማስገደዱ ጉዳይ ሙስሊም ሴቶችን ከእምነታቸዉና ከትምህር እንዲሁም ከእምነታቸዉና ሰርተዉ ከመኖር ምረጡ እየተባሉ የሚደረግባቸዉን ተፅእኖን አጥብቀን እናወግዛለን

• በግፍ ታስረዉ ባሉት የሙስሊም መሪዎች ቤተሰቦች ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ ገብታችሁ ወዳጆቻችሁንን መጠየቅም ሆነ ምግብ ማቅረብ አትችሉም ተብለዉ የሚደርስባቸዉን መጉላላት በጥብቅ የምናወግዝ መሆናችንንም እንገልፃለን

• እንዲሁም ጠቅላይ ሚኒስቴር ሃይለማርያም ደሳለኝ ካንድ ጠቅላይ ሚንስቴር በማይጠበቅ አፀያፊ አነጋገር ጨዋዉንና ታታሪ ሰራተኛዉን የስልጤን ብሄረ ሰብ መዝለፋቸዉን አጥብቀን እንቃወማለን

• በቪዎች የሚቆጠሩትን ካገርና ከወገን ተለይተዉ ቤተሰቦቻቸዉንና ዘመዶቻቸዉን ለመርዳት የሚደርስባቸዉን ያካልና የመንፈስ ተፅእኖን በመቇቇም ለሚያደርጉት መስዋእትነት መመስገንናና መደነቅ ሲገባቸዉ ጠቅላይ ሚኒስተር ሃይለማርያም ባልተገራ አንደበታቸዉ እህቶቻችንን ገረዶች ብለዉ አንቇሸዉ መጥራታቸዉ እጅጉን አስከፍቶናል። የኢትዯዽያ ህዝብንም ይቅርታ ይጠይቁ ዘንድ እናሳስባለን።

• በተጨማሪም በቅርቡ ሰማያዊ ፓርቲ በጠራዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሰልፈኞች ላይና እንዲሁም ባህር ዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ የወጣዉ ክርስቲያን ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመዉን ኢሰብአዊ መንግስታዊ እርምጃ አጥብቀን እናወግዛለን

“ፈርስት ሂጅራ ፋዉንዴሽን የኢትዯዽያ መንግስት ከቀን ወደቀን የህዝቡን ሰብአዊ መብት እየጨፈለቀ መቀጠሉን አጥብቀን እንደሚያወግዝና ሌላዉም የሰዉ መብት ያገባኛል የሚል ስብእና ያለዉ ሰዉ ያወግዝ ዘንድ ጥሪዉን ያቀርባል” በሚል የጥሪ መልክት የ አቋም መግለጫዉ ተቋጭቷል። የፈርስት ሒጅራህ የአመራር አካላት መጠነ ሰፊ የሆነዉን ጭቆናና በደል ለመታደግ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እንደሚሰሩ በመግለጽ በቀጣይነትም የሚያከናዉኗቸዉ የተቃዉሞ መርሃ ግብሮች እንደሚኖሩ ለቢቢኤን ገልጸዋል።

በህይወት እያሉ ተረት ለመሆን የበቁትና በጎጃም ክፍለ ሀገር የደብረ ወርቅ ወረዳ አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ “ቆምጫ አምባው” በዚህ ፎቶግራፍ የምትመለከቷቸው ሰውዬ ናቸው፡፡ አቶ ቆምጬ በአሁኑ ወቅት በትውልድ ከተማቸው በጥብቅና ሙያ ላይ ተሰማርተዋል፡፡ (ፎቶ፡ ዘ-ኢትዮጵያ ጋዜጣ)

Image

ካድሬዎቹ በባህር ዳር የተደረገውን ግድያ በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመ ነው ሲሉ ተናግረዋል::
Minilik Salsawi – ባለፈው አርብ በባህር ዳር ሰላማዊ የሆነ ጥያቄ ይዘው አደባባይ በወጡት ንጹሃን ዜጎች ዙሪያ እና በመጭው ምርጫ ዙሪያ በአዲስ አበባ ብአዴን ካድሬዎቹን በመሰብሰብ ያደረገው ውይይት ክለመስማማት መበተኑን ለምንሊክ ሳልሳዊ የውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል::

እንደ ምንጮቹ ዘገባ ከሆነ ካድሬዎቹ ሕዝብን ማሳመን የማንችልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል::ንጹሃን በአደባባይ መግደል የፖለቲካ ትርፉ ምንድነው የሚሉ እና በባህር ዳር የተደረገው ድርጊት በመጭው ምርጫ ላይ ከባድ ተጽእኖ ያጠላበታል ሲሉ አስተያየታቸን እና ጥያቄዎቻቸውን ሰንዝረዋል::ይህንን ድርጊት ፖሊሶቹ እንዲፈጽሙ ለምን ከፌዴራሉ ትእዛዝ መቀበል አስፈለገ? የክልሉ መንግስት የተደረገውን ሰልፍ በሰላም ለመበተን ያደረገው ጥረት ምንድነው ማብራሪያ እንፈልጋለን ሲሉ ካድሬዎቹ ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ ለውይይት የተጠራው ስብሰባ ወደ ጫጫታ ተለውጧል::

ካድሬዎቹ እንደሚሉት ማንኛውንም ጥያቄ በሃይል እየደፈጠጥን በምርጫው ወቅት ስንሸነፍ ሽንፈታችንን ተከትሎ በህዝብ ላይ ላለመተኮሳችን ማረጋገጫው ምንድነው ይህ ከባድ አደጋ ስለሆነ ባህር ዳር ላይ ለተፈጸመው ግድያ እና ድብደባ የክልሉ መንግስት እና መሪ ድርጅቱ ኢሕአዴግ ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው::ሌሎች አስፈላጊውን ሮሮ ሳያሰሙ ለጉዳተኞች ካሳ ሊከፈል ይገባል በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል::
የካድሬዎቹ ውይይት ከመጭው ምርጫ ላይ ያላቸውን ስጋት እና በህዝብ ላይ ይደርሳል ያሉትን ጥፋት በመናገር ያላቸውን ስጋት የገለጹ ሲሆን እንደ አባልነታቸው ደህንነታቸው ላይ ያለውን ጉዳይ በተመለከተም ጥያቄ አንስተዋል:: ለ 6 ሰአታት ያህል የዘለቀው ስብሰባ በስተመጨረሻ በምክክር ተጨማሪ ስብሰባዎች ይኖሩናል በሚል ካለመስማማት በጫጫታ መበተኑን ምንጮቹ ለምንሊክሳልሳዊ ገልጸዋል:: ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

“ ቅ/ ሲኖዶሱ በአድባራት ሓላፊዎች ላይ ያሳለፈው ሕገመንግሥቱን የሚፃረር ነው ” /ፓትርያርኩ/
Image

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፣ ‹‹የቤተ ክርስቲያን አባቶችና ቤተ ክርስቲያን ዕውቅና በሰጠችው ማኅበር ላይ ተገቢ ያልኾነ ቃል ተናግረዋል›› ባላቸው አንዳንድ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራት አስተዳዳሪዎች ላይ ያሳለፈው ውሳኔ አፈጻጸም ‹‹ሕገ መንግሥቱንና ሰብአዊ መብትን የሚፃረር ነው›› በሚል ፓትርያርኩ ማገዳቸው ተገለጸ፡፡
ፓትርያርኩ ባለፈው ኅዳር 30 ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በጻፉት ደብዳቤ ‹‹አፈጻጸሙ እንዲቆይ›› በማለት ያገዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት በተካሔዱ ጉባኤዎች÷ ‹‹ተገቢ ያልኾነ ቃል ተናግረዋል፤ ይህም አነጋገር ጉባኤውን ቅር አሰኝቷል፤›› ያላቸው የአድባራት አስተዳዳሪዎች፤ቀኖናዊ ምክርና ተግሣጽ እንዲሰጣቸው በአንድ ድምፅ ተስማምቶ ያሳለፈው እንደነበር ተጠቅሷል፡፡
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ በመንበረ ፓትርያርክና በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሾች በተካሔዱት ስብሰባዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን መልካም አስተዳደርና ወቅታዊ ችግሮች የተመለከቱ የጉባኤተኞች አስተያየቶችና ሐሳቦች መቅረባቸውን በደብዳቤያቸው ያስታወሱት ፓትርያርኩ፤ ተሰብሳቢዎቹ ሐሳባቸውንና አስተያየታቸውን በግልጽ መናገራቸውና አሉ የተባሉ ችግሮች መፍትሔ እንዲያገኙ መጠየቃቸው ‹‹በዓለም አቀፍ ደረጃም ኾነ በሀገራችን ለሕዝብ የተፈቀደ ዴሞክራሲያዊ መብት መኾኑ አያጠያይቅም›› ብለዋል፡፡ ሐሳባቸውንና አስተያየታቸውን በግልጽ ያቀረቡ ሰዎችን መገሠጽና መውቀስም ሕገ መንግሥቱን እንደሚፃረር ጠቁመዋል፡፡
ጉባኤዎቹ በቤተ ክርስቲያን ጠሪነት የተካሔዱ እንደነበሩና ተሰብሳቢዎቹም የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት፣ አገልጋዮችና ሠራተኞች መኾናቸውን ፓትርያርኩ ጠቅሰው÷ የጎደለው እንዲሟላ የጠመመው እንዲቃና ያላቸውን አስተያየት በማቅረባቸው ተግሣጽና ማስጠንቀቂያ እንዲሰጣቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳለፈው ውሳኔ ‹‹የስብሰባ ነፃነትንና መብትን ነፍጎ ሐቁ እንዳይነገር›› የሚከለክልና ውጤቱም ‹‹ጊዜ ያለፈበትን አፈና በማንገሥ ችግሮች ተባብሰው እንዲቀጥሉ የሚያደርግ ነው›› ብለዋል፡፡ “በውይይቱ ወቅት ‹‹የዳኅፀ ልሳን ወለምታ›› አጋጥሞም ከኾነ በወቅቱ ማብራሪያና ማስተካከያ ይሰጥበታል እንጂ እንደ ከባድ ጥፋት ተቆጥሮ ሰዎች ሊገሠጹበትና ሊወቀሱበት አይገባም፤ ሕግም አይፈቅድም፡፡” ሲሉ ገልጸዋል – በደብዳቤያቸው፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ‹‹ተገቢ ያልኾነ ቃል ተናግረዋል›› ያላቸው አንዳንድ የአድባራት አስተዳዳሪዎች በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል ቀርበው ቀኖናዊ ምክርና ተግሣጽ እንዲሰጣቸው ያሳለፈው ውሳኔ ‹‹ሕግንና ሰብአዊ መብትን የሚፃረር›› ብቻ ሳይኾን ‹‹ትልቁን ጉባኤ በታሪክና በሕግ ዐዋቂዎች ዘንድ ግምት ውስጥ የሚጥለው እንዳይኾን አቡነ ማትያስ አስጠንቅቀው፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ ጉዳዩን እንደገና በጥልቀትና ከሕግ አንጻር ፈትሾ እንዲያጤነው በማለት አፈጻጸሙ እንዲቆይ አስታውቀዋል፡፡
በሕገ ቤተክርስትያን ት/ሲኖዶሱ በሙሉ ድምፅ ተስማምቶ ያሳለፈውን ውሳኔ ፓትርያርኩ የማገድ ሥልጣን እንደሌላቸው ያመለክታል፡፡ ሕገ መንግሥቱ ከተጠቀሰበት አግባብ አኳያም፣ “ቤተ ክርስቲያናችን በቂ ሕግጋት አሏት፤ እነዚህ ሕግጋት ማዕከሉ ተጠብቆ ሊሠራባቸው ይገባል፤” ሲልም ቅ/ሲኖዶሱ አሳስቧል፡፡
ባለፈው መስከረም መጨረሻ “የቤተ ክርስቲንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልጸግ” በሚል መርሕ በተካሔደው ስብሰባ አንዳንድ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፤ ‹‹ፈጣሪ የለም ይላል፤ አሸባሪና አክራሪ ነው፤›› በማለት ቤተ ክርስቲያኗ ዕውቅና የሰጠችውን ማኅበረ ቅዱሳንን ከዓለም አቀፍ ጽንፈኞች ጋራ እያመሳሰሉ መወንጀላቸው ተገቢ እንዳልኾነና የማኅበሩ አገልግሎት ለቤተ ክርስቲያን አስፈላጊ እንደኾነ ቅዱስ ሲኖዶሱ አረጋግጧል፡፡
‹‹ቆራጣ ደብዳቤ ይበቃዋል፤ ከመንግሥት ጋራ በመተባበር እስከ ጫፍ አድርሱልን፤ በቶሎ ቁረጡት›› እያሉ መጠየቅ፤ ሊቃነ ጳጳሳቱንም “ከፈለጉ ቆባቸውን አስቀምጠው ወደዚያው ይግቡ” እያሉ መዝለፋቸውስ በምን መመዘኛ ነው ዴሞክራሲያዊና ሕገ መንግሥታዊ የሚኾነው በማለት የሚገልጹ የስብሰባው ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ ፓትርያርኩ የውሳኔውን አፈጻጸም ማገዳቸው፣ አድሏዊ እንደሚያደርጋቸውና በካህናቱና በምእመናኑ ዘንድ መንፈሳዊ አባትነታቸውንና ታማኝነታቸውን ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባው እንደሚኾን ጠቁመዋል፡፡

ቃሊቲ እስር ቤት የሚገኙ እስረኞች ባልታወቀ ምክንያት ‹‹ከማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ታዘን ነው›› በሚሉ የፌደራል ፖሊሶች እቃቸው በድንገት እንደተበረበረና እንደተወሰደ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡

ዛሬ እሁድ ታህሳስ 12/2007 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ቃሊቲ እስር ቤትና አካባቢው በበርካታ የፌደራል ፖሊሶች ተከቦ እንደነበር የገለጹት ምንጮቹ ባልታወቀ ምክንያት የሁሉም እስረኞች እቃ በድንገት የተበረበረ ሲሆን በተለይም ፖለቲካ ነክ ጽሁፎች የሰፈሩባቸው ማስታወሻዎችና ሰነዶች መወሰዳቸውን ከእስረኞቹን ጠይቀው እንደተረዱ ምንጮች ገልጸውልናል፡፡

ፖሊስ ባደረገው ብርበራም የታዋቂው ጋዜጠኛ እና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ከ30 በላይ ገጽ የፖለቲካ ትንታኔ ጽሁፎች፣ እንዲሁም የአንዱ ዓለም አራጌ ማስታወሻዎች መወሰዳቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፖሊስ ማስታወሻዎችንና ሌሎቹንም የእስረኞቹን ንብረቶች እያስፈረመ የወሰደ ሲሆን እስከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ድረስ እስር ቤቱ አካባቢ በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት እንደነበሩ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አክለው ገልጸዋል፡፡
Image

“የታዛቢዎችን ምርጫ ለማወክ ተንቀሳቅሳችኋል::” – ፖሊስ ===== Minilik Salsawi
ዛሬ በየቀበሌው የሚካሄደውን የታዛቢዎች ምርጫ ተከትሎ ወደ ሚኖሩበት ጉለሌ ክፍለከተማ ወረዳ 3 ያመሩት የሰማያዊ አባላቶቹ ኢየሩሳሌም ተስፋው እና እመቤት ግርማ የታዛቢዎችን ምርጫ ለማወክ ተንቀሳቅሳችኋል በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የምርጫ ታዛቢ መሆን የሚችሉት ገለልተኛየሆኑ እንጂ የኢህአዴግ አባላት የሆኑ አይደሉም በሚል ባነሱት ክርክር ምክንያት ለማወክ እየሞከራችሁ ነው በሚል ፖሊስ ሊይዛቸው ችሏል፡፡

Image

ሞክረው ( ሄኖክ የሺጥላ )

ትናንት ባህርዳር ላይ አማሮች ተገደሉ ፣ ከትናንት በስትያ አምቦ ላይ ኦሮሞዎች ፣ ከዛ በፊት ጋምቤላ ላይ ፣ ከዛ በፊት አርባ ጉጉ ላይ ፣ ከዛ በፊት በደኖ ላይ ፣ እያለ እያለ ይቀጥላል ። በዘር የከፋፈልነው ሬሳ ኢትዮጵያዊ መሆን ያቃተው ለምን እንደሆነ ባላውቅም አንተ አዛኝ ቅቤ አንጉዋች ግን ምን ታመጣለህ ። ግፋ ቢል ሁለት ገጽ የ ፒዲ -ኤፍ ( PDF ) መግለጫ ታወጣለህ ፣ ትንሽ ትዝታለህ ፣ ትንሽ ትሳደባለህ ፣ አይቀርም በቅርብ ምናምን ብለህ ተስፋ ትሰጣለህ ፣ ግድያው ይቀጥላል ።

ውስጥ ውስጡን የሸዋ አማራ ለኢትዮጵያ ጂው ነው ፣ ወይጦው ጅን ነው ፣ ጎጃሜው አድር ባይ ነው ፣ ጎንደሬው ሲፋቅ ትግሬ ነው ፣ መንዜው በጥርሱ እየሳቀ ገዳይ ነው ፣ ወዘተ ወዘተ ትላለህ ። ውጭ ውጩን የአማራ ታጋይ!!!
ኦሮሞውም ጋ እንዲህ ነው ፣ ወለጋ ኮለል ያለ የጠራ ኦሮሞነት መስፈሪያ ነው ፣ የሰላሌ ኦሮሞ አማራነት ያለቀቀው ኦሮሞ ነው ፣ የሸዋ ኦሮሞ ኦሮሞ አይደለም ፣ የባሌ ኦሮሞ ለ አረብነት ይቀርባል እና ወዘተ፣ ውስጥ ውስጡን ልብህን ያደነደነው ነገር ነው ። ዝለዚህ ከዚህ በሽታህ እስካልዳንክ ድረስ ግድያው ይቀጥላል ፣ አንተም መግለጫ እየሰጡ መኖሩን ትቀጥላለህ ።

ስልጤውም ጋ ፣ ሶዶ ጎርደናውም ጋ ፣ ሰባት ቤቱም ጋ ፣ ቅማንቱም ጋ ( ቅማንት የሚባል ነገር ካለ ) ፣ ይሄ በሽታ አለ ። ይሄን በሽታህን ፣ ይሄን የመከፋፈል ነቀርሳህን ሳትድን ፣ ከቁጭት ውጭ ምንም አታመጣም ። አንዳች ለውጥ በሀገርህ ምድር አይፈነጥቅም ።

እስኪ አምላክ ያሳይህ ትናንት በ ሰሜን ጎንደር ቅማንት እራሱዋን በራሱዋ ታስተዳድር ዘንድ አንዳንድ ሽር ጉዶች እየተደረጉ እንደሆነ ሰማን ፣ መቼም መስማት እምቢ አይባልም ፣ ከመሃል ጎንደር እስከ መተማ ጎንደር ልጆቿን ልትበላ ይኸው ሌላ ውርጅብኝ ሊወርድባት ነው ። አንተ ግን ይሄን ሁሉ የሚያረገው ከትግሬ ክፍለ ሀገር የመጣ ከይሲ ስርዓት ነው ማለት ልብህ ይፈራል ።ጠላቶችህን በስማቸው ለመጥራት ልብህ ይራራል ።

ሌላም ታሪክ ልንገርህ
ጅማ ላይ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያስቀድሱ የተገደሉትን ሰዎች አይተካል ፣ ታዲያ ማን ይመስልሃል ገዳዩ ? ኦሮሞዎች ? አይደለም ! አየህ ያንተ ችግር ይሄ ነው ወያኔ እንድታስብ የሚፈልገውን ነው የምታስበው ፣ ግድያውን የፈጸሙት ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ ፣ ድርጊቱን ያሴረው ግን አሁንም የትግሬ ወያኔ ነው ፣ ወንድም በወንድሙ ላይ እንዲነሳ ያደረገው ። ጅማማ እኮ ጂማ! የሰቃ ጨቆርሳ ሀገር! የጌራ ሀገር! የጉማ ሀገር! የጎማ ሀገር! የሊሙ ሂናሪያ ሀገር! አምስቱ የጊቤ መንግሥታት የለመለሙባት ምድር!!
ጅማ! የአባ ሚዛን ሀገር! የአባ ቆሮ ሀገር! የአባ ገንዳ ሀገር! የአባ ዱላ ሀገር! በኦሮሞ ምድር የዘመናዊ ቢሮክራሲ ጥንስስ የተጀመረባት ሰፈር!
ጅማ! የአቦል ሀገር! የበረካ ሀገር! የቃህዋ ጀባ ሀገር! ለስምንት መቶ ዓመታት ተወዳጅነቱ ሳይቀንስ የዘለቀውን “ቡና”ን ለዓለም ያበረከተች የሙሐባ መንበር!! ጅማ! የተሚማ ሀገር! የገሜቲ ሀገር! የአያንቱ ሀገር! የአስሊያ ሀገር! የበድሪያ ሀገር! የፈይሩዝ ሀገር! ውብ ልዕልታትና ወይዛዝርት የወጡባት ምድር!! ነች ይላታል ጸሐፊው ፣ ጅማ ይህንን አታደርግም ፣ ጅማ ላይ አታቂም ፣ አይንህን ወደ ሰሜን ፣ ልብህን ወደ ትግሬ ወያኔ አዙር !

ይገሉሃል አንተ ግን ባጉል ፍቅር ታጥረሃል ፣ ያጠፉሃል አንተ ግን የትግሬ ወያኔ አጥፊህ መሆኑን መናገር ትፈራለህ ፣ መነኩሴ በጥይት ሲመቱ አንተ ዘረኛ እንዳትባል ትፈራላህ ፣ ሀጻናት ሲገሉ አሁንም በስማቸው ለመጥራት ትፈራለህ ፣ ማን እንደሆኑ እያወቅህ ” እነ አከሌ ” ለማለት በጣም ትፈራለህ ፣ በልብህ ትታበያለህ ፣ በአንደበትህ ትስታለህ ፣ በልቦናህ ግን ከራስህ ጋ ትነጋገራለህ ። ጠላትህን በስሙ እስካልጠራኸው ድረስ አታሸንፍም ፣ ጠላትህን እስካላስገለልከው ድረስ በፍጹም ነጻ አትሆንም ። ገዳዮችህ ሩቅ አይደሉም፣ ብዙዎቹ ያንተ ጎረቤቶች ናቸው ፣ ካንተ ጋ እየበሉ ፣ ካንተው ጋ እየጠጡ የሚውሉት የትግሬ ወያኔዎች ናቸው ይሄን ሁሉ በደል እያደረሱ ያሉት ፣ ይሄንን አንተ አታውቅም ብዬ አላስብም ፣ እርግጥ በደንብ ታውቃለህ ግን እውቀትህ ከውስጥ የማይወጣ የጋን መብራት አይነት ሆነብኝ ፣ ጠላትህ ለመለየት አተኩረህ እየው ( ግንባሩን እየው አላልኩም ) ግንባሩ ፍንጭ ከሰጠህ ማየት መብትህ ነው ፣ ግን አተኩረህ ካየኸው ታውቀዋለህ ። እሱ አንተን ለማጥፋት አንዳች ይሉኝታ የለውም ታዲያ ያንተ የሉኝታ ከወዴት የመጣ ይሆን ። ነገርኩህ እኮ እነሱ ( የትግሬ ወያኔዎች ) ሊገሉህ ኢያሰቡም እንኩዋ ይወልዱልሃል ። ግማሹ ጦርነት ጠላትን ማወቅ ነው ይላሉ አንዳንድ አዋቂዎች ፣ ይህ ትልቅ እውነት ነው ፣ የተቀረው ግማሹ ደሞ ጦርነት መግጠም እንዳይመስልህ ፣ የተቀረው ራስን ማወቅ ነው !

ጠላትህን እስካለየህ ድረስ ጠላትህን አታሸንፈውም ! ይሄ የ ስደት ፖለቲካውን እርሳው ፣ ለአፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል ነው ፣ አንተ ግን ጠላትህን በስሙ ጥራው ። የትግሬ ወያኔ ጠላቴ ነው በል ፣ እሱን ማለት ስትጀምር ማሸነፍ ትጀምራለህ ። ሞክረው! ሞክረው ! ሞክረው !

በመግለጫ ነገር መወራወር የጀመሩት የተቃዋሚ ፓርቲእ አንድነት እና የወያኔው ምርጫ ቦርድ መላተም መጀመራቸውን ከዙሪያቸው የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ በዚህም መሰረት የኢሕአዴግ ተቋም የሆነው የምርጫ ቦርድ አንድነት እና መኢአድን ከ2007 ምርጫ ውጪ ለማድረግ ዳር ዳር እያል ነው ሲሉ አንድ የአንድነት ከፍተኛ አመራር ጽፈዋል:: ከፍተኛ አመራሩ በጽሁፋቸው እንዳሉት የኢህአዴግ ጎፈሬ ከማበጠር ውጪ ምንም ፋይዳ የሌለው “የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ” አንድነትንና በመኢአድን በምርጫው እንዳይወዳደሩ ለማድረግ ላይና ታች እያለ ይገኛል ያሉት አመራሩ እነዚህ ፓርቲዎች ባለፈው ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም. ውህደት ለመፈፀም ተስማመተው የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰው የነበረ ቢሆንም፤ ውህደቱን የከለከለውና እንዲሰናከል ያደረገው ይሄው ምርጫ ቦርድ ተብዬው የመሸጦ ተቋም ነበር። በማለት በጽሁፋቸው አስፍረዋል::

አሁን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ግልፅ እየሆነ ያለው ነገር የዚህ ምርጫ ቦርድ ዋና ዓላማ ፓርቲዎች ተጠናክረው እንዳይወጡ መከላከልና የኢህአዴግ ወንበር መጠበቅ እንደሆነ ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም።ያሉት አመራሩ አያይዘውም ከእንግዲህ ይለይልናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል::

ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ከአሁኑ እንዲጀምር እድል ተፈጥሯል ማለት ነው። አሁን ነው ወገብን ጠበቅ አድርጎ አመራር ለመስጠትና ለመታሰር ዝግጁ መሆን የሚያስፈልገው። እኛ የምንችለው ሁሉ አድርገናል ከዚህ በኋላ የፈለገው ቢሆን የሚፀፅተን ነገር አይኖርም።ሲሉ ህዝቡ ለህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲዘጋጅ እድሉን እንዲጠቀምበት መሪ በመሆን የሚፈለግባቸውን ድርሻ ለመወጣት ፓርቲያቸው መዘጋጀቱን አሳውቀዋል::

የአንድነት አመራሩ እንዳሉት ፓርቲዎቹ በምርጫው እንሳተፋለን ሲሉ፤ ምን አስበው ነው ተብሎ የለም አትሳተፉም የሚባል ከሆነ ይህን መብታቸውን ለማስጠበቅ ተባብረው ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ማካሄድ ግድ ይላቸዋል ማለት ነው። መቼም ዘንድሮ በኢህአዴግ ቤት ማሰቢያው ጨርሶ እንደጠፋ ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም፤ እዚያ ቤት ግን የተፈጠረው ነገር ምን ይሆን? ሲሉ ጽሁፋቸውን ድል የህዝብ መሆኑን በመግለጽ አጠቃለዋል::
Image

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የ2ዐዐ7 ዓ.ም አገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍና ለዚህም መተማመኛው ሕዝቡ መሆኑን ገልፀ ‹‹ተደራጅ 2007 ለለውጥ›› በሚል መፈክር አንግቦ አገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትና ኢህአዴግን በቃህ ለማለት ሌት፣ ከቀን በንቃትና በትጋት እየሠራ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት ነፃ ሚዲያ በታፈነበትና በተዘጋበት አንድነት የራሱን የማተሚያ ማሽን ገዝቶ በየጊዜው ሆን ተብሎ በሚመስል መልኩ በሚጠፋው የኤሌክትሪክ ችግርን ለማሸነፍ የራሱን ከፍተኛ ኃይል ያለው ጀነሬተር በመግዛት በሣምንት የራሱን ጋዜጦችን እያተመ እያንዲያሰራጭ ተገዷል፡፡ ምሁራን፣ ወጣቶች፣ ጋዜጠኞችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለወሳኑ የ2ዐዐ7 ምርጫ ትግል እየተቀላቀሉት ይገኛሉ። አንድነት በአሁኑ ሰዓት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉን በአግባቡ ለመምራትና ለውጥ ለማምጣት በተሻለ ቆመና ላይ ነው ያለው።

በምርጫ ቦርድ በአንድት ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ሆነ በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ የሌለውን የጠቅላላ ጉባኤ አባላትና የምላተ-ጉባኤ ቁጥር በተሻሻለው ደንባችን ውስጥ እንድናካትት የተወሰነብንን ፈርድ ገምድል ድርጊት ሕገ-ወጥ መሆኑን ብናውቀውም ጠቅላላ ጉባኤ መጠራትን እንደ ጉዳት ሳይሆን አንደ ልዩ እድል በመቁጠር፣ 32ዐ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት በመጥራት የምርጫ ቦርድ ተወካይ በተገኘበት የተሳካና አንፀባራቂ ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደናል፡፡ የጠቅላላ ጉባኤውንም ሰነድ ታህሣሥ 1ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም ለምርጫ ቦርድ ገቢ ተደርጓል፡፡

ሁሉ እንደሚገነዘበው በአሁኑ ሰዓት ሕዝቡ በኑሮ ውድነትና በሥራ እጦት ከመሰቃየቱም በላይ ሙስና ሰፍኗል፤ መልካም አስተዳደር የሕግ የበላይነት ከቶውንም ጠፍቷል፡፡ የሕዝብ የነፃነትና የዴሞክራሲ ጥያቄ ገዝፎና አፍጥጦ እየመጣ ነው፡፡ በመሆኑም ኢህአዴግ በፍርሃትና በጭንቀት እየራደ ነው፡፡ ምረጡኝ ብሎ ሕዝብ ፊት ለመቅረብ የሚያስችለው የፖለቲካና የሞራል ኃይል ስለሌለው ውሸት፣ ማስፈራራት ማሰር መግደል ማሸነፊያ መሣሪያዎች እንዳልሆኑትም በግልጽና በትክክል ተደራጅቷል፡፡ አሁን የቀረው ማሸነፊያው መንገድ አንድነት ፓርቲን በመዝጋት ነው የሚል ድምዳሜ ላይ በመድረሱ ጥንቱንም የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች የሆነውን ወኪሉን በመጠቀም በአንድነት ላይ ዘመቻ ከፍቷል፡፡

ታህሣሥ 1ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓም በምርጫ ቦርድ ከፍተኛ አመራር የተሰጠው በቅጥፈትና በውሸት የተሞላው መግለጫም የሚያሳየውና የሚመሰክረው ይህንኑ ነው፡፡ ነገር ግን እውነቱን በአጭሩ እንደሚከተለው እናስቀምጣለን፡፡

አንድነት ፓርቲ ታህሣሥ 19 እና 2ዐ ቀን 2ዐዐ6 ዓም ያካሄደውን የጠቅላላ ጉባኤ ሰነድ ለምርጫ ቦርድ ካስገባ በኋላ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 2ዐ ቀን 2ዐዐ6 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ በዘጠኝ ነጥቦች ላይ ማብራሪያ እንድንሰጥ ጠይቄን መልስ ሰጠን፤ በመቀጠልም ጥቅምት 2ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄ ከዘጠኝ ወደ ሦስት አውርዶ ላከልን ለዚህም አንድነት መልስ ሰጠ፡፡ ቀጥሎም ቦርዱ ህዳር 1ዐ ቀን 2ዐዐ7 በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄውን ወደ አንድ አወረደው እንዲያውም በመጨረሻ ህዳር 19 ቀን 2ዐዐ7 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ፡፡ ‹‹ፓርቲው በሰጠው ምላሽ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ብዛት 32ዐ እንደሆነ አሳውቋል፡፡ ይሁን እንዷ በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ አካቶ ያላቀረበ በመሆኑ ይህንኑ አሟልታችሁ እንድታቀርቡ በአክብሮት እናሳውቃለን›› የሚል ነው፡፡ እኛም ጠቅላላ ጉባኤ ጠርተን ይህንኑ ጥያቄ እንዲሟላ ከማድረጋችንም ባሻገር በሕገ-ደንባችን መሠረት በብሔራዊ ም/ቤት ተመርጠው የነበሩት የፓርቲውን ፕሬዚደንት ሹመት በጠቅላላው ጉባኤ አፀድቀናል፡፡ እንጂ አይነቱን በሕገ-ደንቡና በሥነ-ሥርዓት ለተከናወኑ ጉዳዮች ያልተገባና የተሳሳተ መግለጫ መስጠት በጣም አሳኝ ነው፡፡ በተለይም የሕዝብ ታዛቢዎች ታህሣሥ 12 ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም እንደሚመረጡ እየታወቀ ይህን ዓይነት መግለጫ መስጠት ሕዝቡ በጥንቃቄና በተደራጀ ምልኩ ትክክለኛነትና ሀቀኞች የሆኑ ታዛቢዎችን እንዳይመርጥ ለማሰናከል የታቀደ ይመስላል፡፡ በመሆኑም ዛሬም ሆነ ነገ አንድነት ፓርቲ ከሕዝብ ጋር ሆኖ ትግሉን አጠንክሮ ይቀጥላል አባላትም ሆነ ሕዝቡ ከፓርቲያችን ጎን ተሰልፎ ትግሉን እንዲያጧጡፈው ከአክብሮት ጋር እንጠይቃለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
ታህሣሥ 11 ቀን 2ዐዐ7 ዓም
አዲስ አበባ

Image

ህ.ወ.ሐ.ት 40ኛ ዓመት በዓሉ ለማክበር እያደርገው ያለው አከባበር ከመግለጼ በፊት የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች ለምን የትጥቅ ትግል መረጡ የሚለውን ትንሽ ለአንባብያን መረጃ ሰጥቼ ልለፍ፡፡ ህ.ወ.ሐ.ት የመሰረቱ ሰዎችና የትግራይ ወጣቶች ነፍጥ አንስተው ደርግን በጦርነት አስወግደው የደርግን ስርዓት ለመለወጥ የተነሱበት ዋናው ምክንያት ደርግ ዘውዳዊውን ስርዓት አሰወግዶ በትረ-ሥልጣኑ የጨበጠው ራሱ ታግሎ ያመጣው ለውጥ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሙሁራኖች፣ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች፣ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ አረሶ አደሮች፣ ወዝ አደሮች፣ የመንግስት ሰራተኞች ወ.ዘ.ተ በተደራጀና ባልተደራጀ መንገድ ያነሱት ዲሞክራሲያዊ ጥያቄ ዘወዳዊው ስርዓት ሊመልሰው ሰላልቻለ የበሰበሰው መዋቀሩ በመፍረክረኩ ደርግን ያን አጋጣሚ ተጠቅሞ ስልጣኑን ሊጨብጥ አስቻለዉ፡፡

እነዛ ዲሞክራሲያዊ ጥያቄ አንስተው ፤ዘውዳዊው ስርዓት ያፍረከረኩ ወገኖች ደርግ በግብታውነት በትረ ስልጣኑን በመያዙና እነዚ የህዝቦች ዲሞክራሳያዊ ጥያቄዎች ደርግ በሚድያና በዲኘሎማሲ በመደናገር የህዝባችን ጥያቄ በመቀልበስ ፀረ-ዲሞክራሲያዊ የሆኑ አምባገነን አዋጆች በማወጅ ህዝባዊ ማዕበሉን በማፈን ሁሉም ዓይነት ጥያቄዎች ገና በጥዋቱ ማፈን ጀመረ፡፡

ደርግ የአምባገነንነቱና ፋሽስታውነቱም መግለጫ የዘውዳዊው ስርዓት ከ60 በላይ ሚንስትሮች ፡ ጀኔራሎች በመሰበሰብ በጥይት ደብድቦ ገደላቸው ፤ የህዝቦች ሰለማዊ ትግል ደርግ በዜጎች ደም ታጥቦ ትግሉን አኮላሸው፡፡ በዚህም ምክንያት በኢትዮጵያ ህዝባዊ መንግሥት ሊመሰረት አልተቻለም፡፡ መድበለ-ፓርቲ ፡ ዩንር፣ሁሉም ዓይነት ዲሞክራሲያዊ መብቶች፣ የሃይማኖት ነፃነት፣ ፍትህና የህግ የበላይነት ይከበር፡ የሚሉ ጥያቄዎች መልሳቸው ልክ አሁን የህ.ወ.ሐ.ት/ኢህአዴግ መንግሥት እያደርገው ያለው ዓይነት እምቢ ላለሰው፤ እሰረው ፡ ግረፈው፡ ግደለው፡ እንደሚለው ያለው ደርግም እምቢ ላለሰው ጥይት አጉርሰው ብሎ አወጀ የህዝቦች ጥያቄዎች አፈናቸው ፡፡
በዛን ግዜ የኢ/ያ ህዝቦች በተለይ በንቃተ ህሊና ትንሽ መጥቀው የነበሩ ሙሁራንና ሰራተኛች በደርግ ስርዓት ሰለማዊ ትግል ለማድረግ አይቻልም በማለት በረሃ ወጥተው የትጥቅ ትግል ለማከላሄድ ወሰኑ፡፡ አንዳ አንዶቹም ደርግ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በከተማ ነውጥ ነው ማስወገድ የሚቻለው በማለት የነውጥ ስትራቴጂ መርጠው መንቀሳቀስ ጀምረው ነበር፡፡ በሌላ በኩል ከደርጎን በመሆን በጎ በጎውን መንገድ እንዲከተል መንገድ በማሳየት ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ማድረግ ይቻላል አሉ፡፡ ይህ የዘመኑ ሙሁር የየራሱ የተለያየ ፍልስፍና በመያዝ በየፊናው በመዝመት በአንድነት ታግሎ ዲሞክራሲያዊና ህዝባዊ መንግሥት የመመስረት የህዝቡን ተስፋ አጨለመበት፡፡ በአንፃሩ የዚያን ጊዜ ሙሁራን በየፊናቸው ተደራጅተው በሃገራዊና ብሄራዊ ጥያቄ ሥር ብዙ ፀረ-ደርግ የፖለቲካ ኃይሎች ተመሰረቱ፡፡
ከነዚህ ውስጥ የትጥቅ ትግል ስትራቴጂ ከመረጡት ውስጥ አንዱ ህ.ወ.ሐ.ት ነበር፡፡ በህቡዕና በግልፅ ተደራጅቶ በየካቲት 11/06/1967ዓ.ም በ11 ሰዎች በረሃ ደደቢት ወጥቶ የጥቅ ትግል ጀመረ ፡፡ እኖሆ ህወሐት ዘንድሮ 40ኛ ዓመት የልደት በዓሉ ለማክበር ሸርጉድ እያለ ይገኛል፡፡
ህ.ወ.ሐ.ት ዩዞዋቸው የተነሳ ዓላማዎች፡-
አባገነኑን ፋሽስታዊ ደርግን በማስወገድ ህዝባዊ መንግሥት መመስረት፡
የመድብለ-ፓርቲ ስርዓት እንዲኖርና በነፃ የመደራጀት፣ ነፃ የምርጫ ውድድር መኖር እንዳለበት፡፡
የብሄራዊ መብት የራስን ዕድል በራስ መወሰን ዕድል እንዲይኖር ፡፡ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ መሆኑ፡፡
ብሄራዊ ትግል እንደ የሰልት ትግል ተጠቅሞ መደባዊ ትግሉን እዳር በማድረስ ለኢትዮጵያ አንድነትና እኩልነት መታገል ፡፡
የገጠርና የከተማ መሬት የህዝብ መሆን እንዳለበት፡፡
በፖለቲካም ማርክሰሌኒናዊና ማአዘዲንጋዊ ስነ ሃሰሳብ መመሪያው እንደሆነ፡፡
የአብዮቱ ጠላተች፤ ፉሽስታዊ ደርግ፣ መስፍናዊ ስርዓት፣ ሃብታም ገበሬ ፡ ሃገራዊ ባለ ሃብት፣ ከፍተኛ ሙሁርና ኢንፔርያሊዝም እንደሆኑ ፡፡

ከላይ የተጠቀሰው የኃይል አሰላለፍ በፅሁፍ ተሰንዶ በማኒፈስቶ ደረጃ የተቀመጠ አልነበረም፡፡ እንዲሁ በሰመበለው ነበር የሚነገረው ፡፡ እላይ የተዘርዘረው አÌም የህ.ወ.ሐ.ት አÌም ሆኖ አልቀጠለም ፡፡

በ1968 ዓ.ም አጋማሽ አከባቢ ግን አንድ አስደንጋጭ አÌም ተያዘ፡ ይህ አÌም ታጋዮች ተዋይተውበት ወይም በድርጅቱ በጉባኤ ቀርቦ የፀደቀ አልነበረም፡፡አማራሩ አስቦበት አትለው በግብታውነት አትለው የመጣ አቋም ነበር፡፡ ለታጋዩ፣ ለኢ/ያ ህዝብና ለሌሎች ፖለቲካዊ ድርጅቶች ግን ድንገት ነበር፡፡

ትግላችን ከአማራ ቀኝ ገዥዎች ነፃ ለመውጣት (ነፃ ሪፓብሊክ ትግራይ ለመመስረት) ነው ብለው በትግርኛ፡ በአማርኛ፡ በእንግሊዘኛ የተፃፈ፡ በነ አቶ ስዩም መስፍን ፡መለስ ዜናዊ ፡ ስብሃት ነጋ፡፡ በሙሉጌታ ሓጎስና በሌሎችም የተጻፈ ሥዩም መስፍን ሱዳን ሄደ በመጽሐፍ መልክ አሳትሞ ወደ አገር ገብቶ ለተጋዮችና ለከተማ ደጋፊዎች ለውጭ አገርም እንዲሰራጭ ተደረገ በቃ የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች ጠባብነት ፀሐይ ላይ ወጣ ፡፡
የዚሁ ማኒፌስቶ በቅድምያ የተቃወመ ኢ.ህ.ኣ.ፖ ነበር፡ ቀጥሎ ትንሽ ቀለም በቆጠሩ ታጋዮችና በከተማ ደጋፊዎች ትልቅ ተቃውሞ አገጠመው ፡፡ ጥያቄ ላነሱ ታጋዮች በተለይ ከ1969 ዓ.ም እስከ 1970 ዓ.ም እርምጃ ተወሰደባቸው፡፡ ብዙ ታጋዮች እየሸሹ ከተማ ገቡ፡፡ ዕድል ያገጠማቸውም ወደ ሱዳን ሸሹ፡፡ትላትና በኢ/ያ የመደብለ-ፓርቲ መኖር አለበት የሚል አÌም የነበራቸው የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች በሰሜን ኢ/ያ ለነበሩ ፀረ-ደርግ ኃይሎች መጀመርያ ግንባር ገድሊ ሓርነት ትግራይን (ግ.ገ.ሓ.ት)መቱ፡፡ ቀጥለው ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ ጣራናፊት ኮሚቴ አጠፉ፡፡በመቀጠልም የኢ/ያ ዲሞክራሲያዊ ህብረት(ኢ.ዲ.ህ እና ኢ.ህ.ኣ.ፖ) ግዝፎች ኃይሎች ተዋጡ፡ በድርጅቱ ውስጥም ጦርነቱንና ጠባብነቱንና የተቃወሙ፣የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ አይደለም ብለዉ የተማጎቱ ጅግኖቹም እንደዚህ ተዋጡ፡፡ በቃ የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች ፀረ-መደብለ-ፓርቲና ፀረ-ዲሞክራሲ መሆናቸው ተጋለጠ፡፡ ግን ደግም ፋሽስታዊ ደርግ በትግራይ ህዝብ ጠላትና ወዳጅ ሳይለይ በማከናይዘድ፣ በእግረኛ ወታደር፣ በአየር በጋዝና በናፖልም መርዝ በመጠፍጨፉ ህዝቡ የሩቅ ጀብ ከሚበላኝ የራሴን ጅብ ይብላይኝ በሚል ህዝቡ ዕድሜ ፡ፆታና ሃይማኖት በማይለይ ከህ.ወ.ሐ.ት ጎን ቆሞ ልጆቹ ወደ ትጥቅ ትግሉ እንዲዘመቱ፣ ገንዘቡና በሁሉም ዓይነት ሀብቱ ህ.ወ.ሐ.ትን ለመደገፍ ተነሳ ፡፡
የትግራይ ህዝብ ግን ምንም እንኳን ከደርግ ህ.ወ.ሐ.ት ቢወድም ፡ ህ.ወ.ሐ.ት በጣባብነት አÌሙ የኤርትራን የቅኝ ግዛት ጥያቄ መደገፉ የሻአብያ ካድሬ ሆኖ መንቀሳቀሱ፣ይባስ ብሎ ሻአብያን ከደርግና ከጀብሃ ለመከላከል በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣት ታጋዮች ወደ ሳህል በረሃ በማዝመቱ አምርሮ ይተጋለውና ይቃወመው ነበር፡፡ በዚሁ ተቃውሞ ምክንያት አድመኞች ተብለው እርምጃ የተወሰደባቸው እጅግ ብዙ ፡ አርሶአደሮችና የከተማ ነዋሪዎች ነበሩ፡፡
የትግራይ ህዝብና የህ.ወ.ሐ.ት የልደት በዓል የካተቲት 11፡-
ከላይ እንደዘረዘርኩት ደርግ ጠላትና ወዳጁ ሳይለይ ይጨፈጭፈው ነበር፡፡ የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎችም ያ ጠባብነትና ፀረ-ዲሞክራሲ ባህሪያቸው የህዝብና የተጋዮች ፊት ያሰጋቸው ስለነበር ስግተው ጠባያቸው በመቀየር ብዙ ስለት ይገቡለት ነበር ፡፡ የካቲት 11 የትግል ቀን በመሆኑና ብዙ መስዋእት ስለከፈለበት በዓሉ ሲከበር ከሚወደው አምላክ በማይተናነስ ሁኔታ የየአመቱን በዓል በበለጠ አምልኮት (እምነት) በማሳደር ቤቱ ያፈራውን ሁሉ አይነት የሚበላ የሚጠጣ በመዘጋጀት በሰለማዊ ሰልፍ ልጆቹ በመመልመል ልብስና ቀለብ በመስጠት ወደ ወታሃደራዊ መሰልጠኛ (02) የሚሸኝበት ግዜ ነበር ፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያትም የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች በዛን ግዜ ቃል የገቡለት ሰለት ከድተው ራሳቸው፣ ልጆቻቸውና ዘር-መንዘራቸው ሃብት መካበት፣ምርጥ ቪላዎችና ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ባገር ውስጥና በውጭ ሰርተው የሃገራችን ዶላር እየዛቁ በውጭ ባንኮች አስቀምጠው ለክፉ ቀን እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ ያን ግዜ በታጋይነት ጊዜ፣የመሴ ደቀመዝሙር በነበሩበት ጊዜ፤መድረክ ወጥተው በካድሬዎቻቸውና ራሳቸው ሲናገሩ ህ.ወ.ሐ.ት ደርግ አስወግዶ ባጭር ግዜ የህቡን ችግር ይፈታል የሚል እምነት የሚያሳድር ነበር፡፡ ነገር ግን ህወሐት ቃሉና ተግባሩና ለየብቻ ሆኖ ቀረ፡፡ ህዝቡ ልጆቹን መርቆ ለመስዋእትነት ሲልክ የስደት ፡የድህነት፡ የስራ አጥነት ችግሮች መፍትሄ አግኝበታሎህ ብሎ ተስፋ በመጣል ነበር፡፡ ነገር ግን ህዝቡና ታጋዩ አንድ ያልተገነዘበው ነገር ነበር፡፡እነዚህ የህወሐት ቁንጮ አመራሮች ማንነት በምንመረምርበት ጊዜ ለህዝብ ጥቅም ለመቆም ምንም ምክንያት(background)የላቸውም፡፡ የነሱ ወደ ትጥቅ ትግል መግባት የአባቶቻቸው ስልጣን አሻሽለው ራሳቸውን ገዥዎች ለመሆን አስበው የተነሱ “ታጋዮች” ናቸው፡፡ ስለሆነም ነው አሁን በመቶ ሺ የወጣቱ መስዋእትነት ስልጣን ላይ ወጥተው የአገር ለአላውነት መደፈር፡ የሰብኣዊ መብት ረገጣ ፡ የህግ በላይነት አለመኖር፣ ባጠቃላይ በአገሪቱ በመድብለ-ፓርቲ ስርዓት፣ የዲሞክራሲያዊ መንግሥት መመስረት የቃል መፈክር ሆኖ እንዲቀር ያደረጉት፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ ውድድር ህዝቡ በነፃ የመሰለውን የፖለቲካ ፓርቲ መርጦ መንግሥት እንዳይመሰርት የከለከሉት የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው ስልጣን አሳልፈው ላለመስጠት ነው፡፡ የካቲት 11/1967 ዓ.ም በረሀ ሲገቡ ይህንን ድብቅ ዓላማ ከ4 የአንጎላቸው ክፍል በአንዱ ሥር አስቀምጠው ነበር ሲንቀሳቀሱ የነበሩት፡፡ በትጥቅ ትግሉ ለህዝብ የቆሙ፣ብቃት የነበራቸው ታጋዮች የአሁኖቹ አመራሮች የአባቶቻቸው የስልጣን ኮርቻ ላይ እንዳይወጡ ስጋት ሁነው ስለተገኙ በትጥቅ ትግሉ እንዲቀጥሉ አልተፈለገምና እንዲወገዱ ተደረገ፡፡ ህዝቡ የካቲት 11 የሁሉም ነገር መፍትሔ ናት ብሎ ያምን ነበር፡፡ነገር ግን የካቲት 11 ደርግ ደምስሳ ሰላም፣ ፍቅር፣ የኢ/ያ አንድነት ማረጋገጥ አልቻለችም፡፡ የ17 ዓመት ሙሉ የትጥቅ ትግል፣የመቶ ሺዎች ወጣቶች መስዋእነት ለፊውዳል ልጆች የአባቶቻቸውና የአቶቻቸው ስልጣን እንዲረከቡ አስቻላቸው፡፡ ህዝቡ የካቲት 11 ሲያ ከብር ቀደም ብሎ ከልቡ በመነጨ ፍቅር ነበር የሚያከብራት፡፡ ሁኔታው ቀስ በቀስ እየተረዳው ሲመጣ ግን ዕለቱን ለማክበር ድርጅቱ ህዝቡን በማስገደድ እንዲያከብር ያደርገው ጀመር፡፡ህወሐት/ኢህአዴግ ስልጣን ላይ የወጣው በኃይል በማሸነፍ እንጂ በሐሳብ በማሸነፍ( defeat not win) ስላይደለ የህዝብ መብቶች ማስከበር አይችልም፡፡

የህ.ወ.ሐ.ት 40ኛ የልደት በዓልና የትግራይ ህዝብ፡-
የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች በአፈቀላጤዎቻቸው አማካኝነት ባለፉት 24 ዓመታት የስልጣን ዘመናቸው በኢ/ያ ፍትህ፣ የህግ የበላይነት፣ የዜጎች ሰብኣዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተከብረዋል፣ የብሄር ብሄረሰብ መብት የራስን እድል በራስ የመውሰን መብት ተከብረዋል፡፡ የታገልንበት መደብለ-ፓርቲ ህልውና በኢ/ያ ተረጋግጣል ፡፡ ነፃ የምርጫ ኮሚሽን፣ የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን፣ የእንባ ጠባቂ ኮሚሽን ተÌቁማል፡፡ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተÌቁማል ፡፡ የነፃ የፍትህ አካላት ተመስርተዋል ይሉናል፡፡
በኢኮኖሚም በአለም ደረጃ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ ለመድረስ ተቃርበናል ፡፡ በመሰረተ ልማት፤ በመንገድ፣ በሃድሮ -ኤሌክትሪክ አድገናል ፣ የማይደፈር አባይን ደፍረናል፡፡ የባቡር ሃዲድ እየሰራን ነው፡፡ በቲክኖሎጂ አድገናል፡፡ በእርሻ አድገናል፡፡ የእርሻ ኢንቨስትመት ተስፍፍቷል፡ የመስኖ ስራ ተሰፋፍቷል ፡ ህዝባችን በቀን ሦወስት ግዜ በልቶ እንዲኖር አድርገናል ፡፡ በኢንዳስትሪ ከበለፀጉ አገሮች ተወዳዳሪ ወደ መሆን ደርሰናል፡፡በማህበራዊ አገልግሎት በትምህርት፣ በሕክምና፣ በውሃ ሽፋን በኤሌክትሪክ አገልግሎት ፡ ከነበሩት መንግሥታት በአጭር ዓመታት ውስጥ በበለጠ መሰረታዊ ዕድገት አስመዝግበናል ይሉናል፡፡
በፀጥታና በፍትህ ህዝባችን የተሻለ አገልግሎት አግኝቷል፡፡ የህግ የበላይነት ተረጋግጧል ፡፡ በሃገራችን የተረጋጋና ሰለማዊ ሁኔታ ተረጋግጧል ይላሉ፡፡
የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎችና አጃቢዎቻቸው በ40ኛ የልደት በዓላቸው ይህንን ለመሸፋፈን እያደረጉት ያለ ዝግጅት፡-
ህ.ወ.ሃት በአሁኑ ግዜ 40ኛ የልደት በአሉ ሲያከብር ካለፉት 39 አመታት የበለጠ አከባበር ለማክበር እየተዘጋጀ ነው፡፡ለዚሁም ከውጭ አገር (ከዲያስፖራው) ማህበረሰብ ከ100.000 በላይ እንግዶች እንደሚመጡ ከወዲሁ አውጃዋል፡፡ ካገር ውስጥም ከክልል መሰተዳደሮች ተወካዮች ሰቢክ ማህበራት እነዚህም በመቶሺ የሚቆጠሩ እንግዶች ይመጣሉ፡፡ በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የትግራይ ተወላጅችም ከእንግዶች ውስጥ እንደሆኑ ተነግረዋል፡ የሃገራችን የኪነት ባለሙያዎች ፀሐፊዎች ከወዲሁ እየተነገራቸው ነው፡፡ በትግራይ ክልልም ከሁሉም ዘኖች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች የተወከሉ እድምተኖች በመቶሺዎች ይጠራሉ፡፡ የመቀሌ ህዝብ ከ300,000 በላይ ተጨምሮበት መቀሌ እጅግ ብዙ ሰው ታሰተናግዳለች፡፡ በተጨማሪ በዞን፣ በወረዳና በቀበሌ እስከ ቤተሰብ ቤት ቁጥር በግድ ያከብራል ሃብትም ይባክናል፡፡

በትራንስፖርት መስከም በሃገራችን ያሉ ምርጥ ኤም.ቢ.ኤም ኮብራዎች አውቶቡሶች ይዘጋጃሉ፡፡ በገንዘብ ሲተመን ለነዳጅ ለታዳሚዎች ውሎ አበል የሚወጣ እጅግ ብዙ ሚልዮን ብር ነው፡፡ በዚሁ በመቀሌ ለእድምተኛች የሚወጣ ገንዘብ በመቶ ሚልዮን የሚገመት ነው፡፡ የአየር መንገድና የመከላከያ ሚንስቴር አውሮፕላኖችም ለዚሁ በዓል ማክበር የፀጥታ ኃይሎች የሃገር መከላከያ ፡ ፌደራል ፖሊስ፡ ድህንነትም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሊመጡ ናቸው ፡፡ ለዚሁ በዓል ዝግጅትና ምግብ ለመÙÙዝ ከሚያጠፉት የመንግሥት የስራ ግዜ ሳይቆጠር የሚባክነው ገንዘብ በብዙ መቶ ሚልዮን የሚገመት ይሆናል፡፡

ህ.ወ.ሃ.ት የ40ኛ የልደቱ አመት ለማክበር ይህ ሁሉ ወጪ ሲያወጣ ዛሬ ብቻ አይደለም፡፡ ስልጣን ከያዘ ቀን ጀምሮ እስከዛሬ በቢልዮን የሚገመት ሃብት አባክነዋል፡፡ ይህ የማባከን ጉዳይ ግን በህ.ወ.ሃ.ት ውስጥ ታጥሮ የቀረ አልነበረም፡፡ ሌሎች አጃቢ የፖለቲካ ድርጅቶችም የህ.ወ.ሃ.ት ሞዴልነት በመከተል፡ የብአዴን፣ የአሆዲድ፣የዲህዳን ፡ የጋንቤላ፡ የዓፋር ፡ የቤንሻንጉል፡ የሶማል ፡ የሃደሬ፡ በዓላትም እጅጉን አባካኝ ፍፃሜዎች ታይተዋል ፡፡ በተጨማሪ ለግንቦት 20 ብዙ ባክነዋል አሁንም 20ኛ ዓመት ሊከበር ነው፡፡ ይህ ሁሉ በልማት ስራ ቢውል ኖሮ ስንት ድህነት በቀረፈ ስንት ህዝብ ከስደት በዳነ ነበር፡፡ ህ.ወ.ሃ.ት ግን ራሱን ለማዝናናት ይወዳል፡፡ አለማውም ይኸው ነው፡፡በአሁኑ ግዜ በትግራይ ዲግርና ዲፕሎማ የተመረቀ በመቀሌ ብቻ ከ30,000 በላይ ስራጥ ወጣት አለ፡፡ 10ኛ፣12ና 8ኛ ክፍል የወደቁ ተማሪዎች አይቆጠሩም፡፡ ህወሐት ይህ ሁሉ ቢልዮን ብር ለክርስትናው ከሚያጠፋ እነዚህ በትምህርት ጥራት ዕጦት ምክንያት የወደቁ ተማሪዎች ማስተማርና ማብቃት መምረጥ ነበረበት፡፡ነገር ግን የካቲት 11 የህወሐት አመራር ከድሮውም የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው ስልጣን ለማስረከብ ቀይሰው የተጓዙበት ዕለት በመሆኑ በብልዮን መሆኑ ቀርቶ ዓቅም የላቸውም እንጂ በትሪልዮን ብር በዓሉ ቢከበርላቸው ደስታው አይችሉትም፡፡

የጥፋት ዝግጅቱና ዓለማው ፡-
40ኛ የህወሐት የልደት በዓል ዋናው ዓላማው የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች በአሁኑ ግዜ በትግራይ ህዝብ ዘንድ የነበራቸው አመኔታ ጭራሹን ተማጥጦና ተጠልተው እንደምራቅ የተተፉበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡በመሆኑም በዚሁ በዓል ብዙ የውሸት ይዕድገት ድርሳናት ተደርሰው በፎቶግራፍ፣ በፊልም፣ በሙዚቃ፣ በሬድዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በግብዣና በዲስኩር በማደንዘዝ የህዝብን አቅጣጫ በመቀየርና በማላሳለስ የስልጣን እድሚያቸው ለማራዘም እንደልማዳቸው የትግራይን ህዝብ እንደመጠቀምያ ለማድረግ ነው፡፡ ሌላው ዓላማ በ2007 ዓ.ም የፓርላማ ምርጫ ዘመን እጅጉን ስለሰጉ በዚህ በዓል አመካኝተው የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግና የህዝቡ አስተሳሰብ መቀየር፣ የህዝቡን ብሶት ለማብረድ፤ወጣትን የውሸት ታሪክ በመደርደርና በመፈረክ በኘሮፖጋንዳ ለማዳንዘዝና በአጉል የተስፋ መንገድ እንዲቆም ለማደረግ ነው፡፡
የህ.ወ.ሃ.ት 40ኛው የልደት በዓልና ፋይዳው፡-
ህወሐት የተነሳለት ብሄራዊና መደባዊ ጭቆና በመጣል በህዝብ የተመረጠ ህዝባዊ መንግሥት መመሰረት የሚል ዓላማ ለማሳካት አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎም ከዘውዳዊው ስርዓትና ከፋሽስታዊ ደርግ ስርዓት በባሰ መንገድ ህዝቡን እየጨቆነና እየበዛበዘው ይገኛል፡፡ህዝቡ የድሮ የበሰበሱ በዝበዥ ስርዓቶች አስወግዶ፡ 17 ዓመታት ሙሉ ታግሎ የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው አሮጌውን ስርዓት አሳድሰው ህዝቡን በዘመናዊ መንገድ የሚጨቁኑ ገዥዎች አፍርተዋል፡፡

ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብቶቹ አልተከበሩለትም፡፡ የየካቲት 11 ውጤት ይህ መሆን ነበረበት፡፡ ህዝቡ ደርግን ማስወገድ ብቸኛው መፍትሔ ይመስለው ነበር፡፡የካቲት 11 ገዥዎች ነቅላ ሌሎች ገዥዎች ታመጣለች ብሎ ህዝቡ አስቦ አያቅም ነበር፡፡ ሀቁ ግን ይህ ሆኖ ቀረ፡፡ የካቲት 11 አደራ በልተሻል ብለው ለተቃወሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ታስራለች፣አገር ለቀው እንዲሄዱ እያደረገች ነው፡፡ የካቲት 11 ያ ሁሉ ወጣት በጉያሽ አቅፈሽ፣ለክብርሽ መስዋእት ሆኖ ለአዲስ ገዥዎች አሳልፋ መስጠቷ በየካቲት 11 ያገኘነው ነገር ካለ ልጆቻችን መስዋእት መሆናቸው እንጂ የፈየደችን ነገር የለም እያሉ ናቸው፡፡ የካቲት 11 ይህ ሁሉ ወጣት በልተሽ ለጥቂት የገዥ መደብ ልጆች ጥቅም መቆምሽ ከበደል በደል ነው፡፡

የካቲት 11 40ኛ ዓመትሽ ሲከበር እኛ ህዝቦች ከደርግ መንግሥት የዜሮ ዲሞክራሲ ወጥተን በራሳችን ፍቃድ የኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላውነት ተከብሮ እርስ በራሳችን ተፋቅረን እንኖራለን ብለን ነበር፡፡ በ40ኛ ዓመትሽ በህወሐት/ኢአዴግ መንግሥት እርስ በራሳችን ብጥርጣሬ ዓይን እንድንተያይ፣አንዱ በሌላው ክልል ሄዶ ሰርቶ የመኖር ዕድል ዘግቶ ይገኛል፡፡ እርስ በራሱ እንደጠላት እንዲተያይ እየተደረገ ነው፡፡ ደርግ ሃይማኖት ለማጥፋት ሲጥር ህወሐት/ኢህአዴግ ደግሞ በሃይሞት ነፃነት ጣልቃ በመግባት እርስ በራሳችን የነበረንን የመከባበር እሴት በማደፍረስ አንድነታችንን እንዲላላ በማድረግ ለፖለቲካ ፍጆታው እያዋለው ይገኛል፡፡
ደርግ ዜጎች የመደራጀት፣የመናገር፣የመጻፍ መብት የከለከለ መንግሥት ስለነበር እኛ የጊዜው ወጣቶች ታጥቀን ደርግን እንድናስወግደው ያንችን ጥሪ ሰምተን ታግለናል፡፡ ውጤቱ ለዚህ ብለን አልነበረም፡፡ የፊውዳል ልጆች የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው ሥልጣን ለማስረከብ ብለን አይደለም ደደቢት የወጣነው፡፡

የካቲት 11 አሁን 40ኛ ዓመትሽ እየተከበረ ነው፡፡ እርግጥ ነው ጤና እንዳላገኘሽና በአከባብያችን እንደሌለሽ ይገባናል፡፡ ከአጠገባችን ብትኖሪ ኖሮ ይህ ሁሉ ግፍ ብህዝቡ እየወረደ ዝም ብለሽ ማየት እንደማትችይ ይገባናል፡፡
የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች መሬት ላራሹ፣ የከተማ መሬት በነፃ ለህዝብ በእኩልነት ይታደል ብለው የታገሉና ለህዝብ አነስስተው ደርግን ለመጣል ያስቻላቸው የመሬት ጥያቄ በመክዳት፣ መሬት የመንግስት ናት በማለት የከተማና በከተማ አካባቢ የሚገኙ የህዝብ መሬት በመቀማት በመሸጥ ለራሳቸውና ለዘር መንዝራቸው የሃብት ምንጭ አድርገውታል ፡፡ የገጠር መሬት የህዝቡን ባለቤትነት በመንጠቅ በአርሶአደሩ የማልማት ዓቅም ለሌላቸው ግለሰዎች በመሰጠቱ ወጣት አርሶ አደር የወጣት ጥንቻው ሊያሳርፍበት የሚችል መሬት ባለማግኜቱ ጉሳሳ ጎጆ ሰርቶ የሚተኝበት መሬት ተከልክሎ በረሃና ባህር ተሸግሮ ወደ ስደት ፈልሰዋል ፡፡ በአንፃሩ የህ.ወሃ.ት መሪዎችና ልጆቻች ባገር ውስጥና በውጭ ሰማይጠንቀስ ህንፃዎች ሰርተው የሚኖርበት ሁኔታ ተፈጥረዋል፡፡
የካቲት 11 40ኛ ዓመት የልደት በዓልሽ ስናከብር ይህንን ጉድ ተሸክመን ነው፡፡ግን የካቲት 11 ልጠይቅሽ እነዚህ ቱጃሮች ለመፍጠር ነበር የትግሉ ዓላማ?

አይደለም ፍፁም አይደለም ፡፡ በኛ በኩል አስበነውም አናቅም፡፡እነሱ ግን ይህንን ዓልመው ይጓዙ ስለነበር ያሰቡትን አሳክተዋል፡፡ የካቲት 11 40ኛ ዓመትሽ ስናከብር በሃዘን መሆኑ ማወቅ አለብሽ፡፡ ምኞታችን የነበረው በ40ኛው የልደት በዓልሽ ገጠሪቷ ትግራይ ከ13 ዓመት ዕድሜ በላይ ወጣት የማይኖርበት፣ በገጠር ህፃን፣ ሽማግሌ ከሞተ ሬሳ ተሸክሞ ወደ መቃብር የሚወስድ ወጣት ይጠፋል ብለን ኣናስብ ነበር ግን ሆነ ፡፡ የገጠር ወጣቱ አብዛኛው ወደ ጎረቤት አገሮች ሲሰደድ የቀረው ወጣት ወደ ክልል ከተሞችና አዲስአበባ ፈልሰው ከተሞችን አጣብበዋል ፡፡ ሴት እህቶቻችን ባገር ውስጥም በውጭም ካለፉት ስርአቶች በባሰ ለዝሙት ስራ ተጋልጠው እየተዋረዱ ይገኛሉ ፡፡ ለመጥፎ በሽታ ተጋልጠዋል፡፡ የገጠር ሴቶች ባሎቻቸው ወደ ስደት በመፍላሳቸው ህፃናት ይዘው በሃገር ቤት በረሃብ በበሽታ ይሳቃያሉ፡፡ የካቲት 11 40ኛ ዓመትሽ ስናከብር ይህንን ስቃይ እያየን ነው፡፡

በከተማ ያለው የተማረና ያልተማረ ወጣትም በስራ አጥነት ምክንያት ለፀጥታና ለሰላም ጠንቅ ሆኖ ይገኛል፡፡ በተለይ በዮኒቨርሲቲዎች የተመረቁ ወጣቶችም በመጥፎ ሁኔታ ይገኛሉ፡፡ ያቺ እንደ እሳት አደጋ ማጥፈያ የሚጠቀሙላት ከቡልስ

Image
ከሠሞኑ ወደግብፅ የሚያቀና ህወሀታዊ የልዑካን ቡድን ሲቋቋም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሊጠብቀው በማይችለው መልኩ የልኡካን ቡድኑ ውስጥ የአንድ ሠው ስም ተሠማ “ግርማ ሠይፉ” የሚል በርካቶች ተገረሙ ወይ አንቺ ሐገር ሲሉም አዘኑ፡፡ ከዚህ ቀደም ብቸኛ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በፓርላማ ተብለው በተቀመጡባቸው ያለፉት 4 ዓመታት ለሐገራችን ፖለቲካ ያንን ያህል ለውጥ ባያመጡም፤ የህሊና እስረኞቹ ይፈቱ ዘንድ አሁንም ያንን ያህል ጠንከር ያለ ስረ ባይሠሩም አቶ ግርማ ሠይፉን ሌሎች አካላት ሲተቿቸው ግርማ ሠይፉን ደግፈው ከሚቆሙ አካላት መካከል አንዱ እኔ ነበርኩኝ ብዬ አስባለው፤ አስባለው ያልኩት ስለግርማ ሠይፉ ከኔ በላይም የሚያስብ ሌላ ህወሀት የተሠኘ የሠዎች ስብስብ መኖሩን ስላልተረዳሁና በቅርቡ እየታዩ ያሉትን የግርማን መንሸራተቶች ባለመመልከቴ ነበር፡፡

በሐገራችን ፖለቲካ ማየት ከማንፈልጋቸው ነገሮች የከዳተኝነት ፖለቲካ አንዱ እና ዋነኛው ነው፤ ይህ ህዝብ ለፍቶ ከሚያገኘው የወር ገቢው ላይ ግብር ተወስዶበት ፓርላማ ለሚገኙ የህዝብ ተወካዮች በአበል እና በደመወዝ መልክ ይሠጣል ህዝቡ ይህንን የሚያደርገው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተሠኘው የሚገኙ አባላት መብቴን የሚያስከብር ህግ ያወጡልኛል፤ ስለእኔ መብት ስለቆሙ የታሠሩ የህሊና እስረኞችን የበላይ አካል እንደመሆኑ ያስፈታልኛል ብሎ አለመሆኑ እሙን ነው ምክንያቱም በህወሀት ፓርላማ ውሳኔ ችግሬ ይፈታልኛል ብሎ የሚያስብ ኢትዮጵያዊ ካለ እርሱ የህወሀት አባል መሆን አለበት ሆኖም ተባራሪ ሆነው ፓርላማ ውስጥ የሚታዩ አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የህዝብ ችግር ያሏቸውን ጉዳዮች ነቅሰው አውጥተው ለፓርላማው ሲያቀርቡ እንመለከት ነበር እነዚህ ሠዎችም ሲከዱ ተመልክተናል እውን ግርማ ሠይፉ ካዳ? ግርማ ሠይፉ ካዳ ወይስ አሁንም ለህዝቡ እንደቆመ ነው የሚሉትን ጉዳዮች ከማንሳታችን በፊት ከግርማ ሠይፉ ጋር የልዑካን ቡድኑ አባላት ውስጥ የሚገኙ አባላት እነማን ናቸው የሚሉትን መመልከት ተገቢ ይመስለኛል፡፡

የህዝብ ልዑካን ቡድን ሲቋቋም መታሠብ ካለበት መካከል አንደኛው እና ዋናው ነገር የልዑካን ቡድኑ አባላት በህዝብ የታመኑ፣ በመልካም ስነምግባራቸው አርዓያ የሆኑ እና ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ መሆን ይኖርባቸዋል ወደግብፅ ባቀናው የልዑካን ቡድን ውስጥ የተካተቱት ግን በየትኛውም መለኪያ የህወሀት ጉዳይ አስፈፃሚ ከመሆን ውጪ የህዝብ አመኔታ ያላቸው ግለሠቦች አይደሉም፡፡ ከልዑካን ቡድኑ ውስጥ መካከል አንዱ ሠራዊት ፍቅሬ የተሠኘው ግለሠብ ነው፡፡ ይህ ግለሠብ ልክ እንደሌሎቹ የህወሀት አባላት እና አመራሮች ከወታደር ቤት ወጥቶ ሚሊየነር የሆነ ግለሠብ ነው፡፡ ሠራዊት ፍቅሬ የህዝብ ተወካይ መሆን የማይችልባቸውን ምክንያች ለማንሳት ያህል ከዛሬ ሁለት አመት በፊት በአንድ ተማሪ ላይ በማን አለብኝነት የፈፀመውን የአስገድዶ መድፈር ሙከራ ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ ሠራዊት ፍቅሬ አስገድዶ ሊደፍረኝ ሲል አመለጥኩኝ ያለችውን ግለሠብ አዲስ አድማስ የተሠኘው ሐገር ቤት የሚታተም ጋዜጣ አነጋግሯት እንደነበረና ከጥቂት ቀናት በኋላ በሠራዊት ፍቅሬ የመድፈር ሙከራ የተደረገባት ተማሪ ሁኔታ ተደባብሶ ቀረ ወጣቷ አሁን የት እንዳለች እንኳን አይታወቅም አዲስ አድማስም ከህወሀት ሠዎች ሊደርስበት የሚችለውን ዛቻ በማሠብ ተወው ይህንን ድርጊት የፈፀመው ሰራዊት ፍቅሬ ነው አንዱ የዚህ ልዑክ አባል፡፡

ሌላኛው የልዑካኑ ቡድን አባል ቴዎድሮስ አድሐኖም ወይም እንደሱ አጠራር ቴድሮስ አድሐኖም ነው፡፡ ይህ ግለሠብ አምና በዚህ ሠዓት ሣውዲ አረቢያ ይገኙ ለነበሩ ሠዎች ሞት እና እንግልት ተጠያቂ ሊሆን የሚችል ሠው ነው፡፡ ቴዎድሮስ አድሐኖም የውጪ ጉዳይ ሚኒስተሩነቱን እና የህወሀት አባልነቱን ተጠቅሞ ለሳውዲአረቢያ የንጉሳውያን ቤተሠቦች በላከው ደብዳቤ ኢትዮጵያውያኑ ከሳውዲ ኢሠብዓዊ ድርጊት ተፈፅሞባቸው እንዲወጡ ማድረጉ ይታወሳል ይህ ግለሠብ ስለእውነት እና ስለህዝብ የቆመ ቢሆን ኖሮ የሳውዲ ንጉሶችን አሳምኖ የኢትዮጵያውያን መውጫ ቀን በማስረዘም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ከእልቂት እና ከግፍ ያድን ነበር ሆኖም ዛሬ ይህ ግለሠብ የሠራቸው ወንጀሎች ተደብቀውለት ዛሬ የህዝብ ልዑካን ተብሎ ተሠይሞ ይገኛል፡፡ ግርማ ሠይፉም ከእነዚህ ሠዎች መካከል ይገኛል የህዝብ ልዑካን ቡድን ተብሎ፡፡ ከሠራዊት ፍቅሬ እና ከቴዎድሮስ አድሐኖም ጋር አብሮ መስራትን የመሠለ ምን ከዳተኝነት ይኖር ይሆን?

ግርማ ሠይፉ የልዑካን ቡድኑ ውስጥ መካተቱን ሳይነግረን ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ “ይህ የአሁኑ ሠንደቅ ዓላማ ለእኔ ከበፊቶቹ ይሻለኛል፤ ሁሉም የታሠሩት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች ንፁህ ናቸው ብዬ አላምንም” ምናምን የሚሉ በህዝብ ላይ የተቀለዱ መጥፎ ንግግሮችን በኢንተርቪው እና በብሎጉ ላይ አሰምቶናል በተጨማሪም አምና አንድነት ጠርቶት በነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ላይ ሠልፈኛው ሲግናል አካባቢ ሲደርስ ሲግናል ለአንድ ጎሳ አባላት ብቻ የተሠሩትን ህንፃዎች ተመልክቶ ዝም ብሎ ማለፍ ያልቻለው ሠልፈኛ ሌባ ሙሰኛ እያለ ሲጮህ ዝም በሉ እያለ ሠልፈኛውን ከሀብታሙ አያሌው ለመነጠል ሲሞክር እንኳን በግርማ ላይ ተስፋ አልቆረጥኩም ነበር አሁን ግን ከኢትዮጵያ የምንም ጊዜ ጠላቶች ጋር አበረ፡፡ የልዑካን ቡድኑ ውስጥ ያሉት ሠዎች እኮ በበደኖ እና በአርባጉ የአማራውን ጎሳ የጨፈጨፉ፤ በአምቦ ንፁሐን የኦሮሞ ተማሪዎችን የገደሉ፤ ፤ በጋምቤላ ንፁሀንን ያስፈጁ፤ ፕ/ር አስራትን እና አሠፋ ማሩን የመሳሰሉ ድንቅ የሐገራንን ምሁራን ያስገደሉ፤ እስክንድርን፤ ርዕዮትን፤ በቀለ ገርባን፤ ኤርባና ሌሊሳን፤ የሺዋስ አሠፋን፤ አብርሐ ደስታን፤ ዳንኤል ሺበሺን፤ አበበ ቀስቶን፤ ናትናኤልን፤ ሐብታሙን፤ እና ሌሎችንም ያሠሩ፤ ከጥቂት ቀናት በፊት እንኳን የሠማያዊ ፓርቲን እና የትብብሩ አባላትን ቶርች ያደረጉ፤ በትላንትናው እለት ባህርዳር ላይ ህዝብን ያስፈጁ ሠዎች ጥርቅም ውስጥ ግርማ ዘው ብሎ የገባው፡፡

ግርማ ቆም ብሎ አስቦ ህዝቡን ይቅርታ ብሎ ጠይቆ እራሱን ከፖለቲካ ከማግለል ውጪ ሌላ አማራጭ ይኖረዋል ብዬ አላስብም ፓርቲው አንድነትም ቢሆን እንደግርማ ሠይፉ ያሉ አባላትን ይዞ መቀጠሉ ለፓርቲው አደጋ መሆኑን ተገንዝቦ ህዝቡን ይቅርታ ሊጠይቅ እና ግርማ ሠይፉን ሊቀጣው ይገባል ይህ ካልሆነ ግን ለወትሮውም በሐገራችን ፖለቲካ ተስፋ ለቆረጠው ህዝባችን ጭራሹኑ ፊቱን እንዲያዞር የሚያደርግ ታሪክ ሲወቅሠው የሚኖር ተግባር ከዛም አልፎ ሌሎች እየለፉ ያሉ ፓርቲዎች ላይ ህዝቡ እምነት እንዳይኖረው የሚያደርግ አስወቃሽ ስራ ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ በፊት ከግርማ እና ከፓርቲው መልስ ያስፈልጋል
#ሁኔአቢሲኒያ

Image
የተለያዩ መፈክሮችን የያዙ ፊኛዎች ወደ ተውለብለበዋል :: ፊኛዎቹ የተለያዩ መፈክሮች የተጻፈባቸው ሲሆን ከነዚህም መካከል : – ትግሉ ይቀጥላል ፍትህ ነጥፏል ፤ሂጃብ መለያችን፤ኒቃብ ውበታችን ፤ትግላችን ቀጥሏል
ፍትህን ማዘግየት ፍትህን መንፈግ ነው ፤ትግላችን እንደቀጠለ ነው ::

ፍትህ ፍትህ ፍትህ ;We Need Justice ፤Hijab Is Beauty ፤ justice Is Denied የሚሉት መፈክሮች ይገኙበታል፡፡ በርካታ ፊኛዎች የተውለበለቡና ወደ ሰማይ የተለቀቁ ሲሆን ተቃውሞው በከፍተኛ ድምቀት ተከናውኗል፡፡ መንግስት በሴኩላሪዝም ሽፋን እየፈጸመ ያለውን የሂጃብ ገፈፋ የሚያወግዝ ሲሆን በተጨማሪም በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ እጸፈጸመ ያለውን የፍትህ መዛባት ፤ በማረሚያ ቤቱ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማውገዝ ነው፡፡ መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቋሞውን በሃይል አስቁሚያለሁ ሲል የነበረ ሲሆን ህዝበ ሙስሊሙ ግን ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገልጽዋል፡፡

Please wait, video is loading…

Minilik Salsawi – ባሳለፍነው የትግል አመታት ውስጥ የተቃዋሚዎች እርስ በ እርስ መፈራረጅ መወነጃጀል መናናቅ ለስልጣን ጥመኝነት መሮጥ እንዲሁም ለስም እና ለዝና መትጋት ያለመደማመጥ እና ያለመከባበር ፖለቲካ ተቀራርቦ ያለመነጋገር እና ያለመመካከር ፖለቲካ ሃገራኢ ሆደሰፊነት እና መቻቻልን ያላዘለ ፖለቲካ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተረፈው ነገር ቢኖር ከጭቆን ወደ ጭቆና ማቅ ውስጥ ከመዘፈቅ ውጪ ምንም የናፈቀውን የነጻነት አየር እንዲተነፍስ አላደረግነውም። የተቃዋሚ ሃይሎች ጥንካሬ እንዲጎለብት በየድርጅቱ ውስጥ ያሉትን እንከኖች በማጥራት በጋራ እና በተመቻቸ የሃሳብ መግባባት ተቻችሉ እና ተግባብቶ የትግል ስትራቴጂን ግብ ለማድረስ ለአንድ ወጥ ህዝባዊ እና ሃገራዊ አጀንዳ ተግቶ መስራት ይጠበቅብናል።

ወያኔ የተቃዋሚዎችን እና የለውጥ ሃይሎችን እርስ በእርስ መፈነካከት በማየት አርጩሜውን ተስፋ በሚጣልባቸው ግለሰቦች እና ፓርቲዎች ላይ እያወናጨፈ ባለበት እንዲሁም የውስጥ አሰራራቸውን በመሰለል በትግሉ ውስጥ ያላቸውን ሚና እንዲኮላሽ በመስራት የውስጥ ድክመቶቻቸውን በመጠቀም እርስ በርስ እንዲፋጁ እና ተቃዋሚዎች እንዲከስሙ ጥንካሪያቸውን እንዳያገኙ ሲሰራ ይህንን እንዴት አድርገን በማሻሻል የወያኔን ሴራ ማክሸፍ አለብን የሚል አመኔታ የሚያስገኝ ሕዝባዊ ስራዎችን በመስራት ጥንካሬን ማግነት እንዲሁም ሕዝባዊ ድጋፎችን ማግኘት ግድ የሚልበት ጊዜ ላይ መሆናቸውን ተቃዋሚዎች ሊያውቁት ይገባል::ተቃዋሚዎች ካለፈው ድክመቶቻችን ተምረን ከዘለፋ እና ከስድብ እንዲሁም ከመፈራረጅ የሴራ ፖለቲካ በመውጣት ጥንካሬዎቻችንን የምናሳይበት ለውጥ የምናመጣበት አመት እንዲሆን በጋራ ጠንክረን መስራት አለብን።አንድነት ሃይል ነው የሚለው ብሂል ለሃገራዊ አጀንዳ መተግበር ትልቅ አስታውጾ አለው::ከኛ በላይ ላሳር ከኛ በላይ አዋቂ የለም የሚል አመለካከት ይዞ ከመክነፍ የህዝብን ጥያቄ መሰረት አድርጎ ተቀራርቦ በመነጋገር እና በመወያየት ሃገራጂ ማኒፌስቶ በማምጣት የጋራ ሃገራዊ አጀንዳ በመቅረጽ ለለውጥ መትጋት ግዴታ ነው::

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ይህ ሳይታለም የተፈታ እና የሁሉም የነጻነት ፈላጊ ሃይሎች ጥያቄ ነው። በሃገር ውስጥ ያሉትን ፓርቲዎች መዋቅሮቻቸውን በማጠናከር የውስጥ ድክመቶቻቸውን በመቅረፍ እንዲጠነክሩ የማድረግ ግዴታ ከለውጥ ፈላጊ ሃይሎች ይጠበቃል። መመካከር መተራረም ግድ ይላል። በውጪው አለም የሚገኙ የነጻነት እና የለውጥ ሃይሎች እንዲጠናከሩ እና ከጥልፍልፎሽ ፖለቲካ ወተው ጠንካራ ሃይል እንዲሆኑ የዲያስፖራው ሃይል ከበፊቱ በበለጠ መልኩ ሊሰራ ግድ ይለዋል። የወያኔ የጎን ውጋት እና የራስ ምታት የሆነው ዲያስፖራው የጀመረውን የትግል ስልት እና ትጋት በማስፋት ሚዲያዎችን በማጠናከር እና የነጻ አውጪ ፓርቲዎችን በመርዳት በማግባባት ጠንካራ ሰንሰለት ከሃገር ቤት ጋር በመፍጠር ሕዝብን ከጨቋኞች ነጻ ማውጣት አለበት።ዲያስፖራው በየቀኑ ወያኔ የሚፈጥረውን ተራ የቤት ስራ እና የማደናገሪያ ማዘናጊያ አሉባልታ ፊት ሳይሰጠው በለውጡ ጉዳይ ላይ በማተኮር በሃገር ቤት ያለው ሃይል እንዲስማማ የፖለቲካ ጡዘቶች ክፍተት እንዳይኖር ተቀራርቦ እንዲሰራ ትልቁን ሚና መጫወት አለበት::

የሚዲያ ተቋማት እና የድህረገጽ ውጤቶች ሕዝብን በማስተማር ሕዝብን መብቱን እና ነጻነቱን አውቆ ለሌላው እንዲያስተምር በማድረግ ረገድ አስፈላጊውን ወቅታዊ መረጃ እና መነሳሳትን በማስረጽ ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል። ያለፉ እና የከሰሙ ወሬዎችን እና አሉባልታዎችን ከመርጨት የወያኔ የፈጠራ አደናባሪ እና አዘናጊ አጀንዳዎችን እኝኝ በማለት ከማውራት ብሄር ተኮር ክፋፋይ ሃሳቦችን ከማርከፍከፍ አዛኝ መሳይ መርዝ ሃሳቦችን ከመናገር ተቆጥበን ሕዝቡን ስለመብቱ እና ነጻነቱን በማስተማር ረገድ መትጋት ከተያዘ ለውጥ የማይመጣበት ምንም ምክንያት የለም። ትችትን እና ሂስን ላለመዋጥ እውነትን ላለመቀበል የሚደረጉ ሩጫዎች ታጥቦ ጭቃ እንጂ የትም እንደማያደርሱ እንዲሁም ፓርቲዎችን እና ሰዎችን መፈረጅ እና መወንጀል ሃሳቦችን ማጣጣል ምንም ለውጥ እንደማያመጣ ካለፈው ተምረናል ። ያሳልፍነው የትግል ሂደት ከጭብጨባ እና ስብሰባ ያለፈ ፋይዳ እንዳሌለው ተገንዝበን የወሬ እና ሆይሆይ ትግል ስለማያዋጣ ጥንካሬን እና ለውጥን የምናመጣበትን የትግል ስልት በመመካከር እና በመወያየት ሃሳብን በማቻቻል መረጃ በመለዋወጥ ሃገራዊ የጋራ አጀንዳ ሊኖረን ይገባል እላለሁ።

የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ ሰላማዊም የትጥቅም፣ በባህሪው ትብብርን ይጠይቃል። ሕብረተሰብ በማሳትፍ የሚደረግ የትብብር ሥራ ነውና። የኢትዮጵያ ገዥ ጥምር ድርጅት አንድ አካል የኾነው ህወሓት የፈር ቀዳጅነት ሚናውን ወስዶ የዛሬ አርባ ዓመት በትግራይ በረኻዎች የትጥቅ ትግል ጀምሮ በሚያካሂድበት ጊዜ፣ “ተወዲቡ ብጽንዓት ዝተቓለሰ ይዕወት” (ሲተረጎም፣ ተደራጅቶ በጽናት የታገለ ለድል ይበቃል) የሚል መፎክር ከአነገባቸው መፎክሮች አንዱ ነበር። በነገራችን ላይ የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ኢህአዴግ እንደ መንግስት ሀገር ሲመራ የተከተለው ህዝብን አደራጅቶ እና አስትፎ የመስራት ባህልም ከዚኽ መፎክር የተወረሰ ሳይኾን አይቀርም። ለዚህም ነው ኢህአዴግ ነጥሮ በመውጣት በትጥቅ ትግሉም ሀገር በመምራቱም ወቅት ውጤታማ ሊኾን የበቃው። አሁን በፖለቲካው ተደራጅተው ሳይደራጁም እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተቃውሞ፣ ሕጋዊ የኾኑትም ያልኾኑትም በዋናነት የዚኽ የተባብሮ መስራት ድክመት ስላለባቸው ነው ለውጤት ያልበቁት። ሲጣመሩ፣ ሲቀናጁም ኾነ ሲያብሩ፣ የአብሮ መስራት ምክንያታቸው የመላው ህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ በፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና ፖለቲካዊ ፕሮግራም ነጥሮ የወጣ ፖለቲካዊ አቋም ይዘው መስዋእት ለመክፈል ተዘጋጅተው ሳይኾን በጥላቻ እና የስልጣን ጥም ብቻ መሰረት አድርገው ነው ወደ አንድ የሚሰባሰቡት። በዚኽ አካሔድ ደግሞ ጠብ የሚለ ውጤት አላገኙም። በተለይ ለመስዋዕትነቱ የሚመርጡት ሌላ አካል እንዲኾንላቸው ይፈልጋሉ። እነሱ በአቋራጭ ስልጣን ላይ ለመፈናጠጥ እንዲያስችላቸው። ከዚኽ አንጻር የሀገራችን ተቃዋሚዎች ትጥቅ ትግል አውጀው በሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩት እና በስመ አክቲቪዝም የሚከትሏቸው (ሁለቱንም መንገድ የሚያጣቅሱ ቡድኖች) እንዲኹም በሰላማዊ ሕጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱት በተደጋጋሚ የመተባበር እና ለህዝብ መስዋዕት የመኾን መሰረታዊ ባህሪ ስለሚጎድላቸው እና የስልጣን […]