በፖለቲካው ረገድ የስርኣቱ ገዢ ፓርቲዎች እርስ በርስ አለመተማመን ደረጃ ላይ ከመድረሳቸውም በላይ አመራሮቹ አድፍጠው አንዱን አንዱን እየጠበቀ በፍራቻ አለም ውስጥ እየዋተቱ ይገኛሉ::አቤት የሚባልበት እየጠፋ ነው፡፡ የውሳኔ ሰጪ ያለህ ቢባል መልስ አይገኝም፡፡ ፋይሎች የሚያያቸውና የሚያነባቸው አጥተዋል፡፡ መልካም አስተዳደር ገደል ገብቷል:: ……… የተጭበረበረ አፋኝ ፖለቲካ ያስከተለው የኢኮኖሚ መንኮታኮት የአገሪቱን የፖለቲካ አናቶች ለውጥ እንዳያመጡ በመተብተብ ቀውስ ውስጥ የከተታቸው መሆኑን ከስብሰባዎች እና ከጭብጨባዎች ብዛት እየታዘብን ነው::በሌላ በኩል ሚዲያዎች ህዝብን መዋሸታቸው እና ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ መዋላቸው አገሪቷ እንድትንኮታኮት በር የከፈተ ሲሆን የዚህ መፍትሄ ስልጣን መልቀቅ………………..‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

phpBB [video]

ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት (ቢኒያም ግዛው ከኖርዌይ ኦስሎ)
Biniam Gizaw
Image
ይሄ ምርጫ መቼስ ስንቱን ያስታውሰናል?በደርግ ዘመን እናቶች ወንድ ልጃቸውን ከየጉያቸው እየተነጥቁ እና እየታፈሱ በጦርነት ሲማገዱ ወንድ ልጅ ላለመውለድ. . .
ትዝም አላለሽ ወይ የክፉ አመቱ
ላንቺና ለልጅሽ ያለቀ ስንበቱ
ማህጸኔን ዝጋ ይቅር ምን አባቱ
በእንባ እየዳከርሽ ብለሽ ያልሽበቱ።
እያሉ ፈጣሪን ወንድ ልጅ እንዳይሰጣቸው የለመኑትን ቤቱ ይቁጠራቸው። የአፈሳና የሀገራችንን አንድምታ ለመረዳት ከሰሞኑ በየከተማዎችና ጎዳናዎች ያለው የድብደባ የአፈሳና የሞት ፍርሀት ድባብ ተቀባብሎ ለቃታ የተዘጋጁ ጥይት በእያንዳንዱ ሰላማዊ ዜጋ ጆሮ ስር ተደግኖ እንደሚራመድ በቀላሉ መረዳት ይቻላል።

. . . ጭቃ ከማቡካት ጀምሮ አብሬው ያደኩት ጓደኛዬ ስሙ ጌታቸው ይባላል። እንዴት እንደምንዋደድ እንደምንተሳሰብ እና እንደምንመካከር አትጠይቁኝ። በቃ ጌቾ ምርጥ ጓደኛዬ ነው።

እናም በጊዜው ወያኔ መዲናችን አዲስ አበባ ገቡ ገቡ የሚባልበት ሰአት ኖሮ ግራ መጋባቴን ከባልንጀራዬ ላወራ በአጥር በኩል ጌቾ!ጌቾ! ብል እናቱ ወ/ሮ በለጥሻቸው ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ከበሮአቸውን ጸሀይ ላይ እያገላበጡ ግቻ ያርግህ. . . ጎይቶም አትልም! ብለው ቀልቤን ገፈፉት። ነገሩ ወዲህ ኖሮ እሳቸውም ወ/ሮ በለጥሻቸው ታጋይ ትብለጽ ተብሎ ስማቸው መተርጎሙን ያወኩት ቆይቼ ነገር ከገባኝ በኋላ ነው። ከዚያማ እነአቶ ክፍሉ (ክፍለእግዚእ) እነአዲስ (ታጋይ ሀዲሽ) ወዘተ ስናዳምጥ የጫካ ስም ብቻ ሳይሆን የከተማም ስም እንደነበራቸው ተረዳን።

ከዛ በኋላማ ምኑን ልንገራችሁ በኳስ ሜዳ ሰው የጠፋ ጊዜ በረኛ ካልሆነ ወደ ውጪ የወጣ ኳስ አቀባይ የነበረው ጊቾ በግልጥ ፎሪ የወጣውን እንደፈለገ እና ደስ እንዳሰኘው ጎል ብሎ ሲያፀድቀው ቢደብረንም መስማማት ብቻ ሆነ። አይ የቀን ክፉ! ግንቦት 20። ይኽው እስክንበታተን ድረስ ጎይቶምም እንደኛ ባሉት ላይ ተቀይሮ ሲጎለብት ታጋይ ትብለፅ ደግሞ እነማዘርን በዳቦ ተቆጣጥረው ሲጠረንፉን ከረሙ።

ጦጣ በአንድ ወቅት ለቃለ መጠይቅ ቀርባ ኖሮ ምን ትወጃለሽ? ተብላ ብትጠየቅ የዛፍ ላይ ትግል አለች አሉ። በፀዳ ሜዳ ግልፅነትና እውነት ባለበት ምርጫ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች ማየት ከንቱ እየሆነ መምጣቱ በዕጅጉ ያሳዝነናል ። አንድ ጎጠኛ ብሔረሰብ ብቻ በሚመቸው ፓርላማና በየቀበሌው እንደ ጦጣ በስልጣኑ ላይ እየተንጠላጠለ 23 ዓመት መግዛቱ ስርዓቱ ምንኛ አስከፊ መሆኑን የሚያሳይ ነው።

ኢትዮጵያ ለዘመናት ተከብራ የኖረችና ህዝቦቾም ልዩነትን ወደሆላ በመተው በጋራ ፣በመቻቻል ፣በመካባበር ሀገራቸውን አስከብረው ከዘር እና ከእምነት ይልቅ ኢትዮጵያውነትን በማስቀደም ኢትዮጵያዊነት የገነነባት ሀገር እንደነበረች ይታወቃል እነሆ ዛሬ ወያኔ የሁትሱና ቱትሲን ስርዓት ናፍቆ ገዢ ከኔ ዘር ሌላ ለአሳር እያለ ሰፊውን ህዝብ ለጦርነት ጋብዞታል። ወያኔ ፈጽሞ በኢትዮጵያዊነት የማያምን እና የኢትዮጵያ ህዝበም በአንድነትና በፍቅር እንዲኖር የማይፈልግ ጸረ ኢትዮጵያዊ ሲሆን ይህንንም በመረዳት እኛ ኢትዮጵያኖች አንድነታችን ለወያኔ የራስ ምታት መሆኑን አውቅን አንድነታችንን የሚያጠናክር ስራዎች ላይ ልናተኩር ይገባል :. ዘረኛው የህህዋት መንግስት በአንድ ወቅት አርሱ አደሩ የሀገሬን ገበሬ እኔ አውቅልሀለሁ እያለ ካለበት ሀገር መሬትና ቀኤ ድረስ መጥቶ ልግዛህ እያለ መከራውን ሲያበላው . . .

ሳለቅስ ሳነባ የሰጠኽኝ ሸማ
ጉድ በል ያገሬ ልጅ እንካ መርዶ ስማ
የወንዝህ ማዕረግ በትግሬ ተቀማ

እያለ ለአያትና አባቱ በቅኔ ብሶቱን መናገሩ አፈናና ረግጣውን ቅሚያና ዘረፋውን መቋቋም ቢያቅተው መሆኑ ልብ ይሏል። የፈረንሳዩ ደራሲና ፈላስፋ ቪክቶር ሁጎ “When dictatorship is a fact, revolution becomes a right.” ብሎ ማለቱ አንደ ወያኔ ላለ በአንድ ብሔር የበላይነት ተንፈናጥጦ እንደፈለኩ ልግዛህ ለሚል መንግስት ትክክለኛ አባባል ነው።

ምርጫ ፍትህና ዴሞክራሲ ምን እንደሆነ ለማይገባው መብት ማስከበሪያው ብቸኛ መንገድ ለለውጥ ፀንቶ መታገል ብቻ ነው። በአሳማ መንጋ የምርጫ ውድድር ያው አሸናፊው አሳማ እንጂ ነብር ወይ አንበሳ አይሆንም። በመሆኑም ያው አሳማ ነገም ልርገጣችሁ ማለቱ አይቀርም። በሰብዓዊ ትግል ተስፋ አይቆረጥም የሰፊው ህዝብ መብት ታላቅ ውቅያኖስ ነውና ጥቂት የአምባገነን ጠብታ ሰፊውን ባህር አያደፈርሰውምና አሁንም የሰብዓዊ መብት ትግል አሸናፊ ነው። በጥቂት ዘረኞችና በአንድ ጎሳ የበላይነት የተያዘው የወያኔ አገዛዝ የሰፊውና የታላቁን የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በምንም መልኩ ሊገታው አይገባም ይልቁንም ”ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት” እንዲሉ በማን አለብኝነት የተንሰራፋውን ወያኔና አግዛዙ መቃብሩ ተምሶ ያለቀ መሆኑ ግልፅ ነው። እናም በሁሉም አቅጣጫ የትግላችንን ትንቅንቅ ልንቀጥል ይገባል እላለሁ።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

የምርጫ ቦርድ ቧልት ! YIDNEKACHEW KEBEDE

—————–
ከምንም በላይ ለነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል ትኩርት በመስጠት ሰማያዊ ፓርቲ ለቦርዱ ጥያቄ አቅርቧአል፡፡ ፓርቲያችን ለሚያቀርባቸው ተደጋጋሚ ጥያቂዎች አዎንታዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ምርጫ ቦርድ ሲንደፋደፍ ማየት የተለመደ ክስተት ነው፡፡
————————
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በታሕሣሥ 28/2007 ዓ.ም ባደረግው ስብሰባ፣ሰማያዊ ፓርቲ እስከ ጥር 4/2007 ዓ.ም ፣ምርጫ ቦርድን ይቅርታ በመጠየቅ የይቅርታ ደብዳቤ እንዲያስገባ ውሳኔ ማሳለፉን በ EBC የዜና እወጃው፤ የምርጫ ቦርድ የህዝብ ግንኝነት ኃላፊ ቀርበው ተናግረዋል፡፡ ፓርቲያችን በጉዳዩ ዙሪያ የሚሰጠው ውሳኔ እንደተጠበቀ ሆኖ፣እኔ በግሌ እንዲኸ ዓይነቱ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር የማይሞከር ፍፁም ድፍረት የተሞላበት የሞኝ አሞኝ ጨዋታ ምርጫ ቦርድ ባይሞክረው የተሻለ ነበር፤የሚል እምነት አለኝ !
ሰማያዊ ፓርቲ በመልመልመጥ ወይም በልመና ላይ የተመሠረት የፓለቲካ ውሳኔ እንደማያሳልፍ ዛሬ ብቻ ሣይሆን ከምስረታው ጀምሮ የሚታወቅበት የፀና አቋሙ ነው፡፡ለዚህም ፓርቲያችን ገና ከምስረታው ጅምሮ ከምርጫ ቦርድ የገጠመው ውጣ-ውረድ እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ፣ከተለመደው ከቦርዱ ጋር የመተሸሸት አካሄድ እራሱን በማራቅ በህግ እና በሞራል የበላይነቱን በማረጋገጥ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባ አዋጅ መሠረት ሕጋዊነቱን ያረጋገጠ ፓርቲ ነው፡፡ምርጫ ቦርድ በወቅቱ የፓርቲያችን ውሳኔ በመቃዎም ደፋ ቀና ማላቱ የሚታወስ ቢሆንም ፣ ምንም ዓይነት የሕግም ሆኖ የሞራል ድጋፍ ስለሌለው የፓርቲያችን ውሳኔ በመቀበል፣ እውቅና ሰጥቻለው በማለት ሊያሳውቀን ችሎአል፡፡
ይህ ከሆነ ከ3 ዓመታ በኋላ “ሰማያዊ ፓርቲ ከምስራታው ጀምሮ በቦርዱ ተመዝግቦ እውቅና ሳይሰጠው ፣እንደተቋቋመ በማስመሰል መግለጫዎችን ሲሰጥ ቆይቷል”በማለት ቁጭት አዘል ማስጠንቀቂ ለመስጠት መቻሉን ለማመልከት ቦርዱ እንደመነሻ የተጠቀመበት አንዱ ክስ ነው፡፡ክሱ ግን ፍፁም መሠረት ቢስ ከመሆኑ ባለፈ ፣ትልቅ ተቋም ነኝ ብሎ የሚያስበው ምርጫ ቦርድ “እንደ-ነገረኛ ሰው” ቂም በመያዝ አሁን ላይ ላሰበው መጥፍ ዓላማ ማስፈፀሚያ ለማድረግ ሲጥር መታየቱ ትዝብት ውስጥ የሚጥል አካሄድ ነው፡፡
ሌላው ደግሞ ምርጫ ቦርድ በተለያየ ወቅት የመወያያ ዕርስ በማዘጋጀት ለፓርቲያችን የእንወያይ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ፣ፓርቲያችን ለቀረበለት ጥሪ አዎንታዊ ምላሽ በመስጠት በቦታው ተገኝቷል፡፡ ይሁን እንጂ ከምርጫ ቦርድ ጋር በተደረገው የፓርቲዎች ውይይት፣ሕጋዊ እና መሰረታዊ ጥያቄ በመጠየቅ እንዲሁም ጠንካራ አቋም በመያዝ ከመርጫ ቦርድ ጋር አለምግባባቶች ተፈጥሯአል፡፡ ፓርቲያችን ለሚያቀርባቸው ጥያቄ እንዲሁም ገንቢ ለሆኑ አሰተያየት ቦርዱ እሱ እንደሚለው “ሆደ ሰፊነቱ”ቀርቶ በአግባቡ የፓርቲያችን አቋም የመረዳት አቅም ቢኖረው የት በተደረሰ ነበር፡፡
በተለይ ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ ፓርቲ ይቅርታ እንዲጠይቅ ያስገደደበት ዋና ዋና ምክንያቶች “በምርጫ አልመግባባት እና የግጭት አፈታት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዝግጀት” ታህሳስ 3/ 2006 ዓ.ም፣ “የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ አስመልክቶ የአፈጻፀም የጊዜ ሠሌዳ” ታህሳስ 7/2007 ዓ.ም እና “የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ አስመልክቶ መንግስት ለሚያድርገው የፋይናስ ድልድል” ታህሳስ 22/2007 ዓ.ም በተካሄደው የፓርቲዎች ምክክር ላይ ሰማያዊ ፓርቲ የያዘው አቋም ነው፡፡
ከላይ በተጠቀሱት ዕርስ ዙሪያ በተደረጉ ውይይቶች ሰማያዊ ፓርቲ ፣ገዥው ፓርቲ በጉዳይ ፈጻሚው የምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ በምርጫ ሥም ለመሥራት የተያያዘውን እኩይ ተግባር ራቁቱን የሚያስቀር፣ ምክንታዊ የመወያያ አጀንድ በማቅርብ፣ ሰማያዊ ላቀረበው ጥሪ ቦርዱ ለመቀበል ፍቃዳኛ አለመሆኑ ለማረጋገጥ ተችሎአል፡፡ከምንም በላይ ደግሞ ለነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል ትኩርት በመስጠት ለቦርዱ ጥያቄ አቅርቧአል፡፡ ፓርቲያችን ለሚያቀርባቸው ተደጋጋሚ ጥያቂዎች አዎንታዊ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ምርጫ ቦርድ ሲንደፋደፍ ማየት የተለመደ ክስተት ነው፡፡
ቦርዱ ከመንደፋደፍ ተግባሩ ተላቆ ወደ-እውነተኛ መንገዱ እንዲገባ የተደረገው ተደጋጋሚ ጥርተ ባለመሣካቱ፣ በሰለጠነ መንግድ ምርጫ ቦርድ የሚያዘጋጃጀቸው የውይይት መድረኮች ፓርቲያችን የተጣለበት የህዝብ አደራ ለመወጣት ስብሰባዎችን እረግጦ ውጥቷአል፡፡ይህ ደግሞ የተለመደ የተቃዎሞ መግለጫ ዘዴ ከሆኑት ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ላይ የያዘው አቋም ተገቢ ብቻ ሣይሆን ሕጋዊም ጭምር ነው፡፡ይልቁንስ መሆን ካለበት ፓርቲያችን ለጠየቃቸው ጥያቄ እና ለሰጠው ገንቢ አሰተያየት ፈጣን ምላሽ ባለማግኘቱ ምርጫ ቦርድ ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል፡፡
የምርጫ በርድ ለገዥው መንግስት የማድላት አደገኛ ሱስ መጠመዱን የሚያሳብቅ ደርጊቶች ሲፈፅም ማየት ለኢትዮጵያዊያን አዲስ ነገር አይደለም ፡፡ ይልቁንም እንዲህ አይነቱ አስመሣይ አካሄድ የሚፀየፍ ፣እውነተኛ እና ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ ተቋቁሞ ኃላፊነቱን ሲወጣ ማየት የአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ምኞት ነው፡፡ ሕዝብን የማስተባበር እና የመምራት ኃላፊነት ያለባቸው ፓርቲዎች ሰማያዊ ጭምር ለዚህ ተግተው እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ ይህን ለማለት የበለጠ ድፍርተ የሚሰጠኝ፣ሰማያዊ ፓርቲ ከሌሎች 8 ፓርቲዎች ጋር በመተባበር በመጪው ምርጫ ሂደት ላይ እና በምርጫ ቦርድ ላይ ያለው አቋም ነው፡፡
የ2007 አገር አቀፍ ምርጫ አስመልክቶ “ነፃነት ለፍትሓዊ ምርጫ “በሚል መርዕ በሁለት ዙር የተከፈለ ሕዝባዊ ንቅናቂ በመፍጠር በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ፡፡ ዘጠኙ የትብብር ፓርተሪዎች የመጪው ምርጫ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል ትኩርት በመስጠት እስከ ሕይወት መሰዋትነት በመክፈል የህዝብ የስልጣን ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ቆርጠው ተንስተዋል፡፡ ይህ አይነቱ አካሄድ ያልተዋጠለት ገዥው መንግስት በጉዳይ ፈፃሚው በምርጫ ቦርድ አማካኝነት የትብብሩን እንቅስቃሴ ለመግታት በመጣር ላይ ይገኛል፡፡ ይሁን እንጄ የዘጠኙ ትብብር ፓርቲዎች ተስማምተው ለማስፈፀም የተነሱለትን ዓላማ፣ በኽንዲ ዓይነቱ ተልካሻ ምክንያት ወደኋላ የሚሉበት አንዳችም ምክንት እንደማይኖራቸው ከመነሻቸው የያዙት አቋም የሚያመላክት ነው፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

Image

ብንውጠም ባንውጠውም ቢያቅለሸልሸንም ቢያስመልሰንም ፖለቲካ ውስጥ ካለ እውቀት ተዘፍቀን የምንዋልል የደረቅ ትኩሳት መርህ ተጠቂዎች እና የስሜት ፈረስ ጋላቢዎች ማወቅ ማገናዘብ ባይፈጥርብንም ካሳለፍነው ካለው የሚምጣውን እንዳቅማችን ለማንደርደር ማሰብ እንዲጠበቅብን መመከርን ባንጓጓም አንድ ነገር ግን እንድናውቅ በራሳችን የገደል ማሚቱ ውስጥ እያላተም መጎላኮስ የሚኖርብን ነገር ቢኦር እውነት ሰአቷን ጠብቃ ነጻ ትወጣለች !!! የሚለውን ሃቅ ነው:: እኛ የሚለውን በእናንተ ሂሳብ አወራርዱት::

የዚህ ሰሞን የወሬ መላምቶች ወደ ተግባር በረራ ተለውጠው ብርቱዎቹ አስመራ ከትመዋል:: በደጋፊ በተባባሪ በጠርጣሪ እና በተቃዋሚ ብልቶች መካከል በየማህበራዊ ድህረገጹ እና ፓልቶክ የጡዘት ስሪቶች እየተፈተሉ ነው::ደጋፊ በኢትዮጵያ ላይ ያለው የሰቆቃ ስርአት ከስሩ ተመንግሎ እንዲወድቅ ካለው መልካም ምኞት በሃገር ወዳድነት ስሜት ሃሳቡን ሁሉ እዚያው አድርጎ ይተነገረውን ሁሉ ተቀብሎ በመፍከንከን ላይ ሲሆን ተባባሪዎች ደሞ የነአይዞን ስራቸውን በፖለቲካው ንግድ ውስጥ እያጧጧፉት ነው::ተጠራጣሪው በዋናነት ያተኮረው በሻእቢያ ላይ ያለውን እምነት በማሰላሰል አስመራ ለከተሙት ብርቱዎቹ ኢትዮጵያውያን ደህንነት ሲሆን በለሆሳስ ጸሎቱን በማደረስ ላይ ሲሆን ተቃዋሚ የተባሉት ያው የወያኔ አሽከሮች የዘመኑ ፖለቲካ እና የለውጥ ማእበል ያልገባቸው ድፍርስ ሆዳሞች ሲያላዝኑ ማየት ምን ያህል እውቀት አልባ እንደሆኑ ሲመዘን ያሳፍራል::

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዋና አጀንዳ ሻእቢያ ሳይሆን ወያኔ ነው::በኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ እንግልት እስር ሰቆቃ ግድያ ወዘተ እየፈጸመ የሚገኘው የህዝቦች ጠላት ወያኔ እና ወያኔ ነው!ይህንን ስር አት ለማውረድ በውስጥም በውጭም በስፋት ትግሉ ቀጥሎ ይገኛል:; ከበፊቱ በትሻለ ሁኔታ የተያዘው ትግል ወያኔን እያፍረከረከ በራሱ ፍርሃት እንዲሸበር አድርጎታል::ሊቀጥል የሚገባው ትግል መሆኑ እሙን ነው::በውጪው ያለው ሃይል በትጥቅ ትግል ተሰማርቻለሁ የሚሉ ቡድንኖች ከ15 አመታት በላይ በአስመራ መሽገው ይገኛሉ::እነዚህን ሃይሎች በትለያየ ጊዜ የተቀላቀሉ የጎበኙ የተገነጠሉ ወዘተ አካላት የየራሳቸውን አስተያየት በይፋ ስጥተዋል::ወያኔን ለመጣል ካላቸው ፍላጎት የመነጨ በአስመራ የመሸጉትን ታጋዮች ጎብኝተናል ያሉ ሁሉ ከበጎ ጎኑ ተነስተው ኢሳያስ አፍወርቂን እስከ ማሞገስ እና እጅ እስከመሳም ከመድረስ አልፈው ሁኔታዎችን እያጠሩ ሂደው በተመጣጠነላቸው ሰአት ላይ እውነታውን አፈንድተውታል::እውነታውን በማውጣታቸው ይህን ተከትሎ በአስመራ በነበሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ከግድያ እስከ እስር እና እንግልት ደርሶባቸዋል:;ማምለጥ የቻሉም አምልጠው ኤርትራን ለቀዋል::

ጎን ለጎንም አስመራ ከትመው የሻእቢያ ስራ አያዋጣን ደባውና ሴራው ለኢትዮጵያ ነጻነት በሚደረጉ ትግሎች ላይ ከፍተኛ እንቅፋት ነው በሻእቢያ እርዳታ ነጻነት ሳይሆን ባርነት ነው የገዛነው ታጋዮቻችን በስልተና ሳይሆን በጉልበት ስራ ላይ ተሰማርተው ቀን እየገፋን አንችልም ሻእቢያ በበቂ ሁኔታ አደራጅቶ እንድንዘምት ሊያደርገን ሳይሆን ብስማችን ገንዘብ እየሰበሰበ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ እንጂ ውጤት የለውም ያሉ አስመራን ትተው ሃገር ቤት እስጥ የትጥቅ መሰእረታችንን ዘርግተናል ብለዋል::እንዲሁም ከጨካኙ ወያን ጋር በመቀላቀል የታጋይ ድርጅቶችን ምስጢር በመባከን በመሰለል ደባ የፈጸሙ ቅጥረኞችም የማይርሳ መጥፎ ተባሳ እና የትግል መጓተት አስከትለዋል::

የሰሞኑ አነጋጋሪ ጉዳይ ደሞ አንደ እውነት ካለ በፍጥነት ከዘገየ ደሞ ቀኑን እና ሰአቱን ተብቆ እንደሚያሰማን ራሳችንን አዘጋጅተን እየጠበቅን ነው::ሁኔታዎችን በጠራ መንገድ ተከታትለን አይተን እንዘግባለን ያሉ ብርቱዎቹ ኢትዮጵያውያን አስመራ ደርሰው በረቀቀ መንገድ ችሎታቸውን እና ክህሎታቸውን ተጠቅመው አንድ እውነት ይዘው እንደሚመጡ የታመነ ሲሆን ግን ግን ወዲያው እንደማይተነፍሱን የተረጋግጠ ጉዳይ ነው::ከዚህ በፊትም አስመራ የደረሱ ከታች እስከ አናቱ ኢሳያስ ድረስ ቃለመጠይቅ ያደረጉ ውነታውን ያጠሩት በሂደት ሲሆን እነዚህም ብርቱዎቹ እንደአካሄዳቸው ተመልሰው ያለውን ሁኔታ እና እውነታ በሂደት እንደሚያሳውቁን ተስፋ ሰንቀናል:: ሻእቢያ እና ልጁ ወያኔ በሃሰት ዶክመንተሪ እና በዉሸት ፕሮፓጋንዳ የታወቁ የፈጠራ ደራሲዎች ቢሆኑን ህዝቡ እውነታውን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ በተግስት በመከታተል ትግሉ እያፋፋመ እንደሚገኝ እሙን ነው::በኤርትራ ሃገርን ከዛሬ ነገ ዘምተን ነጻ እናወጣለን ብለው ሰልጥነው በበረሃ የተቀመጡት ታጋዮች ለነሱ ሕይወት እና ደህንነታዊ ጥንቃቄ ሲባል ራሱን የቻለ የቅብብሎሽ ሂደት ቢኖርም እውንት ግን ሰአቷን ጠብቃ ነጻ ትወጣለች::ፖለቲካ የሚገባው ይገባዋል የማይገባው ጭፍን ግን አንብቦ ምራቁን ይዋጥና አርፎ ይጸልይ::

Image

=====================================
አንዳንዶች ከማይቀረው ዕጣ ፈንታቸው አይናቸውን ጨፍነው ይሸሻሉ፤
የሚሸሹበት መንገድ ግን ወደማይቀረው ዕጣ ፈንታቸው በፍጥነት ያደርሳቸዋል፡፡
=====================================

ሰሞኑን ኢህአዴግ በምርጫ ቦርድ በኩል የያዘውን ዘመቻ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ዘመቻው አንድነትን፣ መኢአድንና ሰማያዊ ፓርቲን ከምርጫ 2007 ሜዳ ገፍቶ ማስወጣት ነው፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች በኢህአዴግ ጥቁር መዝገብ ላይ የሰፈሩበት ምክኒያት ደግሞ ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በምርጫ 2007 ኢህአዴግ የሚያጭበረብርበትን መንገድ ዘግተው ከፍ ባለ ድርጅታዊ ጥንካሬና በቁርጠኛ አመራር የኢህአዴግን መጨረሻ ለማወጅ ስለተነሱ ነው፡፡ ኢህአዴግ የሚሸሸው በ2007 ሊገጥመው የሚችለውን የሽንፈት ዕጣ ፈንታ እንደሆነ ተግባሩ ያሳብቅበታል፡፡ ሽሽቱ የኤዲፐስ አይነት ስለሆነ ከዕጣ ፈንታው ሊያመልጥ ግን አይችልም፡፡

ኤዲፐስ፣ በግሪክ አፈታሪክ ውስጥ ያለ ገጸ-ባህሪ ነው፡፡ አባቱ የቲብዝ ንጉስ ነበር፡፡ እናትና አባቱ የልጃቸውን ዕጣ ፈንታ (አባቱን የሚገድል እናቱን የሚያገባ ልጅ እንደወለዱ) ቴረሲያስ ከሚባል አንድ ነብይ ሰምተው ስለነበር እያዘኑ እንዲሞት ይፈርዱበታል፡፡ እናም ለእረኛቸው ግደል ብለው ሰጡት፡፡ እረኛው አልጨከነም፡፡ ለሌላ አሳዳጊ ሰጠው፡፡ ኤዲፐስ ከንጉስ ቤት እንዲገደል ወጥቶ በሌላ ንጉስ ቤት አደገ፡፡ እውነተና እናትና አባቱን ሳያውቅ ጎረመሰ፡፡ ባንድ ክፉ ቀን አንድ ነቢይ የራሱን ዕጣ ፈንታ “አባትህን ትገላለህ እናትህን ታገባለህ” ሲል አረዳው፡፡ ኤዲፐስም አወጣ አወረደና አባቴን ገድዬ እናቴን ከማገባ ብሎ ሰረገላውን አሰናድቶ ፈረሱን መጭ እያለ ከሀገር ለመጥፋት በረረ፡፡ የሚሄደው ሀገር ወደ ቲብዝ ነበር፡፡ ቲብዝ ያለው ንጉስ አባቱ መሆኑን ግን አያውቅም ነበር፡፡ መስቀለኛ መንገድ ላይ ከአባቱ ጋር ተገናኘ፡፡ አሳልፈኝ አላሳልፍም በሚል የክብር ጥያቄ ጠብ ገጠሙ፡፡ ኤዲፐስ አባቱን ገደለው፡፡ ቲብዝ ያለ ንጉስ ቀረች፡፡ ኤዲፐስ የአባቱን ሚስት አግብቶ በቲብዝ ላይ ነገሰ፡፡

የኤዲፐስ ታሪክ ባጭሩ ይሄ ነው፡፡ ኤዲፐስ ከዕጣፈንታው አይኑን ጨፍኖ ሸሸ፡፡ የሸሸበት መንገድ ግን ወደማይቀረው ዕጣ ፈንታው በፍጥነት አደረሰው፡፡

ኢህአዴግም የኤዲፐስን መንገድ የመረጠ ይመስላል፡፡ በ2007 ምርጫ ከማይቀረው የሽንፈት ዕጣ ፈንታው አይኑን ጨፍኖ እየሸሸ ነው፡፡ የሚሸሽበት መንገድ ግን ወደ ማይቀረው ዕጣ ፈንታው በፍጥነት እያደረሰው እንደሆነ በግልጽ እየታየ ነው፡፡

አንድነት ገና ከጠዋቱ ምርጫው ላይ ያለውን አቋምና ስትራቴጂ ግልጽ አድርጓል፡፡ “ምርጫ ውስጥ እንገባለን፣ አንድነት እንዲመረጥ እንቀሰቅሳለን፣ የህዝብን አሸናፊነት ኢህአዴግ በማጭበርበር ቀለብሳለሁ ካለ ደግሞ አስጨናቂ በሆነ ህዝባዊ እምቢተኝነት የህዝብን ድምጽ ለማስከበር የተቀናጀና ቁርጠኛ አመራር እንሰጣለን፡፡” ብሏል፡፡ ይህ አቋም አሁንም ያለ ነው፡፡ ኢህአዴግ ከምርጫው በፊት ማጭበርበር ውስጥ ከገባ ውድቀቱም ከምርጫው በፊት ይሆናል፡፡ ሽሽቱ እጣፈንታውን ቢያፈጥነው እንጂ ከሽንፈት አያስመልጠውም፡፡

ቺርስ! ለነገው ብሩህ ቀናችን፡፡

ስለሺ ሐጎስ

Image

Image

– አንድነት ፓርቲ በድጋሚ የምርጫ ቦርድን ደባ ለማክሸፍ ጠቅላላ ጉባዬ ጠርቷል::
– አንድነት ፓርቲን ከሰላማዊ ትግሉ ለማስወጣት የተደረገውን ደባ ተጋልጧል::
Minilik Salsawi
የወያኔው አምባገነን ጁንታ የአንድነት ፓርቲ በ2007 በሚደረገው ምርጫ ላይ እንዳይሳተፍ በሕወሓት/ኢሕአዴግ ፖለቲካዊ ውሳነ ተደርጎበት ወደ ምርጫ ቦርድ እንደተላለፈ እና ፓርቲውን ከምርጫው ለማስወጣት ደባ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተጠቆመ:: እንደ ምንጮቹ ከሆነ ሕወሓት/ኢሕአዴግ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችን እና አባላትን ከማሰር እና ከማንገላታት ጀምሮ እስከ ምርጫ ቦርድ ማሸማቀቀ እና ሰበብ ማብዛት ቢሞክርም አንድነት ፓርቲ ይህንን ሁሉ ተቋቁሞ በአሸናፊነት መገስገሱ ለገዢው ፓርቲ መደናገጥ በመፍጠሩ ፓርቲው በምርጫ እንዳይሳተፍ ውሳኔ ማስተላለፉን ተገልጿል::

የአንድነት ፓርቲ አደገኛ የሆነበት ሕወሓት/እሕአዴግ ምርጫ ቦርድን ተገን በማድረግ ከምርጫ ለማስወጣት እንዲሁም ተለጣፊ አንድነት ፓርቲ ለመመስረት በመጣር ላይ ሲሆን ዓላማው በአባላት፣ በደጋፊና በህዝቡ ውስጥ ውዥንብር ለመፍጠር ታሰቦ የሚካሄድ ፖለቲካዊ ደባ ነው፡፡ አንድነት ፓርቲ ባስተላለፈው መግለጫ እንዳለው በሀገራችን አስተማማኝ ሠላም እና ዘላቂነት ያለው ደህንነት የሚያረጋግጠው እንደ ምርጫ ቦርድ ያሉ ተቋሞች ነፃ፣ ገለልተኛ እና በህዝብ ዘንድ አመኔታ ሲጣልባቸው ነው፡፡ ይህ ተቋም አሁን በያዘው ሁኔታ ከቀጠለ ከታሪክ ተጠያቂነት አይድንም፡፡ ገዢው ፓርቲም ጧት ማታ የሚያባንነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡

በመሆኑም አሁን ፓርቲያችንን ለመታደግ እና የቦርዱን የመጨረሻ ካርድ ለማስጣል አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርተናል፡፡ ይህ ማለት የትግሉ መጨረሻ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያደረሰብንን የሕግ ጥሰት ይዘን በፍርድ ቤት ክስ እንመሰርታለን፡፡ እስከ አሁን ያለውን ሂደት ስናየው የቦርዱ ፖለቲካዊ ደባ ቀጣይ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ስለሆነም መላው አባሎቻችን፣ ደጋፊዎቻችን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ለምንወስዳቸው ተከታታይ ፖለቲካው ውሳኔዎች እና እርምጃዎች ከጎናችን እንዲቆም ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን፡፡ ብሏል አንድነት ፓርቲ::

እንደ ፓርቲው ምንጮች ምርጫ ቦርድ እና ኢህአዲግ ባሰማራው ጥቂት ቡድን አማካኝነት አንድነት ፓርቲን ከሰላማዊ ትግሉ ለማስወጣት የተደረገውን ደባ አቶ ብርሃኑ ይግለጡ እና አቶ መሳይ ትኩ ያጋለጡ ሲሆን ቭዲዮው ይለቀቃል ተብሎ ይጠበqaል::

Image
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
በየትኛውም የአለም ክፍል በተለያየ አጣራርና ስያሜ ቢሰጣቸውም ምርጫን ለማስፈፀም በሕግ የሚቋቋሙ ተቋማት ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ተቋማት በአንድ ሀገር ዘላቂ ለሆነ ሠላምና መረጋጋት ብሎም ለዴሞክራሲዊ ስርዓት ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡ እንደ ኢትዮጵያ በአንባገነን ስርዓት ውስጥ ላሉ ሀገሮች ደግሞ ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ያላቸው ሚና ከምንም በላይ ከፍተኛ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራው ምርጫ ቦርድ ይህን የመሰለ ግዙፍ ተግባር እንዲያከናውን፣ የሕዝብ እና የሀገር አደራ እንዲወጣ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ የዚህ ተቋም አሰራር በተቋቋመለት ዓላማ፣ ሕግ እና አለም አቀፍ መስፈርት መሠረት ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ዴሞክራሲያዊ እና በህዝብ ዘንድ ተአማኒነት ያለው መሆን ይጠበቅበታል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀደሙት አሠራሮችና ውሳኔ አሰጣጦች በበርካታ ኢትዮጵያውያን እና አለም አቀፍ ታዛቢዎች በአሉታዊ ጎኑ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የ2ዐዐ7 ሀገር አቀፍ ምርጫን ‹‹የኢህአዴግ መጨረሻ›› እናደርገዋልን ብሎ ፖለቲካዊ አቋም ወስዶ እንቅስቃሴ ሲጀምር የምርጫ ቦርድን ቀደምት አሉታዊ ተግባሩን ዘንግቶ አይደለም፡፡ ይህ ተቋም መልካም ስም እንዲገነባ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመሆን እድል ለመስጠት ነበር፡፡ በዚህ ስትራቴጂ መሠረት ቦርዱን በተግባር ፈተና ላይ ጥለነዋል፣ ማንነቱንም ለኢትዮጵያ ሕዝብ እና ለዓለም ማህበረሰብ በማጋለጥ ላይ እንገኛለን፣ ዛሬ ለሁለም የሚዲያ አካላት ያካሄድናቸውን የደብዳቤ ልውውጦች በይፋ አንሰጣለን፣ ሁሉም ዜጋ እንዲደርሰውም እናደርጋለን፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነት ፓርቲን ከ2ዐዐ7 አጠቃላይ ምርጫ ገፍቶ ለማስወጣት ካልተሳካለትም በተዳከመ የአባላትና ደጋፊ ስሜት ውስጥ ገብተን እንድንጫወት የፈለገ ይመስላል፡፡ ይህ ደግሞ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲ በ2ዐዐ7 ዓም ሀገራዊ ምርጫ ከጅምሩ በሁሉም ሂደቶች በንቁ ለመሳተፍ የያዘው አቋም እንዳስደነገጠው፤ ከዚያም አልፎ ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠውን ስልጣን አጣለሁ በሚል መሸበሩን የሚያጋልጥ ነው፡፡ ይህን ፍርሃቱን በህዝብ ፊት በሚደረግ ትግል ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ የመረጠው ሜዳ በብሔራዊ ምርጫ ቦርደ በኩል እንዲሆን ነው፡፡ የቦርዱ ኃላፊዎች ተቋማዊ በሆነ መልክ ደብዳቤ ሲሰጣቸው፣ በደብዳቤ መልስ ከመስጠት ይልቅ በመገናኛ ብዙሃን ምላሻቸውን ቀድመው መናገር ጀምረዋል፡፡ ለዚህም ማሳያው ታህሣሥ 27 ቀን 2ዐዐ7 ዓም የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር አዲሱ ገብረ እግዝአብሔር ከቦርዱ ስብሰባ በፊት በሚዲያ ወጥተው ውሳኔ በመገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል፡፡ ይህ የሚያሳየው ቦርዱ እንደተቋም ሳይሆን በግለሰብ ውሳኔ የሚመራ መሆኑን ነው፡፡ ለዚህም መገለጫው በታህሳስ 30/2007 የደረሰን ደብዳቤ የቦርዱን ምክትል ስብሳቢ ከሚዲያ መግለጫ ጋር ተመሳሳይ መሆኑ ነው፡፡ ከምርጫ ቦርድ ባልተናነሰ ሁኔታ በኢትዮጵያ በህግ የተቋቋሙት እና በህዝብ ሀብት የሚንቀሳቀሱት የመገናኛ ብዙሃንም በፍጥነት ተቀብለው ማስተጋባታቸው በውዥንብር ፈጠራ ላይ ተሳታፊነታቸውን ያሳያል፡፡ ዓላማው በአባላት፣ በደጋፊና በህዝቡ ውስጥ ውዥንብር ለመፍጠር ታሰቦ የሚካሄድ ፖለቲካዊ ደባ ነው፡፡

በሀገራችን አስተማማኝ ሠላም እና ዘላቂነት ያለው ደህንነት የሚያረጋግጠው እንደ ምርጫ ቦርድ ያሉ ተቋሞች ነፃ፣ ገለልተኛ እና በህዝብ ዘንድ አመኔታ ሲጣልባቸው ነው፡፡ ይህ ተቋም አሁን በያዘው ሁኔታ ከቀጠለ ከታሪክ ተጠያቂነት አይድንም፡፡ ገዢው ፓርቲም ጧት ማታ የሚያባንነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት መምጣቱ አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም አሁን ፓርቲያችንን ለመታደግ እና የቦርዱን የመጨረሻ ካርድ ለማስጣል አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርተናል፡፡ ይህ ማለት የትግሉ መጨረሻ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያደረሰብንን የሕግ ጥሰት ይዘን በፍርድ ቤት ክስ እንመሰርታለን፡፡ እስከ አሁን ያለውን ሂደት ስናየው የቦርዱ ፖለቲካዊ ደባ ቀጣይ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ስለሆነም መላው አባሎቻችን፣ ደጋፊዎቻችን እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ለምንወስዳቸው ተከታታይ ፖለቲካው ውሳኔዎች እና እርምጃዎች ከጎናችን እንዲቆም ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን፡፡

ድል የሕዝብ ነው
ጥር 1 ቀን 2ዐዐ7 ዓም
አዲስ አበባ

Minilik Salsawi – ፍላጐታችንን ያከበሩ በመምሰል ፍላጐታቸውን የሚያሟሉ ሰዎች አደገኞች ናቸው፡፡ ፀሐይ የሚሞቅ ውሻ ሁሉ ሞኝ አይደለም፡፡አሉባልታዊና ሐሜተኛ ማህበረሰብ እየተገነባ ከመጣ የመዝቀጥ አሊያም የመበስበስ ክፉ አባዜ መምጣቱን ይጠቁማል፡፡ አሉባልታ የሚቆመው ግልፅነትና መረጃ ሰጪነት ሲከበር ነው፡፡የሌሎችን ግብና አዕምሮ ማማለልንና ማዘናጋትን የሚያውቁበት ሰዎች እንዳሉ አንርሳ! ተስፋ በመስጠት እንደዳማና እንደ ቼዝ ጠጠር (ወታደር) በፈለጉት አቅጣጫ ይገፉናል፡፡ ፍላጐታችንን ያከበሩ በመምሰል ፍላጐታቸውን የሚያሟሉ ሰዎች አደገኞች ናቸው፡፡ ፀሐይ የሚሞቅ ውሻ ሁሉ ሞኝ አይደለም፡፡ ለነገ እበላዋለሁ የሚል ጅል ተኩላ ግን ምን ጊዜም አይጠፋም፡፡ ይህን ሁሉ የሚታዘብ ህዝብ እንዳለ የሚያውቅ ካለ የብልህም ብልህ ነው፡፡ በዚህ የተካኑ ሰዎችን በዐይነ – ቁራኛ ማየት ያባት ነው፡፡ ስሜትን ተቆጣጥሮ ደባና ሴራን ጠንቅቆ ማየትና በጠዋት መንቃት ተገቢ ነው፡፡ ድቀትና ዝቅጠት ሲያይል አሉባልታና ጥርጣሬ ይነግሳል፡፡

በእንዲህ ያለው ሰዓት አፍ – አዊ እየበረከተ፣ ልባዊና ተግባራዊ እየሳሳ ይመጣል፡፡ ይሄኔ መጠንቀቅ ይበጃል፡፡ የአንድ ነገር ዋጋ በዚያ ተገልግለን በምናገኘው ጥቅም አይለካም፡፡ ይልቁንም ያንን ነገር ለማግኘት በምንከፍለው መስዋዕትነት ነው የሚለካው፡፡ አገር እንገነባለን ስንል ይህን ብሂል አለመርሳት ነው፡፡ ይሆነናል የምንለውን ሰው መርጠን ስንሾምም ይህንን አለመዘንጋት ነው፡፡ ባለሙያው እያለ ስለዚያ ሙያ የሚያወራ ሲበዛ ጠንቀቅ ማለት ያሻል፡፡

ፕሮፓጋንዳ ብቻውን ሁሉን ጉዳይ አይጨርስልንም፡፡ አስተዋይ አመራር፣ አስፈፃሚና ተጠያቂነትን ገምጋሚ እንዲኖር ያሻል፡፡ ያ ደግሞ ግልጽነትን ልማድ የሚያደርግ መሆን አለበት፡፡ አሉባልታ የሚቆመው ግልፅነትና መረጃ ሰጪነት ሲከበር ነው፡፡በምንም ዓይነት ግን የፖለቲካ ትግልን እንደማይተኩልን ማሰብ ተገቢ ነው! የፖለቲካ ትግል ከሁሉም በፊት መደራጀትን፣ ተደራጅቶም መስዋዕትነትን፣ በሀገር ላይ ለውጥ የማየት ልባዊ ስሜትን ይጠይቃል! በተግባር ሳይሆን አሉባልታዊና ሐሜተኛ ማህበረሰብ እየተገነባ ከመጣ የመዝቀጥ አሊያም የመበስበስ ክፉ አባዜ መምጣቱን ይጠቁማል፡፡ ተግባራዊና የሚለውን የሚተረጉም ማህበረሰብ ካልፈጠርን ሟርት ይበዛል ::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

Image

አንድነት መኢአድና ሰማያዊ ከምርጫ ቦርድ ጋር ሲካሰሱ መድረክና ኢዴፓ ውይይት ይፈልጋሉ::
Minilik Salsawi-አንድነትና መኢአድ የውስጥ ችግራቸውን ካልፈቱ በምርጫ ላይሳተፉ ይችላሉ::የሚል መግለጫ ምርጫ ቦርድ ም/ሰብሳቢ ዶክተር አዲሱ ገ/እግዚአብሔር በራዲዮ ፋና መስጠታቸውን ተከትሎ;የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ ስብሰባን ረግጦ መውጣቱን አስታኮ በመጭው ምርጫ ላይ ውጥረት ማጥላቱን መረጃዎች ሲጠቁሙ በሌላ በኩል መድረክ እና ኢዴፓ የግንቦቱ ምርጫ ሂደት ላይ ቅሬታዎች አሉን በማለት ከወያኔ/ኢሕአዴግ ጋር መደራደር(መወያየት)እንደሚፈልጉ እየተናገሩ ይገኛል::

ምርጫ ቦርድ እያለ ራሱን የሚጠራው ኢሕአዴጋዊ ተቋም አንድነት እና መኢአድ በህገ- ደንባቸው መሰረት ውስጣዊ ችግራቸውን እንዲፈቱ በቦርዱ ቢነገራቸውም ችግራቸውን ሊፈቱ አልቻሉም እያለ ሲከስ መስመራቸውን ስተዋል ብሎ እንዳመጣለት በመወንጀል በምርጫ ሊሳተፉ እንደማይችሉ ቢናገሪም የፓርቲዎቹ አመራሮች ግን ምርጫ ቦርድን በመቃወም አስፈላጊ የሚባሉ ፖለቲካው እርምጃዎችን እና ውሳኔዎችን እንደሚያደርጉ አስጠንቅቀዋል::ይህ በፓርቲዎቹ እና በምርጫ ቦርድ መካከል የተነሳው እሰጥ አገባ እና ፓርቲዎችን ከፋፍሎ መወንጀል በዋናነት ህዝቡን እያነጋገረ መሆኑ ታውቋል:: ከዚህ ጋር በተያያዘ ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቦርድ በጠራው ገንዘብ የማከፋፈል ስብሰባ ላይ በሃሳብ እና በገንዘብ ክፍፍሉ ባለመስማማቱ ስብሰባዉን ረግጦ የወጣ ሲሆን ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ ፓርቲ ይቅርታ ይጠይቀኝ ሲል ኢሕአዴጋዊ መመጻደቅ እያደረገ ይገኛል::የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በምርጫ ቦርድ የይቅርታ ፉጨት እንደማይገርማቸው እና የተቋሙን ልፍስፍስነት እንደሚያመለክት እየተናግሩ ነው::

መድረክ እና ኢዷፓ የግዢው ፓርቲ ታማኝ ተቃዋሚ የሚባሉ ሲሆን በለዘበ ሁኔታ የግንቦቱ ምርጫ ሂደት ላይ ቅሬታዎች አሉን በማለት ከወያኔ/ኢሕአዴግ ጋር መደራደር(መወያየት)እንደሚፈልጉ እየተናገሩ ይገኛል:: ኢሕ አዴግ ምርጫውን ተገን አድርጎ የፖለቲካ ሙስና እየፈጸመ ነው የሚለው መድረክ በምርጫ ታዛቢዎችና አስፈፃሚዎች አመራረጥና በምርጫው ለሚሳተፉ ፓርቲዎች ከመንግስት በሚሰጠው የድጐማ ገንዘብ ክፍፍል ላይ ቅሬታ እንዳለው ጠቁሟል፡፡መድረክ ይህን ይበል እንጂ ምርጫ ቦርድ ውሳኔው የኔ መብቱም የኔ ነው በማለት አምባርቆበታል::ኢዴፓ በበኩሉ ምርጫው ላይ ቅሬታዎች አሉ ቢሊም ገፍቶ እንዳልታየበት እና በገዢው ፓርቲ አስፈላጊውን ትብብር በየክፍለ ሃገሩ እና መሃል አገር ላይ እየተደረገለት ስለሆነ ብዙም ጫና የሚፈጥር ችግር እንዳሌለ ሲናገር አንዳንድ ችግሮችን ለመፍታት ገዢውን ፓርቲ ለውይይት ሲጠይቅ ምርጫ 2007 በተመለከት መድረክ እና ኢዴፓ ምርጫ ቦርድ ጥርስ የሌለው ውሻ መሆኑን በተዘዋዋሪ እየነገሩት መሆኑን ያመለክታል:: ምርጫውን በተመለከተ ገዢውን ፓርቲ መለማመጥ ይቀላል የሚሉት መድረክ እና ኢዴፓ ከገዢው ፓርቲ ከተወያየን የምርጫ ቦርድ ጉዳይ የሞተ ነው ሲሉ ይናገራሉ::‪#‎MinilikSalsawi‬

በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት ” “ስህተቶችን” ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡
የኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡ በመሆኑም ወደቢሮአችን ተደዉሎ ከኢህአዴግ ፅህፈት ቤት የተደወለ መሆኑ ከተገለፀ በኋላ ለጽሑፌ ምላሽ የላኩ በመሆኑ በፍጥነነት እንድናወጣዉ ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጠን፡፡ ምላሻቸዉን ለማዉጣት የእነሱ መደወልም ሆነ ትዕዛዝ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ የዝግጅት ክፍላችን አንድ ጽሑፍ የቀረበበት አካል ምላሹን በዚያዉ በተፃፈበት የህትመት ዉጤት ላይ ማስነበብ እንደሚችል በህግ የተደነገገ መሆኑን ከማወቁም በላይ የትኛዉንም አይነት ሀሳብ ለማስተናገድ ክፍት ነበርና ምላሻቸዉን በጋዜጣችን ላይ ታተመ፡፡ በዚህ ብቻ ግን አልተገቱም፤ በወቅቱ የገዢዉ ፓርቲን ሀሳብ በማቀንቀን ይታወቁ የነበሩት እንደ ዳጉ ኢትዮጵያና ሰነድ ያሉ ጋዜጦች ሀሳቦቼን በሃሳብ መምታት ባለመቻላቸዉ ይሁን ባለመፈለጋቸዉ ተራ ዘለፋዎችን ያወርዱብኝ ጀመር፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የገዢዉ ፓርቲ ደህንነቶች ስልክ በመደወል፣ በዝግጅት ክፍላችን አድራሻ በስሜ ደብዳቤ በመላክና በአካልም በማግኘት ጭምር መንግስትን የሚተቹ ፅሑፎችን እንዳልፅፍ ሊያስፈራሩኝ ሞከሩ፡፡ “ማስፈራራት የሚቻለዉ የሚፈራ ሲኖር ነዉ” እንዲሉ ሙከራቸዉ ዋጋ አልነበረዉም፡፡ ምክንያቱም የመጀመሪያ ፅሑፌን ለህትመት ከማብቃቴ በፊት ልከፍለዉ ስለምችለዉ መስዋዕትነት በሚገባ አስቤበታለሁ፡፡ የሀገሬን ጉዳይ በንቃት የምከታተል ዜጋ እንደመሆኔም ከገዢዉ ፓርቲ የተለየ ሀሳብ ያቀነቀኑ ሰዎች የደረሰባቸዉን በሚገባ አዉቃለሁ፡፡ በመሆኑም ከሁለት መጥፎ ምርጫዎች አንዱን ማለትም እነሱ የደረሰባቸዉን ግፍ እንዳይደርስብኝ የሀገሬን ጉዳይ በተመለከተ ፍዝ ተመልካች መሆንን ወይም በሙያዬ የምችለዉን አስተዋፅኦ አበርክቼ የሚመጣዉን መቀበል መምረጥ ነበረብኝ፡፡ ሁለተኛዉን የተሻለ መጥፎ ምርጫ ከመረጥኩ የሰነበትኩ በመሆኑም እየበረከቱ የመጡትን ማስፈራሪያዎች ከቁብ ሳልቆጥር የጋዜጠኝነት ስራዬን መቀጠል ቻልኩ፡፡ በዚሁ መሰረት ስራ ለመያዝ፣ የደረጃ እድገት ለማግኘትም ሆነ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከደህንነት ስጋት የፀዳ ኑሮ ለመኖር የኢህአዴግ አባል ካልሆነም ደጋፊ መሆን ከጊዜ ጊዜ ግድ እየሆነ መምጣቱን የሚያሳዩ፣ ገዢዉ ፓርቲ እንዳጎናፀፈን የሚገልፅልን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት በተጨባጭ አለመኖሩን የሚሞግቱ፣ የኢህአዴግን እንደሀገር የማሰብ ችሎታ ወይም ፍቃደኝነት አናሳ መሆን የሚተቹና ሌሎችም መንግስት ቀናነት ቢኖረዉ ኖሮ ሊታረምበት የሚያስችሉትን በርካታ ፅሑፎች አቀረብኩ፡፡ አንድ ቀን ጧት ግን አምባገነኑ መንግስታችን ከጀመርኩት ጉዞ ገታኝ፡፡ ሰኔ10/2003 በወቅቱ እሰራባት በነበረችዉ ተወዳጇ ፍትህ ጋዜጣ ላይ የቀድሞዉን ጠቅላይ ሚኒስትር በተመለከተ ፅሑፍ ለህዝብ ማቅረቤን ተከትሎ ሰኔ14/2003 ዓ.ም ለእስር ተዳረግሁ፡፡
ማዕከላዊና ቃሊቲ ምንና ምን ናቸዉ?
ዉድ አንባብያን፤ ፊዘኛዉ መንግስታችን በሽብርተኝነት እንደሚጠረጥረኝ ገልፆ በእጆቼ ካቴና በማጥለቅ በቁጥጥር ስር አዋለኝ ካዋለኝ ከዚያ ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ለቁጥር የሚያታክቱ የመብት ጥሰቶችን እየፈፀመብኝ ይገኛል፡፡ ለአብነት ያህል እጅግ በጣም ጥቂቶቹን እነሆ!
ከህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነዉ የሚባልለት ህገመንግስት በጥበቃ ስር ያሉ ሰዎች በጠበቆቻቸዉ የመጎብኘት መብት እንዳላቸዉ ቢገልፅም እኔና ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ግን ይሄ መብታችን በማዕከላዊ አለቆች ተጥሷል፡፡ ጠበቃዬን ለማግኘት የተፈቀደልኝ ምርመራዉ ከተጠናቀቀና ቃል ከሰጠሁ በኋላ ወደቃሊቲ ለመዉረድ የአስርቀናት ዕድሜ ያህል ሲቀረኝ ነበር፡፡ በቤተሰብና በጓደኞቼ ለመጎብኘት የተፈቀደልኝም ሁለት ወር ከ3 ሳምንታት ክልከላ በኋላ ነበር፡፡ ከጠበቃዬ ጋር እንዳልገናኝ ተደርጎ የሚካሄደዉ ምርመራ የፃፍኳቸዉን ፅሑፎች ለምን እንደፃፍኩ፣ ከበስተኋላዬ ሆኖ የሚገፋኝ አካል ስለመኖር አለመኖሩና የመሳሰሉት ጥያቄዎች ላይ ያተኮረ ቢሆንም አልፎ አልፎ ደግሞ መልኩን ይቀይራል፡፡ አንዳንድ ቀን መርማሪዎቹ በማስተምርበት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በተካሄዱ ስብሰባዎች ላይ ያቀረብኳቸዉን ሀሳቦች እያነሱ ከመንግስት የደህንነት ሀይሎች የሚያመልጥ ምንም ነገር እንደሌለ በመግለፅ ቢጤ ያሰሙኝ እንደነበር ሳልጠቅስ ማለፍ አልፈልግም፡፡፡ እንዲህ አይነቱ ንግግራቸዉ አሰልቺዉን ምርመራ ዘና እልበት ዘንድ የሚረዳኝ የእፎይታ ጊዜ ሰጥቶኛል፡፡ በአደባባይ ስብሰባዎች ላይ የተናገርኩትንና ደህንነት ሊሰልለዉ የማያስፈልገዉን ግልፅ ነገር እንደ ትልቅ የደህንነቶች የስራ ዉጤት ተደርጎ ሲገለፅ ከመስማት በላይ ምን የሚያዝናና ነገር ይገኛል? የት/ቤት ርዕሰ መምህራኖች በሙሉ የኢህአዴግ አባል እንዲሆኑ የተደረገበት ምክንያት መንግስት እንደሚለዉ የትምህርት ፖሊሲዉን ለማስፈፀም ሳይሆን የመምህራንንና የተማሪዎችን የፖለቲካ አቋም ለማወቅና ይህንኑ ሪፖርት ለማድረግ መሆኑን የማይረዳ መምህር ይኖራል? ይህንን ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆኑ ርዕሰ መምህራኖች ሰበብ እየተፈለገላቸዉ ከቦታቸዉ እንዲነሱ ሲደረግስ ስንታዘብ አልኖርንም? “ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል” አለ ያገሬ ሰዉ! ሆዴ ባዶ እንዳይቀር ሁሉን መተንፈሴን ትቼ የጀመርኩትን የማዕከላዊ ምርመራ ጉዳይ ልቀጥል፡፡
የምርመራዉ ይዘት ከጥቂት ሳምንታት በኋላ መልኩን እየቀየረ መጣ፡፡ በሪፖርተርነት እሰራበት የነበረዉ የኢትዮጵያ ሪቪዉ ድረገፅ አዘጋጅ ኤልያስ ክፍሌ የሽብር ተልዕኮ እንደሰጠኝ በሀሰት እንድናገርና ተከሳሽነቴ ቀርቶ ምስክር ሆኜ እንድፈታ ለማድረግ የተለያዩ ጫናዎቸው ይደርሱብኝ ጀመር፡፡ ለአምስት ደቂቃ ያህል ጧትና ማታ ወደመፀዳጃ ቤት ለመሄድ ከሚከፍቱልኝ በስተቀር ለአስራሶስት ቀናት ያህል ብቻዬን አንድ መጥፎ ሽታ ያለዉ ክፍል ዉስጥ ተዘግቶብኝ ከረምኩ፡፡ በዚህ ወቅት ጉዳዬን የያዘዉ ዐቃቤህግ ማዕከላዊ በመምጣት እያስጠራኝ ሀሳቤን የማልለዉጥ ከሆነ እድሜ ልክ ወይም ሞት እንደሚያስፈርድብኝ ይዝትብኝ ነበር፡፡ ሀሰን ሽፋ በበኩሉ በሀሳባቸዉ የማልስማማ ከሆነ የያዘኝን የወጣት ጀብደኝነት ማስተንፈስ ለነሱ ከባድ ስራ አለመሆኑን ነግሮኛል፡፡ በኔ በኩል ደግሞ ከተጠረጠርኩበት ወንጀል ንፁህ መሆኔ እንጂ ኤልያስ ላይ በሀሰት መመስከሬ ሊያስፈታኝ እንደማይገባ ስለማምን ይህንኑ በተደጋጋሚ አስታዉቄ ተከሳሽ መሆንን መረጥኩ፡፡ ኢህአዴግ እስካለ ድረስ የተሻለዉን መጥፎ እየመረጡ መኖር ዕጣፋንታችን ከሆነ ቆየ አይደል?
ማዕከላዊ እያለሁ ከተፈፀሙብኝ የመብት ረገጣዎች ዉስጥ አንዱ የሆነዉ በአንድ ፖሊስ የተሰጠኝ ጥፊና ከግድግዳ ጋር ማጋጨት በተለይ ወንድ የፖለቲካ እስረኞች ከሚፈፀምባቸዉ ለዘላቂ የአካል ጉዳት የሚዳርግ ከባድ ድብደባ አንፃር ሳስተያየዉ የማዕከላዊ መርማሪዎች እንደሚሉት “ቁንጥጫ” ተብሎ ከመግለፅ የሚያልፍ ባለመሆኑ ብዙ ልልበት አልፈልግም፡፡ በወቅቱ የነበርነዉ ሴት እስረኞች ላይ ያን ያህል የከፋ አካላዊ ድብደባ አልተፈፀመም ማለት ግን የማዕከላዊ መርማሪዎች ለሴቶች ይሳሳሉ ማለት አይደለም፡፡ ለማሳያነት እስካሁን ድረስ ማዕከላዊ በተፈፀመባት ከባድ ድብደባ የተነሳ በህመም የምትሰቃየዋን የፖለቲካ እስረኛ እማዋይሽ አለሙን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አይ ማዕከላዊ! ማዕከላዊ ዘና ብለዉ የሚራመዱ ኩሩ የኢትዮጵያ ልጆች በገቡ ሳምንት በማይሞላ ጊዜ ዉስጥ በቃሬዛና በሰዎች ድጋፍ በሸክም ሲያሳልፉና የድረሱልኝ ዋይታ ሲያቀርቡ የሰማሁበት አሰቃቂ ቦታ ነዉ፡፡ ምስላቸዉ ከአይኔ ላይ፣ ጩኸታቸዉ ከጆሮዬ ተጣብቆ የሚኖረዉ እነዚህ ወገኖቼን እያሰብኩ መናደድ መቆጨት የዕለት ተዕለት የኑሮዬ አካል ሆኗል፡፡
የማዕከላዊዉን የመብት ረገጣ እዚህጋ ገታ ላድርገዉና በተለይ የፖለቲካ እስረኞችን ሰብአዊ መብት ከመጨፍለቅ አንፃር አምሳያዉ ወደ ሆነዉ የቃሊቲ እስር ቤት ልለፍ፡፡ ጳጉሜ3/2003 ዓ.ም ቃሊቲ እንደገባሁ በኋላ ላይ የጥበቃ ክፍል ሀላፊ እንደሆነች በተገነዘብኩት ሀላፊ አማካኝነት ጋዜጠኝነቴ ከታሰርኩ በኋላ የቀረ በመሆኑ ግቢዉ ዉስጥ በሚኖረኝ ቆይታ አርፌ መቀመጥ እንደሚኖርብኝ ተነገረኝ፡፡ አልጋ እስከሚለቀቅ ተብሎም እኔና በአንድ መዝገብ የተከሰስነዉ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ ምንም እንኳን ሁለታችንም የሳይነስ በሽታ ያለብን ቢሆንም ሽንት ቤት አጠገብ መሬት ላይ ፍራሽ አንጥፈን እንድንተኛ ተደረገ፡፡ ዉድ አንባቢያን ስለቃሊቲ ስታስቡ ወደ አዕምሮአችሁ የሚመጡት ያማሩ ግንብ ቤቶችና የተዋቡ አልጋዎች ከሆኑ ኢቲቪ እንደሸወዳችሁ ልነግራችሁ እወዳለሁ፡፡ የፓስተር ዳንኤል ገ/ስላሴ ፕሪዝን ፌሎሽፕ የተባለ ድርጅት እንዳሰራቸዉ የሚናገሩት እነዚህ ያማሩ ግንብ ቤቶች ሁለት ክፍሎችና መፀዳጃ ቤት ብቻ ያሏቸዉ ሲሆኑ የተቀሩት በሴቶች ዞን ዉስጥ ያሉ ክፍሎች ከሁለት ያረጁ ግንብ ቤቶች በስተቀር በቆርቆሮ የተሰሩና እስረኞች በተጨናነቀ ሁኔታ የሚኖሩባቸዉ ናቸዉ፡፡ የቃሊቲ ምቾት አልባነት የሚሰማዉ አካልን ብቻ አይደለም፡፡ ቃሊቲ ከአካል በከፋ ሁኔታ ለነፍስና ለመንፈስ ይጎረብጣል፡፡ እንዴት ቢሉ እንዲህ እልዎታለሁ፡፡ የቃሊቲ የሴቶች ዞን ቤተመፃሕፍት ከጥቂት ወራት ጀምሮ በመፅሐፍቱ አይነትም ሆነ ቁጥር መሻሻልን ቢያሳይም እኔ ቃሊቲ ከገባሁ ጀምሮ እስከቅርብ ጊዜያት ድረስ ግን ከመኖር በማይቆጠር ደረጃ የሚገኝ ነበር፡፡ ይህንን ክፍተት ቤተሰብና ጓደኞቼ በሚያስገቡልኝ መፀሐፍት ለመሙላት ባስብም ከግማሽ በላይ የሚሆኑት የሚመጡልኝ መፅሐፍት የቃሊቲን ሳንሱር እንደወደቁ ተገልፆ እኔጋ ሳይደርሱ ይመለሳሉ፡፡ ከነዚህ መፅሐፍት ዉስጥ አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የሚሳትማቸዉ የታሪክ መፅሐፍት ሳይቀር ይገኙበታል፡፡ ቃሊቲ ለመንፈስም አይመችም ያልኳችሁ በዚህ ብቻ አይደለም፡፡ በራሴ ወጪ ኢንድራ ጋኒዲ ናሽናል ኦፕን ዩኒቨርስቲ በርቀት ፖለቲካል ሳይንስ ለማጥናት ከብዙ ዉጣዉረድ በኋላ ተፈቅዶልኝ የተበዘገብኩ ቢሆንም የመማሪያ ሞጁሎቹን ለማስገባት ግን የቃሊቲ አለቆች ፍቃደኛ አልነበሩም፡፡ ከብዙ ደጅጥናት በኋላ ሞጁሎቹ ሲገቡ ደግሞ በትምህርቱ ዙሪያ ላነባቸዉ የሚገቡኝ አጋዥ መፅሐፍት ስለፖለቲካ የሚያወሩ በመሆናቸዉ በፍጹም ሊገቡ እንደማይችሉ የመፅሐፍት ገምጋሚዎቹ አረዱኝ፡፡ ይባስ ብሎ በዚያን ወቅት ከሌላዉ ጊዜ በተለየ ሁኔታ ምንም አይነት መፅሐፍት እንዳይገቡልኝ በመደረጉ ለጠቅላላ ዕዉቀት ያህል ሞጁሎቹን ማንበቤን ብቀጥልም ትምህርቱ ግን በዚህና በሌሎች ምክንያት ለማቋረጥ ተገደድኩ፡፡
በቃሊቲ የኔ ብቻ ሳይሆን ከእኔ ጋር የተቀራረቡ ወይም ደግሞ ሰላምታ ያቀረቡልኝ ሰዎች ሳይቀር መብታቸዉ ተጥሷል፡፡ ከሁለት አመታት በላይ የሚሆነዉን ጊዜ በርካታ እስረኞች በነበሩበት ክፍል ያሳለፍኩ ቢሆንም እኔን እንደሌላዉ እስረኛ ለመቅረብ የሞከሩ በሙሉ ስሜትን የሚጎዳ ወከባ፣ዘለፋና ለየት ያሉ ፍተሻዎችን አስተናግደዋል፡፡
በህክምና ጉዳይ የነበሩብኝን ችግሮች በተመለከተ ቤተሰቦቼ ደጋግመዉ የገለፁት መሠረታዊ ችግር በመሆኑ በዚህ ፅሑፍ ነካ አድርጌዉ ብቻ አልፋለሁ፡፡ ጡቴ ዉስጥ በበቀለዉ እጢ ምክንያት ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የህክምና ክትትል በማደርግበት ወቅት በቀጠሮዬ ቀን ወደ ሆስፒታሉ ከምወሰድባቸዉ ይልቅ የማልወሰድባቸዉ ጊዜያት ይበዙ ነበር፡፡ የግራ ጡቴ ቀዶጥገና ከተደረገለት በኋላ በወቅቱ ክትትል ታደርግልኝ የነበረችዉ ዶክተር በሶስተኛ ቀን የቁስሉ ፕላስትር መቀየር እንዳለበትና በሳምንቱ ደግሞ ክሩ መዉጣት እንዳለበት ገለፀችልኝ፡፡ አብረዉኝ የሚሄዱት አጃቢ ፖሊሶች ከዶክተሬም ጋር ስነጋገር እዛዉ ነዉና የሚቆሙት እንዲህ አይነቱን ነገር ለማድረግ የሚችል ጤናጣቢያ ማረሚያቤቱ እንዳለዉ ተናገሩ፡፡ እኔም ቀጠሮ ቢሰጠኝ እንኳ በዚህ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ወደሆስፒታሉ ተመልሼ መሄድ አዳጋች መሆኑን ስለማዉቅ የተባሉት ነገሮች ቃሊቲ መፈፀማቸዉን አልጠላሁትም፡፡ በመሆኑም ለህክምና ክትትል የሶስት ወራት ቀጠሮ ተሰጠኝ፡፡ ክሩ መዉጣት ባለበት ቀን ስለጉዳዩ ለጥበቃ ክፍሉ አስታወቅኩ፡፡ እነሱም አሁን ደቡብ ሱዳን ከሚገኝዉ ጦር ጋር አብራ ከተጓዘች አንዲት የህወሐት ታጋይ የነበረች ነርስ ጋር አገናኙኝ፡፡ እሷም እዛዉ ጨርሼ መምጣት እንደነበረብኝና እዚህ ክሩን ማዉጣት እንደማይችሉ ነገረችኝ፡፡ የምታሳየኝ ጥላቻ በሷ እጅ የህክምና አገልግሎት ከማግኘት ቢቀር የሚሻል መሆኑን የሚጠቁም በመሆኑ ብዙም ልከራከራት አልፈለኩም፡፡ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ ሌሎች ሀላፊዎች ወደጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንዲወስዱኝ ብጠይቅም “ቀጠሮ የለሽም” በሚል ሰበብ ሳይወስዱብኝ ቀሩ፡፡ በአሁኑ ወቅት የቀኝ ጡቴም ተመሳሳይ እጢ ያለበት በመሆኑ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ቀዶጥገና አደርግ ዘንድ የላከኝ ቢሆንም (ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በእድሳት ላይ በመሆኑ)እጅግ የከፋ ህመም ካልታመምኩ በቀር ቃሊቲ ሆኜ ቀዶጥገና ማድረጉን አልፈለኩም፡፡ በመሆኑም አልፎ አልፎ የሚሰማኝን ህመም በህመም ማስታገሻ መድሀኒቶች በማቃለል የቃሊቲን አስቀያሚ ቀኖች በመግፋት ላይ እገኛለሁ፡፡
ሌላዉ የቃሊቲ ቆይታዬን በተመለከተ ልጠቅሰዉ የምፈልገዉ ጉዳይ ከመንግስት አካላትና ከተለጣፊዎቻቸዉ ጋር ካለፍላጎቴ እንድንገናኝ እየተደረገ የሚፈፀምብኝ የሰብአዊ መብት ረገጣ ነዉ፡፡ ለምሳሌ ያህልአንዱን ብቻ ልጥቀስ፡፡ አምና መጋቢት ወር ዉስጥ አምባሳደር ጥሩነህ ዜናን ጨምሮ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መምጣታቸዉን የገለፁ ሌሎች አስር ሰዎች ከአመት በፊት ወደገባሁበትና ከሌሎች ከአራት ሰዎች ጋር ብቻ ወደምኖርበት ክፍል መጡ፡፡ እኔም ኮሚሽኑ በተለይም ደግሞ አምባሳደሩ የሰብአዊ መብት አከባበርን አስመልክቶ የሚሰጧቸዉ ከእዉነት የራቁ መግለጫዎች የሚያሳዝኑኝ በመሆኑ ለመነጋገር ፍቃደኛ አለመሆኔን በማስታወቅ ከክፍሉ ወጥቼ በሩ ላይ ቆምኩ፡፡ ከሰዎች አንዱ የምኖርበትን ክፍልና አልጋዎቻችንን ፎቶ ሲያነሳ ተመለከትኩ፡፡ ገረመኝ፤ መሬት አንጥፌ ስተኛ፣በተደራራቢ አልጋ የላኛዉ ክፍል ላይ ከጡት ህመም ጋር እየታገልኩ ስተኛና በተፋፈገ ክፍል ዉስጥ ስኖር ለምን የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ፎቶ አላነሳም? ማረሚያ ቤቱ በጥሩ ሁኔታ እስረኞቹን የያዘ መሆኑን ማሳያ ለማድረግ እንደተፈለገ ገመትኩ፡፡ እዉነታዉ ግን ይቺ ያለሁባት በቆርቆሮ የተሰራች ክፍልና ጠባቧ ግቢ አምና መስከረም ላይ በጠያቂዎች የመጎብኘት መብቴ መጣሱን ተከትሎ በጥድፊያ የተዘጋጀች ማግለያ ቦታ መሆኗ ነዉ፡፡ ክፍሉን ብቻ ፎቶ አንስተዉ መሄዳቸዉ ያላረካቸዉ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰዎች በማግስቱ አራት ሆነዉ መጡ፡፡ ሁለቱ ወደግቢዉ ዉስጥ ሲገቡ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ በሩጋ ቆሙ፡፡ ግቢዉ ዉስጥ ከገቡት አንዱ ትላንት ለምን ላናግራቸዉ እንዳልፈለኩ ጠይቆኝ በድጋሚ ከነሱ ጋር መነጋገር ያልፈለኩበትን ምክንያት እያስረዳኋቸዉ እያለ የግቢዉ በር ክፍት ስለነበር ግቢዉ በርጋ ከቆሙት አንዱ ፎቶ ሊያነሳኝ ሲሞክር ለመመልከት ቻልኩ፡፡ ምስሌን አንስቶ ቢሆንና ስለኔ አንዳች አይነት ዉሽት ሲናገሩ ብሰማ ጉዳዩን በዝምታ እነደማላልፈዉ ነገርኩትና ወደቤት ዉስጥ ገብቼ በሩን ዘጋሁት፡፡ ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ከክፍሉ ወጥቼ ኢህአዴግ ማሰሩ ሳይበቃዉ ሰብአዊ መብትን ለማስከበር እንዳቋቋማቸዉ በሚናገረዉ ተለጣፊ ድርጅቶቹ ሳይቀር ሰብአዊ መብቴን ለምን እንደሚጥስ ከሀላፊዎቹ አንዷን በማስጠራት ጥያቄ አቀረብኩላት እሷም ሰዎቹ ካሜራ መያዛቸዉን እንደማታዉቅ ነገረችኝ፡፡ በ2005ዓ.ም ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች የህዝብ ግኑኝነት ክፍል እኔን ለማናገር እንደመጣ የገለፀልኝ ሰዉ ኮቱ ዉስጥ ደብቆ በያዘዉ ሪከርደር ድምፄን ለመቅረፅ ሲሞክር ደርሼበት ይህንን ማድረግ የሚችለዉ የግል ፕሬስም ተገኝቶ ንግግራችንን የሚቀርፅ ከሆነ ብቻ መሆኑን ነግሬዉ ነበር፡፡ ይሄንን ያልኩበት ምክንያት የግል ፕሬሱ ባልተገኘበት ለመንግስት ሚዲያዎች ብቻ አስተያየታቸዉን የሰጡ ግለሰቦች ሀሳባቸዉ ተቆርጦና ተቀጥሎ ለማለት ያልፈለጉት ይዘት ይዞ እንደሚቀርብ አዉቅ ስለነበር ነዉ፡፡ የተናገርኩትን ሙሉዉን ነገር ቀርፀዉ ሊያወጡልኝ የሚችሉ አካላት በሌሉበት ለሰዉዬዉ አስተያየቴን መስጠት ያለፈለኩትም ይኸዉ እንዳይደርስብኝ በመስጋት ነበር፡፡ አስገራሚዉ ነገር ይቺ የኮሚሽኑ ሰዎች ካሜራ መያዛቸዉን እንደማይታወቅ የገለፀችልኝ ሀላፊ ያኔም የሰዉየዉን የድምፅ ሪከርደር መያዝ በተመለከተ ላቀረብኩላት ጥያቄ የሰጠችኝ ተመሳሳይ መልስ ነበር፡፡
የቃሊቲ ጉድ ማብቂያ ስለሌለዉ አንድ የመጨረሻ ጉዳይ ላንሳና የፅሁፌ መነሻ ወደሆነዉ የአመክሮ ጉዳይ አልፋለሁ፡፡ ዉድ አንባቢያን በሀገሪቱ ዉስጥ ያሉ የትኞቹንም እስረኞች አያያዝ የተመለከቱ ህጎችን፣ አዋጆችን፣ ደንቦችንም ሆኑ መመሪያዎችን በጣሰ ሁኔታ ከወላጆቼ በቀር ጠበቃን ጨምሮ በሌላ በማንም ሰዉ የመጎብኘት መብቴን ከተነጠቅኩ አመት ከኣራት ወራት አልፎኛል፡፡ አዛዉንት እናትና አባቴም ከእርጅና፣ ህመምና ድካም ጋር እየታገሉ የቃሊቲን ፈታኝ መንገድ መዉጣትና መዉረዳቸዉን ቀጥለዋል፡፡
ነገረ አመክሮ
ያለፈዉ አመት ነሐሴ ስምንት ቀን ከሰአት በኋላ ወደ ጠበቃ ክፍል ሃላፊዋ ቢሮ በአንዲት ፖሊስ ተጠርቼ ተወሰድኩ፡፡ እዚያም ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ዋናዉ መስሪያ ቤት የይቅርታና የአመክሮ ጉዳይ ክፍል እንደመጣና ኮማንደር አስቻላዉ እንደሚባል ከነገረኝ ሰዉ ጋር ተገናኘሁ፡፡ ኮማንደሩ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ያቀረበልኝ የመጀመሪያዉ ጥቃቄ “ይቅርታ ለምን አልጠየቅሽም? ይቅርታ በመጠየቅ ላይ ያለሽ ሀሳብስ አልተቀየረም ወይ?” የሚል ነበር፡፡ ይቅርታ ያልጠየኩት ስላላጠፋሁና የተፀፀትኩበት ጉዳይ ስለሌለ በመሆኑና አሁንም ምንም የተቀየረ አቋም እንደሌለኝ አስረዳሁተ፡፡ “ይሄ የፍርድቤት ጉዳይ ነዉ፡፡ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ እስካለሽ ድረስ ወደዚያ መመለስ አይኖርብንም” አለኝ፡፡ እኔም አምባገነኑ የኢህአዴግ መንግስት እንዳሻዉ የሚያሽከረክረዉ ፍርድቤት በንፁሃን ላይ የጥፋተኝነት ዉሳኔና ፍርድ ማስተላለፉን አሜን ብዬ ይቅርታ የምጠይቅበት ምንም አይነት ምክንያት እንደሌለ ገለፅኩለት፡፡ ጥቂት ደቂቃዎች ያህል ስለጤንነቴና በጊቢዉ ዉስጥ ስለሚያጋጥሙኝ ችግሮች በተመለከተ ጥያዎችን ስያቀርብልኝ ቆየና ወደ መጣበት ሌላዉ ዋና ጉዳይ ተመለሰ፡፡
“ቅድም ይቅርታ የማልጠይቀዉ ስላልተፀፀትኩ ነዉ ብለሻል፡፡ አመክሮ እኮ የሚሰጠዉ ለተፀፀተ ሰዉ ነዉና እንዴት ልታደርጊ ነዉ?” በማለት ስለ በአመክሮ የመፈታት አካሄድ አንዳንድ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ደንቦችን ጭምር በመጥቀስ ሊያብራራልኝ ሞከረ፡፡ “ታዲያ እንዲህ ከሆነ በይቅርታና በአመክሮ መሀል ምንም አይነት መሰረታዊ ልዩነት የለም ማለት ነዋ?” ለሚለዉ ጥያቄ ቀጥታ መልስ ሊሰጠኝ አልፈለገም ይልቁኑ ሁሉም ታራሚ 2/3ኛዉን የእስር ቅጣቱን ለመፈፀም ሁለት ወራት ገደማ ሲቀሩት እንደታረመና እንደተፀፀተ የሚገልፅ ፎርም መሙላት ስለሚኖርበት እኔም ለመፈታት ከፈለኩ ይህንኑ ማድረግ እንደሚጠበቅብኝ አስረግጦ ነገረኝ፡፡ የፃፍኩት የማምንበትንና መቼም ልቆምለት የምችለዉ እዉነት መሆኑን፣ በዚህ የተነሳ አሸባሪ መባሌ ደግሞ የበለጠ ኢህአዴግን እንድታገለዉ የሚየደርገኝ እንጂ የሚያፀፅተኝ ባለመሆኑ እንዲህ አይነቱን ከማንነቴ ጋር የሚቃረን ፎርም እንደማልሞላ አስረግጬ ነገርኩት፡፡ ኮማንደሩም ላልታረመና ለልተፀፀተ ሰዉ አመክሮ መስጠት ለእነሱም እንደሚከብዳቸዉ ከገለጸልኝ በኋላ “እኛ ፎርሙን ብንሞላልሽስ?” የሚል አስገራሚ ጥያቄ አቀረበልኝ፡፡ እኔ “ታርሜያለሁ” እንዳልኩ ተደርጎ ምንም አይነት ነገር ቢደረግ ሀሰት መሆኑን ከማጋለጥ ወደኋላ እንደማልል አስታወቅኩት፡፡ በዚህ አይነት ተመሳሳይ ሀሳቦች ላይ እየተሸከረከርን ጥቂት ጊዜ ከፈጀን በኋላ እንዳሰብበት አሳስቦኝ ተለያየን፡፡
ይህ ከሆነ ሀሁለት ወራት በኋላ የመፈቻዬ ቀን የነበረዉ ጥቅምት 14/2007 ማለፊን ተከትሎ “የአመክሮ ፎርሙን ለምን አትሞይም?” የሚል ጥያቄ ከተለያዩ ሀላፊዎች ይቀርብልኝ ጀመረ፡፡ ከህዳ&#465

ሻእቢያ ያገታቸውን ታጋዮቻችንን ለፕሮፓጋንዳ ሊጠቀምባቸው እያስገደዳቸው ነው ሲሉ የአማራ ንቅናቄ (አዲሃን)ምንጮች ገለጹ:: ‪

Minilik Salsawi : የኤርትራ መንግስት በህገወጥ መንገድ ያገታቸውን እና የሰወራቸውን ታጋዮቻችንን በአስቸኳይ እንዲለቅ እንጠይቃለን በማለት በተደጋጋሚ መግለጫ ያወጣው የአማራ ንቅናቄ አይን ያወጣው ሻእቢያ ያገታቸውን አባሎቼን ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታው በማስገደድ ሊጠቀምባቸው ነው ማለቱን የንቅናቄው የውስጥ ምንጮች ከሰሜን ጎንደር ገልጸዋል::

ሕዝቦች ትክክለኛ መረጃ የማግኘት መብታቸው እየተገደበ ነው የሚሉት የንቅናቄው ምንጮች ከ70 በላይ የሚሆኑ የድርጅታችን አመራሮች እና ታጋዮቻችን በኤርትራ ወህኒ ቤቶች እየተሰቃኡ ከመሆኑም በላይ እንዲሁም በሺዎች የሚቆተሩ ኢትዮጵያውያን በእስር የማቀቁ ባሉበት ሁኔታ ሻእቢያ የነጻነት አባት በመምሰል በኢትዮጵያውያን ስም የሚሰጠውን ፕሮፓጋንዳ ምንም ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ ንቅናቄውን ዋቢ በማድረግ ጠቁመዋል::

– የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ በተደጋጋሚ የሰጣቸውን መግለጫዎች ዚህ ሊንክ ላይ ያግኙታል::

Please wait, video is loading…

– በድምጽ እዚህ ላይ ይጫኑት :

phpBB [video]

አስመራ የታገቱት የአማራ ንቅናቄ አባላት በሻእቢያ ከባድ እንግልት እየደረሰባቸው ነው::የሚለው ንቅናቄው በዚህ ዙሪያ መግለጫ ያወጣል ተብሎ የተጠበቀ ነው::

Image

እዉነቱ እዚህ ምርጫ ቦርዱ የሚለፍፈው እዚያ ፣ እዉነቱን ይረዱ
=====================================
የምርጫ ቦርድ ምክትል ሃላፊ አቶ አዲሱ ገብረግዚአብሄር በፋና ራዲዮ እንዲሁም ሃላፊው ፕሮፌሰር መርጋ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ መኢአድ እና አንድነት ችግር እንዳለባቸው በመገልጽ በስድስት ቀናት ዉስጥ ፓርቲዎቹ “ችግሮቻቸውን” ካልፈቱ ሕጋዊ እርምጃ ይወሰደባቸዋል ሲል አስጠንቅቀዋል። ምርጫ ቦርድ የገዢው ፓርቲ አገልጋይ እንደሆነ ይነገርለታል።

የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች በሕጉ መሰረት የሚንቀሳቀሱ ሳይሆን የፖለቲካ ዉሳኔ የሚያስፈጸሙ እንደሆኑ በሚያደርጓቸው ኢሕገ መንግስታዊ እንቅስቃሴዎች እያሳዩ እንደሆነ የሚገልጹት የመኢአድ እና የአንድነት አመራር አባላት የተደቀነባቸውን እንቅፋት ከህዝብ ጋር ሆነው እንደሻገሩትን በሙሉ መተማመን እየገለጹ ናቸው።

የመኢአድ እና የአንድነት አመራሮች በአባላት ደረጃ እንደተዋሃዱ፣ አብረዉ እየተሳሩ፣ እየደሙ እንዳለ የገለጹት አመራር አባላቱ መኢአድ እና አንድነት አብረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። መኢአድ በ354 ወረዳዎች አንድነት ደግሞ ከ450 ወረዳዎች በላይ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ የገለጹት አመራሮቹ፣ አገዛዙ በምርጫ ቦርድ በኩል በድርጅቶቹ ላይ እየፈጸመ ያለው ነገር ፣ ድርጅቶቹ በሕዝብ ተቀባይነት እንዳላቸው በመረዳቱ ነው ሲሉ፣ ከህዝብ ጋር ሆነው የሚመጣውን ነገር ሁሉ ለመቋቋም ዝግጁ እንደሆኑ አረጋግጠዋል።

የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ ማሙሸት አማረ ከኢሳት ጋር ያደረጉትን ያዳምጡ
https://www.youtube.com/watch?v=M0OfiIh … e=youtu.be

ምርጫ ቦርድ እያደረገ ባለው ኢ-ሕገመንግስታዊ ተግባራት ዙሪያ የአንድነት አመራር አባል የሆኑት አቶ አለነ ማጸንቱ ለኢሳት ማብራሪይ ሰጥተዋል።

አቶ አለነ፣ በጎጃም ክፍለ ሀገር አገው ምድር አውራጃ ሲሆን የተወለደው፣ የ28 አመት ወጣት ነው። በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1999 በሶሻል ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ፣ በ2004 ደግሞ ሁለተኛውን ድግሬ ተቀብሏል።

በተለያዩ የግል ኮሌጆች ዲን እና አስተማሪ በመሆን እንዲሁም በግል ትምህርት ቤቶች ርዕሠ- መምህር በመሆን አገልግሏል። አሁን ደግሞ በሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒሥቴር የጥናትና ምርምር ቡድን አስተባባሪ በመሆን የተለያዩ መመሪያዎች፣ ፕሮግራሞች እና መርሀ ግብሮችን በማዘጋጀት ለተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች የአሠልጣኞች ሥልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።

በ1997 የመኢአድ(ቅንጅት) በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የወጣቶች አደራጅ፤ ከ2001 እስከ 2002 በአዊ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ እና የህዝብ ተወካዩች ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ፣ ከ2003 እስከ 2005 በአንድነት ፓርቲ በጥናትና ምርምር ቋሚ ኮሚቴ የማህበራዊ ጉዳይ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ ከ2006 ወዲህ ደግሞ በአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ስራ አስፈጻሚ አባል እና የማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛል።

አቶ አለነ ከኢሳት ጋር ያደረገዉን ቃለ ምልልስ ያዳምጡ።
https://www.youtube.com/watch?v=x5DzqIK … e=youtu.be

ባለፈው ሳምንት የወያኔ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያዎች በመታጀብ ጎንደር
አርማጭሆ ውስጥ ሶረቃ በሚባለው አካባቢው አርሶ አደሮችን በኃይልና በማን አለብኝነት
አስነስተው ቦታውን ወደ ትግራይ ክልል ለማጠቃለል ያደረጉት ጥረት ሕዝቡ ከዳር እስከዳር
በመንቀሳቀስና ውጊያ በመግጠም ያከሸፈው መሆኑ ታውቋል። በተደረገው ግጭትም ከሁለቱም
በኩል ጉዳት የደረሰ መሆኑ ከሥፍራው የሚገኙ ዜናዎች ያስረዳሉ። ሁኔታው እስካሁን ያልበረደ
ሲሆን ሕዝቡም ከዳር እስከ ዳር ተጠራርቶ መብቱን ለማስከበርና ንብረቱን ለማስጠበቅ
ባንድነት ለመታገል ወስኗል።

የወያኔ አገዛዝ ሥልጣን ላይ ለመቆየት አገሪቱን በጎሳና በቋንቋ እንዲሁም በሃይማኖት በመከፋፈል
በሕዝብና በሀገር ላይ ከፍተኛ በደል ከመፈጸሙ በተጨማሪ ለዓመታት በጎንደርና በወሎ
ክፍለሀገራት የነበሩትን ሰፊ አካባቢዎች ያለ ሕዝቡ ፈቃድና ስምምነት ቀምቶ በትእቢትና
በማናለብኝነት በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲጠቃለሉ ያደረገ መሆኑ ይታወሳል። የወያኔ እኩይ
ተግባር ሕዝቡን ከፍተኛ ብሶት ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል። ይህ አልበቃ ብሏቸው የወያኔ ሆዳም
ባለሥልጣኖች ደኻውን ገበሬ ከእርሻ ቦታው ላይ አፈናቅለው መሬቱን ለመቀራመት የወሰዱት
እርምጃ በጽኑ የሚወገዝ ነው።

ጸረ ኢትዮጵያ የሆነው የወያኔ ቡድን በሥልጣን ኮርቻ ላይ ከተቆናጠጠ ጀምሮ የኢትዮጵያን
አንጡራ ሀብት ዘርፎና ለቡድኑ መጠቀሚያ አድርጎ በወሰን አካባቢ ያሉ ለም መሬቶችን
ተቃዋሚዎችን ለሚቆጣጠርለትና መስል አጽፋዊ ስጦታ ለሚያደርግለት ለሱዳን አስረክቦ፤ ሰፋፊ
ለም የእርሻ ቦታዎችን ለውጭ አገር ከበርቴዎች በሊዝ ሸጦ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ትውልድ ይቅር
የማይለው ከፍተኛ በደል ፈጽሟል።

ይህን ግፍና በደል ለማስቀረትና የሕዝቡን መብትና ጥቅም ለማስከበር ከቡድኑ ጥቅም በላይ
ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ደንታ የሌለውን ዘረኛና አምባገነን ቡድን በሕዝባዊ ኃይል
ከማውረድ በስተቀር ሌላ አማራጭ የሌለ በመሆኑ ዛሬም ትግላችንን በሕብረት አጠናክረን ወደፊት
እንግፋ የሚለው ጥሪ ወቅታዊ ሆኖ የሚገኝ ነው።

ሕዝባዊ ትግሉን በኀብረት እናጠናክር !!
ፀረ ኢትዮጵያ የሆነው የወያኔ አገዛዝ ይወገዳል !!

MinilikSalsawi : በኤርትራ የሚንቀሳቀሱት የአርበኞች ግንባር እና የግንቦት ሰባት ውህደት የመጀመሪያው ዙር ጉባዬ በዛሬው እለት መጀመሩን የአስመራ ምንጮች ተናግረዋል:: ጉባዬውን በተመለከተ አስፈላጊውን መረጃዎች ዝርዝር እንደደረሰኝ አቀርባለሁ::

ኢሳት ሁለት ጋዜጠኞች ያለውን ሁኔታ እንዲዘግቡ ወደ ኤርትራ የላከ ሲሆን በዚህም መሰረት መሳይ መኮንን እና ፋሲል የኔአለም ወደ ኤርትራ ተጉዘዋል::በኤርትራ ቆይታቸው የውህደቱን ጉባኤ እና የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ የሚቃኙ ሲሆን የሻእቢያን ባለስልጣናት ያናግራሉ ተብሎ ይጠበቃል::

ለማስታወስ ያህል::

Please wait, video is loading…

ላለፉት 28 ዓመታት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ያገለገሉት ዶ/ር መረራ ጉዲና ከኮንትራት ቅጥር አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ከዩኒቨርሲቲው ጋር አለመስማማታቸው ታወቀ። ዶ/ር መረራ ስለጉዳዩ ከሰንደቅ ጋዜጣ ተጠይቀው ካለፈው ሐምሌ ወር 2006 ዓ.ም ጀምሮ ጡረታ እንዲወጡ እንደተጠየቁና ጥያቄውን እንዳልተቀበሉት ተናግረዋል። ለዚህም የሰጡት ምክንያት አንድ ለጡረታ የደረሰ ሰው ሦስት ዓመት እንዲራዘምለት መጠየቅ የሚችልበት የሕግ አግባብ ስላለ ነው ብለዋል። ከሐምሌ 2006 ዓ.ም ጀምሮ የዩኒቨርሲቲው የሶሻል ሳይንስ ኮሌጅ በኮንትራት እንዲሰሩ የቀጠራቸው መሆኑን አስታውሰው ሆኖም የዩኒቨርሲቲ ፐርሶኔል ክፍል ቅጥሩን አልቀበልም በማለቱ እስካሁን ጉዳዩ በእንጥልጥል ላይ መሆኑን ገልፀዋል። በዩኒቨርሲቲው የሴኔት ሕግ መሠረት ኮሌጆቹ የሚፈልጉትን መምህር የመቅጠር መብት እንዳላቸው በማስታወስ የፐርሶኔል ክፍሉ በማያገባው ገብቶ ቅጥሩን ከልክሏል ብለዋል። ከዚሁ አለመግባባት ጋርም ተያይዞ ላለፉት ስድስት ወራት ደመወዛቸው መቋረጡን ጠቅሰው፤ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያላቸውን ሁኔታ ተከታትለው መፍትሄ ከጠፋ መብታቸውን በሕግ ለማስከበር ማሰባቸውን ጨምረው ገልፀዋል። በጉዳዩ ላይ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። ዶ/ር መረራ ጉዲና ከዩኒቨርሲቲው መባረራቸውን ሰሞኑን በአንዳንድ ማኅበራዊ ድረገጾች መዘገቡም አይዘነጋም። ******* ምንጭ፡- ሰንደቅ፣ ታህሳስ 22-2007 More from Horn Affairs Amharicዶ/ር መረራ ጉዲና – ለ6 ወር ደሞዝ አልተከፈለኝም፣ ፕሮፌሰርነት እስካሁን ድረስ አልተሠጠኝምሰንደቅ ጋዜጣ:- ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ በሠነዘሩት አሉባልታ ሊከሰሱ ነውዶ/ር መረራ ጉዲና፡- ኢሳት ጠመንጃ የለውም፣ የትጥቅ ትግልም እያካሄደ አይደለምኢትዮ-ቴሌኮም በ75 የአዲስ አበባ አካባቢዎች የኔትወርክ ችግር ፈታሁ አለዓለማየሁ አቶምሳ – ኪራይ ሰብሳቢነትን አምርሮ የታገለና ያታገለየኢዴፓ መግለጫ – “በሽብርተኝነት ስም […]

(አለማየሁ አንበሴ) ባለፈው ሳምንት በማህበራዊ ድረ-ገጽ በተሰራጨ መረጃ፣የፖለቲካል ሣይንስ መምህርና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና፤ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጡረታ እንደተባረሩ ቢነገርም መረጃው እውነት አለመሆኑን ከአንደበታቸው ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ሆኖም ከዩኒቨርሲቲው ጋር የተፈጠረ ችግር እንዳለ ይናገራሉ – ዶ/ር መረራ፡፡ ችግሩ ምን ይሆን? ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤ይሄንንና ሌሎች ከመምህርነት ሙያቸው ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ጠይቋቸው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አዲስ አድማስ:- ከዩኒቨርሲቲው ጋር የተፈጠረው ችግር መነሻው ምንድን ነው? ዶ/ር መረራ ጉዲና:- ሁሉንም ሲያልቅ መናገር ይሻላል፡፡ ነገር ግን ለ6 ወር ያስተማርኩበት ደሞዝ አልተከፈለኝም፤ መነሻው ይሄ ነው፡፡ ፓርላማ በቆየሁባቸው ጊዜያትም ደሞዝ አይከፈለኝም ነበር፤ የዩኒቨርስቲው ይበቃሃል ተብዬ፡፡ እዚህም እንግዲህ ለ6 ወር በነፃ እያገለገልኩ ነበር ማለት ነው፡፡ አዲስ አድማስ:- ምክንያቱ ተነግርዎታል ? እርስዎስ አልጠየቁም ? ዶ/ር መረራ ጉዲና:- የቅርብ አለቆች እየተነጋገሩበት ነው የሚል ምላሽ ነው የተሰጠኝ፡፡ ግን ማስተማሬን አላቆምኩም፤ በነፃ እያገለገልኩ ነው ማለት ነው፡፡ ምናልባት መፍትሄ ካልተገኘ መብቴን ለማስከበር ወደ ፍ/ቤት ላመራ እችላለሁ፡፡ አዲስ አድማስ:- በዩኒቨርሲቲው ምን ያህል ጊዜ አስተማሩ? ዶ/ር መረራ ጉዲና:- እሱ የአደባባይ ሚስጥር ነው፤ ለ28 አመት ፖለቲካል ሣይንስ አስተምሬያለሁ፡፡ አዲስ አድማስ:- በዩኒቨርስቲው በሃላፊነት የመስራት እድል አጋጥሞት ያውቃል? ዶ/ር መረራ ጉዲና:- አዎ! በሦስት የተለያዩ ጊዜያት የፖለቲካል ሣይንስ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ነበርኩ፡፡ ለምን ያህል ጊዜ እንደሆነ በትክክል ባላስታውስም ለመጨረሻ ጊዜ በኃላፊነት የሠራሁት ከሦስት ዓመት በፊት ነው፡፡ ኢህአዴግ ከገባ በኋላ ሦስት ጊዜ ሃላፊ ሆኜ ሰርቻለሁ፡፡ አዲስ አድማስ:- የተቃዋሚ ፓርቲ […]

ምርጫ ቦርድ ማንም ይዘዘው ማንም ወይም በግል ተነሳሽነት እያደረገ ያለው ነገር የኢትዮጵያን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከምን ጊዜውም በለይ ወደኋላ ለመመለስ እንደሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊረዳው ይገባል፡፡ ምርጫ ቦርድ ምርጫ እንዲያሰተዳድር በተሰጠው ኃላፊነት የፓርቲዎች አስተዳደሪ ለመሆን እየቃጣው ያለ ተቋም ነው፡፡ ስናከብረው ለመከበር ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ለዚህ ተቋም መጠናክር የበኩላችንን መወጣት አለብን ብለን የተነሳን ፓርቲዎችን ጭምር እየገፉ አለቆቹን ለማስደሰት ደም ተግቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህን የሚያደርጉትን ሰዎች ደግሞ በህዝብ ፊት ለብይን እንዲቀርቡ በግልፅ ማጋለጥ ይኖርብናል፡፡

ትላንትና ዶ/ር አዲሱ በሚዲያ ቀርቦ የተናገረው በምንም መልኩ አንድነትን አይመጥንም፡፡ የተቀሩት የቦርድ አባላትም ይመጥነናል ካሉ ትዝብት ላይ ይወድቃሉ፡፡ የምርጫ ቦርድ አባላት ሳያገባቸው እንፈትፍት ሲሉ መፈተፍቱን ለእኛ ተዉልን ነው ያልናቸው፡፡ ዶ/ር አዲሱ በሚዲያ የቦረድ ውሳኔ ሊሆን ይችላል ብሎ ካቀረበ በኋላ ዛሬ ታህሳስ 28 2007 ቦርድ ተሰብስቦ ውሳኔ ሰጥቶዋል፡፡ ይህን ውሳኔ እንገራችሁ ብለው በስልክ ከጠሩን በኋላ የአንድነት ፓርቲ የወረዳ አባላት የሆኑትንም በተመሳሳይ መልክ ጠርተው ነበር፡፡ ለነገሩ ይህ አካሄድ አንድነትን ስለማይመጥን በፅሁፍ እንዲገልፁልን ነግረናቸው ተመልሰናል፡፡ ለማንኛውም ዶ/ር አዲሱ የሰጠው መግለጫ ይህ መግለጫ እንዲሰጥ የወሰኑትን ጨምሮ ለተቀሩት የቦርድ አባላት ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ነው፡፡ ቦርዱ ተሰብሰቦ ምንም ዓይነት ውሳኔ ከመወሰኑ በፊት ውሳኔውን ሚዛን የሚያሳጣ መግለጫ ለመስጠት ምን እንዳጣደፋቸው መገመት ቀላል ነው፡፡ በልባቸው የሚደግፉትን ፓርቲ ለማንገስ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው፡፡

ልክ የዛሬ አምስት ዓመት አንድነት ላይ ተመሳሳይ ግብ ግብ ተፈጥሮ ነበር፡፡ የዚህ ተልዕኮ ፈፃሚዎች ዛሬ ላይ ሆነው ምን እንደተጠቀሙ ሲያሰላስሉ ምን እንደሚሰማቸው ባላውቅም ዛሬ በዚህ ተግባር ላይ የተሰለፉት አባላት ደግሞ ምን እንደሚያደርጉ መጠበቅ ነው፡፡ ለመማር ያልተፈጠረን ሁሉ ምንም ማድረግ ይቻላል? ማንም ተላላኪና ላኪ ሆኖ ቢያገለግልም ዛሬ የተሰማኝ ነገር አንድነት በምርጫ ለመሳተፍ ሲወስን እንደዚህ ዓይነት ተቋማት በምን ያህል ደረጃ ለመዋረድ ዝግጁ እንደሆኑ ለመረዳት የሚያስችል ነው፡፡ አሁንም ትግሉ መራራ፣ የሚያስከፍለው መስዋህትነትም ውድ ሊሆን እንኳን ቢችል የአንድነት አባላት በድል እንደሚወጡት ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ እሩቅ እንደሆነ አውቀን ለጀመርነው ትግል አቋራጭ እንደማንፈልግ መግለፅ ይኖርብናል፡፡

ውድ የአንድነት አባላት ለቀጣይ አንድነት ከምርጫ ቦርድ አሻጥር ለማላቀቅ ለምናደርገው ትግል ቀበቶ ጠበቅ ነው፡፡ ከሰማይ በታች አንድነት ለመፍታት የማይችለው ፈታኝ ነገር ምርጫ ቦርድም ሆነ በውሰጥችን ያሉት ዙንቢዎች ሊያቀርቡ አይችሉም፡፡ ጎበዝ ጠንከር ነው፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡ ትርጉም ያለው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ጥቂት ፓርቲዎች አንድነት አንዱ ነው፡፡ እናም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ና እውነተኛ ፍትህ ለማምጣት የአንድነት መኖር ከፍተኛ ትርጉም አለው፡፡ ፓርቲው የአንድነት ፓርቲ አባላትና የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሣይሆን የራሳችን አቋምና መስመር ይዘን በሌላ ፓርቲ ያለን ሰዎች እንኳ አንድነት እንዲኖር አጥብቀን እንፈልጋለን፡፡ ወደፊት አንድነትም እኛም ቤታችን እያፅዳን መንገድ ላይ መገናኘት አለብን፡፡

ያኔ ብቻ ነው ኢትዮጵያን የምናድናት፡፡ እንዳንራመድ ቀይዶ የያዘን ገመድ እየበጣጠስን፤ ፀረ-ለውጥና አድሃሪ አቋምን እየመከትንና እያፀዳን የዴሞክራሲ እና የሉዓላዊነት ፍለጋው ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል ፡፡ አንድነቶች አሁን ነው የፖለቲካ ፅናታቸው በጥበብ ማሳየት ያለባቸው፡፡ ወንድሞቻችን በርቱ!!!

አንድነት ፓርቲ የኢህኣዴግን ምንነት ላላመኑ ወገኖች ለማጋለጥ በትጋትና በስሌት ሲሰራ ቆይቷል፡፡እየሰራም ነዉ፤እዚህ ደርሷል፡፡ “የሆደ ሰፊዉን ምርጫ ቦርድ” ሆድ በገሃድ አጋልጧል፡፡በነአሞራዉና ወዲ ቐሺ(በተጋሩ ሁሉ) ትግልና ሞት የሚቀልዱትን በህዝብ ፊት ወጥተዉ ዛሬም እንዲዋሹና ለኢትዮጵያችን የፖለቲካ ታሪክ እነማን ምን እንደሆኑ አንድነት ፓርቲ የበኩሉን ሚና ተጫዉቷል፡፡ ለኔ ከባድመ ዉሳኔና ልህዝቡ በወቅቱ ከተነገረዉ ጋር ይመሳሰላል፤ይጠጋጋል፡፡ኢህኣዴግ ምርጫዉን እንደማይፈልገዉ፤ከፈለገዉም ለተለመደዉ ቀልዱ ከነማን ጋርና በምን ሁኔታ እንደሚፈልገዉ ፓርቲያችን ሶስተኛዉን (የአዉሮፓና አሜሪካ ታዛቢዎች የሌሉበት ምርጫ መሆኑን፤የህዝብ ታዛቢዎች የተበላሸ የምርጫ ሂደትና ፓርቲዎችን የማፈራረስ/የማዳከም ስራዎች) ነጥብ አስመዝግቧል፡፡

በዚህ ሂደት ላይ ሰፊ እዉነታ ለህዝብ ይቀርባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ከምርጫዉ ቦርድ መጋረጃ ካሉት ወገኖች ጋር በሃሳብ እየተሸነፈ ግን ተሳትፎዉ ያለተቋረጠ አንድ ከፍተኛ አመራር እንዳለ እናዉቃለን፡፡ሁሉን ነገር በደንብና በመርህ የምንሰራዉ ለኢህኣዲግ/ምርጫ ቦርድ ካለን ፍርሃት ሳይሆን ለወደፊቱ ለምናስተዳድረዉ ህዝባችንና ለኢትዮጵያችን ፖለቲካ ክብር ስንል ነዉ፡፡እናም ከደንብ ወጥተን የሰራነዉ ክዋኔም በግፍ የገፋነዉ አመራርም፤አባልም የለም፡፡በመቻቻል መንፈስ ዲሰፒሊን ተጥሶም እንዲጓተት ተደርጓል፡፡ይህንንም የኢህኣዴግ ተባባሪነት ለታሪክ አስቀምጠነዋል፡፡

ምርጫ ቅንጦት ሆኖብን፤የተከበሩ እየተባሉ ለመጠራት ሳይሆን እፊታችን ላይ ያለ እድልና ስልትም ስለሆነ አንድነት ፓርቲ መጪዉን ምርጫ የምር እንዲሆን ወስኗል፡፡ ኢህኣዴግ ደግሞ ማበላሸቱን ተያያይዞትል፡፡ምርጫ በአምባገነን ቡድኖች ለሚገዙ አገራት ለለዉጥ እንዱ ስልት እንጂ ብቸኛዉ አለመሆኑ ይታመናል፡፡ፓርቲያችን ለለዉጥ ተደራጅም ይላል፡፡እዉነተኛ ፓርቲዎች ከምርጫዉ ባሻገር ላለዉ ግብ እንዲዋሃዱና እንዲተባበሩም ጥሪ አቅርቧል፤ስልቶችን ለማቀራረብም እየጣረም ነዉ፡፡የአንድነት ኣባላት በያለንበት ድርብ ሃላፊነት አለብን፡፡ለአንድነት ሃይሎች ስልቶቻችን ሁሉ በማቀራረብ የተጀመረዉ የስልጣን ሃይሎችን እያራገፉ ትግሉን በሰለጠነና አንድነቱን በጠበቀ መልኩ የማስቀጠልና ልዩነቶችን በማቻቻል ሰፊ መሰረት የማንበር ሃለፊነት አለብን፡፡ ታሪክ ለመስራት እንዘጋጅ፤ፊታችንን ወደ ዋናዉ ግብ እናድርግ፤ከሃዲዱ አንወርድም!

Image

ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ 200 000 ዶላር የሸለመውና የኢትዮጵያ ብቸኛ የማዳበሪያ አቅራቢ የሆነው Yara ዳይሬክተር Thor Leif Enger በሙስና ክስ ፍርድ ቤት ቀረበ

መለስ ዜናዊን የሸለመው በሙስና ተከሶ ፍርድ ቤት ቀረበ
የኖርዌይ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን Yara ላይ ክስ ሊጀምሩ ነው።
**********************************************
በኢትዮጵያ አቆጣጠር 1997 (2005) ለቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ 200 000 ዶላር የሸለመውና ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያ ብቸኛ የማዳበሪያ አቅራቢ የሆነው Yara የተባለው የኖርዌይ ኩባንያ ዳይሬክተር Thor Leif Enger በኖርዌይ ታሪክ ትልቅ በተባለው የሙስና ክስ ነገ ጠዋት Oslo ፍርድ ቤት ቀረበ ።

በጣም የሚገርመው ዳይሬክተሩ የተከሰሰው በህንድ እና ሊቢያ ጉዳይ ሲሆን Yara በእነዚህ ሁለት ሃገራት ውስጥ ባልተገባ መልኩ ጨረታ አሸንፎ ማዳበሪያ የማቅረብ ኮንትራት ያገኘበት መንገድ ለሁለቱ ሃገራት ባለሥልጣኖች ዳይረክተሩ ከጨረታው በፊት 8 ሚሊዮን ዶላር በመስጠቱ መሆኑን የዛሬው የኖርዌይ የዜና አገልግሎት NRK ተዘግቧል። ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ የ71 አመቱ ቱርላይፍ ኤንገን የቀረውን ህይወቱን በእስር ቤት እንደሚያሳልፍ ታውቋል።

ይህንን ቅደም ተከተል ይመልከቱ :
✦June 2005 – Ethiopian police massacred the Ethiopian oppositions on the streets of Addis Ababa.
✦July 2005 – Mr Thorleif Enger Director of Yara awarded 200 000 USD to former P.M Meles Zenawi apparently for his steps towards increasing food production and reducing poverty
✦December 2005 The Norwegian Yara wins contracts to deliver fertilizer in Ethiopia after handing out prizes to the former PM. 30% of the income went to the ruling TPLF’s companies (EFFORT)
✦January 2014 Mr Thorleif Enger the former Director of Yara appears in court indicted for corruption after for paying over $8 million USD in bribes to win fertilizer bids in India and Libya.
✦ In January 2014, Ethiopians residing in Norway (led by me) request the Norwegian National Authority for Investigation and Prosecution of Economic and Environmental Crime (ØKOKRIM) to investigate the bid that Yara won in Ethiopia December 2005. http://www.okokrim.no/artikler/in-english
ልጅ ግሩም

አርማጮ ያለው የወያኔ ጦር በአማራ ንቅናቄው ጦር አሁንም ተሰንጎ ተይዟል::

– ሻእቢያ መረጃ ያሾልካሉ ባላቸው የነጻነት ታጋዮች ላይ ማስጠንቀቂያ አወረደ::
– የውህደቱ ጉባዬ ይካሄዳል ተብሎ እየተጠበቀ ነው:: ቅድመ ምክክሮች እየተካሄዱ ነው::
– የሕወሓት ጄኔራሎች እና የደህንነት ሃላፊዎች ጎንደር እየተመላለሱ ነው::
Minilik Salsawi

ከአስመራ የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ከውህደቱ ቀድመው የሚወጡ የስብሰባው መረጃዎች እና ሻእቢያን የሚመለከቱ ግፎችን በዝርዝር መረጃ ሰጥተዋል የተባሉ የነጻነት ተዋጊ ኢትዮጵያውያን በግምገማ እየታመሱ መሆኑን የሻእቢያ ምንጮች ጠቁመዋል:: አመራሮቻቸውን በግንባር አስቀምጦ ለነጻነት በረሃ የገቡትን ታጋዮች ሰብስቦ በሱዳን ሲም ካርዶች እየተጠቀማቹ መረጃዎችን በኤስኤሜስ ቴክስት እና በኢንተርኔት ታቀብላላቹ የመረጃ መውጣት ፍንጮች እየታዩ ነው ሳይስፋፉ ራሳችሁን አጋልጡ እየተባሉ ሲተራመሱ መክረማቸው ታውቋል::

ስለ አስመራው ትግል ዝርዝር መረጃዎች አሉን የሚሉ የድህረገጽ ሚዲያዎች በርክተዋል በሚል ዙሪያ ከፍተኛ ግምግማ የተካሄደ ሲሆን ሁኔታው መጣራት አለበት በሚል መተራመሱ ሲቀጥል በኤርትራ የኢንተርነት አክሰስ የሚጠቀሙ እንዲታገድባቸው እና ለፕሮፓጋንዳ ሰራተኞች በክትትል እንዲፈቀድላቸው የተደረገ ሲሆን የሱዳን ሲም ካርድ የሚጠቀሙ የበረሃ ልጆች በጠቅላላ ከነስልካቸው እንዲነጠቁ እና ምንም አይነት አክሰስ እንዳይፈቀድላቸው ሻእቢያ ከባድ ማስጠንቀቂያ አውርዷል::መረጃውን የሰጡን የሻእቢያ ምንጮቻችን ከአፋኝ መንግስት ወደ ሌላ አፋኝ መንግስት በሽያጭ ይሁን በተውሶ በማይታወቅ መልኩ ዝውውር አድርገናል ሲሉ የነጻነት ታጋዮቹ ውስጥ ውስጡን ያጉረመረሙ መሆኑን ገልጸዋል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ የውህደቱ ጉባዬ ይጀመራል ተብሎ እየተጠበቀ ሲሆን ቅድመ ምክክሮች መካሄዳቸውን በስብሰባው ለመሳተፍ የሄዱ ቡድኖች የገለጹ ሲሆን ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል::

በአርማጮና በአከባቢው የሚገኘው የአማራ ንቅናቄ ጦር የወያኔን ሰራዊት ሰንጎ በመያዝ እየተዋጋ መሆኑን የድርጅቱ ምንጮች ገልጸዋል::ይወያኔው መንግስት ባከባቢው የተነሳውን ጦርነት መቆጣጠር ባለመቻሉ ከኢታማጆር ሹሙ ጀምሮ የደህንነት ምክትሉ አቶ ኢሳያስ እና የጠ/ሚ የደህንነት አማካሪ አለቃ ጸጋይ ድረስ የአከባቢውን ወታደራዊ እና የደህንነት ባለስልጣናትን ጨምሮ እየተረባረቡ መሆኑን የቅርብ ምንጮች አስታውቀዋል::የአማራ ክልል የደህንነት ሃላፊዎች አቶ ተሾመ እና አቶ አያኖ መቀመጫቸውን ጎንደር በማድረግ ከፍተኛ መረጃ በመሰብሰብ ከወታደራዊ ደህንነቶች ጋር በመቀዳጀት ለፌዴራሉ መንግስት በማስተላለፍ ላይ ይገኛሉ::እንዲሁም ይህንን እንቅስቃሴ በበላይነት ለመምራት የመከላከያ ዘመቻ የበላይ መኮንን የሆነው ጄኔራል ገብረዝጌር መብራትኡ ከአዲስ አበባ ጎንደር በመሄድ ሂደቱን እያስተባበረ ያለ ሲሆን ወደ ሱዳን መንግስትም የደህንነት ምክትል ሹም አቶ ኢሳያስ የተባለ የሚመራው ቡድን መላኩ ታውቋል::

በትላንትናው እላት በከባድ መሳሪያዎች እና ታንኮች ታጅቦ ወደ አርማጮ የገባው የወያኔው ሰራዊት በሽምቅ ውጊያ የሰለጠነ ልዩ ጦር ሲሆን ተጨማሪ ጦር አስቸኳይ ስምሪት ..9 ..9 ..እያደረገ በአከባቢው በመዟዟር ተቃዋሚዎች ይኖሩብታል ያለውን ቦታ ሁሉ በማጽዳት ላይ ሲሆን የሃገር ቤት በወያኔ ህግ ተመዝግበው ያሉ የፖለቲካ ድርጅት አባላት የዚህ ጽዳት ዘመቻ ተጠቂ እንዳይሆኑ ሲያስፈራ ሁኔታውን በአጭር ጊዜ ሳይስፋፋ ሙሉ ሰሜን ጎንደርን እና በከፈል ደቡብ ጎንደርን ለማጽዳት ዘመቻው በደህንነቶች እና በወያኔ ጦር የተጀመረ መሆኑን ምንጮች ከአከባቢው ተናግረዋል::

Image
Eyasped Tesfaye
በኢትዮጲያ ቴሌቪዥን በፖሊስ ፕሮግራም ላይ viewtopic.php?f=2&t=91626 ተቆርጦ ተቀጥሎ የተላለፈው የአንዳርጋቸው ፅጌ ድንቅ የትግል ጥሪ መልዕክት ለሊቱን ሙሉ ሲደንቀኝ ነው ያደረው፡፡ ኢቲቪ በነካካ እጇ ያልተቆራረጠውን ሙሉ ቪዲዮ ደግሞ ብትለቅልን እንዴት ሸጋ ነበር፡፡
አንዳርጋቸው ፅጌ በተቆራረጠው ቪዲዮም ውስጥ እንኳን ያስተላለፋቸው 3 መልዕክቶች ድንቅ ናቸው፡፡ ሙሉውን ንግግሩን ፅፌ እለጥፈዋለሁ፡፡ እስከዛው ግን መልዕክቶቹ እነኚህ ናቸው፡-
1ኛ፡- ለወጣቱ የተላለፈ የትግል ጥሪ፡- ወጣቱ የሴት ጓደኛውን ቀጥሮ ሸሚዙን ሲያስተካክል መዋል ሆኗል ስራው፡፡ እንዴት አድርጎ ከኢትዮጲያ እንደሚወጣ እና ደቡብ አፍሪካ ወይም አሜሪካ እንደሚገባ ብቻ ነው የሚያስበው፡፡ ወደ ፖለቲካው የሚመጣው ወጣት ቁጥር እጅግ አናሳ ነው፡፡ ተፒለፍ እና ኢህአፓ ጊዜ የነበረው ፖለቲካ በትምህርታቸው ጎበዝ የነበሩ ተማሪዎችን ሳይቀር ነበር የሚስበው፡፡ አሁን ግን የፊልም አክተር እና ዘፋኞች የሚኖሩበትን ቤት በፊልም እያየ በምኞት ብቻ የሚኖር ወይም እንዲህ አይነት ቤቶች ወዳሉበት አካባቢ ለመሰደድ የሚፈልግ ወጣት ነው ያለው፡፡ በሚል አንዳርጋቸው ወጣቱ ካረፈበት የእንቅልፍ አዚም እንዲላቀቅ እና ለትግል እና ለመደራጀት እንዲዘጋጅ ያስተላለፈው መልዕክት ነው፡፡
2ኛ፡- የተባበረ ትግል ጥሪ፡- አንዳርጋቸው ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው ለሶስት አካላቶች ነው፡፡ አንደኛ የኦሮሞ የአማራ እና የደቡብ ኤሊቶች ልዩነታቸውን አጥብበው በህብረት እንዲሰሩ የጠየቀበት፡፡ ሁለተኛ በውጭ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች 5 እና 20 እየሆኑ ለየብቻቸው የሚያደርጉትንና እንደ አንዳርጋቸው አገላለፅ ‹‹ዩኒቲ ኦፍ ፐርፐዝ›› የሌለበትን ትግል እንዲተው የተናገረበት እና ሶስተኛ ደግሞ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ዘጠና ፓርቲዎች 1500 ፊርማ ብቻ እያሰባሰቡ እዚህ እና እዚያ የፈሉበትን ሁናቴ የተቃወመበት ነው፡፡
3ኛ፡- ምርጫ ቀልድ መሆኑን ያጋለጠበት መልዕክት፡- መንግስት ግልፅነት ያለው አሰራር ሳይከተል ተቃዋሚዎች እንዴት ብለው ነው የምርጫ ማኒፌስቷቸውን ማዘጋጀት የሚችሉት የሚል ጥያቄ በቪዲዮው ላይ ሲጠይቅ የሚሰማው አንዳርጋቸው ፅጌ ቃል በቃል ‹‹ምርጫው ቀልድ ነው›› ሲልም ይደመጣል፡፡
ሌላው በዚህ ቪዲዮ ላይ ያስተዋልኩት ነገር ከ 6 ደቂቃ ከ 55 ሰከንድ እስከ 7ኛው ደቂቃ ከ 4 ሰከንድ ድረስ እጅግ በጣም ሳግ በተናነቀው እና በተጎዳ ድምፅ ‹‹ከዚህ በኋላ ያለው ነገር የበለጠ ቀውስ እና የበለጠ ኪሳራ በሀገሪቷ እና በህዝቧ ላይ የሚያደርስ ነገር ነው የሚል ዕምነት ነው ያለን›› የሚለው ንግግሩ ነው፡፡ ምኑ ነው የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ ያመጣል ያለው ነገር; ምናልባት ኢቲቪ ትጥቅ ትግሉ የበለጠ ኪሳራ ያመጣል እያለ ነው የሚል ምስል በተመልካች ዘንድ ለመፍጠር አሳባ ነው; ያም ቢሆን ደግሞ ትጥቅ ትግሉ የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ ያመጣል ሲል ማሰማት ነበረባት፡፡ እኔ ግን ሲመስለኝ የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ የሚያመጣ ያለው ምርጫውን እና አሁን ያለውን ስርአት ነው፡፡ ይህን ያልኩበት ምክንያትም በንግግሩ መጨረሻ ላይ የበለጠ ቀውስ እና ኪሳራ የሚያደርስ ነው የሚል እምነት ነው ‹‹ያለኝ›› ሳይሆን የሚለው ‹‹ያለን›› ነው የሚለው፡፡ ይህ ማለት የአንድን ቡድን አቋም እየገለፀ እንዳለ ግልፅ ነው፡፡ በቡድን ደረጃ ያውም አንዳርጋቸው ‹‹እኛ›› እያለ የሚያወራለት ቡድን ደግሞ ስለ ትጥቅ ትግሉ እንዲህ አይነት አቋም እንደሌለው ግልፅ ነው፡፡
በመጨረሻም ቪዲዮውን ደግሜ ደጋግሜ ካየሁት በኋላ የገባኝ ነገር ቢኖር አንዳርጋቸው ባገኛት ትንሽ ቀዳዳም ቢሆን መልዕክቱን ማስተላለፉን እና ምናልባትም ይህ መልዕክት በቴሌቪዥን እንዲሰራጭ ያደረጉት ሰዎች የውስጥ አርበኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ነው፡፡

ኢትዮ-ቻይና በቻይና -አፍሪካ አደባባይ

ኢትዮ ቻይና በቻይና አፍሪካ አደባባይ

ዛሬ ጠዋት 2፡45 ላይ ቦሌ…ከድልድይ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽየሚወስደው መንገድ መጠምዘዣ ላይ ከአስፓልቱ ጠርዞች በአንዱ ጥግ አንድ ቻይናዊ (ቻይና መሰለኝ) ከአንድ ፖሊስ ጋር ሞቅ ያለ ክርክርነገር ገጥሟል….እጁን እያወናጨፈ ያወራል…መቼም “ቻይና”ዊው አማርኛ አጥንቶ ይሆናል እንጂ በዚህ ፍጥነት የሚያወራው ነገር (ቻይንኛ/ማንዳሪንከሆነ) ፖሊሱ የሚገባው አልመሰለኝም…”ቻይና”ው የፖሊሱን ነው መሰለኝ የዱላ ቆመጥ በእጁ ይዟል…አጠገባቸው ስደርስ ቻይናው “temper is come” ሲል ሰማሁት… በእንግሊዝኛ ሊያስረዳውእየሞከረ ነው ማለት ነው….ሰይጣኑን ያመጣው ምን ይሆን ብዬ እያሰብኩ ሳለ ሴት ፖሊስ መጣችና ቻይናው በእጁ የያዘውን ቆመጥ እያየች‹‹ማነው የሰጠው;›› ስትል ሰማሁዋት …”ቻይና”ው በሆነ ብልሃት ከፖሊሱ እጅ እያሳሳቀ የወሰደው ነው የሚመስለው…ወንዱ ፖሊስ ቆመጡንተቀበለ….አንድ አስር እርምጃዎች ወደፊት ስሄድ በርከት ያሉና ሻንጣዎች የያዙ ቻይናዎች ከአካባቢው ሰው ጋር ውዝግብ የገቡ ይመስላል….ሌባ ተተናኩሎዋቸው ይሆናል አልኩ (ያው ሌቦቹ እኛ አይደለን?!) ግን በሚታዩኝ አንድ ሁለት የፌዴራል ልብስ የለበሱ ወታደሮች የታጀበአንድ ጥቁር እንደ ሌባ ተይዞ ስላላየሁ፣ እንዲሁም ከግርግሩ መሃል አንድ ቻይናዊና አንድ ኢትዮጵያዊ ወጣት አንገት ላንገት ሲተናነቁማየቴ ጉዳዩ ሌላ አንደሆነ ጠረጠርኩ….ይሄኔ ሌሎቹ ቻይናዎች ድብድቡ ወደእነሱ እንዳይመጣ ለመከላል ይሁን ወይ የወንድማቸው መመታትደማቸውን አፍልቶት እንጃ ብቻ አጠገባቸው የሚገኘውን ሰው ባለ በሌለ ሃይል መማታት ያዙ…አሁን ተሞኙ አልኩ…እጁን አጣጥፎ የእነሱንዱላ እንደአሻንጉሊት ወይም እንደ ጌም ገፀባህሪት የሚቀበል ሰው ያለ መስሏቸው ይሆን? (ይቺ ናት ጨዋታ አለ ጥልዬ) እዚያየተሰበሰበው ሁሉ በድንጋይም በቡጢም ቻይናዎቹ ላይ ሲረባረብ ጉዳዩ አስፈሪ መልክ ያዘ …. ሁለት ጥይቶች ወደሰማይ ተተኮሱ…አንድ “ቻይና” ፊቱ በደም ተለውሶ ከግርግሩ ውስጥ ሲወጣና “ቻይና”ዎቹ ቁጥሩ በጣም እየበዛ የመጣው ህዝብ እደማይለቃቸው ሲገባቸው (ጥይቶቹምፀቡ የዋዛ እንዳልሆነ ሲገልፁ)….ገለል ገለል አሉ…ጉዳዩ በ”ቁጥጥር” ስር ሲውልና “ቻይና”ዎቹ መሃል አስፓልት ላይ እንዲቀመጡታዘው ደምና አቧራቸውን (“ለሀገሬ የከፈልኩት ነው” ይሉ ይሆናል) እየጠራረጉ ከነሻንጣዎቻቸው ሲቀመጡ….. እኔም ወደጉዳዬ ሄድኩ….

“Made in China” የሚል ጫማ ስንገዛ አንዳንዶቻችን “መቼም እግሬን አይወስዱብኝም”ብለን ነበር…መንገድ ሲሰሩ ስናይ ያገሬ መሀንዲስ ዛሬ እዚህች ጋ…ነገ ደግሞ እዚያች ጋ እየቆፈረ የሆነች ኪሎ ሜትር ላይ አመትመተኛት አቁሞ ትንሽ መፍጠን ሲችል ቻይና ሀገሯ ትገባለች ብለን ነበር… እርግጥ ነው ከአዲስ አበባ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ወጣ ስንልየተተከሉና ግብራቸውን ለመረዳት ስንሞክር አማርኛ እያማረን ቀርቶ በተበደርነው እንግሊዝኛ እንኳ እንዳይገባን የራሳቸው ቋንቋ ብቻየተለጠፈባቸው ግዙፍ ኩባንያዎች ስናይ ፍርሃት ቢጤ የሚሰማን ጥቂቶች አይደለንም (የሀገራችንን መልክ እየቀሙን እንደሆነ ደመ ነፍሳችንእየነገረን)….(ጎበዝ፣ ቻይንኛ መማር አይከፋም…ቢያንስ ምን እያሉ እደሚያሻሽጡን ይግባን እንጂ).…
Image

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በተለምዶ OCR (OldClass Rooms) በሚባለውና የኢትዮጵያና የውጪ ቋንቋዎችና ስነፅፍ እንዲሁም የፎክሎር ትምህርቶቸ በሚሰጡበት ህንፃ ውስጥ የቋንቋዎችጥናት ተቋም ቤተመፃህፍት ነበር (“ነበር” እንበል) የእነዚህ ትምህርቶችን የተመለከቱ መፃህፍት…ጥናቶችና ጆርናሎች የሚገኙበት…የህንፃው አንደኛ ፎቅ ላይ የተሰየመ….ባለፈው ሰሞን በአጋጣሚ ወደዚያ ህንፃ ሳቀና መልኩ ተቀይሮ አገኘሁት….ቤተመፃኅፍቱ ዕድሳትየተደረገለት መስሎኝ ነበር መጀመሪያ… ጠጋ ስል የተስፋፋ የቻይና ግዛት ሆኗል ….የቻይና ኢምፓየር ህንፃው ውስጥ ተገንብቷል…“ConfuciusInstitute” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ…ግርግዳው ላይ የቻይናን ባህል የሚያስጎበኙ በፍሬም የታሸጉ ፎቶ ግራፎች ተሰቅለዋል……ቤተመፃህፍቱየለም (ነፍስ ይማር ብለናል) …. ወዳጆቼ፣ ፈቅደን ስንሰጣቸው የትድረስ እንደሆነ ካላወቅን (እናውቃለን ማለት ይከብዳል-ማወቅም የምንፈልግ አንመስልም) ንቀት ብትነግስብን በማን ይፈረዳል?
Elizabeth Mengistu

ቦሌ ወሎ ሰፈር በግድግዳ ላይ ፅሁፎች እና መፈክር በተፃፈባቸው ወረቀቶች አሽብርቃ አደረች፡፡አቡ ዳውድ ኡስማን በአዲስ አበባ በቦሌ ወሎ ሰፈር የሚገኙ የውስጥ መንገዶች በግድግዳ ላይ ፅሁፎች እና መፈክር በተፃፈባቸው ወረቀቶች አሸበርቃ ማደሯን ምንጮች አስታወቁ፡:
በቦሌ ወሎ ሰፈር ውስጥ ለውስጥ በሚያስኬዱ መንገዶች የሚገኙ ግድግዳዎች እና መንገዶች የህዝበ ሙስሊሙን ሰላማዊ የመብት ትግል የሚያንጸባርቁ መልዕክቶች ተፅፎባቸው አንግተዋል፡፡
ከተፃፉት እና ከተበተኑት መፈክሮች መካከል
አሸባሪ አይደለንም፣ የታሰሩት ሙስሊሞች ይፈቱ,ኮሚቴው ይፈታ፣የሂጃብ
ገፈፋው ይቁም፣ትግሉ ይቀጥላል፣ ፍትህ ናፈቀን

የሚሉ እና በርካታ መፈክሮች በግድግዳ ላይ እና በወረቀቶች ተፅፈው መበተናቸው ታውቋል፡፡
ህዝበ ሙስሊሙ የጀመረውን ሰላማዊ ትግል በማጠናከር የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ድምፁን እያሰማ ይገኛል፡፡
ድል ለጭቁኑ የኢትዬጲያ ሙስሊም!!

Image
Image
Image

More Photos
https://www.facebook.com/profile.php?id … nref=story

በዚህ ወር የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ VOA የአማርኛ ፕሮግራም አራት የሚዲያ ባለሙያዎችን በመጋበዝ ያደረጉትን ውይይት አድርገው ነበር፡፡ በሁለት ክፍል የተሰራጨው ውይይት ተሳታፊዎች፡- ጽዮን ግርማ፣ አርጋው አሽኔ፣ ዳንኤል ብርሃነ እናመስፍን ነጋሽ ነበሩ፡፡ የፕሮግራሙ ርዕሰ-ጉዳይ (በVOA ድረ-ገጽ ላይ የሠፈረው) ጽሑፍ እንደሚከተለው ሲሆን፡- ነጻና ሚዛናዊ ምርጫ ለማካሄድ የሁሉንም ተወዳዳሪዎች ፕሮግራም ለሕዝብ የሚያደርስ በነጻነት የሚዘግብ መገናኛ ብዙኃን ወሳኝነት የዲሞክራሲ ባሕልና መሠረትም ነው። በርካታ ጋዜጠኞች እስር ላይ በሚገኙባትና ያንኑ ያህል ቁጥራቸው የበዛ አገር ጥለው በተሰደዱባት ኢትዮጵያ በነጻነት መዘገብ የሚችሉ ጋዜጠኞች መኖር እያነጋገረ ነው። ለጋዜጠኞች መብት ከቆሙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች አንዱ Freedom House በቅርቡ ስለ አገሮች የነጻ ፕሬስ ይዞታ ባወጣው ዓመታዊ ሪፓርቱ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ቀጥሎ ጋዜጠኞች የታሰሩባት አገር መሆንዋን ዘግቧል። በጸረ ሽብር ሕጉና በወንጀለኛ መቅጫ የተከሰሱ ቢያንስ አስራ ሰባት ጋዜጠኞች በእስራ ላይ እንደሚገኙ ሌሎች በርካቶች እንደተሰደዱ በሪፖርቱ ዘርዝሯል። የኢትዮጵያ መንግስት ባለ ስልጣናት በተደጋጋሚ “ጋዜጠኛ ሰለሆነ የሚታሰር ማንም የለም። በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ብቻ ናቸው የታሰሩት፤” ይላሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰለመጪዉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ለመዘገብ የሚያስችል ነጻ የመገናኛ ብዙኃን ሕዋ አለ? ከአድማጮች ለቀረቡ ጥያቄዎች የሰጡትን መልስ ጨምሮ በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር የሚገኙ ጋዜጠኞች ተጋብዘው ይወያያሉ። ውይይቱ በVOA የተላለፈው በታህሳስ 4 (Dec. 13) እና ታህሳስ 11(Dec. 20) ሲሆን፤ ሁለቱን ክፍሎች አንድ ላይ በማድረግ ከታች ባለው የድምጽ ፋይል አቅርበናቸዋል፡፡ – – – – – ********* More from Horn Affairs AmharicAudio […]

(ታምራት ኃይሌ) ርዕስ፡- የሶሻሊስቱ ጠንቋይ ጉዳይደራሲ፡- ሀማ ቱማተርጓሚ፡- ሕይወት ታደሰአጭር፡- ሥነ ጽሁፋዊ ምልከታገምጋሚ፡- ታምራት ኃይሌ የሶሻሊስቱ ጠንቋይ ጉዳይ The case of the Socialist Witchdoctor የ 22 አጫጭር ትረካዎች መድብል ሲሆን ትረካዎቹ በሁለት ክፍል ተለይተው ቀርበዋል፡፡ በክፍል አንድ አድራሻቸውን ፍርድ ቤት ያደረጉና በክስ መዝገቦች፤ በክርክሮች፤ በጥፋተኝነት ና በቅጣት ውሳኔዎች ላይ የተመሰረቱ አስራ አንድ ትረካዎች እናገኛለን፡፡ ትረካዎቹ አንድም አስራአንድም ናቸው፡፡ አንድነታቸውንም አስራአንድነታቸውንም በኋላ እመለስበታለሁ፡፡ በክፍል ሁለት እንደዚሁ አስራ አንድ ትረካዎች እናገኛለን፡፡ እንደመጀመሪያው በአንድ ቦታ የሚከናወኑ አይደሉም፡፡ ስለዚህ እነዚህን አንድም አስራ አንድም ናቸው ማለት ባይቻልም ፍጹም አይመሳሰሉም ደግሞ ማለት አይቻልም፡፡ በግድ አንድ ለማድረግ ሳይሆን፤ እንቅልፍ በሚያሳጣ ጸጉር ስንጠቃም ለመለያየት ሳይሆን በዚህ በሁለተኛው ክፍል ውስጥ ከተዘረዘሩት ትረካዎች መካከል በአንደኛው ማለትም “በሽብር ሚዛን አስር” መግቢያ ላይ የምናገኘው ኃይለ ቃል የቀሩትን ትረካዎች የጋራ ፍሬ ነገር በማስረዳት ረገድ ለጥቅስ የሚበቃ ይመስላል፡፡ እንዲህ ይላል፡፡ ትረካ ኢትዮጵያ ውስጥ ተመራጭ የጊዜ ማሳለፊያ ቢሆንም፤አሁንም ጥቂት ተጠራጣሪዎች ከሰማኒያ በመቶ በላይ መሀይም ባለበት አገር ውስጥ ድሮም ሌላ አማራጭ ሊኖር አይችልም በማለት ይናገራሉ፡፡ ለማንኛውም በዕድሜ የገፉ ሰዎች የተካኑበት ትረካ በአሁኑ ሰዓት በከፍተኛ ሁኔታ እንደተለወጠ የማይስማማ የለም፡፡ በአሁኑ ጊዜ አሰቃቂዎቹና አስገራሚዎቹ ታሪኮች የሚተረኩት በሽማግሌና ባልተማሩ ሰዎች ሳይሆን በተማሩ ወጣት ካድሬዎችና መገናኛ ብዙሀን ተብሎ በሚጠራው አካል ነው፡፡በድሮ ጊዜ በአጠቃላይ ታሪኮች ለዘብ ያሉና ልጆችን ለማስፈራራት ያህል መጠነኛ ምትሀታዊ ጉዳዮች ያሉባቸው ነበሩ፡፡ ስለሚያወሩ ጥንቸሎች፤ስለሸረኛ ጦጣዎች ስለታላላቅ አናብስት፤ስለተንኮለኛ ጅቦች፤ […]

http://www.eaglewingss.com/%E1%8B%A8%E1 … %E1%8C%A5/

የጠቅላይ ሚኒስትሩ እጅ እጅ ያለዉ ዶሮ ወጥና ፖለቲካ
Samson K.

Posted By Samson K.

በቅርቡ ተጠቅላይ ሚንስትሩ ሃይለማሪያም ደስ አለኝ ዓረብ ሐገር ያዩትን ወገንና አዉሮፓ መጥተዉ ያዩትን የወገን ችግር፣በምፀት ሲገልፁ- ብዙ እንቶ ፈንቶ ተናግረዉ ነበር ፈረንጆቹ bla -bla ይሉታል ፣ ከዛ ዉስጥ ግን አንድ አነጋገራቸዉ ቀልቤን ስባ ሌላም ነገር አስታወሰችኝና ትንሽ ልበል ብዬ እኔም ብዕሬን አነሳዉ ።

ምን ሆነዉ ነው እንደዚህ በሰዉ ሐገር እሚሰቃዩት -ሐገራቸዉ ቢሆኑ ጠግበዉ መብላት እንደሚችሉ, ስደተኛዉን ኢትዮጵያዊም ሆነ ያገሪቷን ክብር በወረደ ቃላት ሲዘባበቱበት ከራሳቸዉ አንደበት ሰማሁና ፣ ታዲያ ይሔን ግዜ ምን አሰብኩ እኝህን ጠቅላይ ሚንስትር በዙሪያቸዉ ያሉ የድሮ ማርክሲስት ኤሊትሶች ይህን እንዲናገሩ እና እንዴት ከጨወታ እያስወጡዋቸዉ እንደሆነና መጨረሻቸዉም ከግዜሩም ከሰይጣኑም እንዳይሆኑ ተደርጎ የስርዓቱ የተሞላ አሻንጉሊት ሲሆኑ ማየቱ እንደዜጋም እንደሰዉም ስላሳዘንኝም ነዉ ።

ባንድ ዎቅት በፈረንሳይ ዓብዮት የፈረንሳይ የተራቡ ጭሰኞች በ፩፯፯፭ 1775 በፈረንጆቹ አቆጣጠር ባነሱት የዳቦ ጥያቄ ልዕልቲቷን ማሪይ አንቶይነት Marie Antointte ዳቦ ከሌለ ለምን ኬክ አይበሉም ዎይንም ደግሞ ኬክ ይብሉ ብላ የተናገረችዉን በወቅቱ የነበረዉ ምሁር ዓብዮተኛ የልዕልቲቷን አባባል በሁለት መንገድ ሰንጥቆ የህዝብ ቁጣ public plight መቀስቀሻ ተደርጎ በወቅቱ የነበረዉን የቡርዥዋ የመደብ አርስቶክራሲ aristocracy ችግር በማሣየትና እና የልዕልቲቷን ኦስትሪያዊነት ከፈረንሳይ ሞናርኪ ሉዊስ ፩፮ኛLouis XVI. ለመገንጠል የርስዋን አባባል ለፖለቲካ ትርፍ ተጠቅመዉበታል ።(ላንባቢያን- እንደማስታወሻ እንደምርቃትም ትሆነን ዘንዳ በዚች ዙሪያ ትንሽ ብናክል)-በነገራችን ላይ እዚህ ጋር አንባቢያን ስለዚህ አባባል በተለያዩ የታሪክ ፅሁፎች ዉስጥ ለምን ኬክ አይበሉም ያለችዉ ማሪያ ተረዝ Maria Therese ትባል የነበረች የፈረንሳዩ የሉዊስ ፩፬ኛ XIV ሚስት የነበረችዉን እንደሆነም ይነገራል ይህንንም የፃፈዉ ለመጀመሪያ ግዜ ዤን ዣኹዊዝ Jean -Jacques Rousseau ይባል የነበረ የፖለቲካ ፈላስፋ ‘ኑዛዜ’ ዎይንም ‘ኮንፌሽን confession ‘ብሎ ባሳተመዉ መፅሐፉ ዉስጥ እንዳሰፈረ የተለያዩ መጣጥፎች ይናገራሉ በዚ ጉዳይ እስካሁን ብዙ የታሪክ ፀሐፍት ለሁለት እንደተከፈሉ ነዉ ፤አንደኛዉ ወገን Marie Antoinette የማሪዬ አንቶይነት አባባል ሲል ሌላኛዉ ደግሞ የማሪያ ተሬዝ Maria Thereseነዉ እንዳለ ነዉ ። Louis XVIIሉዊስ ፩፰ኛም በራሱ ብዕር በ፩፯፱፩ (1791) አጠናቅሮ እንደፃፈና ኣባባሉም የማርያ ተረዝ መሆኑን የፃፈዉ ማስረጃም እንዳለ እሚተርኩ አሉ )

እናም ታዲያ ወደተነሳሁበት ርዕስ ስመለስ የኙ ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማሪያም ደስ አለኝ የጀርመን German ጉብኝት ወገን በመጠለያ ካምፕ ዉስጥ ባዶ ዱቄት ሲበላ አይተዉ የተናገሩት የማሪዬን Marie A.ዎይንም ማሪያ ተረዝ Maria Therese አባባል ስላስታወሰኝ እና መጨረሻቸዉም ስላሳዘነኝም ነዉ። ዱቄት ለምን ይበላሉ ዶሮ እያለ ከሆነ አባባላቸዉ ለኛ ሐገሩ ሐይለ ማሪዬ Marie የዘመናችን ያበሻ አባባል phrase ሆና እንዳትቀር ያስፈራል ፤ ከሆነ እንግዴ ሳንወድ በግድ ከ ማሪዬ Marie .A እና ከ ማሪያ Maria Therese ጎን ሌላ ያበሻ ሃይለ ማርዬ Marie ልንጨምር ግድ ይላል ማለት ነዉ- አጃኢብ ነዉ ። ለኛ ሐገርም ራሳቸዉን ለለዩ የመደብ ማርኪሲስት aristocrats መካከልና በቅዠት እሚኖረዉን የምንዱባን ህይዎት ባጠቃላይ ባያሳይልንም በከፊል ግን የሳቸዉ አባባል ያለዉን የመንግስትና የህዝብ ክፍተት ፍንትዉ አድርጎ ያሳያል – ልብ ያለዉ ልብ ይበል።

ብዙዉን ግዜ ያንድ ሐገር ጠቅላይ ሚንስትር ባገር ጉዳይ ስራ ላይ በሚሆንበት ግዜ የራሱ ያነጋገር ዘይቤዎች፣ የሚናገራቸዉ የሚጠቀማቸዉ ቃላትና አባባሎች ዕጅግ ጥንቃቔ ይደረግባቸዋል ፤ያም እሚሆነዉ የባለስልጣኑ አነጋገርና አካሔድም ሆነ አቀማመጥ ፕሮቶኮል የመላዉን ህዝብ እና ሐገር ስለሚወክል ነዉ ። ስለዚህ የራሱ የሆኑትን ልማዶችና ዕምነቶች በህዝብ ፊት ዎይንም በማንኛዉም የሚዲያ መገልገያ አዉታሮች ላይ ዕንዳይጠቀም የስራዉ ሃላፊነትና የስልጣኑ ደረጃ ባያስገድደዉም ፣ነገር ግን ብያንስ ግድ ይሏል። ይሔም ማለት በቀላል አገላለፅ ክብርንና ደረጃን ሐገርንና ህዝብን በሚመጥን መልኩ ማለት ነዉ፤ ፕሮቶኮል ጠባቂ ዎይንም ደምብ ጠባቂ ሹሙ ቢቻል ቀድሞ ይቀርፀዋል፤ ካልሆነም ቀድሞ ምክር ይሰጣል ። የዶሮ ወጥ ይዞ ስለመጉዋዝና ስለግርድና ስራ፣ ስለ ወገን ሰደተኝነት ማብጠልጠልና ተራ አነጋገርና ቃላትን መጠቀም ትርፉ ራስንና አገርን ማዋረድ ካልሆነ በቀር ሌላ የፖለቲካ ትርፍ አለዉ ቢባል ጅልነት ነዉ።

ለዛዉም ደግሞ ሲደተኞቹ የጦር ምርከኞች ሳይሆኑ ጥገኝነት ጠያቂዎች ሆነው የጀርመን መንግስትም ወስዶ ማስጎብኘቱ ሌላዉ ልብ ያላሉት እና ያልተዘጋጁበት ይመስላል ፤ ይህም ቢሆን ባዉሮፓ የስደተኞች አያያዝ ህግ መሰረት ለጀርመን መንግስትም ቢሆን የፖለቲካ ኪሳራ ነዉ ፤የታደጉዋቸዉን ሰደተኞች ለገዳያቸዉ ዎይ ደግሞ አሳዶ ላስወጣቸዉ መልሰዉ ካስጎበኙም የሚያሳዝን ነዉ። ይልቅ የዶሮ ወጡን ይዘዉ የመጡት ለዘመዶችዎ ከሆነ እና እዛዉ ጣቢያ ዉስጥ በስደተኛ ስም ለልዩ ስራ የተመደቡ ከሆነ ዕርግጥ ነዉ እነዚያ ሰዎች ምን ጎሎአቸዉ እና ምን አጥተዉ አንደሆነ እኛም አናውቅም እርሶንም ያ ከሆነ ያንገበገቦ ሚስኪኑን ትክክለኛ ስደተኛ ሳይደርቡ ለይተዉ ቢነግሩን ጥሩ ነበር።

በጀርመናዉያንም ጓደኞቻቸዉ ‘ኸይም’ heim (መጠለያ) ትርጉሙ ተነግሮአቸዉ’ እተዘጋጀ የስደተኞች ጣቢያ ተኪዶ ወገንን -ያንድ ሐገር ጠቅላይ ሚኒስትር ቆሞ ሲያሾፍና ሲዘባበት ያንን በህዝብ የመገናኛ ጣቢያ እንደ ትልቅ የፖለቲካ ትርፍ ወሰደዉ መደስኮሩ ፣ ፖለቲካ ሳይሆን ተራነትንና መደዴነትም ነዉ። ያገር ክብር የህዝብ ክብርን ከምንም በላይ ተምሳሌት ሆኖ እሚገለፀዉ በመሪዉ ነዉ ይሔን ክብር ነዉ ፈረንጆቹም DIGNITYዲግኒቲ እሚሉት ሐገር ህዝቡ ቢደኸይም በምንም ዓይነት ግን የራስ ክብርን dignityዲግኒቲ አሳልፎ አንድ ያገር ጠቅላይ ሚኒስትር እራሱንና ህዝቡን ባደባባይ አያዋርድም ። በጠቅላይ ሚኒስትሩ የክርስቲያን ሃይማኖት መፅሐፍ ቅዱስ ዉስጥም ሙሴ ያንን በባርነት ስር የነበረዉን ወገኑን አዝኖ አከበረው እንጂ አላዋረደዉም ፤ ክብር ለሰዉ በሰዉነቱ ፣ክብር ለህዝብ በማንነቱ፣ ክብር ለወገን በወገንነቱ ፣መስጠት ልማታዊ ባያረግም ነገር ግን ስልጡን ያረጋል ሙሉ ስብዕናንም ያላብሳል።

ጉብኝቱን የፈቀደልዎት የጀርመን መንግስት ዘመዶችዎ በመጠለያ ጣቢያዉ እንደነበሩ አሳዉቀዉ ከሆነ ፣ይኼም ቢሆን ለራስዎ የፖለቲካም ሆነ የሞራል ኪሳራ ሲሆን ለመላዉ ኢትዮጵያዊ ግን ዉርደት ነው። የጀርመን መንግስት ለርስዎ ጣቢያዉን ማስጎበኘቱም ባለም አቀፍ የስደተኞች አያያዝና የደህንነት ህግ አንቀፅ ጥሰት ሊያስጠይቀዉ እንደሚችል ሊያዉቁትም በተገባ ነበር ፤ ይሔንንም ባደባባይ ሲያወሩ ባዶ አማኝና ባዶ ፖለቲከኛ መሆንዎን ነው የሚያሳየዉ ።ለዚህም ነዉ የፕርቶኮል አስፈላጊነት በመሪ ደረጃ እንዲህ ያሉ ተቀጣጣይ የሆኑ አነጋገሮችን ቀድሞ እሚያርመዉ፤ ያለበለዚያ ራስንም አገርንም ተኩሶ እንደመምታት ነዉ ። ጠቅላይ ሚኒስትራችን የፊንላንድ finish ተማሪም ሆነዉ ኸይም heim ምን ማለት እንደሆነ አለማወቆን በሚድያ መናገርም በዉነት የፖሊቲካ አሽሙርም (political sarcasm) አለያም ደግሞ መሞዳሞድ( humor) ሊሆን አይችልም፤ ይልቅ ትዝብት ዉስጥ ነዉ የጣሎት።ጠቅላይ ሚኒስትራችን በፊኒሽ Finish ምድር የዉሃ ጥናት ትምህርቶን ሲወስዱ master ማስተር አድርገዉ የወጡት በዉሃ ላይ መንሳፈፍን ብቻ ይመስላል ለዚህም ነዉ በፖለቲካዉም ከሞራሉም አኳያ ራስዎን ሳይሆኑ እንደብርቅዬዋ የፊንላንድ ዳክዬ ተንሳፈዉ የሚታዩት the whooper swan ።

ለዚህ ርዕስ መነሻ የሆነን የሰሞኑ ትኩስ የመነጋገሪያ ኣጀንዳ የሆነዉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንጝግር ነዉ። ዋናዉ መልክታችን የሰዉየዉ የራሳቸዉን ህዝብ ማሳነሱና መዝለፉ ላይ ሳይሆን ሰዎቹ የተዘለፉበትን ምክንያቶች ላይ ትንሽ ለማለትና ምናልባትም ጠቅላይሚኒስትሩ ራሳቸዉንና ሰርዓታቸዉን ዞር ብለዉ ቢያዩበት ከሚል ነዉ።

ዛሬ በኢትዮጵያ ስለሚታየዉ የወጣት ሰቶች፣ ወጣት ዎንዶች ፣ የባለሙያ ምሁራን ስደት ዋናዉና ትልቁ ምክንያቱ የኢኮኖሚ ምኪንያት ሳይሆን ባገሪቱ ያለዉ የሰርዓት ኣልበኝነትና ስርአቱ ባመጣዉ የፖለቲካ ጫና ነዉ ።

ዛሬ ያለዉ የገዢዉ ሥርዓት በሰዉ ፍልሰት ንግድ በግልፅ በመሰማራቱና ባሰማራቸዉና ስርዓቱ በዘረጋዉ ዘመናዊ የሰዉ ንግድ ቀለበት ዉስጥ አንዲገቡ በተደረጉ ዜጎችና በተለይ ድግሞ ሆን ተብሎ በዘዴ የመሬት ንጥቂያና ዝርፊያዉ ባልተማሩና ምንም አይነት የስራ ሙያ ትምህርትና ልምድ በሌላቸዉ ሚስኪን የገበሬ ልጆች ከብቶቻቸዉን እና ያላቸዉን ጥሪት በዘዴ እንዲሸጡ እየተደረገ ገበሬዉን ያለዓምራች ሃይል እንዲሆን በማድረግና ያገሪቱን መሬት እና አንጡራ ሃብት ለዉጭ ባለሃብቶች አየተሰጠ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዉስጥ ስዉም መሬቱም እኩል እየተሸጠ እንዲሰደድ በማስገደድና የመኖሪያ ቦታ በማሳጣትም ጭምር ነዉ።

እንዲሁም ዜጋዉን መሬት አልባና አገር አልባ በማድረግ ስደተኛ የሚል ተቀፅላ ስም ዎይንም መጠሪያ እንዲሸከም በመደረጉ ነዉ። ሰደተኛ በሚያደርገዉ የሥርዓቱ ዉጤት የዜጎች ስቃይና ያለፍላጎት የተሸከሙት ስደተኛ የሚለዉን ስም ነዉ ።

ዛሬ ያንድ ኢትዮጵያዊ የስደት ጉዞዉን እና አገር ለቆ የሚወጣበትን ሚክንያቶች በቅጡ ለተገነዘበ ሰዉ ኢትዮጵያዉያኖች ባገራቸዉ ያለዉን ከባድ ስራ ንቀዉ ሳይሆን ባገራቸዉ ያለዉን ከባድ የፖለቲካ ጫና፣ አፈና፣ ግድያ፣ እስር፣ የስራ ዕጦት፣ የምግብ ርሃብ፣ እና የነፃነት ርሃብና ፣ የቁም ቅዠት የሆነዉን የኑሮ ልዩነት ሽሽት የፍትሕ አለመኖር መሆኑ ግልፅና የማያከራክር ነዉ ።

እዚም በረንጆቹ አገር ዛሬ ያበሻን ስደተኛ በለበጣ ለተሻለ ሕይዎት ስደትን የሚመርጥ የስደት ገበያተኛ የሚል ቅፅል ስም አስከማዉጣት ተደርሶአል ፤በዚሁ አገር አባባል እንደወረደ አሲል ሾፐርስ asyl kjopers ፡ በንግሊዝኛዉ አሳይለም ሾፐር ASYLUM SHOPER ማለት ነዉ ። የዚን ወገን ህዝብ እመራለሁ የሚሉ ያገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሐይለማሪያም ደሳለኝ የዶሮ ዎጥ ይዘዉ መምጣታቸዉ ካዉሮፓ ዱቄት ሰፋሪዎች ጋር ሆነዉ የራስ ወገንን ችግር እያዩ ማላገጡ የሚያስከብር ሳይሆን ራስን እሚያዋርድና ራስንም መስደብ መሆኑን ልብ ሊሉት ይገባል ።ዱቔት ሲያቦኩ እና የሰዉ መኪና ተደግፈዉ ፎቶ እሚልኩ ያልዋቸዉ ወገኖች ናቸዉ በያረብ ሃገር ፣ባዉሮፓ፣ ባሜርካ ፣ኤሲያ ሌት ተቀን እየሰሩ ባገራችን ያለዉን የዘመናት ድህነት ለመቀንስና ቢያንስ የየራሱን ቤተሰብ በመደጎም ዙሪያ በዉጭ ያለዉ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ነዉ ትልቁን የለት ተዕለት ኑሮን በመሸፈን ላይ ያለዉ እንጂ መንግስት አደለም ዜጎቹን እየደጎመና እያኖረ ያለዉ ፣ መንግስት ይልቅ በተቃራኒዉ ህዝቡን ኣዋርዶ በያገሩ እየሔዱ ልመናን ስራዬ ብሎ ተያይዞታል ።

ባሁንዋ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሬቱንና ልጁን በዘዴ ከተቀማዉ ያብዛኛዉ ማህበረሰብ ክፍል የሚገኘዉ ወጣት ስደተኛ ሴትም ሆነ ዎንድ በዓረብ ሐገራት ተበትኖ በግርድናም ይሁን በሞያ ስራ ላይ የተሰማራዉ ወገን ፡ በያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ቤተሰብና ማህረሰብ ከዛም አልፎ በዚያች አገር በተለይም የኢኮኖሚዉ ግንባታና የለት ተዕለት የህብረተሰቡ ኑሮ ዉስጥ ከፍተኛዉን ድጋፍና ተሳትፎ አያረገ ያለዉ ይኸዉ ባረብ ሐገራትና በሌላዉ ዓለም የተበተነዉ ሰደተኛ የተባለዉ ኢትዮጵያዊ ወገን ነዉ ።ይህ ደግሞ ሊያስመሰግነዉና ተበረታቶ ትክክለኛዉን የዜግነት ክብሩንና መብቱን ሊከበርለትና ዋስትና ሊኖረዉ ሲገባ ፤አሁን ያለዉ መንግስት በራስ ወገን ስቃይና ደም ፡ንግድ ዉስጥ ተገብቶ በራስ ዙሪያና ለራስ ብቻ እየተኖረ ወገንን ፡አገር አልባ አድርጎ የተበላሸ የዶሮ ወጥ ባዉሮፓና ባረብ አገር ይዞ መዞሩ ከሙቀቱ ወደ በረዶ – ከበረዶዉ ወደ ሙቀቱ ወጡን ይዘዉ ቢያጉዋጉዙ ትርፉ የዶሮ ወጡን ብቻ ሳይሆን ጠቅላይ ሚንስትራችንንም ሆነ ፖለቲካቸዉን እጅ እጅ እንዲሉ አድርጎዋቸዋል ።

ጠቅላይ ሚንስትሩ ስርዓታቸዉ ጠቅልሎ ባመጣዉ ችግር መልሰዉ ራሳቸዉ በራስ ወገን እና ዜጋ ላይ ማላገጥ አዋቂነት ሳይሆን ራስንና አገርን ማዋረድ ነው ። በጀርመን ሐገር የሚገኘዉን ‘ኸይም ‘ Heim መጠለያ ጣቢያ ሂደዉ፣ ዱቔት ሲፈጩ ባዩት ከማላገጥ የሰሩትን ዶሮ ወጥ በትኩሱ ባገር ቤት ጠርተው የበተኑትን ወገን ሊያበሉት ቢሞክሩ ምንኛ በመጠናቸዉ ፣ዶሮ ወጥ ሰርተዉ ባገሪቱ ጎዳና በየቦታዉ ለወደቁ ህፃናትና አረጋዊያን ቢያበሉ ምንኛ በመጠናቸዉ ፣የሰሩበትን ያመታት ጥሪት በገዛ አገራቸዉ በጉምሩክ ፈታሽና በግዜዉ ባለስልጣኖች የተዘረፉት ሴት እህቶቻችን በየመንገዱ ቀን ለቀን ባዶአቸዉን ግራ ገብቷቸዉ ያሉትን ፣እንደገና ዳግም ለመከራ ስደት መንገድ ላይ ያሉትን -በሰዉ ሐገር ያለዉን ከሚጎበኙ በገዛ አገሩ ሰደት ዉስጥ ያለዉን ቢጎበኙ ምንኛ መልካም ነበር።

እርግጥ ነዉ በዚ ልማታዊ መንግስት ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ የፈረንሳይ የታሸገ የመአድን የተጣራ ዉሃ french evian mineral water ገዝቶ የሚጠጣ ባለግዜ የደሃ ሃገር ቡርዥዋ እንዳለ ሁሉ ከቆሻሻ ገንዳ ከዉሻ ጋር እየተጋፋ በተራቡ እና በደከሙ ጣቶች የቁሻሻ ገንዳ ዉስጥ ሲቆፍሩ የሚዉሉም አሉ ፤ይኼንን ሃይማኖተኛዉና ፖለቲከኛዉ ጠቅላይ ሚንስትራችን ምናልባት ከየትኛዉ የስራ ዘርፍ ዉስጥ እንደመደቡት ባናውቅም ዛሬ ያ ሚስኪን ወገን ወስፋቱን መዝጊያ ለማግኘት ፡ከጠዋት እስከማታ ከተራቡ ዉሾች ጋር መከራዉን ሲቆፍረዉ እየኖረዉ ነው ፣ ጠቅላይ ሚንስትራችን ሰደተኛዉን ባገሪቱ ዉስጥ ያለዉን ከባድ ስራ ሸሸተዉ የወጡ ብለዉናል ፤ እንዴት አይሸሽ ከባዱስ ስራ የትኛዉ ይሆን?? ለጠቅላይ ሚንስትራችን ፣ ሰዉ ተሰልፎ በቁሙ ለጉርሻ ትርፍራፊ ምግብ ባደባባይ ሲሰለፍ ፣ ህፃናት በጎዳናና በመማሪያ ክፍል መሃል ከተማ ዉስጥ እየተራቡ ፣ ወገን በቁሙ በየበረሃው በቁሙ እየተበለተ፣ ወገን በየሃይቁ እንደሳርዲን ታጭቆ ፡ በመጨረሻም እንደ ጉማሬ ተነፍተዉ ዉሃ አንሳፎ እየተፋቸዉ በመላዉ ዓለም እየታየ፣ እንደዕባብ በሰዉ አገር እየተቀጠቀጡ ፣ እንደዓሳ በዘይት ፊታቸዉ እየተጠበሰ ፣ በጠራራ ፀሃይ መህል ከተማ ዉስጥ ወጣት ሴት ልጅ በግፍ ተድፍራ ስትገደል ሴቶች እንዴት ሸሽተዉ አይሰደዱ ?? ተነግሮ የማያልቀዉን መከራና ስቃይ ሲጋት እሚኖረዉ በዝቶ እያለ፣ጠቅላይ ሚንስትራችን ይሔን የማህበራዊና የኢኮኖሚ የፖለቲካ ቀዉስ ስደተኛዉ ላይ ደፍድፈዉ በራስ ጥጋብና ምርጫ ህዝቡ እንዳመጣዉ ተደርጎ መዘባበት ትናንት እንደተባለዉ ከርስዎ በፊት በነበሩት ጠቅላይ ሚንስትር ስለድርጀቶ የተነገረዉን መንቀዝና የፖለቲካ የመጨረሻዉ ብስባሴ ባንድ ዎቅት አሰምተዉን ነበር አሁን ማን ይንገረን ? ?

ከሞራልም አኳያ ቢሆን በየትኛዉም የዕምነት መፅሐፍ ቅዱስ ዉስጥ እንዲህ አይነቱን ስብዕናና ክፋት – በሀይማኖት የቅዱስ መፅሐፎቻቸዉ መገሠጭያውንም ማስተማሪያዉንም ከትበዉ ይዘዋል ፤ያን ላንባቢያን እንደምርጫቸዉ ስንተወዉ ለሞራልና ለግብረግብ እንዲሁም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የዕምነት አባቶች ግን የሳቸዉን አነጋገርና ትዕቢት ክፍተቱን ከሞራልና ከክርስትና አኳያ እንዴት እንደሚሞሉት በማስተዋል እንጠብቃለን ፣ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስ ከሆነም ከነማብራሪያቸዉ እንጠብቃለን።

ጠቅላይ ሚኒስትራችን እንዴት እንደሚረዱትና እንደሚያዩት ባናውቅም ዛሬ ያለዉ ሃበሻ ኢትዮጵያዊ ባሜሪካም ሆነ ባዉሮፓ ያለዉ ሂስፓኒክ አደለም ፣ዛሬ ባረብ አገር ያለዉ ሃበሻ- ኢትዮጵያዊ ፡ ይሁዲ አዶለም ይሔንን እሳቸዉ ተምረዉ ባደጉበት የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ትምህርት የህዝብ የራስ ወገንን ክፍተኛ ፍልሰት exodus ለያይተዉ ማየት አለመቻላቸዉ ምናልባትም ያገዛዙ ዋና ኤሊትሶች ፈረንጆቹ horse hood ሆርሰ ሁድ የሚሉትን ለሳቸዉም ባንገታቸዉ አጥልቀዉላቸዉ ይሆን ? እንዲህ ግራ ቀኙን እንዳያዩ አድርገዉ እሚጋልቧቸዉ? ፣እጅ- እጅ ብሎ እጅ- እጅ ካለ የዶሮ ዎጥ ጋር ዝም ብሎ መጋለብ ፣ አሳፋሪም አስነዋሪም ነዉ።

ተፃፈ – ስለ- ክብር፤ ለመላዉ ስደተኛ ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲሁም በህይዎት ለሌሉ እና ባገራቸዉም ካገራቸዉ ዉጭ በግፍ ላለቁ ሁሉ።

ከምንም በላይ ግን ያኔ ከመነሻው ለአገር እና ለህዝብ የሚጠቅም ፓርቲ እንመስርት ብለን፣ገንዘባችን፣ ጊዜያችን፣ እውቀታችን ሳንሰስት በመስጠት፤በወቅቱ ፓርቲ እንመስርት ማለታችን ትክክል እንደነበር የዛሬ ውጤታችን ምስክር ነው !
—————————- YIDNEKACHEW KEBEDE ——————————————
ሰማያዊ ፓርቲ ከተመሰረተ አሁን ሦስተኛ ዓመቱ ነው፣የአገራችን አሉታዊ እና አዎንታዊ ፖሊቲካ ድርጊቶችና ክስተቶችን በመመርመር የመፍትሔ አካል ለመሆን በአገር ወዳድ ኢትየጵያዊያን ታህሳስ 22/2004 ዓ.ም በይፋ ተመሰረተ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በእውነት እና በእውቀት ላይ የተመሠረተ ሰላማዊ ትግል በማድረግ ፣የዜጎች የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ አባላቱ እና ደጋፊዎችሁ እያሣየነው ያለው ቁርጠኝነት እና ታማኝነት ለፓርቲያችን ጥንካሪ ዋንኛ መሠረት ነው፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ከምስረታው ጀምሮ ያስመዘገባቸው አኩሪ ድሎች፣ በአገራችን እየተንቀሳቀሱ ከሚገኙ ቁጥራቸው ከበዛ ፓርቲዎች ተርታ፣ በግንባር ቀደምትነት ከሚጠሩ አንዱ ለመሆነ ችሎአል፡፡ፓርቲያችን ከተመሠተር እና ወደ እንቅስቃሴ ከገባ አጭር ጊዜ ቢሆነውም ፣በኢትዮጵያዊያን ካለው ተቀባይነት እና በገዥው መንግስት ላይ እያሣደረ ያለው አስጨናቂ ተፅኖ በመመልከት አንዳንድ ታዛቢዎች ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ ? በማለት ይጠይቃሉ፣ መልሱ ግን አጭር ነው፡፡ እሱም ጠንከራ ጓዳዊ ትስስር ፣ጥልቅ የሆነ የአገር ፍቅር ስሜት፣ለዓላማ መሞት፣ በእውቀት እና በእውነት ላይ የተመሰረት ሰላማዊ ትግል ተግባሪዊ ማድረግ ፣ለፓርቲያችን ውጤት የአንበሳውን ድርሻ ይይዛል፡፡
ይህ ማለት ግን ፓርቲያችን ሊደርስበት ካሰበው ደረጃ እጅግ በጣም ትንሽ መሆኑ ሁላችንም የምንረዳው ሃቅ ነው፡፡ የሁላችንም የጋራ ዓላማ፣ ህዝብ የአገሩና የሥልጣን ባለቤትነቱ እንዲረጋገጥ ማድረገግ ነው ! ይህን ለማሳካት አሁን ላይ ፓርቲያችን ያስመዘገበው ድል የዋናው ትግላችን ውጤት ማሣያ መለኪያ እንጂ ፍፃሜ አይደለም፡፡ እርግጥ ነው ከትግሉ ጅምሮ አንስቶ የጠልፎ መጣል የተለመደው አዙሪት ፓለቲካ፣ ፓርቲያችን ፈተና ውስጥ የከተተው ቢሆንም በአመራሩ ጠንካራ ውሳኔ ከገጠመው ፈተና በብቃት ለመወጣት የተቻለው ሲሆን፣ወደፊትም እንዲኸ ዓይነቱ ክስተት እንዴት መወጣት እንዳለበት ት/ት ያገኘበትም መልካም አጋጣሚ ጭምር ነው፡፡
ፓርቲያችን ከሌሎች በአገር ውስጥ ከሚንቀሣቀሱ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር በመተባበር መጪው አገር አቀፍ ምርጫ 2007፣ ፍታሓዊ እና ዲሞክራሳዊ እንዲሆን ጠንክሮ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን፣በ2005 ዓ.ም ሊካሄድ ታስቦ የነበረ የአካባቢ ምርጫ፣ ገዥው መንግስት በቻውን ተወዳድሮ ብቻውን ያሸነፈበት የይስሙላ ምርጫ መሆኑን የ33 ፓርቲዎች ጠንካራ ትብብር ያስገኘው ውጤት ነው ! የዚህም ውጤት ባለቤት ከሆኑ ፓርቲዎች ውስጥ ሰማያዊ ከዋናዎቹ አንዱ ነው፡፡አሁንም ወደፊትም ለአገር እና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ፓርቲያችን በጥናት ላይ የተደገፈ ከእውነተኛ የዲሞክራሲ ኃይሎች ጋር የሚያደርጋቸው ማናቸውም ዓይነት ግንኙነት በፓርቲያችን ደንብ መሠረት ገደብ የተጣለበት አይደለም፡፡
ገዥው መንግስት የፓርቲያችንን ጥንካሪ በአግባቡ በመረዳት፣በምናደርጋቸው ሰላማዊ ትግል ምክንያት በመፍጠር በተደጋጋሚ ከሚወስዳቸው የእስራት እና ደብዳባ እርምጃ ባለፈ ፓርቲያችንን ለማፍረስ በግልፅ እና በስውር እየተነቀሣቀሰ ይገኛል፡፡ከዚህም በላይ የፓርቲያችን ሰላማዊ ተጋይ አቶ የሺዋስ አሰፋ ከአ/አ፣ አቶ በፍቃዱ አበበ ከአርባምንጭ እና አቶ አግባው ሰጠኝ ከሰሜን ጎንደር በሽብርተኝነት ከሱ እያሰቃያቸው ይገኛሉ፡፡ይሁን እንጂ የጀመረነው ሰላማዊ ትግል ከዚህም በላይ ዋጋ እንደሚያስከፍል ቀድመን የተረዳነው ስለሆነ ወደፊት እንጂ ወደ-ኋላ ማለት በእኛ ዘንድ ነውር መሆኑ ጠንቅቀን እናውቃለን !
ፓርቲያችን ባሣለፈው ሦስት ዓመታ ውስጥ የገጠመው ውስጣዊ እና ውጫዊ ችግሮች ማንኛወም ጠንካራ ፓርቲ ሊገጥመው ከሚችለው የተለይ ነገር አይደለም ፡፡ሆኖም ግን ያጋጠሙት ችግሮች ለመፍታት የተሄደበት መንግድ ማንኛውም ፓርቲ እና የፓርቲ አባላት ከሚሄዱበት በአንፃራዊ እጅግ በጣም የተሻለ ነበር ፡፡አሁንም ወደፊትም ችግሮች መኖራቸው የማይቀር መሆኑ ታሣቢ በማድረግ፣ የፓርቲው አባል የሆን ጥልቅና ዝርዝር ውይይት በግልፅ በማካሄድ ክፍተቶቻችን እንደምንሞላ ተስፋ አድርጋለው፡፡
ከምንም በላይ ግን ያኔ ገና ከመነሻው ለአገር እና ለህዝብ የሚጠቅም ፓርቲ እንመስርት ብለን፣ገንዘባችን፣ ጊዜያችን፣ እውቀታችን ሳንሰስት በመስጠት፤በወቅቱ ፓርቲ እንመስርት ማለታችን ትክክል እንደነበር የዛሬ ውጤታችን ምስክር ነው !ለዚህም በመብቃታችን መስራች አባላት ለሆን እንኳን ደስ አለን፣አላችሁ! ለማለት እወዳለው፡፡
የጀመራችሁት አገር የማዳን ትግል የእናተ የመስራቾች ብቻ ሳይሆን የእኛም ጭምር ነው !በማለት ከፓርቲው ምስረታ ጀምሮ እስካሁን ሰማያዊን በመቀላቀል በአመራርነት እና በአባልነት በማገልገል ፣አኩሪ የትግል መሰዋትነት እየከፈላችሁ ለምትገኙ ለገዥው ለወያኔ መንግስት የእግር እሳት ለሆናችሁ የእኔ ትውልድ ጓዶች እንኳን አደረሳችሁ !
ፓርቲያችን አሁን ላይ ያለበት ደረጃ እንዲደርስ በአሳብ እና በገንዘብ እየረዳችሁ ለምትገኙ በአገር ውስጥ እና በውጪ የምትገኙ ድጋፍ ሰጪዎቻችን ፣ድካማችሁ ፍሬ እያፈረ በመሆኑ የሚሰማችሁ ደስታ ለተጫማሪ ድጋፍ እንደሚነሳሳችሁ ተስፋዬ የበዛ ነው !ከምንም በላይ ግን ሁሌም ለማይለይን የሃሳብ እና የገንዘብ ድጋፋችሁ አገራዊ ግዴታችሁ ቢሆንም፣ በቀናነት እና በአገር ወዳድነት ለምታደርጉት ድጋፍ ምስጋና ተገቢ ነው፡፡ምስጋናውን ከአክብሮት ጋር እንድትቀበሉ በመጠየቅ ፣ለዚህ በመብቃታችን እንኳን አደረስን በማላት የ3ኛ ዓመት የእንኳን አደረስን የግል መልእክቴን በዚህ አጠቃልላለው፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !
Image

Image
ከ26 ዓመታት በፊት የደርግ መንግሥት በትግራይ ክልል በሐውዜን ሕዝብ ላይ ያካሄደው የአውሮፕላን ድብደባ በስተጀርባ የእሥራኤል መንግሥት እጅ እንዳለበት የቀድሞ የህወሓት ሊቀመንበር አቶ ስብሃት ነጋ ይፋ አደረጉ።
አቶ ስብሃት ይህን የገለፁት በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የደርግ 604 ኮር የተደመሰሰበትን የወታደራዊ ሳይንስ ጥበብ አስመልክቶ ሰሞኑን በሽሬ ከተማ በተሰናዳ የውይይት መድረክ ላይ ነው።
አቦይ ስብሃት ሲያስረዱ፣ “የቀዝቃዛው ጦርነት ማክተምን ተከትሎ ታላቋ ሶቪየት ሕብረት መፈራረስ ጀመረች። ይህን ክስተት ተከትሎ ሶቪየት ሕብረት ከኢትዮጵያ እየወጣች መጣች። በእሷ እግር የተተካውም የሩሲያ ፌዴሬሽን ለደርግ አገዛዝ ከዚህ በፊት ይደረግ የነበረውን ወታደራዊ እርዳታ አቋረጠ። ይህን ዓለም ዓቀፍ የፖለቲካ ዳይናሚዝም ተከትሎ አሜሪካ መራሹ የምዕራብ ዓለም እና የእሥራኤል መንግስት ከደርግ ጋር ወዳጅ ሆኑ። የደርግ አገዛዝን መውደቅን ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን የጂኦ-ፖለቲካል ኃይል አሰላለፍ በመፍራት የምዕራቡ ዓለምና እሥራኤል ደርግን ወዳጅ አድርገው በእኛ የትግል እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ እርምጃዎች መውሰድ ጀመሩ” ብለዋል።
አያይዘውም፣ “በወቅቱ ሕወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅሙ እየጠነከረ እየመጣ በመሆኑ አሜሪካና እሥራኤል ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብተዋል። የአዲስ አበባው መንግስት ወዳጅ ስለሆኑ እንዴት ከተጀመረው የትጥቅ ትግል ሊያድኑት እንደሚችሉ ብዙ መንገዶችን ሞክረዋል። በጊዜው ደርግን ለማትረፍ ያልሞከረ የምዕራብ ሀገር አልነበረም። ሁሉም የሚችለውን አድርጓል። አሜሪካ ለማደራደር ስትሞክር እሥራኤል ግን የተለየ ሚና ወሰደች” ሲሉ ወንጅለዋል።
“አሜሪካ አንዴ ወደ ሮማ ሌላ ጊዜ ወደ ለንደን እንድንመጣ ጠራችን። ሮማ ላይ ጂሚ ካርተር አስጠርቶን የነበረ ቢሆንም፣ የደርግ ልዑካን ቡድን እናንተ ስለኢትዮጵያ ምን ያገባችኋል አሉን። ወደ ለንደን ተጠርተን ስንሄድ ግን ሁሉን ነገር ስለጨረስን ደርግን ጥለን ነበር” ብለዋል።
እስራኤል ግን ወደ ሮማ ከመሄዳችን በፊት፣ ደርግን በጦር መሳሪያ በማስታጠቅ ጀምራለች። ደርግ የታጠቀውን የክላስተር ቦምብ እ.ኤ.አ ጁን 22 ቀን 1988 ሐውዜን በገበያ ቀን ህዝቡ ላይ አዘነበው። በጥቃቱም ከ2ሺ 500 በላይ ህዝብ ማለቁን ተናግረዋል። አያይዘውም፤ “ይህ ሁሉ የህዝብ ዕልቂት በእሥራኤል አስታጣቂነት የተፈጸመ ነበር” ሲሉ አቦይ ስብሃት ለተሰብሳቢው በሃዘን ተውጠው አስረድተዋል።
የቀድሞ የደርግ መንግሥት ርዕሰ ብሔር የነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማሪያም ወደ ዙምባቡዌ የሸሹት በምዕራብ ሀገሮች ድጋፍ መሆኑ ሲነገር ነበር። ኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማሪያም በኢትዮጵያ ፍርድ ቤት በዘር ማጥፋት ወንጀል የሞት ፍርድ ቢተላለፍባቸውም አንዳቸውም የምዕራቡ ሀገራት የዙምባቡዌ መንግስት አሳልፎ እንዲሰጥ ግፊት አድርገው አያውቁም።
በ ፋኑኤል ክንፉ – www.sendeknewspaper.com

Image

የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለይም ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹በሰላማዊ ሰልፍ ስም የህብረተሰቡን ሰላም ለማደፍረስ እያደረገ የሚገኘውን እንቅስቃሴ በተመለከተ›› መረጃ እንዲሰጡት ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች ቅጽ እያከፋፈለ መሆኑ ታወቀ፡፡

ምንም እንኳ በቅጹ ላይ ዜጎች ስለ ሰማያዊ ‹‹ጥሩና መጥፎ›› አስተያየት እንዲሰጡ ቢልም መጀመሪያ ላይ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በሰላማዊ ሰልፍ ስም የህብረተሰቡን ሰላም ለማደፍረስ እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ በተመለከተ›› ሲል ፓርቲው የህዝብን ሰላም እያደፈረሰ ነው ሲል ፈርጆታል፡፡

ቅጹ ከተሰጣቸው መካከልም አንድ የኮልፌ ቀራኒዮ ነዋሪ ቅጹን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቀው ሲል ለኢትዮ ምህዳር የላከ ሲሆን ‹‹ይህንን አስገራሚ ቅጽ እንድንሞላ በአንድ ክ/ከተማ በተገኘንበት ስብሰባ ላይ ለተሰብሳቢው ሁሉ ታደለ፡፡ ታዲያ ሁሉም ቅጹን ወስዶ ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ እኔም የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቀው ለጋዜጣችሁ ዝግጅት ክፍል ልኬዋለሁ፡፡ አይገርምም ሕገ-መንግስት የሚፈቅደው ሰላማዊ ሰልፍ አንቀጽ በመንግስት አስፈጻሚዎች ሲጣስ›› በሚል አስተያየታቸውን አስፍረዋል፡፡

አርማጮ በአማራ ንቅናቄ ሰራዊት እና በወያኔ ሰራዊት በውጊያ ተወጥራለች::
Image

Minilik Salsawi : በአርማጮ አከባቢ በአማራ ንቅናቄ ሰራዊት እና በወያኔ ሰራዊት መካከል ከባድ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑን የንቅናቄው ምንጮች ከአከባቢው አስታወቁ::የህዝቡ ተሳትፎ በከፍተኛ ደረጃ እየታየ ባለበት እና ህዝቡ እና የንቅናቄው ወታደሮች በመቀናጀት ዱር ቤቴ ብለው ወደ ጫካ መግባታቸው ሲታወቅ በመተማ ሸዲ አከባቢ በትላንትናው እለት በወያኔው ጦር ላይ ጥቃት አድርሶ ወደቦታው የተመለሰው የአማራ ንቅናቄ ሰራዊት ከሕዝቡ ጋር በመተባበር እጅግ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እንደማረከ ምንጮቹ ተናግረዋል::

ካለፈው አርብ ጀምሮ የተነሳው ውጊያ በአሁን ወቅት ቀጥሎ ያለ ሲሆን በዛሬው ለሊት ከፍተኛ የቶክስ እሩምታዎች እና የከባድ መሳሪያ ድምጾች በአከባቢው እየተሰሙ መሆኑ ታውቋል::በአብድራፊ አብሃጂራ ሶረቃ ግጨው ማርዘነብ ማይጸማር ሃሙስ ገበያ ዳንሻ ማይካድራ እና አከባቢው ጦርነቱ ይስፋፋባቸዋል የሚል ከፍተኛ ስጋት ስላደረ በአከባቢው የወያኔ ሰራዊቶች በብዛት መስፈራቸው ሲታወቅ አዳዲስ ታንኮችን የጫኑ ከባባድ መኪኖች በቦታው ደርሰዋል:: እንዲሁን ወደ ሱዳን ክልል ዘልቀው የገቡ እና ከሱዳን ወታደሮች ጋር አሰሳ የሚያደርጉ ወያኔዎችን እንዳጠቁ የአማራው ንቅናቄ ወታደሮች ተናግረዋል::

በአርማጮ እና አከባቢው የተከሰተውን ግጭት በተመለከተ የአማራ ንቅናቄ ሰራዊት መግለጫ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል::

(ፋኑኤል ክንፉ) ከ26 ዓመታት በፊት የደርግ መንግሥት በትግራይ ክልል በሐውዜን ሕዝብ ላይ ያካሄደው የአውሮፕላን ድብደባ በስተጀርባ የእሥራኤል መንግሥት እጅ እንዳለበት የቀድሞ የህወሓት ሊቀመንበር አቶ ስብሃት ነጋ ይፋ አደረጉ። አቶ ስብሃት ይህን የገለፁት በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የደርግ 604 ኮር የተደመሰሰበትን የወታደራዊ ሳይንስ ጥበብ አስመልክቶ ሰሞኑን በሽረ ከተማ በተሰናዳ የውይይት መድረክ ላይ ነው። አቦይ ስብሃት ሲያስረዱ፣ “የቀዝቃዛው ጦርነት ማክተምን ተከትሎ ታላቋ ሶቪየት ሕብረት መፈራረስ ጀመረች። ይህን ክስተት ተከትሎ ሶቪየት ሕብረት ከኢትዮጵያ እየወጣች መጣች። በእሷ እግር የተተካውም የሩሲያ ፌዴሬሽን ለደርግ አገዛዝ ከዚህ በፊት ይደረግ የነበረውን ወታደራዊ እርዳታ አቋረጠ። ይህን ዓለም ዓቀፍ የፖለቲካ ዳይናሚዝም ተከትሎ አሜሪካ መራሹ የምዕራብ ዓለም እና የእሥራኤል መንግስት ከደርግ ጋር ወዳጅ ሆኑ። የደርግ አገዛዝን መውደቅን ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን የጂኦ-ፖለቲካል ኃይል አሰላለፍ በመፍራት የምዕራቡ ዓለምና እሥራኤል  ደርግን ወዳጅ አድርገው በእኛ የትግል እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ እርምጃዎች መውሰድ ጀመሩ” ብለዋል። አያይዘውም፣ “በወቅቱ ሕወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅሙ እየጠነከረ እየመጣ በመሆኑ አሜሪካና እሥራኤል ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብተዋል። የአዲስ አበባው መንግስት ወዳጅ ስለሆኑ እንዴት ከተጀመረው የትጥቅ ትግል ሊያድኑት እንደሚችሉ ብዙ መንገዶችን ሞክረዋል። በጊዜው ደርግን ለማትረፍ ያልሞከረ የምዕራብ ሀገር አልነበረም። ሁሉም የሚችለውን አድርጓል። አሜሪካ ለማደራደር ስትሞክር እሥራኤል ግን የተለየ ሚና ወሰደች” ሲሉ ወንጅለዋል። “አሜሪካ አንዴ ወደ ሮማ ሌላ ጊዜ ወደ ለንደን እንድንመጣ ጠራችን።  ሮማ ላይ ጂሚ ካርተር አስጠርቶን የነበረ ቢሆንም፣ የደርግ ልዑካን ቡድን እናንተ ስለኢትዮጵያ ምን […]

በመጪው የካቲት ከሚከበረውን የህወሓት 40ኛ አመት የልደት በዓል ይከበራል፡፡ ከበዐሉ አከባበር ዝግጅት አንዱ የሆነው፤ ከትጥቅ ትግሉን ዋነኛ ሥፍራዎች የተወሰኑት ከታህሳስ 13 -16 ቀን 2007 በታዋቂ አርቲስቶች እና ጋዜጠኞች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡ ጉብኝቱ የተጀመረው በደደቢት ሲሆን፣ በዚያው ቦታ ላይ በተዘጋጀ ግዜያዊ የሣር ዳስ ውስጥ ገለጻ ተሰጥቶ ነበር፡፡ በዕለቱ ተናጋሪ የነበሩት የህወሓት መሥራቾች አባይ ፀሐዬ፣ ስብሐት ነጋ፣ ስዩም መስፍን እና አቦይ ካህሳይ እንዲሁም የብአዴን መሥራች በረከት ስምዖን ነበሩ፡፡ የገለጻቸውን ቅጂ ከታች ካለው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ፡፡ —— *********** More from Horn Affairs AmharicAudio | በኦሮሞ ተማሪዎች ስለተካሄዱት ተቃውሞዎች የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ዘገባAudio| የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ አመራር በአዲሱ ማስተር ፕላን ላይ የሰጡት መግለጫAudio| ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ በመቐለ ያደረጉት ንግግርበደቡብ ሱዳን ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስታቸው እንዲታደጋቸው ይሻሉሚኒስትር ሽፈራው:- በቅርቡ ለሚመረቀው ተንዳሆ ስኳር መዘግየት ህንዶችን ወቀሱዓባይ ወልዱ፡- ህወሓትን ለድል ያበቃው የውጭና የሌሎች ድጋፍ ሳይሆን የጠራ ሕዝባዊ መስመር ነው

ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ ነው

• ‹‹ኢህአዴግ አይገዛንም!›› ተማሪዎቹ
ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ የደብረማርቆስ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (መሰናዶ) ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡

ተማሪዎቹ በትናንትናው ዕለት ኢህአዴግን የሚተቹ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በማንሳታቸው ይሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ ወጥተው 20፣ 20 ሆነው በጠባብ ክፍል እንዲሰለጥኑ ከመደረጉም ባሻገር ጥያቄ የሚያነሱት ላይ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ዛሬ ጠዋት ጥያቄ ያነሳሉ የተባሉት ተማሪዎች ስልጠና ወደሚሰጡባቸው ትምህርት ቤቶች ግቢ እንዳይገቡ ከመደረጉም ባሻገር የድብዛ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ስልጠናውን መቃወማቸውን ተከትሎ ፖሊስ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሰሙ የተክለሀይማኖት መልስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እርምጃውን በመቃወም ለድብዛ ተማሪዎች ድጋፍ መስጠታቸው ተገልጾአል፡፡

የሁለቱም ትምህርት ቤት ተማሪዎች በጋር በመሆን ከተማው አደባባይ ላይ በመውጣት ‹‹አህአዴግ አይገዛንም፣ ኢህአዴግ ሌባ፣…›› የመሳሰሉ መፈክሮችን በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለጻቸውን ተከትሎም ፖሊስ ተማሪዎቹን እያፈሰ ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዱ ተሰምቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ጥያቄ የሚጠይቁና ፖሊስ ተቃውሞውን አደራጅተዋል ብሎ የሚጠረጥራቸውን ተማሪዎች እየፈለገ እያሰረ መሆኑን ተማሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን በ17ቱም ወረዳዎች የሚገኙ ተማሪዎች ስልጠናውን ካልወሰዱ ከትምህርት ቤት እንደሚባረሩና ፈተና ላይ እንደማይቀመጡ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ስልጠናውን መቃወማቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡

ለውጡ ይመጣል! ጥያቄው ግን ተዘጋጅተናል ወይ? ነው፡፡
————————————————-
ስለ 1966ቱ ለውጥ ብዙ ተብሏል፡፡ በለውጡ ወቅት የነበሩትን ሰዎችም ሆነ ሌሎቹን የሚያስማማ አንድ ነገር ቢኖር የለውጡ ግብታዊነት እና ለውጡን ሊሸከም የሚችል ድርጅት በወቅቱ አለመኖሩ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ቆመን ለውጡ ገና ነው ብለን ብንዘናጋ እንደ ኃይሌ ፊዳ ልንሳሳት የምችልባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ይመስሉኛል (ሀይሌ ፊዳ ከብርሀነ መስቀል ጋር ባደረጉት ውይይት ለውጡ ገና ነው ብዙ አመታትንም ይፈልጋል ብሎ ነበረ)፡፡ ከዚያ ይልቅ ለውጡን ለመቀበል በሚያስችል ተክለ ሰውነት ላይ ለመገኘት ምን እናድርግ የሚለው ላይ መዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡

ብዙዎች በመኢሶን እና በኢህአፓ መካከል የነበረው ልዩነት ያለፈውን ትውልድ ዋጋ እንዳስከፈለው ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ አንዳንዶች የሁለቱ ልዩነት የእናቸንፋለን እና የእናሸንፋለን የቃላት ጨዋታ ነበረ ሲሉ በሚያነሱት ሀሳብ ባልስማማም (ልዩነታቸው መሰረታዊ ነበር ብዬ ስለማምን) የሁለቱ ልዩነት ግን ትውልዱን ዋጋ ማስከፈሉን የማይቀበል ማንም ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡

ስለሁለቱ ልዩነት ሲነሳ ቢያንስ በሁለት ወቅቶች ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡
የመጀመሪያው ከለውጡ በፊት የነበረው እና ከለውጡም በኋላ እስከተወሰነ ድረስ አብሮ የዘለቀው የሁለቱ ፓርቲዎች የመደጋገፍ ጊዜ ነው፡፡ በአልጀርስ የነበረው የኢህአድ/ኢህአፓ መስራች ቡድን ከሀይሌ ፊዳው የመኢሶን መስራች ቡድን ጋር በአንዳንድ ነጥቦች ሳይስማሙ ቢለያዩም ልዩነታቸው ሰፊ የሚባል አልነበረም፡፡ ለዚህም ማሳያው የኢህአፓ ልሳን የነበረችው የዴሞክራሲያ የመጀመሪያ ዕትሞች እና የመኢሶን ልሳን የነበረችው የሰፊው ህዝብ ድምፅ ጋዜጣ የመጀመሪያ ዕትሞች በይዘት መመሳሰል እና በሀሳብ መደጋገፍ ነው፡፡ ይህ ሂደት እነ ሀይሌ ፊዳ ከውጪ ወደ ሀገር ቤት እስኪገቡ ድረስ የቀጠለ እንደነበርም ታሪክ መዝግቦ ያስቀመጠው ሀቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ወቅት ደግሞ ለውጡ ከመጣ በኋላና እነ ሀይሌ ፊዳ ሀገር ቤት ከገቡ በኋላ ያለው እና በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለው ልዩነት መሰረታዊ እየሆነ የሄደበት እና በጣም የተለጠጠበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ወቅት በመኢሶን እና በኢህአፓ አመራሮች መካከል ግንኑነት ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም (ለአብነትም ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ከዶ/ር ሀይሌ ፊዳ ጋር፤ ነገደ ጎበዜ ከአለማየሁ ሀይሌ(ደርግ ውስጥ ሰርጎ የገባ የኢህአፓ ሰው ነው ይባል ነበር) ጋር ተገናኝተው አውርተዋል) ከረፈደ በኋላ የተደረገ ውይይት በመሆኑ ያመጣው ለውጥ አልነበረም፡፡

በእኔ እይታ ለሁለቱ ድርጅቶች አለመስማማት አቢዩ ምክንያት ከለውጡ በኋላ ኢህአፓ ሰፊ ህዝባዊ መሰረት (ማስ ቤዝ) ማግኘቱ በመኢሶን በኩል ለደርግ ሂሳዊ ድጋፍ እየሰጡ መቀጠል ይሻላል ወደሚለው ሀሳብ እንዲሄዱ የገፋቸው ይመስለኛል፡፡ ከመነሻው የነበራቸውን አነስተኛ ልዩነት አጥብበው በጋራ ቢሄዱ ኖሮ አንዳቸው ተለይቶ ህዝባዊ መሰረት የሚገነባበት እና ሌላኛቸው ህዝባዊ መሰረት ለመያዝ ከወታደሩ ጋር የሚሰለፍበት ሁናቴ አይኖርም ነበር፡፡

ለማንኛውም ይህን ያነሳሁት በታሪኩ ላይ ለመነታረክ ሳይሆን ዛሬም ከታሪክ ሳንማር ያለፈውን ስሀተት እንዳንደግም ካለኝ ፍርሀት ነው፡፡
ዛሬ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለይም ሰማያዊ እና አንድነት በጋራ ሆነው ለሚመጣው ለውጥ ራሳቸውን ካላዘጋጁ በስተቀር ከለውጡ በኋላ ልዩነታቸውን አጥብበው ለውጡ ተፈጥሯዊ ይዘቱን ጠብቆ ለሀገር በሚጠቅም መልኩ ለማስቀጠል ይችላሉ ማለት ዘበት ነው፡፡ ልዩነታቸውን አሁን ላይ ማጥበብ እና በጋራ መቆም ካልቻሉ ከለውጡ በኋላ እንደ ጠላት የሚተያዩበትም እድል እጅግ በጣም የሰፋ ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በተለይም ደግሞ ለውጡን ተከትሎ ከሁለት አንዳቸው ከፍ ያለ መስዋዕትነት የከፈሉ እንደሆነ፡፡

የተቃዋሚዎች በአንድ መቆም ለለውጡ ተዘጋጅቶ ለመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለውጡን ለማምጣትም የተሻለው እና አጭሩ መንገድ ነውና የየፓርቲዎቹ አመራሮች(በተለይም የሰማያዊ እና የአንድነት) ዛሬ ነገ ሳይሉ ቁጭ ብለው በመነጋገር ወደ አንድ የሚመጡበትን እና በጋራ ህዝቡን የሚያታግሉበትን መንገድ እንዲፈጥሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ ፡፡
Image

በደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ መረር ያለ ተቃውሞ ተነስተዋል::
በጎጃም የመሰናዶ ተማሪዎች የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሙ አሰሙ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሁሉም ትምህርት ቤቶች የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቁመው እንዲወስዱ የተደረገውን የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ምንጮን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ወቅት የህዝቡ አስተሳሰብ፣ የግል ሚዲያ፣ ተቃዋሚዎች ለኢትዮጵያ እድገት ጠንቅ ተደርገው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎች ይህንን አቀራረብ ተቃውመውታል፡፡ በአንጻሩ ከወራት በፊት ስልጠናውን የወሰዱት መምህራንም ዳግመኛ ስልጠናውን እንዲወስዱ ተደርገዋል እየጠደረጉ ሲሆን ዝምታን መምረጣቸው ተገልጾአል፡፡

ተማሪዎቹ ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ ከሆነ ለተቃዋሚዎችም ይፈቀድ፣ ለምን ለግጭት የሚጋብዙ ቅስቀሳ ትቀሰቅሳላችሁ፣ የኢህአዴግ ፖሊሲ ምሁራንንም ጭምር ለስደት የዳረገ ነው፣ ከቻይና እና ከኮሪያ የሚያስተሳስረን የታሪክም ሆነ የባህል መሰረት የለንም፣ ኢህአዴግ 23 አመት ያልተገበረውን ዴሞክራሲ ሊያስተምረን አይችልም›› የሚሉ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡

በስልጠናው ወቅት ተቃውሞዎች እየተነሱ ሲሆን በተለይም ደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ ላይ ተማሪዎቹ ‹‹ኢህአዴግ ሌላ፣ ኢህአዴግ ሌባ›› የሚል ጩኸት በማሰማታቸው ሲሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ 20፣ 20 ሆነው በየክፍሉ እንዲሰለጥኑ ተደርገዋል፡፡ በተለይ በደብረማርቆስ ከተማ በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹ የካድሬ ስልጠና አንሰለጥንም በማለት መረር ያለ ተቃውሞ እያሰሙ እንደሚገኙ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡
የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአንተርኔት ድረገጾች ፈቃድ ማውጣት የግድ መሆኑን ደንግጎአል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል የመረጃ መረብ አማካኝነት ለስርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ፕሮግራም በአገር አንድነትና ሉአላዊነት ላይ አደጋ የሚጥል ፣በአገር ደህንነት፣ ክብርና ጥቅም ላይ ጉዳት የሚያደርስ ፣የአገር ሚስጢርን የሚገልጽ ፣ አመጽና ጦርነትን የሚቀሰቅስ፣ የሰው ልጆችን ስብዕና ፣ነጻነት ወይንም ስነምግባር የሚጻረር ፣የሌሎችን እምነት የሚያንኳስስ መሆን እንደሌለበት ደንግጎአል፡፡
በተጨማሪም ሥራዎቹ ማንኛውንም የህብረሰተብ ክፍል፣ ብሔር፣ጎሳ፣ቀለም፣ጾታ፣ዘር፣ቋንቋ፣ሃይማኖት፣ማህበራዊ አመጣጥ፣ ወይንም ሌላ መሰል አቋምንና ክብርን የሚነካ ወይም የሚያዋርድ፣ በህዝቦችና በሃይማኖቶች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይንም ጥላቻ የሚያስፋፋ፣ የግለሰብን ስም የሚያጠፋ፣፣ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆችን አመለካከት ስሜት የሚጎዳና ወደአልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያዘነብሉ የሚገፋፋ፣ የህብረሰተቡን ሞራል የሚጥስ ወይንም በሕግ የተከለከለ ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽም መሆን የለበትም ይላል፡፡
ተጠያቂነትም በተመለከተ ረቂቅ አዋጁ እንዳሰፈረው በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራም ለሚያስከትለው ማንኛውም የወንጀል ድርጊት ወይም የፍትሐብሄር ጉዳት የፕሮግራሙ ሃላፊና የብሮድካስት አገልግሎት ሰጪው በአንድነት ተጠያቂ ይሆናሉ ይላል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራምን ቁጥጥርን በተመለከተ ከህብረተሰቡ በቅሬታ መልክ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመመርመር፣ተቆጣጣሪ የመመደብ ስልጣን ወደፊት ለሚቋቋመው ባለስልጣን መ/ቤት ሃላፊነቱን ይሰጣል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የቴሌቪዥንን ከአናሎግ ወደዲጂታል ሽግግርን ለማቀላጠፍና የግል ቴሌቪዥን ለመፍቀድ ይረዳል ተብሎአል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢትዮጵያ የሚዲያ ባለስልጣን የሚባል መ/ቤት ይቋቋማል፡፡
የብሮድካስት አግልግሎት የሚመራበትን ሥርዓት ለመደንገግ ከ15 ዓመታት በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 178/1991 የግል ቴሌቬዥን ጣቢያ ፈቃድ ለግል ባለሃብቶች የፈቀደ ቢሆንም ይህ ተግባራዊ ሳይሆን አዋጁ በቁጥር 533/1999 የተሻሻለ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተሸሻለውም አዋጅ ቢሆን የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ የተፈቀደ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ኢትዮጵያ ለዚህ ደረጃ ገና አልበቃችም በማለት አዋጁ እንዳይፈጸም እስካሁን ድረስ መከልከሉ የሚታወቅ ነው፡፡

(ወልደብርሃን ስሁል) የዛሬ መቶ ሰባ ዓመት አካባቢ አንዲት “ሚጢጢየ” አውሮፓዊት ሃገር ማንም ሳይቀድማት ኢትዮጵያን በጉልበት ይዛ ቅኝ ለመግዛት “ክተት ሰራዊት ምታ ነጋሪት ብላ” ቆርጣ ተሰናዳች። በቆዳ ስፋቷ አንድ ትልቅ ወረዳ እምታክል ናት። አፍሪካ ውስጥ ግን የራሷን መቶ እጥፍ የሚያክል ግዛት መቆጣጠር እሚያስችል አቅምና እብሪት ነበራት። ህልሟን ለማሳካት ፕሮጀክት ቀርፃ feasibility study አካሄደች። እቅዷና ጥናቷ ያነጣጠረውም በዘመነመሳፍንቷ ኢትዮጵያ ላይ ነበር። የቀይ ባህር አካባቢ ደከም ባለ አውሮፓዊ ሃይል እንዲያዝ ትሻ የነበረችው ታላቋ ብሪታንያም ይሁንታ ሰጠቻት፤ በወርራ ቅኝ ልትገዛን ቆርጣ ለተነሳችው ቤልጅየም! ቤልጅየም ለኢትዮጵያ ያሰበችው ፕሮጄክት ብሎንዲል ከሚባል እብሪተኛ ሰው የጀብድ ልክፍት ጋር የተቆራኘ ነበር። ግብፅ በወርኔር ሙዚንጀር፤ ጣልያን በፔትሮ አንቶኖሊ ምን እንዳደረጉን ጠንቅቀን እናውቃለን። ከነሱ በፊት ቀድሞ ስለተሰናዳልን የብሎንዲል Humanitarian Mission ግን ብዙ አናውቅም። ነገሩ ያስገርማል እንጂ አያስቅም። “ገድለ‐ብሎንዲል” በጥቂቱ እንዲህ ነበር፦ የቤልጂግ መንግስት መጀመርያ በ1841 ከፍተኛ በጀት መድቦ ብዛት ያላቸው የስለላ ወኪሎቹን ወደ ግብጽ አሰማራ። ወኪሎቹም “ለሳይንሳዊ ጥናት እና ለሰብአዊ ተልእኮ” በሚሉ ሽፋኖች ካይሮ ላይ ከትመው ስለ ኢትዮጵያ ጥናት ጀመሩ። ማንኛውንም ዓይነት መረጃ በዝርዝር እየቀራረሙ ከሚያቀርቡት ሪፖርት የቤልጂየም ንጉስ ቀዳማዊ ሊዮፖልድ “በውስጧ ሁከት የነገሰባት ኢትዮጵያን” በቀላሉ መውረርና መቆጣጠር እንደሚችል አመነ። ለወረራም ቋመጠናም የሰላዮቹ አስተባባሪ በአካል ወደ ኢትዮጵያ ሂዶ “ሰብዓዊ ተልእኮ” የሚል ስም ያለው ጉብኝት እንዲያካሂድ አዘዘው። ዋናው ተልእኮው ግን ለወረራ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥር እና ባስቸኳይ እሚተገበር የድርጊት መርሃ ግብር እንዲያዘጋጅ ነበር። […]

Image
ከአውሮፓ ወደ ኤርትራ ለውህደቱ ስብሰባ እንዲሄድ የተወከለው በጀርመን የሚኖረው አቶ ካሳዬ መርሻ ወደ አስመራ እንዳይገባ በሻእቢያ መከልከሉ ሲታወቅ ከፊል ኤርትራዊ እንደሆነ የሚታወቀው እና ከአውስትራሊያ የተወከለው የወልቃይት ተወላጅ አቶ አለልኝ ከሻእቢያ ፈቃድ ማግኘቱ ታውቋል:: ነዋሪነት በጀርመን የሆነው እና ለአርበኞች ግንባር ትግል ታላቅ አስታውጾ እንዳበረከተ የሚነገርለት አቶ ካሳዬ መርሻ በግንባሩ አባላት አስፈላጊዉን ወጪ ተሸፍኖለት ለጉዞ ሲንደረደር በሻእቢያ መከልከሉ በውጪ የሚኖሩ የግንባሩ አባላትን ያሳሰበ ቢሆንም ሁኔታውን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል::

በዚህ ምክንያት በውጪ የሚኖሩ የአርበኞች ግንባር አባላት እና ደጋፊዎች የተወከለው አቶ ካሳዬ እንዳይመጣ በሻእቢያ መከልከሉን በተመለከተ ያላቸውን ተቃውሞ በደብዳቤ መላካቸው ሲታወቅ በአስመራ የሚገኙ የግንባሩ አመራሮች ሁኔታውን እንዲፈቱ በደብዳቤያቸው ያሳውቁት አባላቱ በአግባቡ የተወከለው ሰው በውህደቱ ጉባዬ ላይ እንዲገኝ ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል::የወከሉት ሰው በመከልከሉ በውህደቱ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬም አስምረውበታል::በቂ ሃይል እና ተንካራ መዋቅር እንዳለው የሚነገርለት አርበኞች ግንባት አባላቱ በኢትዮጵያ ለሚመጣው ለውጥ ተግተው እንደሚሰሩ እና ማንም እንደማያስቆማቸው ተናግረዋል::

አንድ አስተያየት ሰጪ እንደተናገሩት በሃገር ቤት ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃገራዊ አቋም እንዳይኖራቸው ሕወሓት/ኢሕ አዴግ በሰርጎ ገብነት እየገባ እንደሚያፋልሳቸው ሁሉ በውጪ የሚኖሩ ድርጅቶችንም እንዲሁ ሻእቢያ በውስጥ ጉዳያቸው እየገባ እሱ በሚፈልገው መልኩ እንዲሽከረከሩ ያደርጋል ሲሉ ተደምጠዋል::

ከጀርመን የተወከሉት አቶ ካሳዬ ወደ አስመራ እንዳይገቡ ካልተፈለገበት አንዱ ምክንያት ከዚህ ቀደም በግንባሩ ላይ በሻእቢያ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማስቀረት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ ሲሆን የግንባሩ አባላት እና ታጋዮች ይህንን በደንብ ስለሚያውቁ በውህደቱ ላይ እንዲገኝላቸው ፍላጎቱ ቢኖራቸውም ሻእቢያ ግን አንድ ጊዜ ጥርስ ስለነከሰበት እንዳይመጣበት ከልክሏል::እንዲሁም በውጪ የሚኖሩ አባላት ውህደቱ ላይ ችግር ካለ እንዲወገድ ወደፊትም ችግሮች እንዳይፈጠሩ አመራሩን ለማስተካከል እና አማራጮችን መጠቀም በሚል ስልት አቶ ካሳዬ የራሱን የፖለቲካ ልምድ ተጠቅሞ ሊያስተካክል ይችላል እንዲሁም ያሉትን ችግሮች እንዲስተካከሉ በፊትለፊት ይናገራል የሚሉ ፍራቻዎች በሻእቢያ ስላሉ የተወከሉት አባል ወደ አስመራ እንዳይገቡ ከልክለዋል::

አቶ ካሳዬ ወደ አስመራ ሁለት ጊዜ ካሁን ቀደም ሂዶ ካለምንም ፍርሃት ለሻእቢያ ግንባሩን በተመለከተ ያለውን ችግር እና ወደፊት መሆን የለበትን ጉዳይ ካለፍርሃት አፍረጥርጦ ስለተናገረ እንዲሁም አቶ ካሳዬ የአርማጮ ተወላጅ በመሆኑ በአከባቢው ያለውን እና በግንባሩ ታጋዮች ዙሪያ ያለውን ጉዳይ አንስቶ ካለፍርሃት ለሻእቢያ መናገሩ ለአሁኑ መከልከል ምክንያት ቢሆንም ጉዳዩን ለመፍታት አስመራ እና አውሮፓ ያሉ የግንባሩ አመራሮች እየጥሩ መሆኑን ምንጮች ከአስመራ ተናግረዋል:
******************************************************************************
የወያኔ አየር ሃይል ባልደረቦች ይዘውት የገቡትን ሄሊኮፕተር ተከትሎ አቶ ኢሳያስ አፍወርቂ የአዲስ አመትን ጋዜጣዊ መግለጫ አስታከው ይናገራሉ ተብሎ በመጠበቅ ላይ ሲሆን የወያኔ ቃል አቀባዮች ሌመንግስት ታማኝ ለሆነ ጋዜጣ ሄሪኮፕተሩ ለማስመለስ ጥረት አለመደረጉን መግለጻቸው ቢታወቅም የሕወሓት ጦር ጄኔራሎች ግን ካልተመለሰ ምሳችንን አስመራ እንበላለን ሲሉ መደንፋታቸው የወያኔ ባለስልጣናቱን አለመናበብ አመልክቷል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ወያኔ በውጪ ከሚኖሩ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ለመደራደር ማንዣበቡን ፍንጮች ጠቁመዋል:: ወያኔ በስልጣን የመቆየት እድሉ እንደተመናመነ በማወቁ ድርድር የማድረግ ፍላጎት ማሳየቱ እና በታሪክ ልንከስም ነው ያሉት ባለስልጣንን ተከትሎ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ገዢው ፓርቲ የገባበትን አጣብቂኝ ሊወጣው ባለመቻሉ ውንደለመደው በማዘናጋት ጊዜ መግዣ መፈለጉን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል:: ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬