* የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ለሻዕቢያ አሉታዊ የሆነ አቋም ያለማቋረጥ ይይዙና ይወተውቱ ነበር * የህወሓት/ኢህአዴግ ሠራዊት አዲስ አበባ ሲገባ አብሮ የመጣው የሻዕቢያ ተዋጊ ብዛት 300 ገደማ ነበር በሕወሓት (ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) የትግል ታሪክ እንደ ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ የሚወሰደው የ1981ዱ የሽረ ጦርነት ከመካሄዱ ጥቂት ወራት በፊት ሻዕቢያ በትጥቅ ትግሉ ስኬት ላይ ተስፋ አጥቶ እንደነበር ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ገለጹ፡፡ በሽረ አካባቢ የነበረውን የቀድሞ ሠራዊት 604ኛ ኮር በጋራ የመምታት ሀሳብ ከህወሓት በቀረበ ግዜ፤ ከሻዕቢያ የተሰጠው ምላሽ ‹‹12 ክፍለሀገር ለ2ክፍለሀገር ሞቢላይዝ እያደረገ መቼ ድል እንምናደር አናውቅም – በረጅም ተነል ውስጥ የድል ጭላንጭል አይታየንም›› የሚል እንደነበር አውስተዋል፡፡ ጄኔራሉ ይህንን የተናገሩት ባለፈው ሳምንት ባደረግንላቸው ቃለ-መጠይቅ በሕወሓት እና በተለምዶ ሻዕቢያ ተብሎ በሚጠራው (ያኔ ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ሕግሓኤ) አሁን ሕዝባዊ ግንባር ለዴሞክራሲ ለፍትሕ) በሚባለው የኤርትራው ገዢ ፓርቲ መሀል ስለነበረው ግንኙነት በሰጡት ምላሽ ላይ ነው፡፡ ከሻዕቢያ ጋር የነበረው ግንኙነት ሚዛኑን የሳተ ነው የሚለውን ክስ የማይጋሩት ጄኔራል ጻድቃን፤ ህወሓት ከአልጀሪያ እስከ ቬትናም፣ ከኩባ እስከ ቻይና ከነበሩ የትጥቅ ትግል ታሪኮች ልምድ ለመውሰድ ይሞክር የነበረ ከመሆኑ አንጻር ከጎረቤቶቹ ከሻዕቢያና ጀብሀ ልምድ መውሰዱ ተገቢ ነው ብለዋል፡፡ ስለግንኙነቱ እንደማሳያ ሁለት ክስተቶች እንዲጠቀሱ ተጠይቀው ሲመልሱ፡- በ1973 ገሩ ስርናይ፣ በማርዲ፣ ኡናሽሀቅ፣ ወዘተ በሚባሉት የድንበር አካባቢዎች (ዛሬ አህፈሮም ወረዳ) ለገበሬው መሬት የማከፋፈል ጉዳይ አወዛግቦ የነበረበትን ታሪክ አስታውሰዋል፡፡ በወቅቱ ጻድቃን በማዕከላዊ ኮሚቴ ተመድበው በአካባቢው ያስተባብሩ የነበረ […]

ሰሞኑን የትግሬ-ወያኔ እጀታ የሆነው የምርጫ ቦርድ፣ በመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና በአንድነት ለፍትሕና ዲሞክራሲ ፓርቲ (አንድነት) ላይ «ከምርጫ ውድድር የማገድ» ውሣኔ ማሣለፉን ሰምተናል። ይህም ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶች፣ ፖሊስ፣ አቃቢ ሕግ፣ መከላከያ ሠራዊቱ እና መሰል በ«ሕገ-መንግሥቱ ተቋቋሙ» የተባሉት ተቋሞች በሞላ የወያኔ ሕዝባዊ ድርጅቶች መሆናቸውን በይፋ እና በማያሻማ መንገድ ከታዩባቸው አያሌ ተግባሮች መካከል አንዱ ሆኖ የሚጠቀስ ነው። የምርጫ ቦርዱ ውሣኔ በራሱ ምርጫ ቦርድ የወያኔ ሕዝባዊ ድርጅትና እጀታ ከመሆኑ የመነጨ ብቻ ሣይሆን፣ የተቃዋሚው ጎራ ደጋግሞ በሄደበት እና ምንም ዓይነት ውጤት ባላስመዘገበበት መንገድ መጓዙ ጭምር እንደሆነ ሊስተዋል ይገባል።

የትግሬ-ወያኔ በምርጫ ተሸንፎ ሥልጣን እንደማይለቅ ያለፉት አራት የይስሙላ ምርጫዎች ከበቂ በላይ ነቃሾች ናቸው። ይህን በተመለከተ የ1997ቱን የምርጫ ውጤት ተከትሎ የትግሬ-ወያኔ በወሰደው የድምፅ ነጠቃ፣ ታዛቢ የነበሩት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር አቶ መለስን ለማለስለስ ባደረጉት የማግባባት ሙከራ ያረጋገጡት ሃቅ ነው። አቶ መለስ በወቅቱ የሰጣቸው መልስ፦ «ኢሕአዴግ በምርጫም ሆነ በኃይል ሥልጣን ከለቀቀ የሚጠብቀን አንድ እና አንድ ብቻ ነው። ይኸውም በአገር ክህደት ተከሰን ወህኒ መውረድ ነው። በመሆኑም ለ፲፯(አሥራ ሰባት) ዓመታት አፈር ግጠን የጨበጥነውን ሥልጣን በሕዝብ ድምፅ አንለቅም።» ሲል ነበር እቅጩን እና የማይለወጠውን የትግሬ-ወያኔን ዓላማ የገለጸው። በተመሣሣይ ሁኔታ የሕወሓት እና የኢሕአዴግ የፖሊት ቢሮ አባል የነበረው አቶ ገብሩ አሥራትም «ሉዓላዊነትና ዲሞክራሲ በኢትዮጵያ» በሚለው መጽሐፉ የሚነግረን ይህንኑ ነው። ስለዚህ ምርጫ ቦርድ ሰሞኑን የሰጠውም ውሣኔ የዚሁ ተከታይ አካል በመሆኑ፣ ድርጊቱ አስገራሚም፣ አስደንጋጭም አይሆንም። ባለፉት ፳፬ (ሃያ አራት) ዓመታት የኖርንበት ዓለም የታዘበው ዕውነታ ነውና። አስገራሚና አስደንጋጭ የሆነው ተቃዋሚው በወያኔ ሁለንተናዊ ፍላጎት ቁጥጥር ሥር መሆኑን አለመገንዘቡ ነው። እኒህ ተቃዋሚዎች ጉዟቸው ያልተለወጠ እና በየአምስት ዓመቱ በሚደረግ የምርጫ ዘመቻ የተገዛ ነው። ይህ ጉዞ ለውጤት ያላበቃ መሆኑ ተደጋግሞ እየታዬ፣ ውጤት እንደማያስገኝ በታወቀ መንገድ መጓዙ፣ ችግሩ ከመንገዱ ሣይሆን፣ ከተጓዡ እንደሆነ ትግሉ የሚገኝበት ሁኔታ ያሣያል። ስለሆነም ተቃዋሚ ኃይሎች ከ1997ቱ የምርጫ ሂደት እና ውጤት ከታዩት አዎንታዊ እና አሉታዊ የጉዞ አቅጣጫዎች ትምህር የቀሰሙ አይመስልም።

ሁለተኛው የተቃዋሚ ድርጅቶች መሠረታዊ ችግር በአደረጃጀታቸው ላይ ያጠነጠነ ነው። የትግሬ-ወያኔ በማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ብቻ ሣይሆን በዕድሮች ሣይቀር የራሱን ሥውር መዋቅር አስርጎ አደራጅቷል። ሰሞኑን በመኢአድ እና በአንድነት ላይ የተከሰተው ችግር ግን፣ ተቃዋሚ ድርጅቶች የትግሬ-ወያኔን የሤራ ስልት ባለመገንዘብ ከነ አየለ ጫሚሶ ዓይነት ሠጎ ገቦች ድርጅቶቻቸውን ማጽዳት አለመቻላቸውን ቁልጭ አድርጎ ያሣያል። ሰለዚህ የአደረጃጀት ሥልታቸው የወያኔን ሠርጎ ገቦች ሊያንተረትር በሚችል መልክ እስካልተቃኘ ድረስ፣ በምንም ሁኔታ የትግል ጉዞ አቅጣጫቸው በወያኔ እና በአጋሮቹ ላይ ተጽዕኖ ሊያሣድር አይችልም። ይህም ብቻ አይደለም፤ ተቃዋሚው የሙጥኝ ብሎ የያዘው «በሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ብቻ የትግሬ-ወያኔን በምርጫ አሸንፈን ሥልጣን እንይዛለን» የሚለውን ብቸኛ የትግል መሣሪያው አድርጎ መያዙ፣ ለትግሬ-ወያኔ ሠርጎ መግባት የተመቻቸ ሁኔታ ከመፍጠሩ ባሻገር፣ የነቁትን የኅብረተሰብ ክፍሎች በቀላሉ የአገዛዙ ዒላማ እንዲሆኑ አድርጓል። ይህም ትግሉን ተተኪ መሪዎች በማሣጣት መሪ አልባ በማድረጉ፣ የሕዝቡን የወኔ ሥንቅ እንዳሟጠጠ በድርጅቶቹ ውስጥ በቂ ትኩረት የተሰጠው ያለመሆኑን ያመለክታል።

የተቃዋሚው ኃይል የትግሬ-ወያኔን ባሕሪ የሚመጥን የትግል ሥልት መከተል ባለመቻላቸው፣ ወያኔ «ግሞ» ሲል «ጥንቦ» ማለት አልቻሉም። በተደጋጋሚ በአገር ቤት ካሉ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚደመጠው የትግል ስልት፦ «በሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ብቻ የትግሬ-ወያኔን በምርጫ አሸንፈን ሥልጣን እንይዛለን» የሚል ነው። ሆኖም የሰላማዊ ትግል ሥልት በምርጫ ዘመቻ ብቻ የተገደበ አይደለም። የምርጫ ዘመቻ ለሰላማዊ ትግል ጠቃሚ የሚሆነው ዲሞክራሲያዊ ተቋሞች የሚባሉት ማለትም፦ ነፃ እና ገለልተኛ የሆነ የምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶች፣ አቃቤ ሕግ፣ ፖሊስ፣ የመከላከያ ሠራዊት እና ወገንተኛ ያልሆኑ የብዙኃን መገናኛ ተቋሞች መኖር፣ ወዘተርፈ፣ በአጠቃላይ የሕግ የበላይነት ሰፍኖ ከማንም ተፅዕኖ ውጭ በነፃ የመሥራት የዜግነት መብት ሲረጋገጥ ነው። እነዚህ ተቋሞች በሌሉበት ሁኔታ ግን፣ በምርጫ ፖለቲካ ወያኔን ከሥልጣን እናወርዳለን ብሎ ምርጫን በብቸኛ የትግል መሣሪያነት የሙጢኝ ብሎ መያዝ፣ ታጋዩ ሕዝብ ሥቃይን እና በደልን ተለማምዶ የ፵(አርባ) ቀን ዕድሌ ነው ብሎ እንዲያምን እና ለወያኔ አገዛዝ ምቹ እንዲሆን ሠፊ በር የሚከፍት መሆኑ በግልፅ ሊታመንበት ይገባል። በተግባርም የሚታየው ይኼው ነው። የመንግሥት ሥራ አስፈጻሚ መዋቅር፣ የፍትህ አካሎች እና የብዙሃን መገናኛ ተቋሞች በአንድ ዘረኛ ቡድን ፍላጎት እና ቁጥጥር ሥር በዋሉበት ሀገር፣ በምርጫ ሥልጣን እረከባለሁ ማለት ሸንበቆ ያፈራል፣ በቅሎ ትወልዳለች፣ ዝንብ ማር ትጋግራለች፣ ፀሐይ በምሥራቅ ትጠልቃለች እንደማለት ይቆጠራል። እንደሞረሽ-ወገኔ እምነት፣ ሰላማዊ ትግሉ የተለየ መንገድ መከተል ይኖርበታል። ወቅታዊ የትግሉ መፈክር «ለዲሞክራሲ፣ ለዕኩልነት እና ለብልጽግና» ሣይሆን ቅድሚያ ለነፃነት ትግል መሆን አለበት። አገር እና ሕዝብ ሳይኖሩ፣ ዲሞክራሲ እና ዕኩልነት ሊታሰቡ የሚችሉ ጉዳዮች አይደሉምና!

በመሆኑም፣ የተቃዋሚው ጎራ፣ የትግሬ-ወያኔን እንደተኩላ ከብቦ የሚቦጫጭቅበትን፣ አጠቃላይ ሕዝባዊ እንቢተኝነትን የትግሉ መርህ አድርጎ ሊንቀሣቀስ ይገባዋል። ስለዚህ ቀዳሚው የትኩረት አቅጣጫ መሆን ያለበት በየአካባቢው ያለውን የትግሬ-ወያኔን የስለላ መዋቅር በመበጣጠስ፣ ሕዝቡ የራሱ አለቃ የሚሆንበትን ዘዴ በመሻት፣ የትግሬ-ወያኔን እና አጋሮቹን ለነፋስ በመስጠት፣ የአገዛዝ ዕድሜያቸውን ለማሳጠር መንቀሣቀስ ነው። ይህ ደግሞ ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከመሀል እስከዳር ሕዝቡን በማደራጀት በእንቢተኝነት ስሜት እንዲነሣ ማነቃነቅ ያስፈልጋል። የትግሬ-ወያኔ አፋኝ ቡድን የኃይል መከፋፈል የሚፈጠርበት፣ ለቅልብ ጦሩ ሆድ መሙያ የሚከፍለው በጄት የሚያጣበት፣ በገዥው ቡድን መካከል የኃሣብ መከፋፈል የሚፈጠርበት፣ የማስፈጸም አቅሙ የሚሟሽሽበት፣ እርስ በርሳቸው የሚጠራጠሩበት ሁኔታን የሚፈጥር ሥራ መሠራት አለበት። ለዚህም በደህንነቱ፣ በሠራዊቱ፣ በፖሊሱ፣ በቢሮክራሲው መሀል ሠርጎ በመግባት ዓላማ እና ዕቅዳቸውን ማክሸፍ ያስፈልጋል። ሕዝቡም «ላልወከልነው አካል ግብር አንከፍልም፣ የእኛ ባልሆኑ ተቋሞች አንገዛም፣» የሚለውን ስሜት እና እምነቱን ሊያጎለብት ይገባል። በትግሬ-ወያኔ የተለያዩ የንግድ እና የአገልግሎት ተቋሞች፣ ማለትም፥ የትራንስፖርት፣ የሆቴል፣ የንግድ ቤቶች እንዳይጠቀም በልዩ ልዩ መንገዶች በማስተማር ወያኔ እና አባሎቹን ከማናቸውም ማህበራዊ እና ባህላዊ እንቅስቃሴዎች በማግለል ብቻቸው እንዲቆሙ መደረግ አለበት። «መጡብን» ሳይሆን፣ «መጣንባችሁ» ሊባሉ ይገባል። ከእንግዲህ ተቃዋሚው ጎራ ሙሾ ማውረዱን ማቆም አለበት። መርዶ የሽንፈት እንጂ፣ የድል ምልክት ባለመሆኑ፣ «እንዲህ ሆን፣ እንዲ,ህ ተደረገን» የሚሉት እሮሮዎች ሊገቱ ይገባል።

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የትግሬ-ወያኔ በሁለቱ የሰላማዊ ትግል አራማጅ ድርጅቶች ላይ የወሰደውን እርምጃ የተመለከተው ከትግሬ-ወያኔ ጉዞ እና ዓላማ አንፃር የሚጠበቅ እንጂ፣ ዱብ ዕዳ እና እንግዳ ነገር አድርጎ አይደለም። በአንፃሩ «ማሽላ ሲያር ይስቃል» እንዲሉ፣ ይህ እርምጃ ለፀረ-ወያኔ ትግል እልህ፣ ቁጭትና የመጠቃት ስሜትን የሚፈጥር ነው ብለን እናምናለን። ስለሆነም የተቃዋሚው ጎራ በአንድ ብሔራዊ ዓላማ ዙሪያ እንኳን መሰባሰብ ባይችል፣ በፀረ-ወያኔ አቋሙ በአንድ ግንባር ወይም ኅብረት ሥር እንዲሰለፍ ሠፊ በር የከፈተ ያህል ይቆጥረዋል። ስለዚህ በአገር ቤትም ሆነ በውጭ የሚገኘው ተቃዋሚ ኃይል ከምንጊዜውም በበለጠ ተቀራርቦ በመነጋገር በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ላይ የተጠናከረ እና ሁሉን- አቀፍ ትግል እንዲያደርግ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያዊነት ስም ጥሪያችንን እ,ናቀርባለን።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!
ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!
የትግሬ-ወያኔ ዘረኛ ቡድን ነው፤ በመሆኑም መወገድ አለበት!

የደቡብ ምስራቅ እዝ ውስጥ የተነሳው ውጥረት እየተካረረ ነው::2 ኮሎኔሎች ታስረዋል::

Minilik Salsawi በሰራዊቱ ውስጥ የዘረኝነት ጥቃት እየተፈጸመ ነው::የሰራዊቱ ተቃውሞ እንዳይስፋፋ ወያኔ ሰግቷል::በምስራቅ ኢትዮጵያ የሰፈረው የደቡብ ምስራቅ እዝ የመከላከያ ሰራዊት አባልት ከአለቆቻቸው ጋር የፈጠሩት አለመግባባት እየተካረረ መምጣቱን በቦታው የሚገኙ ወታደራዊ ደህንነቶች ያደረሱት መረጃ ጠቅሷል::ከቀድሞ በተለየ ሁኔታ የመከላከያ ሰራዊቱን እየሰበሰቡ መገምገም ማሰር የቀጠለ ሲሆን ከመሃል አገር ተመድበው የመጡ አዳዲስ አባላት በሰራዊቱ መካከል ገብተው ውጥረቱን ለማርገብ እና ለማዘናጋት ቢያስተባብሩን እንዳልተሳካ ታውቋል::

በሕገመንግስቱ በማእረግ እድገት እንዲሁም በጥቅማጥቅሞች ዙሪያ የተነሳው ጥያቄ ከወር በፊት አራት ወታደራዊ መኮንኖች መታሰራቸው ሲታወስ ከሁለት ቀን በፊት በተደረገው ግምገማ ኮሎኔል አብደላ ጫልቺሳ እና ኮሎኔል ተከተላቸው በወጉ የተባሉ ወታደራዊ መኮንኖች ወደ እስር ቤት መወርወራቸው ታውቋል::የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ሕገመንግስቱ መሰረት ያደረገ አስተዳደር በኢትዮጵያ የለም ሕዝቡ በፖለቲካ በኢኮኖሚ ተጎዳ የሚል ጉዳዮችን በውይይት መድረካቸው ጊዜ አንስተው ቢወያዩበትም ጉዳዩ ተስፋፍቶ ከውይይት መድረክ ወደ ክርክር እና ተቃውሞ የተቀየረ መሆኑን እና በእዙ ውስጥ ውጥረት እንዲነግስ ማድረጉን የጠቀሱት ምንጮች የማእረግ እድገትን በተመለከተ ለአንድ ብሄር ብቻ እንደሚሰጥ እና ሃገሪቱን በጋራ እስካገለገልን ድረስ የእንጀራ ልጅ የሚባል ነገር የለም አድልዎ እየተደረገ ነው የሚል ተቃውሞ የተፈጠረ ሲሆን በጥቅማ ጥቅም ዙሪያ እንዲሁ እንደ ማእረግ እድገቱ የዘረኝነት ጥቃት እየተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ አቤቱታ እያሰሙ መሆኑን ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::መከላከያ ሰራዊቱ ያነሱት ጥያቄ/ተቃውሞ ወደ ሰሜን እና ምእራብ እዝ እንዳይስፋፋ በጥንቃቄ የተያዘ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::

Image

ከ1971 ጀምሮ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት የህወሓት ከፍተኛ አመራር የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ‹‹እኔ የማውቀው ከደርግ ከሚገኘው ንብረት አብዛኛውን ከሕዝብ ስንካፈል እንጂ ከውጭ ለእርዳታ የመጣውን ገንዘብ ከሕዝብ ቀምተን ለጦር መሣሪያ ስናውል አይደለም›› አሉ፡፡ ጄኔራሉ ይህን ያሉት ባለፈው ሰኞ ጥር 30-2007 ባደረግንላቸው ቃለ-መጠይቅ ላይ፡- ለ1977ቱ ረሀብ የመጣው ዕርዳታ ለድርጅት ሥራ እንዲውል ተደርጓል ስለሚለው የዶ/ር አረጋዊ በርኸ ስሞታ ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ነው፡፡ ዶ/ር አረጋዊ ከቀደምት የህወሓት አመራሮች አንዱ ሲሆኑ የማርክሳዊ ሌኒናዊ ሊግ ትግራይ(ማሌሊት) ምሥረታን ተከትሎ ከድርጅቱ ለቅቀው በአውሮፓ የሚኖሩ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዶ/ር አረጋዊ ለዕርዳታ ከመጣው ገንዘብ 50 በመቶ ለማሌሊት ማጠናከሪያ፣ 45 በመቶ ለወታደራዊ ወጪ ተመድቦ 5 በመቶ ብቻ ለሕዝብ እንዲውል በማዕከላዊ ኮሚቴ ተወስኖ ተግባራዊ ተደርጓል የሚሉ ሲሆን፤ በወቅቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ግን የዛሬ 5 ዓመት በአሜሪካ ራዲዮ አማርኛ ፕሮግራም ላይ በሰጡት አስተያየት እንደዚያ ዓይነት ውሳኔ አልተወሰነም በማለት መቃወማቸው ይታወሳል፡፡ በሌላ በኩል በቅርቡ ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አመራር ገብሩ አሥራት በቅርቡ ባሳተሙት መጽሐፍ፡- በወቅቱ ድርጅታዊ ድጋፍ የሚያደርጉ መንግስታት የሚጠቀሙት መሥመር ያንኑ የሰብዐዊ ዕርዳታ የሚመጣበትን መሥመር በመሆኑ እና ሁሉም ገንዘብ አንድ ቋት ውስጥ የሚገባ በመሆኑ ስሞታው የወቅቱን አሠራር ካለመገንዘብ የሚመጣ ነው የሚል አጭር አስተያየት አስፍረዋል፡፡ እነዚህን አስተያየቶች በመጥቀስ ጥያቄ ያቀረብንላቸው በወቅቱ የማለሌሊት/ህወሓት ፖሊት ቢሮ አባል እና የሠራዊቱም ቺፍ ኦፍ ስታፍ የነበሩት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ስሞታውን አጣጥለውታል፡፡ በወቅቱ በተለይ በረሀቡ […]

ተቃዋሚዎችን በጥላቻ የሚመለከተው ወያኔ አሁንም የክስ ዋራንት ለመቁረጥ አሰፍስፏል::

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – በተጭበረበረ ፖለቲካ አገር አስተዳድራለሁ የሚለው ወያኔ ተቃዋሚዎች በመንግስታዊ ተቋማት ላይ አፍራሽ ተልእኮ ያራምዳሉ በማለት ሊያጠቃቸው መነሳቱን በሚቆጣጠራቸው ሚዲያዎች ያለእፍረት እየተነፈሰ መሆኑ በመስማት ላይ ነን::በፍትህ እና በምርጫ ቦድ እንዲሁም በማስተዳድራቸው ተቋማት ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ እያካሄዱ ዲሞክራሲ እንዳያብብ እንቅፋት እየሆኑ ነው ያለው ወያኔ ራሱን የዲሞክራሲ ተበቃ አድርጎ በመሳል በአፍራሾች ላይ ውርምጃ እውስዳለሁ ሲል ሰበብ እየፈጠረ መሆኑን አድበልብሎ የሰራቸው እና የፈጠራ ውጤቶቹ የሆኑ አንዳንድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሚባሉትን ካድሬዎቹን ሲያስደሰኩር ሰምተናል::

በመፍረከስከስ ላይ መሆኑን የሚያሳብቅበት ወያኔ በአንድነት ፓርቲ ላይ ዬማፍረስ እንዲሁም መኢአድን የመበጥበጥ ስራ ከሰራ በኋላ ተበደልም የሚሉ የፍትህ ያለ በሚሉበት ሰአት በሌላ ወንጀል ሰማያዊን ለማሸግ ማሰፍሰፉን እርግጫው ይናገርበታል::በአገሪቱ እያደረገ ያለው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ወንጀሎች ከማህበራዊ ድቀት ጋር ተደምረው ለምርጫ ቢቀርብ እንደሚሸነፍ ያረጋገጠው እና አከርካሪው የተመታው ወያኔ ላለመሞት በሚያደርገው መፈራገጥ ያሸንፉኛል ያላቸውን ፓርቲዎች እና ግለሰቦችን ጠልፎ በመጣል በመሳሪያ ሃይሉ ተማምኖ ወደ እስር ቤት ለመወርወር ማሰፍሰፉ አምባገነንነቱ ምን ያህል አግጥጦ እንደወጣ ያሳያል::

ዲሞክራሲያዊ ተቄማት የሚባሉት እንደ ምርጫ ቦርድ እና የፍትህ አካላት ነጻ እና ገለልተኛ ባልሆኑበት አገር ነጻነትን እና መብትን ለማስከበር የሚታገሉ ድርጅቶችን ለመዋጥ ባሰፈሰፈ የፖለቲካ ዘንዶ ራሱ እንደሚዋጥ ያላሰበው ወያኔ ነጻ እፓርቲዎች እና ግለሰቦች ሊታዘዙልኝ አልቻሉም እንደኔ ሊያስቡ አልቻሉም በሚል በጥላቻ የተሞላው ወያኔ የፓርቲ አመራሮችን ሰብስቦ ለማሰር ማሰፍሰፉ በሃገሪቱ እየተስፋፋ ያለው ህገወጥ መንግስታዊ አሸባሪነት ሃገር ወዳዶችን እና ለውጥ ፈላጊዎች አጥፍቶ ለመጥፋት ምን ያህን እንደተነሳ በገሃድ ይመሰክራል::

የፍትህ አካላት እና ዲሞክራሲያዊ ተቋማት ከነሚዲያ በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ስር በዋሉበት አገር ዜጎች በሰበብ አይታሰሩም አይሰደዱም አይገደሉም ማለት ዘበት ነው::ኢሕአዴግ መሰሎቹን ይዞ ወደ ሚያጭበረብረው ምርጫ ለመዝለቅ እንዲያስችለው ጠንካሮችን ከጨዋታው ውጪ በማድረግ ግስጋሴውን ተያይዞታል::የአውሮፓ ህብረት የመሰሉ ሃገሮች ለውጥ አልባ በሆነ ምርጫ እስጥ በታዛቢነት አንሳተፍም በማለት እጃቸውን የሰበሰቡ ሲሆን ወያኔ እንደ ምርጫ ቦርድ ያሉ አጋሮቹን ይዞ ሆይሆይታውን በመቀጠል ንጹሃንን በማሰር ፓርቲዎችን በማፍረስ ላይ ነው::ይህንን የተቃወሙ የለውጥ ሃይሎችንም በአፍራሽነት በመፈረጅ ላይ መሆኑን የራሱ ሚዲያዎች እየተናገሩ ነው::

ህዝብን በፖለቲካ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ መስክ ቁም ስቅሉን እያሳየው ነው:: የሃገሪቱ ህገ መንግስት ከሚፈቅደው ውጪ እና ውጪ በፖለቲካ መስክ የአይናቸው ቀለም ያላማረ ተቃዋሚዎች ይደበደባሉ ይታሰራሉ ይገረፋሉ በፍርድ ቤት በሃሰት መረጃ ከህግ ትእዛዛት ውጭ የረዥም አመት እስር ይከናነባሉ:: እንደ መንግስት ባለስልጣናት ሳይሰርቁ ደፋ ቀና ብለው ያፈሩት ንብረት ይወረሳል::ከዛም አለፍ ካለ በአደባባይ ይረሸናሉ:: በደህንነት ሃይሎች ይገደላሉ:: ይህ የሚያሳየው የጸጥታ ሃይሎች ከህግ በላይ ሆነው ፍትህን መግደላቸው ነው:: የፖለቲካ ድርጅቶች እንዳይንቀሳቀሱ የጸጥታ ሃይሎች እንቅፋት ከመሆን አልፈው ወደ አንድ ፓርቲ ያደላ ኮንትሮባንዳዊ ፖለቲካ እየፈጸሙ ነው::ሕዝቦች ለነጻነት በሚያደርጉት ትግል ውስጥ አምባገነኖች የሚያደርሱት ጭቆና ትግሉን ያፋፍመዋል እንጂ አያዳክመውም:: በሃገር ውስጥ ይሁን በውጪ ሃገር የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ለወያኔ መውደቅ ከበፊቱ በበለጠ ለትግላችን ስኬት እስከ ድል ደጃፎች ድረስ በመገስገስ ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ነጻነታችንን በማረጋገጥ የወያኔን አምባገነን ስርአት በመጣል የጋራ አገራችንን ለመገንባት የምንነሳበት ወሳኝ ወቅት ላይ መሆናችንን ለማረጋገጥ እወዳለሁ::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በትግል 10 ዓመታ ካስቆጠረ በኋላ፤ በ1977ዎቹ የፖለቲካ አመራር የሚሰጥ አደረጃጀት ማርክሳዊ ሌኒናዊ ሊግ ትግራይ(ማሌሊት) በሚል ስያሜ እንደመሠረተ ይታወሳል፡፡ ያ አደረጃጀት ዓለም-አቀፋዊውን የአሰላለፍ ለውጥ ተከትሎ ከ1983 በኋላ እንዲቀር መደረጉ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በአብዛኛው ሕዝብ እምብዛም አይታወቅም፡፡ ይሁን እንጂ ህወሓት ከ1970ዎቹ አጋማሽ በኋላ ላሳየው የወታደራዊ እና ድርጅታዊ እመርታ ምክንያቱ የማሌሊት ምሥረታ ያስከተለው የርዕዮተ-ዓለም ጥራት ነው ብሎ ያምናል፡፡ በአንጻሩ የቀድሞው የድርጅቱ አመራር ገብሩ አሥራት በቅርቡ ባሳተሙት መጽሐፍ፡- በወቅቱ የተገኙት ለውጦች ያለማሌሊት ሊከሰቱ የሚችሉ የአደረጃጀት ለውጥ ውጤቶች ናቸው የሚል ሀሳብ አንስተዋል፡፡ ባለፈው ሰኞ ጥር 30-2007 ቃለ-መጠይቅ ያደረግንላቸው ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሰኤ ካቀረብነው ጥያቄዎች አንዱ ማሌሊትን የተመለከተ ነበር፡፡ ከ1971 ጀምሮ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት እና ማሌሊት ሲቋቋም ከመጀመሪያዎቹ 9 የፖሊት ቢሮ አባላት አንዱ የነበሩት እንዲሁም የህወሓት ሠራዊት ቺፍ ኦፍ ስታፍ የነበሩት ጻድቃን፤ * የማሌሊት ምሥረታን እና በሕወሓት መዋቅር ላይ የነበረውን ፋይዳ ያብራሩ ሲሆን አያይዘውም * የህወሓትን ወታደራዊ ስትራቴጂ ጽንሰ-ሀሳቦች፣ * ከደርግ 603ኛ ኮር ጋር በሽረ የተደረገውን ውጊያና ተዛማጅ ታሪካዊ ሁነቶችን እንደሚከተለው አብራርተዋል፡፡ [እስከ 1993 የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማጆር ሹም የነበሩት ሌፍተናንት ጄኔራል ጻድቃን፤ የህወሓት-ሻዕቢያ ግንኙነት፣ የ1977ቱ ረሀብ፣ በኤርትራ ወረራ ወቅት የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ሚና፣ የቀድሞው ሠራዊት መበተን እና ሌሎች ዐብይ ርዕሰ-ጉዳዮች እንዲሁም ስለራሳቸው ለቀረቡ ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሾች በተከታታይ እናቀርባለን] —— Watch Video below.   ************* More from Horn Affairs AmharicVideo […]

5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላትና 2 ፓይለቶች ጠፉ!!

ጥር ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአየር ሃይል ምንጮች እንደገለጹት ከሁለት ሳምንት በፊት 5 የአየር ሃይል የጥበቃ አባላት እስከነ ሙሉ ትጥቃቸው እንዲሁም 2 ፓይለቶች ከድሬዳዋ አየር ሃይል ጠፍተዋል። የጥበቃ አባላቱም ሆነ ፓይለቶቹ ያሉበትን ለማወቅ የተደረገው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። ይህንን ተከትሎ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ከመቶ አለቃ ማእረግ በላይ ያላቸውን አየር ሃይል አባላት ሰብስበው ግምገማ አካሂደው ነበር።

ጄ/ል ሳሞራ “የአየር ሃይል አባላት ለምን ይከዳሉ? አሁን ያላችሁትስ ምን ታስባላችሁ?” የሚል ጥያቄ ለተሰብሳቢው ያቀረቡ ሲሆን፣ የአየር ሃይል አባላቱም ከፍተኛ የሆነ የአስተዳደር በደል እንደሚደርስባቸው፣ ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ክፍያ እንደሚከፈላቸው፣ በመኖሪያ ቤት እጦት እንደሚሰቃዩ ገልጸዋል። መኮንኖቹ በርካታ ችግሮችን ዘርዝረው ያቀረቡ ቢሆንም፣ ጄ/ል ሳሞራ ችግሮችን ከመስማት ውጭ ምንም አይነት ምላሽ ሳይሰጡ ሄደዋል።

የአየር ሃይል አባላት ሞራል ( ስሜት) መዳከም ገዢው ፓርቲ በሩሲያ ቅጥር አብራሪዎች ላይ እምነቱን እንዲጥል አድርጎታል። የትግራይ ተወላጅ የሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ እና ቴክኒሻን ብርሃን ግደይ ከመቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ ጋር በመሆን ስርአቱን አናገለግልም ብለው ሄሊኮፕተር ይዘው መጥፋታቸው፣ የህወሃትን የዘር ፖለቲካ መሰረት እንዳናጋው ምንጮች ይገልጻሉ። ለወትሮው ይታመኑ የነበሩ የትግራይ ተወላጅ የአየር ሃይል አባላት ሳይቀሩ የሚታመኑ ሆነው ባለመገኘታቸው፣ባለስልጣናቱ አይናቸውን የውጭ ቅጥረኞች ላይ እያዞሩ ነው።

ስርዓቱን አናገለግልም ብለው የጠፉት የአየር ሃይል አባላት የተቃዋሚ ድርጅቶችን ተቀላቅለው እየታገሉ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአፍሪካ መሪዎችም ሆነ የሌሎች አገራት መንግስታት ለስብሰባ ወደ አዲስ አበባ በሚመጡበት ጊዜ ለደህንነት ስራም ሆነ ለልዩ ጥበቃ የሚመደቡት የአንድ ብሄር ተወላጆች ናቸው በማለት የሌሎች ክልሎች የደህንነት አባላት ቅሬታ ማሰማታቸው ታውቋል።

የ24ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ከተካሄደ በሁዋላ ለግምገማ ከተጠሩት ምድብተኛ የደህንነት ሰራተኞችና የጸጥታ አካላት መካከል አንዳንዶች፣ ” ለመሪዎችና ለእንግዶች ደህንነት የሚመደቡት ጠባቂዎች የአንድ አካባቢ ተወላጆች ብቻ መሆናቸው፣ “ስርአቱ የእናንተ አይደለም፣ አናምናችሁም” የሚል መልክት አለው በማለት በድፍረት ለገምጋሚዎች ተናግረዋል።

“በብሄራችን ምክንያት ተበድለናል” ያሉት የደህንነት ሰራተኞችና ጠባቂዎች፣ ደረሱብን ያሉዋቸውን በርካታ ችግሮች ዘርዝረው አቅረበዋል። ” በኢትዮጵያ ውስጥ አሸባሪዎች ራሳቸውን እያደራጁና መረባቸውን እየዘረጉ በመጡበት ሁኔታ የምናምነውን ሰው እንመድባለን” የሚል መልስ ግምገማውን ከሚመሩ መሪዎች የተሰጠ ሲሆን፣ ተሳታፊዎች በተሰጠው መልስ ማዘናቸውን በግምገማው የተሳተፉ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።

(አዲስ ከድሬዳዋ) የቀድሞ ዩጎዝላቪያ አካል የነበሩት ክሮሺያና ሰርቢያ (የቦስኒያ ሙስሊሞችን እና ሞንቴኔግሮዎችን ጨምሮ) ሶሻሊዝም ሲንኮታኮት ከተበታተኑት የዩጎዝላቪያ ሪፑብሊኮችና ራስገዝ አስተዳደሮች መካከል ናቸው፡፡ እነኚህን ሪፑብሊኮች ቀድሞዉኑ ምን አንድ አደረጋቸው፣ በኋላስ ለምን መለያየት ፈለጉ የሚለው ትንሽ ግራ ያልተለመደ የሚመስል ነገር አለው፡፡ ከዩጎዝላቭ ሪፑብሊኮች በህዝብ ብዛትና ተፅዕኖ የመፍጠር አቅም ቀዳሚ የነበሩት ሰርቦች እና ክሮአቶች ቋንቋቸው የዲያሌክትን(ቀበሌኛን) ያህል እንኳ የማይለያይ ተመሳሳይ ነው፡፡የቋንቋ ምሁራንም ለየብቻ ማስቀመጥ ከብዷቸው ሰርቦክሮአት ይሉት ነበር ቋንቋውን(አሁን ለየብቻ ነው ብዙ ቦታ ላይ የሚፃፈው)፡፡ ዘራቸውም እንደስማቸው ሁለቱም ዩጎ ስላቮች(የደቡብ ስላቮች) ናቸው፡፡ ታሪካቸውን ያየን እንደሆነም ብዙ ነገሮችን ይጋራሉ፡፡ ኢኮኖሚያቸውን ያየን እንደሆነም ከአውሮፓ ድሀ እና በአንፃራዊነት ኋላቀር ከሚባሉ ህዝቦች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ታዲያ በምንድን ነው የሚለያዩት – በሐይማኖት- አለቀ፡፡ በሀይማኖት ብቻ፡፡ ሰርቦች ኦርቶዶክስ ናቸው፣ ክሮአቶች ደግሞ ካቶሊኮች ናቸው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ሰርቦች የኦሮቶዶክሱ ቅዱስ በፈጠረው ሲርሊክ ፊደል ይፅፋሉ፣ ካቶሊኮቹ ክሮአቶች ደግሞ ሮማዊ በሆነው ላቲን ፊደል ይፅፋሉ፡፡ እነዚህ ህዝቦች የደቡብ ስላቭ አንድነት አቀንቃኝ በነበረው ቲቶ አንድ ሆነው ሲኖሩ ቆይተው(አንድነቱ ግን ወደህዝቡ ያልሰረጸ እና በቲቶ ተሰሚነት ላይ የተመሰረተ ስለነበረ) ማርሻል ቲቶ ሲሞት አንደኛው ህዝብ ከሌላኛው ብሔር በወጣ መሪ ለመተዳደር ዝግጁ ስላልነበር ዩጎዝላቪያ በእቁብ መመራት ጀመረች፤ ዘንድሮ ከሰርቢያ፣ ቀጥሎ ከሞንቴኔግሮ፣ ከዚያ ከክሮሺያ፣ ከዚያ ከሜቄዶኒያ፣ ከዛ ከስሎቬኒያ፣ . . .እያሉ በየአመቱ በፈረቃ ዩጎዝላቪያን ሲያስተዳድሩ ቆዩ፡፡ ያው አስተዳደራቸው ራሱ ምንያህል አንድነት እንደሌላቸው የሚያሳይ ነውና ጊዜው ሲደርስ ሁሉም ሪፑብሊኮችና ራስገዝ […]

Image

ሦስቱ ጋዜጠኞችና ስድስቱ ጦማሪያን ዛሬ በልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ምድብ ችሎት ቀርበው ለ የካቲት 11 ተቀጠሩ፡፡ በ26/05/2007 ዓ.ም. የመሀል ዳኛው አቶ ሸለመ በቀለ ይቀየሩልን ሲሉ በፅሁፍ ያቀረቡት አቤቱታ የግራና የቀኝ ደኛው ውድቅ ሲያደርጉት የመሀል ዳኛው አቶ ሸለመ በቀለ በራሴ ፈቃድ ከችሎቱ እራሴን አንስቻለሁ ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ታዳሚ ገልፀዋል፡፡

በተያያዘ ዜና ሰባተኛ ተከሳሽ ጦማሪ አቤል ዋቤላ ትላንት ከፍርድ ቤት ወደ ማረሚያ ቤት በሚመለስበት ወቅት እጅህ በካቴና ለምን አልታሰረም ብለው የማረሚያ ቤቱ ሰራተኞች እጄን በውሻ ሰንሰለት አስረው አሳድረውኛል ብሎም ዛቻና ዘለፋ ደርሶብኛል እንደዲሁም ማአከላዊ ታስሬ እያለሁ በደረሰብኝ ድብደባ ጀሮዬ ላይ ጉዳት ስለደረሰ ለማደዳመጥ ጀሮዌ ላይ የማረገውን ድምፅ ማዳመጫ መሣሪያ በማረሚያ ቤቱ ሰራተኞች ተነጥቂያለሁ ሲል እንባ በተናነቀው ንግግር ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል፡፡ ፍርድ ቤቱ ለማረሚያ ቤቱ ተወካይ ለምን ይህ እንደተደረገ እና ያደረገውን ሰው በፅሁፍ እንዲያቀርብ ለየካቲት 11 ቀን 2007 ዓ.ም እንዲያቀርብ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

ሦስቱ ጋዜጠኞች እና ስድስቱ ጦማሪያን ደኛው ይቀየርልን ሲሉ ያቀረቡት አቤቱታ አግባብ አይደለም ያለው ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ አንቀፅ 2519 መሠረት የ500 ብር ቅጣት ይቀጡ የነበረው በስሜታዊነት ነው በማለት መቀጫውን ውድቅ አድርጓል፡፡ በየካቲት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. የእምነት ክህደት ቃል በአዲስ የመሀል ዳኛ መሠረት ይሰማል ሲል ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን አስተላልፏል፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) : መጨውን የኢሕአዴግ የሞኖፖል ምርጫ ጥሪ ተቀብለው ወደ ምርጫ እንገባለን ያሉ የተቃዋሚ ድርጅቶች ያስመዘገቧቸውም እጩ ተወዳዳሪዎች አስፈላጊዉን ገንዘብ እና ጥቅማ ጥቅም በመስጠት የመደለል ስራ ሊጀመር ነው ሲሉ የውስጥ አዋቂ ምንጮች ከኢሕአዴግ ጽ/ቤት የተገኙ መረጃዎች ጠቆሙ::የተቃዋሚ ድርጅቶች እያቀረቡ ያሉትን እጩዎች ስም እና ሙሉ አድራሻ ለኢሕአዴግ ጽ/ቤት የሚያስተላልፈው የገዢው ፓርቲ አጋር ተቋም የሆነው የምርጫ ቦርድ በክልል ወኪሎቹ እጮዎችን ከደህንነት አባላት ጋር በመሆን የማግባባት ስራ እንዲሰራ እና ከኢሕአዴግ ጽ/ቤትም አስፈላጊው በጀት ተመድቦ በሰፊው አፋጣኝ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ተወስኗል::

አብዛኛዎች የብሄር ድርጅቶች ወደ ምክር ቤቱ እንዲገቡለት የሚፈጋው ኢሕአዴግ ለታማኝ ተቃዋሚው ኢዴፓ እና በመድረክ ፓርቲ ውስጥ ላሉ ተለጣጭ ወሬ አቀባይ ተለጣፊ አመራሮች ወንበር እንዳዘጋጀላቸው ታውቋል::የአሜሪካ እና የአውሮፓ ሕብረት ዲፕሎማቶች ወያኔ ከተቃዋሚዎች ጋር እንዲወያይ እያደረጉ ያለው ጥረት አንድነትን በማፍረስ እና መኢአድን በመበጥበጥ ቀጣይ እኩይ ስራዎችን በመስራት ዲፕሎማቶቹ ያቀረቡትን ሃሳብ ለማጣመም ቢሰራም ወያኔ እንዳልተሳካለት ታውቋል::ወያኔ የሰራቸው ጸረ ተቃዋሚዎች እኩይ ተግባራት በዲፕሎማቶች ተቀባይነት አለማግኘቱ ታውቋል::

ሆዳሞችን እና አንሾካሻኪዎችን በዚህ በሰለጠነ ዘመን ላይ በመፍጠር የሚታወቀው የወያኔው ጉጀሌ ተጨማሪ አምስት አመታት በመግዛት ኢትዮጵያን ለመበታተን እና ሃግራዊ አንድነት እና ፍቅር ለማጥፋት ቢሰራም አልተሳካለትም:: እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል የሚለው ወያኔ በአለም አቀፍ ደረጃ ወንጀሉ የታወቀለት እና በሕግ የሚፈለግ አሸባሪ ድርጅት መሆኑን የሚወጡ ዘገባዎች ሲያመለክቱ ኢትዮጵያውያን ሃገራችንን ከመንግስታዊ አሸባሪ ውድመት በጋራ ሁነን የመከላከል የዜግነት ግዴታ አለብን በማለት ለመናገር እወዳለሁ::

በመድብለ ፓርቲ ሰርዓት ስልጣን ይያዛል ብሎ ማመን ህዝቡን ማታለል ነው

የአንድነት ፓርቲ አላማዎችና እሴቶች በገዢው ፓርቲ እና ምርጫ ቦርድ ህገወጥ ሴራ አይጠፋም!!! – ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሠጠ መግለጫ

ገዢው ፓርቲ ለጻፋቸው ህጎችም ሆነ ይህን እንዲተገብሩ ኃላፊነት የወሰዱትን ሰዎች ክብር በሚያዋርድ መንገድ፤ በየደረጃው ያሉ ምርጫ ቦርድ ኃላፊዎችም ለመዋረድ ፈቃደኛ ሆነው በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) አባላት አንድ ድምፅ ለማግኘት ለተቸገረ፤ ነገር ግን ለገዢው ፓርቲ ለመላላክ ቁርጠኛ ለሆነ ግለሰብ ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱ የሚታወስ ነው፡፡ ይሁን እንጂ አንድነት ፓርቲ የተቋቋመበት መሰረት የምርጫ ቦርድ ዕውቅና ሳይሆን በእያንዳንዱ አባላት ዘንድ የሚቀጣጠለው የነፃነት ስሜት እና ኢትዮጵያዊነት ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲን መንፈስ፣ አላማዎቸና እሴቶች በዚህ ዓይነት እኩይ ደባ ከአባላትና ደጋፊ አዕምሮ ማውጣት አይቻለም፡፡

የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በገዢው ፓርቲ ደህንነት የተደራጁ የፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔ አባላት ያልሆኑ ሰዎች ያካሄዱትን ህገወጥ ስብሰባ ጉባዔ ነው በማለት እውቅና ሰጥቻለሁ ሲል፤ የተሰበሰቡት ሰዎች የአንድነት አባላት መሆናቸውን እና የጠቅላላ ጉባዔ ተወካይ መሆናቸውን አረጋግጣችኃል ወይ? ለሚል ቀላል የጋዜጠኛ ጥያቄ መልስ መስጠት አልቻሉም፡፡ ዕቅዱም አንድነትን እንደተቋም ማፍረስ ስለነበር ይህን ሊያስፈፅም ለሚችል ተላላኪ መስጠታቸውን በይፋ ከተናገሩ በኋላ በማግስቱም የፓርቲውን ፅ/ቤት በጠብመንጃ አፈሙዝ አስወርረው ለህገወጥ ቡድን በህገወጥ መንገድ አስረክበዋል፡፡
የአንድነት ፓርቲ በዚህ ዓይነት ህገወጥ ድርጊት የሚፈርስ አይደለም፡፡ የአንድነት አባላት በየትም ቦታ የምትገኙ ሁሉ ይህን ህገወጥ እርምጃ በፅኑ እየተቃወማችሁ ለነፃነትና ለኢትዮጵያዊነት የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመከፍል ዝግጁ መሆን ይኖርባቸኋል፡፡ አንድነት ፓርቲ በሰላማዊ ትግል ስልት የሚያምን በመሆኑ ይህን ትግል በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል አበክሮ ይስራል፡፡ እያንዳንዱ አባልም አሁን በተፈጠረው ሁኔታ ሳይደናገጥ ለሰላማዊ ትግል ያለውን ፅናት እንደሚያስቀጥል እምነታችን ነው። በአንድነት ስራ አስፈፃሚ እምነት አሁን ባለው ሁኔታ የመድብለ ፓርቲ ፖለቲካ ተቀበረዋል የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰናል።

በመሆኑም ስርዓቱ ለመድብለ ፓርቲ ፖለቲካ የሚመች የአስተሳሰብ ለውጥ እሰካላመጣ ድረስ ምርጫን በየአምሰት ዓመት የሚደረግ ክብረ በዓል አድርጎ ለማድመቅ እና የህዝብ ሀብት ለማባከን በሚደረግ ሂደት ተሳተፊ ለመሆን አዲስ ፓርቲ መመስረትም ሆኖ አሁን ካሉት ፓርቲዎች ጋር ተቀላቅሎ መታገል የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ ምክንያቱም እነርሱም ልከ በአንድነት ላይ እንደተደረገው በሀይል እንዲፈርሱ የማይደረጉበት ምንም ዓይነት ዋስትና አለ ብለን ስለማናምን ነው። ከዚህ በኋላ በመድብለ ፓርቲ ሰርዓት ስልጣን ይያዛል ብሎ ማመን ህዝቡን ማታለል ነው የሚል ፅኑ እምነት አለን፡፡ ነገር ግን አሁንም የፓርቲ ፖለቲካ አላበቃም ብለው የሚያምኑ የአንድነት አባላት ካሉ በራሳቸው ነፃ ውሳኔ ወደ ፈለጉት ፓርቲ ተቀላቅለው የመታግል መብታቸው የተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ ህዝብ አሁን ካለበት አምባገነናዊ ስርዓት ተላቆ ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሸጋገር ለማድረግ ህዝቡ የትግሉ ባለቤት ሆኖ የስርዓት ለውጥ እንዲመጣ እኛም የበኩላችንን ሀገራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ቁርጠኞች ነን፡፡

ድል የህዝብ ነው!!!
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)

የአንድነት አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ

ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት› በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስታወቁ፡፡
በእነ በላይ ፍቃዱ አመራርነት አንድነት ፓርቲን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሲመሩ የነበሩ አመራሮች ዛሬ ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ከቀድሞ ፓርቲያቸው አንድነት ጋር የፕሮግራምም ሆነ የስትራቴጂ ተመሳሳይነት ወዳለው ሰማያዊ ፓርቲ ተቀላቅለው ሰላማዊ ትግላቸውን ለመቀጠል መወሰናቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
መግለጫውን የ‹ቀድሞው አንድነት ፓርቲ› አፈ ጉባዔ የነበሩት አቶ አበበ አካሉ፣ ምክትል አፈ ጉባዔው አቶ ፀጋዬ አላምረው፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ እንዲሁም የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ሌሎችን በመወከል ሰጥተዋል፡፡

‹‹የምናምነው በሰላማዊ ትግል ብቻ ነው፡፡ ይህን ሰላማዊ ትግል ለመምራት ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ብቁ ነው ብለን በማመን ፓርቲውን ተቀላቅለናል›› ብለዋል በመግለጫው ላይ የተወከሉት አዲሶቹ የሰማያዊ አባላት፡፡
በዚህ መሰረትም በርከት ያሉ አመራሮችና አባላት በይፋ የሰማያዊ ፓርቲ የአባልነት ፎርም ሞልተዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን አስመልክቶ መግለጫ ለመስጠት ወደ ሰማያዊ ቢሮ ባቀኑበት ወቅት ፖሊስ ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ድረስ በመግባት ‹‹በሰማያዊ ስም መግለጫ የሚሰጡ አካላት እንዳሉ ሰለሰማን ነው›› በሚል ለፓርቲው አመራሮች ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡
Image

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች በዛሬው እለት ካንጋሮ ፍርድ ቤት ቀርበዋል::
Image
– ጋዜጠኛ ኤዶም ጸጉሯን በመላጨት ኢፍትሃእኢነት እና ዘረኝነት መስፋፋቱን በይፋ ተቃውማለች::
– የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ዳኛ እንዲቀየርላቸው ማመልከቻ አቅርበዋል::
Minilik Salsawi
በዛሬው እለት ፍርድ ቤት የቀረቡት ዞን ዘጠኝ ጦማርያን ጋዜጠኞች እንዲሁም የዲብርሃን አዘጋጅ የሆነው ዘላለም ወርቃለማሁ እና ከጋምቤላ በአሸባሪነት የተፈረጁ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል::በኢትዮጵያ የሆላንድ ኤምባሲና ሌሎች ዲፕሎማቶች በፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለመከታተል ተገኝተዋል::

በዛሬው እለት ጋዜጠኛ ኢዶም ጸጉሯን በመላጨት በወያኔ መንግስት እና በእስር ቤቱ ያለውን በፍርድ ቤቱ የሚታየውን አድልዎ የሚደርሰውን ኢፍትሃዊነት እና ዘረኝነት በመቃወም አሳይታለች::..ተከሳሽ ተብለው በወያኔ የተፈረጁት ወገኖቻችን ዳኛው እንዲቀየሩላቸው የተየቁበትን አቤቱታ ከታች ያንብቡት::
ImageImage

Image

http://www.eaglewingss.com/
ተከለከለ አሉ የንጉስ ኣዳራሽ … የክት ያልለበሰ አይገባም በጭራሽ!

ተከለከለ አሉ … የንጉስ ኣዳራሽ
የክት ያልለበሰ … አይገባም በጭራሽ

የክት ልብሱን’ማ የሃገሪቱን ኣንጡራ ሃብት እንክት አድርገው ከበሉት በላይ ማን አሳምሮ ሊለብሰው? ባይሆን በኮፒ ራይት ካልተጠየኩ- እኔው ራሴ አሻሽዬ ብዘፍነውስ? ተከለከለ አሉ የንጉስ ኣዳራሽ … ተኩሶ ያልለበሰ አይገባም በጭራሽ !

ምርጫ እና ተቃዋሚ ድርጀቶችን በለመለከተ፡ ሰሞኑን የጦር ሰራዊቱ ልበል የጦር ኣራዊቱ አውራ ያሳዩት ንቀትና ዛቻ ሲገርመን፤ የፖሊስ ኣራዊቱ እርግጫ ተከተለ። ይኼ ነገርርር … ብለን ገና የጀመርነውን ዓረፍተ-ነገር ሳንጨረስ፡ ምርጫ ቦርድ ድሞን ደመደመው ፦ ምርጫ’ም መኢአድ’ም አንድነት’ም የሉም አለን። ለነገሩ ”ምን ተስፋ አይቆርጥም” ሆኖብን አንጂ፡ ሰዎቹ ከ-እምበር ተጋዳላይ ወደ እብሪተኛ ገዳይ የተሻገሩበት የ97ቱ ምርጫ፡ አሳፋሪም አስተማሪም ምዕራፍ ነበር።

ተቃዋሚ ድርጅቶች አድገው እና ረዝመው ከንጉሱ አዳራሽ በተጠጉ ቁጥር፡ መንግስት እንደ ሸገር መናፈሻ ጥድ በራሱ መልክ እና ቅርጽ አሳጥሮ ይከረክማቸዋል። ትላንት ቅንጅት፣ ዛሬ ደግሞ አንድነት እና መኢአድ። ታዲያ ምን ተሻለ ጓበዝ? በክቱ ልብስ ካልሆነ፥ ያው ያዘቦቱን (የልምዱን) ተኩሶ መግባት እንጂ.

ፍቅርሽ አስጨንቆ … መላወስ አቃተኝ
ተደናበርኩለሽ … ጥይት እንደሳተኝ
ሳተና ነበርኩኝ … ተኳሽ በመውዘሬ
ለዘበናይ ብቻ … እጄን ሰጠሁ ዛሬ

እርግጥ ነው የሩቁንም ሆነ የቅርቡን ሰላማዊ ሰልፍ ስንታዘብ፡ ህዝባችን ከፍተኛ ጨዋነት ይታይበታል። ፖሊስ ከሰራዊት ምግባርና ተግባር ወጥቶ አራዊት ሆኖ ሲናከስና ሲራገጥ፡ ህዝቡ ዱላወን በትዕግስት ተቀብሎ፦ ደሙን አፍስሶ፣ አጥንቱን ስብሮ ወደ ቤቱ በወሳንሳ ይገባል። በወገናዊነቴ ስቃዩና መከራው ቆጭቶኝ ስሜታዊነት ቢፈታተነኝም፥ ትዕግስቱን ግን ከምስራቅ አውሮፓና ከሰሜን አፍሪካ ሰልፈኞች ጋር አወዳድሬ ”ለምን?” ብዬ አልጠይቅም። ወያኔ እንጂ ዘረኛው፡ ህዝቡ አይደለ’ማ። መንግስት እንጂ ለህዝቡ ፍቅር ያጣው፡ ህዝቡ ዛሬም ቢሆን በመቻቻል አብሮ የመኖር ባህሉን አልጣለውም። ጫካ ውሎ ጫካ አድሮ፡ አውሬ ሆኖ ለመናከስ፣ ያደገበትን የከተማ ስርዓትና ህብረተሰባዊ ገብረ-ገብ ለመፈረካከስ ህዝቡ ወያኔ ወይንም የዱር እንስሳ አይደለም። ያ ባይሆን ኑሮ’ማ ሳተናነቱና ተኳሽነቱ የዘር ነበር። የትላንቱ የአያት ቅድመ-አያቶቻችን እልህ ኣሻራ፡ በዚህ ትውልድ ደም ወስጥ ደብዛው ጠፍቷል የሚል ዜጋ የለም።

ውስጡን እንፈትሽው ከተባለም፥ የዩክሬንና የካይሮ አብዮተኛ እንደ ረሃብተኛ በአዉሮፓና አሜሪካ፡ አልፎም በሀይማኖትና በወገንተኝነት በተደራጁ መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት እየታገዘ፦ ከብስኩት እስከ ወተት፣ ከውስጥ-ልብስ እስከ ብርድ-ልብስ በሬሽን እየታደለው ጌታዋን እንደተማመነችው በግ ላት ውጪ አደረ እንጂ፥ እንደኛዎቹ ደፋር ወንዶች፡ አንድ ሃገሩን አፍቅሮ አንድ ራሱን ሆኖ መች ተሰለፈ? መቼ ተቀጣቀጠ? ባይሆን፦ ሰልፉ እና ተቃውሞው የተፈለገውን ትኩሳት እንዲያሳይ ”ዲያስፖራው ምን ሰራ? ምን አገዘ?” የሚለውን ጥያቄ ማንሳት አግባብ ነው። ከመደብደብ፡ ይደባደብ ካልን፦ ለደሙ ማድረቂያ፣ ለቁስሉን ማጠቢያ፣ ለራሱ እና ለቤተሰቡ መደገፊያ፣ ጉልበት ሞራል የሚሆነው ምን ረብ ያለው ስራ ተሰራ? ፖለቲካችን- የአፄ ምኒልክ አብራክ ፡የአቦይ ስብሃት በረከት፡ የሌንጮ ለታ ብላቴና እያለ ከራሳችን አልፎ ግቢ ውስጥ ኣንድ ሆኖ የሚኖረውን ህዝብ እንዲበታተን ከመመረዝ ወጪ ምን ወዝ ኣለው? ብሎ መጠየቅ አግባብ ነው።

በፍቅር ማነቂያው … ዶሮ እንዳይል በከንቱ ኧሪ አንቺን ወዶ
ክራሩን ሰት ሰሚ … ብቅ በይ ቆሜያለሁ ከበርሽ ማዶ

እስቲ ዘር፣ ድርጅት ሳይከፋፍል፡ ሙስሊም ክርስቲያን ሳይል፡ በአደባባይ በዱላና በሰደፍ የሚቆስለውን ሰልፈኛ የሚያሳክም የሚያግዝ አንድ የጋራ ጥሪት (fund) ይኑረን? እስቲ የወገን ድካም እና ኧሪታ ከንቱ እንዳይሆን ከጎኑ ሆነን ትግሉን እናክርረው? በሰለፉ እና በእምቢተኝነቱ ሂደት የሚደሙትን፣ የሚቆስሉትን፣ ኣልፎም ከስራና ከትምህርት ገበታቸው ላይ የሚታገዱትን የሚበዥ ኣንድ ኣካል ሲቋቋም፣ ወገናዊነቱና የትግል አጋርነቱ በተግባር ሲረጋገጥ፡ ያኔ የተፈለገውን ትኩሳት በአደባባይ ማየት ይቻላል። ለዚህም በጎ ተግባር፡ ራሳችንንም ሆነ እኛን የመሰሉትን ለማሳመን፣ አምነንም ግዴታችንን ለመወጣት አቅም እና ጉልበት እንዳለን ለአፈታ አልጠራጠርም።

አፈር ጭቃው ሲቆፈር፣ በማጥ በድጡ ህዝብ ሲያልቅ ዳር ቆመን ስንታዘብ ውልን፤ ደልድዩ ተሰርቶ ሲያልቅ’ና ሲመረቅ፥ መቀስ ይዞ ሪቫን ለመቁረጥ፣ አበባ ታቅፎ ከፊት ለመራመድ መሽቀዳደም፡ ያስተዛዝባል። ዛሬ ህዝባችን መሻገሪያው እንጂ የጠፋው አሻጋሪው አይደለም። ስልጣኔ እና ዕውቀት ወረርሽኝ ሆነው፡ በትንፋሽ’ና በንክኪ እንደማይተላለፉ የመጣነው አየነው፡ የቀሩትም አደመጡት። ውጭ ሃገር መኖሩ፡ ከፈረንጅ ጋር ውሎ ማደሩ፡ ሀገርቤት ያለውን ፖለቲካና ፖለቲከኛ አስንቆ እኔ ድልድይ ሆኜ አሻግርሃለሁ ለማለት ድፍረት አይሆንም። ይልቅስ ብቅ ብሎ ተቀላቅሎ፡ ትግሉን ጎን ለጎን –በብረት እና በብልሃት- ማስኬዱ ይበጃል።

አይወጣም ደረጃ … ቢፎክር ሴቼንቶ
እንደ እኔ ካልሄደ … በፍቅር ተገፍቶ
መድፈሪያሽ ወርቅ ነው … ብርም አይገዛሽ
ልብ የሌለው ሀብል … ግድም አይሰጥሽ

ወያኔ “ተፎካካሪ ድርጅት ስለሌ እንጂ ስልጣኔን በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለመልቀቅ ዝግጁ ነኝ“ ብሎ ሰለፎከረ፣ ይወጣል፣ ይሄዳል ብሎ ማሰቡ ዘበት ነው። ሰባ የጦር ጄነራል፣ ሺህ መቶ-አለቃ (ቼንቶ) – በፍቅርም ይሁን በፀብ፣ በአጥንትም ይሁን በብረት ካልተገፋ በስተቀር እንዴት ይነቃነቃል? ዛሬማ ብሩንም ወርቁንም ይዘውታል፤ ምን ያስደነግጣቸዋል? ከኪሳቸው ተርፎ- ህዝቡ የባለቤትነት ጥያቄ ቢያነሳ እንኳ በሚል ስጋት፡ “የዲያስፖራው የጋራ ሃብት ነው” ብለው ሊያታልሉት፡ ህዝብ ዘርፈው፣ ቅዬ ንደው እራሳቸው ለሚገነቡት ፋብሪካ ተለጣፊ ባለሃብት የሚሆን ውሻና ድመት ከባህር-ማዶ ማፈላለግ ጀምረዋል። ምናለ – ህዝቡም ደደብ፣ አዲስም ደደቢት አንዳይደሉ ቢገባችው? ለነገሩማ ንቀት ይዟቸው እንጂ ልዩነታችንንስ ተረድተወታል።

እስቲ ላለመናቅ ትግላችን ሀሞት ይኑረው፤ የምር ሆኖ ይምረር። እንደዛ ጥርሱን እንደ በቆሎ እሸት ፈለፍሎ አንደበላው ሆዳም ቀልደኞች አንሁን። እነሱም ግድ ያላሉን፦ ከማወራትና ሀ-ብሎ አፍን ከመክፈት ውጪ ልብ የላቸውም ብለው ነው። ያለውን አለ፣ የሌለውን ደግሞ የለም እንበል። በባዶ መኮፈስ፣ ገብስ ሳይሆን ወረቀት እየበላ የሚዘለውን ፈረስ መጋለብ አስናቀን እንጂ ወንዝም አላሻገረን። ታላላቆቻችን በኣዲስ ዘመን በሳተላይት ያደሉን ኣዲስ የትግል ስልትም ቢሆን፡ አንደ ታናናሾቻችን የእንቁጣጣሽ ንድፍ- በወረቀትና በቀለም አሽብርቆ ቀረ። የወሬ ሳይሆን የስራ፣ የተግባር ዓመት ነው የተባለለትም 2007፡ ይኸው ፀጥ ረጭ እንዳለ የስነ-ምግባር ዓመት መስሏል፤ ፀባይ የምንገዛበት። ጆሮዬ የቱንም ያህል ቢረዝም፡ በእግሮቼ ኣውራ ጣት ቆሜ ብንጠራራም፡ ከገመትኩት አካባቢና ድንበር 7000 ማይልስ ርቆ ዲሲ ላይ ጠቢቡ ሳይሆን ጠባቡ ሰለሞን ከተኮሳት ጥይት በስተቀር፡ የሰማሁት ኮሽታ፣ ያየሁት ብልጭታ የለም። እኛ ሳንተኩስ ቀኑ ተተኩሶ ዓመቱ ተጋመሰ። ነው ወይስ- ዘመኑ ሰልጥኖ፣ መሳሪያውም ዘምኖ – ታንክ እና ክላሹም አንደሽጉጡ ሳይለንሰር (silencer) ተገጠመለት?

ጓበዝ፥ ብዙ ከማውራት ትንሽም ብትሆን የአቅምን መስራት ይበጃል – ያስከብራል። የመሀሉ ጦር ደፍሮ ለጨበጣው ሲቁነጠነጥ፡ እኛ “አቅም አለን” ካልን- ዳር ሆነን ለቀናት ቢያንስ ለሰዓታት የተኩስ ሽፋን መስጠት ይሳነናል? አለበለዚያ፦ መድረኩ ስለቀረበ ብቻ ሀ፡ብሎ አፍን መክፈቱ ሌላ ትርጉም እስካልተሰጠው ድረስ ለጠላት ማዛጋት፡ ለወዳጅ ማዘናጋት ነው። አሁን ይበቃል። እውነትን ተናግሮ ህዝብን ወደ ኣንድ አቅጣጫ መመለሱ፡ ሀይልን አጠናክሮ ትግልን ያጎለብታል፣ ድልን ያቀርባል። ልብ ሳይኖረኝ አፌን ከፍቼ ሀ-ብል፡ ማን ግድ ሊለው?

ይውጣ ይወጣ … እግሬ ይዛል በእርምጃው
ከሷ አይብስም … ሰባ ደረጃው

የዛሬ ፅሁፌን ከማጠቃለሌ በፊት፡ የአንድነት ሃይሎች በድፍረት የቆረጡለትን- ተመልሶ አደባባይ የመውጣት ወሳኔ ላደንቅ እወዳለሁ። እርግጥ ነው የተከፈለውና የሚከፈለው መስዋዕትነት ከባድ ነው። ሆኖም ግን፡ ለእናት ሃገር ሺ ጊዜ ቢሰለፉላት፣ እግር ቢዝል – ቢደክምላት ያንስባታል እንጂ አይበዛባትም። የሶስት ሺህ ዘመን ማንነትን፣ የአብሮነት ፍቅርንና አንድነትን ለመጠበቅ ሲባል፦ ሰባ አይደለም ሰባ ጊዜ ሰባ-ሰባት ደረጃ ይወጣል፤ ሰባ አይደለም ሰባ ጊዜ ሰባ-ሰባት መሰናክል ይዘለላል።

መጣሁ ከኮሪያ ይዤልሽ ሰዓት … ይቀጥላል

*PS. የዘፈኑ ስንኝ ትርጉም ሙሉ በሙሉ የዚህ ፅሁፍ ፀሀፊ እንጂ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከግጥሙ ደራሲም ሆነ ከዘፋኙ ፍቺ ጋር መስተሳስር የለውም

አንድነቶች በምርጫ ጨዋታዉ ግጥሚያዉ ሳይጀመር አሸንፈናቸዋል፤በሰላማዊ ትግሉም የመጨሻዉን ሽንፈት ይጎነጫሉ!!
Image
ምርጫ 2007 ለለዉጥ ብለን ተነሳን፡፡በሙሉ ልብና ዝግጅት ለህዝቡ አማረጭ ለመሆን ለምርጫ የሚየስፈልገዉን ግብኣት ይዘን ተሰለፍን፡፡አጥቂዎችን ከተከላካዮች ለይተን ደጀኖችን ከኃላ አሰልፈን በትምህርት ዝግጅትና በአባላት ጥራት እንዲሁም በሃሳብ የበላይነት ከኢህአዴግ የሚበልለጡ እጩዎችን አዘጋጀን፡፡ከሃቀኛ ፓርቲዎች ጋር ላለመወዳደር በሰጥቶ መቀበል መርህ ለመዳረደርና ለህዝቡ ብቁ ተመራጭ ይዞ ለመቅረብ ተደራዳሪ ኮሚቲም አቋቋምን፡፡ህወሓት ሃሳብ የለዉም፡፡ቢኖረዉም ያረጀ ነዉ፡፡ለዚህ ትዉልድ አይመጥንም፡፡የሚጮኸዉን ያህል ቀርቶ ከኣባለቱ ሩብ ያህል እንኳን አድማጭ የለዉም፡፡እኛ ብዙ ተምረናል፡፡ከወደቁትና ዛሬም በጽናት ከሚታገሉቱ ቡድኖችና ግለሰቦች ትምህርት ቀስመናል፡፡ከአሮጌዉ ህወሓትም ይሁን ከወጣቱ ሰማያዊ ፓርቲ የምንቀስመዉን ቀስመናል፤ለመማር ዝግ አይደለንም፡፡ለዉህደትና ለትብብርም እንዲሁ፡፡እደሉም ስላልነበራቸዉ እነሱ የብሄረሰብን ጥያቄ ከነስታሊን መጽሃፍት የቃረሙት ሲሆን እኛ በተግባር አብርን ኖረን የምናዉቀዉ፤በብሄረሰብ መሰረት ከተደራጁ ሃይሎች ጋር ግንባር ፈጥረን ችግረቸዉን ተረድተን የህዝብን ጥያቄ በተግባር ለመመለስ የቆረጥን በህዝብና በሃገር ሉኣለዊነት የማንደራደር የዘመኑ አስተሳሰብ ዉጤት ነን፡፡በመሳሪያና በገንዘብ ሳይሆን በሃሳብ የበላይነት ኮርተን፤ ዳኛዉን ሳይሆን ህዝቡን ተማምነን ለምርጫ ጨዋታዉ ዝግጁ ሆነን ነበር፡፡
ሽንፈቱ ከወዲሁ የገባዉ ህወሓት መጋረጃ ዉስጥ ሆኖ ጨዋታዉን ከወዲሁ አበላሸዉ፤አንድነት ፓርቲን ቢያሸዉ ቢደፈጥጠዉ ጎማ ሆነበት፡፡አልፈርጥለት ሲል የመጨረሻዉን አደረገ፡፡በጠራራ ጸሃይ ከህግ በላይ በጉልበት ዋናዉን ቢሮ ወረረዉ፡፡ምን እንደወሰዱ ምንስ እንዳስገቡብን አናቅም፡፡እርጉዝ ሴት በዱላ መትተዉ የወርቅ ሃብል የወሰዱ፤ጽ/ቤት ገብተዉ ምን እንደሚያደርጉ መገመት ይቻላል፡፡ያለ ህግዊና በእማኝ ፊት ርክክብ እንደልማዳቸዉ የህዝብ ሃብት ነጥቀዋል፡፡በሂደቱም ግለሰቦችና የህወሓትን ተግባር ለመፈጸም የተቋቋሙ ተቋማት ጥቁር ታሪካቸዉን ሲያኖሩ በእስር እየማቀቁ ያሉቱ የለዉጥ ሃይሎችና በዚህ ሂደት የለዉጥ ሃይሉን ከሚመራዉ ጋር የቆሙ የእንድነት አባላትና ደጋፊዎች ታሪካቸዉን በወርቅ ቀለም ጽፈዉ አኑረዋል፡፡እንዲሆም ድርጊቱን በማዉገዝ ከጎናችን የቆማችሁ ሁሉ በነጻነት ትግሉ የክብር ቦታ አላችሁ፡፡
አንድነቶች በበምርጫ ጨዋታዉ ግጥሚያዉ ሳይጀመር አሸንፈናቸዋል፤በሰላማዊ ትግሉም የመጨሻዉን ሽንፈት ይጎነጫሉ፡፡ ዛሬም የነጻ አዉጪን ስም የተሸከመዉ ህወሓት የሚያስበዉ እንደራሱ ነዉ፡፡የፓርቲ ስም፤አርማና ማህተም በዚህ ትዉልድ ቦታ እንደሌላቸዉ አልተረዳዉም፡፡የትዉልዱ ጥያቄ በእኩልነት ላይ መሰረትዋን ያኖረች ጠንካራ ሃገር እንጂ እወክለዋለሁ የሚለዉን ህዝብ እንኳን በበለጠ የሚያፍን የፓርቲ ስም አይነት አይደለም፡፡የአንድነት ፓርቲ ፕሮግራምና የኛ ራእይና በኛና በህዝብ ልብ እንዲሁም በሌሎች ፓርቲዎች ዉስጥ እንደሚገኝ አልገባቸዉምና ፓርቲን ሲነጥቁ ሰላማዊ ትግሉን የገደሉ፤እኛንም የበተኑ መስሎአችዋል፡፡የለዉጥና የአንድነት ሃይል ይበልጥ ይጠናከራል እንጂ አይበተንም፡፡እርግጥ ነዉ የመድበለ ፓርቲ ስርኣትን አደጋ ላይ ጥለዉታል፡፡ህዝባዊ ሰላማዊ ትግሉ ላይ ግን ጉልበትና ተጨማሪ እድል ጨምረዉለታል፡፡ የአንድነትና የለዉጥ ሃይሎች ዛሬም ይበልጥ ቁርኝነታችንን በማጠንከር ለሰላማዊ ትግሉ መጎልበት ያለንን አቅም ልናበረክት ይገባል፡፡ሁላችንም እድሉን እንጠቀምበት፤የጠበቡ ቤቶችንም ለሁሉም እንዲሆኑ ባፋጣኝ እናስፋቸዉ !
ይህ ተዉልድ የቃል እዳ አለበት፤እነአንዷለምም እነ አሞራዉም የሚሉቱና እያሉ ያሉቱ ይህን ነዉ፤ ፍትህና ነጻነት በኢትዮጵያችን በትግላችን ይሰፍናሉ!!

አንድነት – መግለጫ

ጥር 21/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ የምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም ያለበትን ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በዚህ ደረጃ እንዲዋራድ ከጀርባ ሆኖ አመራር የሚሰጠው ገዢ ፓርቲም ሆነ መንግሰት በዚያው ልክ የሚገባቸውን የተዋረደ ደረጃ የያዙበት ዕለት ነው ብለን እናምናለን። አንድነት ፓርቲ አንድም የህግ ጥሰት ሳይፈፅም የሚያደርጋቸውን ሁሉ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በሀገሪቱ ህግ እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ በህግ ሽፋን የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና ሬዲዮ፣ የመንግሰት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር የከፈቱት ዘመቻ የመጨረሻ የሆነውን አንድም ህጋዊ መሰረት የሌለውን ህገወጥ ውሳኔ በአንድነት ፓርቲ እና አባላት ላይ አሰተላልፈዋል።

ገዢው ፓርቲና መንግሰት በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲነበብ ያደረጉት የፖለቲካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከወረቀት አልፎ በተግባር እንዳይታይ ግብዓት መሬቱን ፈፅመዋል። በዚህ ፀያፍ ተግባር ከፊትም ሆነ ከጀርባ ሆነው የተሳተፉ ግለሰቦችም ሆኖ ተቋማት በታሪክ ተገቢው የውርደት ቦታ እንደሚይዙ እምነታችን ነው። ይህ ህገወጥ አካሄድ ህጋዊ መሰመር እንዲከተል የበኩላቸሁን ድርሻ የተወጣችሁ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በሀገር ውሰጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ሁሉ በተለይ በገዢው ፓርቲ እኩይ ሴራ በሀስት ተወንጅላችሁ በወህኒ ቤት ለምትማቅቁ ታጋዮች ታሪካችሁ በወርቅ ቀለም ተፅፎዋል። በቀጣይም ያለምንም መዘናጋት እና ተሰፋ መቁረጥ በምናደርገው ሰላማዊ ትግል በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት ትንሳኤ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለንም።

የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በህገወጥ መንገድ ለሆዳቸው ባደሩ ጥቂት አንድነት ፓርቲ አባላት እና በአንድነት አባልነት በማይታወቁ የገዢው ፓርቲ ጥርቅሞች ለተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት ያነገብነው የነፃነት መንፈስ በምርጫ ቦርድ በሚሰጥ ሰርተፊኬትና ዕውቅና ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኝ ስለአልሆነ ለነፃነት የምናደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የምንቀጥል ሲሆን፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የአንድነት መዋቅሮች እና የአንድነት አባላት ለዚህ ህገወጥ ቡድን በግልፅ እውቅና እንዲነሱ እንጠይቃለን። ፓርቲያችን በመጨረሻ ሰዓት እንኳን ተፈትነው ለወደቁ ተቋማት እድል ለመስጠት ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ወሰኖ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ ቢሆንም፤ በዛሬው ዕለት ጥር 22/ 2007 ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የፓርቲያቸን ፅ/ቤት በፖሊስ ተወሮ የፓርቲው ንብረት ያለምን ህጋው ርክክብ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎዋል። በአሰተዳደር የተሰጠን ውሳኔ በፍርድ ቤት የማሰለወጥ ህጋዊ ሰርዓት እንዳለ ቢታወቅም ህገወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔን በፖሊስ ወረራ ለማሰፈፀም የተሄደበት መስመር ገዢው ፓርቲና መንግሰት አሁንም ከጫካ አሰተሳሰብ ያለመውጣቸውን እና የአውራ ፓርቲ ፍልስፍናቸውን በማናለብኝነት ለመተግበር መቁረጣቸውን የሚያሳይ ነው። በዚህ ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂው ትእዛዙን ያስተላለፈው ክፍል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል። ሰለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች፣ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት እንዲጎለብት ፍላጎት ያለችሁ ሁሉ ይህን እኩይ ተግባር በማውገዝ ተጨባጭ እርምጃ እንድትወሰዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ድል የህዝብ ነው!!!

ጥር 22/ 2007 ዓ.ም.

የተማሩ ናቸው። አገራቸውን የሚወዱ። በሕዝባቸውና በአገራቸው ዉስጥ የሚደረገዉ ግፍ እንዲቆም በጽሁፋቸው የሚመክሩ። ማንም ላይ ጥላቻ የሌላቸው። ኢፍትሃዊነትን የሚጠሉ ። አምባገነንነትን እንጂ ማንንም የማይጸየፉ። በጽሁፋቸው ፍቅርን ሰብከዋል። ነጻነትን አውጀዋል። «ዜጎች እንደ እንስሳ ታስረዉና ታፍነው መኖር የለባቸውም። ነጻነታቸውና ስብእናቸው ሊጠበቅላቸው ይገባል» እያሉ ተከራክረዋል። ለሰብአዊነት ተሟግተዋል። ሰው ሲከብር እንጂ ሲዋረድ፣ ሲነሳ እንጂ ሲወድቅ፣ ሲድን እንጂ ሲሞት፣ ሲበለጸግ እንጂ ሲደኸይ ማየት አልፈለጉም። በቢሯቸው፣ በቤታቸው፣ ሴቶቹ በቦርሳቸው፣ ወንዶቹ ደግሞ በኪሳቸው ቦምብ ወይም ፈንጂ አልተገኘባቸው። በድብቅ የዶለቱት ወይንም የሰሩት ነገር የለም። የጻፉትና የተናገሩት ሁሉም በግልጽና በአደባባይ ነው። የተወሰኑቱ አርቲክል ዘጠኝ ከሚባል ድርጅት ጋር ግንኙነት አላቸው። እነዚህ ወገኖች የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ( bloggers) ናቸው።

አርቲክል ዘጠኝ እንደ አይሰስ፣ ወይም አልካይዳ ያለ ደርጅት አይደለም። የአርቲክል 19 ድርጅት አመጣጥ እንደዚህ ነው። የተባበሩት መንግስታት የሰባአዊ መብት ድንጋጌ (THE UNIVERSAL DECLARATION OF HUMAN RIGHTS የሚባል አለ። የዚህ ድንጋጌ አንቀጽ 19 ( አርቲክል 19) «Everyone has the right to freedom of opinion and expression; this right includes freedom to hold opinions without interference and to seek, receive and impart information and ideas through any media and regardless of frontiers.» ይላል።

በዚህ አንቀጽ ላይ የተጻፈው ነጻነት በአለም ዙሪያ ሁሉ እንዲከበር ለመርዳት (አድቮኬት ለማድረግ) የተቋቋመ የሲቪክ ማህበር ነው፣ አርቲክል ዘጠኝ። ይህ ማህበር አርቲክል 19 የሚል ስያሜ ይዞ፣ በአሜሪካ፣ በአዉሮፓ ባሉ በርካታ አገሮች፣ በኬንያ፣ በቱኒዚያ ፣ በባንግላዲሽ ሳይቀር እውቅና አግኝቶ የሚንቀሳቀስ ነው። በአገራችን ዉስጥ በኢሕአዴግ መንግስት ተጋብዞ በምርጫ ዙሪያ ስልጠናዎች የሰጠ ድርጅት ነው።

ይህ የተባበሩት መንግስታት አንቀጽ 19 ድንጋጌ በኢትዮጵያ ፌዴራል ሕገ መንግስት አንቀጽ 29፣ ንኡስ አንቀጽ 1 እና 2 ላይ በግልጽ ተቀምቷል። «Everyone shall have the right to hold opinions without any interference.Everyone shall have the right to freedom of expression without interference. This right shall include freedom to seek, receive and impart information and ideas of all kinds, regardless of frontiers, either orally, in writing or in print, in the form of art, or through other media of his choice.» ይላል የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 29።

በተባበሩት መንግስታት የሰባአዊ መብት ድንጋጌ አንቀጽ ( አርቲክል 19) ወይንም የኢትዮጵያ መንግስት አንቀጽ 29፣ በኢትዮጵያ ተግባራዊ እንዲሆን የሚጽፉ፣ የተደራጁ ሰላማዊ ዜጎች ናቸው። ለሕገ መንግስቱ ፣ ለሕግ ከበሬታ ያላቸው ናቸው።

ነገር ግን ከዘመናዊነት ፍጹም የራቁ፣ በሚድል ኤጅ ይኖሩ ከነበሩ በአስተሳሰብ የማይተናነሱ፣ አዲስ አበባ ያሉ ገዢዎች ግን፣ ራሳቸው ያወጡትን ሕገ መንግስት ረጋግጠው ፣ ሽብርተኞች ናቸው በሚል ክስ ከሰዋቸው ከፍተኛ መከራና እንግልት እየፈጸሙባቸው ነው። ይኸው ለአሥራ ሰባተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ገና ጠፋተኛ ነኝ አይደለሉም የሚል ቃል አልሰጡም። አሥራ ሰባት ጊዜ ፍርድ ቤት ሄደዋል ? አዎን 17 ጊዜ።

እንግዲህ ይህ የሚያሳየው ኢትዮጵያ አሳዛኝና አሳፋሪ ግፎች የሚፈጸምባት አገር መሆኗን ነው። ኢትዮጵያ ለጥቂቶች ገነት፣ በአሥር ሚሊዮን ለሚቆጠሩ ልጆቿ ሲኦል የሆነች እንደሆነች ነው። ይሄን ለመቀየር ሕጋዊ በሆነ መልኩ እንቅስቃሴ ተደረገ። ይሄን ለመቀየር እነ ጆን ኬሪ ጠየቁ። ነገር ግን የሕወሃት ሽፍቶች ሊሰሙ አልቻሉም። እነርሱ ማሰር እንጂ መፍታት፣ መደብደብ እንጂ የወቀደን ማንሳት፣ ዜጎችን እንዲፈናቀሉና እንዲሰደዱ እንጂ ዜጎችን ማሰባሰብ አያወቁም። ጨካኞች ናቸው። ስብእና አይሰማቸው።

በመሆኑም እንደ አገር እንደ ህዝብ መቀጠል ከፈለግን እነዚህ ሰዎችን እነርሱ ካሰመሩት መስመር አልፈን መሄድ መቻል አለብን። የነርሱ ጭካኔ ሊያስፈራራን አይገባም። እነርሱ የፈለገ ጭራቅ ቢሆንም፣ ጥቂቶች ናቸው። እኛ ሚሊዮኖች ነን። በያዙት ጠመንጃ፣ አሁን እንደ ንስር ትልቅ ቢመስሉንም ፣ እኛ ሁላችንም ከተነሳም እንደ ዝንብ እናጠፋቸዋለን።

በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት ‹‹ፀረ- ሰላም ህፃናት››

አቶ ቀኖ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ውስጥ በጥበቃነት ይሰራሉ፡፡ አቶ ቀኖና ጎረቤቶቻቸው ሰብሰብ ሲሉ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ በተለይ ኢህአዴግ ስለሚወስዳቸው ህገ ወጥ እርምጃዎች፣ ስለተቃዋሚዎች ጥንካሬና ድክመት… የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ያወራሉ፣ ይወያያሉ፣ በሚያከራክሯቸው ነገሮችም ይከራከራሉ፡፡ ይህ የእነ አቶ ቀኖ ሰፈር ሰዎች የውይይት መድረክ በእነሱ ብቻ ተወስኖ አልቀረም፡፡ ጉዳዩ በመደጋገሙ ህፃናት ልጆቻቸው ሳይቀር ‹‹ሰማያዊ፣ አንድነት፣ መድረክ፣ ኢህአዴግ…..›› እያሉ የአቅማቸውንና የገባቸውን ያህል ያወራሉ፡፡ ቤተሰቦቻቸው ሲከራከሩና ሲያወሩ ከሰሙት! በዚህ አቋማቸውም ህፃናቱ ‹‹ፀረ ሰላም›› ተብለው ታስረውበታል፣ ተደብድበውና ይቅርታ ጠይቀውም ተለቀዋል፡፡

ማክሰኞ ጥር 19/2007 ዓ.ም ነው፡፡ ከቀኑ 11፡30 አካባቢ አራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘው መስከረም 2 ት/ቤት ተማሪዎች የሆኑት 14 ያህል ህጻናት ወደ ቤታቸው እየተመለሱ ነው፡፡ ህፃናቱ እንደወትሯቸው ከት/ቤተ መልስ እየተጨዋወቱ፣ እየተቀላለዱ፣ እየተሯሯጡ ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ ናቸው፡፡ መሃል ላይ ግን ቤተሰቦቻቸው በተደጋጋሚ የሚያነሱትን ጉዳይ አንስተው መከራከር ጀምረዋል፡፡ የ13 አመት እድሜ ያለውና የ6ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው የአቶ ቀኖ ልጅ ‹‹ኢህአዴግኮ ፈሪ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲን ይፈራዋል›› ይላል፡፡ ጓደኛው ደግሞ ‹‹ኢህአዴግማ የሚፈራው አንድነትን ነው፡፡›› ይላል፡፡ ሌላኛው ደግሞ ‹‹መድረክ የሚባል ፓርቲምኮ አለ፡፡ እሱንም ይፈራዋል፡፡ ኢህአዴግ ፈሪ ነው!›› ይላል፡፡ ሌሎቹም ቤተሰቦቻቸው ውሃ፣ መብራትና ኔትዎርክ ሲጠፋ፣ ኑሮ ሲወደድ፣ ሙስና ሲያስመርራቸው በስርዓቱ ላይ ከሚያሰሙት ሮሮ መካከል የሚያስታውሱትን እየጠቀሱ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ይከራከራሉ፣ ያወራሉ፡፡ ይቀልዳሉ!

ይህኔ ነው አስገራሚው ነገር የተከሰተው፡፡ ፖሊስ 14ቱንም ህፃናት በ‹‹ፀረ ሰላም›› እንቅስቃሴያቸው ከእነ ሙሉ የትምህርት መሳሪያቸው በቁጥጥር ስራ ካዋላቸው በኋላ በጥፊና በእርግጫ እያለ ወደ ወረዳ 7 ፖሊስ ጣቢያ ይወስዳቸዋል፡፡ ፖሊስ ጣቢያ ከደረሱ በኋላም ‹‹ተንበርከክ!›› ተብለው ‹‹ማን ነው ሰማያዊ፣ አንድነት፣ መድረክ እያለ ሲያወራ የነበረው?›› እየተባሉ ህፃናት ላይ ይፈፀማል ተብሎ የማይታሰብ ድብድባ ይፈፀምባቸዋል፡፡ ህፃናቱ ‹‹ፀረ ሰላም›› ለተባለው እንቅስቃሴያቸው ቅጣትና ማስፈራሪያ ከተደረገባቸው በኋላ ‹‹ከአሁን በኋላ አይደግመንም›› ብለው ይቅርታ ጠይቀው በ‹‹ፖሊስ ሆደ ሰፊነት›› ከምሽቱ 1 ሰዓት አካባቢ ከእስር ተለቀዋል፡፡

እነዚህ ህጻናት ‹‹ዳግመኛ አይለምደንም!›› ብለው ይቅርታ ባይጠይቁ ኖሮ ታስረው ሊያድሩም ይችሉ ነበር፡፡ ምን አልባትም ፖሊስ ‹‹ያልተፈቀደ ቅስቀሳ አድርገዋል፣ ህገ መንግስቱን ለመናድ ጥረዋል፣ ህዝብን ለማናወፅና አመጽ ለመቀስቀስ ተደራጅተው ተንቀሳቅሰዋል፣ ምርጫው ሰላማዊ እንዳይሆን እየሰሩ ነው….›› የሚል ክስ እንደማይመሰርት እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡ እስካሁን ፖሊስ ሲያቀርባቸው ካየናቸው አስቂኝ የቀጠሮ ማራዘሚያ ‹‹ምክንያቶች›› አንጻር ‹‹አብረዋቸው የሚማሩት ሌሎች ግብረ አበሮቻቸው አልተያዙም፣ ቢወጡ አሁንም ተመሳሳይ ‹ፀረ ሰላም› ተግባር ይፈፅማሉ፣ መረጃ ይደብቁብኛል›› በሚል ተጨማሪ ቀን ይሰጠኝ ላለማለቱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡

ስርዓቱን ለመከላከል ሲባል እስሩ እዚህ ደርሷል!

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
January 31,2015
የገዢውን ፓርቲና መንግስትን ሽፍትነት ያጋለጠው አንድነትን የማፍረስ የምርጫ ቦርድ ውሳኔ በኢትዮጵያዊን ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም!!!
ጥር 21/2007 ዓ.ም በኢትዮጵያ ታሪክ የምርጫ ቦርድ የሚባል ተቋም ያለበትን ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ በዚህ ደረጃ እንዲዋራድ ከጀርባ ሆኖ አመራር የሚሰጠው ገዢ ፓርቲም ሆነ መንግሰት በዚያው ልክ የሚገባቸውን የተዋረደ ደረጃ የያዙበት ዕለት ነው ብለን እናምናለን፡፡ አንድነት ፓርቲ አንድም የህግ ጥሰት ሳይፈፅም የሚያደርጋቸውን ሁሉ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብና በሀገሪቱ ህግ እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ በህግ ሽፋን የገዢው ፓርቲ ልሳን የሆነው ፋና ሬዲዮ፣ የመንግሰት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር የከፈቱት ዘመቻ የመጨረሻ የሆነውን አንድም ህጋዊ መሰረት የሌለውን ህገወጥ ውሳኔ በአንድነት ፓርቲ እና አባላት ላይ አሰተላልፈዋል፡፡
ገዢው ፓርቲና መንግሰት በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲነበብ ያደረጉት የፖለቲካ ውሳኔ በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ከወረቀት አልፎ በተግባር እንዳይታይ ግብዓት መሬቱን ፈፅመዋል፡፡ በዚህ ፀያፍ ተግባር ከፊትም ሆነ ከጀርባ ሆነው የተሳተፉ ግለሰቦችም ሆኖ ተቋማት በታሪክ ተገቢው የውርደት ቦታ እንደሚይዙ እምነታችን ነው፡፡ ይህ ህገወጥ አካሄድ ህጋዊ መሰመር እንዲከተል የበኩላቸሁን ድርሻ የተወጣችሁ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በሀገር ውሰጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ ሁሉ በተለይ በገዢው ፓርቲ እኩይ ሴራ በሀስት ተወንጅላችሁ በወህኒ ቤት ለምትማቅቁ ታጋዮች ታሪካችሁ በወርቅ ቀለም ተፅፎዋል፡፡ በቀጣይም ያለምንም መዘናጋት እና ተሰፋ መቁረጥ በምናደርገው ሰላማዊ ትግል በሀገራችን ኢትዮጵያ የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት ትንሳኤ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለንም፡፡
የምርጫ ቦርድ ተብዬው ተቋም በህገወጥ መንገድ ለሆዳቸው ባደሩ ጥቂት አንድነት ፓርቲ አባላት እና በአንድነት አባልነት በማይታወቁ የገዢው ፓርቲ ጥርቅሞች ለተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ ዕውቅና ሰጥቻለሁ ማለቱን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ አባላት ያነገብነው የነፃነት መንፈስ በምርጫ ቦርድ በሚሰጥ ሰርተፊኬትና ዕውቅና ማዕቀፍ ውስጥ የሚገኝ ስለአልሆነ ለነፃነት የምናደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል የምንቀጥል ሲሆን፤ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የአንድነት መዋቅሮች እና የአንድነት አባላት ለዚህ ህገወጥ ቡድን በግልፅ እውቅና እንዲነሱ እንጠይቃለን፡፡
ፓርቲያችን በመጨረሻ ሰዓት እንኳን ተፈትነው ለወደቁ ተቋማት እድል ለመስጠት ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ወሰኖ እንቅሰቃሴ በማድረግ ላይ ቢሆንም፤ በዛሬው ዕለት ጥር 22/ 2007 ከቀኑ ሰባት ሰዓት ጀምሮ የፓርቲያቸን ፅ/ቤት በፖሊስ ተወሮ የፓርቲው ንብረት ያለምን ህጋው ርክክብ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎዋል፡፡ በአሰተዳደር የተሰጠን ውሳኔ በፍርድ ቤት የማሰለወጥ ህጋዊ ሰርዓት እንዳለ ቢታወቅም ህገወጥ አስተዳደራዊ ውሳኔን በፖሊስ ወረራ ለማሰፈፀም የተሄደበት መስመር ገዢው ፓርቲና መንግሰት አሁንም ከጫካ አሰተሳሰብ ያለመውጣቸውን እና የአውራ ፓርቲ ፍልስፍናቸውን በማናለብኝነት ለመተግበር መቁረጣቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህ ህገወጥ ድርጊት ተጠያቂው ትእዛዙን ያስተላለፈው ክፍል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡
ሰለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣የሰብዓዊ መብት ተማጋች ድርጅቶች፣ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲሁም በኢትዮጵያ ሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሰርዓት እንዲጎለብት ፍላጎት ያለችሁ ሁሉ ይህን እኩይ ተግባር በማውገዝ ተጨባጭ እርምጃ እንድትወሰዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!!!
ጥር 22/ 2007 ዓ.ም
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

ማስረሻ ባደንጋ (አባስ) ሰሞኑን የኢትዮጵያ ፖለቲካ የመንደር ወሬ ሆኖ የከረመውና እስከአሁንም መጨረሻው ያለየለት ዋና ጉዳይ ሆኖ የሰነበተው ከወደ ኤርትራ የሚሰማው የሁለት ብረት ያነሱ ኃይሎች ውህደት ነው፡፡ ይህ ውህደት ከጅምሩ ግልፅነት የጎደለውና ብዙዎችን ግራ በማጋባቱ ለብዙ ትችቶች የተመቸና የተዳረገ ነበር፡፡ በኢትዮጵያ …

ከውህደቱ ጀርባ – ማስረሻ ባደንጋ (አባስ) Read more »

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ በተመለከተ መግቢያ በቦርዱ ዕዉቅና ያገኘዉና በስራ ላይ ያለዉ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ የ2001 ዓ.ም ስለመሆኑ፣ ደንቡ የፓርቲዉ አመራሮችም ሆነ አባላት መብትና ግዴታቸዉን አዉቀዉ በእንቅስቀሴዉ ዉስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል እንደሆነ፣ በአመራሩ/በበታች አካሎችና አባሎች መካከል ዴሞክራሲያዊ የሆነ መከባበር ላይ የተመሰረተ አሰራር ለመፍጠር እንደሆነ በግልጽ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ መኢአድ በአሁኑ ጊዜ በሁለት ቡድን በመከፈሉ የፓርቲዉ የስራ እንቅስቃሴ ተገቷል በሚባል ደረጃ ያለ ስለመሆኑ እንረዳለን፡፡ አሁን ተመርጠናል በሚሉት በእነ አቶ ማሙሸት አማረ ቡድን የተፈጸሙ የህግ ጥሰቶችን እንደሚከተለዉ ማንሳት ይቻላል፡፡ 1ኛ. የፓርቲዉ ፕሬዚደንትን ከጠቅላላ ጉባኤ አባላት መካከል መመረጥ እንዳለበት፣ የፓርቲዉ ተ/ምክትል ፕሬዚደንት ደግሞ የጠቅላላ ጉባኤ አባል መካከል ከመሆኑ ባሻገር የማዕከላዊ ምክር ቤት አባል መሆን እንዳለበት የፓርቲዉ ደንብ በአንቀጽ 7.4 እና 4.2.2 ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ይሁንና አሁን የተመረጡት ግለሰቦች በ2003 ዓ.ም ከፓርቲዉ አባልነት የተሰረዙ ከመሆኑም በላይ ለሶስት ተከታታይ ወራት የአባልነት መዋጮ ያልከፈለ አባልነቱ ቀሪ እንደሚሆን ስለሚደነግግ ለዚህ ኃላፊነት መስፈርቱን የማያሟሉ ሰዎች በመመረጣቸዉ የህግ ጥሰት ተፈጽሟል፡፡ 2ኛ. ፓርቲዉ አካሂጃለሁ የሚለዉን የጠቅላላ ጉባኤ ዉጤት ሪፖርት፣ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ጥቆማ ሲያደርግ እና ሌሎች የፓርቲዉን ወሳኝ ክንዉኖችን ሲያሳዉቅ በፓርቲዉ ማህተም የተረጋገጠ ሰነድ ማቅረብ እንዳለበት የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2000 አንቀጽ 20/1/ በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ ይሁንና ፓርቲዉ በዚህ አግባብ አረጋግጦ ሊያቀርብ አልቻለም፣ ይባስ ብሎ ህጋዊ ማህተም በሌሎች የፓርቲዉ ቡድን እጅ መኖሩ እየታወቀ ተመሳሳይ […]

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ /አንድነት/ በተመለከተ የፓርቲዉ የቦርድ ዕዉቅና ያለዉ መተዳደሪያ ደንብ የ2004 ዓ.ም ስለመሆኑ፣ ቦርዱ የrፓርቲዉን እንቅስቃሴ ከዚሁ የቦርዱ ዕዉቅና ካለዉ ደንብ አንጻር ሲመረምር እንደቆየና አሁንም ከዚያዉ አኳያ የመረመረ ስለመሆኑ ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡ ከፓርቲው ውስጠ ደንብ መግቢያ ስንነሳ፡- መግቢያ አንዱና ዋነኛዉ የህግ አዉጭዉን አካል ሃሳብ የምንረዳበት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከፓርቲዉ መተዳደሪያ ደንብ መግቢያ መረዳት እንደሚቻለዉ መተዳደሪያ ደንቡ የፓርቲዉ አመራሮችና አባላት የሚመሩበትና የሚገዙበት እንደሆነ፣ በፓርቲዉ አደረጃጀት መሰረት የተለያዩ አካላት ጤናማና ዴሞክራሰያዊ የሥራ ግንኙነት እንዲኖራቸዉ የሚያስችል፣ የስራና ኃላፊነት ክፍፍል የሚፈጥር እና ግልጸኝነትና የተጠያቂነት መርህ የሚፈጥር እንደሆነ በግልጽ ሰፍሮ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ይሄንን የህግ አዉጭዉን ሃሳብ ተከትሎ ስራዎች ሲተገበሩ አይታዩም፡፡ ደንብ የሚያወጣዉ የፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ነው፡፡ ሌላ አካል ቦርዱን ጨምሮ ማንም ሊያወጣላቸዉ አይችልም፣ አይገባምም፡፡ ነገር ግን ደንብ ከወጣ እና ለቦርዱ ቀርቦ ዕዉቅና ካገኘበት ጊዜ ጀምሮ የፓርቲዉ አመራርም ሆነ አባላት ለደንቡ ተገዥ መሆን ይጠበቅባቸዋል፤ ቦርዱም በተሻሻለው የኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ አዋጅ ቁጥር 532/1999 ዓ.ም. እና በተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2ዐዐዐ ዓ.ም. መሠረት ይሄንን ደንብ የማስከበር ኃላፊነት አለበት፡፡ አሁን ተመርጠናል በሚሉት በእነ አቶ በላይ ፈቃዱ ቡድን በኩል የተፈጸሙ ዋና ዋና የህግ ጥሰቶች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡ 1ኛ. የፓርቲዉ ፕሬዝዴንት ጨምሮ ኃላፊዎች አመራረጥ በተመለከተ በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 572/2000 አንቀጽ 8/2/ረ/ እና በፓርቲዉ ደንብ አንቀጽ 13.3.1 መሰረት በጠቅላላ ጉባኤ መመረጥ […]

http://www.eaglewingss.com/%E1%89%A0-%E … %E1%8B%AD/

በ ኖርዌጅያንዋ የሶስት ወር ፀሃይ
January 30, 2015
በ ኖርዌጅያንዋ የሶስት ወር ፀሃይ
Samson K.

By Samson K.

በሶስት ወሯ የፀሃይ ድምቀት
ሰዉ ራሱን ከፍቶ ሊያሳርግ የራስን ድብርት፤
ተደርድረዉ ውበት እና ድብርት
ዉስጠትና ዉጭ – ሊሆኑ የምድር ትዕይንት ፤
አንዱ ሊያራግፍ የታፈኑ የወራትን ድብርት ፣
የታፈነች ፅጌረዳም ድንግል የዉበት አሸት ፣
ራስዋን ፈልቅቃ አንደ ባህሩ እምቡጥ ቀንድ ኣውጣ –
ራሰዋን ልታሳይ -ራስዋን ልጣ – ከደመና ጋግርት ፤ዉበትን ልታዋጣ

የነፍሳት ህብረት በዝግመተ ጋግርት ላይ- – ለዚያ ድብርት፤ለጣዉንቱ ጭጋግ ጭንቀት
ለዚያ ቅዠት አዚም-፣ ዉግምት፣ ዝጋት፣ ግዚያዊ ስንብት
ሕይወት ጓጉታ ራስዋን ልተነፍስ ዉስጣዊ ስቃይዋን
ፍላጎትዋን ለሶስት ወርዋ ፀሐይ ንግስት፤

ፀሃይን ለመሞቅ የመሞቅ ግርግር -ለዉጭ ብርሃን ጨረር እሽቅድምድም
ሁሉ ራሱን ሰጥቶ ራሱን ከፍቶ ፀሀይቷን ሊቆዝም
የሰባን ፅልመት የደመና ጋግርት -ሊያቀልጥ ከራስ ላይ የራስ አዚም ፤
ሽብሽብ ቁርፍድ ቆዳ ከራስ ለጋ እንቡጥ ፅጌረዳ
መሳ ለመሳ ፣ስጋ ከነፍስ፣ ሳቅ ካዘን ፣ መደዳ- ለመደዳ
ታፍነዉ የከረሙ ከዛ ጋግርት ጭፍጝግ- የደመና ጓዳ ፤

ሁሉም ራሱን ፈታ- እሷን አምኖ ፀሃይቷን- ያችን….. ባዳ
ራሱን ሊያራግፍ ከራሱ ያዚም ኣቁማዳ
ቢፍታታ ቁርፍድ ቆዳ ከራስ ፅገረዳ ፣በሶስት ወሯ የፀሃይ ማለዳ፤
ነፍሳት እስዋን አምነው ሊ ሞ ቋ ት – ሁሉም ራሱን ሰጥቶ ሊታደላት
በራስ ናፍቆት ጉጉት፣ እስዋን ጥበቃ ራሱን ስጥቶ፣ ሊሞቃት
እስዋን ሙቆ ፣እስዋን ጠጥቶ፣ እስዋን ተጠርቅቶ ፣ እስዋን ሊፈነዳት ፤

እውነትና ሐሰት ፣ ደስታና ስቃይ
ፍቅርና ኩነኔ፣ ገመናና ሃፍረት
በሙቀትዋ -በብርሃንዋ -በስዋ አደባባይ እንዲያ ተበረግደዉ ፣
በግለትዋ ግለዉ ነፍሳት ተዘናግተዉ
መሸሽጊያ ሳይኖራቸዉ ፣
ምነዋ ማዝገሟ ቁ…ል..ቁል – ድንገት ሳይታሰብ – ደግሞ ………ሳትነግራቸዉ ፤

Ray1

ነካስ ለጋስ ኖሯል ..ይሄ ጋግርት የጭጋ ግ ደመና
ጭጋግ ሆኖ ራስን መሸሸጊያ
ራስን መደበቂያ -በራስ ዉስጥ- የራስን ገመና
በወራት የበረዶ ጝጝር- በፅልመተ የጭጋግ ደመና ፤

ግዜና መከራ አስኪያልፍ በደመና ራስን ድብብቆሽ
ራስን ሊያሳርፉ -ራስም ፣የራስን አንድዮሽ
በጭፍጝጝ ደመና በፅልመት -ዉሸታሙን ዉጩን ድብብቆሽ
ራስን በራስ ቀብሮ – ራስ ሲያምጥ ፣ ራስን ሊያቆይ – በራስ ዉስጥ -የብርሃን ግርዶሽ ፤

አስተማረኝ አሳየኝ ፣ባዳዋን ዉሸታሟን የፀሃይ ንግስት
አንዱ ግሎ ገሎ ሲዝናናባት – አንዱም ግሎ ገሎ ሲታይባት
አንዱም ዉስጡ በርዶ ዉጩን ሲቀልጥባት- እስዋን ቆሞ ሲቃጠላት ፤
ራስ ቆሞ በራስ ተዋርዶ
ለራስ አዛኝ አልቃሽ ጠፍቶ
ስም በሰዉ ሐገር – ሐገር በሰዉ ተሸልቶ
በሰዉ ሐገር ፀሃይ ራስ ተበርግዶ፤

የዘር ዕምነት እዚም እዚያም- ታስሮ- – በራስ አንገት -የሰዉ ማተብ
በሰዉ ሐገር ፀሃይ፣ እንተፍ እንተፍ፣ የመምሰል -ዱብ ዱብ
ሰዉ ሲሮጥ ራሱን ጥሎ ሊያሳይ -መፈጠሩን በሰው አምሳል
ሰዉ -ለሰዉ አድሮ ራሱን ጥሎ ሲልሹዋሽዋ- -እንደነዚያ የበረዶ ዉሾች ያንገት ፅናፅል፤
አየነዉ… ከደመና ያንን በሰዉ አርጥባን ድግስ ደጋሹንም ስሙን ፋቂ ስደተኛ – ባላገሩን ፖለቲከኛ
ነግሮ ኣስገዳይ የጁን በጁ ፣ ኣደግዳጊ ባዶ የምላስ ዳንኪረኛ- ባላገሩን ዘመንተኛ
ኣየነው ያዉም ከጨለማ ፤ በሶስት ወራ ፀሃይ እስዋን ታምኖ ሲጫወት አርበኛ

‘ሀ’
-ብታማላት
ለ-‘ ሁ’ ፣
‘ሁ’ም
ብታሳብቅ ለ- ‘ሂ’ ፣

ሂ -ግን ይኸዉ አለች
‘ሀ’ ብላ አፍዋን ሳትከፍት
እንደሳቀች ሂሂሂሂሂ ……..እንዳለች
ምን ይጠቅም ? ብላ ማሰማቱ የራስ.
አ..ሄሄ…. እህ ህን
….አ..ሆ.ሆ.ን..
እኔስ እኖራለዉ ዉስጤ – በራስ አምባዬ
በእዮሃ አበባየ -መስከረም ጠባዬ
በቀዳማዊ አፍሪካዊ ንግስት ያስራሶስት ወራ ፀሃዬ
እኔስ እደምቃለዉ ገና ከዚህም ከፅልመተ ደመና
ከራስ አምባየ በዚያች አፍሪካዊት
የጨረቃ ድምብል ቦቃ –
አፄ ቤት ከገባችዉ አዉቃ፤
እንዲህ…እንዲያ… እያለ እያዋዛ የነገረኝ
ያ -የራስ ሃሳብ የደመና ጓደኛዬ ፣
ነካስ ዕውነት ኖሯል መ ሻ ሉ
ያ በጭፍጝጝ ደመና ያለዉ የራስ መብራት ጓዳዬ።

ShareThis
Share this:

(ናይሮቢ፣ ጃንዋሪ 29 ቀን 2015ዓ.ም.) – የኢትዮጵያ መንግስት ተቃውሞን ለማፈን የሚያካሂደውን የእስር፤ የውንጀላ እና ህገ-ወጥ የሃይል እርምጃ ዘመቻ በ2014 ዓ.ም. አባብሶ ቀጥሎበታል ሲል ሂዩማን ራይትስ ዎች ዛሬ ይፋ ባደረገው የ 2015 የዓለም ሪፖርት አስታወቀ። መንግስት ለሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎች የሚሰጠው ምላሽ …

በኢትዮጵያ ግንቦት 2015 ዓ.ም ከሚካሄደው ምርጫ አስቀድሞ የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ አስከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል (Human Rights Watch) Read more »

የኢህአዴግ ምርጫ ቦርድ አንድነት በተለጣፊዎቹ በእነ ትግስቱ አወሉ እየተመራ ወደ ምርጫ እንዲገባ ወሰነለት። ሕጋዊው አንድነት በተለጣፊው መተካቱ ተረጋገጠ። ዝርዝር መረጃ እንደደረስን እናቀርባለን።

Minilik Salsawi እየተፍረከረከ ያለውና የመተማመን መንፈስ የጠፋበት የወያኔው ጁንታ ባለፈው ወር ያደረገውን የደህንነት ሃላፊዎች ስብሰባ ውስኔን ተከትሎ ከትግራይ ክልል ብቻ የተመለመሉ 2800 ሰዎች ለደህንነት ስልጠና አዲስ አበባ ገብተው መጠቃለላቸው ተሰምቷል::በደህንነት ሃላፊዎቹ ውሳኔ መሰረት በሌላው ክልል ዜጎች ላይ ያለው እምነት የሞተ ስለሆነ በደህነንቱ ስራ ላይ ስልጠና እንደማይሰጣቸው ታውቋል::ከክልሎች የደህንነት ተቋሙን የሚቀላቀሉ ማንኛቸውም ዜጎች እድሉ እንደማይሰጣቸው እና ያሉትንም ከደረጃቸው ዝቅ ያሉ ቦታዎች በመመደብ ሃገራዊ እና መንግስታዊ የምስጢር መረጃዎችን እንዳያገኙ መከላከል ያስፈልጋል የሚሉት የደህንነት ሃላፊዎቹ የደህንነት ተቋሙ ውስጥ መተማመን እንዲስፋፋ አድርገዋል ሲሉ ከክልሎች የመጡ ደህንነቶችን ወንጅለዋል::

መረጃውን የሰጡኝ ለኢሚግሬሽን እና ደህንነት ቢሮ ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንዳሉት አዳዲስ ስልጠና ተሰቷቸው የሚመደቡ ደህንነቶች አስፈላጊውን ጥቅማ ጥቅም እና በፈለጉበት አገር ላይ ለወደፊት ኑሮ የሚሆን መኖሪያ ቤት ሳይቀር እንደሚገነባላቸው ቃል ተገብቶላቸዋል::በደህንነት ተቋም ውስጥ ከፍተኛ የሆነ አለመተማመን መንገሱን ያወሱት ምንጮቹ በገሃድ ከምናየው የባለስልጣናቱ ውንብድና በተጨማሪ የሃገር (የብሄራዊ ጥቅም)ምስጢር ሳይቀር ለውጪ ሃይሎች እየተሸጠ መሆኑን ገልጸዋል::እንዲሁም ህገመንግስቱን እና ተቃዋሚ ሃይሎችን በተመለከተ የሚነሱ ጥያቄዎች የደህንነት ሃላፊዎቹ በደህንነት አባላቱ ላይ ያላቸውን እምነት እንዲሸረሸር ያደረገ መሆኑን ሲናገሩ ራሳቸው ሃላፊዎቹ የሚፈጥሩት ጫና አለመተማመኑን አስፍቶት እያለ የትግራይ ተወላጆች ባልሆኑ ዜጎች ላይ መደፍደፉ እንደማያዋጣ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

የሕወሓት የደህነንት ተቋሙ የትግራይ ተወላጆችን መልምሎ ወደ አዲስ አበባ ያመጣበት ሌላው ምክንያት ከዚህ ቀደም የደህነንት ተቋሙ አባላት የነበሩ የትግራይ ተወላጆች በጦር ሰራዊቱ እና በፖሊስ ሰራዊቱ ውስጥ ከተራ ወታደርነት እስከ መኮንንነት ማእረግ ተሰቷቸው ሰርገው እንዲገቡ የተደረገ መሆኑን ምንጮቹ ተናግረዋል::በተለይ በፖሊስ ሰራዊቱ ውስጥ የፖሊስ ሳይንስ ሙያ ሳያጠኑ በከፍተኛ የአመራር ቦታዎች ላይ እና በየፖሊስ ጣቢያ አዛዥነት ላይ የተመደቡ የደህንነት አባላቱ በዜጎች ላይ ከባድ የሆነ ሰቆቃ እየፈጸሙ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::

አንድነት ፓርቲ እሁድ ጥር 24 ደሴ የሚያካሄደው ሰልፍ ከከተማው አስተዳዳር እውቅና የተሰጠ ሲሆን ሰልፉ በደሴ አራዳ አከባቢ ከሚገኘው የአንድነት ቢሮ ተነስቶ መጨረሻ ሆጤ አደባባይ ነው የሚያበቃው። ሰልፉ ከ2:00 እስከ 7:00 ሰዓት የሚቆይ ሲሆን እንደተለመደው የደሴና የአከባቢዋ ህዝብ በነቂስ ይወጣል ተብሎ …

አንድነት ፓርቲ እሁድ ጥር 24 በደሴ ከተማ ህዝባዊ ሰልፍ ያካሂዳል Read more »

(ሠመረ ሞገስ) የብሄራዊ ስታዲየም ፕሮጀክት ዝርዝር የዲዛይን ስራዎች በመጪው የካቲት ወር አጋማሽ እንደሚጠናቀቅ የፕሮጀክቱ አማካሪ አስታወቀ፡፡ በስታዲየሙ ዙሪያ የሚታጠረው የአጥር ግንባታ 91 በመቶ ደርሷል። በአዲስ አበባ ቦሌ ገርጂ አካባቢ በመገንባት ላይ ያለው ብሄራዊ ስታዲም 60 ሺህ ተመልካች የመያዝ አቅም ሲኖረው ለግንባታው 2 ቢሊዮን ብር ወጪ ተይዞለታል። የስታዲየሙ ግንባታ በሁለት ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። የፕሮጀክቱ አማካሪ ሜ.ኤች ኢንጂነሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ኢንጂነር መሰለ ኃይሌ እንደተናገሩት ”የቅድመ ዲዛይን ስራዎች ተጠናቆ የዝርዝር ዲዛይን ስራዎች በመሰራት ላይ ናቸው”:: ዝርዝር ዲዛይኑ የኤሌክትሪክ ዝርጋታ፣ የሜዳ ስፋት፣ የመሬት ጥናት፣ በጦር ውርወራ ጊዜ ርቀቶችን መለካት የሚያስችሉ ዘመናዊ መሳሪያዎችና የሽብር ጥቃት ለመከላከል የሚያስችሉ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችና ሌሎች ዲዛይኖች ያካተተ ነው። የመጨረሻ ዝርዝር ዲዛይን ስራ በመጪው የካቲት ወር እንደሚጠናቀቅ ነው ዶክተር ኢንጀነር መሰለ የተናገሩት። ስለሆነም ግንባታውን ለማስጀመር በመጪው መጋቢት ወር ጨረታ ይወጣል። 60 ሄክታር ላይ የሚያርፈው አዲሱ ብሄራዊ ስታዲየም የመሬት ጥናቱ በመጠናቀቅ ላይ ነው፡፡ እንደ ኢንጂነሩ ገለጻ ስታዲየሙ ዓለም አቀፍ ደረጃን ጠብቆ የዓለም ዋንጫና የኦሎምፒክ መክፈቻና መዝጊያ ውድድሮችን እንዲያስተናግድና የተጀመሩ ዝርዝር ዲዛይን ስራዎች ጥራታቸውን ተጠብቆ እንዲሰሩ ለማድረግ ከኮሪያ፣ ከአውስትራሊያ እና ከእንግሊዝ አገር አማካሪዎችን አካትቷል፡፡ ድርጅቱ የመጨረሻ ዝርዝር ዲዛይን እየሰራ ያለው ከፌዴራል ስፖርት ኮሚሽንና ከከተማ ልማት ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስተያየት ከተሰጠው በኋላ ነው። በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የግንባታዎች ፋሲሊቲ የስራ ሂደት ዳይሬክተር አቶ ጥበበ ጎርፉ በበኩላቸው እንደተናገሩት በስታዲየሙ ዙሪያ […]

( ሄኖክ የሺጥላ ) ወያኔ በብረት ትግል ይወድቃል ። በብረት ትግል ብቻ አላልኩም ። ይሄማ ግብጽንም ፣ ቱንዝያንም ፣ ሊብያንም ፣ ቦርኪና ፋሶንም አረ እኛነታችንንም አለማወቅ ነው ። አሁን አሁን የምሰማው አስተያየት ግን የሚገርም ነው ። አባላትና ደጋፊዎች የኢትዮጵያ ነጻነት …

ድል በትግል ( ሄኖክ የሺጥላ ) Read more »

#‎Ethiopia‬ ፖሊስ የህዝብነው ያሉ አንደበቶች በሀይል በትር እንዲዘጉ ተደረገ የኢትዮጵያ ፖሊሶች ለተቀጠሩለት ህገ መንግስት ሳይሆን ለአዛዦቻቸው ታማኝነታቸውን ዳግም አረጋገጡ ከነፍሰጡር ሴት እስከ ሽማግሌና አሮጊት የበቀል እርምጃ መብቴን ያስከብርልኛል ባሉትና በተማመኑበት ፖሊስ ተወሰደባቸው ::

phpBB [video]

በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የሃሰት ምስክርነት የሰጠው ግለሰብ ታወቀ:: Minilik Salsawi
Image
ይህ በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ወጣት ሄኖክ ተስፋዬ ይባላል፡፡ ሁልጊዜ አርብ በመስጊዶች እየተገኘ ንፁሀን የእስልምና እምነት ተከታዮችን በሀሰት ውንጀላ የሚያሳስር የወያኔ ጆሮ ጠቢ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነችውን ወጣት ወይንሸት ሞላን የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ የሚደርሰውን ግፍ ለመከታተል በሄደችበት ወቅት ፀጉሯን ጨምድዶ ከፎቅ ላይ እየጎተተ በማውረድ ከፖሊሶች ጋር በመሆን ከፍተኛ ድብደባ አድርሶባታል፡፡

በወቅቱ በእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ ለደረሰው ድብደባና ስቃይም ተጠያቂ የሆነ ሰው ነው፡፡ይህ ወጣት በብዙ የእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ በሀሰት ምስክርነት በፍርድ ቤት የሰጠ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም መንግስት ሰማያዊ ፓርቲን ለማፍረስ እየሰራው ባለው ሴራ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ነን በማለት ፓርቲው እንደተከፋፈለ ለማስመሰል ከባልደረቦቹ ጋር ስልጠና እየወሰደ መሆኑ ታውቋል፡፡
Image

-ከመጭው የኑሮ ውድነት ጉዳት ለመዳን በጋራ ተነስተን ይህንን ወንበዴ መንግስት ማፍረስ ይጠበቅብናል::
Minilik Salsawi የወያኔው መንግስት ለግሉ ዘርፍ ያለው አመለካከት ደካማ መሆኑ እና ከፖለቲካ ባለስልጣናት ጋር ቁርኝት ያላቸው ነጋዴዎች ለመክበር የሚያደርጉት ሩጫ የህዝቡን የኑሮ ውድነት ጣራ እንዲነካ አድርገውታል::እንዲሁም የኢኮኖሚ ውንብድና በሃገሪቱ ላይ እየተፈጸመ ነው::የስራ አጦች ቁጥር መጨመር ሃገሪቱን የወንጀለኞች መናኸሪያ እያደረጋት ነው::በአገሪቱ የተንሰራፋው የሙስና እንቅስቃሴ ዋነኛው የኢኮኖሚው ማነቆ ከመሆኑም በላይ የፍትህ እና የንግድ ስርኣቱ መላሸቅ የኢኮኖሚ ቁጥጥሩን ስላ ላላው ለዋጋ ንረቱ መንስኤ ናቸው::

በአላቂ እቃዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት ይከሰታል በሃገር ውስጥ ምርቶች ላይም ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ በሚቀጥለው አንድ አመት ይመጣል የግሉ አምራች ዘርፍ ጥሬ እቃዎችን ወደ ሃገር ውስጥ በሚያስገባበት ጊዜ የተወሰነ የቀረጥ ክፍያ አለመኖሩ እና የመንግስት ባለስልጣናት እንዳሰኛቸው በየጊዜው እየቀያየሩ የህገር ውስጥ ምርቶች እንዲጎዱ የማኑፋክቸሪውም ዘርፍ እንዲዳከም በማድረግ ችግር እንዲፈጠር አድርገዋል::

የባንኮችን መዳከም የስራ አጥነትን የስደትን የፖለቲካ ተጽእኖን የህዝቡን ምሬት ለመረዳት ለማሻሻል ምንም የማይሰራው የወንበዴዎች ስብስብ ባለስልጣኑ በሞኖፖል ንግዱን ይዞታል የውጪ ዜጎች ህገወጥ የኢኮኖሚ ስርኣት ዘርግተዋል ከፍተኛ ብዝበዛ በሃገሪቱ ምጣኔ ሃብት ላይ እየተደረገ ነው::ሕዝቡ ዳግም ወደ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያዘገመ መሆኑን አውቆ በጋራ በመነሳት ይህንን ወንበዴ መንግስት መጣል ያለበት መሆኑን መገንዘብ ሲኖርበት ለመጭው ትውልድ ከወንበዴዎች የጸዳች ሃገር የማስረከብ የዜግነት ግዴታ አለብን::

(ሔኖክ ሰለሞን) በእነ አቶ በላይ የሚመራው የአንድነት ፓርቲ ቡድን በህገ ወጥ መንገድ ሊያካሂድ የነበረው ሰልፍ መበተኑን የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ጉዮች ቢሮ አስታወቀ አዲስ አበባ፣ (ኤፍ.ቢ.ሲ) በእነ አቶ በላይ ፈቃዱ የሚመራው አንድነት ለዴሞክራሲና  ለፍትህና ፓርቲ ዛሬ በህገ ወጥ መንገድ ሊያካሂድ የነበረው ሰልፍ መበተኑን የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ጉየዮች ቢሮ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አስታወቀ ፓርቲው ለሰልፉ ከከተማ መስተዳደሩ በህጋዊ መልኩ ፈቃድ ሳያገኝ ነው፣ ሰልፉን ቀበና አከባቢ በሚገኘው ቢሮው ለማድረግ መሞከሩን ነው ቢሮው የገለፀው። ፖሊስ ህጉን በተከተለ መንገድ ሰልፉን ለማስቆም ቢሞክርም አንዳንድ የፓርቲው አበላት በፖሊስ ላይ  አምባጓሮ ለማስነሳት ሞክረው ነበር ብለዋል የቢሮው ሃላፊ ወይዘሮ ፍሬሀይወት አያሌው። ይሁንና ፖሊስ በትአግስት ሰልፉን ለመበተን መቻሉን ገልፀዋል። በሰልፉ ለመሳተፍ ከሞከሩት ውስጥ የታሰረ የፓርቲው አባል እንደሌለም አስታውቀዋል። የአስተዳደሩ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ባሳለፍነው ሳምንት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ቡድኑ ሰላማዊ ሰልፉን እንዳያካሂድ የተከለከለው ሰለማዊ ሰልፍ ሲካሄድ መሟላት ያለበትን አስፈላጊ ቅጽ ባለሟሟላቱ መሆኑ ተገልዖ ነበር። ቅፁ የሚጠይቃቸው በሰልፉ ላይ የሚያዙ መፈክሮችን እና ሰልፉ ከየት ተነስቶ የት እንደሚጠናቀቅ የሚገልፁ መረጃዎችን ጨምሮ ሌሎች መሟላት የሚገባቸውን የሰላማዊ ሰልፍ ማካሄጃ መስፈርቶችን አንዳላማላም በመግለጫው መጠቀሱ የሚታወስ ነው። ********* ምንጭ፡- ፋና፣ ጥር 17፣ 2007 — — More from Horn Affairs Amharic‘የእነበላይ ፍቃዱ አንድነት’ መግለጫ:- ‹‹የምርጫ ቦርድ ታሪካዊ ወንጀል እየፈፀመ ነው››መኢአድ – ቦርዱ የሰጠኝን የቤት ስራ የጨረስኩ በመሆኔ የምጠራው ጉባኤ የለምየነትዕግስቱ አወል የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደየአንድነት […]

በአቶ ትእግስቱ አወሉ የሚመራው የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤውን ባለፈው ቅዳሜ በቶፕ ቪው ሆቴል አካሂዷል። በጠቅላላ ጉባኤው 239 አባላት ተጠርተው 193ቱ ተገኝተዋል። ይህም ከግማሽ በላይ በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዳቸውን በጉባኤው ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት አቶ ትዕግስቱ አወሉ ተናግረዋል። ሶስት የፓርቲው አባላት ማለትም አቶ ትዕግስቱ አወል፤ አቶ ጋሻው አሰፋና አቶ ደረጄ ሚሊዮን ለፓርቲው ፕሬዝዳንትነት በእጩነት ቀርበዋል፡፡ ከአዳማ የፓርቲውን ቅርንጫፍ በመወከል የተገኙት አቶ ጋሻው አሰፋ ከውድድሩ ራሳቸውን ያገለሉ ሲሆን ሁለቱ እጩዎች በሚስጥር በተካሄደ የድምፅ አሰጣጥ ተወዳድረዋል፡፡ አቶ ትዕግስቱ አወል ከተሰጠው ድምፅ 136 ሲያገኙ አቶ ደረጄ ሚሊዮን ደግሞ 48 ድምፅ በማግኘታቸው አቶ ትዕግስቱ ፓርቲውን በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ዳግመኛ ተመርጠዋል፡፡ ጠቅላላ ጉባዔው ለኦዲትና ኢንስፔክሽን የቀረቡለትን 10 እጩዎች አወዳድሮ 7 አባላትን መርጧል፡፡ በተመሳሳይ ለብሔራዊ ም/ቤት አባልነት 57 ዕጩዎች ቀርበውለት በ55ቱ ላይ ድምፅ ሰጥቷል፡፡ የጠቅላላ ጉባኤውን እና አጠቃለይ ውሳኔዎቹን ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እንደሚያቀርቡም አቶ ትዕግስቱ ተናግረዋል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዚህ ጉባኤ ላይ ተወካዩን አልላከም፡፡ በሌላ ወገን ያለው የአቶ በላይ ፈቃዱ ቡድን ደግሞ ምንም አይነት ጠቅላላ ጉባኤ አላካሂድም በሚለው አቋሙ እንደፀና ነው። ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለቱ የፓርቲው አመራር ነን የሚሉ ቡድኖች ችግራቸውን በጠቅላላ ጉባኤ ፈተው እንዲመጡ የሰጠው ተጨማሪ የሁለት ሳምንት ጊዜ የፊታችን ማክሰኞ ይጠናቀቃል። ****** More from Horn Affairs Amharicመኢአድ – ቦርዱ የሰጠኝን የቤት ስራ የጨረስኩ በመሆኔ የምጠራው ጉባኤ የለምየነበላይ ፍቃዱ አንድነት ሊያካሂድ የነበረው ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ […]

የወያኔ ወታደሮች በሰላሌ አውራጃ ጎሮ መስቀላ ተብሎ በሚጠራ ከተማ የታጠቁ ተቃዋሚዎች ብለው የጠረጠሯቸውን ሁለት ግለሰቦች፥ አቶ ከተማ ውበቱ እና ለጊዜው ስሙ ያልታወቀውን ጓደኛውን፥ በአደባባይ ከረሸኑ በኋላ ሬሳቸውን በከተማ መሃከል እየጎተቱ ለህዝብ ሲያሳዩ ቆይተው መጨረሻ ላይ መሃከል ከተማ ሰቅለዋቸዋል። ድርጊቱ የተፈጸመው …

በሰላሌ አውራጃ 2 ግለሰቦች በወያኔ ፖሊሶች በአደባባይ ተረሽነው ሬሳቸው በከተማ መሃል ተጎተተ – ፎቶ Read more »

ክንፉ አሰፋ በመጀመርያ “ዶክተር” ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ደጋፊና ተደጋፊ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በሙሉ ጠሯቸው። ሰበሰቧቸው። እንዲህም አሏቸው። “ወደ ደደቢት አብራችሁን ትሄዳላችሁ፤ እዛ እንደደረሳችሁም አመጣጣችንንና አካሄዳችንን በደንብ አድርጋችሁ ታጤናላችሁ። ከዚያ ስትመለሱ ሁሉንም ነገር ለህዝቡ ትናገራላችሁ።…” በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር …

የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ Read more »

አንድነት በዛሬው ዕለት መነሻውን ከደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ መድረሻውን ደግሞ የንጉስ ተክለሀይማኖት ቤተመንግስት ከሚገኝበት ተክለሀይማኖት አደባባይ ያደረገ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዷል፡፡ ፓርቲው ባደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የፓርቲው አባላት፣ ደጋፊዎች እና የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በሰልፉ ላይ የተገኙት ታዳሚዎችም ምርጫ ቦርድና ገዢው ፓርቲ …

አንድነት ፓርቲ በደብረማርቆስ በዛሬው እለት ያካሄደው ሰልፍ ይህን ይመስል ነበር – ፎቶዎች Read more »

ይህ ቪዲዮ እንደሚያሳየው የወያኔ ፖሊስ ፋሽስታዊ ድብደባ የአንድነት ፓርቲ በዛሬው እለት የጠራውን ሰላማዊ ሰልፉ ሊያቆም አልቻለም። የአንድነት መሪዎችና አስተባባሪዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፥ ህዝቡ ግን ጥሪያቸውን ተቀብሎ ድምጽ ማሰማቱን ቀጠለ። ምክንያቱም ፍርሃቱን ሰብሮ ለነጻንቱ ለመቆም የቆረጠን ህዝብ ምንም ሃይል ሊያስቆመው …

የወያኔ ፖሊስ ፋሽስታዊ ድብደባ የአንድነት ፓርቲ በዛሬው እለት የጠራውን ሰላማዊ ሰልፉ ሊያቆም አልቻለም – ቪዲዮ Read more »