ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት በኢትዮጵያ ይከሰታል::
-ከመጭው የኑሮ ውድነት ጉዳት ለመዳን በጋራ ተነስተን ይህንን ወንበዴ መንግስት ማፍረስ ይጠበቅብናል::
Minilik Salsawi የወያኔው መንግስት ለግሉ ዘርፍ ያለው አመለካከት ደካማ መሆኑ እና ከፖለቲካ ባለስልጣናት ጋር ቁርኝት ያላቸው ነጋዴዎች ለመክበር የሚያደርጉት ሩጫ የህዝቡን የኑሮ ውድነት ጣራ እንዲነካ አድርገውታል::እንዲሁም የኢኮኖሚ ውንብድና በሃገሪቱ ላይ እየተፈጸመ ነው::የስራ አጦች ቁጥር መጨመር ሃገሪቱን የወንጀለኞች መናኸሪያ እያደረጋት ነው::በአገሪቱ የተንሰራፋው የሙስና እንቅስቃሴ ዋነኛው የኢኮኖሚው ማነቆ ከመሆኑም በላይ የፍትህ እና የንግድ ስርኣቱ መላሸቅ የኢኮኖሚ ቁጥጥሩን ስላ ላላው ለዋጋ ንረቱ መንስኤ ናቸው::
በአላቂ እቃዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት ይከሰታል በሃገር ውስጥ ምርቶች ላይም ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ በሚቀጥለው አንድ አመት ይመጣል የግሉ አምራች ዘርፍ ጥሬ እቃዎችን ወደ ሃገር ውስጥ በሚያስገባበት ጊዜ የተወሰነ የቀረጥ ክፍያ አለመኖሩ እና የመንግስት ባለስልጣናት እንዳሰኛቸው በየጊዜው እየቀያየሩ የህገር ውስጥ ምርቶች እንዲጎዱ የማኑፋክቸሪውም ዘርፍ እንዲዳከም በማድረግ ችግር እንዲፈጠር አድርገዋል::
የባንኮችን መዳከም የስራ አጥነትን የስደትን የፖለቲካ ተጽእኖን የህዝቡን ምሬት ለመረዳት ለማሻሻል ምንም የማይሰራው የወንበዴዎች ስብስብ ባለስልጣኑ በሞኖፖል ንግዱን ይዞታል የውጪ ዜጎች ህገወጥ የኢኮኖሚ ስርኣት ዘርግተዋል ከፍተኛ ብዝበዛ በሃገሪቱ ምጣኔ ሃብት ላይ እየተደረገ ነው::ሕዝቡ ዳግም ወደ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያዘገመ መሆኑን አውቆ በጋራ በመነሳት ይህንን ወንበዴ መንግስት መጣል ያለበት መሆኑን መገንዘብ ሲኖርበት ለመጭው ትውልድ ከወንበዴዎች የጸዳች ሃገር የማስረከብ የዜግነት ግዴታ አለብን::