በሳውዲ፣ የመን፣ ደቡብ ኣፍሪካና ሊብያ በኢትዮጵያውያን ላይ ችግር ባጋጠመ ጊዜ በቦታው የሌሉ ብዙ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ መንግስት በነዛ ኣገራትና ቡድኖች ላይ እንዲወስደው የሚጠብቁት እርምጃ ኣርበኛዊ እርምጃ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ ጥሎበት (በባህሪው) ኣርበኛዊ ዲፕሎማሲ ኣያራምድም፡፡ ቢያንስ መንግስት በኣንዳንድ ወገኖች የሚነሳበትን የ”ወኔ-ቢስነት” ክስ ለመከላከልና ለዜጎቹ እንደሚቆረቆር ለማሳየት ያክል እንኳን (ባያደርገዉም) በቴሊቪዥን ብቅ ብሎ ዘራፍና ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ኣይሆንለትም ወይም ኣያምንበትም፡፡ ይሄ ማለት ግን መንግስት ምንም ኣይነት እርምጃ ኣይወስድም ማለት ኣይመስለኝም ፡፡ በኢትዮጵያውያን ላይ ችግርና ጥቃት በደረሰ ቁጥር እኛ ዜጎች እንደምናሳየው ኣይነት ቁጣ የመንግስት ፊት (ግንባር) ላይ ባናየዉም በጊዜው እንደየሁኔታው የተሻለ የሚለው እርምጃ ይወስዳል የሚል ግምት ኣለኝ፡፡ ይሄንን ባህሪው ተቃዋሚዎቹ የፖለቲካ ነጥብ ለማስቆጠር ኣንዳንድ ደጋፊዎቹ ደግሞ የሚደግፉትን ፓርቲ/መንግስት ባህርይ በደንብ ካለመረዳት ኣሊያም በስሜትና ሃዘኑና ጥቃቱ በሚፈጥርባቸው ተፅእኖ ምክንያት መንግስትን ይወቅሳሉ፡፡ ለነገሩስ የኛን ስሜትና ምክር እየተከተለ እርምጃ የሚወስድ መንግስት ቢሆን ኖሮ ይሄኔ ከሱዳንና ግብፅ (በኣባይ ምክንያት)፣ ከሳውዲ ኣረቢያ (በዜጎች ምክንያት)፣ ከኤርትራ (በሄሊኮፕተር ምክንያት) እንዲሁም ከሌሎች ኣገሮች ጋር ጦርነት ውስጥ እንገባ ኣልነበር ? የሰሞኑ የ ISIL ጉዳይ ግን ትንሽ ስሜትን ይፈታተናል፡፡ ድህነት ኣንገሽግሽዋቸውና የቤተሰቦቻቸውን ኑሮ ለመቀየር የሰሃራ በረሃን ኣቋርጠው የመሞትና የመትረፍ ኣጋጣሚው እኩል የሆነበትን የሜዲትራኒያን ባህር የጀልባ ጉዞ ለማድረግ የተዘጋጁትን ወጣት ወገኖች በኣደባባይ ኣንገታቸው ሲቀላና ሰረሸኑ ማየትን የሚያክል ዘግናኝ ነገር የለም፡፡ ህዝባችን በሃዘንም በቁጭትም ኣደባባይ ወጥቶ ሆ ቢል፣ እስቸኳይ የኣጸፋ እርምጃ እንዲወሰድ ቢጠይቅ ኣይገርምም፡፡ ጥያቄው […]

ምነዋ መንግሰተ ሰማይ! የምህረትሽ ቀን ራቀ? ምነው ትንግርትሽ ረቀቀ ? ምነው ኪዳንሽ ታጠፈ … ወዝሽ ወዘናሽ ነጠፈ? እንደ ዳጉሳ ድፍድፍ … ላቦትሽ ተንጠፈጠፈ አሳርሽ ጠሎ አሰፈፈ ምነው እርሾው ተማጠጠ …. ጎታው ጎተራው ታጠጠ ረሀብ ላንቃው ፈጠጠ….ያዳም ልጅ አፅሙ ገጠጠ ምነው ጭር አለ ቀየው! ሀሩር ነዲዱ በረታ ኮርማው ጥማዱ ተረታ ምነው ነበልባሉ አየለ … ማሳው ተንቀለቀለ […]

በተለያዩ የባለ ሥልጣናትና የእምነትመሪዎች መግለጫዎች ላይ በሊቢያ ምድር የተሠዉትን ሰማዕታት በኢትዮጵያዊነታቸው ወይም በስደተኛነታቸው ብቻ አደጋ እንደደረሰባቸውተድርጎ እየተነገረ ነው፡፡ እነዚህ ክቡራን ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ የተሠዉትም እምነታቸውን አንለውጥም ስላሉ ነው፡፡አይሲስ የሠዋቸው በኢትዮጵያዊነታቸው አይደለም፡፡ አይሲስኮ ዜግነት የለውም፡፡ ዐረቦች፣ አውሮፓውያን፣ አፍሪካውያን እስያውያን የተቀላቀሉትአሸባሪና አሰቃቂ ድርጅትና አስተሳሰብ ነው፡፡ እንዲያውም ባለፈው ሰሞን ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከእንግሊዝ ወደ አይሲስ ለመግባትያደረጉትን ጥረት በመገናኛ ብዙኃን […]

ወጣቱ የቪኦኤ ጋዜጠኛ ስሙን እንዲደብቅለት ከተማፀነ በኃላ እንዲህ አለ – ”….እኔ ያለሁት ትሪፖሊ ውስጥ ነው።አሁን ከግማሽ ሰዓት በፊት ፊታቸውን የተሸፈኑ ሰዎች እኔ ወደምኖርበት ግቢ ገቡ እና ወደ 40 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ይዘው በመኪና ሄዱ።ከተወሰዱት ውስጥ በቅርቡ ኦፕራሲዮን የሆነች እና ነፍሰ ጡር አለችበት። እነማን እንድሆኑ ማወቅ አልቻልኩም።እኔ ተደብቄ ነው ያመለጥኩት። እዚህ እስላም እና ክርስቲያን ኢትዮጵያውያንን ሊለያዩን ሞክረው […]

በእኔ ዲ/ን አብርሃም ወርቁና ዲ/ን ዮሴፍ አባይ አስተባባሪነት ስድስት ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ይዘን በሰማዕታቱ በነኢያሱንና ባልቻ መኖርያቤት ከቀኑ 10:45 ሄደን አፅናንተን ተመልሰናል ቅዱስ ፓትርያርኩን ይዘን ለመሄድ ያደረግነው ሙከራ በኘሮግራም መደራረብ ምክንያት አልተሳካም ነገር ግን ልጆች ናቸው ብለው ሰሰይንቁን ማፅናናት ኃላፊነት አለብን ብለው ጥሪአችንን አክብረው 1ኛ/ብፁዕ አብነ ሉቃስ የሲኖዶሱ ዋና ፀሐፊና የሁመራ ሀ/ስ ሊቀ ጳጳስ […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስትያን ሲኖዶስ ዛሬ ሚያዝያ 13/2007 ባወጣው ባለ9 ነጥብ መግለጫ፡- በሊቢያ ውስጥ በተደረገው አሰቃቂ ድርጊት ቤተ ክርስቲያንኒቱ እጅግ ያዘነች መሆኗን ገልጾ በዚህ ግድያ ውስጥ ግን ሟቾቹ ሰማዕት በመሆን የተጠቀሙ ጀግኖች እንጂ ተጐጂዎች እንዳልሆኑም ጭምር ማሰብ እንደሚገባ ገልጿል፡፡ በነገው ዕለት በአዲስ አበባ የሚገኙ ገዳማት እና አድባራት በአጠቃላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት ጸሎተ ፍትሐት እንዲያደርሱ ጥሪ አስተላለፏል፡፡ በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናትም ሁሉ ከሚያዚያ 14 ጀምሮ ለ7 ተከታታይ ቀናት በሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ምህላ እንዲያረግ ቅዱስ ሲኖዶስ አያይዞ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ አክሎም ለሟቾቹ የሰማዕትነት ክብርን በቀኖናው መሠረት መስጠት እንዲቻል ቤተሰቦቻቸውን የሚያውቁ ምዕመናን ፎቶአቸውንና ስማቸውን አሰባስባው ለቅዱስ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ አዝዟል፡፡ ሙሉ የሲኖዶስን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ ከሥር ካለው ምስል ያንብቡ ወይም እዚህ ጋር በመጫን (link) ዳውንሎድ ያድርጉ፡፡ *********** — More from Horn Affairs AmharicSendek | የጁነዲን ሳዶ ባለቤትን ጨምሮ 29 ሰዎች በሽበርተኝነት ተከሰሱETV | የግንቦት 7ቱ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን ተይዞ ለኢትዮጵያ ተላልፎ ተሰጥቷልማዕተብም መስቀልም በግለሰቦች ነፃነት ውስጥ የሚካተት ነው – ዶ/ር ሺፈራው ተክለማርያምየዩኒቨርስቲዎች ሃይማኖታዊ ስነስርአትና አለባበስ ደንብን በመቃወም በሽብር የተሳተፉ ግለሰቦች ጥፋተኛ ተባሉሕገ-መንግስት እንዲያከብሩ ሲመከሩ – በሃይማኖታችን ጣልቃ ተገባ ይላሉ (ሚ/ር እውነቱ ብላታ)ማዕተብ ከሂጃብ

http://www.eaglewingss.com/
እስከመቼ ነው?
ዛሬ ውስጤን የሚያናውጠው ማዕበል፡ ከጥቂት ግለሰቦች በስተቀር የአብዛኛውን ኢትዮጵያዊ አእምሮ እንደ ትንሽ ታንኳ እያናጋ፡ አንዴ ከራሱ ምናብ የሃሳብ ቋጥኝ ጋር፡ አንዴም ከአምላክ ምስጢራዊ ፈቃድ ዓለት ጋር እያጋጨው እንዳለ ይገባኛል። ታዲያ፥ ስሜት በቀላሉ ሰብረው በማያመልጡት የምሬት ሠራዊት ሲከበብ፣ ተስፋ በድቅድቅ የሞት ጭጋግ ውስጥ ሲደበቅ፣ ለነፍስና – ለስጋ፡ ለአእምሮና – ለእጅ፡ እንደ መፃፍ ያለ ከባድ ህመም የለም። ልብ ብርቱ በሆነ የሀዘን ጦር ሲቆፈር፡ ጉልበትን ሰብስቦ ሃሳብን አምጦ መውለድ አይደለም፡ እውነታንም ቁጭ ብሎ መታዘብ ይከብዳል። ያኔ፥ እፅፋለሁ ላለ ጣት፡ ብዕር እንደ ብረት ለሽክም ይከብዳል። ቢሆንም ግን፡ የቆሰለው አእምሮዪ በተደጋጋሚ አንድ ጥያቄ ይጠይቀኛልና፡ በዝምታ ከማስታምመው – ይኸው ተንፍሼ ልገላገለው ሞከርኩ።

የማከብርህ ኢትዮጵያዊ ወገኔ፥ ተፈጥሮ ሳትሰስት፡ ከዓለም ሁሉ አብልጣና አድልታ የሰጠችንን የዘፍጥረት እና የስልጣኔ ብኩርና፡ እንደ ኤሳው ለሆዳችን – ለምስር ወጥ – ሸጠን፡ እስከመቼ ነው እንደ ዝቃጭ እንደ አተላ፡ ህይወታችን ክብር፣ ሞታችን ዝክር የሚያጣው? እስከመቼ ነው ዘረኞች የዘሩልንን አዝመራ ስናጭድ – ስንውቃ ውለን፡ ሲመሽ ምርት ሳይሆን ምሬት ሰብስበን ወደ ቤታችን የምንገባው? እስከመቼ ነው ሰሜን ጫፍ ተቀምጠው፡ ከደቡብ ጫፍ የተወረወረ ጠጠር ሊስታቸው እስከሚሳነው ድረስ እየሰፉ እና እየሰቡ ያሉት የፖለቲካ መሪዎቻችን፡ ከአፍንጫችን በላይ ያንጠለጠሉልንን የነፃነት ካሮት ላንደርስበት-ላንበላው አህያ ሆነን ስንጋልብ እና ስን’ጋለብ ዘመን የሚያልፈው? እስከመቼስ ነው ምስኪኑ ወገናችን ደረቱ ላይ ተደግኖ የተተኮሰበት የመሳሪያ ጥይት እስኪስተው ድረስ በየሰከንዱ-በየደቂቃው በረሃብ እየከሳ እና እያነሰ፡ በየበራሃው በኖ ተኖ፣ በየባህሩ ዝሎ ሰጥሞ የሚያልቀው?

በወንደሞችህ የግፍ ሞት ልብህ የተሰበረው ኢትዮጵያዊ ወገኔየነፃነት ትግል እኮ ዓላማ እንጂ ባህል አይደለም። ተጀምሮ ማለቅ፤ መነሻ አምድ፣ መደምደሚያ ግብ ሊኖረው ይገባል። የባርነት ሰንሰለት አልበጠስ ብሎ ከከረረ፡ አልቋጭ ብሎ ከረዘመ፡ እንደ ወግ-ባህል ከዘመን ዘመን፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ ከተሻገረ፡ ቆም ብሎ ማስተዋል፤ መሪ ተመሪን መቃኘት ግድ ይላል።

ዛሬ በኣራቱም የዓለም ማዕዘናት ህዝባችን እየቆጠረ ላለው ፍዳና ሰቆቃ መነሻ ምክንያቱ ፖቲካዊ እንጂ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ አንዳልሆነ ለመረዳት፡ ማንም የርዕዮተ ዓለም ፈላስፋ አሊያም የምጣኔ ሃብት ሊቅ መሆን አይጠበቅበትም። ፖለቲካዊ ችግር ደግሞ ከምንም በላይ ፖለቲካዊ መፍትሔን ይሻልና፡ ፖለቲካችን እንዴት እና ወዴት ነው? ዜጎቻችን ትላንት- ሳውድ ዓረቢያ፡ ዛሬ- የመንደቡብ ኣፍሪካሊቢያ ላይ እየተጋቱ ያሉትን መከራ ከምንጩ ለማድረቅ፣ ነገም ተመሳሳይ ጥፋት ካይሮ ላይ ከመከሰቱ በፊት ችግሩን ከችካሉ ለመንቀል ልምን ተሳነን? ጉድለታችን የመሪ? የተመሪ? ወይንስ አጠቃላይ የድርጀታዊ መዋቅር እንከን ነው የሚለውን መጠየቅ እና በአፋጣኝ መመለስ ወቅቱ ይመስለኛል። እርግጥ ነው ዛሬም ቢሆን፡ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጀቶች ከብሉይ ኪዳን የመማፀኛ ግንብ በተለየ መልኩ መዋቀርና ተቀዳሚ ዓላማቸው ተገዳዩን ማትረፍ እንጂ ገዳዩን ማቀፍ መሆን የለበትም ብዪ አምናለሁ። ዘራፊው ዘርፎ፣ ገዳዩም ገድሎ እጁ ሲዝል እና ሲደከም፡ ሀጢያቱን ለማስተሰረይ፣ ከህዝብ ለመታረቅ ዘሎ የሚቀላቀለው እና የሚያንቀላፋበት ጎራ – እንደ እኔ ግለሰባዊ እምነት- ወህኒ-ቤት እንጂ አንድነት፣ መድረክ፣ ሸንጎ ወይንም ግንቦት ሰባት መሆን ያለበት አይመስለኝም።

አምላክህ እግዚአብሔር ርስት አድርጎ በሚሰጥህ በምድርህ መካከል ሦስት ከተሞችን ለራስህ ትለያለህ። ነፍሰ ገዳይ ይሸሽባቸው ዘንድ ወደ እነርሱ የሚወስደውን መንገድ ታዘጋጃለህ … (ኦሪት ዘዳግም / ምዕራፍ 19 : 2)

ላለፉት በርካታ አመታት እንደታዘብነው ግን፦ ሀገር እንደ ቡሄ ሙልሙል ገምሶ፣ ህዝብ እንደ አክርማ ቀጭቶ፣ ዘርፎ እና አዘርፎ የበቃው ባለስልጣን መሽሽጊያው አንድም ቤተ-መቅደስ ኣለበለዚያም የተቃዋሚው ድርጅት ነው። ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፡ ወንጀለኞች ሰይጣናዊ ባህሪያቸውን በሃይማኖታዊ ጠበል አርጥበው፣ በተቃዋሚ ፎጣ አድርቀው በአዲስ ካባ ብቅ ሲሉ እንደ ቅዱስ መላዕክት የሚሰገድላቸው የአይሁዳውያኑ የመማፀኛ ቅጥር መሆናቸው እስካላበቃ ድረስ፡ የነፃነት ኣላማችን ዕውን የሚሆነው፣ የመከራችን ቋጠሮ በዘላቂነት የሚፈታው – በዕድል እንጂ በትግል እንዳልሆነ መጠርጠር የለብንም።

ከረሃብ ወደ ስድብና ውርደት ተመሳሌነት ያሻገሩህ ኢትዮጵያዊ ወገኔ፥ ጽሁፌን ከማጠቃለሌ በፊት ዛሬም እንደ ትላንቱ የማሰምርበት እውነት ቢኖር፦ ህዝባችን ከእንሰሳ ባነሰ ክብር በየመንገዱ ተቀጥቅጦ ሲገደል ዝም ብሎ ከማየት የከፋ የወገን በደል የለምና፡ እንደ ዜጋ የሚጠበቅብንን ሁሉ በማድረግ የተረፉትን ለመታደግ፣ የረገፉትንም ቤተሰቦች ለማፅናናት ዛሬ! አሁን! ቃል ብቻ ሳይሆን ከትግሉም መሃል መግባት ይኖርብናል።

መፈራረሳችን፣ ስድባችን፣ መዋረድና መታረዳችን ዓላማቸው ብቻ ሳይሆን አለማቸውም ለሆነው ጎጠኞች፡ የሃዘን ሲቃችን ብሔራዊም ባይሆን ጎሳዊ መዝሙራቸው ነው። የድረሱልን ለቅሶና ጩኸታችን፡ “አከርካሪውን ሰበርነው – ጥርሱን አወለቅነው” ብለው ለተሳለቁብን ዘረኞች፡ የዓላማቸውን መሳካት የሚያበስር ደወል፣ የግባቸውን ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ቃጭል ከመሆን ባሻገር ፋይዳ እንደሌለው ተረድተን፤ ራሰን፣ ወገንን እና ሃገርን የማዳን ዘመቻውን ከራሳችን በራሳችን መጀመር ብልህነት ነው። የዓባይን ውሃ ለኣባዮቹ ትተን፡ የወገናችንን፣ የአዛውንት እናትና አባቶቻችንን የኣይን ፍሳሽ- ዕንባ – ለመገደብ፡ የትግል ቦንድ (ውህደት) መፍጠሩ ከመቼውም በላይ አስፈላጊ የሆነበት ወቅት ላይ ደርሰናልና ወንድ – ሴት፣ እስላም – ክርስቲያን ሳንል በተግባር በስነ-ምግባር እንተባበር።

ኤግል-ዊንግስ-ሶሳይቲ በደቡብ ኣፍሪካ፣ በየመን፡ አንዲሁም በሊቢያ ህይወታቸው ለጠፋው ዜጎቻችን የተሰማንን ከፈተኛ ሃዘን ስንገልፅ፡ ለቤተሰቦቻቸውም አምላካዊ መፅናናትን እየተመኘን ነው። ችግሩ ከመሠረቱ አልተወገደምና፤ በኣሁኑ ወቅትም በአደጋ ወስጥ ላሉት ወንድሞችና እህቶቻችን፡ ከበረከታችን ሳንሰስት በጉልበት፣ በዕውቀትና በገንዘብ የምንችለውን ሁሉ ከማደረግ ባሻገር ትግሉ ለመከራው ዘለቄታዊ መፍትሔ እስኪያመጣ ድረስ፡ የአምላክ ሰፊ መዳፍ የመጠለያ ድንኳን እንዲሆናቸሁ ምኞትና ፀሎታችን ነው።

ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በተለያዮ ሀገራት በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ እና የሌላ ሀገር ተወላጅነት ባላቸዉ ንፁሀን ዜጉች ላይ በተፈፀመዉ አሰቃቄ የግድያ ወንጀል አዝነን ሳናበቃ ፦ ዛሬ ደግሞ በሊቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመዉን እጅግ አሳዛኝ ፤ አረመኔያዊ ተግባር ስይና ስንሰማ የተሰማኝን ሐዘን ለመግለፅ ቃላትም ሆነ ቋንቋ ያጥረኛል። እንኳን የኔ በሚሉት የራስ ወገን ይቅርና ክቡር በሆነዉ […]

ሰበር ዜና አሁን የደረሰን ዜና እንደሚያመለክተው ከተማ ውስጥ ማን እንደበተነው ያልታወቀ ነገ የስራ ማቆም አድማ እና ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ የሚጠይቅ ወረቀት ተበትኗል! በየታክሲውና ከተማ ውስጥም መነጋገሪያ እንደሆነ ታውቋል። ፖሊስ ሰልፈኛው ወደ ሜክሲኮ እንዳይሄድ ለማገት ቢጥርም ህዝቡ ግን አንቆምም ብሎዋል ሰልፉ አዲስ አበባን ሲዞር ሊውል ነው! አሁን ሰልፈኛው ወደ ከቄራ ወደ ሜክሲኮ እየዞረ ነው! ፖሊስ ምንም […]

ሊቢያ ላይ በአይ ኤስ አይ ኤስ በተገደሉት ኢትዮጵያውያን መንግስት ትኩረት አለመስጠቱን ተከትሎ በርካታ ህዝብ በተቃውሞ ወደ ቤተ መንግስት እያቀና ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ከሟቾቼ ቤተሰቦች ተነስቶ በመስቀል አደባባይ አልፎ አሁን ውጭ ጉዳይ ላይ ደርሷል:: የነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር በቦታው ተገኝቶ እየዘገበ ይገኛል፡፡Filed under: NEWS Tagged: Addis Ababa, Addis Ababa University, Africa, African Commission on Human and Peoples’ […]

በየመን፣ በደቡብ አፍሪካና በሊቢያ ስለሚሞቱት ዜጎቻችን የሚሰጡት መንግሥታዊ መግለጫዎች ሁለት ነገር የጎደላቸው ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ሰብአዊ ስሜት፡፡ ማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር ስለሌላው ሰብአዊ ፍጡር መከራና ስቃይ ሲሰማ መጀመሪያ አንዳች የኀዘን ስሜት ይሰማዋል፡፡ ከዕውቀት ይልቅ ስሜት ለሰዎች ቅርብ ነውና፡፡ ባለሥልጣን ቢሆን፣ ፖሊስ ቢሆን፣ ዳኛ ቢሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሆን ሰው ነውና ስሜት አለው ተብሎ ይታሰባል፡፡ ያዝናል፣ ይከፋዋል፣ ልቡ ይረበሻል፣ ሆዱ ይባባል፣ ኅሊናው ይደማበታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ስለዚህም የመጀመሪያው ሥራው ማዘን ቀጥሎም ኀዘኑን በወጉ መግለጥ ነው፡፡

ሰሞኑን የማያቸው መግለጫዎቻችን ግን የኀዘን ወግ በሀገራችን የሌለ የሚያስመስሉ ናቸው፡፡ መሪዎቻችን ወደ አደባባይ ወጥተው ለሞቱት ወገኖቻችን እንደ ኢትዮጵያዊነት ኀዘናቸው የሚገልጡት፣ ጥቁር ልብስ ለብሰው የምናያቸው፣ ነጠላ የሚያዘቀዝቁት ስንት ሰው ሲሞትብን ነው? የሚያስብሉ ናቸው፡፡ ኀዘንኮ ፖለቲካ አይደለም፣ ፓርቲ አይደለም፣ ርእዮተ ዓለም አይደለም፣ ሊብራልም አብዮታዊ ዲሞክራሲም አይደለም፡፡ ኀዘን ሰብአዊነት ነው፡፡ የሚመራቸው ዜጎቹ፣ የሚያሠማራቸው በጎቹ ሲታረዱና ሲሞቱ ኀዘኑን በይፋ የማይገልጥ መሪና እረኛ መቼ ነው ኀዘኑን የሚገልጠው?

ዜጎቹ በሕገ ወጥ መንገድም ይሂዱ በሕጋዊ፣ ድንበር ጥሰውም ይሂዱ በአውሮፕላን ተሳፍረው፤ መጀመሪያ ሰዎች፣ ቀጥሎም የዚህች ሀገር ዜጎች ናቸውና ኀዘን ይገባቸዋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ሰው አገኘዋለሁ ብሎ ከሚያስበው ክብር አንዱ በሞቱ ጊዜ የክብር ልቅሶና ኀዘን ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከአካባቢያቸው ላለመራቅ፣ ከራቁም ለመመለስ ከሚሰጧቸው ምክንያቶች አንዱ ‹በክብር ዐርፎ በክብር መቀበርን፣ የክብር የኀዘን ሥነ ሥርዓትን ማግኘትን› ነው፡፡
ካገሬ እንዳወጣህ አገሬ መልሰኝ
በሹም የታዘዘ አፈር አታልብሰኝ፤
እንኳን የሚቀብረው የሚያዝንለት አጣ
ምን ወግ ማረግ ያያል ካገሩ የወጣ፤
የሚሉት ለዚህ ነበረ፡፡

የመንግሥት አካላት ለምን ይኼንን ለመዘንጋት እንደፈለጉ አልገባኝም፡፡ የደቡብ አፍሪካው ቃጠሎና ግድያ ሲመጣ የሀገራችን ፕሬዚዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ብቅ ብለው ‹‹በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ባለው ነገር ከልብ እናዝናለን፣ ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ጋር ተነጋግረን አስፈላጊውን እናደርጋለን፤ ተመሳሳይ ችግር ለወደፊቱ እንዳይከሰትም አንሠራለን› ዓይነት ሰውነት ያለበት መግለጫ ጠብቄ ነበር፡፡ የለም፡፡ ሲሆን በሀገራችን የልቅሶ ሥነ ሥርዓት መሠረት፡፡ አሁን ደግሞ ዓለም ያወቀው አሸባሪ ‹አይ ሲስ› ኢትዮጵያውያኑን በክርስትና እምነታቸው ብቻ ሲሠዋቸው የተሰጠው መግለጫ ስሜት የሌለበት፣ ማዘን መደሰታቸውን የማይገልጥ፣ እንኳን ሰው እንስሳ የሞተብን የማያስመስል ሆነ፡፡ ከማጣራቱም ከምኑም በፊትኮ ስሜቱ ይቀድማል፡፡፡ አዝናችኋል ወይ? ስትሰሙና ስታዩ ምን ተሰማችሁ? የአሜሪካ መንግሥት እንደዚያ ዓይነት መግለጫ ሲያወጣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ያንን ነው ወይ መስማት ያለብን? ለመሆኑ መሪዎቻችን ኀዘናቸውን የሚገልጡት ምን ስንሆን ነው? ለምንድን ነው ሁሉም ነገር ፖለቲካ የሚሆነው?

ሁለተኛው የሚጎድለው ነገር ደግሞ ፍጥነት ነው፡፡ አትሌቶቻችን በኦሎምፒክ ሲያሸንፉ የባለሥልጣናቱ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት ሯጮቹ ቆርጠውት ካለፉት ሪቫን ቀጥሎ የሚመጣ ዜና ነበር፡፡ አትሌቶቹ ደክሟቸው ከመሬት ሳይነሡ የባለሥልጣናቱ መልእክት ለሚዲያ ይደርስ ነበር፡፡ በዚህ የሁላችንም ኀዘን በሆነው ጉዳይ ግን ለምን መዘግየት እንደተመረጠ ግልጽ አይደለም፡፡ ማጣረቱ፣ መረጃ መሰብሰቡ፣ ተጨማሪ የዲፕሎማሲ ሂደቶችን መሄዱ ጊዜ ይወስዳል፡፡ ማዘን ግን ጊዜ አይወስድም፡፡ ቪዲዮው ተለቅቋል፡፡ ሲሞቱ እያየን ነው፡፡ መልካቸው የኛው ነው፡፡ አይሲስ የገደላቸው ‹ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች› ብሎ ነው፡፡ የዓለም ሚዲያዎች ያንኑ እያስተጋቡ ነው፡፡ ይኄ ለኀዘን ያንሳል? አፈፍ ብሎ ተነሥቶ ‹በሆነው ነገር እናዝናለን፤ ልባችን ተነክቷል፤ ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን፤ ዝርዝሩን በየጊዜው እንነግራችኋለን› ለማለት ስንት ሰዓት ይወስዳል? የደቡብ አፍሪካው ችግር ደረሰ እንደተባለ ሙጋቤን ለውግዘት የቀደማቸው የለም፡፡ የኛዎቹስ የት ሄዱ?
መንፈሳዊ መሪዎችስ የት ናቸው? አንዳንዶቹ ውጭ ሀገር መሆናቸው እየተሰማ ነው፡፡ ሲሆን ይህንን ሲሰሙ አቋርጦ መምጣት፤ ካልሆነም ባሉበት ሆኖ አባታዊ ኀዘንን መግለጥና በእምነቱ የሚገባውን ማድረግ ይገባ ነበር፡፡ ሲኖዶሱስ ምን እየሠራ ነው? አልሰማም ይሆን? ዛሬ ጠዋት ቢያንስ በአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናት ጸሎት መደረግ አልነበረበትም? ባፈው ካይሮ ሄዳችሁ ከግብጽ ቤተ ክርስቲያን ምንድን ነው ያያችሁት? በጎቹ እረኛ የላቸውም ማለት ነው? አባቶች የሚያዝኑት ምን ሲገጥማቸው ነው? እረኛው የሚያለቅሰው ስንት በጎች ሲታረዱ ነው?

ቤተ ክርስቲያኒቱ ነገሩን በዝምታ የምታልፈው ከሆነ እኛ እንደ ጥንታዊቷ ቤተ ክርስቲያን ትውፊታዊ ቀኖና እነዚህን በክርስትናቸው ምክንያት የተሠው ክርስቲያኖች ‹ሰማዕታተ ሊቢያ› ልንላቸው ይገባል፡፡ የሰማዕትነታቸውንም በዓል ማክበር አለብን፡፡ በስንክሳሩ ማስገባት ባንችል ታሪካቸው በኅዳጉ ማስፈር አለብን፡፡ ማንም ይሁኑ ማን፣ በሚገባ የተማሩም ይሁኑ ያልተማሩ፣ ከመካከላቸው የማያምኑም እንኳን ቢኖሩ የተገደሉበት ምክንያት ክርስትና ነውና ሰማዕታት ናቸው፡፡ ያውም ‹ኢትዮጵያውያን ሰማዕታት›፡፡ በስንክሳሩ እንደምናነበው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን የክርስቲያኖች መንደርና ቤተ ክርስቲያን እየተወረረ ክርስቲያኖቹ ሲሠው ገና ያልተጠመቁት፣ ነገሩ ያልገባቸው፣ ክርስትናን ለመቀበል ያልወሰኑት ሁሉ አብረው ተሠውተዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግን የተሠውበት ምክንያት ክርስትና በመሆኑ ሁሉንም ሰማዕታት ብላቸዋለች፡፡ የእነዚህም ክብር እንዲሁ ነው፡፡

እነርሱ በሰማይ ዋጋ አላቸው፡፡ አክሊለ ሰማዕታትንም ተቀብለዋል፡፡ እኛ ግን ሰማዕታቱን ባለማክበራችን ክብር ይጎድልብናል፡፡ ‹በረከታቸው ይደርብን› እንጂ ‹ነፍስ ይማር› አንልም፡፡

የኢኮኖሚ ችግር ሲፈጠር ስደተኛዉን ኢላማ ኣድርጎ ጥቃት መሰንዘር በደቡብ ኣፍሪካ ብቻ የታየ ችግር ኣይደለም። ግሪክ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ሩስያ እና በብዙ ኣገሮች የታየ የተለመደ ክስተት ነው። ህንዳውያን በግሪክ ጎዳና ለመንቀሳቀስ ኣዳጋች እየሆነባቸው እንደሆነ ሁሉ ሞስኮም ኣሁን የውጭ ዜጋ እንደልቡ እማይንቀሳቀስባት ከተማ ሁናለች፤ ለምን ቢባል የኢኮኖሚ ችግር።በነዚህ ኣገሮች ከፈተኛ የፀረ ስደተኛ ጥቃትም እሚፈፀምባቸው ኣገሮች እየሆኑ ነው:: ይሄ ነገር ከዘር እና ከጥቁረት እያገናኙ ደቡብ ኣፍሪካውያንን የቀኝ ገዢዎች ንድፈ ሃሳቦች እየተጠቀሙ “ድሮስ ጥቁር….ለነፃነት ኣቅም ያልደረስ እንስሳ” ምናምን እያሉ የትምክህት ቃል መሰንዘር የጉዳዩን ትክክለኛ ገፅታ ኣለመረዳትን ነው እሚያሳየው። የኢኮኖሚ ችግር ወደ ፖለቲካዊና የፀጥታ ችግር እንደሚቀየር ሳይታለም የተፈታ ሃቅ ነው። በሩዋንዳም በሌሎች ኣገራትም የታየው ይህ ነው። እንዲህ ኣይነት ሁኔታ ለሰነፍ ፖለቲከኞች ጥሩ ኣጋጣሚ ይፍጥራል፤ የሰነፍ ፖለቲካ ደግሞ ቀላል ግን ኣውዳሚ ስለሆነ ዉጤቱ ኣሁን ደቡብ ኣፍሪካ ላይ እያየን ያለነው ኣይነት እልቂት ያስከትላል።ኣንዱን በማስወገድ “መፍትሄ” ለመሻት መጣር ነው የሰነፍ ፖለቲካ ማለት።ለዚህ መዋቅራዊ መደላድል እሚፈጥረው ግን የኢኮኖሚ ችግር ነው። ሁቱዎች ቱትሲዎች ላይ ገጀራቸውን ከማሳረፋቸው በፊት የዋጋ ንረት እና ስራ ኣጥነት ሂወታቸው ላይ ገጀራዉን ኣሳርፎ ነበር። ይህ ቀቢፀ ተስፋነት ሰለፍ ፖለቲከኞች ተመቻቸው እና ዘርን ለማጥፋት ተጠቀሙበት። ደቡብ ኣፍሪካ ላይ እየተፈፀመ ያለ ነገርም ከጄኔቲክ ሳይሆን ከኢኮኖምያዊ ሁኔታ መመሰቃቀል እሚመነጭ ነገር ነው። የደቡብ ኣፍሪካ ለየት እሚያደርገው የኣፓርታይድ ስርኣት በፖለቲካው ረገድ “ሲገረሰስ” የኢኮኖሚው ሁናቴ በነጮች እንደተያዘ እንዲቀጥል መፈቀዱ ነው። ማንዴላ ከዚ ዉጪ ኣማራጭ […]

ከአርአያ ተስፋማሪያም ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱና ባለቤቷ ዘሪሁን በዲሲ እንደሚገኙ ታውቋል። ባላፈው ቅዳሜ ከዲሲ ከሚተላለፈውና ንጉሴ በተባለ “ጋዜጠኛ” ከሚሰናዳው ራዲዮ ጋር ቃለምልልስ ያደረገው ዘሪሁን በዲሲ በሚገኙ የሃበሻ ሬስቶራንቶች ከባለቤቱ ጋር ሲዝናና ኢትዮጵያውያን እየሰደቡት፣ እያስፈራሩትና አንዳንዶች ደግሞ ስልክ እየደወሉ በሱማሊኛ ቋንቋ ተቃውሟቸውን …

የህወሃት በቀቀኖች ሚሚ ስብሃቱና ባለቤቷ ዘሪሁን ተሾመ በዲሲ – አርአያ ተስፋማሪያም Read more »

ክንፉ አሰፋ እለተ እሁድ ከቀትር በሁዋላ አንድ የስልክ ጥሪ ደረሰኝ። ቁጥሩ +251 945226530 ነበር። ስልኩን አነሳሁት። “ሃሎ” “አቤት” “አለማየሁ ነኝ። መን አባክ ነው የምትጽፈው። እኔ አላማዬ ነው። አንተን ግን አንገትህን ቆርጬ ነው የማሳይህ። ለማየት ያብቃህ። ያን የምትጽፈውን ጽሁፍ… እኔ ምንም …

በስለላ ከሆላንድ የተባረረው የጋዜጠኛውን አንገት እቆርጣለሁ አለ Read more »

ፒያሳ አካባቢ ያየነው ትንሽ ለየት ይላል፡፡ መርካቶን አሊያም ከዛም አለፍ ያሉትን የአዲስ አበባ ክፍሎች በቁጥጥር ስራቸው አውለው ወደ አራት ኪሎ እየገሰገሱ የሚመስሉ ፈርጣማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፒያሳ ላይ ገዥ መሬት ይዘዋል፡፡ መኪና አይቀርባቸውም እንጅ መኪና መንገዱን ግማሹን እነሱ እየተንፈላሰሱበት ነው፡፡ ተቆጣጥረውታል! ደግሞ ኮዳና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሳቸውን ግጥም አድርገው ታጥቀዋል፡፡ አንድ ሁለት እርምጃ እንዳለፉ የሚተኩሱ በሚመስል ሁኔታ መሳሪያቸውን ዘቅዝቀው ይዘውታል፡፡ በተጠንቀቅ! በቃ ፒያሳን የጦር ቀጠና አስመስለዋታል፡፡

ከሶስቱ መካከል አንዱ የሁለቱን ደህንነት ለመጠበቅ በሚመስል መልኩ ወደኋላ ይቀራል፡፡ ሰውንም፣ ወርቅ ቤቶቹንም፣ መኪናዎችንም ዘወር ዘወር ብሎ ያያል፡፡ እንደገና ፈጠን ፈጠን ብሎ ይቀላቀላቸውና በአንድ ላይ ወደቀኝና ግራ እያማተሩ መሳሪያቸውን ዘቅዝቀው ይነጉዳሉ፡፡

ሌላ ሶስት አባላት ያሉት ‹‹ጋንታ›› ይከተላል፡፡ እነዚህም በተመሳሳይ ሶማሊያ አሊያም ኤርትራ ድንበር ያሉ ነው የሚመስሉት፡፡ ቀኝና ግራ፣ ወደኋና ወደፊት ይቅበዘበዛሉ፡፡ የቆሙ መኪናዎችን ጠጋ ብለው ያያሉ፡፡ አላፊ አግዳሚው ላይ ያፈጣሉ፡፡ ከእነሱ በኋላ ደግሞ ጯፉ እሳት የተቆሰቀሰበት የሚመስለውን ዱላ ከአጋማሹ ላይ የያዙ አራት ‹‹ተራ አስከባሪዎች›› (ካልሲ አባራሪዎች) ይከተሏቸዋል፡፡ ደጀን ጦር መሆናቸውን ነው፡፡
በዛሬው እለት Getachew Shiferaw አዲስ አበባን እንዲህ ቃኛት::
ማሳሰቢያ፡- አብረውኝ ከነበሩት ሁለት ጓደኞቼ ጋር ፎቶ የማንሳት ፅኑ ፍላጎት የነበረን ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች ፎቶ ማንሳት ሳይቻለን ቀርቷል!
Image

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ከጎንዬሽ ጉዳዬች ውጪ ለ25ተኛ ጊዜ (በአጠቃላይ ለ27ተኛ ጊዜ) የተሰየመው ችሎት ዛሬም የደረጃ ምስክሮችን ሲያሰማ ውሏል፡። ከሳምነትት በፌት የተሰየመው ችሎት አቃቤ ህግ 41 ምስክሮች አሉኝ ነገር ግን ላገኛቸው ስላልቻልኩ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ቆይተው ተጨማሪ ማፈላለጊያ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ጠይቆ ለዛሬ የተቀጠረ ቢሆንም ዛሬም “የሽብር ተግባሩ “ ዋና ምስክሮች ባለመገኘታቸው ፍተሻ ላይ ተገኝተናል […]

የዘንድሮ ምርጫ ኣሸንፎ ለመውጣት የህወሓት መንግስት ኣርባው ሲያስወጣ “…ከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ ፈጥሬ ድጋፍ ኣገኛለው…” ብሎ ኣስቦ ነበር። ይሁን እንጂ ከድጋፍ በላይ ተቃውሞ በመውለድ ያሁሉ ጥረቱ መና ሁኖ መቅረቱ ህወሓት ተረድተዋል። ድሮም በወከባ የሚገኝ ህዝባዊ ድጋፍ እንደሌለ የሚታወቅ ነው። ህወሓት ጥረቱ ከንቱ ሲቀር የዘየደው መላ በትግራይና የሚያዋስኑት የኢትዮ ኤርትራ ድንበር ኤርትራ የጦርነት ድባብ በመፍጠር የምርጫው ኣቅጣጫ […]

አቡበከር አህመድ  መንግስት በሴኩላሪዝም ስም ህብረተሰቡን በተለይ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከእምነቱ ለማስወጣት የሚያደርጋችውን ጥረቶች አጠናከሮ የቀጠለ ሲሆን የዚህ እቅድ አንደ አካል የሆነወን ድርጊቱን ማንኛዉም አይነት የእምነት አዲስ ተቋማት በአድስ አበባ ከተማ ዉስጥ እንዳየገነቡ በሚል መመራያ ማዉጣቱን ምንጮች አስታዉቀዋል። በየትኛዉ እምነት አማኞች ፈጣሪያቸውን በአንድነት የሚያመልኩበት ቦታና የእምነቶቻቸውን ጥሪ የሚያደርጉበት ቦታ የእምነት የእምነት ተቋማቸዉ ሆኖ እያለ ከተማዋ እጅጉን […]

በቨርጂኒያ ሀገረ ግዛት ፣ በሬገን ብሄራዊ የአየር ማረፊያ ተርሚናል ውስጥ አብርሀም ዘመድአገኘሁ የተባለ፣ መስማት የተሳነው እና የጎዳና ተዳደሪ የሆነ ኢትዮጵያዊ ወንድማችን ምንም በማያውቀው እና ባልፈፀመው ወንጀል አይፓድ ሰርቀሀል በሚል በፖሊስ ተይዞ ለስድስ ሳምንታት በወይህኒ ቤት አሳልፏል። አብርሀም ከተያዘበት ሰአት ጀምሮ ለሀያ አራት ሰዓታት በምን ምክንያት እንደታሰረ ካለማወቁም በተጨማሪ ያረፈበት የእስር ቦታ ( jail ) መስማት […]

ክቡር አቶ አባይ ፀሐዬ የህ.ወ.ሓ.ት/ኢህአዴግ መስራች አባል ታጋይና በአሁኑ ግዜ በሚኒስትር ማአርግ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማእከል ዋና ዳይርክተር ናቸው፡፡ ከጋዜጠኛ ዘርአይ ሀ/ማርያም በኦህዴድ ታሪክና የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳዮች ቆይታ አድርገዋል፡፡ ሙሉ ቃለ-ምልልሱ ከዚህ በታች በጽሑፍ የቀረበ ሲሆን፤ ቪዲዮውን ደግሞ ከታች መመልከት ይችላሉ፡፡ —— ዘርአይ ኃ/ማርያም:- በትጥቅ ትግሉ ዘመን ኦህዴድ የኢህአዴግ አንድ አባል ድርጅት ሆኖ መቆሙ የነበረው ፋይዳ ምን ነበር? አቶ አባይ ፀሐዬ፡- የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦህዴድ/ አንድ የኢህአዴግ አባል ድርጅት ሆኖ መደራጀቱ በመጋቢት 1982 ዓ.ም ፋይዳው ከዛ በፊት የኦሮሞ ህዝብ በዴሞክራሲያዊ አላማ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝብ አስተሳስሮ የሚያታግለውና የሚመራው ዴሞክራሲያዊ ድርጅት በማጣቱ የተፈጠረ ድርጅት ነው፡፡ ከዛ በፊት የነበረ የኦሮሞ ህዝብ ትግል የብሄር ጭቆናው የሌላው በደልንም ከተጀመረበት /ከተፈጠረበት ግዜ ጀምሮ ሲታገል የቆየ ህዝብ ነው፡፡ በብሄራዊ መብቱም ለአጠቃላይ የኢኮኖሚያዊና ዴሞክራሲያዊ አጠቃላይ መብትም፡፡ ግን ከዛ በፊት የነበሩ ድርጅቶች የተለያዩ በኦሮሞ ህዝብ ስም የተደራጁ ድርጅቶች ቢኖሩም አንደኛ ጠንካራ የህዝብ ድጋፍ እና ጠንካራ የህዝብ ማደራጀት ስራ አልነበረባቸውም፡፡ ወደ ህዝብ ገብተው ህዝቡን አደራጅተው ከህዝቡ ጋር ሆኖ የህዝቡን ስሜት አዳምጠው ሀይል የፈጠሩ አቅም የፈጠሩ ጠንካራ ድርጅቶች ጠንካራ የትጥቅ ትግል ሰራዊት የፈጠሩ አልነበሩም፡፡ ስለዚህ እየተደነቃቀፉ እየተኳላሹ ወደ አጎራባች ሀገሮች ወጣገባ እያሉ ነው ግዚያቸውን ያሳለፉትበአብዛኛው፡፡ ሁለተኛ መላውን የአማራ ህዝብና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደጠላት የሚወስዱ ናቸው የነበሩ፡፡ ይህ ደግሞ የኦሮሞ ህዝብ ፍላጎትና ጥያቄ አልነበረም፡፡ የህዝቡ ጥያቄ የፖለቲካ ዲሞክራሲ የማንነትና የኢኮኖሚ […]

የኢትዮጵያ መንግስትን በጦር ሀይል ለመጣል ሚታገሉት “የኢትዮጵያ የተባበሩት አርበኞች ግንባር” በደቡብ ሱዳን ግጭት ውስጥ ከፕሬዘዳንት ሳልቫኪር ሀይል ጎን ተሰልፎ የተቃዋሚውን የሪክ ማቻርን ሀይሎች ይወጋል በሚል የቀረበባቸውን ክስ ውድቅ አደረጉ. በሪክ ማቻር የሚመሩት የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚዎች በቅርቡ እንዳስታወቁት ከሆነ በምእራብ ኢትዮጵያ ጋምቤላ ክልል ሚንቀሳቀሰውና በቀድሞው የአካባቢው አስተዳዳሪ በሆኑት በቶዋት ፓልቻይ የሚመራው የኢትዮጵያ አርበኞች ግንባር ኢትዮጵያን ለመውጋት […]

(ኃይለሚካኤል ዘስላሴ) በዓለም ያለት የተለያዩ የሕግ ሥርዓቶች ከሚሰማሙባቸው የሕግ ጽንስ ሐሳቦች አንዱ የሕጋዊ ሰውነት ጽንስ ሐሳብ ነው፡፡ በዚህ ጽንስ ሐሳብ መሠረት ከተፈጥሮ ሰው በተጨማሪ እንደተፈጥሮ ሰው የሚቆጠር ወይም ሰው የሆነ አካል አለ፡፡ በዚህም መሠረት ሁለት ዓይነት ሰዎች አሉ ማለት ነው፡፡ አንደኛው ሰው የተፈጥሮ ወይም ግለ ሰብ ሲሆን ሁለተኛው ሰው ደግሞ በሕግ የሰውነት መብት (ግዴታም ጭምር) ያለው ወይም የተሰጠው አካል ማለትም ማኅበር፣ የንግድ ማሕበር ወይም ድርጅት ነው፡፡ በመሠረቱ ማነኛውም ሰው የተፈጥሮም ይሁን በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው ወይም ያለው አካል የመብትና የግዴታ ባለቤት ነው፡፡ በዚህም ውል መዋዋል፣ የነብረት ባለቤት መሆን፣ መክሰስና መከሰስ ይችላል፡፡ ከቤተሰብ ሕጎች እና ከአንዳንድ የወንጀል ሕግ ድንጋጌዎች በስተቀር የየአገሩ ሕጎች በተፈጥሮ ሰውና በሕግ የሰውነት መብት ያለው አካል በእኩልነት ተፈጻሚነት አላቸው፡፡ የተፈጥሮ ሰው የመብትና ግዴታ ባለቤት የሚሆነው እና በሕግ ኃላፊነት የሚኖረው በተፈጥሮ ሰው በመሆኑ ነው፡፡ ግዑዝ የሆኑ አካላት ማለትም ማሕበራት የንግድ ማኅበራት እንዲሁም ድርጅቶች እንደ ተፈጥሮ ሰው የሚቆጠሩትና በሕግ የሰውነት መብት ይጣቸዋል የሚል ጥያቄ ለመመለስ በርካታ ንደፈ-ሐሳቦች ተቀምሯል፡፡ እነዚህ በርካታ ንድፈ-ሐሳቦች በሁለት ክፍሎች ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ የመጀመሪያወ ምናባዊ ወይም ሕግ ወለድ ንድፈ ሐሳብ (fiction theory) የሚባለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ እርግጠኛ ንድፈ ሀሳብ (Real theory) በመባል የሚታወቀው ነው፡፡ እነዚህ ንደፈ ሃሳቦች ጥልቅ መሠረት እና ትንታኔ ያላቸውና አመሠራረታቸውና ዕድገታቸው ሰፊ እና ከመንስት አመሠራረት ጋር የተያያዘ ቢሆንም ለአጠቃላይ ግንዛቤ ይረዳል በሚል በሁለቱም ንድፈ […]

ትላንት አመሻሽ ላይ በዲሲ 16ኛው መንገድ “የእኛ እድር” የተሰኘ ድራማ ይታይ ነበር። ዝግጅቱን ለመታደም ከኢየሩስና አብራት ከምትማረው ታዳጊ ኤልሳ ጋር በስፍራው ተገኘን። ድራማው ይጀመራል ከተባለበት ጊዜ ለ1 ሰዓት ተኩል ዘግይቶ ነበር። (ሃበሻና ቀጠሮ መቼ እንደሚታረቁ አይታወቅም)…ዝግጅቱ እስኪጀምር ወግ ቀጠልን። ታዳጊ ኤልሳ አሜሪካ ከአባቷ ጋር የመጣችው ከ5 አመት በፊት ነበር። የ16 አመቷ ኤልሳ በገፅታዋ ብሶትና መከፋት […]

መረጃ ለነፃነት በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ አማኑኤል ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የመምህራን ስብሰባ ላይ የምረጡን ቅስቀሳውን ይዞ የቀረበው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጠመው፣ በደረሰን መረጃ መሰረት የማቻከል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የኔነህ እና የወረዳው የትምህርት ዝሕፈት ቤት ሃላፊው አዲሱ የተባሉት በወረዳው እየተካሄደ በነበረው የመምህራን የርዕሳነ መምህራንና የሱፐርቫዘሮች ስብሰባ ላይ በአጀንዳነት የቀረበውን የትምህርት ጥራትና የውጤት ተኮር […]

Image

ከኦባማ ቀጥሎ በአሜሪካ ከፍተኛው ደመወዝ ተከፋይ ነበሩ
ከ2ሺ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን አከናውነዋል
ወንድሞቻቸው፡- ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን ይባላሉ

ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኤሌክትሮን ክበበው፤ ለ33ኛ ጊዜ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የ2015 “የዓመቱ የዓለማችን ልዩ ስም” ውድድር ላይ ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በቀዳሚነት እየመሩ እንደሆነ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ዘንድሮም የተለያዩ አገራት ዜጎችና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ 64 ግለሰቦች ያልተለመዱ ስሞች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ኤልክትሮን ክበበው፤ በ1ሺህ 132 ድምጽ፣ በ89.6 በመቶ ውጤት በቀዳሚነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በኢሜልና በተለያዩ መንገዶች ከቀረቡለት በርካታ ለየት ያሉ ስሞች 64 ያህሉን በመምረጥ፣ ለአንድ ሳምንት ያህል በድረ ገጽ አማካይነት ድምጽ እንዲሰጥባቸው የሚያደርገው የውድድር ኮሚቴው፤ የመጨረሻውን ውጤት ከጥቂት ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
የሰማይ እንሽላሊት፣ ጣፋጭ ቡና፣ ዳላስ፣ ቶክዮ፣ ቴኒስ እና የመሳሰሉ የአገር፣ የቦታ፣ የእቃ፣ የሰብል ወዘተ መጠሪያዎችን የያዙ የተለያዩ አገራት ዜጎች በዘንድሮው ውድድር እንደተሳተፉ አወዳዳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
በዘንድሮው ውድድር ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በመምራት ላይ ለሚገኙት የ47 አመቱ ዶ/ር ኤሌክትሮን ይህን ስም ያወጡላቸው፣ ኤሌክትሪካል ኢንጂነር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አባታቸው አቶ ክበበው ነበሩ፡፡
ልጆቻቸው የእሳቸውን ፈለግ ተከትለው በሳይንሱ ዘርፍ ላይሰማሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ያደረባቸው አቶ ክበበው፤ በልጆቻቸው ልቦና ውስጥ ገና በለጋ እድሜያቸው የሳይንስን ስሜት ለማስረጽ በማሰብ ነው፣ ባልተለመደ ሁኔታ ለልጆቻቸው ከኤሌክትሪሲቲ ጋር የተያያዙ ስሞችን ያወጡት፡፡
አቶ ክበበው፤ ለአምስቱ ልጆቻቸው ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን የሚሉ ስሞችን አውጥተዋል፡፡ ዶ/ር ኤሌክትሮን በስማቸው ብቻ አይደለም የሚለዩት፡፡ ከስማቸው በላይ ብዙዎችን ያስገረመው፣ በህክምና ሙያቸው የአሜሪካ መንግስት የሚከፍላቸው ዳጎስ ያለ ደመወዝ ነው ይላል ድረ-ገጹ፡፡
ከአራት አመታት በፊት “ዊኪኦርግቻርትስ” የተባለ ተቋም “የአመቱ የአሜሪካ መንግስት 1000 ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች” በሚል ባወጣው ዝርዝር ውስጥ፣ ዶ/ር ኤሌክትሮንን ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ቀጥሎ ከፍተኛ ደመወዝ የሚያገኙ የመንግስት ሰራተኛ በማለት በሁለተኛነት አስቀምጧቸዋል፡፡
በአዲስ አበባ በሚገኘው ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የተማሩት ዶ/ር ኤሌክትሮን ክበበው፤ በአሜሪካ ሳንፍራንሲስኮ ከሚገኘው ዪኒቨርሲቲ ኦፍ ካሊፎርኒያ በህክምና የተመረቁ ሲሆን የአሜሪካን ቦርድ ኦፍ ሰርጀሪን የቀዶ ህክምና ሰርተፊኬትም አግኝተዋል፡፡
ላለፉት 20 አመታት በሳንፍራንሲስኮ በኢንዶክሪንና ታይሮይድ ካንሰር ዘርፍ የአጠቃላይ ቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ዶክተሩ፤ በአሜሪካ ብሄራዊ የካንሰር ኢንስቲትዩት፣ የካንሰር ምርምር ማዕከል የኢንዶክራይን ኦንኮሎጂ ቅርንጫፍ ሃላፊ ሲሆኑ የካንሰር ጄኔቲክስ ክፍሉንም በበላይነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ዶክተሩ በእስካሁኑ የሙያ ዘመናቸው ከሁለት ሺህ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን ያከናወኑ ሲሆን ከ150 በላይ የጥናት ጽሁፎችንና መጽሃፍትን ለህትመት እንዳበቁ “ብሬኪንግጎቭ” የተሰኘ ድረገፅ አመልክቷል፡፡

ኢትዮጵያዊው በተመድ የአለም የጤና ድርጅት ባለስልጣን በታይላንድ ኢትዮጵያዊቷን ሰራተኛውን ሲያስቃይ ተደረሰበት::

ኢትዮጵያዊቷን ለሁለት አመት አግተው በታይላንድ ሲያሰቃይዋት የነበሩት ኢትዮጵያውያን ናቸው::

ዶክተር ዮናስ ተገኝ የተባለ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ የሚሰራ ግለሰብ ለኢትዮጵያዊቷ ስቃይ ተጠያቂ መሆኑ ተደርሶበታል::ባለፈው ሳምንት አለምነህ ዋሴ በአዋዜ ፕሮግራሙ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስን ዋቢ አድርጎ በለቀቀው የአንዲት ኢትዮጵያዊት የታይላንድ ሰቆቃ (http://www.clickhabesh.com/?p=105552) አሰቃዮቿ ተብለው በሰራተኝነት ቀጥረው የወሰዷት በተባበሩት መንግስታት የአለም ጤና ድርጅት የታይላንድ ባለስልጣን ዶክተር ዮናስ ተገኝ እና የትዳር አጋራቸው ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ተረጋግጧል::

አለምነህ ዋሴ ኤ ኤፍ ፒን ዋቢ አድርጎ የገለጻት ኢትዮጵያዊ ከሃገር ቤት በቤት ሰራተኝነት ሊያሰሯት ከወሰዴት በኋላ ለአመታት ደሞዟን ሳይከፍሉ ከተዋት እስከ ማታ ደረቅ ሩዝ እንድትበላ በማድረግ ከውሻ ጋር ባንድ ክፍል እንድትተኛ በማድረግ ሲያሰቃይውት እንደነበር እና በስተመጨረሻ ራሷን ለማጥፋት ስትሞክር ሰው ደርሶላት አድኗት ለአንድ የሰብ አዊ መብት ድርጅት እንደሰጣት እና በአሁን ሰአት ጉዳዩን የታይላድ ፖሊስ እየተከታተለው እንደሆነ መገለጹ ይታወሳል::

ኢትዮጵያዊቷን በቤት ሰራተኝነት አምጥቶ ሲያሰቃያት የነበረው ግለሰብ ራሱን ከወንጀሉ ነጻ በማድረግ ምንም ወንጀል እንዳልፈጸመ እና ትክክለኛ ሰው አድርጎ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በኢሜይል ሊያስተባብል ሞክሯል::(viewtopic.php?f=2&t=95181)በዘመናዊ ባርነት ላይ የተመሰረተ የመብት ገፈፋ ያካሄደው ግለሰም የ25 አመቷን እና ስሟ እስካሁን ያልተጠቀሰውን ኢትዮጵያዊት በ2000 ብር ክፍያ ከኢትዮጵያ አምጥቶ ሰብአዊነት በጎደለው ሁኔታ ሲያሰራት እንደነበር የገለጸው ባንኮክ ፖስት ግለሰቡን ለማናገር ቢፈልግም ዶክተር ዮናስ ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል::

እጅግ ያማል!! ደሞ ነገሩን በይቅርታ እነ በፍቅር መፍታት ሲገባው አለማፈሩ ለኤ ኤፍ ፒ ኢሜይል ያደርጋል::http://mereja.com/forum/viewtopic.php?f=2&t=95181
Image

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ባሳለፍነው ቀናት ጀምሮ በፌዴራል ፖሊሶች እና በአዲስ አበባ ፖሊሶች ላይ ጠንከር ያለ ግምገማ እየተካሄደ መሆኑን ሲታወቅ የፖሊሶቹ ሞባይል ስልኮች ሳይቀሩ ድንገት በደህንነት ሃይሎች እየተፈተሹ እና አላስፈላጊ የተባሉ እና ለወያኔ የማይመቹ የተጫኑ ዘፈኖች ፎቶዎች እና የተለያዩ ዶክመንቶች ሲሰረዙባቸው የነበረ ሲሆን በርካታ ፖሊሶች በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ሲደረግ የተወሰኑ ደሞ ክትትል እንዲደረግባቸው ታዟል:ከስራቸው የታገዱ እና የታሰሩ እንዳሉም ተጠቁሟል::

በአዲስ አበባ ለከተማው ፓሊስና ለፊደራል ፓሊስ ድንገት የተጀመረው ገምገማ እረፍት አንዳይወጡ በእረፍት ላይ ያሉት እንዲመጡ ተደርጎ በድንገት ሞባይል ተሰብስቦ በውስጡ የተለያዩ በመንግስትና በባለስልጣን የሚያላግጡ ቀልዶች የቴዲ አፍሮ ከሊፕ የተገኝበት የአማርኛና የኦሮምኛ ሀይለኛ ቀሰቃሽ ዘፈኖች የተገኘበት ከተለያዩ ሰዎች ጋር የተላላኩት መልክቶች ተጎርጉረው የተገኙባቸው እንዳስፈላጊው እርምጃ እንደተወሰደባቸው ሲገለጽ የታገዱ የታሰሩ ደሞዛቸውን የተቀጡ ሲኖሩ ወደፊት በድጋሚ ቢገኝባቸው ትልቅ ችግር ሊፈጠርባቸው እንደሚችል ማስጠንቀቂያ ተሰቷቸዋል::

የለውጥ ሃይሎች በወታደሩ እና በፖሊስ ሃይሉ ዙሪያ ጠንካራ ስራ መስራት ይጠበቅባቸዋል ያሉት የመረጃው አድራሾች ፖሊሶች የሚያቀናጅ ሃይል እና የሚያስተባብር ሃይል ማጣታቸው እንዲሁም እንደ ደርግ ሃይል ትበተናላችሁ ሌላ ስልጣኑን ቢይዝ በማለት የሚደረገው ማስፈራሪያ በወያኔ እየተደረገባቸው መሆኑ ስለሆነ ከለውጥ በኋላ በስራቸው እንደሚቀጥሉ እና ከለውጥ ሃይሎች ጎን ቆመው ይህንን አምባገነን ስር አት እንዲገረስሱ አስፈላጊ የሆነ የግንዛቧ ማስጨበጫ ስራዎች እንዲሰሩ አሳስበዋል::

Image

የወያኔ ወታደሮች ስርሀቱን በመክዳት ላይ መሆናቸው ተሰማ የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ለ10ኛ ጊዜ ተመለሰ የወያኔ ሰላዮች በማህበራዊ መገናኛዎች አማራና ኦሮሞን ሊያጋጭ ይችላሉ የተባሉ ክብረነክ ጽሁፎችን እንዲያሰራጩ ታዘዙ። ኢትዮጵያ የደቡብ ሱዳንን ተፋላሚዎች ከማስታጠቅ ጀርባ እጇ አለበት ተባለ የአል-ሻባብ ታጣቂዎች በኬንያ ጋሪሳ ዩኒቨርሲቲ 147 ተማሪዎችን መግደላቸው ታወቀ በናይጄሪያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ አሸነፋ   አሰግድ ታመነFiled under: NEWS Tagged: Addis […]

ህወሃት መሪ ያጣ ድርጅት ነው። እኔ ለህወሃቶች የምመኝላቸው፣ እውነተኛ እራእይ ያለው መሪ እንዲያገኙ ነው። ለነገ ሳይስቡ ዛሬ ሆድን በኪሳራ ከሞምላት፣ እራስን ከማወደስ፣ ሌሎችን ከማኮሰስ፣ አፈናቅሎ ከመውረስ፣ አምታቶ ከመዝረፍ፣ በሃሰት ከመክሰስ፣ ህዝብን ፈርቶ ከመኖር፣ በደካማ ዜጎች ስቃይ ከመደሰት፣ በዘርና በጎጥ ከመከፋፈል፣ በባዶው ከመጎረር፣ የሃሰት ክብርና ዲግሪ ከጥቁር ገበያ በርካሹ ከመሰብሰብ፣ ጥራት የሌላቸው የሰው አሻንጉሊቶች ከመሰብሰብ የሚያድን […]

ግብጽ 13 ተኛ ስትባል ኢትዮጵያ 46 ተኛ ላይ ተቀምጣለች የፈረንጆቹ 2015 የአለም ሀገራት የጦርና ወታደራዊ አቅም በግሎባል ፋየር ፓወር ተቋም አማካኝነት ማክሰኞ እለት ይፋ ተደርጓል. ተቋሙ በዘንድሮው ሪፖርቱ ከ 50 ባላነሱ የመመዘኛ መስፈርቶች የመዘናቸውን የአለም 106 ሀገራት የወታደራዊ ጡንቻ አቅም በደረጃ ማስቀመጡን አስታውቋል. የሀገራት የወታደር ቁጥር, ለጦር ሰራዊታቸው የሚመድቡት አጠቃላይ በጀት, የጦር መሳሪያዎቻቸው ብዛት, ጥራትና […]

አንድ የት ሂዱ ነው? ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን ‹‹የሙጢኝ!›› ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን ‹‹የሙጢኝ!›› እንላላን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞትን ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ […]

በጋሞ ጎፋ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ አልጌ ቀበሌ ፖሊስ በንፁሃን ላይ የጭካኔ እርምጃ መውሰዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በአባያ ሀይቅ ዙሪያ በእርሻ ስራ ላይ የተሰማሩት ነዋሪዎች መሬት ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት እንደተሰጠባቸው መነገሩን ተከትሎ የአካባቢው ሽማግሌዎች ከሶስት ጊዜ በላይ ለክልሉ አስተዳደር ማመልከቻ ቢያስገቡም መልስ ሊያገኙ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡ የክልሉ አስተዳደር ምንም አይነት መልስ ባይሰጥም የዞኑ አስተዳደር ‹‹መሬቱ ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት ተሰጥቷል፡፡›› የሚል ውሳኔ በማስተላለፉ ነዋሪዎቹ ይህን የዞኑን አስተዳደር ውሳኔ እየተቃወሙ ይገኛሉ፡፡ ይህን የህዝቡን ተቃውሞ ተከትሎም ፖሊስ በአባያ ነዋሪዎች ሰፈር እየመጣ እያስፈራራ እንደሚመለስ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

የካቲት 30/ 2007 እንደተለመደው ፖሊስ ነዋሪዎቹን ለማስፈራራት ወደ ሰፈር በሄደበት ወቅት ነዋሪዎቹ ፖሊሶቹን ‹‹ከሰፈራችን ውጡልን!›› እንዳሏቸው ተገልጾአል፡፡ ይሁንና ፖሊስ ከሰፈራቸው እንዲወጡለት የጠየቁትን አዛውንቶችን ጨምሮ ነዋሪዎች ላይ ድብደባ መፈጸሙ ተገልጾአል፡፡ ፖሊስ አዛውንቶቹ ላይ ድብደባ መፈጸሙን የተቃወሙ ወጣቶች ላይ ጥይት በመተኮስ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ወስዷል፡፡ በወቅቱም አንድ ሰው ሲሞት ከ8 ሰዎች በላይ ከፍተኛ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው ተገልጾአል፡፡

እስካሁን ድረስ በንጹሃኑ ላይ የጭካኔ እርምጃ የወሰዱት ፖሊሶች ምንም አይነት ህጋዊ እርምጃ እንዳልተወሰደባቸውና በስራ ገበታቸው ላይ እንደሚገኙም የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

Image

ጊዜው 1997 ነው። አብዛኛዎቻችን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፥ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች እንዲሁም ተመርቀን ስራ አጥተን ሰፈር ውስጥ የምንውል ስራ አጦችና ( በኢህአዲግ አባባል አደገኛ ቦዘኔዎች) ወጣትነት ጉልበታችንን በስራ ለመፈተን እየተንቀሳቀስን የነበርን ወጣቶች ትኩስ ኋይሎች ነበርን።

በወቅቱ በተነሳው የለውጥ እንቅስቃሴ አንዳችንን ከአንዳችን ሳይለይ በጊዜው የነበርነውን ሁሉ ማርኮን አጥብቀን በመከታተል በሂደቱ በተለያየ መልኩ ተሳታፊ ሆነን አገኘነው። በከፍተኛ ሁኔታ በለውጡ ማዕበል ውስጥ ሁላችንም እየተናጥን ነበር።

ለውጥ!የዚህ ትውልድ አባላት የሆንን በወቅቱ ምንም አይነት ይሁን እንጂ ለውጥ እንፈልግ ነበር። ለውጡም በምንም መልኩ ይምጣ አጠቃላይ መንግስታዊ ለውጥ ተካሂዶ ከማየት ባሻገር በአገር
ግንባታ ውስጥ መሰረታዊ የነበሩትን ጥያቄዎች የሚመልስ ለመሆኑ እርግጠኞች ለመሆን በብዙም አልተጨነቅንም። የተካሄደው የፖለቲካው እንቅስቃሴ ለውጡ ለውጡ እንዲዳፈን የተደረገበት መንገድ ትውልዱን በደንብ አገሩን እንዲያስባት አድርጎታል። ለዚህም በአዲስ ነገር ጋዜጣ በመስፍን ነጋሽ በኩል ወደ አደባባይ የወጣው የትውልዱ የመጀመሪያ ጥያቄ የነበረው ይህቺ አገር የማን ናት የሚለው ነበር። ይሄንንም ጥያቄውን ሲያውጠነጥን አገሩ የጥቂቶች ሆና ነው ያገኛት ስለዚህም ትውልዱ የኔ የሚላት አገር እንድትኖረው ሻተ።

ምን አይነት ሀገር? የ1997 ምርጫ ትውልዱን ብዙ አስተምሮታል። በህዝብ ዘንድ የነበረው የስርዓት ለውጥ ፍላጎት እንዲዳፈን የሆነው እንደሀገር ምን ስላልነበረን ነው? የሚለውን ጥያቄ አንስቶ በእጅጉ እንዲያብሰለስለው ሆኖዋል። ተብሰልስሎ ብቻ አልቀረም አልቀረም ለጠየቃቸው ጥያቄዎች ራሱ በመብሰልሰሉ ውስጥ መልሱን አግኝቶት ነበር። ይኸውም የነፃ ተቋማት ያለመኖር ችግር
የለውጡን ፍላጎት እንዳዳፈነው ተረድቶታል።

ስለሆነም ነፃ የፍትህ ተቋማት፥ ነፃ ሚድያ፥ ነፃ የሲቪክ ተቋማት፥ ነፃ የመከላከያ ኋይል፥ ነፃ የፖሊስ ሰራዊት እንዲሁም የደህንነት ኋይል የተገነባች ሁሉም ጥያቄዎች በጠረጴዛ ዙሪያ የሚፈቱባት
ሀገርን ሽቶዋል። ለመሻቱ ተግባራዊነት ደግሞ በዚህ ወታደራዊ ነፍጥ አንጋቢ አንባገነን ሁሉን ጨፍልቆ መውሰድ በሚፈልግ ስርዓት ውስጥ ሊተገበር እንደማይችል አረጋግጦዋል። የትውልዱ
ጥያቄ ሊመለስ የሚችለው አጠቃላይ የስርዓት ለውጥ ማምጣት ሲቻል ብቻ እንደሆነ ተረድቶዋል። ለውጡ እንዴት ይምጣ? ትውልዱ ባለፉት 10 አመታት በተለያዩ ወቅቶች እርስ በእርስ
በነበረው ግኑኝነት ለውጥ፥ ለውጥ ብሎ ደጋግሞ አንስቶዋል። ይህ ትውልድ አሁን ወጣትነቱ ወደ ማብቂያው እየሄደ ቤተሰብም አፍርቶ ወደ ጉልምስናው መጀመሪያ እየገባ ነው።

በወጣትነቱ የጠየቃቸው ጥያቄዎች ሳይመለሱ የወጣትነት ዘመኑ መጨለም ሊጀምር እየዳመነ ነው። ትውልዱ የጥያቄዎቹ እንዲሁም የታሪኩ ባለዕዳ ነው። ያነሳቸውን ጥያቄዎችና የታሪክ ኋላፊነቱን የሚወጣበት ጊዜው አሁን ነው። ወጣትነቱ ከመጨለሙ በፊት ባለታሪክ የሚሆንበት ለነገው ትውልድ ለሱ ልጆች የታሪኩን የተፃፈ ገፅ የሚያነብበት የዕርጅናው ወራት ሲመጣ ለልጆቹ የሚተርከው የተፃፈ ገፅ እንዲኖረው አሁን ወደ አደባባዮቹ የመትመሚያው የመጨረሻው ጊዜ ላይ ነው።

ይህ እንዴት ይሆናል? ለውጡን በምን መልኩ ማካሄድ ይቻላል? ብሎ የደረሰበት መደምደሚያ ህዝባዊ እምቢተኝነትን በሀገሩ ላይ በመተግበር ወደ አደባባዮቹ መትመም ያንተ የጦርነት አውድማ
አሲንባ ወይም ደደቢት አይደለም በሀገርህ ላይ ያሉት አደባባዮችህ ናቸው። ሀገር እንዳይኖርህ ሀገር አልባ ያደረገህን ስርዕት ከስሩ መንግሎ ማፍረስ ነው። ይህ ሲሆን ያኔ ባለታሪክ ይሆናል ጥያቄዎቹም ይመለሳሉ። ያኔ ታድያ የታሪኩ ባዶ ገፅ እየተገለጠ በሚነበብ፥ በሚተረክ የተፃፈ ገፅ ይሞላል።በጉልምስናህም ዘመን ኩራት፥ ክብር የሰው ልጆች ፍላጎት የሆነው ይኖርሃል፥ በማሻውም እድሜህ ለልጆችህ
የታሪክህን ገፅ እየገለጥክ ያኔ እነሱ በማንነታቸው ኮርተው የኔ ብለው የሚኖሩባትን ሀገር ዲሞክራሲያዊት፥ ፍትሃዊት፥ የነፃ ህዝቦች መኖሪያን፥ የሀገር ባለቤትነትን ማረጋገጥ የቻልክ አባት መሆንህን ትተርክላቸዋለህ።

አርአያዎች ከየትም አትፈልግ የትውልድህ አባላት የሆኑት ያንተን የነፃነት ውልድ እያማጡ ያሉ አሉልህ። ተመልከት እነ አንዷለም አራጌን፥ ተመልከት እነ ሃብታሙን አያሌውን፥ ተመልከት እነርዕዮትን፥ ተመልከት ተመስገንን ያንተን ምጥ ሲያምጥ፥ ተመልከት እነ ማህሌትን፥ እነ ኤዶምን፥ እነበፍቄን፥እነ ናቲን፥ እነ ዘላለምን እን አቤልን. ……….ለአንተ ትውልድ ጥያቄዎች ዋጋ እየከፈሉ ነው። ምን ቤት አለህና ቤትህ ትገባለህ ያንተ ቤት አደባባዮችህ ናቸው። ለባርነት ማዶ አትመልከት ለነፃነትህ ወደ ራስህ ቤት ተመልከት።

እንደመደምደሚያ ይህ ትውልድ ብዙ ተብሎዋል በጫት የናወዘ፥ ከራሱ ባሻገር አገራዊ ራዕይ የሌለው ወኔ አልባ፥ አደገኛ ቦዘኔና ብዙ አልባሌነቱን የሚነግሩት ማንነት ተደርቦለታል። እሱ ግን እንደዚህ እንዳልሆነ የሚያስመሰክርበት አሁን ታሪክ 2007ን ሰጥቶታል። አብዮቱንት ተሸክመው የሚዞሩት እንኳን አልፈሩም ትውልዱስ ስለምን ይፈራል? እሱ ከትላንት አባቶቹ በምን ያንሳል? እንደ ቱኒዝያ፥
ግብፅ፥ ቡርኪና ፋሶ አቻዎቹ የለውጡ ባለቤት እንደሆነ ያረጋግጣል የሚል እምነት አለኝ አደባባዮቹም የሀገሩን ልጆች ወጣቶቹን ናፍቀዋል።

ወራዙት ይአቅቡከ (ያፈቅሩከ)

Image

Tekle Bekele – ለኔ እዉነተኛዉ የአንድነት ፓርቲ ትናንት በፍ/ቤት ዉሳኔ ተቀብሯል፡፡ዱባና ቅል አበቃቀሉ ለየቅል እንደሆን ቀድም ሲል አዉቀናል፡፡ዳኛ ብርቱኳንም ፍርህይወትም ዳግም አልተከሰቱም፡፡እንደ ኢህአዴጉ የምርጫ ዉጤት 99.6 ከመቶዉ አመራሩና አባላቱ በምርጫ ቦርድ እንዲበተኑ የተበየነበት እንዲሁም በደጋፊዎች የተገዛ ንብረት ያለፍ/ቤት ትእዛዝ በመንግስት ታጣቂ ፖሊሶች የተዘረፈበት አንድነት የፍትህ ተቋሙን ለመፈተሸ ም/ቦርዱን መክሰሱ ይታወቃል፡፡
ም/ቦርድን መክሰሳችን አግባብ እንዳልሆነ አንቀጽ ተጠቅሶ ከማስፈራሪያ ጋር ክሱ ዉድቅ ተደርጓል፡፡ መፍትህ መረገጡን ባደባባይ አስመስክረናል፤ሃላፊነታችንንም ተወተናል፡፡ቀጣዩን በቀጣይ ሂደት የምናየዉ ይሆናል፤እንደሚፈልጉት ተበትነን አንቀርም፡፡አንድነቶች በያለንበት እንረጋጋ!!
ታላቋ ምእራብ አፍሪካዊት ሃገር ናይጀሪያ እዚህ የደረሰችዉ ዉድ ዋጋ ከፍላ ነዉ፡፡ከናይጀሪያም በላይ ዋጋ ብንከፈልም በልተዉ በማይጠግቡ በሎች ትግሉ እየተነጠቀ ዛሬም እዛዉ ላይ ነን፡፡ታላቅዋ የምስራቅ አፍሪካ ኮከብ ሀገረ ኢትዮጵያ በልማት ስም ክብሯ እንዲወርድ እየተደረገች ትገኛለች፡፡እናም በዲፕሎማሲ፤በዲሞክራሲ፤በኢኮኖሚም ይሁን በሁለንተናዊ ልማት የአለም ማህበረሰብ በአፍሪካ ትኩረት ናይጀሪያ ሆናለች፡፡ኢትዮጵያ የምትፈለገዉ ለክፍለአሁጉሩ የደህንነት አጋርነት ብቻ ነዉ፡፡
የናይጀሪያ ተፎካካሪ ፓርቲዎችና(የተቀናቃኝ ፓርቲዎች ትብብርና ዉህደት ያስከተለዉን ዉጤትም ልብ ይሏል) የተወዳዳሪ ግለሰቦች ሚና ቀላል ባይሆንም ለናይጀሪያ ተስፋ የሆናት ግን ህዝቡ ነዉ፡፡የኢትዮጵያችንም የለዉጥ ተስፋ ህዝቡ ነዉ፡፡በዚህ ወቅት የተቃዋሚ የፖለቲካ ሃይሎች አሰላለፍም የጎላ ድርሻ ይኖረዋል፡፡
Image

ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በአባይ ወንዝ ፍትሃዊ አጠቃቀም ላይ በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ ሲያደርጉት የነበረውን ድርድር ወደ ፖለቲካ ኮሚቴ ከፍ በማድረግ ለወራት የዘለቀ ድርድር በሶስቱ አገራት ረዕሰ መዲናዎች ላይ ሲያካሂዱ ቆይተዋል። እነዚህ ድርድሮችም ፍሬ አፍርተው አገራቱ የአባይ ወንዝን ዓለም አቀፍ መርህዎችን ተከትለው ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ስምምነት ትናንት በሱዳን ካርቱም ተፈራርመዋል። በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣ በግብፅ ፕሬዚዳንት አብዱል ፋታህ ኤልሲሲ እና በሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር መካከል የተፈረመው ስምምነት ሶስቱንም አገራት እኩል ተጠቃሚ እና ዓለም አቀፍ መርህዎችን መሰረት ያደረገ ነው ተብሎለታል። የዚህን ስምምነት ሰነድ ሙሉ ቃል ከአስረጅ ጋር እንደሚከተለው ቀርቧል። መግቢያ የግብፅ አረብ ሪፐብሊክ፣ የኢትዮጵያ ፌዴራሊያዊ ዴሞክራሲያ ሪፐብሊክ እና የሱዳን ሪፐብሊክ እየጨመረ የሚገኘውን ድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብቶቻቸውን የመጠቀም ፍላጎትን መሰረት በማድረግ የናይል ወንዝ የግብፅ፣ የኢትዮጵያ እና የሱዳን ህዝቦች ህይወት እና ልማት ምንጭ የሆነ ሀብት መሆኑን በመገንዘብ ሶስቱ አገራት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ለተዘጋጁት ቀጣይ መርህዎች ይሰራሉ። በዚህ የስምምነቱ የመግቢያ ክፍል ላይ ቀደም ሲል ግብፅ የናይል ወንዝ ለግብፃውያን የህይወት ጉዳይ ለኢትዮጵያውያን ግን የቅንጦት ያህል ለመልማት ብቻ የሚፈልጉት አደርጋ የያዘችውን አቋም በመቀልበስ ናይል ለሶስቱም አገራት ዜጎች ህይወት እና ልማት መሰረት መሆኑን በእኩል እውቅና የሰጠ ነው። 1. የትብብር መርህ – በጋራ መግባባት ላይ የተመሰረተ ትብብር፣ የጋራ ፍላጎት፣ መልካም አሳቢነት፣ ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ እና የአለም አቀፋዊ ህጎች መርህዎችን የተከተለ – የታችኛውም ሆነ የላይኛው የተፋሰሱ ሀገራት […]

Minilik Salsawi ትላንትና ከምሽቱ 2 ሰአት ላይ በኦሮሚያ ክልል አምቦ አከባቢ አንድ ከፍተኛ የወያኔ ወታደራዊ ባለስልጣን መገደሉ ታወቀ::አምቦ በከፍተኛ የጸጥታ ቁጥጥር ስር መውደቋ ተረጋግጧል::በአከባቢው የመብራት እና የስልክ አገልጎት ተቋርጦ ያደረ ሲሆን ይህንን የአከባቢው ነዋሪዎች ለሰይፈ ነበልባል ራዲዮ ጣቢያ ጋዜጠኛ እዮብ ባይሳ በሰጡት ቃለመጠይቅ አረጋግጠዋል::

በቀበሌ 2 በተባለ አከባቢ ሲያልፍ የነበረውንየወያኔ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን የገደለው ማንነቱ ያልታወቀ ሲሆን አምቦ በከፍተኛ የደህንነት ቁጥጥር ስር ነች ያሉት ነዋሪዎቹ በጊዜው ጉዳዩን ያልተረዱና ከፍተኛ መደናገጥ እንደደረሰባቸው የተናገሩ ሲሆን ፖሊሶች እና ማንነታቸው የማይታወቁ የጸጥታ ሃይሎች ነዋሪዎችን እያስቆሙ እና እየፈተሹ እንደነበር ታውቋል::

ከአስረ አንድ ወራት በፊት ወያኔ የነደፈውን እና ገበሬዎችን የሚያፈናቅለውን የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም ከ27 00 በላይ የአምቦ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ ወተው የነበረ መሆኑ ሲታወስ የሕወሓት አግአዚ ሰራዊት ከ30 በላይ ያልታጠቁ ተማሪዎችን እና ነዋሪዎችን የገደለ እና የቤተሰባቸውን ደህንነት ለማረጋገጥ በቦታው የነበሩ ዜጎች ሳይቀር ለሞት እና ለቁስለት መዳረጋቸው የታወቀ ሲሆን የዘጠኝ አመት ሕጻን ታዳጊ ሳይቀር በሕወሓቶች መገደሉ ይታወሳል : ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

http://ayyaantuu.com/horn-of-africa-new … mbo-today/

Image

ነብሱን ይማረውና ነውጠኛው ቅንጅት በ1997ዓ.ም የማይናቅ የህዝብ ድምጽና ድጋፍ ያገኘው ከኢህአዴግ የተሻለ ብቃት ስለነበረው ወይም ያቀረበው የፖሊሲ አማራጭ ሳቢ ስለነበረ እንዳልሆነ ሁላችንም እናውቀዋለን፡፡ ወይም የህዝባችን ኑሮ ሊቀይር የሚችል የመነጠቀ ሐሳብ በማቅረብ አልነበረም፡፡ ጅብ በቀደደው ውሻ ይገባል እንደሚባለው የኢህአዴግ ንዝህላልነትና ቸልነትነት እንጂ! ይህን ያልኩት ያለምክንያት አይደለም፡፡ ኢህአዴግ ከቅንጅት ቡድን ጋር ለክርክር ሲቀርብ ማሰብ እና ማድረግ የነበረበት ብዙ ስትራተጂዎች ነበሩ፡፡ እንደምናስታውሰው ቅንጅቶች በነበረባቸው የብልጣ ብልጥነት (ተራ የአራዳነት) ስብእና በከፍተኛና በሚያስገርም ጥበብ የኢሀአዴግን ደካማ ጎን ተጠቅመውበታል፡፡ የኢህአዴግ ቸልተኝነት፣ በክርክር ታክቲክ በልጦ አለመገኘት እንዲሁም እዚህም እዛም ይታዩ የነበሩ የመልካም አስተዳደር እጦት ፣ የአፈጻጸም ግድፈቶች እና የልማት እጥረቶችን በሚሊዮን ግዜ በማጋነን ፣ ልብ የሚነኩ ቃላቶች በመደርደር የተወሰነ ህብረተሰብን በማሳመን ረገድ ቅንጅቶች ከፍተኛ ብልጫ አሳይተዋል፡፡ በኔ ግምት ይህን ሊያደርጉ የቻሉበት ዋናው ምክንያት 1ኛ የኢህአዴግ ጠንከር ላለ ፖለቲካዊ ክርክር በቂ ዝግጅት አለማድረግ እና የሰራውን ስራ በሚማርክ ቃለት እና በሚመጥን መልኩ መግለጽ አለመቻሉም ጭምር ነው፡፡ 2ኛ ደግሞ መቶ በመቶ በሚያስብል መልኩ አጀንዳው በኢህአዴግ የፖለቲካ መስመር ፣ ርእዮት ዓለምና ኢህአዴግ በሚመራው የመንግስት የፖሊሲ አፈጻጸም ዙርያ መሆኑ ነው፡፡ ታድያ ብልጣ ብልጦች የቅንጅት ተከራካሪዎች እነሱ ገምጋሚዎች ኢህአዴግዬ ደግሞ ተገምጋሚ ሆና መቅረብዋ ምን ያህል ለነሱ አመቺ ሜዳ እንደነበረ ማንም ሰው ሊስተው አይችልም፡፡ ቅንጅቶች ይህን ክፍተት በመጠቀም ኢህአዴግ የሰራውንና ያልሰራውን ስራ አፈር ድሜ አበሉት፡፡ ኢህአዴግ በትምህረት ፣ በልማት ፣ በጤና ፣ በድህነት ቅነሳ […]

azeb mesfinመውደቂያው የደረሰው ወያኔ እርስ በርሱ መበላላት ጀምሯል:ትግላችንን አጠናክረን መቀጠል ያለብን ወሳኝ ወቅት ላይ ነን:: የደህንነት ሹሙ ጌታቸው ማለት እንደ ወይዘሮ አዜብ አነጋገር “…ሰታዊ መሲሉ ክምተመን ዝናከስ..” እንደሆነ ሲታወቅ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወይዘሮ አዜብ በቤተሰቦቻቸው ስም ያቋቋሙት ድርጅት እና ያፈሩት ሃብት እና ንብረት ላይ ክትትል እንዲደረግ አቶ ጌታቸው አሰፋ ቡድናቸውን ማዘዛቻው ወይዘሮዋ በደህንነት ሹሙ ጥርስ ውስጥ ዳግም መታኘክ መጀመራቸው ታውቋል::ወዳጆቻቸውን ተገን በማድረግ በቤተሰቦቻቸው ስም የሚገቡ ከባድ እና ቀላል መሳሪያዎች እንዲሁም የተለያዩ ቁሳቁሶች ቀረጥ ስለማይከፈልባችው ጥያቄ በአዜብ መስፍን ላይ ቢያስነሳም ወይዘሮዋ ከተጠየቅን አብረን ነው መጠየቅ ያለብን ሲሉ ከዚህ ቀደም መልስ መስጠታቸው እና ከዘረፋ ጋር ጋር የተያያዘ ጥቄዎች ሲነሳባቸው በጄኔራሎች ካኪ ስር መደበቅ ተግባራቸው መሆኑ ለደህንነት ፈላጭ ቆራጮ እንዳልተዋጠላቸው ታውቋል::

ከዚህ ቀደም በቤተመንግስቱ የውስጥ ሽኩቻ ውስጥ ቂም በቀል እንዳለባቸው የሚነግርላቸው የደህንነቱ ሹም አቶ ጌታቸው ወይዘሮ አዜብን አጥምዶ የሰው መሳቂያ ለማድረግ ከማሴር አልተቆጠቡን ሲሉ የወይዘሮዋ የቅርብ ሰዎች በምሬት ይናገረሉ:: ወዳጅ መሳይ ተናዳፊ እባብ ሰታዊ መሲሉ ክምተመን ዝናከስ ብላ አዜብ የምትጠራው ጌታቸው በዘመዶቿ ስም ያፈራችውን ንብረት የመውረስ እና ሸጦ ገንዘቡን በሌላው እንደለመደው ከሃገር የማሻገር እቅድ እንደያዘ የቅርብ ወዳጆቿ አክለው ገልጸዋል::በደህንነት ሰዉየውና በሴትየዋ መካከል ያለውን ቅራኔ ፈትቶ ጉዳዩን ለማረጋጋት አቶ በረከት ስምኦን እና ጄኔራል ሳሞራ ጥረት ላይ መሆናቸው ታውቋል::

በውጪና በውስጥ ስልጣኑን ለህዝብ እንዲያስረክብ ትልቅ ጫና የበዛበት ወያኔ ከሃገር እና ህዝብ ሃብት በተጨማሪ እርስ በርሱ መበላላት እና መዘራረፍ የጀመረ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ትግላችንን አጠናክረን በመቀጠል ይህንን የበሰበሰ ዘራፊ ስር አት ለማስወገድ በጋራ እና በአንድነት በመታገል የዜግነት ሃላፊነታችንን መወጣት አለብን::