አንድነት ፓርቲ እሁድ ጥር 24 በደሴ ከተማ ህዝባዊ ሰልፍ ያካሂዳል

UDJ protest rally in Dessie, Ethiopia
አንድነት ፓርቲ እሁድ ጥር 24 ደሴ የሚያካሄደው ሰልፍ ከከተማው አስተዳዳር እውቅና የተሰጠ ሲሆን ሰልፉ በደሴ አራዳ አከባቢ ከሚገኘው የአንድነት ቢሮ ተነስቶ መጨረሻ ሆጤ አደባባይ ነው የሚያበቃው። ሰልፉ ከ2:00 እስከ 7:00 ሰዓት የሚቆይ ሲሆን እንደተለመደው የደሴና የአከባቢዋ ህዝብ በነቂስ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህ በተጨማሪ አንድነት በቀጣይ እሁድ በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በደብረታቦር እና በሌሎች የክልል ከተሞች ላይ ሰልፍ ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ ነው የሚገኘው።