የአቶ መላኩ ጉዳይ ለሕገመንግሥት ጉባዔ ተመራ
በግንቦት ሰባት ጉዳይ የተከሰሱትም ጉዳይ ችሎት ቀረበ።
በግንቦት ሰባት ጉዳይ የተከሰሱትም ጉዳይ ችሎት ቀረበ።
News, Ethiopians in America, Americana, Democracy and Women and Family
ወደብ ኣልባዋ ኢትዮጵያ ለወጪ እና ገቢ ሸቀጧ ከሞላ ጎደል የምትጠቀመው በጂቡቲ ወደብ እንደሆነ ይታወቃል። ከዚሁ የተነሳ በጂቡቲ ወደቦች ከሚስተናገዱት ገቢና ወጪ ምርቶች ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውም የኢትዮጵያ ሸቀጦች እንደሆኑ ይገመታል።
የአየር ንብረት መለዋወጥ ዓለምን እያሰጋ ያለ ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል። በከባቢ ሙቀት መጠን መጨመር ምክንያት ፤ የጎርፍ፤ የአዉሎ ነፋስ፤ የባህር ላይ ማዕበል አደጋዎች፤ በዓለማችን በተለያዩ ቦታዎች መከሰታቸዉ ነባራዊ ሁኔታ ነዉ። እነዚህን አደጋዎች ለመከላከል፤ እንዲሁም
የሥልጣኔ በር በምትባለው የአክሱም ከተማ የሚገኙት ከአንድ ውቅር ድንጊያ የተቀረጹት ሐውልቶችዋ ብቻ አይደሉም የቱሪስት መስሕብ የሆኑት።
ውዝግብ ከሚታይባቸው አካባቢዎች በሚወጣ የአልማዝ ማዕድን ንግድ አንፃር የተጀመረውን ትግል የማጠናከር ዓላማ የያዘው በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ « ኬ ፒ ሲ ኤስ » በመባል የሚታወቀው « የኪምበርሊ ፕሮሰስ ሰርቲፊኬሽን ስኪም »
የስዑድ አረቢያ መንግስት ያለ ሕጋዊ ፈቃድ በግዛቱ ይኖሩ የነበሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዉጭ ሀገር ዜጎች ፈቃዳቸዉን እንዲያስተካክሉ የሰጠዉ የምህረት ጊዜ ካለቀ በኋላ ባጠናከረችዉ አሰሳ በሺዎች የሚቆጠሩትን ወደየመጡበት መመለሱን ተያይዛዋለች።
የዕለቱ ዜና
ዐረቢያ፥ ረቢያ፥ የቄዳር ግፊያና ግፍ።
ኅዳር ፱ ቀን ዓ. ም.
ከእስልምና እምነት መምጣት በፊት ዐረቦች የሚኖሩት መካ፣ ያትሪብ፣ መዲና ወዘተ ተብለው ይጠሩ
በነበሩ ሠፈሮች አካባቢ ነበር። ዐረቦች የአስተዳደር ሥርዓት ፣ የህግ ሥርዓት ወይም የእደ ጥበብ
ስምሪት አልነበራቸውም። መንግሥትና መንግሥታዊ አስተዳደር የሚባል ነገርም አያውቁም ነበር።1
ቁሬሺ፣ ባኑ ሃሺም፣ ባኑ ኡማያ ወዘተ በሚባሉ ጎሳዎች ተለያይተው ግን ይጣሉ ነበር።2 ጣዖት
አምላኪዎችም ነበሩ። ካባ የተባለ ድንጋይም ያመልኩ ነበር። እስከ አራት መቶ ዓ.ም. አካባቢ ዐረቦች
ለሚናገሩት ቋንቋ መፃፊያ ፊደል አልነበራቸውም። ከእስልምና መምጣት አስቀድሞ በንግግር ግጥም
መፎካከር የዐረቦች ባህል ነበር።3 እጅግ በጣም ግጥም የሚገጥመውን ሰው መጅኑን እያሉ ይጠሩት ነበር። ዐረቦች
ከእስልምና በፊት የነበረውን ዘመን ጃሂሊያ ወይም የድንቁርና ዘመን ብለው ይጠሩታል።
በዚህ ጊዜ ነበረ አንድ ሙሀመድ የሚባል ዐረብ መካ አጠገብ በሚገኜው የሂራ ኮረብታ ላይ ሳለሁ ጅብሪል ነገረኝ
ብሎ አዲስ እምነት በአቅራቢያው ላሉ ሰዎችና ለዘመዶቹ የሰበከው። በልዩ ልዩ የምዕራባዊ ትረካዎች እንደሚነገረው
ሙሀመድ በሂራ ኮረብታ ላይ ጅብሪል ነገረኝ ካለበት ጊዜ በፊት እሱ በሚኖርበት አካባቢ ክርስትናን ለማስፋፋት
ክርስቲያኖች ብቅ ይሉ እንደነበረ ይነገራል። ከነዚህም ውስጥ ዋናዎቹ ኢትዮጵያውያን ነበሩ። ከኢትዮጵያውያንም
መካከል የሂመራ (የየመን) ንጉሥ አብርሃ ዐረቦች ወደ ሰንዓ መጥተው በሰንዓ የተገነባውን ትልቁን የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በግቢው ተደብቀው በመጸዳዳት ባረከሱ ጊዜ ዐረቦቹን ለመቅጣትና የመካን የካባ
ጣዖት ለማፍረስ ሥንቅ በዝሆኖች ጭኖ ያደረገው ዘመቻ ይታወሳል።4 ሙሀመድ ይዞት ለተነሳው እምነት መሠረተ
ሃሳቡን ያገኘው ክርስትናን ለማስፋፋት እሱ ወደሚኖርበት አካባቢ ከሄዱ ኢትዮጵያውያን የወንጌል አስተማሪዎች
መሆኑን በእስልምና እምነት በተለይም በቁርአን ውስጥ ያሉ ጭብጦች ያመለክታሉ።
የእስልምና እምነት ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ “ኢሳ” የሚባል ስም ነው የተሰጠው። በሌሎች አገሮች የነበሩ
ወንጌላውያን ኢየሱስ ክርስቶስን፥ “የሽዋ” ወይም “ሄሱስ” ወይም “ጀሽዋ” ወይም “ጂሰስ” ወይም “አየሱስ” እያሉ
ነበር የሚጠሩት። በእስልምና ውስጥ ላለው “ኢሳ” ለሚለው ቃል በጣም የሚቀርበው የግዕዙ “ኢየሱስ” ሲሆን
ቀጥሎም የግሪኩ “አየሱስ” ነው። ሙሀመድ ቃሉን ከግዕዙ ወይም ከግሪኩ መውሰዱን ለመለየት ቀላሉ ማነጻጸሪያ
ሙሀመድ “ማርያም” የሚለውን ቃል ከየት እንዳገኜው መለየት ነው። በእስልምና “ማርያም” የሚለው ቃል ድንግል
ማርያምን ለመጥራት የሚጠቀሙበት ሲሆን ቃሉ በግሪክ “ማሪያ” የሚል ሲሆን በግዕዝ ደግሞ “ማርያም” ነው።
ለድምዳሜ በቂ ባይሆኑም ከዚህ አጠራር በቀላሉ ሙሀመድ ቃሉን ከግዕዝ ሰዎች እንዳገኘው መንገዱን ያሳያል።
እብራይስጥና ግዕዝ ተቀራራቢ በመሆናቸው ምክንያት አጋጣሚውን በመጥለፍ አንዳንድ ታሪክን ለመሠሪ ዓላማ
ለመጠቀም የተነሱ ምዕራባውያን እና አይሁድ ነን ባዮች ሙሀመድ የእስልምና እምነትን መሠረተ ሃሳብ ያገኘው
ከአይሁዶች ነው ለማለት ይቃጣቸዋል። ነገር ግን ሙሀመድ ሃሳቡን ከአይሁዶች እንዳላገኘው ብዙ ማስረጃወችና
አመልካቾች አሉ። በመጀመሪያ አይሁድ በኢየሱስ ክርስቶስ አያምኑም። ስሙንም አይጠሩም። እንኳን አምላክ ነቢይ
ነውም አይሉም። ቅድስት ድንግል ማርያምንም በእምነታቸው አያውቋትም። በተጨማሪ “ኤልያስ” የሚለውን
መጠሪያ እስላሞች የሚጠሩት እንደ ግዕዙ “ኤልያስ” ብለው እንጂ እንደ እብራይስጡ “ኤልያሁ” ብለው
አይደለም። በተለይም ደግሞ የእስላሞች ቁርአን መጠሪያው “መጽሐፍ” ተብሎ ነው። “መጽሐፍ” የዐረብኛ ቃል
አይደለም ከግዕዝ ውጭ በሌላ ቋንቋ ውስጥም አይገኝም። እስልምና ይህን ቃል የወሰደው ከግዕዝ ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ አዲሱን እምነቱን እንዳያስፋፋ በመካና በመዲና ተቃውሞ ሲያጋጥመውና በዳሩል ናድዋ
የተሰበሰቡት የቁሬሺ ጎሳ ባላንጣዎቹ ተከታዮቹን ሊገድሉ ሲያሳድዷቸው ፥ ሙሀመድ ለተከታዮቹ፣ “ፍትህን
ሳያጓድል የሚያስተዳድር ደግ ንጉሥ በእውነት ምድር በሐበሻ አገር ይገኛልና ወደ እርሱ ሂዱ። ያስጠጋችኋል።”5
አላቸው። ተከታዮቹም ወደ አክሱም ተሰደዱ። ንጉሠ ነገሥቱም ተቀብለው አስትናገዷቸው። እዚህ ላይ ትኩረት
የሚያስፈልገው “የሐበሻው” ንጉሥ ደግ መሆናቸውን ማን ነገረው? ፍትሕን ሳያጓድሉ የሚፈርዱ መሆናቸውንስ
እንዴት አወቀ? የሚለው ጥያቄ ነው። ከአይሁድ ወይም ከግሪክ ወይም ከፋርስ ወደ ዐረብ አገር የሚመጡ ሰዎች ስለ
“የሐበሻ” ንጉሥ ደግነት ሊነግሩት አይችሉም። ስለ ኢትዮጵያ ንጉሥ ደግነት ለሙሀመድ ሊነግሩ የሚችሉት
ከኢትዮጵያ ወደ ዐረቦች ሠፈር የሄዱ ኢትዮጵያዊ የክርስትና ተከታዮች ወይም የወንጌል መምህራን ናቸው።
እንግዲህ እነዚህ መረጃዎች የሚያሳዩት ሙሀመድ እስልምናን ለወገኖቹ ለመስበክ መነሻ የሚሆነውን ትምህርት
ያገኘው ከኢትዮጵያውያን መሆኑን ነው።
2
የሙሀመድ ተከታዮች አክሱም እንደደረሱ መልካም መስተንግዶ እንደተደረገላቸው የዐረብ ተራኪዎች
እራሳቸው ዘወትር ይመሰክራሉ። በተለይም ደግሞ ቁሬሺ የሚባሉት የሙሀመድ ተቃዋሚዎች አክሱም ድረስ
ለንጉሠ ነገሥቱ እጅ መንሻ ይዘው በመምጣት በሽሽት የመጡት የሙሀመድ ተከታዮች ወንጀለኞች ናቸውና
ስጡን፣ ወደ ዐረብ አገር መልሰን እንውሰዳቸው ብለው ሲጠይቋቸው ንጉሠ ነገሥቱ የሁለቱንም ወገን ቃል ካዳመጡ
በኋላ ስደተኞቹን አሳልፌ አልሰጥም ማለታቸው እስካሁን ይነገራል። እነዚህ የሙሀመድ ተከታዮች የሆኑ ስደተኞች
ወደ ዐረቦች አገር ቢመለሱ አደጋ ላይ እንደሚወድቁ ያዩት ነጉሠ ነገሥቱ ስደተኞቹ በሂመራ (የመን) እንዲሠፍሩና
እንዲኖሩ ፈቀዱላቸው። አሁንም እዚህ ላይ ከላይ የተጠቀሱት ነዳጅ ፈላጊ ሃሰተኛ ምዕራባዊ ተራኪዎችና አይሁድ
ነን ባዮች ከእስልምና በፊት የመንን ፋርሶች አጥቅተው ይዘዋት ነበር የሚል ሃሰት ይተርካሉ። ከነሱ የሃሰት ትረካ ሌላ
እነሱ ለሚሉት ነገር ጭብጥ ማስረጃ የለም። የመን የኢትዮጵያውያን ምድር እንደነበረችና በውስጧም
ከኢትዮጵያውያን በቀር ዐረብ የሚባል ጎሳ እንዳልነበረባት፣ ዐረብኛ ቋንቋም እንዳልትነገረባት፤ ይልቁንስ የሂመራ
ሰዎች የሚናገሩት ቋንቋ፣ የሚጽፉትም ጽሁፍ ግዕዝ እንደነበረ፣ ባህላቸውም “የሐበሻ” እንደነበረ የሚያረጋግጡ
በጣም በርካታ ማስረጃዎች አሉ። የሙሀመድ ተከታዮች በኢትዮጵያ ከተሰደዱ በኋላ ጊዜው ሲረጋጋ አንዳንዶቹ
እየተመለሱ እስልምናን አስፋፉ። ከሞት አፋፍ ላይ ደርሶ የነበረው እስልምና በኢትዮጵያው ንጉሥ ደግነት ምክንያት
እንደገና አንሰራራ።
እንግዲህ ይህን የመሰለ መስተንግዶ የተደረገላቸው ዐረቦች ግን እስልምናቸውን ሲያስፋፉም ሆነ ሲገድሉ፣ በመሬት
ንጥቂያም ላይ ሲሰማሩ ርኅራኄ ያደረገችላቸውን ኢትዮጵያ በርኅራኄ ዐይን አይተዋት አያውቁም። ብዙ ዐረቦች
“ኢትዮጵያ ስላስጠጋቻችሁ እሷን አትንኩ” ብሎ ሙሀመድ ተናግሯል ሲሉ ይደመጣሉ። ይሁንና ከእስልምና በኋላ
ዐረቦች ኢትዮጵያን ሳይነኩ የሰነበቱበት ዘመን የለም። ከእስልምና ማንሰራራት በኋላ ኢትዮጵያ በእስልምና
የደረሰባትን ውድቀት ሲመለከቱ ንጉሠ ነገሥቱ ለነዛ ለተሰደዱ ዐረቦች ያደረጉላቸው መስተንግዶ ከደግነትም አልፎ
የየዋህነት እንደነበር አዙሮ ለሚያይ ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል። ንጉሠ ነገሥቱ እጃቸውን ዘርግተው ዐረቦቹን
መቀበላቸው ለኢትዮጵያ ተናዳፊ እባብን እጅ ዘርግቶ እንደመቀበል ነው የሆነባት።
የመንን ወሰዱ። ኢትዮጵያውያንን አረዱ። የቀሩትንም መንገድ ላይ ጣሏቸው።
ከተደረገላቸው ከዚህ ሁሉ ቸርነት በኋላ ዐረቦች እስላምናን
ለማስፋፋትና የሌሎችን መሬቶች ለመንጠቅ ሲሰማሩ የመጀመሪያ ሰለባ
ያደረጉት የኢትዮጵያን አውራጃ ሂመራን (የመንን) መውረርና የራሳቸው
ማድረግ ነበር። ዐረቦች በሂመራ ኢትዮጵያውያን ላይ የሠሩት ግፍ
ምዕራባውያን አፍሪካውያንን በባርነት ቀንበር ከገዙበት ግፍ ቢበልጥ
እንጂ አያንስም። ዓረቦች ሂመራን (የመንን) ሲወሩ መጀመሪያ በሰንዓ
የሚገኘውን እጅግ የተዋበውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ህንፃ
ቤተክርስቲያን ነበር ያፈረሱት። ክርስቲያኖችንም አረዱ። የቀሩትን
ኢትዮጵያውያን አስገድደው አሰለሟቸው። በባርነትም ገዟቸው።
የመንንም አጥለቀለቋት። እጅግ የሚዘገንኑ ግፎችንም በኢትዮጵያውያን ላይ ፈጸሙባቸው። ልጆቻቸው
ታሪካቸውን እንዳያውቁ አደነቆሯቸው። የሚበሉት፣ የሚጠጡትና የሚለብሱትም አሳጧቸው። አክሃዳም
(ጠራጊወች) የሚል ስምም አወጡላቸው። አክሃዳሞች ከሽንት መጥረግና ከጫማ ማጽዳት ውጭ ሌላ ሥራ
አይፈቀድላቸውም፡፤ ልጆቻቸውም አይማሩም። ዐረቦች “እቃህን ውሻ ቢነካው እጠበው፤ አክሃዳም ከነካው ግን
ጣለው”¶ የሚል ፈሊጥ አወጡላቸው። ዐረቦች አክሃዳም እያሉ የሚጠሯቸውን ሥራና ትምህርት ብቻ ሳይሆን
የከለከሏቸው ሰው መሆንን ጭምር ነው።
ከየመን ወረራ በኋላ ዐረቦች እስልምናን በማንገብ የሌሎች ሰዎችን
መሬቶች ለመንጠቅ ወደ ሰሜን አፍሪካ፣ ወደ መካከለኛው
ምስራቅና ወደ ፋርስ ዘመቱ። የተከላከሏቸውን በጎራዴ እያረዱ
ገደሉ፣ የቀሩትን እስላም አደረጓቸው፣ መሬታቸውንም ሁሉ
ወሰዱ። በተለይ ጥቁሮችን በማጥፋት ከሲሶ በላይ የሚሆነውን
የአፍሪካ መልክዓ ምድር በንጥቂያ ወሰዱ። ኢትዮጵያን በዙሪያዋ
ከበቧት። በግድም በውድም ብዙ ኢትዮጵያውያንን አሰለሙ። በዳር ድንበርም በማህል አገርም ያሉ
ኢትዮጵያውያንን ካሰለሙም በኋላ የክርስቲያን መንግሥት ስለሆነ ለመካከለኛው መንግሥት አትገዙ፣
ጎጦቻችሁንም ከመካከለኛው መንግሥት ገንጥሉ የሚሉ ፋትዋዎችን በመደንገግ ሙስሊም የሆኑትን
3
ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ላይ ለጦርነት በማነሳሳት ኢትዮጵያን በአመጽ ለብዙ መቶ ዓመታት አስጨነቁ።
የባህር በሮቿንም ያዙ።
ዐረቦች ቆስጠንጥኒያ ተብሎ የሚጠራውን አገር በንጥቂያ ከወሰዱ በኋላ ኦስማንየ የሚባል የቱርክ የእስልምና
መንግሥት ተቋቁሞ እሱም በመስፋፋትና እስልምናን በማስፋፋት ብዙ የዓለም ክፍሎችን ይቆጣጠር ጀመር።
ኦስማንየ የተባለው የእስልምና ቀንበር ጫኝ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን መሣሪያ
በማስታጠቅ ኢትዮጵያን ለብዙ አመታት በአመጽና በጦርነት አደቀቁ። በተለይም አህመድ ግራኝ በመባል
የሚታወቀውን ሙስሊም በማስታጠቅ ከምሥራቅ ኢትዮጵያ እስከ ሰሜን ኢትዮጵያ ድረስ በጦርነት አመሷት።
አብያተ ከርስቲያናትን አወደሙ። ቅዱሳን መጻሕፍትን አቃጠሉ። ካህናትን እና ምእመናንን አረዱ። የኢትዮጵያ
ንጉሠ ነገሥት የዐረብ ስደተኞችን ካስተናገዱ ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በችግር፣ በጦርነትና በሰላም ማሳጣት
ዐረቦች እንዳመጡት እስልምና ኢትዮጵያን ያዎካት የለም። የዐረቦች እስልምና አዋኪነቱ በማበጣበጥ ብቻ የተገታ
አይደለም። ታሪክንም በመበረዝ ጭምር ነው።
በተለይ ባለፉት ሃምሳ አመታት በዐረባዊው በግብጽ መንግሥትና ካይሮ በሚገኘው የዓለም ሙስሊሞች
እንዲከተሉት የእስልምና መመሪያ ወይም ፋትዋ ማፍለቂያ ማእከል በሆነው በአል አዛር ተቋም አበረታችነት
በኢትዮጵያ የተኪያሄዱት ሁከቶች ኢትዮጵያን ትልቅ አደጋ ላይ የጣሉ ነበሩ። ይህ የዐረቦች የአመጽ ጥንስስ
በኢትዮጵያ ብዙ ደም ካፈሰሰ በኋላ “ኤርትራ” ተብላ የምትጠራውን የኢትዮጵያ አካል ከነነዋሪዎቿ ከኢትዮጵያ
ገንጥሏል። በእስልምና ስም የሚመጣው የዐረቦች የብጥብጥ እርሾ በማሀል አገር፣ በምሥራቅ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ
ኢትዮጵያ፣ በሶማሊያ ወዘተ እስካሁን ድረስ ጥፋቱን እንደቀጠለ ነው።
ዐረቦች እስልምናን ተጠቅመው በሚፈጥሩት ሁከት ምክንያት ኢትዮጵያ በመታመሷና ድህነትም ላይ በመውደቋ
በተለይ ባለፉት አርባ አመታት ውስጥ ብዙ ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ኢትዮጵያን ትተው በመሰደድ በተለያዩ
የዓለም አገሮች ተበታትነዋል። ከነዚህም ውስጥ ጥቂቶቹ ወደ ዐረቦች አገር ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ ተሰድደው በዛ እስከ
አሁን ይኖራሉ። ሆኖም ግን ከዚህ ቀደም በታህሳስ ወር ½ ዓ.ም. ሰላሳ አምስት የሚሆኑ የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምእመናን የክርስቶስን ልደት በቤታቸው ተሰብስበው ስላከበሩ የሳዑዲ ዐረቢያ መንግሥት
እነዚህን ክርስቲያኖች በእሥራትና በድብደባ ካንገላታቸው በኋላ ክሳዑዲ ዐረቢያ አባሯቸዋል።6 ዐረቦች
የመጀመሪያው ሂጅራ እያሉ በሚያስታውሱት ስደታቸው ከዐረብ አገር ተሰድደው ወደ ኢትዮጵያ መጥተው
ኢትዮጵያውያን ላደረጉላቸው አቀባበል፣ የተሰደዱትንም ችግር እንዳያገኛቸው በኢትዮጵያ እንዲኖሩ መልካም
መኖሪያ ለሰጧቸው ኢትዮጵያውያን የከፈሉት ውለታ እነሆ ኢትዮጵያውያን በዐረቢያ በተሰደዱ ጊዜ ዱላ፣
እሥራትና ካገር ማባረር ሆነ። ዛሬም እንደትናንትናው ዐረቦች
ኢትዮጵያውያንን የማጥቃትና የማዋረድ ሥራቸውን
ቀጥለውበታል። በተለይ ሰሞኑን በሳዑዲ ዐረቢያ
ኢትዮጵያውያንን እያሳደዱ በመያዝ እየደበደቡ አጉረዋቸዋል።
አንዳንዶችንም ገድለዋቸዋል። ኢትዮጵያውያን ሴቶችን
ከቤታቸው እያወጡ አስራ አምስት እና ሃያ እየሆኑ ሰብአዊነት
በሌለው ሰይጣናዊ ሁኔታ ደፍረዋቸዋል። ከቤታቸውም
ከተሰደዱበትም ቦታ እያወጡ ጥለዋቸዋል። የርኅራኄ መስተንግዶ
የተደረገላት ቄዳር ግፍን መለሰች። በቄዳር ድንኳኖች ውስጥ
ያላችሁት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኢትዮጵያውያን
ወንድሞቻችሁንና እህቶቻችሁን ተመልከቱ። ሰላምን ከሚጠሉ ጋር ነፍስ ብዙ ጌዜ ኖረች። ኢትዮጵያ ማረፊያ ሰጥታ
ሰላምን ለቄዳር ልጆች ሰጠች፣ የቄዳር ልጆች ግን ስላምን ነሷት። መኖርያቸው ለራቀ፣ በቄዳር ድንኳኖች ላደሩ
ወዮ፥ እግዚአብሔር ተናግሯልና እንደ ምንደኛ ዓመት በአንድ ዓመት ውስጥ የቄዳር ክብር ሁሉ ይጠፋልና።
እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
1 Muller, Herbert J.: The Loom of History, 1958
2 Grunebaum, G. E.: Classical Islam – A History 600-1258 – 1970
3 Margoliouth, D.S.: Mohammed and the Rise of Islam, 1931
4 Discover True Islam: free-minds.org
5 Safieddine, Shahnaze: Migration to Abyssinia & Wikipedia, the free encyclopedia
6 Nazret.com: Saudi Arabia Deports 35 Ethiopian Christians for Praying, August 4, 2012
ሳውዲ አረቢያ በተለይም በመንፉሃ ሪያድ የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ መረጃዎችን ስንለዋዎጥ ባጅተናል ። አሰቃቂውን የወገን ጉዳት አብረን አውግዘን ፣ ወገኖቻችን ደራሽ ያገኙ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ በመላ አለም ያሰማነው ድምጽ ፍሬ አፍርቷል ! ደስ ሲል … በሁከቱ የተፈጠረውን ችግር ፣ የፈሰሰውን እንባና ደም የአይን ምስክሮችን በአካል ላነጋገረና ህመሙን ሲታመም ለከረመ የእኔ ቢጤ ዛሬ የተገፊው ወገን […]
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
እኛን በታሪክ አስቦት የምንኖረውን የኢትዮጵያ ትውልዶች ሲያኮራን የኖረው በአያት ቅድማያቶቻችን ተጋድሎ በነጻነት መኖራችን ነው። እንዲህ ሆነ። እዚህ ዳላስ ለብዙ ጊዜ የማውቀው የውጭ ዜጋ በተገናኘንበት ጊዜ ሁሉ የጣሊያንን የሁለተኛው አለም ጦርነት ሳያስታውሰኝ አያልፍም። እናም ሊያስታውሰኝ የሚከጅለው ለትንሽ ከቅኝ ግዛት አመለጣችሁ ይለኛል። እኔም እንደልማዴ በጀሮ ከአባቴ የሰማሁትን ገድል ሳልነግረው አልፌ አላውቅም። እርሱም የበለጠ እንደምበሳጭ ስለሚያውቅ አይ እንግሊዝ […]

በጥቅምት ወር 2006 ዓ.ም አጋማሽ በኤርትራ ጎዳና መታየታቸው የተነገረላቸው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከአደባባይ እና ከኤርትራ ቴሌቪዥን ዕይታ ውጪ መሆናቸው በአስመራ ከተማ ነዋሪዎች ከፍተኛ የሆነ መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል።
የሰንደቅ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደገለፁት “ከዚህ በፊት ፕሬዝደንቱ ከሚሰቃዩበት የጉበት በሽታ ጋር በተያያዘ ለከፍተኛ ሕመም ተዳርገዋል። በአሁን ሰዓት በኳታር ሆስፒታል ሕክምና እየወሰዱ ይገኛሉ” ብለዋል።
በአስመራ ከተማ ውስጥ እየተናፈሰ ያለው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከበሽታቸው አገግመው ሀገር ሊያስተዳድሩ ይችላሉ የሚሉ በአንድ ወገን በሌላ ወገን ያሉት ከዚህ በኋላ ፕሬዝደንቱ ሀገር በሚያስተዳድሩበት ቁመና ውስጥ ሊገኙ አይችሉም የሚሉት ይገኙበታል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግስት እ.ኤ.አ. በግንቦት 10 ቀን 2013 ወደ ኤርትራ የሚጓዙ የአሜሪካ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያርጉ የሚያሳስብና ከተቻለ ወደ ኤርትራ ጉዞ እንዳያደርጉ የሚመክር የማሳሰቢያ መልዕክት በዚሁ ሳምንት በድጋሚ ለዜጎቹ አስተላልፏል።
“የኤርትራና የአሜሪካ ጥምር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ያስራቸዋል። ስለታሰሩ ዜጎች ከአሜሪካ መንግስት ማብራሪያ ሲጠየቅም ምላሽ አይሰጥም። አስመራ የሚገኘውም የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጎቹ መታሰራቸውን ሰምቶ ማብራሪያ ለአስመራ መንግስት ቢያቀርብም ምላሽ አይሠጥም” ሲል መግለጫው ተቃውሞውን አሰምቷል።
በተለይ እ.ኤ.አ. ከ2012 ጀምሮ የኤርትራ መንግስት በግለሰብ ደረጃ ዜጎቹን አውቶማቲክ መሳሪያ በማስታጠቁ በቀላሉ የአሜሪካ ዜጎች ለአደጋ ተጋላጭ ይሆናሉ ከሚል ስጋት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ታጣቂዎች በአስመራ ከተማ ሚሊሽያ በሚል ስለሚታወቁ ማንኛውንም ሰው በፈለጉት ቦታና ሰዓት መፈተሽ ይችላሉ። በዚህም የተነሳ በአስመራ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻና የሃይማኖት ቦታዎች ለመጎብኘት የሚመጡ የአሜሪካ ዜጎች በእነዚህ ታጣቂዎች ላይ ሊደርስባቸው ከሚችለው ስጋት ለመዳን ከአሜሪካ መንግስት ዕውቅና ውጪ እንዳይንቀሳቀሱ መግለጫው አሳስቧል።
በኦክቶበር 3 ቀን 2013 በላምባዱሳ ለተሰውት 350 ኤርትራዊያን ማስታወሻ በተደረገ ስነ-ስርዓት በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር አካባቢ ኤርትራዊያን በመንግስታቸው ላይ ባሰሙት ቅሬታ ከፍተኛ ተቃውሞ መቀስቀሱ የሚታወቅ ነው።፡
የኢሳያስ አፈወርቂ ጤና መሻሻል ካላመጣ በአስመራ ወታደራዊ ባለስልጣናት መካከል የስልጣን ሹኩቻ መነሳቱ አይቀርም ሲሉ የዲፕሎማቲክ ምንጮቻችን ለሰንደቅ ጋዜጣ አስተያየታቸውን ገልፀዋል። አያይዘውም፤ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምም የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት እ.ኤ.አ. 2009 የአስመራ መንግስት በሚከተለው የትርምስ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ መነሻነት በኤርትራ መንግስት ላይ ባስተላለፈው ማዕቀብ የተነሳ እስከ ዛሬ ድረስ የአስመራ መገናኛ ብዙሃን በአሜሪካ መንግስት ላይ ከፍተኛ የስም የማጥፋት ፕሮፖጋንዳ እየፈጸመ መሆኑ ይታወቃል።¾
Written by ኤልያስ, AddisAdmassNews.com
“በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት ሙሉ በሙሉ ተከብሯል” – የጋዜጠኞች ማህበራት
“በኢትዮጵያ ሚዲያ ላይ ለውጥና ማሻሻያ እናደርጋለን” መንግስት
ኢህአዴግ ሌሊት ሌሊት የምረጡኝ ቅስቀሳ እያጧጧፈ ነው!
እንደኔ አላጋጠማችሁ እንደሆነ አላውቅም እንጂ ኢህአዴግ ሌሊት ሌሊት የምርጫ ቅስቀሳ ጀምሯል (ህገ መንግስታዊ መብቱ እኮ ነው!) እኔን የገረመኝ ግን ቅስቀሳው ሳይሆን ቀኑን ትቶ ሌሊትን መምረጡ ነው፡፡ (ቀንማ “ቢዚ” ነው!) ባለፈው ሳምንት ነው፡፡ ሰኞ ወይም ማክሰኞ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ሌሊት ላይ እንቅልፍ እምቢ አለኝና ኢቴቪን ከፍቼ ቁጭ አልኩኝ (ብቸኛ “አጫዋቼ” ነው አላልኳችሁም!) ምናልባት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ወይም 10 ሰዓት ገደማ ይሆናል፡፡ ኢቴቪ የኢህአዴግ የሴቶች ሊግ አባላትን የልማት እንቅስቃሴ የሚያስቃኝ ፕሮግራም ማቅረብ ጀመረ፡፡ (“የሴቶች ሊግ” የተሰኘ አዲስ ፕሮግራም ሳይሆን አይቀርም!) በኋላ ሲገባኝ ግን የልማት ሳይሆን የምረጡኝ ቅስቀሳ ነገር ነው፡፡ እኔ የምለው … በህዝብ ንብረት ቅስቀሳ ይቻላል እንዴ? (ኢህአዴግም እኮ የህዝብ ንብረት ነው!) አንድ ጥያቄ ግን አለኝ፡፡ የ2007 ምርጫ ወደ 2006 ተዛወረ እንዴ? ለቀጣዩ ዓመት ምርጫ ዘንድሮ ቅስቀሳ አይጀምርም ብዬ እኮ ነው! እናላችሁ … በኮብልስቶንና በሌሎች “ደሃ-ተኮር” ስራዎች ላይ የተሰማሩ ሴቶች አስተያየት ሲሰጡ፣ እንደሌላው ጊዜ ስማቸው ወይም የሥራቸው ዓይነት አይደለም ቲቪ ስክሪኑ ላይ የተጠቀሰው፡፡
ለእያንዳንዱ ተናጋሪ “ሊግ አባል” የሚል መግለጫ (Caption) ነው የተሰጠው። (መቼ የተጀመረች ግልፅነት ትሆን?) አንደኛዋ የሊግ አባል፤ ኢህአዴግ ከጓዳ (ማጀት) አውጥቶ ለአደባባይ እንዳበቃት ገለፀች፡፡ እሷም ብትሆን በጥቃቅን ሳትደራጅ በፊት ነው የሊጉ አባል የሆነችው፡፡ (ባለውለታ ናት ማለት ነው!) ቀጠለች-ሴትየዋ፡፡ “ለሴቷ አማራጭ ያለው ፓርቲ ነው” ስትል አውራ ፓርቲውን በደንብ አሞካሸችው (በእሷ ዓይን “ሲያንሰው” እኮ ነው!) ትንሽ ቅር ያለኝ ግን ምን መሰላችሁ? አባል ለመሆን መዘግየቷ ነው። “በ2001 ዓ.ም ነው አባል የሆንኩት” ብላናለች፡፡ (ያን ሁሉ ዓመት የማን አባል ነበረች?) በነገራችሁ ላይ …ከሴቶች ሊግ አባላት ውስጥ 99 በመቶ ያህሉ በሥራ ላይ የተሰማሩ (employed ወይም self employed) ሲሆኑ በቅርቡ አንድም ሥራ አጥ (zero unemployment) የሊግ አባል እንደማትኖር የሊጉ ሊቀመንበር ተናግረዋል፡፡

(ልብ አድርጉ! “አንድም የሊግ አባል” ነው የተባለው!) በነገራችሁ ላይ … ሊጉ የሚመራው “ሰጥቶ መቀበል” (ፈረንጆቹ Give and take ይሉታል) በሚለው መርህ ነው፡፡ በአበሽኛ “እከክልኝ ልከክልህ” የሚባለው መሰለኝ፡፡ እናላችሁ … የሊጉ አባላት በ2002 እና በአካባቢና ማሟያ ምርጫዎች ኢህአዴግን በመምረጥ ብቻ ሳይሆን እንዲመረጥ በመቀስቀስም ለፓርቲያቸው ያላቸውን የማይናወጥ “ታማኝነት” አሳይተዋል ብላለች – የሴቶች ሊግ ሊቀመንበሯ፡፡ (ካላሳዩማ አለቀላቸው!) እኔ የምለው … የሊግ አባል የመሆን ዕድል ላላገኙ የጦቢያ ሴቶች የሥራ ዕድልና ብድር የሚሰጣቸው ማነው? (ጥያቄ እኮ ነው!) እንደው ለጨዋታ ያህል ነው እንጂ… በኢቴቪ በውድቅት ሌሊት የተላለፈው የሴቶች ሊግ የምርጫ ቅስቀሳ ምንም ክፋት የለውም (አሳቻ ሰዓት ከመቅረቡ በቀር!) የሊጉን ቅስቀሳ ኮምኩሜ ልተኛ ስል ግን አንድ ሃሳብ መጣልኝ። “Drink Responsibly” ወይም “በሃላፊነት ስሜት ተጐንጩ” የሚለውን የቢራ ማስታወቂያ ታውቁታላችሁ አይደል? ኢህአዴግን ጨምሮ ሁሉም የጦቢያ ፓርቲዎች ራሳቸውን ሲያስተዋውቁና ሲቀሰቅሱ “Support Responsibly” ወይም “በሃላፊነት ስሜት ይደግፉ!” የሚል ማስታወቂያ ቢያክሉበት አልኩ-ለራሴ፡፡
(እንዴ … የፖለቲካ የአልኮል መጠን እኮ ከቢራ የአልኮል መጠን በብዙ እጅ ይልቃል፡፡) እኔ የምለው … ባለፈው ሳምንት በአፍሪካ ህብረት የተካሄደውን የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች ፎረም እንዴት አያችሁት? የአፍሪካ ነገር ሁሌ ችግሯን ሁሉ በፈረንጆቹ ላይ ማላከኳ አናደደኝ እንጂ ጋዜጠኞቹ መወያየታቸውና መወቃቀሳቸው የሚበረታታ ነው። አንድ ቀን ከምዕራባውያን ላይ ወርደው ራሳቸውን መቻላቸው አይቀርማ! የእኔን ትኩረት የበለጠ የሳበው ግን ጉባኤው እንዳይመስላችሁ! በፎረሙ መጠናቀቂያ ላይ ሦስት የጦቢያዋ “የጋዜጠኞች ማህበራት” ያወጡት “ድንቅ” የአቋም መግለጫ ነው። (ሦስቱ ማህበራት ለኢትዮጵያ ብቻ ነው ወይስ ለሶማሊያም?) እናላችሁ … የማህበራቱ መግለጫ የጋዜጠኞች ሳይሆን የ“አብዮታዊ መንግስት” ወይም “ድርጅት” ነበር የሚመስለው፡፡ ከአቋም መግለጫቸው መካከል አንደኛው ደግሞ ከኢህአዴግ ቃል በቃል የተኮረጀ ነው (ኮማ ሳይቀር!) ልዩነቱ ምን መሰላችሁ? ኢህአዴግ በተደጋጋሚ “በኢትዮጵያ ውስጥ ከሙያቸው ጋር በተያያዘ የታሰሩ ጋዜጠኞች የሉም” የሚል ምላሽ ሲሰጥ ደንፍቶ አያውቅም። እነሱ ግን ቀላል ቀወጡት! አገር ይያዝልን እኮ ነው ያሉት፡፡ ቦታው ስላልተመቻቸው ነው እንጂ ሽለላና ቀረርቶ ሁሉ ዳድቷቸው ነበር፡፡
(ኢህአዴግ ራሱ እኮ ሳይታዘባቸው አይቀርም!) እኔማ ምነው በገመገመልኝ ብዬ ነበር፡፡ ለካስ የኢህአዴግ አባል አይደሉም (ናቸው እንዴ?) የጋዜጠኞች ማህበራቱ ሁለተኛው የአቋም መግለጫ ደግሞ “በኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት ከየትኛውም የአፍሪካ አገራት የበለጠ ተከብሯል” የሚል ነው፡፡ ይሄኛውም በድንፋታና በጩኸት የታጀበ ነበር፡፡ ይሄን የሰሙ የአፍሪካ ጋዜጠኞችና የሚዲያ መሪዎች አገራቸው እስከሚገቡ እንዴት እንደሚቸኩሉ አልታያችሁም? (ለመሳቅ እኮ ነው!) እንኳን እነሱ ኢህአዴግም ይሄኔ በመግለጫው ፍርስ ብሏል (አይነግረንም እንጂ!) እውነቴን እኮ ነው … መንግስት ራሱ “በአገራችን የፕሬስ ነፃነት ሙሉ በሙሉ ተከብሯል” ብሎ አያውቅም፡፡ (ከየት አመጡት ታዲያ?) በነገራችሁ ላይ … የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች ፎረም መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ … መንግስታቸው፤ በኢትዮጵያ ሚዲያ ላይ ለውጥና ማሻሻያ እንደሚያደርግ ተናገሩ እንጂ “የፕሬስ ነፃነታችን እንከን የለሽ ነው!” ብለው አልተመፃደቁም፡፡ “ዲሞክራሲውም … ነፃ ፕሬሱም … የሰብአዊ መብት አያያዙም ወደፊት ከልማቱ ጋር እየተሻሻለ ይሄዳል” ነው – የኢህአዴግ አቋም፡፡ (“ከጳጳሱ በላይ አማኝ” አሉ!) የጋዜጠኞች ማህበራቱ ጉዳይ በዚሁ ቢያልቅ “ተመስገን” ነበር፡፡ ባለፈው ሳምንት ምሽት ደግሞ “የነፃ ጋዜጠኞች ማህበር” ፕሬዚዳንትና ጋዜጠኛ ሳምሶን ማሞ ይሄንኑ ጉዳይ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያብራሩ ተጋብዘው ነበር – በኢቴቪ፡፡
የሚገርመው ታዲያ የምሽቱ አጀንዳ “በኢትዮጵያ የታሰሩ ጋዜጠኞች አሉ የሉም” ወይም “የፕሬስ ነፃነት ተከብሯል አልተከበረም” የሚለው አልነበረም። የአገር ሉዓላዊነት ማስከበር፣ አንድነትና ነፃነትን ማስጠበቅ ወዘተ … ሆነና አረፈው (የአቋም መግለጫ በማውጣት “አርበኝነት” የለም እኮ!) የኢቴቪ ጋዜጠኛው (ጋባዡ ማለት ነው) ታደሰ ሚዛን፤ ለጋዜጠኞች ማህበሩ ፕሬዚዳንት አስገራሚ ጥያቄ አቀረበ (ሃሳቡን እንጂ ቃል በቃል አይደለም!) “በቀጣይ እንደ CPJ ያሉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ነን ባዮች ‘በኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ታስረዋል፣ የፕሬስ ነፃነት ታፍኗል’ እያሉ የሚያወጡትን መግለጫ እንዴት መከላከል ይቻላል?” ፕሬዚዳንቱም አስገራሚ ምላሽ ሰጠ፡፡ “ፅናትና መስዋዕትነት ይጠይቃል” በማለት፡፡ የምን ፅናት ነው? የምንስ መስዋዕትነት? እውነቱን መናገር እኮ በቂ ነው – እንደ ኢህአዴግ፡፡ (እውነት አንፃራዊ መሆኗ እንዳይረሳ!) ሁለቱን ጋዜጠኞች ወይም የ “ነፃ ጋዜጠኞች” ተወካዮች በኢቴቪ የጋበዘው ጋዜጠኛ፤ አንድ ነገር ግን ሳይሸወድ አልቀረም፡፡ (“አውቆ በድፍረት ሳያውቅ በስህተት” ሊሆን ይችላል!) ምን መሰላችሁ? የጋዜጠኞች ማህበራት ያወጡትን መግለጫ፣ የአገርን አንድነት (ዳር ድንበር) እንደማስከበር ነው የቆጠረው፡፡
(በአቋም መግለጫ “አንድነት” ተከብሮ አያውቅም እኮ!) እናም … ማህበራቱ ወደፊትም ተመሳሳይ መግለጫ በማውጣት የአገሪቱን አንድነት ለማስጠበቅ ይጥሩ እንደሆነ ጠየቀ – ወደ ውይይቱ መጠናቀቂያ ላይ፡፡ (ወይ ፍሬን መበጠስ!) መልሱም “ፍሬን የበጠሰ” ስለሆነ ትቼዋለሁ፡፡ አንድ ጥያቄ አለኝ፡፡ ሦስቱ የጋዜጠኞች ማህበራት ዓላማ ምንድን ነው? (የጋዜጠኞችን መብት ማስከበር እንዳይሉኝ ብቻ!) “ኢህአዴግ ማረኝ” ማለት ይሄኔ ነው፡፡ (“የባሰ አለና አገርህን አትልቀቅ” አሉ!) እናንተ … እኔም ፖለቲካዊ ወጌን በአቋም መግለጫ ልቋጨው ዳድቶኝ ነበር፡፡ (አንድዬ እኮ ነው ያዳነኝ!) በሉ ሰሞኑን በቴክስት የደረሰኝን “ቧልት” ላካፍላችሁና ልሰናበት፡- “ዓለም አቀፍ የቤተሰብ ዕቅድ ጉባኤ ላይ የተሳተፈችና የቡራዩን የስነ ተዋልዶ ጤና ኤክስቴንሽን የጐበኘች አንዲት አሜሪካዊት፣ በተለይ ለኢቴቪ በሰጠችው ቃለ ምልልስ፤ ‘ምነው እኔም ኢትዮጵያ ውስጥ በወለድኩ’ ስትል አድናቆቷን ገለፀች” (ማንም ምንም ቢል የምዕተ ዓመቱ የልማት ግብ እንደሆነ መሳካቱ አይቀርም!!) ድል ለዋልያዎቹ!!
ክፍል አምስት (ወለላዬ ከስዊድን)
ምስጢሩ ወደኛ እየቀረበ ይሆን?
የምስጢሩን መጽሐፍ እያሳጠርኩ በመጻፍ ላይ እያለሁ ምስጢሩን የሚያጠናክር ነገር ገጠመኝ። ከወዳጄ ያሬድ ክንፈ ጋር አልፈን አልፈን ውሃ የምንጎነጭባት ቤት አለች። እንደወትሮው በዛው ቤት ተገኝተናል። አንዲት ወጣት ስዊድናዊት ልታስተናግደን መጣች። ለጓደኛዬ የሞቀ ሰላምታ ሰጠችው። ስትስቅ ጉንጭና ጉንጮቿ ላይ የሚወጡት ጎድጓዳ ምልክቶች ዓይን ይስባሉ።
ግርማ ጌታቸው ካሳ
ኢሕአዴግን እንደ አንድ የሚመለከቱ፣ ሁሉን አባላቶቹን በጅምላ የሚፈርጁ ጥቂቶች አይደሉም። ነገር ግን ኢሕአዴግ ውስጥ የተለያዩ ቡድኖች አሉ። አንዱ የገነባውን አንዱ ያፈርሳል። አንዱ ሲያነሳ አንዱ ይጥላል። አንዱ ሰላማዊ ሰልፍ ሲፈቅድ፣ አንዱ በጎን የዜጎችን ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ይጋፋል። አንዱ የታሰሩ የሕሊና እስረኖች እንዲፈቱ ሲፈልግ፣ ሌላው “እዚያው ቃሊቲ ይበስብሱ” ይላል። አንዱ በጎና ቀና ሕሊና ሲኖረው፣ ሌላው ደግሞ የጠመመና የጫካ አስተሳሰብ ያለው ሆኖ ይገኛል።
አንዱዓለም ተፈራ
ዘግናኙ የስደተኛ ኢትዮጵያዊያን ግፍ በሳዑዲ አረቢያዊያን እጅ፤ ከፊታችን ተደቅኗል። ሁላችን በያለንበት፤ “ለምን? ምን አደረግን? መጨረሻው ምንድን ነው? መቼ ነው ይኼ ሁሉ የሚያበቃው?” እያልን እርስ በርሳችን እየተጠያየቅን ነው። እኛ ወደ የምንፈልገው መንገድ ካልገባን፤ ሌላ ሊይስገባን የሚችል ኃይል የትም የለም። በሳዑዲ አረቢያ የተደረገውን ኢሰብዓዊ ድርጊት፤ ሁላችን ኢትዮጵያዊያን በግል በራሷና በራሱ እንደተደረገ በደል አድርገን ወስደነዋል። ተገቢም ነው።
Ethio-Mihidar Journalists, Hawassa, court
ትናንት እንደ ቀልድ … በያዝነው የፈረንጆች 2013 ዓም በወርሃ መጋቢት አጋማሽ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ” ህጋዊ ሰነድ ያልያዙትን አስወጣለሁ !” ብላ አወጀች ። ቀጠለና አፈሳ አሰሳው ተከተለ! አስፈሪው ያ ክፉ የጭንቅ ቀን በሳውዲው ንጉስ ሌላ የምህረት አዋጅ ተተክቶ ህገ ወጥ የተባሉትን ህጋዊ በሚያደርግ ህግ ተተካና የምህረቱ አዋጅ በያዝነው ህዳር መባቻ እንደሚያልቅ በተጠቆመው አዲስ የምህረት አዋጅ […]
ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በመሠረተባቸው ክስ ሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየቀረቡ ያሉት የኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ አዘጋጆች ጉዳያቸው አዲስ አበባ ላይ እንዲታይ ያቀረቡት ጥያቄ ዛሬም ተቀባይነት አላገኘም።
አዘጋጆቹ ወደፍሬ ነገሩ ገብተው እንዲከራከሩ ብይን የሰጠው የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለኅዳር ሃያ አምስት ቀጠሮ ሰጥቷል።
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡
News, Ask the Doctor, Agriculture and Business
የዓለም ዜና
የሳዉድ ዐረቢያ መንግስት ላለፉትሰባት ወራት ሰጥቶ የቆየዉ የምህረት ቀነ ገደብ ካለፈ ከጥቂት ጊዜ ወዲህ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ትልቅ ችግር ላይ ይገኛሉ። ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ 30,000 የተመዘገቡ ዜጎች አሁን በሳውዲ ማቆያ ሠፈር በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
ከዘንባባ የሚገኘዉ ዘይት በእንግሊዝኛ ፓልም ኦይል የሚሰኘዉ ለምግብነት ከሚዉሉ የዘይት ዓይነቶች አንዱ ነዉ። ለሰዉ ልጅ ጥቅም መዋል የጀመረዉም ከአምስት ሺህ ዓመታት በፊት እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በአብዛኛዉ የመንግስት ስላከናወናቸዉ ፍሪያማ ዉጤቶች ላይ ብቻ ዘገባ ያቀርባል ሲል የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ነቀፈ።
ዛሬ በማዕከላዊ ሶማሊያ በለድዌይን ከተማ ውስጥ በኣንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ ከ10 ሰዎች በላይ ተገድለው በርካቶች መቄሰላቸው ተሰማ።
በመኪና ላሊ የተጠመደ ቦምብ መፈንዳቱን ተከትሎ ታጣቂዎችም ተኩስ ከፍተው ለማምለጥ የሞከሩ ፖሊሶችን ሲገድሉ ማየታቸውን የዓይን እማኞች ተናግሯል።
የፊታችን ዕሁድ ፆመ ነቢያት ይጀመራል።የገና ፆምን ለመፆም ተዘጋጅተዎል?ዘንድሮ ፆም ለነፍስ ብቻ ሣይሆን ለስጋም ጠቃሚ እየሆነ ነውና ሀኪም ቀይ አብርቶ በስጋ ምክንያት ሥጋት ላይ መሆንዎን ሣያረዳዎ በንስሃ አባትዎ ምክር ፆሚ ይሁኑ።
ቢፆሙ ሸንቃጣ ይሆናሉ።ስጋዎ ፈተና ላይ አይወድቅም።መንፈስዎ ይረጋጋል።ባይፆሙ ኪሎዎ ይጨምራል።ከሀኪም ፊት አይርቁም።ቁና ቁና ይተነፍሣሉ።ወጪዎ ይጨምራል።አልጋና ብልግና ሊያዘወትሩ ይችላሉ።
ኪስዎ ከመጀመርያው ፆሚ ከሆነ የኔ ምክር እርስዎን አይመለከትምና ዘና ይበሉ።ፆም ሲፆሙ ሆድዎን ብቻ ማዕቀብ አይጣሉበት። ምላስዎን አደብ አስገዟት።ዓይንዎን ከዳሌና ጭን ላይ ይንቀሉ።ጆሮዎ የአመት ረፍት ያስወጡት።እግርዎ አይንጦልጦል።ያኔ የወጣልዎ ምርጥ ፆሚ ይሆናሉ።አንድ ነገር ረሣሁ።በልብዎ ግርግዳ ያከማቹትን የቂምና የጥላቻ ዶሴ ፈጥነው ይደልዙ።ልብዎ በቂም ኔትወርክ ተጨናንቆ ወደ ፈጣሪዎ የሚያደርጉት ማንኛውም ጥሪ አይሠማምና ውዝፍ ሂሣብዎን ያወራርዱ።ያኔ የገናን ፆም ለመፆም ሚኒማውን ያሟላሉ።
ዕሁድ ጧት ቸርች ሲመጡ ልብስዎ ብቻ ሣይሆን ልብዎም ፀዳ ብሎ ይምጣ።እኔ እንዲህ ብያለሁ ።እርስዎስ??
አክሊለ ሠማያት ዘ መካነ ሠላም
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz

ሜሮን አድማሱ ከኖርዌይ
በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵዊያን በሚኖሩባት ሳውዲ ዐረቢያ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ እያደረገችው ያለችው ኢሰብዓዊ ድርጊት ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ሲሆን፣ ከአንድ ኃይማኖት አለን ከሚል ሀገር የማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ነው። በታሪክ እንደሰማነው የነብዩ መሐመድ ተከታዮች ሲሠደዱ ኢትዮጵያ በጊዜው ተቀብላ መኖሪያና ማምለኪያ ቦታ እንዳልሰጠቻቸው ሁሉ፤ ዛሬ ግን በኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ላይ እያደረሰችባቸው ያለው ስቃይና እንግልት ውለታ በይነቷን ያሳያል።
ግርማ ጌታቸው ካሳ
አይኖቼ በደም ቀሉ። ልቤ ተሰበረ። ከሳውዲ አረቢያ፣ ከባህር ማዶ፣ የወገኖቼ ጩኸትና ሮሮ፣ ከጣራዬ በታች የመነጨ ይመስል፣ በጆሮዬ በቅርበት ያቃጭላል። በርግጥ እንደ አገር፣ እንደ ሕዝብ፣ እንደ ኢትዮጵያዊ መዋረዳችንን አየሁ። በተለይም ደግሞ በአሁኗ ሰዓት፣ እንደ ወገን ምንም ማድረግ ባለመቻሌ ውስጤ ደበነ። የማድርገውን ሳጣ መሬት ተንበረከኩ። አይኖቼን ወደ ላይ አንስቼ፣ እጆቼን ዘረጋሁ።
Medrek’s demo deffered
corruption, court, melaku …
ቦጋለ ዳኜ – ከካሊፎርንያ
ቅኔ፤ ግጥምና የተለያዩ ድርሰቶች ባጠቃላይ ሲጠሩ ‘ሥነ ጽሑፍ’ ይባላሉ። ሥነጽሑፍ የሚለው ሐረግ ጥሬ ትርጉም ‘የጽሑፍ ውበት’ ማለት ነው። ለሥነጽሑፍ ይህ ስያሜ የተሰጠበት አንዱ ምክንያት ድርሰቶች ሲጻፉ በቃል አመራረጥ ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ መሆኑን፤ ሥነ ጽሑፍ መዋብ እንደሚገባው ለመግለጽ ጭምር ይመስለኛል።
የሳውዲ አረብያ መንግስት በቅርቡ “የመኖርያ ፈቃድ የላቸውም፤” ያላቸውን በዚያች አገር የሚኖሩ የውጭ አገር ሠራተኞች ለማስወጣት በያዘው ዘመቻ ከፍተኛ ግፍና በደል የደረሰባቸው ወገኖቻቸው ጉዳይ ነው በቁጣ ግልብጥ ያሉት ሠልፈኞች በዛሬው ዕለት ለቅዋሜ አደባባይ የወጡት።
በብዙ መቶዎች የተቆጠሩት ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን ከዋሽንግተን ዲሲው የሳውዲ ኤምባሲ ደጃፍ ባካሄዱት በዚህ ሠልፍ፥ የሳውዲ መንግስት ‘ከአገሬ ውጡ!’ ያላቸውን የተለያዩ አገር ዜጎች የሰብዓዊ መብት እንዲያከብር፥ የኃይል እርምጃውን እንዲያስቆምና ተጠያቂ ይሆን ዘንድ ከልዩ-ልዩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዛቶች የመጡትን ጨምሮ የተለያዩ የሃይማኖት መሪዎችና የማኅበራት ተጠሪዎች ባሰሙት ጥሪ ጠይቀዋል።
የዘገባውን ዝርዝር ለመስማት የሚቀጥለውን ይጫኑ።
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ትናንት ዕሁድ ፤ ኅብር 8 / 2006 ዓ.ም ሊያደርግ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ወደ ኅዳር 29 / 2006 ዓ.ም ለማዛወር መወሰኑን አስታውቋል፡፡
መድረክ ሰላማዊ ሰልፉን ትናንት የሠረዘው የከተማዋ የሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባዎች ዕውቅና ሰጭ አካል ለመድረክ በፃፈው ደብዳቤ በዕለቱ በከተማይቱ የተለያዩ ዓለምአቀፍ ስብሰባዎች እንደሚካሄዱ ገልፆ ለጥበቃ ይሠማሩ የነበሩ የፀጥታ ኃይሎች ዕጥረት ስላለ የግንባሩን ጥያቄ ማስተናገድ እንደማይችል በማስታወቁ መሆኑን የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡
በመጭ ቀናትም በከተማይቱ ውስጥ ተመሣሣይ ክንውኖች ስለሚደረጉ በዚህ ወቅት እንዲህ ዓይነት ጥያቄዎችን ማስናገድ እንደማይቻልም አስተዳደሩ መግለፁን ሊቀመንበሩ አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ…
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥራ አምስተኛ የወንጀል ችሎት በአቶ መላኩ ፈንታ፣ አቶ ገብረዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ እንዲሁም አንዳንድ ተዋቂ ባለሃብቶች ላይ አቃቤ ሕግ የመሠረተውን ክሥ በመደበኛው የሕግ ሥነ-ሥርዓት መሠረት እንደሚመለከተው ወሰነ።
የአንደኛውን ተከሣሽ የአቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይ መመልከት ይችል እንደሆነ ለመወሰን ግን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ለዝርዝሩ የመለስካቸው አምሃን ዘገባ የያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
News, Sports, African Topics and Health
እአአ ከ 610 ዓ ም ጀምሮ የእስልምና ኃይማኖት መገኛ እና ማስፋፊያ ማዕከል በመሆን ትታወቃለች። በማዕከላዊው ምስራቅ በፋርስ ባህረ ሰላጤ እና በቀይ ባህር መካከል በተንጣለለው የዓረቢያ በረሃ ላይ ጆርዳን ኢራቅ ኩዌት የመን ኦማን ቀጠር እና የተባበሩት ኣረብ ኢማራት በምድር ያዋስኗታል።
እአአ ከ 610 ዓ ም ጀምሮ የእስልምና ኃይማኖት መገኛ እና ማስፋፊያ ማዕከል በመሆን ትታወቃለች። በማዕከላዊው ምስራቅ በፋርስ ባህረ ሰላጤ እና በቀይ ባህር መካከል በተንጣለለው የዓረቢያ በረሃ ላይ ጆርዳን ኢራቅ ኩዌት የመን ኦማን ቀጠር እና የተባበሩት ኣረብ ኢማራት በምድር ያዋስኗታል።
በኢትዮጵያ ለተካሄዱት የሕፃናት ልምሻ ክትባት ዘመቻዎች ከፍተኛ አስተዋፅዎ አድርገዋል በማለት ለቀድሞ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ አለም አቀፍ ሮታሪክ ላብ ሽልማት አበርክቶላቸዋል።
ምንሊክ ሳልሳዊ :- ይህ በአለም ላይ የማይካድ እውነት ነው:: ምንም ከሃገሩ ካለምክንያት አይሰደድም የአንድን ሃገር ድንበርም ጥሶ ካለምክንያት አይዘልቅም:: ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ወደ አረብ አገራት ገብተዋል:: የይልፍ ወረቀት ገዝተው በአየር የወጡትን ጉዳይ ለጊዜው ተወት እናድርገው እና በዛሬው ወቅት ህገወጥ እየተባሉ በአረቦቹ እና በስርኣቱ መሪዎች ስለሚወነጀሉት ኢትዮጵያውያን አጠር ያለ ነገር እናንብብ::
ወደ አረብ አገራት የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን በሁለት ይከፈላሉ እነዚህ ስደተኞች አብዛኛዎቹ በባህር አቋርጠው እና አስቸጋሪ ፈተናዎችን አልፈው በሰላም ወደ ፈለጉበት የደረሱ የሸሹ የተደበቁ እጅግ አሳዛኝ ዜጎች ናቸው:: በሁለት ከፍለን ስናያቸው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስደተኞች ብለን እናስቀምጣቸዋለን :; እነዚህ የሁለት ፈርቅ ስደተኞች በጅቡቲ እና በሱማሌላንድ ወደቦች በጀልባዎች ተጭነው የተረፈ ተርፎ የገባ ገብቶ አሁን ላሉበት ሁኔታ ደርሰዋል::እስኪ ከፍለን እንመልከታቸው::
የፖለቲካ ስደተኞች
እንዚ የፖለቲካ ስደተኞች በብዛት የተሰደዱት ከኦሮሚያ ክልል ሲሆን እነዚህ ኢትዮጵያዊ ስደተኞች በተለያየ ጊዜ የእነግ አባላት ናችሁ የኦነግ ጦር ረዳቶች ናችሁ ኦነግን ትደግፋላችሁ በሚል የተለያዩ ችግሮች እና መከራዎች ሲደርሱባቸው ድብደባ እና እስር ሲፈጸምባቸው ይህንን በመሸሽ እንዲሁም የቤተሰቦቻቸውን እና የራሳቸውን የእርሻ መሬት ሲነጠቁ የስራ እድላቸው በፖለቲካ እምነታቸው ሲጋረድባቸው ስርኣቱ በፈጠረው የፖለቲካ ጫና ቤተሰብ ማስተዳደር ሲሳናቸው ወደ የመን ሳኡድ አረቢያ ደቡብ አፍሪካ እና የተለያዩ አገሮች በምድር ጉዞ ይሰደዳሉ:; እንዲሁም ሴት ልጆች በቤተሰባቸው ላይ ፖለቲካው የፈጠረን ጫና ለማሸነፍ ሲሉ እንዲሁ ይሰደዳል:: እንዚህ የፖለቲካ ስደተኞች ራሳቸውን ለማሸነፍ ሲፍጨረጨሩ ህገወጥ ወይንም ወንጀለኛ አድርጎ ማየት ሃላፊነት የጎደለው አስተሳሰብ ነው::
የኢኮኖሚ ስደተኞች
በሃገሪቱ የተንሰራፋው የዘረኝነት ጁንታ አብዛኛው ህብረተሰብ እንዳይሰራ ግሬጣ ከመሆኑም በላይ የፖለቲካው አናት የንግድ ድርጅቶቹን በማስፋፋት በሃገሪቱ አንጡረ ሃብት እየተጫወታ ዜጎችን ለድህነት አገሪቱንም ለድቀት ዳርጓል::የሃገሪቱ የትምህርት ጥራት ትውልድ እንዳያፈራ ተደርጎ አመድ ከተለወሰ በኋላ የስራ አጥ ቁጥሩ በእጥፍ ጨምሯል:: የምእራባውያኑ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን እድገት ስለማይፈልጉ አምባገነንነትን በማበረታታት የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ይነዛሉ::እንዲሁም እንደ ቻይና የመሳሰሉት አገራት ከቀን ሰራተኛ ጀምሮ በተለያዩ ለውጪ ዜጎች በማይፈቀድ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው የአገሪቱን ወጣት በስራ አጥነት እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርገውታል:: ይህ አይነቱ መንግስት ባለስልጣናት ነጋዴነት ሙሰኝነት የውጪ ዜጎች ካለደረጃቸው ዝቅ ብለው የሚበጠብጡት የስራ እድል አሻሚነት ተደማምሮ በአመት ከ 800.000 በላይ ስራ አጥ ስለሚፈጠር የስደት መንስኤ ሊሆን ችሏል::ወደ አረብ አገራትም የሚሰደዱ ዜጎች የዚህ እና የተያያዥ የኢኮኖሚ ችግሮች ሰለባ ከመሆናቸውም በላይ ይህ ደግሞ የስርኣቱ ለዜጎች የኑሮ እድገት ግዴለሽነት ያመለክታል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ የብሄራዊ እፍረት መንስኤ የሆነው ስርኣት በሚከተለው የፖለቲካ እና የእኮኖሚ ፖሊሲ ምክንያት ዜጎች አገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እና ለሞት ለእስር ለስቃይ እና ለመንገላታት እንዲዳረጉ ሚናውን ተጫውቷል:: ይህንን መፍትሄ ለማምጣት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገናል በጋራ አገር ላይ በጋር እንድንሰራ እኛ እናውቅላቹዋለን የሚል ስርኣት ከነአካቴው ሊቆም እና ሃይ ሊባል ይገባዋል: ኢትዮጵያውያን በአረብ አገራት እየደረሰ ያለው መከራ የምን ውጤት ነው መፍትሄውስ ምንድነው ብለን ቆም ብለን የምናስብበት ጊዜ ነው:: ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር ስርኣቱ አሁንም ካለው እኩይ አድራጎቱ ሊቆጠብ ስለማይችል ነገ በሌላም አገር የምንኖር ኢትዮጵያውያን ችግሮች ቢደርሱብን የገዛ ዜጎቼ ሳይሆን የሚለው አብሮ ህገወጥ እና ወንጀለኛ ብሎ በመፈረጅ ለሞት እና ለስቃይ ከመዳለግ ወደኋላ ስለማይል የትግል አድማሳችንን በማስፋት ወንጀለኛው ህገወጡ በሃገሪቱ የተንሰራፋው ስርኣት መሆኑን የማጋለጥ ግዴታ አለብን;;ጎን ለጎንም የመፍትሄ ሰዎች እየሆንን ባለው ስርኣት ላይ ጫና በማሳደር መትጋት ድርሻችን ነው::

አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።
ምነው ሰቆቃችን በዛ?
ሐገር እንደሌለው በዋዛ።
ለውጡ ሆኖብን ከድጡ ወደማጡ
ስንቶች ሐገራቸውን ጥለው ወጡ?
ብልሹ አገዛዝ ነግሶብን
ኢትዮጵያዊያን ተዋረድን።
ያዋረድን ግን ወያኔ ነው
ዓይን እያለሁ የማያየው
ጆሮ እያለው የማይሰማው።
ሴቶቻችን ሲደፈሩ ክብራችን ሲንኮታኮት
ኢቲቪ የወያኔ የውሸት ቋት።
አንቺ ያልታደልሽ ሐገር
አኬልዳማ የደም ምድር።
አምላክ ሆይ እንባችንን አብስና
ገላግለን ከዚህ ዘመን ፍጠንና
ሐገር እያለን እንደሌለን
በጣም እናሣዝናለን።
በርጉማን እየተመራን እስከመቼ
በሣውዲ እያለቁ ወገኖቼ
ዱሮ ግንደበረት የቀረው
ሣውዲ ላይ ባርነታችን የነገሠው
በወያኔ የተነሣ ነው።
ለአፍሪካ የምትተርፍ ሐገር
እንዲህ ሆና ስትቀር?
ጌታ ሆይ ገላግለን ከእዬዬ
መሪ ስጠንና እንደ እምዬ።
*በሣውዲ መከራ ላይ ለወደቁ ወገኖቼ መታሠቢያ
18/11/2013
penethiopian
በዩጋንዳ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ!!!
በሳውዲ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍና ሰቆቃ በማውገዝ የሳውዲ መንግስት ለዓለም አቀፉ የሠብዓዊ መብቶች መከበር የፈረመውን ስምምነት እንዲያከብርና ዜጎቻችን ላይ እያደረሠ ያለውን ኢሞራላዊ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆምና ለሠው ልጆች ሰብዓዊነት እንዲያሳይ ለመጠየቅና በቀጣይ በምስራቅ አፍሪካ ያለውን የስደተኞች ሁኔታ ለመምከር የወገኖቻችን መከራና ስቃይ ነግ በኔ ሊሆን ይችላል ብሎ በማሠብ በአንድነት ሆነን ለመምከር አንዳንድ ቅድመ ዝግጅቶች ለማድረግ ከጎናችን እንዲቆሙ እንጠይቃለን።
ቀጣይ እንቅስቃሴያችንን በ<efjaehrco>ፌስ ቡክ ላይ ማስታወቅያችንን ይከታተሉ።
በህዝባዊ ተቃውሞ ለመሣተፍ በ<[email protected]>ይመዝገቡ።
በዩጋንዳ ነግ በኔ የወገን ለወገን ደራሽ የጋራ ድምፅ አስተባባሪ ኮሚቴ
[email protected]>
ህዳር 7 ቀን 2006 በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢሳት ድጋፍ ኮሚቴዎችና አድማጮች ሁሉ ባለፉት ጥቂት ቀናት በሳዑዲ አረቢያ ነዋሪ በሆኑ የኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ እየደረሰ የሚገኘውን እጅግ ዘግናኝ ድብደባ፣ ግድያና ሴቶችን አስገድዶ መድፈር በከፍተኛ ቁጭትና ሃዘን ተከታትለናል። የኢሳት የዝግጅት ክፍልም ይህንኑ ልዩ ትኩረት ስጥቶ መረጃዎችን እግር በእግር ሲያቀርብ ቆይቷል። የተሻለ ሕይወት ለመኖር በሚል ተስፋን ሰንቀው በስደት ሀገር […]
ኢትዮጵያዊ ባልሆነ መንግስት መገዛት ይብቃን! ጌታቸው ሽፈራው
አንድ የኢህአዴግ ታጋይ አሊያም ሲቪል ካድሬ ሲሞት በቴሊቪዥን ሳይቀር ይለፈፍለታል፡፡ በሳውዲ እየሞቱ ለሚገኙት ኢትዮጵያውያን ግን አንድም ነገር አልተደረገም፡፡ ሌላው ይቅርና መሰሎቹ አጭበርብረው ‹‹ምርጫ አሸነፍን›› ሲሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ለማጉረፍ ማንም የማይቀድማቸው እነ ኃ/ማሪያም አሁን ምንም አላሉም፡፡ በተቃራኒው ድምጽ ለማሰማት የወጡትን በጨካኝ ፖሊሶቻቸው አስደበደቡ፡፡
ወደ ጣሊያን ሲያቀኑ ያለቁት የአፍሪካ ስደተኞችን ሞት አስመልክቶ ሰንደቅ አላማው ዝቅ ብሎ ተውለብልቧል፡፡ የኢትዪጵያውያንን ነፍስ ምን ያህል አርክሰው ቢያዩት ነው? ለአንድ ቀን ሀዘን፣ ለአንድ ቀን ሰንደቅ አላማውን ዝቅ ለማድረግ አልፈቀዱም፡፡ ስለዛ አምባገነን መሪያቸው ግን ሁሌም ይቆዝሙብናል፣ ይለምኑብናልም፡፡ ኢትዮጵያን እንደነጠቁን ሰላማዊ ሰልፉን በመከልከል ዳግመኛ አረጋግጠውልናል፡፡ በተቃራኒው ከኤስያ፣ እስከ አውሮፓና ሰሜን አሜሪካ የእኛዎቹ ወገኖች እንደልባቸው ሰላማዊ ሰልፍ እያደረጉ ነው፡፡
እንዲያውም ድጋፍ እየተደረገላቸው፡፡ ትናትና ፌስ ቡክ ላይ እንዳነበብኩት አንድ የአውሮፓ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ሲያሳውቁ የድምጽ ማጉያ የመሳሰሉ መሳሪያዎች ከሌሏቸው ማዘጋጃ ቤቱ ሊያውሳቸው እንደሚችል አረጋግጦላቸዋል፡፡ እንደ ሳውዲ ካሉት ውጭ ለኢትዮጵያውያን አገራቸው ካለው ይልቅ የተሰደዱበት መንግስታት ደግና ርሁሩሆች ናቸው፡፡ ለእኔ ኢህአዴግ ኢትዮጵያዊ ላለመሆኑ ከዚህ ውጭ አስረጅ አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡ የግድ እንደ ግራዚያኒ በየ ቤታችን ገብቶ በቆጨራ እስኪቆርጠን መጠበቅ የለብንም፡፡ ካድሬ ሆነ ተቃዋሚ፣ አማራ ሆነ ኦሮሞ፣ ትግሬ ሆነ ወላይታ ኢህአዴግ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን እስካለሰበ ድረስ ከስቃዩ ሊያመልጥ አይችልም፡፡ መለስ ከሞተበት ጊዜ ጀምሮ ኢህአዴግ ገንዘብ ሲያሰባስብ የነበረው እንደ ሳውዲ ባሉ አገራት ከሚገኙት ዜጎቻችን ጭምር ነው፡፡ የልመና ጊዜ በሮ የደረሰው የውጭ ጉዳይ አሁን በቲውተር ከሚቀልደው ያለፈ ሊፈይድ አልቻለም፡፡ ካድሬም ብትሆን አይቀርልህም፡፡

በጊዜያዊ ጥቅም ከሆነማ ጣሊያንም ለባንዳዎቹ ከፍተኛ ጥቅም ሰጥታለችኮ፡፡ እነ ራስ ሀይሉ በወር 175 ሺህ ሊሬ ይከፈላቸው ነበር፡፡ የፋሽስቱን ስርዓት ያልተቃወመ ወጣት አሁን ኢህአዴግ ከሚያደርገው በላይ ተከፍሎታል፡፡ እናቶች፣ ካድሬ ቄሶችና ሌሎችም ኢህአዴግ አሁን ከሚያደርግላቸው በላይ ጣሊያንን እንዳይቃወሙ ጥቅማጥቅም ተሰጥቷቸዋል፡፡ በኋላ ግን በጅምላ ተጨፍጭፈዋል፡፡ እናም ይህን ኢትዮጵያውይ ያልሆነ መንግስት ኢትዮጵያዊ ማድረግ አይቻልም፡፡ በቃ! ከዚህ በላይ በደል መሸከም አንችልም፡፡ ከዚህ በላይ ባይተዋር መሆን አንፈልግም፡፡ ከዚህ በላይ ማንባት አንሻም፡፡ ኢህአዴግን በግልጽ በቃህ የምልበት የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ አዎ! ኢትዮጵያዊ ባልሆነ መንግስት መገዛት ይብቃን! Getachew Shiferaw.

Ethiopian migrants sleep out in the open near a transit centre where they wait to be repatriated in the western Yemeni town of Haradh, on the border with Saudi Arabia, (REUTERS/Khaled Abdullah) dailystar.com
********************************************************************************************************************
በአብዛኛው የኢህአዴግ ድርጅቶችን ብቻ በማሳተፍ የምዝገባ ዘመቻው ቀጥሏል
ዛሬ መልካም ዜናን ከሪያድ መጠለያዎች ሰማሁ !
* 66 በሚደርሱት መጠለያ የሚገኙት ኢትዮጵያን ይዞታ መሻሻል ጀምሯል
* የምግብ የውሃና የህክምና አገልግሎቱ ሽፋን አበረታች ነው ፣ አቅርቦቱ ሙሉ በሙሉ በሳውዲ መንግስት የሚሸፈን ነው
* ለህጻናትና ለአቅመ ደካማ ሴቶች ትኩረት እየተሰጠ ነው
* የተሻለ መጠለያ ለማስተላለፍ የተደረጉ ሙከራዎች በተጠላዮች ፍርሃቻ ከሽፈዋል
* ተጠላዩ ግን ፍርሃት አለበት ፣ ከመጠለያው ውጭ ያሉ ዜጎች በሚሰጡት ነዋሪው ሊያረጋገው አልቻለም
የጅዳው አስጊ ሁኔታና የቆንስል መስሪያ ቤቱ የሽሜሲ ዘመቻ፡-
* የጅዳ ቆንስል ላልተወሰነ ጊዜ ተዘግቷል
* የመረጃ እጥረት አሁንም አለ
* በጅዳ አንዳንድ አካባቢዎች ህገ ወጥ ወገኖች በመረጃ እጥረት ወደ ሁከት እንዳይሸጋገሩ ያሰጋል
* መኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ነዋሪዎች እንዲታገሱ ህጋዊ ነዋሪዎች እየተማጸኑ ነው
* የቆንስላው ሃላፊዎች ትኩረት ወደ ሽሜሲ ጊዜታዊ እስር ቤት ሆኗል
* በአብዛኛው የኢህአዴግ ድርጅቶችን ብቻ በማሳተፍ የምዝገባ ዘመቻው ቀጥሏል
* በቆንስሉ መዘጋት ብዙዎችን አስቆጥቷል ” የታመመ ቢሞት እንደጰት እንቅበር? ፖስፖር ቢታደስ ማስተካከል ቢያስፈልግ ምን እናድርግ? የጋብቻ ወረቀት ማረጋገጫና እና ተመሳሳይ ግልጋሎት ስንፈልግ የት እንሂድ? ” ሲሉ በማጠየቅ በአስቸኳይ ቆንስሉ እንዲከፈት ነዋሪዎች መንግስትን ተማጽነዋል
* የሰው ሃይል እጥረት አለ፣ ሶስት ኢኒስፔክተሮች ከሃገር ቤት ጅዳ ገብተው ስራቸውን ጀምረዋል
* በጎ እናድርግ የሚሉ ነዋሪዎች ተበራክተዋል ፣ የቆንስሉን መልስ እየጠበቁ ነው