የቀጣፊዎቹ ልሣን የሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ትናንት ማታ በመስኮቱ ሦስት ሆዳም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር አመራሮች አቅርቦ ነበር።ሦስቱ ሆድ አደሮች በበረከትና በሺቀጥል ከማል ተጠፍጥፈው የተሠሩ የጋዜጠኞች ማህበር መሆናቸው ነው።
ኢነጋማ አባላቱና አመራሩ ተጠራርገው ከሐገር ከተባረሩበት የጥቅምቱ መሬት አንቀጥቅጥ ሕዝባዊ ማዕበል በአግአዚ ጭፍጨፋ ከከሸፈ ወዲህ የነበረከት ስሪቶቹ በቀቀኖች አይናቸውን በጨው አጥበው ዕአንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የኢትዮጵያን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው ዕዕሲሉ ለፈጣሪዎቻቸው ታማኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
ጋዜጠኛ ባንዳ ሆኖ ህሊናውን ሲያመክን ማየት እንዴት ያሣዝናል፧
በእስክንድር፣በርዕዬትና በውብሸት ኮራሁ።በአብርሐም፣በወንደሠንና በመሠረት አታላይ አፈርኩ።ሦሥቱም አታላዮች መሆናቸው ነው።ያታለሉት ግን ራሣቸውን ነው።ህሊናቸውን ነው።
የሐገራችን ሚዲያ መቃብር ከወረደ ስምንተኛ ዓመቱን በምንዘክርበት በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኞችን አሸባሪ እያለች ዘብጥያ የምትወረውር ሐገር ውስጥ የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች መድረክ በመባል የሚታወቀው አኅጉር አቀፍ የሚዲያ ባለድርሻዎች የውይይት መድረክ ስድስተኛ ጉባዔውን ሲያከናውን በመለስ ዜናዊ ሚስጥራዊ መመርያና የተፈቀደ በጀት አማረ አረጋዊ ባለ ቀይ ጃኖው የሪፖርተር ጋዜጣ አሣታሚና የ ኤም ሲ ሲ ባለቤት እንዳለውዕየአፍሪካ ሚዲያ መሠረታዊ ችግሮች ሁለት ነጥቦችን አንስቷል፡፡ በዋናነት የጠቀሱት የሚዲያ ተቋማቱ አቅም ማነስና የሚዲያ ነፃነት ችግሮች መሆናቸውን፣ ሌላኛው ደግሞ የውጭ አገሮች አድልኦና ፍላጐት ነው ፡፡ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርም ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ቢሆንም፣ ነገር ግን በሰፊው እየተዘገበ ያለው ስለኢትዮጵያ ብቻ ነው ዕአማረ አረጋዊ ዕበኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርምዕሲሉ መናገራቸው የግሉ ፕሬስ የነፃነት ችግር እንዳለበት ከመሸም ቢሆን ያመኑ ይመስላል።
በቀጣይ ልጅ ደመቀ መኮንን አሉት እንደተባለው ጋዜጠኞቹ በሙያቸው ምክንያት አለመታሰራቸውን ገልጸዋል፡፡
ዕጋዜጠኞቹ በተግባር በሽብር እንቅስቃሴ ውስጥ ተገኝተዋል ለዚህም ተገቢውን ሕጋዊ ሥርዓት የተከተለ ዕርምጃ ተወስዶባቸዋል፤ዕዕ
ዕኢትዮጵያ ካለችበት ቀጣና አንፃር የሽብር እንቅስቃሴ ዋነኛ ሥጋቷ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥት የህልውና ጉዳይ አድርጐ ይመለከተዋል፤ዕ ብለዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
ዕበጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው።ዕያሉት ጋዜጠኛ ስሙ ማን ይሆን፧በረከት ለምን ይህን ተናገሩ ብሎ እንደማይቆጣዎ ተስፋ እናድርግ፧ተላላኪው ቢሆኑም ቅሉ።
የኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣በወርቃማ ቃላት ይህን ብለዋል። ዕሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ጋዜጠኞችን ማሰርና መቅጣት ኋላ ቀር የሆነ አስተሳሰብ ነው፤ዕ ሲሉ ገልጸውታል፡፡
የሚዲያ ነፃነት በኬንያ መሠረቱ እንዲስፋፋ መንግሥታቸው የሚያምን መሆኑን የሚናገሩት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ይህንን የሚያደርጉት ለሚዲያ ተቋማቱ ሲባል ብቻ ሳይሆን ኬንያውያን ሥልጣን ላይ ያስቀመጧቸው መሪዎች እንዴት እያስተዳደሯቸው እንደሆነ የማወቅ መብት ስላላቸውና ስለሚገባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አንዳንድ የጉባዔው ተሳታፊዎች የአኅጉሪቱ የፖለቲካ አመራሮች ወይም መንግሥታት የሥልጣን ቆይታቸውን ለማራዘም የአኅጉሪቱ የሚዲያ ነፃነትን በሚያወጧቸው የተለያዩ አፋኝ ሕጐች ገድበዋል፡፡ የሚዲያ ባለሙያዎችም በእነዚህ ሕጐች ሰለባ ሆነዋል በማለት ጋዜጠኞች ተከራክረዋል፡፡ በርካቶችም ሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ሕይወታቸውን እስከማጣት ደርሰዋል በማለት በውይይቱ የተሳተፉ ጋዜጠኞችና የመስኩ ባለሙያዎች የአኅጉሪቱን የፖለቲካ አመራሮች ወቅሰዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ የሚዲያ ባለሙያዎች ባገኟቸው አጋጣሚዎች ሁሉ በሙያቸው ምክንያት በርካታ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እስር ቤት እንደሚገኙ በማሳያነት ይጠቅሳሉ፡፡
ይህን የመሠለ መድረክ መዝጊያ ላይ ነው የነበረከት በቀቀኖች ዕበኢትዮጵያ አንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የሐገራችንን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው።ዕየሚሉን።
ህሊና ከሌላቸው ሆዳምና አድርባይ ጋዜጠኞች ይሠውረን።
ፔን ዘ ኢትዮጵያ