ጥንተ ስቅለቱ በዩጋንዳ ምድር
በልዩ ድምቀት እየተከበረ ነው።
መንበረ ፓትርያርኩን በሰሜን አሜሪካ ባደርገው በስደት ላይ በሚገኘው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው የካምፓላ መካነሠላም መድሐንያለም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የደብሩ ማሕበረ ካህናትና ማህበረ ምዕመናን የጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለቱን ዛሬቅዳሜ መጋቢት ሃያ ሰባት በከፍተኛ መንፈሣዊ ሥነ ሥርዓት እየተከበረ ነው።በአሁኑ ሠዓት የዕለቱ ቅዳሤ እየተከናወነ ሲሆን የዕለቱ ወንጌል ከማቴዎስ ምዕራፍ ሃያስምንት ተነቦአል።በቀጣይምበዓሉን በተመለከተ የወንጌል ማዕድ በደብሩ አስተዳዳሪቀሲስ ፀሐይ ደስታ ይቀርባል ። ታቦተ ኅጉ ይወጣል ዑደት ይደረጋል ።በመሪጌታ ይሄይስ ዓለሙ መሪነት በደብሩ ፈለገ ህይወት ሰንበት ትቤትመዘምራን ወረብ ይቀርባል።

<ሃሌ ሉያ መርሕ በፍኖት
ሞገሦሙ በፍኖት።
ዝንቱ መስቀል ለአዳም ዘአገብዖ ውስተ ገነት።>
በመጨረሻም ቃለ ምዕዳንና ፀሎተ ቡራኬ ተሠጥቶ የበዓሉ ፍፃሜ እንደሚሆን ከደብሩ ሠበካ ጉባዔ አስተዳደር ጽ/ቤት የወጣው መግለጫ ጠቁሞአል።

አክሊለሠማያት ዘ መካነሠላም

ሁዳዴ ፆምን ለመፆም ተዘጋጅተዎል??

ነገ ሠኞ የካቲት አስራ ሠባትቀን ሁለት ሺ ስድስት ዓመተ ምህረት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ዐብይ ፆም ይጀመራል።
ለመፆም ተዘጋጅተዎል?ዘንድሮ ፆም ለነፍስ ብቻ ሣይሆን ለስጋም ጠቃሚ እየሆነ ነውና ሀኪም ቀይ አብርቶ በስጋ ምክንያት ሥጋት ላይ መሆንዎን ሣያረዳዎ በንስሃ አባትዎ ምክር ፆሚ ይሁኑ።
ቢፆሙ ሸንቃጣ ይሆናሉ።ስጋዎ ፈተና ላይ አይወድቅም።መንፈስዎ ይረጋጋል።ባይፆሙ ኪሎዎ ይጨምራል።ከሀኪም ፊት አይርቁም።ቁና ቁና ይተነፍሣሉ።ወጪዎ ይጨምራል።አልጋና ብልግና ሊያዘወትሩ ይችላሉ።
ኪስዎ ከመጀመርያው ፆሚ ከሆነ የኔ ምክር እርስዎን አይመለከትምና ዘና ይበሉ።ፆም ሲፆሙ ሆድዎን ብቻ ማዕቀብ አይጣሉበት። ምላስዎን አደብ አስገዟት።ዓይንዎን ከዳሌና ጭን ላይ ይንቀሉ።ጆሮዎ የአመት ረፍት ያስወጡት።እግርዎ አይንጦልጦል።ያኔ የወጣልዎ ምርጥ ፆሚ ይሆናሉ።አንድ ነገር ረሣሁ።በልብዎ ግርግዳ ያከማቹትን የቂምና የጥላቻ ዶሴ ፈጥነው ይደልዙ።ዲሌት ያርጉት።የቂምና የበቀል ጎሬ የሆነ ልብና ጭንቅላት ይዘው ከአምላክዎ ጋር መገናኘት እንደማይችሉ ይገንዘቡ።ልብዎ በቂም ኔትወርክ ተጨናንቆ ወደ ፈጣሪዎ የሚያደርጉት ማንኛውም ጥሪ አይሠማምና ውዝፍ ሂሣብዎን ያወራርዱ።ያኔ ሁዳዴን ፆም ለመፆም ሚኒማውን ያሟላሉ።
ሃምሣ አምስት ቀናት ወጥረው ቢፆሙ ለስጋዎም ሆነ ለነፍስዎ ርጋታና ዕርካታ ያገኛሉ።ቅበላን ለመሆኑ እንዴት አሣለፉት? ጮማ ቆረጡ? ከጠጇስ ጨለጡ ?ከስጋ ወደ ሽሮ ሊሸጋገሩ የቀረዎ እራት የተባረከ ይሁን።
አክሊለ ሠማያት ዘ መካነ ሠላም

ሐበሾቹ ነገ ጠዋት የጌታን ጥምቀት በዩጋንዳ በልዩ መንፈሣዊ ስርዓት ያከብሩታል!!!

መንበረ ፓትርያኩን በሰሜን አሜሪካ ባደርገው በስደት ላይ በሚገኘው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው የካምፓላ መካነሠላም መድሐንያለም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የደብሩ ማሕበረ ካህናትና ማህበረ ምዕመናን በዩጋንዳ ነገ ጠዋት ጥር ዐሥራ ዐንድ ቀን የጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓልን በከፍተኛ መንፈሣዊ ሥነ ሥርዓት እንደሚያከብሩ ተገለፀ።
ከሠንበት ቅዳሤ በኋላ የመድሃኒያለምና የቅዱስ ሚካዔል ታቦታት በምዕመናን ታጅበው በመሪጌታ ይህይስ ዓለሙ መሪነት ያሬዳዊ ዝማሬ የዕለቱ ምልጣን<ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ ወልደነ ዳግመ እማየ ወእመንፈሠ ቅዱስ እሙነኮነ ለፀሐየ ፅድቅ አስተርዕዮቱ አማን መንክር ስብሐተ ጥምቀቱ > የሚቀርብ ሲሆን የደብሩ ማሕበረ ካህናት ከማህበረ ምዕመናን ጋር ፈጣሪ አምላካቸውን በያሬዳዊ ዜማ ያመሠግናሉ። ጥምቀተ ባሕሩም ይባርካል።
አስተማማኝ የፖሊስ ጥበቃ ስለሚደረግ ምዕመናን መኪናቸውን ደብሩ ባዘጋጀው የማቆሚያ ስፍራ በማድረግ ያለስጋት በዓሉን እንዲያከብሩ የቤተክርስትያኒቱ አስተዳደር ጽ /ቤት መልዕክቱን አስተላልፏል።
ሐበሾቹ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን በካምፓላ መካነሠላም መድሐንያለም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን በዩጋንዳ በጋራ በመሆን ፈጣሪያቸውን በተለይ ዘወትር ዕሁድ እንደሚያመሠግኑ ይታወቃል።አባ ኃይለማርያም በአሉን በማስመልከት የወንጌል ማዕድ የሚያቀርቡ ሲሆን የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ፀሐይ ደስታ በበበዓሉ ፍፃሜ ላይ ቃለ ምዕዳን እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል።

የካምፓላ መካነሠላም መድሐንያለም ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ማህበረ ካህናትና የደብሩ አስተዳደር ጽ /ቤት ለመላ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሐነ ጥምቀቱ አደረሣችሁ እያሉ መልካም ምኞታቸውን እንዳስተላለፉ የዚህ ዜና ዘጋቢ ጨምሮ ገልጿል።
አክሊለ ሠማዕት
penEthiopian

የኡጋንዳ ፖሊስ የነገው ስብሠባ መታገዱን ገለፀ!!!
ትናንት አመሻሽ ላይ የካባላጋላና የሴንተራል ፖሊስ ኮማንደሮች የኢትዮጵያዊያን ማህበረሰብ በኡጋንዳ አመራር የሆኑትን አቶ ዘለቀ ጀበሮንና የማህበራዊ ጉዳዮች ተጠሪ የሆኑትን ጋዜጠኛ ደረጀ በጋሻውን በጽ/ቤታቸው ያነጋገሩት አዛዦች ኮሚኒቲው የጠራው ስብሠባ በበላይ አካላት ትዕዛዝ መታገዱን እንደተገለፀላቸው ለኮሚኒቲው ቅርበት ያላቸው ወገኖች ጠቆሙ።
ከኮሚኒቲው ቦርድ አባላት መካከል አቶ ዘለቀ ጀበሮንና ጋዜጠኛ ደረጀ በጋሻውን ብቻ ፖሊስ ጠርቶ ማነጋገሩ ብዙዎችን ያስገረመ ሲሆን ኮሚኒቲው አዳራሽ ተከራይቶና ለማህበረሠቡ በበራሪ ወረቀትና በፌስ ቡክ ጥሪ አስተላልፎ ሕዝባዊው ስብሠባ ሊካሄድ ዐርባ አምስት ሠዓታት ሲቀረው በማስታወቅያው መልዕክት የተደናገጠው የወያኔ የኡጋንዳ ቆንስላ ለኡጋንዳ መንግስት ደብዳቤ ፅፎ የዕሁዱን ስብሠባ እንዳሳገደ ደብዳቤውን በፖሊስ ኮማንደር ዕጅ እንደተመለከተ ጋዜጠኛ ደረጀ በጋሻው ጠቁሞ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሕዝባዊ ስብሰባውን የጠራው በሠላማዊ መንገድ ለመወያየትና በሳውዲ ያሉ ወገኖችን መከራና እንግልት ለመጋራትና ወገናዊነትን ለማሣየት እንጂ ሌላ ምንም አይነት ድብቅ አጀንዳ እንደሌለው ጠቁመው የወያኔ የኡጋንዳ ቆንስላ የሕዝብን ድምፅ ለማፈን መንቀቀሱ ትzብት ላይ እንደሚጥለው ጠቁመዋል።
በመጨረሻም የፖሊስ ኮማንደሮቹ ያስተላለፉትን መመርያ በመቀበል ኡጋንዳ በዓለም አቀፉ የስደተኞች ስምምነት መሠረት የፖለቲካ ጥገኝነት አግኝተን የምንኖርባት ሐገር በመሆኗ የጠራነውን ስብሰባ በመመርያው መሠረት ማቆማችንን በማሣወቅ ከፖሊስ ጋር ያደረጉት ውይይት ተጠናቋል ሲሉ ጋዜጠኛ ደረጀ ጠቁመዋል።

የዛሬይቱ ቀን በህይወቴ አዲስ ምዕራፍ የጀመርኩባት ዕለት ናት።እናት ሐገሬ ኢትዮጵያን ለቅቄ የሞያሌን ኬላ ተሻግሬ የኬንያን ምድር የረገጥኩባት ታሪካዊ እለት ።ኅዳር ሠላሣ ቀን አስራ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ስምንት ዓመተ ምሕረት ዕለተ ዐርብ ከቀትር በፊት።ከደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ሰሜን ኬንያ ጋንቦ ቀበሌ የገባሁበት ቀን ስምንተኛ ዓመት መታሠቢያ።
የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አስር ቁጥር ሃያ ሦሥትን ይመልከቱ። ባላሠቡትና ባልጠበቁት ጊዜና ሰዓት ከትውልድ ቀዬዎ ሊሠደዱ ይችላሉ።ዛሬ ምስራቅ አፍሪቃ ምድር ወገብ አቅራቢያ ቪክቶርያ ሐይቅ ዳርቻ ላይ ሆኜ የተሠደድኩበትን ምክንያት ሣሠላስል መሠደዴ አግባብነት ነበረው ወይስ እንደ ኮነሬል መንግስቱ ፍርጠጣ ነው ለማለት ህሊናዬ ዘወትር እንደጠየቀኝ አለ።
ሟቹ የወያኔ ጠቅላይ ሚንስትር የግንቦት ሠባቱን የምርጫ ውጤት በአጋዚ ጥይት ከቀለበሡትና ሕገ መንግስቱ በሕገ አራዊት ከተለወጠ በኋላ የሐገር ቤት ሠላማዊ ትግልና የፕሬስ ነፃነት ጥቅምት ሃያ ሁለት ቀን አክትሟል።
ጋዜጠኞች፣የሠብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተለቅመው ሲታሠሩ፣ወጣቱ ያለ ሀጥያቱ በየጦር ካምፑ ሲታጎር የኔ ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማንም ግልፅ ነበር። ጥቅምት ሃያ ሁለት አመሻሽ ላይ ሱፍና ከረባት፣መነፅርና ፕሮቶኮል ቀርተው አልባሌ በመልበስና በመምሠል ከቦታ ቦታ ስሽሎኮለክ ብቆይም ነገሮች ከመሻሻል ይልቅ እየተበላሹ በመምጣታቸው ወደ ኬንያ ለመጓዝ ህዳር ሃያ ሁለት አካባቢ የወሰንኩ ይመስለኛል።
ጠቅላይ ሚንስትር ለገሠ ዜናዊ በኛ ላይ ጦር ሲያውጁ ያቀረቧቸው አማራጮች ት<ዝ ይሉኛል።
፩ አርፎ መቀመጥ ፪መሠደድ ፫ጫካ መግባት ፬ቃሊቲ ።
ለነፃነት የሚደረገውን ትግል ለማገዝ በወቅቱ የኔ ምርጫ መሠደድ ነበር።ሠላማዊ ትግል አላዋጣ ሲል ጠመንጃ ማንሣት የግድና ተገቢ መሆኑን ከነማንዴላ ኤኤንሲ ፓርቲ ውሣኔ መማር ይቻላል።
አማርኛ ቃለ መጠይቅ ለቪኦኤ ለመስጠት የሚጠየፉት የብአዴኑ በረከት ስምዖን የማስታወቅያ ሚንስትር በነበሩበት ፩፱፱፪ የፓርላማ ምርጫ ወቅት በአፍሪቃ አዳራሽ የክርክር መድረክ ላይ ወያኔ ስልጣን በጠመንጃ እንደያዘና በምርጫ ቢሸነፍ ስልጣን ለመልቀቅ ዝግጁ ነወይ ስል ላቀረብኩላቸው ጥያቄ ደርግ መብታችንን በመርገጡ ጠመንጃ አንስተናል ሲሉ መናገራቸውን አስታውሣለሁ።መብቱ የተረገጠ ሕዝብ ጠመንጃ ሊያነሣ እንደሚገባ በረከት የተገነዘቡ ይመስላል።
የኔ ድርሻ እንደጋዜጠኛና የሠብዓዊ መብት ተሟጋች ከሐገር ከተሠደዱ ቦኋላ የፈረንጅ ሐገር ኑሮ ለምዶ ሆዳም ዲያስጶራ መሆን ሣይሆን የተሠደዱበትን ዓላማ ባለመዘንጋት ሐገራዊና ህሊናዊ ግዴታን መወጣት ነው።
የፓለቲካ ስደተኛ ነኝ ብሎ የኬዝ ደራሲ መሆንና የስደተኛ መታወቅያ ታቅፎ ከንቱ የተስፈኛ ህይወት መምራትን ልንጠየፈው ይገባል።ሁለት ሺ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆኖ ወያኔን ወያኔ ብሎ መጥራት የሚፈራ ማንነት ይዞ መንከላወስ በታሪክና በትውልድ እንደሚያስወቅስም መረዳት ያስፈልጋል።
ሁለት ልብ ሆኖ ሁለት ማልያ እየለበሡ በአንድ ሜዳ ላይ መጫወት አይገባም።እኔ የፓለቲካ ስደተኛ ነኝ።የየትኛውም የፓለቲካ ድርጅት አባል አይደለሁም።መሆንም አልፈልግም።ያ ማለት ግን የሐገሬ ጉዳይ አያገባኝም፣ካናዳ ገብቼ የስደት ኑሮ ለመኖር የመጣሁ የኤኮኖሚ ስደተኛ ነኝ፣ኬዜ ተቀባይነት እንዲያገኝ ምርጥ የኬዝ ደራሲዎች የፃፉልኝን ገፀ ባህሪ በተገቢው መድረክ የምተውን ተወናይ።ካልሆነም ፍራሼ ስር የደበቅኩትን ፓስፓርት አድሼ ምሣዬን ካምፓላ በልቼ ለራቴ አዲስ አበባ የምበር ዋቴ።ዛሬ ይህን ሁሉ ያስቀባጠረኝ እንደዋዛ ከሐገር፣ከቤተሠብ፣ከጓደኛ ተለይቼ ሁለት ሺ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሁለት ቀናት በስደት መቆየቴን በመዘከር ነው።
ህይወት ይቀጥላል።አዲስ አበባ ላይ መፃፍና መኖር ብከለከልም ካምፓላ ላይ እየፃፍኩ እኖራለሁ።ብዕሬ ዝም አትልም።እውነትን፣ነፃነትን፣ፍትህን በሐገሬ ሠማይ ላይ እስክመለከት ድረስ እፅፋለሁ።ሕገመንግስቱ ከወሬና ከመነበብ ባሻገር በተግባር እስኪፈፀም፣ሕዝቤ በነፃና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሕዝብ የሚመርጣቸው ፓርቲዎች ስልጣን እስኪረከቡ ድረስ እፅፋለሁ ፣እናገራለሁ።
ማንዴላን የታራክ ሠገነት ላይ የሠቀላቸው ለነፃነት የከፈሉት ክቡር ዋጋ ነው።ሞት እንደሆነ አይቀሬ ነው ።እየሞቱ ከመኖር ለትውልድ ነፃነት በየመስኩ የአቅማችንን እናበርክት መልክቴ ነው።
እስክንድር፣ውብሸት፣ርዕዬት፣አንዱዓለምና በርካቶች……..የኛ ማንዴሎች ናቸው።
እንደአንዳቸውም ባለመሆኔ ባዝንም ባለሁበትም ቢሆን ስለነሡና ስለሐገሬ ልጮህ እወዳለሁ።አምላኬም ይረዳኛል።ዛሬ አዲስ የልደት ቀኔ ናት።ዕድሜዬም ስምንት ነው።አዲስ ህይወት ከኬንያ ጋንቦ ጀምሬ አሁን ካባላጋላ ላይ ነኝ።የነፃነት ትግሌ ግን እስከመቃብሬ በብዕሬ ይቀጥላል።ትግልእስከመቃብር።
ደረጀ በጋሻው<pen Ethiopian>

ኢትዮጵያዊው ስደተኛ ሣሙዔል መኮንን <አቡሽ> ዛሬ በዘጠኝ ሠዓት በካንፓላ መካነ ሠላም መድሐንያለም ቤተክክርስትያን በድንግል መሬት ተቀበረ።ወጣት ሣሙዔል መኮንን <አቡሽ>ከሐገሩ ተሠዶ ከወጣ አምስት ዓመታት የተቆጠረ ሲሆን ወደሌላ ሐገር ለመሻገር ሣይችል የምድር ጉዞውን በምድር ወገቧ ዩጋንዳ ጨርሷል።ከሃምሣ ያላነሡ ሥደተኞች በቀብሩ ላይ መገኘታቸውን የፔን ዘ ኢትዮጵያ ዘጋቢ የታዘበ ሲሆን ወጣቱ በጉበት ህመም ባለፈው ማክሠኞ ጧት በተኛበት ሞቶ መገኘቱን ሀኪሞች ጠቁመዎል።

ታላቁ የነፃነት አርበኛ ኔልሰን ማንዴላ በአይቀሬው ሞት ሲረቱ ጆሀንስበርግ ብቻዋን የሀዘን ቡልኮ አላጠለቀችም።መላ ዓለም በሀዘን በረዶ ተመቷል።አፓርታይድን ወደ ከርሠ መቃብር ያወረደ ጀግና በአይቀሬው ሞት ተረታ።
እንደኔ ምኞት አፍሪቃ በየማዕዘኑ የማንዴላን አይነት መሪ ብታገኝ ምን ያህል የታደለች አህጉር በሆነች ነበር<>የተባበሩት የአፍሪቃ አንድ ገናና ስቴት በሆንን ነበረ።ነገ የሚሆነውን ለመተንበይ ነብይ መሆን ቢያስፈልግም አሁን ያለችው አፍሪቃ ከሃምሣ አራት ግዛትነት ወደ አንዲት አህጉር እንድትመጣና አንዲት ሐገር ለመሆን በየቤታችን ያለው ማነቆና የገዢ ፓርቲዎች ማቱሣላዊ ቆይታ ድቅድቅ ላይ መሆናችንን ጠቋሚ ነው።ወደ ስልሣና ሠባ ትናንሽ ሐገራት እንዳንከፋፈልም የሚያሠጉ ሁኔታዎችም መኖራቸውን መገንዘብ ይኖርብናል።
ከማንዴላ ጋር የጠበቀ ቁርኝት የነበራት የኔዋ ፀረ አፓርታይድ የነበረችው ኢትዮጵያ ጠያይም ሐገር በቀል አፓርታይዳዊ ስርዓት አራማጆች እያቆጠቆጠባት መሆኗን መደበቅ ለኔ ህሊና አይመጥንም።
የስራ ባልደረባዬ እስክንድር ነጋ በግፈኞች የተፈረደበት ጠበንጃ አንስቶ ወይም ፓርቲ መስርቶ ለስልጣን ስለታገለ እንዳልሆነ አሳሪዎቹ ጭምር የሚገነዘቡት መራራ ሐቅ ነው።
እስክንድርና ማንዴላ የነፃነት ታጋዮች ናቸው።ማንዴላ አፓርታይድን ለመዋጋት ቢያንስ ወታደራዊ ስልጠና በሐገራችን ጭምር እንደወሠዱ ከታሪክ ተገንዝበናል።እስክንድር የጦር መሣርያና የጦር ሠፈርፊትም ይሁን ወደፊት ከእስር ሲወጣ እንደማይረግጥ ስለማውቀው ላረጋግጥ እችላለሁ።የእስክንድር ኡዚ ብዕሩ ነው።ሟቹ ለገሠ ዜናዊ ጥይት በማይበሳው መኪና ታጅቦ ሲጓዝ አናቱን ብሎ ያዞረው ከእስክንድር ቀለም ተፊ ሠላማዊ ኡዚ ብዕሩ የተተኮሰ ህዝባዊ ማዕበል ቀስቃሽ ፅሁፉ ነው።ያሣሠረውም ሙያውና ሕዝባዊ አመለካከቱ ነው።
ከአሜሪካ ቅምጥል ኑሮን ንቆ የመጣው ለውጥ መጥቷል፣በሐገሬ በሙያዬ የበኩሌን ላበርክት ብሎ በመወሰኑ ነበር።ከሃያ ዓመታት በላይ ስርዓቱን በስክሪብቶ ሲፋለም የኖረው።
ማንዴላ ቢባል ኣይበዛበትም።ለሃገሩ ብሎ ያላጣው ነገር የለም።
ነገ እንደ እስክንድር ነጋ አይነት ዜጎች የሐገራችን ተስፋ ይሆናሉ።የነ ስብሐት ነጋ ስርዓት ሲመሽበትና የነብርሃኑ ነጋ ዘመን ሲመጣና እውነተኛ የሚተገበር ህገ መንግስት ሲዘርጋ ህዝቡ የመረጠው ፓርቲ ስልጣን ላይ ሲወጣ የዛሬ ስምንት ዓመት ጥያት ወደወሁባት የአፍሪቃ መዲናይቱ እትብቴ የተቀበረባት እውነተኛዎ ሪፐብሊክ ኦፍ ዴሞክራቲክ ኢትዮጵያ በወጣሁበት ሞያሌ ሳይሆን በቦሌ እገባለሁ።ዘወትር የምጠብቃት ቀን ደሞ ትመጣለች።
ማንዴላ ታሪክ ሰርቶ አልፏል።ኢትዮጵያዊያን የራሣችንን ኤኤንሲ መስርተን በማቆጥቆጥ ላይ ያለውን አፓርታይዳዊ ሥርዓት በህዝባዊ ሱናሚ ኣስወግደን እስክንድርን በፍትሐዊ ምርጫ እንደማንዴላ ለመሪነት ለማብቃትና ቃሊቲ ያሉ ጀግኖቻችንን ነፃ ለማውጣት የማንዴላን ፈልግ እንከተል የሚለው መልዕክቴ በዛሬዋ ዕለት በስደት ከምማቅቅባት ሐገር ይድረሳችሁ ።
ነፍስ ይማር ለታላቁ የአፍሪቃ ብርቅዬ ልጅ ኔልሠን ማንዴላ
ደረጀ በጋሻው
የቀድሞ የአስኳል ጋዜጣ
ዋና አዘጋጅ
ምስራቅ አፍሪቃ

በውጪ ሐገር በስደት ላይ በሚገኘው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው የካምፓላ መካነሰላም መድሃንያለም ቤተክርስትያን በዩጋንዳ የህዳር ሚካዔልን የንግስ በዓል ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አንዳከበሩት በስፍራው የነበረው የፔን ዘ ኢትዮጵያ ዘጋቢ ገለፀ።
ከለሊቱ አስራአንድ ሠዓት ጀምሮ በማህሌት የጀመረው ክብረ በዓል በደብሩ መሪጌታ ይህይስ ዓለሙ ያሬዳዊ ዝማሬ ቀርቧል።<ውእቱ ሚካዔል መልዓከ ኃይለ ልዑል።ውእቱ ልዑለ መንበር ይስአለነ……>
በዕለቱ ቅዳሤ በርካታ ምዕመናን የታደሙ ሲሆን ከማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አስራ ስምንት ከቁጥር አስራአምስት እስከ ሃያ አንድ በቆሞስ አባ ኃይለማርያም ተነቧል። ስርዓተ ቁርባን ከተከናወነ በኋላም በቆሞስ አባ አብዩ የዕለቱን በዓል በማስመልከት ኦሪት ዘፀአት ምዕራፍ አስራ አራት ከቁጥር አስራ ዘጠኝ ጀምሮ ያለውን ቃል በተመለከተ የወንጌል ማዕድ ቀርቧል።
የቅዳሤ ስርዓቱ እንዳበቃም ታቦተ ህጉ በካህናትና ምዕመናን ታጅቦ በክብርና በምስጋና ዜማ ታጅቦ በአውደ ምህረቱ ላይ መሪጌታ ይህይስ <አንተኑ ሚካዔል መና ዘአወረድከ።ወአንተኑ ለእስራዔል መና ዘአወረድከ።>በያሬዳዊ ዜማ ወረብ አቅርቧል።
የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ፀሐይ ደስታ በበዓሉ ፍፃሜ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እግዚአብሔር አምላክ እስራዔላዊያንን ከግብፅ የባርነት ቀንበር ነፃ የወጡበትን ዕለት በመዘከር ይህንን ታላቅ በዓል ቤተክርስትያን በድምቀት እንደምታከብረውና በዓሉ የስደተኞች በዓል ሊባል እንደሚችል ጠቁመው ስደተኞች ሁላችን እግዚአብሔር አምላክ እስራዔላዊያንን ከግብፅ የፈርዖን አገዛዝ እንዳዳናቸው ሁሉ እኛንም ለሐገራችን ያብቃን ሲሉ ቃለ ምዕዳን ሰጥተዎል።
በመጨረሻም የአምልኮ ነፃነት በተረጋገጠባት ዩጋንዳ ኤርትራዊያንና ኢትዮጵያዊያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የፖለቲካ ድንበር ሣያግዳቸው በአንድ ደብር ፈጣሪያቸውን ሲያመሠግኑ የዚህ ዜና ዘጋቢ ተመልክቷል።
Pen Ethiopian

የፊታችን ዕሁድ ፆመ ነቢያት ይጀመራል።የገና ፆምን ለመፆም ተዘጋጅተዎል?ዘንድሮ ፆም ለነፍስ ብቻ ሣይሆን ለስጋም ጠቃሚ እየሆነ ነውና ሀኪም ቀይ አብርቶ በስጋ ምክንያት ሥጋት ላይ መሆንዎን ሣያረዳዎ በንስሃ አባትዎ ምክር ፆሚ ይሁኑ።
ቢፆሙ ሸንቃጣ ይሆናሉ።ስጋዎ ፈተና ላይ አይወድቅም።መንፈስዎ ይረጋጋል።ባይፆሙ ኪሎዎ ይጨምራል።ከሀኪም ፊት አይርቁም።ቁና ቁና ይተነፍሣሉ።ወጪዎ ይጨምራል።አልጋና ብልግና ሊያዘወትሩ ይችላሉ።
ኪስዎ ከመጀመርያው ፆሚ ከሆነ የኔ ምክር እርስዎን አይመለከትምና ዘና ይበሉ።ፆም ሲፆሙ ሆድዎን ብቻ ማዕቀብ አይጣሉበት። ምላስዎን አደብ አስገዟት።ዓይንዎን ከዳሌና ጭን ላይ ይንቀሉ።ጆሮዎ የአመት ረፍት ያስወጡት።እግርዎ አይንጦልጦል።ያኔ የወጣልዎ ምርጥ ፆሚ ይሆናሉ።አንድ ነገር ረሣሁ።በልብዎ ግርግዳ ያከማቹትን የቂምና የጥላቻ ዶሴ ፈጥነው ይደልዙ።ልብዎ በቂም ኔትወርክ ተጨናንቆ ወደ ፈጣሪዎ የሚያደርጉት ማንኛውም ጥሪ አይሠማምና ውዝፍ ሂሣብዎን ያወራርዱ።ያኔ የገናን ፆም ለመፆም ሚኒማውን ያሟላሉ።
ዕሁድ ጧት ቸርች ሲመጡ ልብስዎ ብቻ ሣይሆን ልብዎም ፀዳ ብሎ ይምጣ።እኔ እንዲህ ብያለሁ ።እርስዎስ??
አክሊለ ሠማያት ዘ መካነ ሠላም

ምነው ሰቆቃችን በዛ?
ሐገር እንደሌለው በዋዛ።
ለውጡ ሆኖብን ከድጡ ወደማጡ
ስንቶች ሐገራቸውን ጥለው ወጡ?
ብልሹ አገዛዝ ነግሶብን
ኢትዮጵያዊያን ተዋረድን።
ያዋረድን ግን ወያኔ ነው
ዓይን እያለሁ የማያየው
ጆሮ እያለው የማይሰማው።
ሴቶቻችን ሲደፈሩ ክብራችን ሲንኮታኮት
ኢቲቪ የወያኔ የውሸት ቋት።
አንቺ ያልታደልሽ ሐገር
አኬልዳማ የደም ምድር።
አምላክ ሆይ እንባችንን አብስና
ገላግለን ከዚህ ዘመን ፍጠንና
ሐገር እያለን እንደሌለን
በጣም እናሣዝናለን።
በርጉማን እየተመራን እስከመቼ
በሣውዲ እያለቁ ወገኖቼ
ዱሮ ግንደበረት የቀረው
ሣውዲ ላይ ባርነታችን የነገሠው
በወያኔ የተነሣ ነው።
ለአፍሪካ የምትተርፍ ሐገር
እንዲህ ሆና ስትቀር?
ጌታ ሆይ ገላግለን ከእዬዬ
መሪ ስጠንና እንደ እምዬ።
*በሣውዲ መከራ ላይ ለወደቁ ወገኖቼ መታሠቢያ
18/11/2013
penethiopian

በዩጋንዳ ለምትኖሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ!!!
በሳውዲ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍና ሰቆቃ በማውገዝ የሳውዲ መንግስት ለዓለም አቀፉ የሠብዓዊ መብቶች መከበር የፈረመውን ስምምነት እንዲያከብርና ዜጎቻችን ላይ እያደረሠ ያለውን ኢሞራላዊ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲያቆምና ለሠው ልጆች ሰብዓዊነት እንዲያሳይ ለመጠየቅና በቀጣይ በምስራቅ አፍሪካ ያለውን የስደተኞች ሁኔታ ለመምከር የወገኖቻችን መከራና ስቃይ ነግ በኔ ሊሆን ይችላል ብሎ በማሠብ በአንድነት ሆነን ለመምከር አንዳንድ ቅድመ ዝግጅቶች ለማድረግ ከጎናችን እንዲቆሙ እንጠይቃለን።
ቀጣይ እንቅስቃሴያችንን በ<efjaehrco>ፌስ ቡክ ላይ ማስታወቅያችንን ይከታተሉ።
በህዝባዊ ተቃውሞ ለመሣተፍ በ<[email protected]>ይመዝገቡ።
በዩጋንዳ ነግ በኔ የወገን ለወገን ደራሽ የጋራ ድምፅ አስተባባሪ ኮሚቴ
[email protected]>

ዩጋንዳ ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በሕይወት አለ?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ካምፓላን ማዳረስ ኣያስፈልግም።የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሚሊኒየሙ አከባበር ግዜ ነበረ። ከዛ ተሽመደመደ።ጁላይ ኢለቨን ካምፖላ በአልሻባብ አጥፍቶ ጠፊዎች አሰቃቂ ፍንዳታ በደረሠ ግዜ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አለሁ ብሎ ሲሯሯጥ ታየ።ከዛ በኋላ ነበር ኖቬምበር አስራአራት ቀን ሁለት ሺ አስር የኢትዮጵያ ኮሚኒቲን
ኖቬምበር አስራአራት ከሚሊኒየሙ በፊትና በኋላ ኮሚኒቲው ያከናወናቸውን ተግባራት የሚያትት ዝርዝር የስራና የሂሣብ ሪፖርት ቀርቦ የነበረው።ለአንድ ዓመት ያህልም በወገኖች ድጋፍ ቢሮ እስከመክፈትና የአባልነት መታወቅያም ለማህበረሠቡ አዳርሶ ነበር።ኮሚኒቲው በወቅቱ ያሣየው ፍጥነት የወያኔን ወኪሎች አስግቶአቸው ይሁን ወይም በሌላ ምክንት ቢሮውም ተዘጋ ፣አመራሩም ላይገናኙ የተማማሉ መሠለ።ከወያኔ ቆንስላ ሃላፊዎች ጋርም ምስጢራዊ ስብሰባ የተወሰኑ የኮሚኒቲው አመራሮች አደረጉ የሚል ወሬ ተሠማ።ያኔ ኮሚኒቲው ተሸረሸረ።
ዩጋንዳ ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መተዳደርያ ደንቡ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ አባል መሆን እንደሚችል ስለሚገልፅ የወያኔ ቆንስላ ሠራተኞች ካሣደዱዋቸው የፖለቲካ ስደተኞች ጋር የአንድ ኮሚኒቲ አባል ለመሆን ሲመዘገቡ ታይተዋል።በየትኛውም ስፍራ የፅዋ ማህበርም ቢሆን ወያኔዋቹ በይፉም ሆነ በህቡህ ያን ማህበር ካልተቀላቀሉ፣
አልያም ካላፈረሱና ወይም በነሡ ሣንባ የሚተነፍስ ተለጣፊ ካልመሠረቱ ሞታቸው ነው።
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በዩጋንዳ ዛሬ ስሙ ከመኖሩ ባሻገር ተሽመድምዶ ያለው ፖሊዮ ይዞት አይደለም።የኮሚኒቲው አመራሮች የያዙትን ቦታ ለመልቀቅ ፈቃደኝነት ያላቸውም አይመስልም።የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ከሚሊኒየሙ በፊትም ሆነ በኋላ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሚያደርጋቸውን ተግባራት በቅርበት ያውቃል።እንደዜጋም አቅሙ የፈቀደውን በማድረግ በወያኔ ቆንስላ ጥቁር መዝገብ በጠላትነት ተፈርጆ እንደሚገኝ የካምፓላ ሰማይ የሚያውቀው ዕውነታ ነው።
ወያኔ የሚሊኒየሙን በዓል በሱ ፊታውራሪነት ካምፓላ ላይ ለማክበር ሲሯሯጥ በወቅቱ ወያኔ ንፁሀንን እስር ቤት አጉሮ በዓሉን በጋራ እንድናከብር ሊያግባባና ሊያስፈራራ ሲሞክር የታሠሩት ይፈቱ፣ብሔራዊ ዕርቅ ይደረግ ብለን የተወሰንን ወገኖች በመናገራችንና ሚሊኒየሙን ያለወያኔ ተሣትፎ በደመቀ ሁኔታ በማሣለፋችን ነበረ የወያኔ ጥርስ ውስጥ የገባነው።
ባለፉት ሦሥት አመታት የወያኔ ቆንስላ ዩጋንዳ ካምፖላ ላይ እውነተኛ የፖለቲካ ስደተኞችንን በማሳደድ፣በማሠለልና መፈናፈኛ በማሳጣት ሕብረተሠቡን በዘር እስከማደራጀት ሠርቷል።
ኮሚኒቲውን አሽመድምዷል።ከአመራሩ የተወሠኑትን ፖስፖርት በመስጠት ከስደተኛነት አላቋል።የወያኔ ቆንስላ ቤተኛ የሆኑም እንዳሉ የአደባባይ ሚስጥር ነው።
በርካታ ወገኖች ኮሚኒቲው ባይቀበርም እንደሞተ ያምናሉ።እንደገና ለማጠናከርም ቢሞከር አሁን ካሉት የአመራር አባላት መካከል ከወያኔ ጋር በግልፅም ይሁን ውስጥ ለውስጥ የሚሞዳሞዱትን ለይቶ ለማውጣት አስቸጋሪ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።
ከሁለት ዓመት በፊት በሕጋዊው ሲኖዶስ የሚመራውን የካምፖላ መካነ ሠላም መድሐንያለም ቤተክርስትያን የወያኔ ቆንስላ ካህናትና፣ ዲያቆናት እንዲሁም መዘምራንን በስውር አደራጅቶ ያካሄደው ትርምስ በእውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ከከሸፈና የአመፁ መሪ የነበሩት የቀድሞ አስተዳዳሪ የስደተኛ እስታተሳቸውን ወርውረው በወያኔ ፖስፖርት የአምስት ኪሎውን ቤተክህነት ከተቀላቀሉ ወዲህ ነገሮች እየጠሩ መጥተዎል።
ካምፖላ ላይ የፖለቲካ ስደተኛ መታወቅያ በደረታቸው ፣የወያኔ አክቲቭ ፓስፖርት ትራሳቸው ስር ሸጉጠው ትክክለኛ ስደተኞችን የሚሠልሉና ለአደጋ የሚያጋልጡትን ሆድ አደሮች ለማጋለጥ በዩጋንዳ የሚኖሩ ስደተኞች ለህልውናቸው ሲሉ በህብረት ሊቆሙ ይገባል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጥቂት የፖለቲካ ስደተኞች ስደተኛውን ብቻ ያቀፈ የስደተኞች ማህበር ለመመስረት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ሲሆን ለስደተኛው መብት መከበር የሚሠራ ከማናቸውም የፖለቲካ ሃይሎች ተፅዕኖ ነፃ የሆነ ማህበር ለመመስረት የበኩሌን እገዛ ሳደርግ ብቆይም ለደህንነቴ ስጋት የሚፈጥሩ ሁኔታዎች በመፈጠራቸው ከማናቸውም ማህበረሠቡን ከሚመለከቱ ጉዳዮችራሴን አግልዬ እንደምገኝ ለመጠቆም እወዳለሁ።በተቻለ አቅም ስደተኛው የራሱን ማህበር ከወያኔ ሠርጎ ገቦች እንዲጠብቅ አሳስባለሁ።
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ እስከዛሬ የታመሙትን ወገን በማስተባበር ለማሣከም ያደረገው መልካም ተግባር ፣
የሟች ወገኖችን አስከሬን ከቤተሠብ ጋር መክሮ ለሐገራቸው አፈር እንዲበቁ በመስራቱ፣ምስኪን ስደተኞች ሲሞቱ በመቅበር የሠራውን ስራ በመዘከር ወደ ወያኔ ጉያ የተሸጎጠውና ፖራላይዝዱ ኮሚኒቲ እኔም ልክ የዛሬ ሦሥት አመት በተከናወነው የማሟያ ምርጫ የቦርድ አባል ሆኜ እስከዛሬ መቆየቴን እየጠቆምኩ በመላ ዓለም የምትገኙ ኮሚኒቲዎች ልምዳችሁን እንድታካፍሉኝ እንደ አንድ ዩጋንዳ ላይ በሚኖር ሐገር አልባ ስደተኛ በአክብሮት እጠይቃለሁ።
ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ሁሉ ፀሀፊው በንፁህ ህሊና እውነቱን ብቻ ለመግለፅ ህሊናው ዝግጁ መሆኑን ይጠቁማል።
ጋዜጠኛ ደረጀ በጋሻው
ከኮሚኒቲው ቦርድ አባላት አንዱ

የቀጣፊዎቹ ልሣን የሆነው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ትናንት ማታ በመስኮቱ ሦስት ሆዳም የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማህበር አመራሮች አቅርቦ ነበር።ሦስቱ ሆድ አደሮች በበረከትና በሺቀጥል ከማል ተጠፍጥፈው የተሠሩ የጋዜጠኞች ማህበር መሆናቸው ነው።
ኢነጋማ አባላቱና አመራሩ ተጠራርገው ከሐገር ከተባረሩበት የጥቅምቱ መሬት አንቀጥቅጥ ሕዝባዊ ማዕበል በአግአዚ ጭፍጨፋ ከከሸፈ ወዲህ የነበረከት ስሪቶቹ በቀቀኖች አይናቸውን በጨው አጥበው ዕአንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የኢትዮጵያን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው ዕዕሲሉ ለፈጣሪዎቻቸው ታማኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
ጋዜጠኛ ባንዳ ሆኖ ህሊናውን ሲያመክን ማየት እንዴት ያሣዝናል፧
በእስክንድር፣በርዕዬትና በውብሸት ኮራሁ።በአብርሐም፣በወንደሠንና በመሠረት አታላይ አፈርኩ።ሦሥቱም አታላዮች መሆናቸው ነው።ያታለሉት ግን ራሣቸውን ነው።ህሊናቸውን ነው።
የሐገራችን ሚዲያ መቃብር ከወረደ ስምንተኛ ዓመቱን በምንዘክርበት በአሁኑ ወቅት ጋዜጠኞችን አሸባሪ እያለች ዘብጥያ የምትወረውር ሐገር ውስጥ የአፍሪካ ሚዲያ መሪዎች መድረክ በመባል የሚታወቀው አኅጉር አቀፍ የሚዲያ ባለድርሻዎች የውይይት መድረክ ስድስተኛ ጉባዔውን ሲያከናውን በመለስ ዜናዊ ሚስጥራዊ መመርያና የተፈቀደ በጀት አማረ አረጋዊ ባለ ቀይ ጃኖው የሪፖርተር ጋዜጣ አሣታሚና የ ኤም ሲ ሲ ባለቤት እንዳለውዕየአፍሪካ ሚዲያ መሠረታዊ ችግሮች ሁለት ነጥቦችን አንስቷል፡፡ በዋናነት የጠቀሱት የሚዲያ ተቋማቱ አቅም ማነስና የሚዲያ ነፃነት ችግሮች መሆናቸውን፣ ሌላኛው ደግሞ የውጭ አገሮች አድልኦና ፍላጐት ነው ፡፡ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርም ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ቢሆንም፣ ነገር ግን በሰፊው እየተዘገበ ያለው ስለኢትዮጵያ ብቻ ነው ዕአማረ አረጋዊ ዕበኢትዮጵያ የሚዲያ ነፃነት ችግር ቢኖርምዕሲሉ መናገራቸው የግሉ ፕሬስ የነፃነት ችግር እንዳለበት ከመሸም ቢሆን ያመኑ ይመስላል።
በቀጣይ ልጅ ደመቀ መኮንን አሉት እንደተባለው ጋዜጠኞቹ በሙያቸው ምክንያት አለመታሰራቸውን ገልጸዋል፡፡

ዕጋዜጠኞቹ በተግባር በሽብር እንቅስቃሴ ውስጥ ተገኝተዋል ለዚህም ተገቢውን ሕጋዊ ሥርዓት የተከተለ ዕርምጃ ተወስዶባቸዋል፤ዕዕ

ዕኢትዮጵያ ካለችበት ቀጣና አንፃር የሽብር እንቅስቃሴ ዋነኛ ሥጋቷ ነው፡፡ በመሆኑም መንግሥት የህልውና ጉዳይ አድርጐ ይመለከተዋል፤ዕ ብለዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው በማለት አስረድተዋል፡፡
ዕበጋዜጣዊ የሙያ ተግባሩ የተከሰሰ አንድ ግለሰብ ብቻ ነው።ዕያሉት ጋዜጠኛ ስሙ ማን ይሆን፧በረከት ለምን ይህን ተናገሩ ብሎ እንደማይቆጣዎ ተስፋ እናድርግ፧ተላላኪው ቢሆኑም ቅሉ።
የኬንያው ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣በወርቃማ ቃላት ይህን ብለዋል። ዕሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ጋዜጠኞችን ማሰርና መቅጣት ኋላ ቀር የሆነ አስተሳሰብ ነው፤ዕ ሲሉ ገልጸውታል፡፡

የሚዲያ ነፃነት በኬንያ መሠረቱ እንዲስፋፋ መንግሥታቸው የሚያምን መሆኑን የሚናገሩት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ይህንን የሚያደርጉት ለሚዲያ ተቋማቱ ሲባል ብቻ ሳይሆን ኬንያውያን ሥልጣን ላይ ያስቀመጧቸው መሪዎች እንዴት እያስተዳደሯቸው እንደሆነ የማወቅ መብት ስላላቸውና ስለሚገባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አንዳንድ የጉባዔው ተሳታፊዎች የአኅጉሪቱ የፖለቲካ አመራሮች ወይም መንግሥታት የሥልጣን ቆይታቸውን ለማራዘም የአኅጉሪቱ የሚዲያ ነፃነትን በሚያወጧቸው የተለያዩ አፋኝ ሕጐች ገድበዋል፡፡ የሚዲያ ባለሙያዎችም በእነዚህ ሕጐች ሰለባ ሆነዋል በማለት ጋዜጠኞች ተከራክረዋል፡፡ በርካቶችም ሙያዊ ተግባራቸውን በመወጣታቸው ሕይወታቸውን እስከማጣት ደርሰዋል በማለት በውይይቱ የተሳተፉ ጋዜጠኞችና የመስኩ ባለሙያዎች የአኅጉሪቱን የፖለቲካ አመራሮች ወቅሰዋል፡፡ ተሳታፊዎቹ የሚዲያ ባለሙያዎች ባገኟቸው አጋጣሚዎች ሁሉ በሙያቸው ምክንያት በርካታ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እስር ቤት እንደሚገኙ በማሳያነት ይጠቅሳሉ፡፡
ይህን የመሠለ መድረክ መዝጊያ ላይ ነው የነበረከት በቀቀኖች ዕበኢትዮጵያ አንድም ጋዜጠኛ በሙያው ምክንያት አልታሠረም።የምዕራቡ ሚዲያ የሐገራችንን ሚዲያ ገፅታ አለአግባብ እየኮነነ ነው።የኢትዮጵያ ሚዲያ ነፃ ነው።ዕየሚሉን።

ህሊና ከሌላቸው ሆዳምና አድርባይ ጋዜጠኞች ይሠውረን።

ፔን ዘ ኢትዮጵያ

ለሸገር ልጆች፦፦፦
የድሮ አራዶች እነ ድንጋይ ኳሱ
ቦርቸሌን ከርቸሌን በደንብ ያዳረሱ።
ለወሬ ነጋሪ ካሉ የተረፉ፧
ምን አለ ቢያወጉን፧ምን አለ ቢጽፉ፧
ያዲሳባ ልጆች አብሮ አደጎቼ፣
በናፍቆት ባዘኑ እያነቡ አይኖቼ።
ድንገት ሣናስበው እንደተለያየን፣
በሞያሌ ሾልከን በቦሌ እንገባለን፣
አይቀርም አንድ ቀን፦እናወራዋለን፣
በአመቺው ዘዴ እንተርከዋለን፣
ዕድሜና ጤናውን አምላክ ካልነፈገን።፧
ሁል ግዜ ድሪሜ፣
የዘወትር ህልሜ፣
እንዳይነፍገን ዕድሜ።
እስከምንገናኝ በአካል በዐይነ ስጋ፣
ፌስ ቡክ ያገናኘን እርሱም እስኪዘጋ።
*ድንገት ለተለያየነው አብሮ አደጎቼና ወዳጆቼ ሁሉ መታሠቢያ ተፃፈ።
ተዱ ዘአራዳ ከዩጋንዳ