መስከረም ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የታዋቂዋ አርቲስት የቀብር ስነስርዓት በ ቅድስ ስላሴ ካቴደራል ወዳጅ ዘመዶቿና አድናቂዎቿ በተገኙበት ተፈጽሟል። አርቲስት ሰብለ ተፈራ በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ወሎ ሰፈር እየተባለ በሚጠራው አይቤክስ ሆቴል አካባቢ በግንቦት ወር 1968 ዓም. የተወለደች ሲሆን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በንፋስ ስልክ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቃለች። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷንም በዛው …

መስከረም ፬ (አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ታጋይ መኮንን ተስፋዬ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት ድርጅቱ ከሚያዚያ እስከ ነሃሴ በነበሩት ወራት ከታች እስከ ላይ የ7 ዓመታት ግምገማ አድርጓል። የሞላ አመራር “ትህዴንን ወደ ድል አላበቃውም ይቀየር” የሚል ጥያቄ በመላ ሰራዊት አባላት መነሳቱን የተነገሩት ምክትል አዛዡ፣ ሞላ አስጎደም አገርህን አድን ከሚለው አዲስ ጥምረት መመስረት ጋር …

መስከረም ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ትህዴን፣ የቀድሞው የድርጅቱ መሪ ሞላ አስገዶም የተወሰኑ ተከታዮቹን በመያዝ በሱዳን በኩል አድርጎ ኢትዮጵያ መግባቱን ተከትሎ በሰጠው መግለጫ ” የተወሰኑ በትግሉ የቆዩና ግላዊ ጥቅማቸው የተነካባቸው ግለሰቦች ትግሉን ባሻቸው መንገድ ሊጠመዝዙት ስላልቻሉና በአብዛናው ታጋይ በመድረክ ተይዘው መፈናፈና ስላጡ ተስፋ ቆርጠው ከትግሉ ጎራ ሸስተዋል” ብሎአል። ንቅናቄው …

የባለፈው ሣምንት በኤርትራ የጋራ ንቅናቄ ከመሠረቱት አራት በትጥቅ ትግል የተሠማሩ ንቅናቄዎች የአንደኛው የትግራይ ሕዝብ የጋራ ንቅናቄ መሪ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸው ተገልጿል፡፡

የግብፅ ፖፕ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ለመስቀል በዓል አዲስ አበባ ይገባሉ

የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፖፕና ፓትርያርክ ቴዎድሮስ ዳግማዊ በመስቀል በዓል አከባበር ላይ ለመታደምና የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ፣ መስከረም 15 ቀን 2008 ዓ.ም. አዲስ አበባ ይገባሉ፡፡

የኮፕቲክ ፓትርያርክ ቴዎድሮስ አራት ቀናት በሚወስደው ቆይታቸው መስከረም 16 ቀን 2008 ዓ.ም. የሚከበረውን የመስቀል ደመራ በዓል ላይ ከመታደማቸው በተጨማሪ፣ ወደ አክሱምና ላሊበላ አቅንተው ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ሥፍራዎችን እንደሚጎበኙም ታውቋል፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪም በሚኖራቸው ቆይታ በአዲስ አበባ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላትን፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ከታዋቂ ግለሰቦች ጋር እንደሚነጋገሩ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ከፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመና ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ፣ እስካሁን ግን የተረጋገጠ ነገር አለመኖሩን አክለው አብራርተዋል፡፡  

ፓትሪያርኩ የአዲስ አበባ ጉዟቸውን አስመልክቶ ከሳምንት በፊት ከግብፅ የውኃ ሀብት ሚኒስትር ሆሳም አል ሞጋሃዚ ጋር መነጋገራቸው የተዘገበ ሲሆን፣ በውይይታቸውም ወቅት ግብፅ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ጥያቄዎች አንስተው ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ከአቡነ ማትያስ ጋር ውይይት እንዲያደርጉ ሚኒስትሩ መጠየቃቸውና የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ተዘግቧል፡፡ 

ፖፕ ቴዎድሮስ በበኩላቸው ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ሁለቱ ቤተ ክርስቲያናት ባላቸው ታሪካዊ ግንኙነት የተነሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዚህ ረገድ እየተባበሯቸው እንደሆነና አስተዋጽአቸውም ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል በማለት ስታር አፍሪካ የተሰኘ ድረ ገጽ ላይ የወጣ ዘገባ ያትታል፡፡

የኢትዮጵያ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ባለፈው ጥር ወር ግብፅን ለስድስት ቀናት በይፋ በጎበኙበትና በካይሮ ፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግሥት ከፕሬዚዳንት አልሲሲ ጋር በተወያዩበት ወቅት፣ ፕሬዚዳንቱ የዓባይ ወንዝ ለኢትዮጵያውያን የልማት ምንጭ ቢሆንም ለግብፅ ግን ልማት ብቻ ሳይሆን የደም ሥር መሆኑን መናገራቸው ይታወሳል፡፡ 

አቡነ ማትያስም በበኩላቸው በጠንካራ ትስስር ላይ የተመሠረተው የሁለቱ አገሮች ግንኙነት፣ ከዓባይ የሚመነጭ ውኃ የማያቋርጥ የጋራ ሀብት በመሆኑ በፍትሐዊነትና በእኩልነት ተጠቃሚ የሚኮንበት ይሆናል ማለታቸውም አይዘነጋም፡፡ 

ፖፕ ቴዎድሮስ ዳግማዊ እ.ኤ.አ. በ1952 ማንሱራ በተሰኘ የግብፅ ከተማ የተወለዱ ሲሆን፣ በ1975 ከኤሌክሳንዳርያ ዩኒቨርሲቲ በፋርማሲ የመጀመሪያ ዲግሪ አግኝተዋል፡፡ ለጥቂት ዓመታት በመንግሥት ቁጥጥር ሥር የሚገኝ መድኃኒት ፋብሪካን ከአስተዳደሩ በኋላ፣ ቅዱስ ፒስሆግ የተባለ ገዳም በመግባት የሥነ መለኮት ትምህርት በማጥናት እ.ኤ.አ. በ1989 ተመርቀዋል፡፡ 

የአቡነ ሺኖዳ ሕልፈተ ሕይወትን ተከትሎ በአሁኑ ወቅት 118ኛው የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን ከሦስት ዓመት ወዲህ በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡   

 

 

ሄሊኮፕተራችንስ መቸ ነው የምትመለሰው ?? (አሌክስ አብርሃም) ባለፈው ግምቱ ከ30 ሚሊየን ዶላር በላይ የሚያወጣ የኢትዮጲያን የጦር ሄሊኮፕተር ይዘው ኤርትራ ገቡ የተባሉት ‹‹ከሃዲው››አብራሪና ረዳት አብራሪዎች …. ከብሔራዊ የመረጃና የደህንነት አገልግሎት እና ከፌዴራል ፖሊስ የጋራ ፀረ ሽብር ግብር ሀይል ‹‹የተሰጣቸውን ተልእኮ›› ሲጨርሱ …

ሄሊኮፕተራችንስ መቸ ነው የምትመለሰው ?? (አሌክስ አብርሃም) Read more »

Minilik Salsawi :- የደምሕት ታጋይ ሞላ አስገዶምን ተከትሎ ብዙ የኮካዎች ውሮሸባ የቀወሱ ሃሳቦች የስም ማጥፋቶች የተበሳጩ ኪሳራዎች የደቀቁ የተልፈሰፈሱ ዲያስፖራዎች የእርስ በእርስ ግልምጫዎች እና ዘለፋዎች አሳፋሪ ዘመቻዎች እና ፍረጃዎች ወዘተ ያላነበብነው ነገር የለም::እውነት ከማይዋጥላቸው ድንጉጥ ያልበሰሉ ፖለቲከኞች ጀምሮ ኪሳራ የተከናነቡ …

መንግስታዊ ውዥንብር – የአረና ሰዎች ሽርጉድ – የመንደርተኝነት አጀንዳ ድምዳሜው (ምንሊክ ሳልሳዊ‬) Read more »

  የአርቲስት ሰብለ ተፈራ የቀብር ስነሥርዓት ብዙ ሺህ አድናቂዎቿ እና ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተፈጸመ::ባለቤቷ የሚያሽከረክረው መኪና ከቆመ መኪና ጋር ተላትሞ የአርቲስቷ ሕይወት በአዲሱ ዓመት ያለፈ ሲሆን ባለቤቷ ሞገስ ተስፋዬ ላለፉት 3 ቀናት እስር …

የአርቲስት ሰብለ ተፈራ የቀብር ስነሥርዓት ተፈጸመ ::ባለቤቷ ሞገስ ተስፋዬ በ15 ሺ ብር ዋስ ተለቀቀ:: Read more »

ከመግለጫው በስተጀርባ ጌታቸው ሺፈራው የትህዴን ሊቀመንበር የነበሩት አቶ ሞላ አስግዶም ከኤርትራ መውጣታቸውን ተከትሎ በህወሓት/ኢህአዴግ እና በተቃዋሚዎች በኩል ያልተጠበቁ ስሜቶች ተስተናግደዋል፡፡ ከተቃዋሚዎች በላይ ግን ራሱ ስርዓቱና ደጋፊዎች በክስተቱ ስሜታዊ ሆነው፡፡ ለዚህም በስርዓቱ ደጋፊ ሚዲያዎችና በደህንነት ተቋሙ እየተላለፉ ያሉትን መረጃዎች ማየት በቂ …

የሻዕቢያ ተላላኪ ሲላቸው የነበሩትን ሰው በአንዴው የራሱ ተላላኪ አድርጓቸዋል፡፡ ከመግለጫው በስተጀርባ ጌታቸው ሺፈራው Read more »

    በአለማየሁ አንበሴ የፍቅር አዲስ – “ምስክር” ታዋቂዋ ድምፃዊት ፍቅር አዲስ ነቃጥበብ፤እንደ ብዙዎቹ ድምጻውያን ሁሉ ለብዙ ዓመታት ድምጽዋን ሳንሰማ ቆይተናል፡፡ 2007 ዓ.ም ሊሰናበት ጥቂት ቀናት ሲቀሩትና አዲሱ ዓመት ለመጥባት እየተሽኮረመመ ሲጠባበቅ እሷ በመሃል 8ኛ የዘፈን አልበሟን ይዛ ከተፍ አለች፡፡  …

ፍቅር አዲስ ነቃጥበብ ስምንተኛ አልበሟን አውጥታለች Read more »

አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ባሻቸው መንገድ ሊጠመዝዙት ስላልቻሉ ከትግሉ ጎራ ሸሽተዋል። – (አስመራ የሚገኘው ትህዴን) #Ethiopia #MinilikSalsawi አስመራ የሚገኘው ትህዴን መግለጫ አወጣ – “የሸሹት የግል ጥቅማቸው የቀረባቸው ናቸው” – ከትህዴን የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ድርጅታችን ትህዴን በየካቲት 1993 ዓ/ም ብረት አንስቶ …

አቶ ሞላ አስገዶም ትግሉን ባሻቸው መንገድ ሊጠመዝዙት ስላልቻሉ ከትግሉ ጎራ ሸሽተዋል። (አስመራ የሚገኘው ትህዴን) Read more »

ድርጅቱ ችግሩን ቀርፌያለሁ ይላል

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የክፍያ ሥርዓት ችግር እንደገጠመው ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅት በበኩሉ ችግር ተፈጥሮ እንደነበር አምኖ በአሁኑ ወቅት መቀረፉን ገልጿል፡፡ 

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅቱ ማዕከላዊ የክፍያ ሥርዓት (ቢሊንግ ሲስተም) ከሁለት ወራት በፊት በገጠመው ችግር ሳቢያ፣ የደንበኞችን ወርኃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ ለሁሉ ለተባለው የተቀናጀ የአገልግሎት መክፈያ ማዕከል መላክ እንዳልተቻለ ምንጮች ይገልጻሉ፡፡ 

ደንበኞች ወደ ክፍያ ለሁሉ በሚሄዱበት ጊዜም ትክክለኛ መረጃ እንደማይነገራቸውና በሌላ ጊዜ እንዲመጡ ብቻ እንደሚገልጹላቸው ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ 

ጉዳዩን በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የክፍያ ለሁሉ የሥራ ኃላፊዎች የተፈጠረው ችግር እነሱን እንደማይመለከት ይገልጻሉ፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሚሰጠን የደንበኞች ወርኃዊ ፍጆታ መረጃ መሠረት ደንበኞችን ማስከፈል ነው ሥራችን፡፡ መረጃ ካልደረሰን ማስከፈል አንችልም፤›› ብለዋል፡፡ 

በመሆኑም ጉዳዩ የበለጠ የሚመለከተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በዚሁ መሠረት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅት የውጭ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ገብረ እግዚአብሔር ታፈረ ተጠይቀው ችግሩ ተፈጥሮ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ 

የማዕከላዊ የክፍያ ሥርዓት ሰርቨር የመረጃ ካርድ በመቃጠሉ ምክንያት ችግሩ እንደተፈጠረ የተናገሩት የውጭ ግንኙነት ኃላፊው፣ ካርዱ በአገር ውስጥ ስለማይገኝና ከውጭ ተገዝቶ እስኪገባ ድረስ የሐምሌ ወር የኤሌክትሪክ ፍጆታን ደንበኞች ማለትም ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚዎች ከሆኑ ድርጅቶች በስተቀር መክፈል አለመቻላቸውን አስረድተዋል፡፡ 

በአሁኑ ወቅት ግን ችግሩ የተቀረፈ በመሆኑ የሐምሌ ወር የክፍያ ቢል መውጣቱንና ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ ደንበኞች የነሐሴ ወር ፍጆታቸውን መክፈል እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡ 

የቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ለሁለት በመክፈል በ64.7 ቢሊዮን ብር የተፈቀደ ካፒታልና በ16.2 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል የተቋቋመው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ማኔጅመንት ፓወር ግሪድ ኮርፖሬሽን ለተባለ የህንድ ኩባንያ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ 

ኩባንያው ዘመናዊ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎትን በመስጠት ደንበኞችን ማርካት ዋነኛ ኃላፊነቱ ሲሆን፣ መንግሥት ለሁለት ዓመት 16.7 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል የሰጠው የማኔጅመንት ኮንትራት ነሐሴ 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ተጠናቋል፡፡ 

 

በያሬድ ቁምቢና ውብዓለም ተስፋዬ የአዲስ አመት ዋዜማ ጳጉሜ 5 ቱሉ ዲምቱ አቃቂ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ‹የመዳን ቀን ዛሬ ነው› እና‹ የጅራፍ ንቅሳት› የተሰኙ ሁለት የራሷን ግጥሞች አቅርባለች፡፡ ገና በስራዋ ስትታይ ድንቅ የትወና ብቃትና ፈጠራዋ የብዙዎችን ቀልብ መሳብ የቻለች ብርቅዬ ድንቅ አርቲስት ነበረች …ሰብለ ተፈራ፡፡ ፍጹም ባልተጠበቀ እና ድንገተኛ […]

አባቶቻችንን የተማርንባቸውን መድረሳዎች ለመስራት እና እዚህ ለማድረስ ከፍተኛ መስዋእትነት እንደ ከፈሉ ታሪካቸውን ሲነግሩን እና ያለፉትን ስርአቶች ጋር ተናንቀው እዚህ እንዳደረሱት የማይካድ ሃቅ ነው ፡፡ በሀገራችን መስጅዶችና መድረሳዎች ባለፉት ስርአት ደም ፈሶባቸዋል አጥንት ተክስክሶባቸዋል፡፡ መስጅዶችና ኢስላማዊ ትምህርት ቤቶችን እዚህ ለማድረስ በርካታ …

የትግላችን መነሻ ምንድን ነው ? በአሁኑ ሰአት በየ አካባቢያችን ምን እየተከናወነ ነው ? (አብዱረሂም አህመድ:BBN) Read more »

አርቲስት እንድሪስ አህመድ ከ45 አመታት በፊት ነበር በብሄራዊ ቴዓትር ስራ የጀመሩት። ወሎ ክፍለ ሃገር ቢወለዱም ዳንስ የተማሩት በቅጽል ስሙ ውቤ በርሃ ተብሎ በሚታወቀው ደጃች ውቤ ሰፈር ነበር። አርቲስ እንድሪስ አህመድ ቡጊና ትዊስት ከደነሱበት ብሄራዊ ቴዓትር በጡረታ ቢሰናበቱም አሁን በፊልም ትወና ላይ ተሰማርተዋል።

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

በኤርትራ ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረው የትህዴን ጦር በመሪው ሞላ አስገዶም እየተመራ ወደ ኢትዮጵያ ገባ:: #Ethiopia ወያኔ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከ700 በላይ እንደሚሆኑ የተገመተው የደህሚት ጦር ከነ ሙሉ ትጥቁ ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ በሁመራ እና በመተማ አድርጎ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መምጣቱን የፋና …

በኤርትራ ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረው የትህዴን ጦር በመሪው ሞላ አስገዶም እየተመራ ወደ ኢትዮጵያ ገባ:: ወያኔ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። Read more »

ዘረኝነትና ጥላቻ በመንግሥት ደረጃ በሚሰበክበት አገር፣ ድንቁርና እጅግ በተጫናቸው የወያኔ ቱባ ባለሥልጣናት ሕዝብ በሚዘለፍበት፣ ታሪክ ተጣሞ የአንድ ቋንቋ ተናጋሪን የሕብረተሰብ ክፍል በሌላው ላይ ለማነሳሳት ሌት ተቀን የሚደክሙና ጉርጓድ የሚምሱ ቡድኖችና ግለሰቦች ባሉበት አገር፣ ፍርሃትና ጥርጣሬ በነገሱበትና አፈና በበረታበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ አገር እንደ ቴውድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ‹ ያሉ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በማሕበረሰቡ ውስጥ ያላቸው ሚና በዘፈን […]

የገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ አጋር የሆነው የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) ሥራ አስፈጻሚ አባላት መካከል አለመግባባት መፈጠሩ ተሰማ፡፡ በዚህ ምክንያት የክልሉን ቋሚ መስተዳድር መመሥረት እንዳልተቻለ ምንጮች ገልጸዋል፡፡አለመግባባቱ የተፈጠረው አብዴፓንና የአፋር ክልልን ላለፉት 20 ዓመታት ሲመሩ በቆዩት የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ እስማኤል ዓሊ …

በአፋሩ አብዴፓ አመራሮች መካከል የሥልጣን አለመግባባት መፈጠሩ ተሰማ Read more »

የማያበራው የፋና ብሮድካስቲንግ ቅጥፈት …………… በምህረት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው ኡስታዞቻችን እና ወንድሞቻችን በሰሩት ጀብድ ይኮራሉ እንጂ አይፀፀቱም !!! ……………….. አቡ ዳውድ ኡስማን ……………………… ጳጉሜ 6 ቀን 2007 ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በድህረገፁ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች እና ፍትህ ሚኒስተር ለ 238 የሚሆኑ እስረኞች …

የማያበራው የፋና ብሮድካስቲንግ ቅጥፈት (አቡ ዳውድ ኡስማን ) Read more »

ጳጉሜ 4 ቀን 1966 ዓም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከዙፋናቸው እንዲወርዱ በድምፅ ብልጫ ከተወሰነና ቅድመ ዝግጅቶች ከተጠናቀቁ ኋላ የህዝቡን ቁጣ ለመቀስቀስ ይረዳል ከተባሉ ፕሮፖጋንዳዎች ዋነኛው የነበረው ዜና ተላለፈ። ” …በዛሬው እለት የዘመን መለወጫ ለኢትዮጲያ ሕዝብ የማይሆን ተስፋ ማቅረብ አንፈልግም። ምክንያቱም የአንገበገባቸው …

ታሪክን የኋሊት = መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ ም Read more »

ከሰሞኑ በአራት የትጥቅ ወይም ‹‹ ሁለገብ›› የትግል አማራጭ በሚከተሉ የ‹‹ነጻነት ›› ታጋይ ፓርቲዎች መካከል የትብብር ስምምነት ተፈርሞ የ‹‹ምስራች›› ተነግሮን ሳያበቃ ከተባባሪዎቹ የአንዱ /ደምኃት/ ሊቀመንበር ከትግል ሜዳው ‹‹መሸሽ›› ተከትሎ በዚሁ ፌስ ቡክ አምድ ላይ የሚጻፈው እጅግ አከራካሪና መረን የለቀቀ ግልብ ኃሳብ …

ስሜትና ፕሮፖጋንዳናን ከፖለቲካ የመደባለቅ አባዜና አደጋው Girma Bekele Read more »

አስተማማኝ ሰላም የሚመጣው – ግርማ ካሳ አቶ ሞላን በተመለከተ፣ የአገዛዙ ሜዲያዎችም ወሬዉን በሚያስገርም ሁኔታ እያዳመቁት ነው። የአራቱ ድርጅቶች ጥምረት እንደፈረሰም ይናገራሉ”Ginbot-7, Arbegnoch, and DMHIT Merger collapsed leaders and rebel soldiers fleeing from Eritrea” ሲል ትግራይ ኦንላይን አይጋ ደግሞ “Dmhit and …

አስተማማኝ ሰላም የሚመጣው – ግርማ ካሳ Read more »

2007 ለለውጥ ብሎ የተነሳው የለውጥ ሃይል ከትግሉ ተሞክሮዎችን እንደቀሰመ ይታወቃል::ባለፈው አመት ወያኔ ሃይል ተጠቅሞ ከፍተኛ የሆነ ችግር በለውጥ ሃይሉ ላይ ከመፍጠሩም በላይ የጠበበውን የፖለቲካ ምሕዳር ጭራሽ ደፍኖታል::ለውጥ ፈላጊ ሃይሉ ከግድያ ጀምሮ እስር እና ስደትን በሰፊው አስተናግዷል::ወያኔ በስልጣን ላይ ለመቆየት ያል …

የለውጥ ሃይሎች ካለፉት የትግል ተሞክሮዎች መማር ያስፈልገናል:: (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »

አራት በትጥቅ ትግል የሚያምኑ ድርጅቶች፣ የአፋር ድርጅቶች ንቅናቄ፣ የአማራ ሕዝብ ንቅናቄ፣ የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደሚት) እና የግንቦት ሰባት አርበኞች ንቅናቄ ፣ በዚህ ሳምንት ዉስጥ አገር አድን ንቅናቄ በሚል ስያሜ መቀናጀታቸው በስፋት መዘገቡ ይታወሳል። ዶር ብርሃኑ ነጋ የቅንጁት ሊቀመንበር፣ አቶ ሞላ አስግዶም ደግሞ ም/ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል። የአራቱ ድርጅቶች መቀናጀት ይፋ በሆነ በጥቂት ቀናት ዉስጥ ጳጙሜን […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን የጠለፈው ረዳት ፓይለት መኪና ለጨረታ ቀረበች

በጥር 2006 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ጣሊያን ሲበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን ጠልፎ ጄኔቫ ስዊዘርላንድ ያሳረፈው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ ንብረት የሆነች የቤት መኪና በሐራጅ ለጨረታ ቀረበች፡፡ 

የሰሌዳ ቁጥር አአ 2-A32521 መኪና ጨረታ ያቀረበው ዘመን ባንክ ነው፡፡ ረዳት አብራሪው ለመኪና ግዢ ከዘመን ባንክ የተበደረው ብድር ስላልተከፈለው ባንኩ ተሽከርካሪዋን በጨረታ ለመሸጥ መገደዱን አስታውቋል፡፡ 

ባንኩ ተሽከርካሪዋን ለጨረታ ያቀረበው በሐራጅ መነሻ ዋጋ ብር 261,503.37 ነው፡፡ ጨረታው የሚካሄደው በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም. ነው፡፡ ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን መኪናዋን የገዛው ከአውሮፕላን መጥለፉ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ኃይለ መድኅን ስዊዘርላንድ ውስጥ የፖለቲካ ጥገኝነት ቢጠይቅም የአገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎት ፍርድ ቤት አንድ ጊዜ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ጉዳዩ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ አይታወቅም፡፡ ለስዊዘርላንድ ኢሚግሬሽን ባለሥልጣን በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢቀርብም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ 

ኢትዮጵያ ውስጥ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በግለሰቡ ላይ ክስ መሥርቶ፣ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሌለበት 19 ዓመት ፅኑ እስራት እንደተፈረደበት ይታወሳል፡፡ 

 

የአገሪቱ የነዳጅ ግዢ ጥያቄ ተነሳበት

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዓመታዊ የአገሪቱን የነዳጅ ፍጆታ ለመሸፈን የሚያካሂደውን ዓለም አቀፍ ጨረታ በመተው፣ በድርድር ከኩዌት መንግሥት ለመግዛት የተከተለውን አቅጣጫ ነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች ተቃወሙ፡፡ ድርጅቱ ተቃውሞውን አልተቀበለም፡፡

የአንዳንድ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ተወካዮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የነዳጅ ግዢ ጨረታ ማውጣት በመተው የተለያዩ የነዳጅ ውጤቶችን ከኩዌት በድርድር በመግዛት ላይ ይገኛል፡፡ ዕርምጃውን የተቃወሙት የኩባንያ ተወካዮች ውሳኔው አገሪቱን ዋጋ እንደሚያስከፍላት ይናገራሉ፡፡ 

‹‹አንደኛ ከኩዌት የሚገዛው ነዳጅ ውድ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከኩዌት ለሚገዛው ነዳጅ በበርሜል 0.30 ዶላር ጭማሪ ይከፍላል፡፡ ወይም በአንድ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ የ60 ሚሊዮን ብር ጭማሪ አለው፤›› ይላሉ፡፡ 

የኩባንያው ተወካዮች በሁለተኛ ደረጃ የሚያነሱት የነዳጅ ጥራት ጥያቄ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በአሁኑ ወቅት በመግዛት ላይ ያለው ነዳጅ የሊድ (እርሳስ) እና ሰልፈር መጠን ከፍተኛ በመሆኑ በአካባቢ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድራል ብለዋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በበኩሉ የቀረቡትን ወቀሳዎች አስተባብሏል፡፡ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር በሰጡት ምላሽ፣ ከኩዌት መንግሥት ነዳጅ በቀጥታ መግዛቱ የተለያዩ ጠቀሜታዎች አሉት ብለዋል፡፡ 

የኢትዮጵያ ዓመታዊ የነዳጅ ፍላጎት ከአገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ጋር ተቀራራቢ በሆነ ቁጥር፣ በዓመት አሥር በመቶ በማደግ በአሁኑ ወቅት ሦስት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ደርሷል፡፡ አገሪቱ ለነዳጅ ግዢ የምታወጣው የውጭ ምንዛሪ 2.8 ቢሊዮን ዶላር ነው፡፡ ከወጪ ንግድ የምታገኘው ደግሞ በዓመት ሦስት ቢሊዮን ዶላር ነው፡፡ 

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አገሪቱ ላላት የአውሮፕላን ነዳጅ ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ከኩዌት የሚገዛ ሲሆን፣ 50 በመቶ የሚሆነውን የናፍጣ ፍላጎት የምታሟላው ከኩዌት በድርድር በሚገዛ ናፍጣ ነው፡፡ ሰባ አምስት በመቶ የሚሆነው የቤንዚን ፍጆታ ከሱዳን መንግሥት ይሸመታል፡፡ ሃያ አምስት በመቶ የሚሆነው የቤንዚን ፍጆታና 50 በመቶ የናፍጣ ፍጆታ የገዛው በግልጽ ጨረታ ከነዳጅ ነጋዴዎች ነው፡፡ የኩዌቱን ነዳጅ የሚያቀርበው የኩዌት መንግሥት ንብረት የሆነው ኩዌት ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን ሲሆን፣ 20 በመቶ ቤንዚንና 50 በመቶ የሚሆነው ናፍጣ የሚመጣው ሳዑዲ ዓረቢያ ከሚገኘው ያንቡ የድፍድፍ ነዳጅ ማጣሪያ ነው፡፡ 

የኢትዮጵያ የዕለት የቤንዚን ፍጆታ አንድ ሚሊዮን ሊትር፣ ናፍጣ 5.8 ሚሊዮን ሊትር፣ የአውሮፕላን ነዳጅ 1.8 ሚሊዮን ሊትር ነው፡፡ ዓመታዊ የነጭ ጋዝ ፍላጎት ደግሞ 260,000 ሜትሪክ ቶን ነው፡፡ ኅብረተሰቡ የኤሌክትሪክ ምድጃዎች በስፋት መጠቀም በመጀመሩ የነጭ ጋዝ ፍላጎት እየቀነሰ መጥቷል፡፡ በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች በ13 የመጠባበቂያ ነዳጅ ዴፖዎች የሚገኙ ሲሆን፣ 360,000 ሜትር ኪዩብ የማጠራቀም አቅም አላቸው፡፡ 

ኢትዮጵያ ከኩዌት ነዳጅ መግዛት የጀመረችው ከኩዌት መንግሥት ጋር ረዥም ጊዜ የፈጀ ውይይት ከተደረገ በኋላ እንደሆነ አቶ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ሚኒስትሮቻችን ሁለት ሦስት ጊዜ ወደ ኩዌት የተመላለሱ ሲሆን፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ከኩዌት የነዳጅ ሚኒስትር ጋር ተገናኝተው የኢትዮጵያን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ከስምምነት ላይ በመድረሳቸው ነው፤›› ብለዋል፡፡ 

በተደረሰው ስምምነት መሠረት 70 በመቶ የአውሮፕላን ነዳጅ ፍጆታ፣ 50 በመቶ የናፍጣ ፍጆታ ከኩዌት ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን መገዛት መጀመሩን አቶ ታደሰ አስታውሰዋል፡፡ ባለፈው ዓመት የአውሮፕላን ነዳጅ አቅርቦት ኢትዮጵያ ለኩዌት ባቀረበችው ጥያቄ መሠረት ወደ 100 በመቶ አድጓል፡፡ 

ባለፈው ሳምንት በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በአቶ አህመድ ሺዴ የሚመራ የኢትዮጵያ መንግሥት ልዑክ ወደ ኩዌት ተጉዞ፣ ከኩዌት የነዳጅ ሚኒስቴር ኃላፊዎች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ በወቅቱም አቶ አህመድ የኩዌት ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን ለኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት የሚያቀርበውን የናፍጣ መጠን እንዲጨምር ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ከተቻለ የኢትዮጵያን 100 በመቶ የናፍጣ ፍላጎት እንዲያሟሉ ካልሆነ ግን 70 በመቶ እንዲሸፍኑ ጥያቅ አቅርበዋል፡፡ 

የኩዌት ባለሥልጣናት በበኩላቸው ቀደም ብለው የገቡዋቸው በርካታ ውሎች ስላሉ፣ 100 በመቶ መሸፈን እንደማይችሉ ገልጸው 70 በመቶ የሚለውን ጥያቄ (በ20 በመቶ ማሳደግ) ግን ገምግመው ምላሽ እንደሚሰጡ ለኢትዮጵያ ልዑክ አስረድተዋል፡፡ 

‹‹ከኩዌት ነዳጅ የመግዛት ዕድልን በብዙ ልምምጥ ያገኘነው ዕድል ነው፤›› የሚሉት አቶ ታደሰ፣ ከኩዌት ነዳጅ መገዛቱ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ያስረዳሉ፡፡ 

‹‹ከኩዌት በምንገዛበት ወቅት 90 ቀናት የመክፈያ ጊዜ ይሰጡናል፡፡ ሱዳን የምትሰጠን 30 ቀናት ነው፡፡ ነዳጅ ነጋዴዎች ከ30 እስከ 45 ቀናት ብቻ ነው የሚሰጡን፡፡ የኩዌት ነዳጅ አቅርቦት አስተማማኝ ነው፡፡ ባሉት ቀነ ገደብ ያቀርባሉ፡፡ የዋጋ ክለሳ እንደ ነጋዴዎቹ በየጊዜው አያደርጉም፡፡ የሚጠቀሙት የራሳቸውን መርከቦች በመሆኑ ርካሽ መርከብ ሲፈልጉ ጊዜ አያቃጥሉም፤›› የሚሉት አቶ ታደሰ፣ የዋጋ ልዩነትን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ዝርዝር ጠቀሜታዎችን መመልከት እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል፡፡ 

‹‹ለምሳሌ እኛ ለኩዌት በበርሜል የምንከፍለው ፕሪሚየም ክፍያ (ትራንስፖርትና አገልግሎት) 4.50 ዶላር ነው፡፡ ለነዳጅ ነጋዴዎች በበርሜል 4.10 ዶላር ነው፡፡ ከነጋዴዎች ስንገዛ ኢንሹራንስ የምንከፍለው ራሳችን ነን፡፡ ነጋዴዎቹን ኢንሹራንስ ጨምሩበት ብንላቸው ዋጋቸው ሰባት ዶላር ይገባል፡፡ የኩዌት ግን ኢንሹራንስን ጨምሮ 4.50 ዶላር ብቻ ነው፤›› ብለዋል አቶ ታደሰ፡፡ 

የነዳጅ ጥራትን አስመልክቶ ለቀረበው ተቃውሞ በሰጡት ምላሽ የኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት በአሁኑ ወቅት የሚገዛው ቤንዚን ከእርሳስ ነፃ የሆነ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹ሊድ ያለው ቤንዚን መግዛት አቁመናል፡፡ ዓለም ሊድ ያለው ቤንዚን መግዛት አቁሟል፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡ 

‹‹ኢትዮጵያ ከኩዌት የምትገዛው ናፍጣ ውስጥ ያለው የሰልፈር መጠን 0.2 በመቶ ሲሆን፣ ከነጋዴዎች የሚገዛው ናፍጣ 0.05 በመቶ ሰልፈር ይዘት አለው፡፡ የናፍጣ ዋጋ ባለው የሰልፈር መጠን ይወሰናል፡፡ 0.2 በመቶ ሰልፈር ያለው ናፍጣ በበርሜል 57.76 ዶላር፣ 0.05 በመቶ ሰልፈር ያለው 58.76 ዶላር፣ 0.005 በመቶ 60.16 ዶላር፣ 0.001 በመቶ 61.16 ዶላር ዋጋ አለው፤›› ብለዋል፡፡ 

‹‹0.001 በመቶ ሰልፈር ያለውን ናፍጣ ገዝቶ ማምጣት ይቻላል፤›› የሚሉት አቶ ታደሰ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት መኪኖች ዕድሜ ጠገብ በመሆናቸው የሰልፈር ይዘቱ ዝቅተኛ የሆነ ናፍጣ ገዝቶ ማምጣቱ ጠቀሜታ እንደሌለው ይናገራሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት መኪኖች በአብዛኛው አሮጌ በመሆናቸው ከፍተኛ የካርቦን ልቀት አላቸው፡፡ 

‹‹በአገራችን ያሉት ብዙዎቹ መኪኖች ሦስት መንግሥታት ያገለገሉ ናቸው፡፡ ከፍተኛ ዋጋ ያለውን ናፍጣ ገዝተን ብናመጣ መኪኖቹ ነዳጁን በአግባቡ መጠቀም የሚችሉ ባለመሆናቸው አላስፈላጊ ዋጋ መክፈል ብቻ ይሆናል፤›› ያሉት አቶ ታደሰ፣ ሌሎች አገሮች ከፍተኛ ዋጋ ያለውን ነዳጅ ሲያስገቡ የመኪና ዕድሜ ገድበው እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ‹‹ኬንያ ከስምንት ዓመት በላይ ዕድሜ ያለውን መኪና ማስገባት አይቻልም፡፡ በናይጄሪያ ከአምስት ዓመት በላይ ያለውን መኪና ማስገባት አይቻልም፡፡ ወደ እኛ አገር ተጨባጭ ሁኔታ ስንመጣ ይህን ማድረግ አይቻልም፡፡ አንድ ኤንትሬ የጭነት መኪና አሥር ቤተሰብ ያስተዳድራል፡፡ ከፍተኛ ዋጋ ያለውን ናፍጣ ከማስመጣታችን በፊት ዕድሜ ጠገብ ተሽከርካሪዎችን ማስወገድ አለብን፡፡ በርካታ ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ አሮጌ መኪኖችን በአሁኑ ወቅት ማስወገድ አይቻልም፡፡ ምናልባት ያን ማድረግ የሚቻለው ወደ መካከለኛ ገቢ አገርነት ስንሸጋገር ይሆናል፤›› ብለዋል፡፡ 

የነዳጅ ኩባንያ ተወካዮች የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት እ.ኤ.አ. ለ2016 የሚውል ነዳጅ ለመግዛት ነሐሴ 17 ቀን ጨረታ ማውጣት የነበረበት ቢሆንም፣ እስካሁን ጨረታውን አለማውጣቱን ይህም የጨረታ ግዢ ሙሉ በሙሉ ቀርቷል የሚል ሥጋት እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል፡፡ 

አቶ ታደሰ ድርጅታቸው ጨረታ ማውጣቱን እንዳልተወ፣ የጨረታ ሒደቱ እንዲዘገይ የተደረገው ከኩዌት የሚገዛው የነዳጅ መጠን እስከሚታወቅ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ 

የኩዌት መንግሥት የሚያቀርበው የነዳጅ መጠን ከታወቀ በኋላ ጨረታው እንደሚወጣ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ተጨማሪ የአውሮፕላን ነዳጅ እንዲያቀርቡ ጠይቀናል፡፡ የሚያቀርቡትን የናፍጣ መጠን የፍጆታችንን 70 በመቶ እንዲሆንም ጠይቀናል፡፡ ምላሻቸውን አይተን ጨረታውን እናወጣለን፤›› ብለዋል፡፡ 

ከሱዳን እስከ 80 በመቶ ቤንዚን የሚገኝ በመሆኑ የተቀረው 20 በመቶ ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን፣ ኩዌት ከናፍጣ ፍጆታ 70 በመቶ ልታቀርብ ትችላለች፡፡ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት 800,000 ሜትሪክ ቶን ናፍጣና 60,000 ሜትሪክ ቶን ቤንዚን ለመግዛት ጨረታ ያወጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ 

 

የገዥው ፓርቲ ኢሕአዴግ አጋር የሆነው የአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ) ሥራ አስፈጻሚ አባላት መካከል አለመግባባት መፈጠሩ ተሰማ፡፡ በዚህ ምክንያት የክልሉን ቋሚ መስተዳድር መመሥረት እንዳልተቻለ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 

አለመግባባቱ የተፈጠረው አብዴፓንና የአፋር ክልልን ላለፉት 20 ዓመታት ሲመሩ በቆዩት የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ እስማኤል ዓሊ ሴሮ ቡድንና እሳቸውን ተክተው በተመረጡት የአብዴፓ ሊቀመንበር አቶ ጠሃ መሐመድ ቡድን መካከል መሆኑን፣ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የአብዴፓ ሊቀመንበር አቶ ጠሃ መሐመድ የክልሉ መንግሥት የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ፣ በሌሎች ክልላዊ መንግሥቶች የሥልጣን አወቃቀር መሠረት የፓርቲው ሊቀመንበር እንደመሆናቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርም ሊሆኑ ይገባል የሚል ክርክር፣ በአቶ ጠሃ ቡድን አማካይነት መነሳቱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

ይህ ጥያቄ ግን አብላጫ ድምፅ ባለው የአቶ እስማኤል ዓሊ ሴሮ ቡድን በኩል ተቀባይነት ማግኘት አለመቻሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በዚህ ምክንያት አቶ ጠሃ መሐመድና አቶ እስማኤል ዓሊ ሴሮ የሌሉበት የፓርቲው የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ከአንድ ወር በፊት ተካሂዶ፣ አቶ እስማኤል ለተጨማሪ ሦስት ወራት በጊዜያዊ ፕሬዚዳንትነት እንዲቆዩ፣ ካልሆነ ደግሞ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ጊዜያዊ አስተዳደር ይመሥርት በሚለው ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ በስተመጨረሻም ከክልሉ ምክር ቤት ውጪ ሥራ አስፈጻሚው ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት መሾሙን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በዚሁ መሠረት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የውኃ ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ አወል አርባ፣ በጊዜያዊ ፕሬዚዳንትነት ለሦስት ወራት መመረጣቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይሁን እንጂ በወደፊቱ ጉዳይ ላይ መግባባት ባለመቻሉ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰሞኑን በአዲስ አበባ እየመከረ እንደነበር፣ በዚህ ስብሰባ ላይም የኢሕአዴግ ተወካዮች ለታዛቢነትና ለማስታረቅ መገኘታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ 

በትጥቅ ትግሉ ወቅት አቶ እስማኤል ዓሊ ሴሮ የሕወሓት አባል የነበሩ ሲሆን፣ በትጥቅ ትግሉ የተሳተፉ የአፋር ክልል ተወላጅ ናቸው፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የአብዴፓ ሊቀመንበር በመሆን ለ20 ዓመታት አገልግለዋል፡፡ 

በግንቦት ወር 2007 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ ክልሉን በመወከል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት ተመርጠዋል፡፡    

በአብዴፓ ውስጥ የተፈጠረውን አለመግባባትና እየተካሄደ ስለነበረው ድርድርና ምክክር ለአብዴፓ ጽሕፈት ቤት፣ ለክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ፣ ለኢሕአዴግ የውጭ ግንኙነት ጽሕፈት ቤትና ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥያቄ ቢቀርብም ምላሽ ማግኘት አልተቻለም፡፡  

 

‹‹ምርመራ ዘመናት የሚያስቆጥር የአርኪዮሎጂ ቁፋሮ አይደለም›› የተጠርጣሪው አቶ ወንድሙ ቢራቱ ጠበቃ

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነሐሴ 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ውለው በእስር ላይ የሚገኙት የኦሮሚያ ክልል ባለሥልጣን አቶ ወንድሙ ቢራቱ፣ የአውሮፕላን ትኬት በመግዛት በግብዣ መልክ ለባለሥልጣናት ጉቦ መስጠታቸው ተገለጸ፡፡

አቶ ወንደሙ የተጠረጠሩባቸውን የሙስና ወንጀሎች እየመረመረ የሚገኘው የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው በሥልጣን ዘመናቸው ወደ ውጭ አገር በመሄድ ምን ያህል ገንዘብ እንዳወጡና ለባለሥልጣናት የአውሮፕላን ትኬት በመቁረጥ በግብዣ መልክ ጉቦ የሰጡበትን ሰነድ ከሚመለከተው ተቋም መጠየቁን አስረድቷል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዳው፣ ተጠርጣሪው የተጭበረበረ ሰነድ ሕጋዊ በማስመሰል መሬት የሸጡበትና ከባንክ ገንዘብ የተቀበሉበት ሰነድ ተሰብስቧል፡፡ ጉቦ በቼክ የተቀበሉበት ሰነድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተሰብስቧል፡፡ ከሁለት ሰዎች ሦስት ሚሊዮን ብር ጉቦ መቀበላቸውን ከሚያረጋግጡ ሰዎች የምስክርነት ቃል መቀበሉንም ቡድኑ ገልጿል፡፡ ከጉምሩክ ከጠየቀው የማስረጃ ሰነድ ከፊሉን መሰብሰቡን፣ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች ለሚደረገው ምርመራ ደጋፊ ሰነድ በማቅረብ እየተከታተለ እንደሆነና አንድ ተጨማሪ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር አውሎ ቃሉን መቀበሉን መርማሪ ቡድኑ አስረድቷል፡፡

የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት የጠየቀ ሲሆን፣ ምክንያቱንም አስረድቷል፡፡ ተጠርጣሪው ብዙ ቤቶችና ቦታዎች እንዳሏቸው ጥቆማዎች በመምጣታቸው ከአራት ከተሞች ማኅደሮችን መሰብሰብ እንደሚቀረው፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ያልተሰበሰቡ ማስረጃዎችን መሰብሰብ፣ ተጨማሪ ሰነዶችን ለፎረንሲክ ምርመራ በመላከ ትክክለኛነቱን አረጋግጦ መሰብሰብ፣ ሌሎች ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን አድኖ መያዝና የምስክሮችን ቃል መቀበል ስለሚቀረው መሆኑን አስረድቷል፡፡

አቶ ወንድሙ ቀደም ባሉት ቀጠሮዎች እሳቸው የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት አባል ከመሆናቸውም በተጨማሪ፣ በእሳቸው ላይ የሚቀርብ ማንኛውንም ተጠያቂነት የመጠየቅ ሥልጣን ያለው የክልሉ መንግሥት መሆኑን በመናገር ሲከራከሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ተጠርጣሪው አሁንም በጠበቃቸው አማካይነት እንደገለጹት፣ የተጠረጠሩበትን የሙስና ወንጀል የማየት ሥልጣን ያለው የኦሮሚያ መንግሥት ብቻ ነው፡፡ የመመርመርና የመክሰስ ሥልጣን ያለው የኦሮሚያ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ብቻ ነው፡፡ ይሄም በፌዴራል የፀረ ሙስና አዋጅ 433/97 አንቀጽ 7(4) እና በአዋጅ ቁጥር 434/97 አንቀጽ 7(2/4) ተደንግጓል ብለዋል፡፡ ፌዴራል የክልሉን ሥልጣን ማክበር እንዳለበት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 50(8) መደንገጉንም አስረድተዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ የዳኝነት ሥልጣን ስለሌለውና ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ መስጠት ስለማይችል፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 50(8) እና በወ/መ/ሥ/ሥ/ቁ 110 መሠረት ክሱን ዘግቶ ተጠርጣሪው እንዲያሰናብታቸው ጠይቀዋል፡፡

የፖሊስ ምርመራ ተጠናቆ ቀዳሚ ምርመራ ውስጥ መግባቱን የጠቆሙት የአቶ ወንድሙ ጠበቃ፣ የምርመራ ሥራ ዘመናት የሚያስቆጥር የአርኪዬሎጂ ቁፋሮ አለመሆኑንና በፍጥነት መፈጸም ያለበት የሕግ ሥራ በመሆኑን በመጠቆም ተጨማሪ ቀጠሮ መሰጠት እንደሌለበት አመልክተዋል፡፡

የወንጀሉ መፈጸም አጠራጣሪ መሆኑንና ተጠርጣሪውን ዋስትና ሊያስከለክላቸው እንደማይችል የገለጹት ጠበቃው፣ ወንጀሎቹ መፈጸማቸውን የሚያስረዳ ምንም ዓይነት ማስረጃ ካለመገኘቱም በተጨማሪ ተጠርጣሪው ወንጀሉን መፈጸማቸውም አጠራጣሪ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አጠራጣሪ ወንጀል የቅጣት ጣሪያው ምንም ያህል ቢሆንም የዋስትና መብት እንደማያስከለክል ጠቁመው፣ መርማሪ ቡድኑ የጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ታልፎና መዝገቡ ተዘግቶ ከእስር እንዲፈቱ ወይም የመንቀሳቀስ መብታቸው ተገድቦ በዋስ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ከሰማ በኋላ በሰጠው ትዕዛዝ፣ የተጠርጣሪው ጠበቃ ቀደም ባለው ቀጠሮ መርማሪ ቡድኑ በጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ምንም እንዳልሠራ መግለጻቸውን በሚመለከት መዝገቡን ተመልክቶ፣ ጠበቃው እንዳሉት ሳይሆን ቡድኑ ምርመራ ማድረጉን ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡ የተጠርጣሪ ጠበቃ የደንበኛቸውን ጉዳይ የፌዴራል መንግሥት ወይም ፍርድ ቤቶች ማየት እንደማይችሉና ሥልጣኑ የክልሉ መሆኑን በመጥቀስ መዝገቡ ተዘግቶ አቶ ወንድሙ በነፃ እንዲሰናበቱ ያቀረቡትን አቤቱታ እንዳልተቀበለው አስረድቷል፡፡ ያልተቀበለበት ምክንያት ቀደም ባሉ ቀጠሮዎች ተመሳሳይ ጥያቄ ቀርቦ ችሎቱ ብይን የሰጠበት መሆኑን በመግለጽ፣ ለመርማሪ ቡድኑ ተጨማሪ ዘጠኝ ቀናትን በመፍቀድ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

አቶ ወንድሙ ሥልጣናቸውን በመጠቀምና ከፌዴራል ባለሥልጣናት ጋር በመመሳጠር አገራዊ ጠቀሜታ ላላቸው የተለየ ክህሎት ለሚጠይቁ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የተፈቀደውን ከቀረጥ ነፃ መኪና ማስገባት መብት በመጠቀማቸው፣ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ሀብት በማከማቸት፣ በሕገወጥ መንገድ ያካበቱትን ሀብት ሕጋዊ በማስመሰል፣ በዘመዶቻቸው ስም ሀብት በማስቀመጥ፣ ለመንግሥት መግባት የነበረበትን ታክስና ቀረጥ ለግል መጠቀሚያ በማድረግ፣ ጉቦ በመቀበልና በማቀባበል ወንጀሎች መጠርጠራቸውን የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን ቀደም ባሉት ችሎቶች ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

 

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በመቀሌ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ላይ በጥንቃቄ ተመርጠው የተጠሩ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ። አንጃው ይህንን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀው “12ተኛ ጉባኤ እንዴት አለፈ …?” በሚል አጀንዳ በየመንግሥት መስርያ ቤቶች፣ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች […]

አቶ ሞላ አስገዶም ላለፉት ረዥም አመታት ምንም ሳይሰራ ውጤት ስላላመጣን አሁን የመሰረትነው የአገር አድን ንቅናቄ በተግባራዊ ስራ ላይ በመሰማራት በቂ የሆነ ዝግጅት እና የሰው ሃይል ስላለን ወያኔን በአፋጣኝ መውረር አለብን የሚል አቋም በመያዝ በንቅናቄው መስራች ስብሰባ ላይ መናገራቸው የሻእቢያን ሰዎች …

መሪያቸው ታጋይ ሞላ አስገዶምን ተከትለው ሱዳን የገቡ የደምሕት ተዋጊዎች ምስል ከታች ይገኛል:: Read more »

በምዕራባዊ ዞን ቓፍታ ሑመራ የምትገኘው የበረከት ከተማ ዛሬ ዓርብ ከሰኣት 06/ 13 / 2007 ዓ/ም ማን እንደተኮሰው የማይታወቅ የከባድ መሳርያ ድብደባ እንደተፈፀመባት የከተማዋ ኑዋሪዎች በስልክ ገልፀውልናል። በከባድ መሳርያ ድብደባው የደረሰ ጉዳት ይኑር ኣይኑር ኣልታወቀም።

የትግራይ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ሃላፊና የክልሉ ዳኞች ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም በሙስና ስለተገመገሙ ከሃላፊነታቸው መውረድ አለባቸው ሲሉ የህወሓት ጉባኤተኞች የወሰኑትን ውሳኔ እስከ አሁን ድረስ እንዳልተተገበረ ተገለፀ። እንደ ምንጮቻችን መረጃ መሰረት የአባይ ወልዱ ሚስት የሆኑት ወ/ሮ ትርፉ ኪዳነማሪያም ላለፉት አመታት የትግራይ ክልል የሲቪል ሰርቪስ ሃላፊ ሆነው በሰሩበት ጊዜ በመስሪያ ቤቱ አዳዲስ ለውጦች ባለማምጣታቸው የተነሳና ጊዜው […]

Molla Asgedom

የየትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ ሊቀመንበር መክዳት በትጥቅ ትግሉ ላይ ጥርጣሬዎች በድርጅቱ ውስጥ ድንጋጤን ፈጥሯል:‪ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – የትጥቅ ትግሉን ሂደት ከፍተኛ የሰነድ ምስጢሮችን በመያዝ እና አስቸኳይ ወረራ በወያኔ ላይ መጀመር አለበት የሚለው አቋማቸው ሻእቢያ ጥርስ ወስጥ እንደከተታቸው በደረሳቸው …

የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ ሊቀመንበር መክዳት በትጥቅ ትግሉ ላይ ጥርጣሬዎች በድርጅቱ ውስጥ ድንጋጤን ፈጥሯል:‪:(ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »

በሃሰት በሽብር ወንጀል የተፈረደባቸው በኡስታዝ አቡበከር አህመድ መዝገብ ከሚገኙት ኮሚቴዎቻችን እና ወንድሞቻችን መካከል ስድስቱ አዱስ አመቱን ምክንያት በማድረግ በይቅርታ መንግስት እንደፈቱ መወሰኑን የመንግስት ልሳን የሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ አስታውቋል፡፡ እንዲፈቱ እንደተወነሰለቻው ከተገለፀው መካከል 1.ኡስታዝ ያሲን ኑሩ 2.ኡስታዝ ባህሩ ዑመር ፣ 3. …

በኡስታዝ አቡበከር አህመድ የክስ መዝገብ በሃሰት ከተፈረደባቸው መካከል ስድስቱ ተፈቱ Read more »

ህዝበ ሙስሊሙ በህዝበ ሙስሊሙ መፍትዬ አፈላለጊ ኮሚቴ ላይ መፈረዱን ተከትሎ  በአንዋር መስጂድ የትግሉን ቀጣይነት የሚያብሰረውን አሃዱን አሃድ የትግላችንን ሎጎ አንድ ቁጥር በወረቀት ላይ በመፍክር በመፃፍ አንዋር መስጂድ ፍፁም ሰላማዊ የሆነውን ተቃውሞ አሰማ!! 22 ዓመት ተፈርዶብን ዝም የምንል ይመስላቹሃል! ! ፍትህ …

በአንዋር መስጂድ ደማቅ ተቃውሞ ተደረገ! Read more »

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድምጻችን ይሰማ የትግል ስትራቴጂውን በአዲስ መንገድ እንደሚቀይስ ማስታወቁን ተከትሎ፣ የመጀመሪያውን ትግል አንድ ቁጥር በመያዝ ትግሉን ጀምሯል። ሙስሊሙ ማህበረሰብ በቅርቡ ፍርድ ቤት በሙስሊም መሪዎች ላይ የሰጠውን ፍርድ ” የተቀበረች ፍትህ ቀባሪዋን ትቀብራለች፣ አምባገነናዊ ፍርድ አንቀበልም” የሚል መፈክር በማሰማት ተቃውሞ አሰምቷል። አሃዱን አሃድ፣ ትግላችን ይቀጥላል፣ ድምጻችን ይሰማ፣ ኮሚቴው ይፈታ፣ …

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አሳይቷል በዘንድሮ የአዲስ አመት ገበያ፣ የዶሮ ዋጋ ከበፊቱ በእጥፍ የጨመረ ሲሆን በአቃቂና በሳሪስ አካባቢ ዶሮ ከ200 ብር እስከ 400 ብር የሚሸጥ ሲሆን፤ በግ ከ1100 እስከ 3500 ብር፣ በሬ ከ4500 እስከ 25ሺ ብር፣ ፍየል ከ750 እስከ 4ሺ ብር እየተሸጡ ነው፡፡ በሾላ ገበያ በግ ከ900 ብር እስከ 4500 ብር፣ …

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የኬሚስትሪ ትምህርት ክፍል ባጠናው ጥናት ከአዋሳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የሚወጣው ኬሚካል ሃይቁንና ወንዙን በመበከሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ህይወት አደጋ ላይ ወድቋል። ከፋብሪካው የሚወጣው ውሃ በቀጥታ ወደ ጥቁር ውሃ ወንዝ የሚፈስ ሲሆን፣ ወንዙም ወደ ሃይቁ የሚፈስ በመሆኑ ተጨማሪ ስጋት ፈጥሯል። የኬሚካሉ ወደ ውሃው መግባት የአሳዎችን ስደት እንደሚያስከትል የሚገልጸው …

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመጪው መስከረም ወር 2008 መቶ በመቶ በኢህአዴግና አጋሮቹ በተያዘው ፓርላማ ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ሁለተኛው የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ ይፋ ለማድረግ በሚል በእነሠራዊት ፍቅሬ እና ሽዋፈራው ደሳለኝ አጋፋሪነት ከምሽቱ 3 ሰዓት ጅምሮ በሚሌኒየም አዳራሽ ጠ/ሚኒስትር አቶ ኃለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሚገኙበት ታላቅ የፌሽታ በዓል ተዘጋጅቷል፡፡ እነሠራዊት ፍቅሬ …

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከባህርዳር እስረኞችን ጭኖ አዲስ አበባ ወደሚገኘው ማእከላዊ እስር ቤት በመጓዝ ላይ ያለ ሚኒባስ ታክሲ ፣ ማለዳ 1 ሰአት ተኩል አካባቢ ሾላ ሰሜን ሆቴል ወይም መቀጠያ ሃበሻ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሲደርስ ፣ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በመቆሙ በውስጡ ከነበሩት 13 እስረኞች መካከል 6ቱ ከመኪናው በመውረድ አምልጠዋል። የተቀሩት ከሚኒባስ ባለመውረዳቸው …

ጷግሜን ፭፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የደቡብ ሱዳን ስደተኞች በተጠለሉባቸው የስደተኞች መጠለያዎች ውስጥ የተቀሰቀሰው የኮሌራ ወረሽኝ በአጎራባች የደቡብ ሱዳንና የኢትዮጵያ ድንበሮች አካባቢ ስጋት እየፈጠረ ነው። ይህንን ተላላፊ ገዳይ በሽታ ለመግታት የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ድርጅትና ዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በጥምረት ክትባትና የንጹህ ውሃ አገልግሎት አቅርቦት መስጠት ጀምረዋል።በአስር የስደተኞች መጠለያ …

ከትናንት ሐሙስ አንስቶ ለ 10 ቀናት የሚዘልቅ የፎቶ አውደ ርዕይ ዩናይትድ ስቴትስ- ኒው ዮርክ ከተማ ተከፍቷል። በዚህም አውደ ርዕይ ላይ የ11 ወጣት ኢትዮጵያውያን የፎቶ ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል።

ማስረጃዎች ለሕጋዊ ጥያቄ በሚያመቹበት ኹኔታ በአፋጣኝ ተዘጋጅተው እንዲቀርቡ ታዟል በጥምር እና በተናጠል ተጠያቂ የሚኾኑ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች በስም ዝርዝር ይለያሉ የቤት እና የመኪና ሽልማት የተሰጣቸው አለቆች እና የስጦታው ምክንያት ተብራርቶ ይቀርባል   *          *          * የመሬት፣ የሕንጻ እና የልማት ይዞታዎች የኪራይ ውላቸው ለአንድ ዓመት ብቻ ይኾናል ከሦስተኛ ወገኖች ጋር ለመዋዋል እንዲቻል የቀረበው የውሳኔ ሐሳብ በቋሚ …

የዞን 9 ጦማርያን ከታሰሩ አንድ አመት ከአምስት ወራት የተቆጠረ ሲሆን ወዳጅ ጋዜጠኞችን ጨምሮ ከጠቅላላው ዘጠኝ እስረኞች መካከል አራት ጦማርያን አሁንም በእስር ላይ በመሆናቸው ሁለተኛ እንቁጣጣሻቸውን በቅሊንጦ እስር ቤት ያከብራሉ ፡፡ ባለፉት አንድ አመት ከአምስት ወራት 36 ግዜ ፍርድ ቤት የተመላለሱ ሲሆን እስራቸው እና የፍርድ ሂደቱ በ2007 ዓ/ም ምን ይመስል እንደነበረ በመጠኑ እናያለን፡፡


የዞን 9 የእስር መስመር


መስከረም 2007  -የዓመቱ መጀመሪያ ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ በጻፈው  የቀድሞው አብዮተኛ ኑዛዜ  ተጀመረ፡፡ ጽሁፉ በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ የዞን9 ጦማር ላይ ታትሟል፡፡


ጥቅምት 2007 የህግ የበላይነት እና ጸረ ሽብርህጉ ሲገመገም የሚለው ‹‹የጸረ ሽብር ሕጉና›› የአሁኗ ኢትዮጲያ ያላቸውን ግንኙነት አንዲሁም ምን ተፅእኖ እንዳለው የሚያሳየው ልዬ ሪፓርተዥ ተዘጋጀ፡፡
ጥቅምት 11 2007 ዓ/ም በእስር ላይ ይገኙ የነበሩትን ጦማሪት ማህሌት ፋንታሁንን እና ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬን የእስር ቤት አያያዝ አስመልክቶ የቀረበውን አቤቱታ ለማየት ችሎቱ ተሰየመ፡፡ በእለቱም እስር ቤቱ የተለየ አያያዝ መኖሩን ክዶ የተከራከረ ሲሆን ፍርድ ቤቱም አንደተለመደው እንዳይደገም በሚል የማረሚያ ቃል ችሎቱን አጠናቀቀው፡፡

ከጥቅምት 12 ጀምሮ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ለዞን9 ጦማርያን 6 ወር የእስር ቆይታን አስመልክቶ ለቤተሰቦቻቸውን ድካም የማገዝ የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ በዞን9 ጦማርያን ወዳጆች አማካኝነት በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ፡፡

ጥቅምት 25 – የዞን9 ጦማርያን ለአስረኛ ፍርድ ቤት ቀረቡ ፡፡


ህዳር 2007  –

ህዳር 1 ቀን የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይማርያም ደሳለኝ በተለያዬ ሚዲያዎች ላይ ሲቀርቡ የሚሰጡትን አስተያየት ሕገ-መንግስታዊነትን የጣሰ መሆኑን አስመልክተው ደብዳቤ ጻፉ፡፡ ደብዳቤው የተከሳሾችን በህግ ፊት ንጹህ ሆኖ የመቆጠር መብት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየጣሱ እንደሆነ እና እንዲታረም የሚጠይቅ ነበር፡፡

ሕዳር 3  ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ ለ11ኛ ፍርድ ቤት ቀረቡ ፡፡ በዚህ የፍርድ ቤት ውሎም አቃቤ ህግ በአምስት ጉዳዬች ላይ ክሱን አንዲያሻሽል ትእዛዝ ተሰጠው ፡፡ ( ሊፈጽሙ ነው የተባለውን የሽብር ወንጀል በግልጽ ማስቀመጥ፣ ቡድኑ እየተባለ የተቀመጠው ቡድን ማን እነደሆነ በግልጽ ማስቀመጥ፣ የሥራ ክፍፍልን አስመልክቶ የተጠቀሰውን በግልጽ መስቀመጥ ፣ ተላከ የተባለውን 48000 ብር አስልክቶ በግልጽ ከማን አንደተላከ ማስቀመጥ ፣ ስልጠና የተባሉት ምን እንደሆኑ በግልጽ ማስቀመጥ እና የሽብር ስልጠና ሰጪ ድርጅቱን በግልጽ ማስቀመጥ ይገኙበታል)

ሕዳር 17 – በጦማርያኑ የዋስትና መብትን አስመልክቶ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደርጎ በእስር መቆየታቸው እርግጥ ሆነ ፡፡

ሕዳር 24 – ተሻሻለ የተባለው ክስ በድጋሚ ለፍርድ ቤት ቀረበ ፡፡ ጠበቆች የተሻሻለው ክስ ላይ አስተያየታቸውን አንዲሰጡ ተነገራቸው፡፡ ተሻሻለ የተባለው ክስ ቡድኑ ግንቦት 7 ነው ከማለት ውጪ ምንም አይነት መሻሻል ሳይደረግበት ነበር ለፍርድ ቤት የቀረበው ፡፡


ታህሳስ 2007

ታህሳስ 7 – ጦማሪ ዘላለም ክብረት በእንግሊዘኛ የጻፈው የናፍቆት ደብዳቤ  ታተመ

ታህሳስ 9 – ጦማሪ አቤል ዋበላ ‹‹ሕልም እንደሆነ አይታሰርም›› የሚለው ተወዳጅ ጽሁፉ በዞን9 ጦማር ላይ ታተመ ፡፡

ታህሳስ 27 ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ በድጋሚ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ፍርድ ቤቱ ክሱ አንዲሻሻል ታዞ ነገር ግን በተለያዩ አራት ጉዳዮች ላይ አሁንም ባለመሻሻሉ በድጋሚ አንዲሻሻል ሁለተኛ ትእዛዛ ሰጠ፡፡


ጥር 2007

ጥር 6 የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኛ ወዳጆች በድጋሚ ፍርድ ቤት ቀረቡ ፡፡ በእለቱ አቃቤ ህግ በድጋሚ አሻሻልኩት ያለውን ክስ ይዞ ቀረበ፡፡

ጥር 20 – ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግ ያቀረበውን ያልተሻሻለ ክስ እንደተሻሻለ መቁጠሩን በመግለጽ ተከሳሾች የህብረተሰቡን ደህንነት ወይም ጤና በማወክ በጸረ ሽብር ህጉ አንቀጽ 4 መከሰሳቸውን አጸና፡፡ የወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ የተጠቀሰበትን አንቀጽ በቀደመው ብይን ውድቅ በማድረጉም የተከሳሾች ጉዳይ ‹‹በጸረ ሽብር›› ሕግ ብቻ እንዲዳኝ ተወሰነ፡፡ የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተቀጠረ፡፡

ጥር 26 – የዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች በድጋሚ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ፍርድ ቤቱ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ከመስጠታቸው በፊት መሃል ዳኛው አንዲነሱላቸው አቤቱታ አቀረቡ፡፡ ችሎቱም አቤቱታውን ሰምቶ ለመወሰን ሌላ ቀጠሮ ተሰጠ፡፡

ጥር 27 – በዚህም ቀጠሮ የተገኙት ተከሳሾች ሁለቱ ዳኞች ተሟልተው የዳኛው ይቀየርልን አቤቱታን መስማት ስላልቻሉ  በማግስቱ ለጥር 28 ተቀጠሩ ፡፡

ጥር 28 – በዚሁ እለት መሃል ዳኛው ባልተገኙበት ሁለቱ ዳኞች ጉዳዩን አይተው መሃል ዳኛው በፍርድ ሂደቱ ወቅት ጣልቃ አልገቡም አንዲሁም አፋጣኝ ፍትህን አላጓደሉም በማለት ውሳኔ መስጠታቸው ተገለጸ፡፡ ይህንን ተከትሎ የመሃል ዳኛው ምንም አንኳን በጉዳዩ ላይ ዳኞች ችሎቱ ላይ አንድቀጥል ቢፈልጉም ለእኔ ግን አንዲህ እየተባል ክሱ ላይ መቆየት አግባብ ስለማይሆን ራሴን ከችሎቱ አግልያለሁ በማለት አስተያየታቸው ሰጡ ፡፡ ( ነገር ግን ችሎቱን አሁንም የሚያስችሉት እኚሁ ዳኛ ናቸው) ፡፡

በተመሳሳይ እለት ጦማሪ አቤል ዋበላ ከማረሚያ ቤት የደረሰበትን የመብት ጥሰት ( በውሻ ሰንሰለት ታስሮ መቀመጥ እና በማዕከላዊ ሳለ በደረሰበት ድብደባ እንዲጠቀም የተገደደውን የጆሮ ማዳመጫ መሳሪያውን መቀማት) አስመልክቶ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቀረበ ፡፡ ይህን አቤቱታውን በጽሁፍ አንዲያቀርብ ከፍርድ ቤት ቢነገረውም በእለቱ የነበረው ሂደት ብዙዎን በፍርድ ቤት ውስጥ እንባ አራጨ፡፡ በእለቱ የነበሩት የእስር ቤት ተጠሪ የማውቀው ጉዳይ የለም በማለት የመብት ጥሰቱን ክደዋል፡፡


የካቲት 2007

የካቲት 11 – የዳኛው መቀየር አቤቱታን ፍርድ ቤቱ ውድቅ ካደረገው በኋላ የዞን 9 ጦማርያ እና ጋዜጠኞች የካቲት 11 ቀን ለ20ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት በመገኘት የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ በእለቱን ጦማሪ በፍቃዱ ‹‹የሽብር ተግባር አልፈጸምኩም ሽብር ተፈጽሞብኛል›› ሲል፣ ጦማሪ ናትናኤል በበኩሉ ‹‹እዚህ አገር ፍትህ ቢኖር ኖሮ እኔ የቆምኩበት ቦታ ላይ መቆም የሚገባቸው ከሳሾቼ ናቸው፤ ምንም አይነት ወንጀል አልፈጸምኩም›› የሚል ቃሉን ሰጥታል፡፡ ጦማሪ አጥናፍ ‹‹ምንም አይነት ወንጀል አልፈጸምኩም›› ያለ ሲሆን ጦማሪ አቤል በበኩሉ ‹‹የኅብረተሰቡን ደህንነት ለመጉዳት አላቀድኩም ለሽብር ተግባርም አላሴርኩም ብሏል፡፡››  የሴት እስረኞችን አያያዝ አስመልክቶ አጭር ቀጠሮ የሰጠን ሲሆን አጠቃላይ የማስረጃ ማሰማት ሂደቱን ግን ከአንድ ወር ከ10 ቀን በኋላ በተከታታይ ለሶስት ቀን ቀጥሮታል፡፡

የካቲት 18 – የሴት እስረኞችን አያያዝ አስመልክቶ ችሎቱ የተሰየመ  ጉዳዬን ለማየት በድጋሚ ቀጠሮ ሰጥታል፡፡  


መጋቢት 2007

መጋቢት 21 – የሰው ምስክር ናቸው ተብለው የቀረቡ ሰዎችን ምስክርነት መስማት ተጀመረ ፡፡ ሁሉም ምስክሮች እቃዎች ሲፈተሹ ያየን ነን በማለት የተያዙ እቃዎቸን ከማየታቸው በስተቀር ያቀረቡት የተለየ የወንጀል ምስክርነት አልነበረም ፡፡ ምስክሮቹ ተከሳሾን መለየት ሲያቅታቸው የተስተዋሉ ሲሆን በመጀመሪያው ቀን 6 ሰዎች ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ የተከሳሽ ጠበቆች ባልተካደ ነገር ላይ የፍርድ ቤቱም የተከሳሾችም ጊዜ መባከን አይገባውም እቃውም የእኛ አይደለም የሚል ቃል አልሰጠንም ስለዚህ የደረጃ ምስክሮች መስማት ይቁም ቢሉም ፍርድ ቤቱ ታዛቢዎቹን መስማት መቀጠል አለበት በማለቱ የተገኙ እቃዎችን ሲዘረዝሩ ከርመዋል ( መጽኃፍት ፣ መጽሄቶች፣ አርቲክሎች ላፕ ቶፕ ስልኮች እና ሲምካርዶች የመሳሰሉት ከፍተሻ ዝርዝሩ ውስጥ የተገኙ ናቸው)

መጋቢት 22 – ተጨማሪ 8 ምስክሮች በተመሳሳይ ሁኔታ ቃላቸውን ሲሰጡ ውለዋል፡፡ ከነዚህ በላይ ምስክሮችን ማቅረብ ያልቻለው አቃቤ ህግ ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቁ ለመጋቢት 30 ቀጠሮ ተሰጥታል፡፡

መጋቢት 30 – አቃቤ ህግ ምስክሮቼ ጠፍተውብኛል፡፡ የሲዲ ማስረጃዎችንም የያዘው ሰው በአገር ውስጥ ስለማይገኝ ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ የሚል ጥያቄ አቅርቦ በመፈቀዱ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶ ችሎቱ ተበትናል ፡፡

መጋቢት 25 – ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ይድረስ ለኢቢሲ ጋዜጠኞች የጻፈው ጽሁፍ ታትሞ ወጥቷል፡፡


ሚያዝያ 2007

ሚያዝያ 16-19  የ6ቱ ጦማርያንን እና የ3ቱን ጋዜጠኞች እስር አንደኛ አመት አስመልክቶ ለነጻነታቸው ዋጋ የሚከፍሉትን እናወድስ የሚል የሁለት ቀናት ማስታወሻ ተዘጋጀ፡፡ በማስታወሻው ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ የደረሰባቸውን የመብት ጥሰት ዝርዝር እና የተያዙበትን እለት የነበረውን ድባብ ያሳየ ሲሆን ከ3 ሺህ በላይ ሰዎች በሁነቱ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል ፡፡  በዚሁ የማስታወሻ ዝግጅት ላይ የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የላኩት የአንደኛ አመት ማስታወሻም ተስተናግዷል፡፡


ግንቦት 2007

ግንቦት 2

በዞን 9 ወዳጆች አማካኝነት የተዘጋጀው ሁለተኛው የቤተሰቦቻቸውን ሸክም መጋራት የሚለው የአንድ ሳምንት ዘመቻ ለሁለተኛ ጊዜ ተካሄዷል፡፡

ግንቦት19-21 በነዚህ ቀናት በዋለው ችሎት ላይ ከፍተኛ መወዛገብ ያሳየው አቃቤ ህግ ሲዲዎቹን እንደማስረጃ ማስመዝገብ ባለመቻሉ እና ምስክሮችንም ማቅረብ ስላልቻለ ሲዲዎቹ ከማስረጃ ላይ አንዲወገዱ እንዲሁም ተጨማሪ ምስክሮችን ለማቅረብም የተወሰነው ጊዜ በቂ ሆኖ አልተጠቀመበትም በሚል ምክንያት ተጨማሪ እድል እንዳይሰጠው ተወስኗል ፡፡

አቃቤ ህግ አንደኛ ተከሳሽ ሶልያና ሽመልስ ላይ አለኝ ያለውን የሲዲ ማስረጃ አስመልክቶ ሌሎች ተከሳሾች ማየት አለባቸው ወይስ ፍር ቤቱ በጽህፈት ቤት ማየት አለበት የሚለውን ለመወሰን ሰኔ 8 ተቀጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ቀን ችሎት ውስጥ አቤል ዋበላ ከዳኞች ጋር በነበረው አለመስማማት የተነሳ የችሎት መድፈር ጥፋተኛ ተብሎ ለቅጣት ለግንቦት 25 ተቀጠረ፡፡

ግንቦት 23 – ሥነ-ስርዓት የሚለው የጦማሪ አቤል ዋበላ ጽሁፍ ታትሟል፡፡

ግንቦት 25 አቤል ዋበላ በችሎት መድፈር በገደብ 4 ወር ተፈርዶበታል ፡፡


ሰኔ 2007

ሰኔ 8 – ፍርድ ቤት የቀረቡት 9 ተከሳሾች  ከብይን ለሃምሌ 13 የተቀጠሩ ፡፡ በእለቱም አንደኛ ተከሳሽ ላይ የቀረበውን የሲዲ ማስረጃ በጽህፈት ቤት አይተን እንደማስረጃ ቆጥረነዋል፡፡ ለሌሎች ተከሳሾም መድረስ አይገባውም በማለት ችሎቱ ወሰነ


ሃምሌ 2007

ሃምሌ 1 ቀን 2007 ዓ/ም ባተጠበቀ ሁኔታ ሶስቱ ጋዜጠኞች እና ሁለት የዞን9 ጦማርያን ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር መፈታታቸው ዜና ተሰማ ፡፡ በእለቱ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ፣ ጋዜጠኛ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ እና ጦማሪ ዘላለም ክብረት ሲፈቱ በማግስቱ ጠዋት ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ እና ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁን ተፈቱ፡፡

በተመሳሳይ ቀን በቀሪዎቹ 5ቱ ተከሳሾች ላይ ክሱ አንደሚቀጥል የመንግስት ወዳጅ የሆነው ሬዲዬ ፋና በድረ ገጹ አሳወቀ ፡፡

ሃምሌ 9-11 ለሶስት ቀናት የሚቆይ እስቲ አንነጋገር የማስረጃን ነገር በሚል የተዘጋጀው ዘመቻ ተካሄደ ፡፡ ይህ ዘመቻ ሃሳቡ ተከሳሾች ላይ ማስረጃ ተብለው የቀረቡ ጉዳዬችን ለአደባባይ ማብቃትና ቀሪ አራት ታሳሪዎች የሚከላከሉት ምንም ነገር እንደሌለ ለማሳወቅ የታለመ ነበር ፡፡

ሃምሌ 10 – ጦማሪ በፍቃዱ ቁዘማ፣ ከአቃቤ ሕግ ማስረጃዎች በፊት እና ጦማሪ ናትናኤል የዕለት ተዕለት ጥያቄዎቻችን ብይናቸውን አስመልክቶ የጻፋቸው ጽሁፎች ታተሙ፡፡

ሃምሌ 13 – ፍርድ ቤቱ የአንድ ምስክር ቃል ተገልብጦ አልደረሰኝም በማለት ብይኑን መስራት አለመቻሉን ገልጾ ጽሁፉ መገልበጡን ለማረጋገጥ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ ፡፡

ሃምሌ 22 – የተከሳሾች ጽሁፍ ተገልብጦ ማለቁን አረጋግጫለሁ ያለው ፍርድ ቤቱ ከጽህፈት ቤት በማስቻል በድጋሚ ለጷጉሜ 2 ቀጠሮ ሰጠ

ሃምሌ 25 – ጥቂት ስለማእከላዊ የሚል ጽሁፍ ታተመ፡፡


ሜ 2007

በአመቱ የመጨረሻ ሳምንት የመጨረሻ የእስር ሳምንታቸው ይሆናል ተብሎ ተስፋ ቢደረግም ፍርድ ቤቱ ዳኞች አልተሟሉም በሚል ሌላ ሰበብ ሁለተኛ እንቁጣጣሻቸውን በእስር እንደሚያሳልፉ ያረጋገጠውን የ31 ቀን ቀጠሮ በመስጠት ለመስከረም 27 ለአራተኛ ጊዜ በአጠቃላይ ደሞ ለ37ተኛ ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ ፡፡