የአርቲስት ሰብለ ተፈራ የቀብር ስነሥርዓት ተፈጸመ ::ባለቤቷ ሞገስ ተስፋዬ በ15 ሺ ብር ዋስ ተለቀቀ::

የአርቲስት ሰብለ ተፈራ የቀብር ስነሥርዓት ብዙ ሺህ አድናቂዎቿ እና ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተፈጸመ::ባለቤቷ የሚያሽከረክረው መኪና ከቆመ መኪና ጋር ተላትሞ የአርቲስቷ ሕይወት በአዲሱ ዓመት ያለፈ ሲሆን ባለቤቷ ሞገስ ተስፋዬ ላለፉት 3 ቀናት እስር ቤት ቆይቷል:: ዛሬ ጠዋት ፍርድ ቤት የቀረበው ሞገስ በ15 ሺህ ብር ዋስ የተለቀቀ ሲሆን በቀብር ስነስርዓቷ ላይም የርሷን ፎቶ ግራፍ የያዘ “ሰብልዬ ሁሌም እወድሻለሁ” የሚል ቲሸርት ለብሶ ተገኝቷል::
