የህዝብ ታዛቢ በመሆን ሊያገለግሉ የሚችሉ ሰዎችን ለመምረጥ በየቀበሌው በተደረገው ታዛቢዎችን የማስመረጥ ሂደት ላይ የገዢው ፓርቲ አባላት በታዛቢነት መመረጣቸውን በምርጫው ሂደት ላይ የነበሩ ተሳታፊዎች ለፍኖተ-ነፃነት ገለፁ፡፡ በዛሬው እለት ታዛቢዎችን በማስመረጥ ሂደት ላይ “የገዢው ፓርቲ አባላት ህዝቡን በማግለል እርስ በእርስ በመመራረጥና የምርጫ ሂደቱን በድብቅ እያካሄዱ” መሆኑን የገለፁት የፍኖተ-ነፃነት ምንጮች “ይህ አካሄድ ህገ-ወጥ እና የምርጫውን ደንብ የጣሰ” መሆኑን […]

.እስክንድር ነጋ እና አንዱዓለም አራጌ ማስታወሻቸው ተወስዶባቸዋል፤ ቃሊቲ እስር ቤት ሙሉ ፍተሻ እንደተደረገበት ዛሬ እኩለ ቀን ላይ እስረኞችን ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ አቅንተው የነበሩ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አመለከቱ፡፡ ከፌደራል ወንጀል ምርመራ እንደመጡ በተነገረላቸው ሰዎች ሙሉ ቃሊቲ እስር ቤት ፍተሻ እንደተደረገበት ከእስረኞች እንደተገለጸላቸው ያመለከቱት ምንጮች እንዳሉት ፍተሻው የእያንዳንዱን የእስረኛ ክፍል ያካተተ ነበር፡፡ በዚህም ወቅት የእስረኞች ማስታወሻዎችና ሌሎች […]

በዛሬዉ እለት የህዝብ ታዛቢ በመሆን ሊያገለግሉ የሚችሉ ሰዎችን ለማስመረጥ በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት/አካላት፤አመራሮችም ጭምር በተለያዩ የምርጫ ጣብያዎች እንደተገኙ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡የታዘቡትን እያካፈሉን ሲሆን እኔም ያየሁትን ላካፍል ወደድኩ፡፡የታዘብኩት የየካ ክ/ከተማ ወረዳ ዘጠኝን ነዉ፡፡መቐለ ከተማ ወረዳ ሓዉልቲ ያለሁ ነበር የመሰለኝ፡፡አስተባበሪዎቹ፤የወረዳዉ ካድሬዎች፤የአንድ ላምስት አስተባባሪዎች፤በሰፈሩ የማዉቃቸዉ ደህንነት ነን ባዮች ወዘተ ከተጠራዉ ህዝብ በቁጥር አያንሱም፡፡የሚሉትን በሙሉ እኔና ታዛቢ አድርጌ የወሰድኩት የማይጨዉ […]

“የታዛቢዎችን ምርጫ ለማወክ ተንቀሳቅሳችኋል::” – ፖሊስ ===== Minilik Salsawi
ዛሬ በየቀበሌው የሚካሄደውን የታዛቢዎች ምርጫ ተከትሎ ወደ ሚኖሩበት ጉለሌ ክፍለከተማ ወረዳ 3 ያመሩት የሰማያዊ አባላቶቹ ኢየሩሳሌም ተስፋው እና እመቤት ግርማ የታዛቢዎችን ምርጫ ለማወክ ተንቀሳቅሳችኋል በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የምርጫ ታዛቢ መሆን የሚችሉት ገለልተኛየሆኑ እንጂ የኢህአዴግ አባላት የሆኑ አይደሉም በሚል ባነሱት ክርክር ምክንያት ለማወክ እየሞከራችሁ ነው በሚል ፖሊስ ሊይዛቸው ችሏል፡፡

Image

ከኛ በላይ ላሳር ከኛ በላይ አዋቂ የለም የሚል አመለካከት ይዞ ከመክነፍ የህዝብን ጥያቄ መሰረት አድርጎ ተቀራርቦ በመነጋገር እና በመወያየት ሃገራዊ ማኒፌስቶ በማምጣት የጋራ ሃገራዊ አጀንዳ በመቅረጽ ለለውጥ መትጋት ግዴታ ነው::አንድነት ሃይል ነው የሚለው ብሂል ለሃገራዊ አጀንዳ መተግበር ትልቅ አስታውጾ አለው::የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ይህ ሳይታለም የተፈታ እና የሁሉም የነጻነት ፈላጊ ሃይሎች ጥያቄ ነው። ያዳምጡ :: […]


ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–

በጎንደር የነገሡት የኢትዮጵያ ነገሥታት በታሪካዊ ሚናቸው በእኩል ሚዛን ላይ አይቀመጡም፡፡ አንዳንዶቹ በሰሩት ስራ ስማቸው ዘመንን ተሻግሮ ይዘከራል፡፡ አንዳንዶቹ ግን ስልጣን አልባ ሆነው በስም ብቻ “ንጉሥ” እየተባሉ ይጠሩ ነበር፡፡ የሁላቸውንም ታሪክ መዘርዘር የኛ ዓላማ ባለመሆኑ እርሱን ለታሪክ መጻሕፍት እንተወው፡፡ ለበረካ ያህል ግን ሁለት ነገሥታትን በትንሹ እናውሳቸው፡፡
===ተረት መሳዩ ንጉሥ===
ከስሙ ጀምሮ ሁለመናው ይገርማል፡፡ ታሪኩ እንደ ተረት ያስደምማል፡፡ አንዳንዴ የሚሰራቸው ነገሮች ደግሞ ከባግዳዱ ኸሊፋ ሀሩን አል-ረሺድ ጋር ያመሳስሉታል፡፡
ይህ ንጉሥ “ባካፋ” ይባላል፡፡ አጼ ባካፋ የነገሠው በአድማ ነው፡፡ አጼ ዳዊት ሳልሳዊ በሚባለው ወንድሙ ላይ አምጾ ነው ስልጣንን የተቆጣጠረው፡፡ ታዲያ ለአመጽ ሲነሳ መጀመሪያ ላይ በለስ አልቀናውም፡፡ በውጊያ ስለተሸነፈ ራሱን ሸሽጎ ከአንድ ደብር ለመኖር ተገደደ፡፡ በዚያ ደብር እያለም በአንድ መምህር ስር ቅኔና ዜማ መማር ጀመረ፡፡ እያደር ከዚሁ መምህር ጋር ሚስጢረኛ ሆነ፡፡ ታሪኩንም አንድ በአንድ አጫወተው፡፡
  በአንድ ውድቅት ሌሊት እርሱና መምህሩ ለመጸዳዳት ይወጣሉ፡፡ እዚያ እያሉም ባካፋ ለመምህሩ “መሪጌታ! የኔን ነገር እንዴት ነው የሚያዩት?.. ይህንን ወንድሜን አሸንፌ መንገሥ የምችል ይመስልዎታል?” የሚል ጥያቄ አቀረበ፡፡ መምህሩም “የምትነግሥ ይመስለኛል፤ ነገር ግን ጸሎት ማብዛት አለብህ፣ በጸሎት ሀይል የማይቻል የለም፤ ታዲያ ቀኙ ያንተ ሆኖ አልጋውን በወሰድክ ጊዜ እኔን እንዳትረሳኝ” አለው፡፡ ባካፋም በፍጹም ላይረሳው ቃል ገባለት፡፡
   ዓመታት አለፉ፡፡ ባካፋም ወንድሙን ድል አድርጎ ነገሠ፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ድሪቶ የለበሰ ባላገር መጥቶ ከቤተ መንግሥቱ ፊት ቆመ፡፡ ዘበኞቹንም እንዲህ የሚል መልዕክት ለባካፋ እንዲያደርሱለት ለመናቸው፡፡
“ታስታውሳለህ ባካፋ የተባባልነውን
እኔ የአብረሃምን አባት ሆኜ አንተ ሚስቱን”
   ዘበኞቹ የባላገሩን ንግግር እንደ እብድ ወሬ ቆጠሩትና ለባካፋ ላለመንገር ለገሙ፡፡ አንዱ “ነቄ” ዘበኛ ግን ሰውዬው ቅኔ የተናገረ ስለመሰለው “ንጉሡ መልዕክቱን መስማት አለባቸው” በማለት ወደ አጼ ባካፋ ሄዶ ተናገረ፡፡ ባካፋም “እንዴ?! የቅኔ መምህሬ ናቸው፤ በቶሎ አስገቡልኝ” በማለት ዘበኞቹን አዘዛቸው፡፡ በዚህ መንገድ ባካፋ ከጥንቱ መሪ ጌታ ጋር ተገናኘ፡፡ ያኔ የገባውንም ቃል ተግባራዊ አደረገ፡፡
  በነገራችን የቅኔውን ሚስጢር አግኝታችሁታል አይደለም?… የአብረሃም አባት “ታራ” ነው፡፡ የአብረሃም ሚስት ደግሞ “ሳራ” ናት፡፡ ስለዚህ መምህሩ ለማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት “እኔ ሳራ አንተ ታራ” የሚል ነው፡፡ ይህም ሁለቱ ሰዎች ሲጸዳዱ ያደረጉትን ውይይት የሚያስታውስ ነው፡፡
*****
    በሌላ ጊዜ ደግሞ ባካፋ እንደ ባግዳዱ ኸሊፋ “ሃሩን አል-ረሺድ” ማንነቱን ቀይሮ ሀገሩን ይጎበኝ ነበር፡፡ ከአንድ ምንጭ አጠገብ ሲደርስ አንድ እረኛ ገጠመውና “የዚህ ሀገር ንጉሥ እንዴት ነው?” አለው፡፡ እረኛውም “ጥሩ ነው፤ ተስማምቶናል፤ ሀገሩ ጥጋብ ነው፤ ደሀን አይበድልም” የሚል መልስ ሰጠው፡፡ ይሁንና ባካፋ ሆን ብሎ እረኛውን መተንኮስ ጀመረ፡፡ “ምን ጥጋብ ነው ትላለህ? እንዲህ ዓይነት ግፈኛ ንጉሥ ነግሦም አያውቅ፤ ደሀውንም እንደርሱ የሚበድል የለም” አለው፡፡ እረኛው “ሰውዬ! እኔ አልዋሸሁም፤ ይህንን ነገረኛነትን ተወኝ፤ ምላስህን ያዝልኝ” አለው፡፡ ባካፋ ግን ትንኮሳውን ቀጠለ፡፡ በዚህ ጊዜ እረኛው ሽመሉን መዝዞ “እምቢ ካልከኝ በዚህ ዝም ትላለህ” በማለት ባካፋን እስኪበቃው ድረስ ደበደበው፡፡
     ከሳምንት በኋላ እረኛው ወደ ቤተመንግሥት ተጠራ፡፡ “ለምን” ብሎ ቢጠይቅ መልስ አልተሰጠውም፡፡ በመሆኑም ፍርሃት ወረረው፡፡ “ምን አጥፍቼ ይሆን?” እያለ ተጨነቀ፡፡ እንዲሁ በጭንቀት እንደተወጠረ ቤተመንግሥት ሲደርስ ከሳምንት በፊት የደበደበው ሰውዬ በዙፋን ላይ ቁጭ ብሎ አገኘው፡፡ እረኛው የባሰውኑ ተርበተበተ፡፡ ይሁንና ንጉሡ የፈገግታ ምልክት ሲሰጠው ልቡ መለስ አለችለት፡፡ ንጉሡም እንዲህ አለው፡፡
  “ከሳምንት በፊት ላሳየሁ ሐቀኝነት አንድ መቶ ከብቶችን ተሸልመሃል”
===የቤተመንግሥቱ ጭውውትና ታሪክ ቀያሪው ፋኖ====
አሁን ደግሞ በጎንደር ቤተ-መንግሥት የተደረገ አንድ ጭውውት እንጥቀስላችሁ፡፡
1ኛ ተናጋሪ (እቴጌ መነን)
አረ ለመሆኑ ምን ይሆን አሳቡ
ሸፍቶ የሄደው ከነቤተሰቡ?
*****
2ኛ  ተናጋሪ (ራስ ዓሊ)
ሰውዬው ኩሩ ነው የተነፋ ልቡ
ይዞ ማዋረድ ነው ይበርዳል ጥጋቡ::
*****
3ኛ ተናጋሪ (አንድ መነኩሴ)
ሰውዬው ብርቱ ነው ስሙ የተጠራ
ጎበዝ እኔ ነኝ ባይ ሀይልን የማይፈራ
በዘዴ በትዕግስት ማባበል ይሻላል
በሀይል ብንለው በጣም ያውከናል፡፡
*****
4ኛ (እቴጌ መነን)
እንዲህ ስትሉ ነው ስሙ የገነነው
የፈራነው መስሎት አገር የሚያብጠው
ዘዴ መላ አታብዙ ጦር ይታዘዝና
ቢቻል ከነነፍሱ ይምጣ ይያዝና
እምቢ ካለም ይሙት በገዛ ጥፋቱ
ላንድ ወንበዴ ሽፍታ አይስጋ መንግሥቱ፡፡
*****
  ይህ ጭውውት በ1840ዎቹ በጎንደር ቤተመንግሥት እልፍኝ ከተደረገ ምክክር የተቀነጨበ ነው፡፡ ይህም “ቴዎድሮስ” በተሰኘው የደጃች ግርማቸው ተክለሃዋሪያት መጽሐፍ የመጀመሪያ ገጽ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ በጭውውቱ ውስጥ “ለምን ሸፈተ” ተብሎ እንደ አጀንዳ የቀረበው የያኔው ደጃች ካሳ ሀይሉ ጉዳይ ነው፡፡ በዚያን ወቅት ካሳ ሀይሉ ከተራ ቤተሰብ ተወልዶ በአስገራሚ ሁኔታ የቤተ መንግሥቱ አባል ሆኖ ነበር፡፡ ታሪክ አለው፡፡
  
ደጃች ካሳ በወጣትነቱ ሽፍታ ሆኖ በቋራና በደምቢያ ይዘዋወር ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ ኢትዮጵያዊያን ሱዳንን ከሚቆጣጠሩት የቱርክ/ግብጽ ገዥዎች ጋር የድንበር ላይ ውጊያ ያካሄዱ ነበር፡፡ ታዲያ በአንዱ ውጊያ ላይ የዘመኑ ዋና መስፍን የነበሩት የራስ ዓሊ ልጅ የሆነችው ወይዘሪት ተዋበች ተማረከች፡፡ ይህም ወሬ ለካሳ ጆሮ ደረሰ፡፡ ካሳ በወቅቱ ሽፍታ ቢሆንም የኢትዮጵያዊያን መሸነፍና በምርኮ መጋዝ በጣም አበሳጨው፡፡ በመሆኑም በቱርኮች ላይ ድንገተኛ አደጋ ጥሎ አተረማመሳቸው፡፡
  ካሳ ይህንን ሲያደርግ ተዋበች ምርኮኛ መሆኗ በቁጭት ውስጥ ጥሎአት በመርዝ ጩቤ ሰውነቷን ወግታ ራሷን ለማጥፋት ሙከራ በማድረግ ላይ ነበረች፡፡ ይሁንና ካሳ በቦታው ደርሶ መርዙ ወደ ሰውነቷ ጠልቆ ሳይገባ ከደሟ ውስጥ መጥጦ ተፋው፡፡ በዚህም የተዋበች ህይወት ተረፈች፡፡ ካሳም ተዋበችን በጀርባው አዝሎ ከውጊያው ስፍራ እየሮጠ ወጣ፡፡ ወታደሮቹም በቶሎ እንዲያፈገፍጉ ትዕዛዝ ሰጣቸው፡፡
   ካሳ ነፍሲያዋን ያተረፈላትን ተዋበችን ለአባቷ ለራስ ዓሊ አስረከባት፡፡ ራስ ዓሊም በጀግንነቱ ተደስተው እሷኑ ዳሩለት፡፡ ሽፍትነቱን ትቶ በቤተመንግሥት እንዲኖርም አደረጉት፡፡ ይሁንና የቤተመንግሥቱ ህይወት በነጻነት መኖርን ለለመደው ካሳ የግዞት ያህል ሆነበት፡፡ በዚያ ላይ መኳንንቱ “የኮሶ ሻጭ ልጅ” እያሉ የሚያሳዩት ንቀት በጣም አቃጠለው፡፡ ተዋበችም በባሏ ላይ በሚደርሰው ንቀትና ማሽሟጠጥ በገነች፡፡ እናም በአንድ ውድቅት ላይ “አንተ ካሳ! ጎራዴህን ታጠቅና ተነሳ፤ ምንጊዜም ከጎንህ ነኝ” አለችው፡፡ ካሳም ሸፈተ፡፡
*****
  እንግዲህ ከላይ የቀረበው ጭውውት ካሳ በሸፈተ በማግስቱ የተደረገ ነው፡፡ በዚያ ቀን በተደረገው ምክክር ደጃች ወንድይራድ የካሳን እጅ ይዞ እንዲመጣ ታዘዘ፡፡ ወንድይራድም ከቤተመንግሥቱ ቀርቦ እየጎረነነ ትዕዛዝ መቀበሉን አረጋገጠላቸው፡፡ ይሁንና ከልክ ያለፈው የወንድይራድ ጉራ ያልጣማቸው ራስ ዓሊ “አንተ ወንድይራድ! ካሳ እንደ ሌላው ሽፍታ አይምሰልህ፤ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው አደገኛ ተዋጊ ነው” በማለት ምክር ቢጤ ቢወርውሩለት ዳጃች ወንድይራድ እንዲህ የሚል የንቀት መልስ ሰጣቸው፡፡
አይስሙ ጌታዬ ሰው የሚለውን
አያስፈራም ካሳ ይንዛ ጉራውን፡፡
ገና መጣ ሲሉት አገር ጥሎ ይሸሻል
ወይንም ካንዱ ደብር ገብቶ ይደውላል፡፡
እንኳን አንድ ሽፍታ ቀማኛ ወንበዴ
ብዙ እመልሳለሁ በጦር በጎራዴ፡፡
እኔ ነኝ ወንድይራድ ታማኝ አሽከርሽ
ያን የኮሶ ሻጭ ልጅ የምቀጣልሽ፡፡
    የወንድይራድ ፉከራና ድንፋታ ከካሳ ጆሮ ገባ፡፡ ካሳም “እናቴን እንዲህ የሰደበውን ባለጌ ባላሳየው እኔ ካሳ አይደለሁም” በማለት መሃላውን አስቀመጠ፡፡ ሁለቱ ሀይሎች ተገናኙ፡፡ ውጊያው ገና ከመጀመሩ የወንድይራድ ፉከራ የአሸዋ ላይ ቤት ሆኖ ፈረሰ፡፡ እቴጌ መነን (የራስ ዓሊ እናት) የተመኩበት ዳጃች ወንድይራድም ተማረከ፡፡ ካሳም መሃላውን ተግባራዊ አደረገ፡፡ ወንድይራድን ቀንና ማታ ኮሶ እያጠጣው ገደለው፡፡
   ከዚያ በኋላ ካሳ በሀገሩ ላይ ገነነ፡፡ ማን ይቻለው እንግዲህ? ደጃች ውቤም ሆኑ ራስ ዓሊ፣ ደጃች ተድላ ጓሉም ሆኑ ደጃች ጎሹ ሁሉም ተራ በተራ ተሸነፉ፡፡ ካሳን ያሸንፋሉ ተብለው የተጠበቁት እቴጌ መነንም በናቁት አማቻቸው እጅ ምርኮኛ ሆነው ወደቁ፡፡ የጥንቱ የቋራ ሽፍታም “ዳግማዊ ቴዎድሮስ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ” ተብሎ ነገሠ፡፡ ንጉሥ ለስሙ ብቻ ቤተመንግሥት የሚቀመጥበት ዘመነ መሳፍንትም አበቃ፡፡ ኢትዮጵያም አዲስ ታሪካዊ ጉዞዋን ተያያዘችው፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ግንቦት 23/2007
አዳማ
——
(ማስታወሻ፡ ይህ ጽሑፍ ከቀጣዩ መጽሐፌ የተቀነጨበ ነው፡፡ ጽሑፉን በኢንተርኔት ማውጣት ቢቻልም በየትኛውም የህትመት ሚዲያ ማተም ክልክል ነው)
Afendi Muteki is a researcher and author of the ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his blog and his facebook page by clicking the following links

በአድባራት አለቆች ላይ የተላለፈው ውሳኔ ‹‹ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ነው›› /ፓትርያርኩ/ ‹‹ቤተ ክርስቲያናችን በቂ ሕገጋት አሏት፤ ማእከሉ ተጠብቆ ሊሠራባቸው ይገባል፤›› /ሲኖዶስ/ ልዩ እና አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ስለ መጥራት ምክክር መደረጉ ተጠቁሟል (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፸፱፤ ታኅሣሥ ፲፩ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፣ ‹‹በቤተ ክርስቲያን አባቶች እና …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

2014 ዓም የዓለም አቀፉ ትኩረት በአፍሪቃ ላይ ያረፈበት ዓመት ነበር። ዓመቱ አራተኛው የአውሮጳ ህብረት እና የአፍሪቃ ጉባዔ፣ የመጀመሪያው የዩኤስ እና የአፍሪቃ መሪዎች ጉባዔ የተካሄደበት፣ ከፍተኛ የአፍሪቃ ባለሥልጣናት

ታኀሳስ ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በትላንትናው እለት በባህርዳር ከተማ በተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ የገዢው መንግስት ወታደሮች በህዝቡ ላይ እያደረሱ ያለውን ተመጣጣኝ ያልሆነ  እርምጃ የባህርዳር ከተማ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች በአስቸኳይ እንዲያቆም በሰጡት መግለጫ ጠይቀዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ የሃይማኖት አባቶችን ከሁለት ቀን በፊት በመሰብሰብ በመስቀል አደባባይ ላይ ሊሰሩት ያሰቡትን ጉዳይ እንዳወያዩዋቸው የገለጹት የሃይማኖት አባቶች …

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ) አንድነት – በባህርዳር ከተማ በንፁሀን ዜጎች ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ያደረሱ በህግ ፊት ይቅረቡ! ********************************************************************** ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ *********************************************************************** አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በትናንትናው ዕለት ታህሳስ 10/ 2007 ዓም በባህርዳር ከተማ መንግስት ኃይሎች የጥምቀት ክብረ በዓል ታቦት የሚያርፍበትን ቦታ […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የ2ዐዐ7 ዓ.ም አገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍና ለዚህም መተማመኛው ሕዝቡ መሆኑን ገልፀ ‹‹ተደራጅ 2007 ለለውጥ›› በሚል መፈክር አንግቦ አገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትና ኢህአዴግን በቃህ ለማለት ሌት፣ ከቀን በንቃትና በትጋት እየሠራ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት ነፃ ሚዲያ በታፈነበትና በተዘጋበት አንድነት የራሱን የማተሚያ ማሽን ገዝቶ በየጊዜው ሆን ተብሎ በሚመስል መልኩ በሚጠፋው የኤሌክትሪክ ችግርን ለማሸነፍ የራሱን […]

ሞክረው ( ሄኖክ የሺጥላ )

ትናንት ባህርዳር ላይ አማሮች ተገደሉ ፣ ከትናንት በስትያ አምቦ ላይ ኦሮሞዎች ፣ ከዛ በፊት ጋምቤላ ላይ ፣ ከዛ በፊት አርባ ጉጉ ላይ ፣ ከዛ በፊት በደኖ ላይ ፣ እያለ እያለ ይቀጥላል ። በዘር የከፋፈልነው ሬሳ ኢትዮጵያዊ መሆን ያቃተው ለምን እንደሆነ ባላውቅም አንተ አዛኝ ቅቤ አንጉዋች ግን ምን ታመጣለህ ። ግፋ ቢል ሁለት ገጽ የ ፒዲ -ኤፍ ( PDF ) መግለጫ ታወጣለህ ፣ ትንሽ ትዝታለህ ፣ ትንሽ ትሳደባለህ ፣ አይቀርም በቅርብ ምናምን ብለህ ተስፋ ትሰጣለህ ፣ ግድያው ይቀጥላል ።

ውስጥ ውስጡን የሸዋ አማራ ለኢትዮጵያ ጂው ነው ፣ ወይጦው ጅን ነው ፣ ጎጃሜው አድር ባይ ነው ፣ ጎንደሬው ሲፋቅ ትግሬ ነው ፣ መንዜው በጥርሱ እየሳቀ ገዳይ ነው ፣ ወዘተ ወዘተ ትላለህ ። ውጭ ውጩን የአማራ ታጋይ!!!
ኦሮሞውም ጋ እንዲህ ነው ፣ ወለጋ ኮለል ያለ የጠራ ኦሮሞነት መስፈሪያ ነው ፣ የሰላሌ ኦሮሞ አማራነት ያለቀቀው ኦሮሞ ነው ፣ የሸዋ ኦሮሞ ኦሮሞ አይደለም ፣ የባሌ ኦሮሞ ለ አረብነት ይቀርባል እና ወዘተ፣ ውስጥ ውስጡን ልብህን ያደነደነው ነገር ነው ። ዝለዚህ ከዚህ በሽታህ እስካልዳንክ ድረስ ግድያው ይቀጥላል ፣ አንተም መግለጫ እየሰጡ መኖሩን ትቀጥላለህ ።

ስልጤውም ጋ ፣ ሶዶ ጎርደናውም ጋ ፣ ሰባት ቤቱም ጋ ፣ ቅማንቱም ጋ ( ቅማንት የሚባል ነገር ካለ ) ፣ ይሄ በሽታ አለ ። ይሄን በሽታህን ፣ ይሄን የመከፋፈል ነቀርሳህን ሳትድን ፣ ከቁጭት ውጭ ምንም አታመጣም ። አንዳች ለውጥ በሀገርህ ምድር አይፈነጥቅም ።

እስኪ አምላክ ያሳይህ ትናንት በ ሰሜን ጎንደር ቅማንት እራሱዋን በራሱዋ ታስተዳድር ዘንድ አንዳንድ ሽር ጉዶች እየተደረጉ እንደሆነ ሰማን ፣ መቼም መስማት እምቢ አይባልም ፣ ከመሃል ጎንደር እስከ መተማ ጎንደር ልጆቿን ልትበላ ይኸው ሌላ ውርጅብኝ ሊወርድባት ነው ። አንተ ግን ይሄን ሁሉ የሚያረገው ከትግሬ ክፍለ ሀገር የመጣ ከይሲ ስርዓት ነው ማለት ልብህ ይፈራል ።ጠላቶችህን በስማቸው ለመጥራት ልብህ ይራራል ።

ሌላም ታሪክ ልንገርህ
ጅማ ላይ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያስቀድሱ የተገደሉትን ሰዎች አይተካል ፣ ታዲያ ማን ይመስልሃል ገዳዩ ? ኦሮሞዎች ? አይደለም ! አየህ ያንተ ችግር ይሄ ነው ወያኔ እንድታስብ የሚፈልገውን ነው የምታስበው ፣ ግድያውን የፈጸሙት ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ሊሆኑ ይችላሉ ፣ ድርጊቱን ያሴረው ግን አሁንም የትግሬ ወያኔ ነው ፣ ወንድም በወንድሙ ላይ እንዲነሳ ያደረገው ። ጅማማ እኮ ጂማ! የሰቃ ጨቆርሳ ሀገር! የጌራ ሀገር! የጉማ ሀገር! የጎማ ሀገር! የሊሙ ሂናሪያ ሀገር! አምስቱ የጊቤ መንግሥታት የለመለሙባት ምድር!!
ጅማ! የአባ ሚዛን ሀገር! የአባ ቆሮ ሀገር! የአባ ገንዳ ሀገር! የአባ ዱላ ሀገር! በኦሮሞ ምድር የዘመናዊ ቢሮክራሲ ጥንስስ የተጀመረባት ሰፈር!
ጅማ! የአቦል ሀገር! የበረካ ሀገር! የቃህዋ ጀባ ሀገር! ለስምንት መቶ ዓመታት ተወዳጅነቱ ሳይቀንስ የዘለቀውን “ቡና”ን ለዓለም ያበረከተች የሙሐባ መንበር!! ጅማ! የተሚማ ሀገር! የገሜቲ ሀገር! የአያንቱ ሀገር! የአስሊያ ሀገር! የበድሪያ ሀገር! የፈይሩዝ ሀገር! ውብ ልዕልታትና ወይዛዝርት የወጡባት ምድር!! ነች ይላታል ጸሐፊው ፣ ጅማ ይህንን አታደርግም ፣ ጅማ ላይ አታቂም ፣ አይንህን ወደ ሰሜን ፣ ልብህን ወደ ትግሬ ወያኔ አዙር !

ይገሉሃል አንተ ግን ባጉል ፍቅር ታጥረሃል ፣ ያጠፉሃል አንተ ግን የትግሬ ወያኔ አጥፊህ መሆኑን መናገር ትፈራለህ ፣ መነኩሴ በጥይት ሲመቱ አንተ ዘረኛ እንዳትባል ትፈራላህ ፣ ሀጻናት ሲገሉ አሁንም በስማቸው ለመጥራት ትፈራለህ ፣ ማን እንደሆኑ እያወቅህ ” እነ አከሌ ” ለማለት በጣም ትፈራለህ ፣ በልብህ ትታበያለህ ፣ በአንደበትህ ትስታለህ ፣ በልቦናህ ግን ከራስህ ጋ ትነጋገራለህ ። ጠላትህን በስሙ እስካልጠራኸው ድረስ አታሸንፍም ፣ ጠላትህን እስካላስገለልከው ድረስ በፍጹም ነጻ አትሆንም ። ገዳዮችህ ሩቅ አይደሉም፣ ብዙዎቹ ያንተ ጎረቤቶች ናቸው ፣ ካንተ ጋ እየበሉ ፣ ካንተው ጋ እየጠጡ የሚውሉት የትግሬ ወያኔዎች ናቸው ይሄን ሁሉ በደል እያደረሱ ያሉት ፣ ይሄንን አንተ አታውቅም ብዬ አላስብም ፣ እርግጥ በደንብ ታውቃለህ ግን እውቀትህ ከውስጥ የማይወጣ የጋን መብራት አይነት ሆነብኝ ፣ ጠላትህ ለመለየት አተኩረህ እየው ( ግንባሩን እየው አላልኩም ) ግንባሩ ፍንጭ ከሰጠህ ማየት መብትህ ነው ፣ ግን አተኩረህ ካየኸው ታውቀዋለህ ። እሱ አንተን ለማጥፋት አንዳች ይሉኝታ የለውም ታዲያ ያንተ የሉኝታ ከወዴት የመጣ ይሆን ። ነገርኩህ እኮ እነሱ ( የትግሬ ወያኔዎች ) ሊገሉህ ኢያሰቡም እንኩዋ ይወልዱልሃል ። ግማሹ ጦርነት ጠላትን ማወቅ ነው ይላሉ አንዳንድ አዋቂዎች ፣ ይህ ትልቅ እውነት ነው ፣ የተቀረው ግማሹ ደሞ ጦርነት መግጠም እንዳይመስልህ ፣ የተቀረው ራስን ማወቅ ነው !

ጠላትህን እስካለየህ ድረስ ጠላትህን አታሸንፈውም ! ይሄ የ ስደት ፖለቲካውን እርሳው ፣ ለአፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል ነው ፣ አንተ ግን ጠላትህን በስሙ ጥራው ። የትግሬ ወያኔ ጠላቴ ነው በል ፣ እሱን ማለት ስትጀምር ማሸነፍ ትጀምራለህ ። ሞክረው! ሞክረው ! ሞክረው !

በመግለጫ ነገር መወራወር የጀመሩት የተቃዋሚ ፓርቲእ አንድነት እና የወያኔው ምርጫ ቦርድ መላተም መጀመራቸውን ከዙሪያቸው የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ በዚህም መሰረት የኢሕአዴግ ተቋም የሆነው የምርጫ ቦርድ አንድነት እና መኢአድን ከ2007 ምርጫ ውጪ ለማድረግ ዳር ዳር እያል ነው ሲሉ አንድ የአንድነት ከፍተኛ አመራር ጽፈዋል:: ከፍተኛ አመራሩ በጽሁፋቸው እንዳሉት የኢህአዴግ ጎፈሬ ከማበጠር ውጪ ምንም ፋይዳ የሌለው “የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ” አንድነትንና በመኢአድን በምርጫው እንዳይወዳደሩ ለማድረግ ላይና ታች እያለ ይገኛል ያሉት አመራሩ እነዚህ ፓርቲዎች ባለፈው ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም. ውህደት ለመፈፀም ተስማመተው የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰው የነበረ ቢሆንም፤ ውህደቱን የከለከለውና እንዲሰናከል ያደረገው ይሄው ምርጫ ቦርድ ተብዬው የመሸጦ ተቋም ነበር። በማለት በጽሁፋቸው አስፍረዋል::

አሁን ከየትኛውም ጊዜ በላይ ግልፅ እየሆነ ያለው ነገር የዚህ ምርጫ ቦርድ ዋና ዓላማ ፓርቲዎች ተጠናክረው እንዳይወጡ መከላከልና የኢህአዴግ ወንበር መጠበቅ እንደሆነ ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም።ያሉት አመራሩ አያይዘውም ከእንግዲህ ይለይልናል ሲሉ አስጠንቅቀዋል::

ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ከአሁኑ እንዲጀምር እድል ተፈጥሯል ማለት ነው። አሁን ነው ወገብን ጠበቅ አድርጎ አመራር ለመስጠትና ለመታሰር ዝግጁ መሆን የሚያስፈልገው። እኛ የምንችለው ሁሉ አድርገናል ከዚህ በኋላ የፈለገው ቢሆን የሚፀፅተን ነገር አይኖርም።ሲሉ ህዝቡ ለህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲዘጋጅ እድሉን እንዲጠቀምበት መሪ በመሆን የሚፈለግባቸውን ድርሻ ለመወጣት ፓርቲያቸው መዘጋጀቱን አሳውቀዋል::

የአንድነት አመራሩ እንዳሉት ፓርቲዎቹ በምርጫው እንሳተፋለን ሲሉ፤ ምን አስበው ነው ተብሎ የለም አትሳተፉም የሚባል ከሆነ ይህን መብታቸውን ለማስጠበቅ ተባብረው ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ማካሄድ ግድ ይላቸዋል ማለት ነው። መቼም ዘንድሮ በኢህአዴግ ቤት ማሰቢያው ጨርሶ እንደጠፋ ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም፤ እዚያ ቤት ግን የተፈጠረው ነገር ምን ይሆን? ሲሉ ጽሁፋቸውን ድል የህዝብ መሆኑን በመግለጽ አጠቃለዋል::
Image

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የ2ዐዐ7 ዓ.ም አገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍና ለዚህም መተማመኛው ሕዝቡ መሆኑን ገልፀ ‹‹ተደራጅ 2007 ለለውጥ›› በሚል መፈክር አንግቦ አገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣትና ኢህአዴግን በቃህ ለማለት ሌት፣ ከቀን በንቃትና በትጋት እየሠራ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት ነፃ ሚዲያ በታፈነበትና በተዘጋበት አንድነት የራሱን የማተሚያ ማሽን ገዝቶ በየጊዜው ሆን ተብሎ በሚመስል መልኩ በሚጠፋው የኤሌክትሪክ ችግርን ለማሸነፍ የራሱን ከፍተኛ ኃይል ያለው ጀነሬተር በመግዛት በሣምንት የራሱን ጋዜጦችን እያተመ እያንዲያሰራጭ ተገዷል፡፡ ምሁራን፣ ወጣቶች፣ ጋዜጠኞችና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለወሳኑ የ2ዐዐ7 ምርጫ ትግል እየተቀላቀሉት ይገኛሉ። አንድነት በአሁኑ ሰዓት ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉን በአግባቡ ለመምራትና ለውጥ ለማምጣት በተሻለ ቆመና ላይ ነው ያለው።

በምርጫ ቦርድ በአንድት ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ ሆነ በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ የሌለውን የጠቅላላ ጉባኤ አባላትና የምላተ-ጉባኤ ቁጥር በተሻሻለው ደንባችን ውስጥ እንድናካትት የተወሰነብንን ፈርድ ገምድል ድርጊት ሕገ-ወጥ መሆኑን ብናውቀውም ጠቅላላ ጉባኤ መጠራትን እንደ ጉዳት ሳይሆን አንደ ልዩ እድል በመቁጠር፣ 32ዐ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት በመጥራት የምርጫ ቦርድ ተወካይ በተገኘበት የተሳካና አንፀባራቂ ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደናል፡፡ የጠቅላላ ጉባኤውንም ሰነድ ታህሣሥ 1ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም ለምርጫ ቦርድ ገቢ ተደርጓል፡፡

ሁሉ እንደሚገነዘበው በአሁኑ ሰዓት ሕዝቡ በኑሮ ውድነትና በሥራ እጦት ከመሰቃየቱም በላይ ሙስና ሰፍኗል፤ መልካም አስተዳደር የሕግ የበላይነት ከቶውንም ጠፍቷል፡፡ የሕዝብ የነፃነትና የዴሞክራሲ ጥያቄ ገዝፎና አፍጥጦ እየመጣ ነው፡፡ በመሆኑም ኢህአዴግ በፍርሃትና በጭንቀት እየራደ ነው፡፡ ምረጡኝ ብሎ ሕዝብ ፊት ለመቅረብ የሚያስችለው የፖለቲካና የሞራል ኃይል ስለሌለው ውሸት፣ ማስፈራራት ማሰር መግደል ማሸነፊያ መሣሪያዎች እንዳልሆኑትም በግልጽና በትክክል ተደራጅቷል፡፡ አሁን የቀረው ማሸነፊያው መንገድ አንድነት ፓርቲን በመዝጋት ነው የሚል ድምዳሜ ላይ በመድረሱ ጥንቱንም የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች የሆነውን ወኪሉን በመጠቀም በአንድነት ላይ ዘመቻ ከፍቷል፡፡

ታህሣሥ 1ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓም በምርጫ ቦርድ ከፍተኛ አመራር የተሰጠው በቅጥፈትና በውሸት የተሞላው መግለጫም የሚያሳየውና የሚመሰክረው ይህንኑ ነው፡፡ ነገር ግን እውነቱን በአጭሩ እንደሚከተለው እናስቀምጣለን፡፡

አንድነት ፓርቲ ታህሣሥ 19 እና 2ዐ ቀን 2ዐዐ6 ዓም ያካሄደውን የጠቅላላ ጉባኤ ሰነድ ለምርጫ ቦርድ ካስገባ በኋላ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 2ዐ ቀን 2ዐዐ6 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ በዘጠኝ ነጥቦች ላይ ማብራሪያ እንድንሰጥ ጠይቄን መልስ ሰጠን፤ በመቀጠልም ጥቅምት 2ዐ ቀን 2ዐዐ7 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄ ከዘጠኝ ወደ ሦስት አውርዶ ላከልን ለዚህም አንድነት መልስ ሰጠ፡፡ ቀጥሎም ቦርዱ ህዳር 1ዐ ቀን 2ዐዐ7 በተፃፈ ደብዳቤ ጥያቄውን ወደ አንድ አወረደው እንዲያውም በመጨረሻ ህዳር 19 ቀን 2ዐዐ7 ዓም በተፃፈ ደብዳቤ፡፡ ‹‹ፓርቲው በሰጠው ምላሽ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ብዛት 32ዐ እንደሆነ አሳውቋል፡፡ ይሁን እንዷ በተሻሻለው መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ አካቶ ያላቀረበ በመሆኑ ይህንኑ አሟልታችሁ እንድታቀርቡ በአክብሮት እናሳውቃለን›› የሚል ነው፡፡ እኛም ጠቅላላ ጉባኤ ጠርተን ይህንኑ ጥያቄ እንዲሟላ ከማድረጋችንም ባሻገር በሕገ-ደንባችን መሠረት በብሔራዊ ም/ቤት ተመርጠው የነበሩት የፓርቲውን ፕሬዚደንት ሹመት በጠቅላላው ጉባኤ አፀድቀናል፡፡ እንጂ አይነቱን በሕገ-ደንቡና በሥነ-ሥርዓት ለተከናወኑ ጉዳዮች ያልተገባና የተሳሳተ መግለጫ መስጠት በጣም አሳኝ ነው፡፡ በተለይም የሕዝብ ታዛቢዎች ታህሣሥ 12 ቀን 2ዐዐ7 ዓ.ም እንደሚመረጡ እየታወቀ ይህን ዓይነት መግለጫ መስጠት ሕዝቡ በጥንቃቄና በተደራጀ ምልኩ ትክክለኛነትና ሀቀኞች የሆኑ ታዛቢዎችን እንዳይመርጥ ለማሰናከል የታቀደ ይመስላል፡፡ በመሆኑም ዛሬም ሆነ ነገ አንድነት ፓርቲ ከሕዝብ ጋር ሆኖ ትግሉን አጠንክሮ ይቀጥላል አባላትም ሆነ ሕዝቡ ከፓርቲያችን ጎን ተሰልፎ ትግሉን እንዲያጧጡፈው ከአክብሮት ጋር እንጠይቃለን፡፡
ድል የህዝብ ነው!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
ታህሣሥ 11 ቀን 2ዐዐ7 ዓም
አዲስ አበባ

-ዶ/ር ዳንኤል ተፈራና ዶ/ር ፀሀይ ለኢሳት ጋዜጠኛ ለአቶ ፋሲል የኔ ዓለም ስለ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ለሰጧቸው መልሶች የቀረበ አስተያየት- ከፈቃዱ በቀለ መግቢያ በቅርቡ ሁለት በአሜሪካን አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ኢኮኖሚስቶችን የኢሳት የቴሊቪዝን ጋዜጠኛ የሆነው አቶ ፋሲል የኔ ዓለም ኢትዮጵያ ከውጭ የምትበደረው ብድር መጠን እያደገ ስለመምጣቱና ስለኢኮኖሚው አጠቃላይ ሁኔታ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ በመጋበዝ በመሰላቸውና በሚታያቸው፣ እንዲሁም ከተማሩት […]

ሰብአዊ መበቶችን በመጣስ፣ ግፍ በመፈጸምና አፈናን በማጠናከር እደሜ የሚሸምት የአገዛዝ ሥርዓት የእያንዳንዱን ሰው መንፈሳዊና አካላዉ ጥንካሬ የማዳከም፣ ቅስምን የመስበርና ፍርሃትን የማንገስ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ሁሉ በብሶት የሚወለዱ፣ እምቢኝ ለግፈኞች፣ እምቢኝ ለአንባገነኖች፣ እምቢኝ ለነጻነቴ የሚሉ መንፈሰ ጠንካራ ጀግኖችንና ታጋዮችንም ይወልዳል:: የአለማችን ስመ ጥርና ዘመን የማይረሳቸው የነጻነት ታጋዮች እነ ማህተመ ጋንዲ፣ ማርቲን ሉተር ኪነግ፣ ማንዴላ፣ ኡንግ ሳን […]

Image

ህ.ወ.ሐ.ት 40ኛ ዓመት በዓሉ ለማክበር እያደርገው ያለው አከባበር ከመግለጼ በፊት የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች ለምን የትጥቅ ትግል መረጡ የሚለውን ትንሽ ለአንባብያን መረጃ ሰጥቼ ልለፍ፡፡ ህ.ወ.ሐ.ት የመሰረቱ ሰዎችና የትግራይ ወጣቶች ነፍጥ አንስተው ደርግን በጦርነት አስወግደው የደርግን ስርዓት ለመለወጥ የተነሱበት ዋናው ምክንያት ደርግ ዘውዳዊውን ስርዓት አሰወግዶ በትረ-ሥልጣኑ የጨበጠው ራሱ ታግሎ ያመጣው ለውጥ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሙሁራኖች፣ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች፣ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ አረሶ አደሮች፣ ወዝ አደሮች፣ የመንግስት ሰራተኞች ወ.ዘ.ተ በተደራጀና ባልተደራጀ መንገድ ያነሱት ዲሞክራሲያዊ ጥያቄ ዘወዳዊው ስርዓት ሊመልሰው ሰላልቻለ የበሰበሰው መዋቀሩ በመፍረክረኩ ደርግን ያን አጋጣሚ ተጠቅሞ ስልጣኑን ሊጨብጥ አስቻለዉ፡፡

እነዛ ዲሞክራሲያዊ ጥያቄ አንስተው ፤ዘውዳዊው ስርዓት ያፍረከረኩ ወገኖች ደርግ በግብታውነት በትረ ስልጣኑን በመያዙና እነዚ የህዝቦች ዲሞክራሳያዊ ጥያቄዎች ደርግ በሚድያና በዲኘሎማሲ በመደናገር የህዝባችን ጥያቄ በመቀልበስ ፀረ-ዲሞክራሲያዊ የሆኑ አምባገነን አዋጆች በማወጅ ህዝባዊ ማዕበሉን በማፈን ሁሉም ዓይነት ጥያቄዎች ገና በጥዋቱ ማፈን ጀመረ፡፡

ደርግ የአምባገነንነቱና ፋሽስታውነቱም መግለጫ የዘውዳዊው ስርዓት ከ60 በላይ ሚንስትሮች ፡ ጀኔራሎች በመሰበሰብ በጥይት ደብድቦ ገደላቸው ፤ የህዝቦች ሰለማዊ ትግል ደርግ በዜጎች ደም ታጥቦ ትግሉን አኮላሸው፡፡ በዚህም ምክንያት በኢትዮጵያ ህዝባዊ መንግሥት ሊመሰረት አልተቻለም፡፡ መድበለ-ፓርቲ ፡ ዩንር፣ሁሉም ዓይነት ዲሞክራሲያዊ መብቶች፣ የሃይማኖት ነፃነት፣ ፍትህና የህግ የበላይነት ይከበር፡ የሚሉ ጥያቄዎች መልሳቸው ልክ አሁን የህ.ወ.ሐ.ት/ኢህአዴግ መንግሥት እያደርገው ያለው ዓይነት እምቢ ላለሰው፤ እሰረው ፡ ግረፈው፡ ግደለው፡ እንደሚለው ያለው ደርግም እምቢ ላለሰው ጥይት አጉርሰው ብሎ አወጀ የህዝቦች ጥያቄዎች አፈናቸው ፡፡
በዛን ግዜ የኢ/ያ ህዝቦች በተለይ በንቃተ ህሊና ትንሽ መጥቀው የነበሩ ሙሁራንና ሰራተኛች በደርግ ስርዓት ሰለማዊ ትግል ለማድረግ አይቻልም በማለት በረሃ ወጥተው የትጥቅ ትግል ለማከላሄድ ወሰኑ፡፡ አንዳ አንዶቹም ደርግ በትጥቅ ትግል ሳይሆን በከተማ ነውጥ ነው ማስወገድ የሚቻለው በማለት የነውጥ ስትራቴጂ መርጠው መንቀሳቀስ ጀምረው ነበር፡፡ በሌላ በኩል ከደርጎን በመሆን በጎ በጎውን መንገድ እንዲከተል መንገድ በማሳየት ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ማድረግ ይቻላል አሉ፡፡ ይህ የዘመኑ ሙሁር የየራሱ የተለያየ ፍልስፍና በመያዝ በየፊናው በመዝመት በአንድነት ታግሎ ዲሞክራሲያዊና ህዝባዊ መንግሥት የመመስረት የህዝቡን ተስፋ አጨለመበት፡፡ በአንፃሩ የዚያን ጊዜ ሙሁራን በየፊናቸው ተደራጅተው በሃገራዊና ብሄራዊ ጥያቄ ሥር ብዙ ፀረ-ደርግ የፖለቲካ ኃይሎች ተመሰረቱ፡፡
ከነዚህ ውስጥ የትጥቅ ትግል ስትራቴጂ ከመረጡት ውስጥ አንዱ ህ.ወ.ሐ.ት ነበር፡፡ በህቡዕና በግልፅ ተደራጅቶ በየካቲት 11/06/1967ዓ.ም በ11 ሰዎች በረሃ ደደቢት ወጥቶ የጥቅ ትግል ጀመረ ፡፡ እኖሆ ህወሐት ዘንድሮ 40ኛ ዓመት የልደት በዓሉ ለማክበር ሸርጉድ እያለ ይገኛል፡፡
ህ.ወ.ሐ.ት ዩዞዋቸው የተነሳ ዓላማዎች፡-
አባገነኑን ፋሽስታዊ ደርግን በማስወገድ ህዝባዊ መንግሥት መመስረት፡
የመድብለ-ፓርቲ ስርዓት እንዲኖርና በነፃ የመደራጀት፣ ነፃ የምርጫ ውድድር መኖር እንዳለበት፡፡
የብሄራዊ መብት የራስን ዕድል በራስ መወሰን ዕድል እንዲይኖር ፡፡ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ መሆኑ፡፡
ብሄራዊ ትግል እንደ የሰልት ትግል ተጠቅሞ መደባዊ ትግሉን እዳር በማድረስ ለኢትዮጵያ አንድነትና እኩልነት መታገል ፡፡
የገጠርና የከተማ መሬት የህዝብ መሆን እንዳለበት፡፡
በፖለቲካም ማርክሰሌኒናዊና ማአዘዲንጋዊ ስነ ሃሰሳብ መመሪያው እንደሆነ፡፡
የአብዮቱ ጠላተች፤ ፉሽስታዊ ደርግ፣ መስፍናዊ ስርዓት፣ ሃብታም ገበሬ ፡ ሃገራዊ ባለ ሃብት፣ ከፍተኛ ሙሁርና ኢንፔርያሊዝም እንደሆኑ ፡፡

ከላይ የተጠቀሰው የኃይል አሰላለፍ በፅሁፍ ተሰንዶ በማኒፈስቶ ደረጃ የተቀመጠ አልነበረም፡፡ እንዲሁ በሰመበለው ነበር የሚነገረው ፡፡ እላይ የተዘርዘረው አÌም የህ.ወ.ሐ.ት አÌም ሆኖ አልቀጠለም ፡፡

በ1968 ዓ.ም አጋማሽ አከባቢ ግን አንድ አስደንጋጭ አÌም ተያዘ፡ ይህ አÌም ታጋዮች ተዋይተውበት ወይም በድርጅቱ በጉባኤ ቀርቦ የፀደቀ አልነበረም፡፡አማራሩ አስቦበት አትለው በግብታውነት አትለው የመጣ አቋም ነበር፡፡ ለታጋዩ፣ ለኢ/ያ ህዝብና ለሌሎች ፖለቲካዊ ድርጅቶች ግን ድንገት ነበር፡፡

ትግላችን ከአማራ ቀኝ ገዥዎች ነፃ ለመውጣት (ነፃ ሪፓብሊክ ትግራይ ለመመስረት) ነው ብለው በትግርኛ፡ በአማርኛ፡ በእንግሊዘኛ የተፃፈ፡ በነ አቶ ስዩም መስፍን ፡መለስ ዜናዊ ፡ ስብሃት ነጋ፡፡ በሙሉጌታ ሓጎስና በሌሎችም የተጻፈ ሥዩም መስፍን ሱዳን ሄደ በመጽሐፍ መልክ አሳትሞ ወደ አገር ገብቶ ለተጋዮችና ለከተማ ደጋፊዎች ለውጭ አገርም እንዲሰራጭ ተደረገ በቃ የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች ጠባብነት ፀሐይ ላይ ወጣ ፡፡
የዚሁ ማኒፌስቶ በቅድምያ የተቃወመ ኢ.ህ.ኣ.ፖ ነበር፡ ቀጥሎ ትንሽ ቀለም በቆጠሩ ታጋዮችና በከተማ ደጋፊዎች ትልቅ ተቃውሞ አገጠመው ፡፡ ጥያቄ ላነሱ ታጋዮች በተለይ ከ1969 ዓ.ም እስከ 1970 ዓ.ም እርምጃ ተወሰደባቸው፡፡ ብዙ ታጋዮች እየሸሹ ከተማ ገቡ፡፡ ዕድል ያገጠማቸውም ወደ ሱዳን ሸሹ፡፡ትላትና በኢ/ያ የመደብለ-ፓርቲ መኖር አለበት የሚል አÌም የነበራቸው የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች በሰሜን ኢ/ያ ለነበሩ ፀረ-ደርግ ኃይሎች መጀመርያ ግንባር ገድሊ ሓርነት ትግራይን (ግ.ገ.ሓ.ት)መቱ፡፡ ቀጥለው ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ ጣራናፊት ኮሚቴ አጠፉ፡፡በመቀጠልም የኢ/ያ ዲሞክራሲያዊ ህብረት(ኢ.ዲ.ህ እና ኢ.ህ.ኣ.ፖ) ግዝፎች ኃይሎች ተዋጡ፡ በድርጅቱ ውስጥም ጦርነቱንና ጠባብነቱንና የተቃወሙ፣የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ አይደለም ብለዉ የተማጎቱ ጅግኖቹም እንደዚህ ተዋጡ፡፡ በቃ የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች ፀረ-መደብለ-ፓርቲና ፀረ-ዲሞክራሲ መሆናቸው ተጋለጠ፡፡ ግን ደግም ፋሽስታዊ ደርግ በትግራይ ህዝብ ጠላትና ወዳጅ ሳይለይ በማከናይዘድ፣ በእግረኛ ወታደር፣ በአየር በጋዝና በናፖልም መርዝ በመጠፍጨፉ ህዝቡ የሩቅ ጀብ ከሚበላኝ የራሴን ጅብ ይብላይኝ በሚል ህዝቡ ዕድሜ ፡ፆታና ሃይማኖት በማይለይ ከህ.ወ.ሐ.ት ጎን ቆሞ ልጆቹ ወደ ትጥቅ ትግሉ እንዲዘመቱ፣ ገንዘቡና በሁሉም ዓይነት ሀብቱ ህ.ወ.ሐ.ትን ለመደገፍ ተነሳ ፡፡
የትግራይ ህዝብ ግን ምንም እንኳን ከደርግ ህ.ወ.ሐ.ት ቢወድም ፡ ህ.ወ.ሐ.ት በጣባብነት አÌሙ የኤርትራን የቅኝ ግዛት ጥያቄ መደገፉ የሻአብያ ካድሬ ሆኖ መንቀሳቀሱ፣ይባስ ብሎ ሻአብያን ከደርግና ከጀብሃ ለመከላከል በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣት ታጋዮች ወደ ሳህል በረሃ በማዝመቱ አምርሮ ይተጋለውና ይቃወመው ነበር፡፡ በዚሁ ተቃውሞ ምክንያት አድመኞች ተብለው እርምጃ የተወሰደባቸው እጅግ ብዙ ፡ አርሶአደሮችና የከተማ ነዋሪዎች ነበሩ፡፡
የትግራይ ህዝብና የህ.ወ.ሐ.ት የልደት በዓል የካተቲት 11፡-
ከላይ እንደዘረዘርኩት ደርግ ጠላትና ወዳጁ ሳይለይ ይጨፈጭፈው ነበር፡፡ የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎችም ያ ጠባብነትና ፀረ-ዲሞክራሲ ባህሪያቸው የህዝብና የተጋዮች ፊት ያሰጋቸው ስለነበር ስግተው ጠባያቸው በመቀየር ብዙ ስለት ይገቡለት ነበር ፡፡ የካቲት 11 የትግል ቀን በመሆኑና ብዙ መስዋእት ስለከፈለበት በዓሉ ሲከበር ከሚወደው አምላክ በማይተናነስ ሁኔታ የየአመቱን በዓል በበለጠ አምልኮት (እምነት) በማሳደር ቤቱ ያፈራውን ሁሉ አይነት የሚበላ የሚጠጣ በመዘጋጀት በሰለማዊ ሰልፍ ልጆቹ በመመልመል ልብስና ቀለብ በመስጠት ወደ ወታሃደራዊ መሰልጠኛ (02) የሚሸኝበት ግዜ ነበር ፡፡

ይህ የሆነበት ምክንያትም የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች በዛን ግዜ ቃል የገቡለት ሰለት ከድተው ራሳቸው፣ ልጆቻቸውና ዘር-መንዘራቸው ሃብት መካበት፣ምርጥ ቪላዎችና ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ባገር ውስጥና በውጭ ሰርተው የሃገራችን ዶላር እየዛቁ በውጭ ባንኮች አስቀምጠው ለክፉ ቀን እየተጠባበቁ ይገኛሉ፡፡ ያን ግዜ በታጋይነት ጊዜ፣የመሴ ደቀመዝሙር በነበሩበት ጊዜ፤መድረክ ወጥተው በካድሬዎቻቸውና ራሳቸው ሲናገሩ ህ.ወ.ሐ.ት ደርግ አስወግዶ ባጭር ግዜ የህቡን ችግር ይፈታል የሚል እምነት የሚያሳድር ነበር፡፡ ነገር ግን ህወሐት ቃሉና ተግባሩና ለየብቻ ሆኖ ቀረ፡፡ ህዝቡ ልጆቹን መርቆ ለመስዋእትነት ሲልክ የስደት ፡የድህነት፡ የስራ አጥነት ችግሮች መፍትሄ አግኝበታሎህ ብሎ ተስፋ በመጣል ነበር፡፡ ነገር ግን ህዝቡና ታጋዩ አንድ ያልተገነዘበው ነገር ነበር፡፡እነዚህ የህወሐት ቁንጮ አመራሮች ማንነት በምንመረምርበት ጊዜ ለህዝብ ጥቅም ለመቆም ምንም ምክንያት(background)የላቸውም፡፡ የነሱ ወደ ትጥቅ ትግል መግባት የአባቶቻቸው ስልጣን አሻሽለው ራሳቸውን ገዥዎች ለመሆን አስበው የተነሱ “ታጋዮች” ናቸው፡፡ ስለሆነም ነው አሁን በመቶ ሺ የወጣቱ መስዋእትነት ስልጣን ላይ ወጥተው የአገር ለአላውነት መደፈር፡ የሰብኣዊ መብት ረገጣ ፡ የህግ በላይነት አለመኖር፣ ባጠቃላይ በአገሪቱ በመድብለ-ፓርቲ ስርዓት፣ የዲሞክራሲያዊ መንግሥት መመስረት የቃል መፈክር ሆኖ እንዲቀር ያደረጉት፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ ውድድር ህዝቡ በነፃ የመሰለውን የፖለቲካ ፓርቲ መርጦ መንግሥት እንዳይመሰርት የከለከሉት የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው ስልጣን አሳልፈው ላለመስጠት ነው፡፡ የካቲት 11/1967 ዓ.ም በረሀ ሲገቡ ይህንን ድብቅ ዓላማ ከ4 የአንጎላቸው ክፍል በአንዱ ሥር አስቀምጠው ነበር ሲንቀሳቀሱ የነበሩት፡፡ በትጥቅ ትግሉ ለህዝብ የቆሙ፣ብቃት የነበራቸው ታጋዮች የአሁኖቹ አመራሮች የአባቶቻቸው የስልጣን ኮርቻ ላይ እንዳይወጡ ስጋት ሁነው ስለተገኙ በትጥቅ ትግሉ እንዲቀጥሉ አልተፈለገምና እንዲወገዱ ተደረገ፡፡ ህዝቡ የካቲት 11 የሁሉም ነገር መፍትሔ ናት ብሎ ያምን ነበር፡፡ነገር ግን የካቲት 11 ደርግ ደምስሳ ሰላም፣ ፍቅር፣ የኢ/ያ አንድነት ማረጋገጥ አልቻለችም፡፡ የ17 ዓመት ሙሉ የትጥቅ ትግል፣የመቶ ሺዎች ወጣቶች መስዋእነት ለፊውዳል ልጆች የአባቶቻቸውና የአቶቻቸው ስልጣን እንዲረከቡ አስቻላቸው፡፡ ህዝቡ የካቲት 11 ሲያ ከብር ቀደም ብሎ ከልቡ በመነጨ ፍቅር ነበር የሚያከብራት፡፡ ሁኔታው ቀስ በቀስ እየተረዳው ሲመጣ ግን ዕለቱን ለማክበር ድርጅቱ ህዝቡን በማስገደድ እንዲያከብር ያደርገው ጀመር፡፡ህወሐት/ኢህአዴግ ስልጣን ላይ የወጣው በኃይል በማሸነፍ እንጂ በሐሳብ በማሸነፍ( defeat not win) ስላይደለ የህዝብ መብቶች ማስከበር አይችልም፡፡

የህ.ወ.ሐ.ት 40ኛ የልደት በዓልና የትግራይ ህዝብ፡-
የህ.ወ.ሐ.ት መሪዎች በአፈቀላጤዎቻቸው አማካኝነት ባለፉት 24 ዓመታት የስልጣን ዘመናቸው በኢ/ያ ፍትህ፣ የህግ የበላይነት፣ የዜጎች ሰብኣዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተከብረዋል፣ የብሄር ብሄረሰብ መብት የራስን እድል በራስ የመውሰን መብት ተከብረዋል፡፡ የታገልንበት መደብለ-ፓርቲ ህልውና በኢ/ያ ተረጋግጣል ፡፡ ነፃ የምርጫ ኮሚሽን፣ የሰብኣዊ መብት ኮሚሽን፣ የእንባ ጠባቂ ኮሚሽን ተÌቁማል፡፡ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተÌቁማል ፡፡ የነፃ የፍትህ አካላት ተመስርተዋል ይሉናል፡፡
በኢኮኖሚም በአለም ደረጃ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ ለመድረስ ተቃርበናል ፡፡ በመሰረተ ልማት፤ በመንገድ፣ በሃድሮ -ኤሌክትሪክ አድገናል ፣ የማይደፈር አባይን ደፍረናል፡፡ የባቡር ሃዲድ እየሰራን ነው፡፡ በቲክኖሎጂ አድገናል፡፡ በእርሻ አድገናል፡፡ የእርሻ ኢንቨስትመት ተስፍፍቷል፡ የመስኖ ስራ ተሰፋፍቷል ፡ ህዝባችን በቀን ሦወስት ግዜ በልቶ እንዲኖር አድርገናል ፡፡ በኢንዳስትሪ ከበለፀጉ አገሮች ተወዳዳሪ ወደ መሆን ደርሰናል፡፡በማህበራዊ አገልግሎት በትምህርት፣ በሕክምና፣ በውሃ ሽፋን በኤሌክትሪክ አገልግሎት ፡ ከነበሩት መንግሥታት በአጭር ዓመታት ውስጥ በበለጠ መሰረታዊ ዕድገት አስመዝግበናል ይሉናል፡፡
በፀጥታና በፍትህ ህዝባችን የተሻለ አገልግሎት አግኝቷል፡፡ የህግ የበላይነት ተረጋግጧል ፡፡ በሃገራችን የተረጋጋና ሰለማዊ ሁኔታ ተረጋግጧል ይላሉ፡፡
የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎችና አጃቢዎቻቸው በ40ኛ የልደት በዓላቸው ይህንን ለመሸፋፈን እያደረጉት ያለ ዝግጅት፡-
ህ.ወ.ሃት በአሁኑ ግዜ 40ኛ የልደት በአሉ ሲያከብር ካለፉት 39 አመታት የበለጠ አከባበር ለማክበር እየተዘጋጀ ነው፡፡ለዚሁም ከውጭ አገር (ከዲያስፖራው) ማህበረሰብ ከ100.000 በላይ እንግዶች እንደሚመጡ ከወዲሁ አውጃዋል፡፡ ካገር ውስጥም ከክልል መሰተዳደሮች ተወካዮች ሰቢክ ማህበራት እነዚህም በመቶሺ የሚቆጠሩ እንግዶች ይመጣሉ፡፡ በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የትግራይ ተወላጅችም ከእንግዶች ውስጥ እንደሆኑ ተነግረዋል፡ የሃገራችን የኪነት ባለሙያዎች ፀሐፊዎች ከወዲሁ እየተነገራቸው ነው፡፡ በትግራይ ክልልም ከሁሉም ዘኖች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች የተወከሉ እድምተኖች በመቶሺዎች ይጠራሉ፡፡ የመቀሌ ህዝብ ከ300,000 በላይ ተጨምሮበት መቀሌ እጅግ ብዙ ሰው ታሰተናግዳለች፡፡ በተጨማሪ በዞን፣ በወረዳና በቀበሌ እስከ ቤተሰብ ቤት ቁጥር በግድ ያከብራል ሃብትም ይባክናል፡፡

በትራንስፖርት መስከም በሃገራችን ያሉ ምርጥ ኤም.ቢ.ኤም ኮብራዎች አውቶቡሶች ይዘጋጃሉ፡፡ በገንዘብ ሲተመን ለነዳጅ ለታዳሚዎች ውሎ አበል የሚወጣ እጅግ ብዙ ሚልዮን ብር ነው፡፡ በዚሁ በመቀሌ ለእድምተኛች የሚወጣ ገንዘብ በመቶ ሚልዮን የሚገመት ነው፡፡ የአየር መንገድና የመከላከያ ሚንስቴር አውሮፕላኖችም ለዚሁ በዓል ማክበር የፀጥታ ኃይሎች የሃገር መከላከያ ፡ ፌደራል ፖሊስ፡ ድህንነትም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሊመጡ ናቸው ፡፡ ለዚሁ በዓል ዝግጅትና ምግብ ለመÙÙዝ ከሚያጠፉት የመንግሥት የስራ ግዜ ሳይቆጠር የሚባክነው ገንዘብ በብዙ መቶ ሚልዮን የሚገመት ይሆናል፡፡

ህ.ወ.ሃ.ት የ40ኛ የልደቱ አመት ለማክበር ይህ ሁሉ ወጪ ሲያወጣ ዛሬ ብቻ አይደለም፡፡ ስልጣን ከያዘ ቀን ጀምሮ እስከዛሬ በቢልዮን የሚገመት ሃብት አባክነዋል፡፡ ይህ የማባከን ጉዳይ ግን በህ.ወ.ሃ.ት ውስጥ ታጥሮ የቀረ አልነበረም፡፡ ሌሎች አጃቢ የፖለቲካ ድርጅቶችም የህ.ወ.ሃ.ት ሞዴልነት በመከተል፡ የብአዴን፣ የአሆዲድ፣የዲህዳን ፡ የጋንቤላ፡ የዓፋር ፡ የቤንሻንጉል፡ የሶማል ፡ የሃደሬ፡ በዓላትም እጅጉን አባካኝ ፍፃሜዎች ታይተዋል ፡፡ በተጨማሪ ለግንቦት 20 ብዙ ባክነዋል አሁንም 20ኛ ዓመት ሊከበር ነው፡፡ ይህ ሁሉ በልማት ስራ ቢውል ኖሮ ስንት ድህነት በቀረፈ ስንት ህዝብ ከስደት በዳነ ነበር፡፡ ህ.ወ.ሃ.ት ግን ራሱን ለማዝናናት ይወዳል፡፡ አለማውም ይኸው ነው፡፡በአሁኑ ግዜ በትግራይ ዲግርና ዲፕሎማ የተመረቀ በመቀሌ ብቻ ከ30,000 በላይ ስራጥ ወጣት አለ፡፡ 10ኛ፣12ና 8ኛ ክፍል የወደቁ ተማሪዎች አይቆጠሩም፡፡ ህወሐት ይህ ሁሉ ቢልዮን ብር ለክርስትናው ከሚያጠፋ እነዚህ በትምህርት ጥራት ዕጦት ምክንያት የወደቁ ተማሪዎች ማስተማርና ማብቃት መምረጥ ነበረበት፡፡ነገር ግን የካቲት 11 የህወሐት አመራር ከድሮውም የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው ስልጣን ለማስረከብ ቀይሰው የተጓዙበት ዕለት በመሆኑ በብልዮን መሆኑ ቀርቶ ዓቅም የላቸውም እንጂ በትሪልዮን ብር በዓሉ ቢከበርላቸው ደስታው አይችሉትም፡፡

የጥፋት ዝግጅቱና ዓለማው ፡-
40ኛ የህወሐት የልደት በዓል ዋናው ዓላማው የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች በአሁኑ ግዜ በትግራይ ህዝብ ዘንድ የነበራቸው አመኔታ ጭራሹን ተማጥጦና ተጠልተው እንደምራቅ የተተፉበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡በመሆኑም በዚሁ በዓል ብዙ የውሸት ይዕድገት ድርሳናት ተደርሰው በፎቶግራፍ፣ በፊልም፣ በሙዚቃ፣ በሬድዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በግብዣና በዲስኩር በማደንዘዝ የህዝብን አቅጣጫ በመቀየርና በማላሳለስ የስልጣን እድሚያቸው ለማራዘም እንደልማዳቸው የትግራይን ህዝብ እንደመጠቀምያ ለማድረግ ነው፡፡ ሌላው ዓላማ በ2007 ዓ.ም የፓርላማ ምርጫ ዘመን እጅጉን ስለሰጉ በዚህ በዓል አመካኝተው የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግና የህዝቡ አስተሳሰብ መቀየር፣ የህዝቡን ብሶት ለማብረድ፤ወጣትን የውሸት ታሪክ በመደርደርና በመፈረክ በኘሮፖጋንዳ ለማዳንዘዝና በአጉል የተስፋ መንገድ እንዲቆም ለማደረግ ነው፡፡
የህ.ወ.ሃ.ት 40ኛው የልደት በዓልና ፋይዳው፡-
ህወሐት የተነሳለት ብሄራዊና መደባዊ ጭቆና በመጣል በህዝብ የተመረጠ ህዝባዊ መንግሥት መመሰረት የሚል ዓላማ ለማሳካት አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎም ከዘውዳዊው ስርዓትና ከፋሽስታዊ ደርግ ስርዓት በባሰ መንገድ ህዝቡን እየጨቆነና እየበዛበዘው ይገኛል፡፡ህዝቡ የድሮ የበሰበሱ በዝበዥ ስርዓቶች አስወግዶ፡ 17 ዓመታት ሙሉ ታግሎ የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው አሮጌውን ስርዓት አሳድሰው ህዝቡን በዘመናዊ መንገድ የሚጨቁኑ ገዥዎች አፍርተዋል፡፡

ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብቶቹ አልተከበሩለትም፡፡ የየካቲት 11 ውጤት ይህ መሆን ነበረበት፡፡ ህዝቡ ደርግን ማስወገድ ብቸኛው መፍትሔ ይመስለው ነበር፡፡የካቲት 11 ገዥዎች ነቅላ ሌሎች ገዥዎች ታመጣለች ብሎ ህዝቡ አስቦ አያቅም ነበር፡፡ ሀቁ ግን ይህ ሆኖ ቀረ፡፡ የካቲት 11 አደራ በልተሻል ብለው ለተቃወሙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ታስራለች፣አገር ለቀው እንዲሄዱ እያደረገች ነው፡፡ የካቲት 11 ያ ሁሉ ወጣት በጉያሽ አቅፈሽ፣ለክብርሽ መስዋእት ሆኖ ለአዲስ ገዥዎች አሳልፋ መስጠቷ በየካቲት 11 ያገኘነው ነገር ካለ ልጆቻችን መስዋእት መሆናቸው እንጂ የፈየደችን ነገር የለም እያሉ ናቸው፡፡ የካቲት 11 ይህ ሁሉ ወጣት በልተሽ ለጥቂት የገዥ መደብ ልጆች ጥቅም መቆምሽ ከበደል በደል ነው፡፡

የካቲት 11 40ኛ ዓመትሽ ሲከበር እኛ ህዝቦች ከደርግ መንግሥት የዜሮ ዲሞክራሲ ወጥተን በራሳችን ፍቃድ የኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላውነት ተከብሮ እርስ በራሳችን ተፋቅረን እንኖራለን ብለን ነበር፡፡ በ40ኛ ዓመትሽ በህወሐት/ኢአዴግ መንግሥት እርስ በራሳችን ብጥርጣሬ ዓይን እንድንተያይ፣አንዱ በሌላው ክልል ሄዶ ሰርቶ የመኖር ዕድል ዘግቶ ይገኛል፡፡ እርስ በራሱ እንደጠላት እንዲተያይ እየተደረገ ነው፡፡ ደርግ ሃይማኖት ለማጥፋት ሲጥር ህወሐት/ኢህአዴግ ደግሞ በሃይሞት ነፃነት ጣልቃ በመግባት እርስ በራሳችን የነበረንን የመከባበር እሴት በማደፍረስ አንድነታችንን እንዲላላ በማድረግ ለፖለቲካ ፍጆታው እያዋለው ይገኛል፡፡
ደርግ ዜጎች የመደራጀት፣የመናገር፣የመጻፍ መብት የከለከለ መንግሥት ስለነበር እኛ የጊዜው ወጣቶች ታጥቀን ደርግን እንድናስወግደው ያንችን ጥሪ ሰምተን ታግለናል፡፡ ውጤቱ ለዚህ ብለን አልነበረም፡፡ የፊውዳል ልጆች የአባቶቻቸውና የአያቶቻቸው ሥልጣን ለማስረከብ ብለን አይደለም ደደቢት የወጣነው፡፡

የካቲት 11 አሁን 40ኛ ዓመትሽ እየተከበረ ነው፡፡ እርግጥ ነው ጤና እንዳላገኘሽና በአከባብያችን እንደሌለሽ ይገባናል፡፡ ከአጠገባችን ብትኖሪ ኖሮ ይህ ሁሉ ግፍ ብህዝቡ እየወረደ ዝም ብለሽ ማየት እንደማትችይ ይገባናል፡፡
የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች መሬት ላራሹ፣ የከተማ መሬት በነፃ ለህዝብ በእኩልነት ይታደል ብለው የታገሉና ለህዝብ አነስስተው ደርግን ለመጣል ያስቻላቸው የመሬት ጥያቄ በመክዳት፣ መሬት የመንግስት ናት በማለት የከተማና በከተማ አካባቢ የሚገኙ የህዝብ መሬት በመቀማት በመሸጥ ለራሳቸውና ለዘር መንዝራቸው የሃብት ምንጭ አድርገውታል ፡፡ የገጠር መሬት የህዝቡን ባለቤትነት በመንጠቅ በአርሶአደሩ የማልማት ዓቅም ለሌላቸው ግለሰዎች በመሰጠቱ ወጣት አርሶ አደር የወጣት ጥንቻው ሊያሳርፍበት የሚችል መሬት ባለማግኜቱ ጉሳሳ ጎጆ ሰርቶ የሚተኝበት መሬት ተከልክሎ በረሃና ባህር ተሸግሮ ወደ ስደት ፈልሰዋል ፡፡ በአንፃሩ የህ.ወሃ.ት መሪዎችና ልጆቻች ባገር ውስጥና በውጭ ሰማይጠንቀስ ህንፃዎች ሰርተው የሚኖርበት ሁኔታ ተፈጥረዋል፡፡
የካቲት 11 40ኛ ዓመት የልደት በዓልሽ ስናከብር ይህንን ጉድ ተሸክመን ነው፡፡ግን የካቲት 11 ልጠይቅሽ እነዚህ ቱጃሮች ለመፍጠር ነበር የትግሉ ዓላማ?

አይደለም ፍፁም አይደለም ፡፡ በኛ በኩል አስበነውም አናቅም፡፡እነሱ ግን ይህንን ዓልመው ይጓዙ ስለነበር ያሰቡትን አሳክተዋል፡፡ የካቲት 11 40ኛ ዓመትሽ ስናከብር በሃዘን መሆኑ ማወቅ አለብሽ፡፡ ምኞታችን የነበረው በ40ኛው የልደት በዓልሽ ገጠሪቷ ትግራይ ከ13 ዓመት ዕድሜ በላይ ወጣት የማይኖርበት፣ በገጠር ህፃን፣ ሽማግሌ ከሞተ ሬሳ ተሸክሞ ወደ መቃብር የሚወስድ ወጣት ይጠፋል ብለን ኣናስብ ነበር ግን ሆነ ፡፡ የገጠር ወጣቱ አብዛኛው ወደ ጎረቤት አገሮች ሲሰደድ የቀረው ወጣት ወደ ክልል ከተሞችና አዲስአበባ ፈልሰው ከተሞችን አጣብበዋል ፡፡ ሴት እህቶቻችን ባገር ውስጥም በውጭም ካለፉት ስርአቶች በባሰ ለዝሙት ስራ ተጋልጠው እየተዋረዱ ይገኛሉ ፡፡ ለመጥፎ በሽታ ተጋልጠዋል፡፡ የገጠር ሴቶች ባሎቻቸው ወደ ስደት በመፍላሳቸው ህፃናት ይዘው በሃገር ቤት በረሃብ በበሽታ ይሳቃያሉ፡፡ የካቲት 11 40ኛ ዓመትሽ ስናከብር ይህንን ስቃይ እያየን ነው፡፡

በከተማ ያለው የተማረና ያልተማረ ወጣትም በስራ አጥነት ምክንያት ለፀጥታና ለሰላም ጠንቅ ሆኖ ይገኛል፡፡ በተለይ በዮኒቨርሲቲዎች የተመረቁ ወጣቶችም በመጥፎ ሁኔታ ይገኛሉ፡፡ ያቺ እንደ እሳት አደጋ ማጥፈያ የሚጠቀሙላት ከቡልስ

Image
ከሠሞኑ ወደግብፅ የሚያቀና ህወሀታዊ የልዑካን ቡድን ሲቋቋም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሊጠብቀው በማይችለው መልኩ የልኡካን ቡድኑ ውስጥ የአንድ ሠው ስም ተሠማ “ግርማ ሠይፉ” የሚል በርካቶች ተገረሙ ወይ አንቺ ሐገር ሲሉም አዘኑ፡፡ ከዚህ ቀደም ብቸኛ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በፓርላማ ተብለው በተቀመጡባቸው ያለፉት 4 ዓመታት ለሐገራችን ፖለቲካ ያንን ያህል ለውጥ ባያመጡም፤ የህሊና እስረኞቹ ይፈቱ ዘንድ አሁንም ያንን ያህል ጠንከር ያለ ስረ ባይሠሩም አቶ ግርማ ሠይፉን ሌሎች አካላት ሲተቿቸው ግርማ ሠይፉን ደግፈው ከሚቆሙ አካላት መካከል አንዱ እኔ ነበርኩኝ ብዬ አስባለው፤ አስባለው ያልኩት ስለግርማ ሠይፉ ከኔ በላይም የሚያስብ ሌላ ህወሀት የተሠኘ የሠዎች ስብስብ መኖሩን ስላልተረዳሁና በቅርቡ እየታዩ ያሉትን የግርማን መንሸራተቶች ባለመመልከቴ ነበር፡፡

በሐገራችን ፖለቲካ ማየት ከማንፈልጋቸው ነገሮች የከዳተኝነት ፖለቲካ አንዱ እና ዋነኛው ነው፤ ይህ ህዝብ ለፍቶ ከሚያገኘው የወር ገቢው ላይ ግብር ተወስዶበት ፓርላማ ለሚገኙ የህዝብ ተወካዮች በአበል እና በደመወዝ መልክ ይሠጣል ህዝቡ ይህንን የሚያደርገው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተሠኘው የሚገኙ አባላት መብቴን የሚያስከብር ህግ ያወጡልኛል፤ ስለእኔ መብት ስለቆሙ የታሠሩ የህሊና እስረኞችን የበላይ አካል እንደመሆኑ ያስፈታልኛል ብሎ አለመሆኑ እሙን ነው ምክንያቱም በህወሀት ፓርላማ ውሳኔ ችግሬ ይፈታልኛል ብሎ የሚያስብ ኢትዮጵያዊ ካለ እርሱ የህወሀት አባል መሆን አለበት ሆኖም ተባራሪ ሆነው ፓርላማ ውስጥ የሚታዩ አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የህዝብ ችግር ያሏቸውን ጉዳዮች ነቅሰው አውጥተው ለፓርላማው ሲያቀርቡ እንመለከት ነበር እነዚህ ሠዎችም ሲከዱ ተመልክተናል እውን ግርማ ሠይፉ ካዳ? ግርማ ሠይፉ ካዳ ወይስ አሁንም ለህዝቡ እንደቆመ ነው የሚሉትን ጉዳዮች ከማንሳታችን በፊት ከግርማ ሠይፉ ጋር የልዑካን ቡድኑ አባላት ውስጥ የሚገኙ አባላት እነማን ናቸው የሚሉትን መመልከት ተገቢ ይመስለኛል፡፡

የህዝብ ልዑካን ቡድን ሲቋቋም መታሠብ ካለበት መካከል አንደኛው እና ዋናው ነገር የልዑካን ቡድኑ አባላት በህዝብ የታመኑ፣ በመልካም ስነምግባራቸው አርዓያ የሆኑ እና ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ መሆን ይኖርባቸዋል ወደግብፅ ባቀናው የልዑካን ቡድን ውስጥ የተካተቱት ግን በየትኛውም መለኪያ የህወሀት ጉዳይ አስፈፃሚ ከመሆን ውጪ የህዝብ አመኔታ ያላቸው ግለሠቦች አይደሉም፡፡ ከልዑካን ቡድኑ ውስጥ መካከል አንዱ ሠራዊት ፍቅሬ የተሠኘው ግለሠብ ነው፡፡ ይህ ግለሠብ ልክ እንደሌሎቹ የህወሀት አባላት እና አመራሮች ከወታደር ቤት ወጥቶ ሚሊየነር የሆነ ግለሠብ ነው፡፡ ሠራዊት ፍቅሬ የህዝብ ተወካይ መሆን የማይችልባቸውን ምክንያች ለማንሳት ያህል ከዛሬ ሁለት አመት በፊት በአንድ ተማሪ ላይ በማን አለብኝነት የፈፀመውን የአስገድዶ መድፈር ሙከራ ማየቱ ተገቢ ነው፡፡ ሠራዊት ፍቅሬ አስገድዶ ሊደፍረኝ ሲል አመለጥኩኝ ያለችውን ግለሠብ አዲስ አድማስ የተሠኘው ሐገር ቤት የሚታተም ጋዜጣ አነጋግሯት እንደነበረና ከጥቂት ቀናት በኋላ በሠራዊት ፍቅሬ የመድፈር ሙከራ የተደረገባት ተማሪ ሁኔታ ተደባብሶ ቀረ ወጣቷ አሁን የት እንዳለች እንኳን አይታወቅም አዲስ አድማስም ከህወሀት ሠዎች ሊደርስበት የሚችለውን ዛቻ በማሠብ ተወው ይህንን ድርጊት የፈፀመው ሰራዊት ፍቅሬ ነው አንዱ የዚህ ልዑክ አባል፡፡

ሌላኛው የልዑካኑ ቡድን አባል ቴዎድሮስ አድሐኖም ወይም እንደሱ አጠራር ቴድሮስ አድሐኖም ነው፡፡ ይህ ግለሠብ አምና በዚህ ሠዓት ሣውዲ አረቢያ ይገኙ ለነበሩ ሠዎች ሞት እና እንግልት ተጠያቂ ሊሆን የሚችል ሠው ነው፡፡ ቴዎድሮስ አድሐኖም የውጪ ጉዳይ ሚኒስተሩነቱን እና የህወሀት አባልነቱን ተጠቅሞ ለሳውዲአረቢያ የንጉሳውያን ቤተሠቦች በላከው ደብዳቤ ኢትዮጵያውያኑ ከሳውዲ ኢሠብዓዊ ድርጊት ተፈፅሞባቸው እንዲወጡ ማድረጉ ይታወሳል ይህ ግለሠብ ስለእውነት እና ስለህዝብ የቆመ ቢሆን ኖሮ የሳውዲ ንጉሶችን አሳምኖ የኢትዮጵያውያን መውጫ ቀን በማስረዘም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ከእልቂት እና ከግፍ ያድን ነበር ሆኖም ዛሬ ይህ ግለሠብ የሠራቸው ወንጀሎች ተደብቀውለት ዛሬ የህዝብ ልዑካን ተብሎ ተሠይሞ ይገኛል፡፡ ግርማ ሠይፉም ከእነዚህ ሠዎች መካከል ይገኛል የህዝብ ልዑካን ቡድን ተብሎ፡፡ ከሠራዊት ፍቅሬ እና ከቴዎድሮስ አድሐኖም ጋር አብሮ መስራትን የመሠለ ምን ከዳተኝነት ይኖር ይሆን?

ግርማ ሠይፉ የልዑካን ቡድኑ ውስጥ መካተቱን ሳይነግረን ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ “ይህ የአሁኑ ሠንደቅ ዓላማ ለእኔ ከበፊቶቹ ይሻለኛል፤ ሁሉም የታሠሩት ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች ንፁህ ናቸው ብዬ አላምንም” ምናምን የሚሉ በህዝብ ላይ የተቀለዱ መጥፎ ንግግሮችን በኢንተርቪው እና በብሎጉ ላይ አሰምቶናል በተጨማሪም አምና አንድነት ጠርቶት በነበረው ሠላማዊ ሰልፍ ላይ ሠልፈኛው ሲግናል አካባቢ ሲደርስ ሲግናል ለአንድ ጎሳ አባላት ብቻ የተሠሩትን ህንፃዎች ተመልክቶ ዝም ብሎ ማለፍ ያልቻለው ሠልፈኛ ሌባ ሙሰኛ እያለ ሲጮህ ዝም በሉ እያለ ሠልፈኛውን ከሀብታሙ አያሌው ለመነጠል ሲሞክር እንኳን በግርማ ላይ ተስፋ አልቆረጥኩም ነበር አሁን ግን ከኢትዮጵያ የምንም ጊዜ ጠላቶች ጋር አበረ፡፡ የልዑካን ቡድኑ ውስጥ ያሉት ሠዎች እኮ በበደኖ እና በአርባጉ የአማራውን ጎሳ የጨፈጨፉ፤ በአምቦ ንፁሐን የኦሮሞ ተማሪዎችን የገደሉ፤ ፤ በጋምቤላ ንፁሀንን ያስፈጁ፤ ፕ/ር አስራትን እና አሠፋ ማሩን የመሳሰሉ ድንቅ የሐገራንን ምሁራን ያስገደሉ፤ እስክንድርን፤ ርዕዮትን፤ በቀለ ገርባን፤ ኤርባና ሌሊሳን፤ የሺዋስ አሠፋን፤ አብርሐ ደስታን፤ ዳንኤል ሺበሺን፤ አበበ ቀስቶን፤ ናትናኤልን፤ ሐብታሙን፤ እና ሌሎችንም ያሠሩ፤ ከጥቂት ቀናት በፊት እንኳን የሠማያዊ ፓርቲን እና የትብብሩ አባላትን ቶርች ያደረጉ፤ በትላንትናው እለት ባህርዳር ላይ ህዝብን ያስፈጁ ሠዎች ጥርቅም ውስጥ ግርማ ዘው ብሎ የገባው፡፡

ግርማ ቆም ብሎ አስቦ ህዝቡን ይቅርታ ብሎ ጠይቆ እራሱን ከፖለቲካ ከማግለል ውጪ ሌላ አማራጭ ይኖረዋል ብዬ አላስብም ፓርቲው አንድነትም ቢሆን እንደግርማ ሠይፉ ያሉ አባላትን ይዞ መቀጠሉ ለፓርቲው አደጋ መሆኑን ተገንዝቦ ህዝቡን ይቅርታ ሊጠይቅ እና ግርማ ሠይፉን ሊቀጣው ይገባል ይህ ካልሆነ ግን ለወትሮውም በሐገራችን ፖለቲካ ተስፋ ለቆረጠው ህዝባችን ጭራሹኑ ፊቱን እንዲያዞር የሚያደርግ ታሪክ ሲወቅሠው የሚኖር ተግባር ከዛም አልፎ ሌሎች እየለፉ ያሉ ፓርቲዎች ላይ ህዝቡ እምነት እንዳይኖረው የሚያደርግ አስወቃሽ ስራ ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ በፊት ከግርማ እና ከፓርቲው መልስ ያስፈልጋል
#ሁኔአቢሲኒያ


ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
የጥንት ግብጻዊያን አንድ ልማድ ነበራቸው፡፡ በየዓመቱ ቆንጆ ልጃገረድ ይመርጡና ለአባይ ወንዝ (ኒል/ናይል) ይሰውለት ነበረ፡፡ እነዚያ ግብጻዊያን ናይል በየዓመቱ መስዋዕቱን ካላገኘ ውሃውን ይቋጥርብናል የሚል እምነት ነበራቸው፡፡ አምር ኢብን ኣስ ሀገሪቱን በያዘ በጥቂት ወራት ውስጥም ግብጻዊያኑ ለወንዙ መስዋእቱን ለማቅረብ እንደሚፈልጉ ነገሩት፡፡ አምር ጉዳዩን ለብቻው ለመወሰን ባለመቻሉ ለኸሊፋው ዑመር ቢን ኸጣብ ደብዳቤ በመጻፍ አንድ ነገር እንዲያደርጉ ጠየቃቸው፡፡ ዑመርም “እንዲህ ዓይነት ኢሰብአዊ የሆነ ድርጊት መከወን በጭራሽ አይፈቀድም” በማለት ውሳኔያቸውን አሳወቁት፡፡ አምርም ለግብጻዊያኑ ይህንኑ ነገራቸው፡፡ በመሆኑም ለናይል ወንዝ ልጃገረድ የመሰዋቱ ድርጊት ተከለከለ፡፡
ታዲያ በዚያ ዓመት የናይል ወንዝ ፍሰት በጣም ቀነሰ፡፡ ግብጻዊያኑም በተፈጠረው ሁኔታ ተጨነቁ፡፡ ወደ አምር በመሄድም “ወንዙ ፍሰቱን የቀነሰው የዓመቱን መስዋእት ስላላገኘ ነው፤ ስለዚህ ልጅቷን እንድንሰዋለት ይፈቀድልን”  በማለት ወጠሩት፡፡ አምርም የተፈጠረውን ሁኔታ ለኸሊፋ ዑመር በደብዳቤ አሳወቃቸው፡፡ ይሁንና ኸሊፋው አቋማቸውን የሚቀይሩ አልሆኑም፡፡ ስለዚህ የሚከተለውን መልዕክት በደብዳቤ አስጻፉ፡፡
  “ይድረስ የአላህ ፍጥረት ለሆነው የናይል ወንዝ! በአላህ ፈቃድ የምትፈስ ከሆነ እንደ ድሮው እንድትፈስልን አላህን እንለምናለን፤ በራስህ ፈቃድ የምትፈስ ከሆነ ግን ውሃህን መያዝ ትችላለህ፤ እኛም አንፈልግህም፡፡”
ዑመር ደብዳቤውን ለአምር በመላክ በወንዙ ውስጥ እንዲጨምረው አዘዙት፡፡ አምርም ግብጻዊያኑን ሰብስቦ መልዕክቱን አነበበላቸውና ኸሊፋው ያዘዙትን ፈጸመ፡፡ ከትንሽ ወራት በኋላም ናይል በሙሉ አቅሙ መፍሰስ ጀመረ፡፡ ግብጻዊያኑም ወንዙ በራሱ ሃይል እንደማይፈስ በማረጋገጥ ከፈርዖኖች ዘመን ጀምሮ ሲፈጽሙት የነበረውን አጉል ድርጊት አስወገዱ፡፡
       *****
በዚያ ዘመን የግብጽ ዋና ከተማ እስክንድርያ ነበረች፡፡ እስክንድርያ በባህር ላይ የተቆረቆረች መሆኗ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ሮማዊያን በባህር በመምጣት ከተማዋን በድንገተኛ ጥቃት ሊያጠፏት እንደሚችሉ የተገነዘበው አምር ቢን ኣስ በውስጠኛው የሀገሪቱ ክፍል አዲስ መዲና ለመቆርቆር ወሰነ፡፡ ለዚህ የተመረጠው ደግሞ ከእስክንድርያ በ200 ኪ.ሜ. የሚርቅ ቦታ ነው፡፡ አምርም አዲሷን ከተማ በ641 መሰረተ፡፡ መስጊድ፣ ለቢሮ የሚያስፈልጉ ቤቶች፣ መኖሪያ ቤቶች፣ የወታደሮች ካምፕ ወዘተ በከተማዋ ውስጥ ተሰሩ፡፡ ለከተማዋም “ፉስጣጥ” የሚል ስም ተሰጠ፡፡
ፉስጣጥ በናይል ወንዝ ምስራቃዊ ዳርቻ ላይ በነበረችው በሮማዊያኑ የ“ባቢሎን” ከተማዋ ጎን ነው የተሰመረተችው፡፡ ይህች ከተማ ለሶስት መቶ ዓመታት የግብጽ ዋና ከተማ በመሆን አገልግላለች፡፡ በነዚያ ዓመታት በሙስሊሞች የኺላፋ ግዛት ግንባር ቀደም ከሆኑ የትምህርትና የንግድ ማዕከላት አንዷ ነበረች፡፡ የእስልምና ስነ-መለኮት ህግ (ፊቅህ) ሊቅና የሻፊዒያ መዝሐብ መስራች የነበሩት ታላቁ ምሁር ሙሐመድ ኢብን ኢድሪስ አሽ-ሻፊዒ በመጨረሻ የህይወት ዘመናቸው የኖሩትና የሞቱት በዚህች ከተማ ነው፡፡ ታዋቂው የታሪክ ምሁር ዓሊ ኢብን ሁሴይን አል-መስዑዲም አብዛኛውን ህይወቱን ያሳለፈውና ሞቶ የተቀበረው በፉስጣጥ ነው፡፡
       *****
በ910 ገደማ በምድረ-ግብጽ የተመሰረተው የፋጢሚይ ስርወ መንግሥት (Fatimid Dynasty) መሪዎች ፉስጣጥን አልወደዷትም፡፡ “ከተማዋ ቅርጽ ቢስ ስለሆነች ውብ ፕላን ያላት ዋና ከተማ ሊኖረን ይገባል” በማለት በ967 ከፉስጣጥ በስተሰሜን 30 ኪሎሜትር ያህል በሚርቅ ቦታ ላይ አዲስ ዋና ከተማ መሰረቱ፡፡ ለአዲሷ ከተማም “አል-ቃሂራ (Cairo) የሚል ስም ሰጡ፡፡ ፉስጣጥም ዝናዋንና እውቅናዋን በአዲሷ ከተማ ተቀማች፡፡
ያም ቢሆን ግን ፉስጣጥ የንግድ ማዕከል በመሆን መስራቷን ቀጥላለች፡፡ ለዚህም የረዷት በከተማዋ ተስፋፍተው የነበሩት የመስተዋት፣የልብስና የሸክላ ስራ ኢንዱስትሪዎች ናቸው፡፡ በ1168 የመስቀል ጦረኞች (Crusaders) ግብጽን ሲወሩ የከተማዋን ህልውና የሚፈታተን አደጋ ተደቀነ፡፡ ከተማዋ እንደሌሎች የመካከለኛ ዘመን ከተሞች የመከላከያ ግንብ አልነበራትም፡፡ ስለዚህ የግብጽ መሪዎች ከተማዋ በጦረኞቹ እጅ ከምትወድቅ ብትቃጠል ይሻላል በማለት ነዋሪቿን ወደ ካይሮ ካዘዋወሩ በኋላ የአምር ቢን ኣስ መስጊድ ካለበት ክፍል በስተቀር የተቀረውን የከተማዋን ክፍል አቃጠሉት፡፡
    ከጥቂት ዓመታት በኋላ ግን ፉስጣጥ በእዉቁ የጦር ጀግና በሰላሃዲን አዩቢ ትዕዛዝ መሰረት እንደገና አንሰራርታለች፡፡ ሆኖም ሰላሃዲን ከተማዋ ለብቻዋ እንድትጓዝ አልፈለገም፡፡ በክፉም ሆነ በደጉ ከዋና ከተማዋ ጋር መሄድ አለባት በማለት ከካይሮ ከተማ ጋር እንድትዋሃድ መሰረቱን ጣለ፡፡ በመሆኑም ጥንት ለብቻዋ የከተመችው ፉስጣጥ እያደር በአዲሷ የካይሮ ከተማ ተዋጠች፡፡
  “ፉስጣጥ” በአሁኑ ጊዜ “መስር አል-አጢቃ” የሚባለው የካይሮ ከተማ ጥንታዊ ክፍል አካል ናት፡፡ የጥንቱ የአምር ቢን ኣስ መስጊድ ወደ ካይሮ ሊገባ የቻለውም ከተማዋ በካይሮ በመጠቅለሏ ነው፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 4/2007

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለምዶ የመስቀል አደባባይ ተብሎ የሚጠራውን የታቦት መውረጃ ቦታ ለግል ባለሃብቶች ለመሸጥ  ታስቧል በሚል ሰሞኑን እንቅስቃሴ በጀመረው የባህርዳር ከተማ አስተዳደር የከተማ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት ድርጊት የተቆጡት የከተማዋ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች እና በፖሊስ መካከል በተነሳው ግጭት ከ 3-5 የሚደርሱ ሰዎች መገደላቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያስረዳል፡፡ 27 ሰዎች ታስረው እየተደበደቡ …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድንገተኛ ተቃውሞው የተካሄደው በመላ አገሪቱ ያለውን የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የመብት ጥያቄን በሃይል መቆጣጠራቸውን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያምንና አዲስ አበባ መስተዳድር የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ባስታወቁ ሁለት ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነው። ዶ/ር ሽፈራው ሙስሊሙ በአደባባይ የሚያደርገውን ተቃውሞ ማቆሙንና ሌላ ስልት መጠቀም መጀመሩን ተናግረው ነበር። ይሁን እንጅ ሙስሊሙ ከዚህ …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል በጅማ ዞን ኤዳ ደሌ ቀበሌ ታዋቂ ቡና ነጋዴ የሆኑት አቶ ነፍሶ ላቫዥ ለዝርፊያ በሄዱ በአራት የፖሊስ አመራሮች ተገድለዋል። አቶ ነፍሶ ጅማ ውስጥ ቡና ነግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ መንገድ ላይ አድብተው ይጠብቁዋቸው የነበሩት ፖሊሶች የያዙትን ገንዘብ እንዲሰጧቸው ሲጠይቋቸው ነጋዴው ፈቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረቸው ፣ ሊያጋልጡን ይችላሉ በሚል ተኩሰው …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚደንት አቶ ሙክታር ከድር ሰሞኑን ለክልሉ 5ሺ473 ፖሊሶች የሰጡት የማዕረግ ዕድገት መጪውን ምርጫን በመንግስት መዋቅር፣ በጀትና ጊዜ ተጠቅሞ ለማሸነፍ ኢህአዴግ የዘረጋው ስትራቴጂ አካል እንደሆነ ታዛቢዎች ተናገሩ፡፡ መጪው ምርጫ ሊካሄድ አምስት ወራት ብቻ በቀሩት በዚህ ጊዜ የማእረግ እድገት በብዛት መስጠት ለምርጫ ከሚሰጥ የጉቦ ቀብድ ተለይቶ አይታይም ያሉት …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ነዋሪዎች እንደገለጹት በሰሜንና በደቡብ የአገሪቱ ክፍሎች የነዳጅ እጥረቱ ተባብሶ ቀጥሎአል፡ በአዋሳ ነዳጅ ለመቅዳት መኪኖችና ሞተረኞች ተሰልፈው ሲጠባባቁ ታይቷል። የነዳጅ  ዋጋ በመላው አለም በከፍተኛ ደረጃ  ቢቀንስም በኢትዮጵያ መጥፋቱ ጉዳዩን አነጋጋሪ አድርጎታል።

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የኬንያ መንግሥት ፤ ሽብር ፈጠራን በገንዘብ ይደጋፋሉ ያላቸውን 15 ቡድኖች ጨምሮ ባጠቃላይ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ የመንግሥት ያልሆኑ ድርጅቶች በሕግ የተመዘገቡትን ደንብ ሽሯል።

በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራትን ሁኔታ የዳሰሰ ጥናትና ዉይይት መካሄዱ፤ ዴንማርክ ስለኤርትራ ስደተኞች ያወጣችዉ ዘገባና ማስተባበያዉ፤ ኬንያ፤ የመንግሥት ባልሆኑ ድርጅቶች ላይ የወሰደችዉ ጥብቅ ርምጃ እንዲሁም ጀርመን የተባበረችበት የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኞች ስልጠና…

የዴንማርክ መንግሥት ስለ ኤርትራ ስደተኞች የሚከተለዉን መርሕ እንዲቀየር ሃሳብ የሚያቀርበዉን የሐገሪቱን የስደተኛ ጉዳይ ዘገባ «ጥልቅ ስህተት ያዘል ዘገባ ሲል» የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት «HRW» አጣጣለ።

‹‹ ስሜ አቤል ዋበላ ነው፡፡ አዲሱ አመት ሲጠባ በአዲስ መንፈስ አዲስ ህልም ለአገሬ ማለም የነበረኝንም ማጠናከር እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያችን የብሄር፣ የሃይማኖት፣ የሀብት፣ የትምህርት፣ የፖለቲካ አመለካከት እና ሌሎችም ልዩነቶች አብሮነታችንን የማያደናቅፉባት ከነልዩነታችን በጋራ ለታላቅነት የምንጠቀምባት ለሁላችንም ዕኩል ዕድል እና ተጠቃሚነት የሚቀርብባት ሁላችንም እንደየ ችሎታችን ለጋራ ደህንነታችን ነፃነታችን እና ብልፅግናችን የምንሰራባት ብቻ ሳይሆን በጋራ ስኬታማ የምንሆንባት እንዲሁም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዕኩል የሚያፈቅራት ኢትዮጵያ እንድትሆን እመኛለው፡፡ ይህ የእኔ ኢትዮጵያዊ ሕልም ነው፡፡››
ከላይ የሰፈረው ጽሁፍ ዞን ዘጠኝ ባዘጋጀው አራተኛው የበይነ መረብ ዘመቻ(Online Campaign) ላይ የተጠቀምንበት ነበር፡፡ የዘመቻው ርዕስ ‹ኑ አብረን ኢትዮጲያዊ ህልም እናልም › ሲሆን የተካሄደውም በ2005ዓ.ም መገባደጃ ወር ጰግሜ ላይ ነው፡፡ በአጋጣሚ ዘመቻው መንግስት የማናውቀውን ‹ወንጀል› እየፈለገብን እንደሆነ ከሁነኛ ምንጮች ከተረዳንበት ወቅት ጋር ገጥሟል፡፡ ለነገሩ ጠቅላይ ሚንስትሩ በቀደም ፓርላማ ቀርበው ‹‹ኢህአዴግ ሀሳብ የሚፈራ ድርጅት አይደለም››ሊሉ እንደፎከሩት ሳይሆን የሃሳብ ልዩነት እንደሚያስበረግገው ስለምናውቅ መስጋታችን አልቀረም፡፡ ከሌሎች ምንጮችም እርግጠኛ ያልሆኑመረጃዎች ደርሰውን ነበር፡፡ ይሄኛው ግን እርግጥ የሆነ ጅቡ ከበራፍ ላይ እንደቆመ የሚያበስር ነው፡፡
እንደ ሌሎች ዘመቻዎች ሕገ መንግስታዊነት፣ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ….. የመሳሰሉ ለሃገራችን “ቅንጦት” የሚመስሉ ርዕሶችን ማንሳት አልፈለግንም፡፡ አሁን የድራማው ዘመን ተቀይሮ እውናዊ  ሆኗል፡፡ ይህም የኔ የምንለው ትውልድ ምን አይነት ውስብስብ ችግር ውስጥ እንደተዘፈቀ በብርቱ እንድናስብ አደረገን፡፡ ለዚህም ነበር ሁሉን የሚያሳትፍ የትውልድ አቻዎቻችንን የሚጠራ ሰፊ ርዕስ የመረጥነው፡፡ ሁላችንም እንደምናስታውሰው ውጤቱ አርኪ ነበር፡፡
ስርዓቱ ግን ስለሃገራችን ያገባናልማለታችንን የትውልድ አቻዎቻችንን መፈለጋችንን አልወደደውም፡፡ የዘውጉን እውናዊነት ለማጠናከር ትምህርት ሊሰጠን ወደደ፡፡ መምህራን፣የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ቤተ ሙከራ ተዘጋጀ፡፡ አንደ አጋጣሚ ብቻ ሆኖ ከዞን ዘጠኝ ኢ-መደበኛ የጦማሪያን ቡድን ስድስታችን እና ሌሎች ሶስት ጋዜጠኞች (ኤዶም ካሳዬ፣ ተስፋለም ወልደየስ እና አስማማው ኃ/ጊዎርጊስ) ለተማሪነት ተመረጥን፡፡ ትምህርቱም ሚያዚያ17/2006 ዓ.ም በፌደራል ፖሊስ ውንጀል ምርመራ ዘርፍ (በተለምዶ ማዕከላዊ) ተጀመረ፡፡
ትምህርት አንድ
የመጀመሪያው ትምህርት የሀገራችን ኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ መረዳት ነበር፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ የፖለቲካ ትንታኔ የሚሰጥ ወዳጃችን በዞን ዘጠኝ የሚደረጉ ሙከራዎችን አድንቆ ተጨማሪ መስራት ያለብንን ስራዎች ሊጠቁመን ‹‹ እናንተ ብዙ ጊዜ የምታተኩሩት የከተማ ፖለቲካ ላይ ነው፡፡ እስኪ ወደገጠር ጫንጮ እንኳን ሂዱ ከገበሬው ጋር ጠጅ እየጠጣችሁ ብሶቱን አድምጡና ጻፉ፡፡›› እንዳለን አስታውሳለሁ፡፡
እኛም ይህን ትችት ሙሉ ለሙሉ ተቀብለን በተግባር ባናደርገውም ከከተማ ወጣ ብሎ ለመመለስ ዕቅድ ይዘን ነበር፡፡ ማእከላዊ ግን ይህን ድካማችንን አቅልልሎ ሁሉንም አይነትኢትዮጵያዊ መልኮችን ከየአቅጣጫው አመጣልን፡፡ እነ ኡባንግን ከጋምቤላ፣ እነዚያድን ከደጋሃቡር፣ እነ አብድልከሪምን አቤኒሻንጉል፣እነ አያያዎን ከጎንደር፣እነ ቄስ ብርሃኔ ከአክሱም፣ እነ ሼህ መሀመድን ከጅማ አሰባሰበልን፡፡ የእስር ቤቱን ጨለማ ቀን እና ጨለማ ሌሊቶች ከልብ በሆኑ ወሬዎች አደመቅናቸው፡፡ ፖለቲካዊ ብልጣብልጥነት ያልነካካው ከጭቆናው የመጀመሪያ ረድፍ ገፈት ቀማሾች የሚቀዳ እውነትን አደመጥን፡፡በሰውነት ከመከበር አንስቶ እስከ የምድሪቱን ፍሬ በዕኩልነት መጠቀም ጥሮ ግሮ ኑሮን ለማሸነፍ የሚያስችሉ ዕድሎች ፍትሕአዊነት፣ ሳይፈሩና ሳያፍሩ ሀሳብን መግለጽ በወረዳና ቀበሌ ደረጃ የሚያስከፍለው ዋጋ፣ ከስር ባሉ የቢሮክራሲው አካላት የሚፈፀም ተቋማዊ ግፍ በአጠቃላይ አድርባይነትና አስመሳይነት በመላው ሀገሪቱ እንዴት እንደሰፈነና ብዙሃኑም ኑሮውን በቀቢጸ ተስፋ እንደሚገፋ ተረዳን፡፡ ሁሉም የጎላው ምስል ግን ዛሬም ፌደራሊዝሙ መሰረታዊ የሆኑትን የስልጣንና የሀብት (Power and Resource)ጥያቄዎች እንዳልመለሰ በጉልህ ይናገራል፡፡
ከመታሰሬ በፊት በነበረኝ ግምት በርካታ የኦሮሞዎ ተወላጆችን በማረሚያ ቤት እንደማገኝ ጠብቄ ነበር የመጀመሪያው ሰሞን  ከዚህ የተለየ ነበር፡፡ በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ከታሰሩ አንዳንድ ሙስሊም ኦሮሞዎችበስተቀር ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች አልነበሩም፡፡ ይሄ ግን ብዙ አልቆየም፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የኦሮሚያ ልዩ ዞንን በሚነካው አዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ ማስተር ፕላን የተነሳ በተፈጠረው ግርግር በርካታ ኦሮሞ ተማሪዎች ከየዩንቨርስቲው ተለቅመው መጡ፡፡ ያን የስቃይ ቤት በሳቅ ጨዋታቸው አደመቁት፡፡ ውይይታችንም ብዙ ርዕሰ ጉዳዮችን ዳሰስን፡፡ እኛም ብዙ ተማርን፡፡ በእነርሱ መሪነት በህብረት የምናዜማቸው የኦሮሚኛ ዘፈኖች የነበርንበትን አስቸጋሪ ሁኔታ አስረሱን፡፡
ከሁሉም ከሁሉም biyya Toodhuufen silaala yaa Biyaa Dubro maagala (የጠይም ቆንጆዎች መፍለቂያ ሀገሬ መጥቼ አይሻለሁ) የሚለውን እንጃ የኔን ቀልብ የሳበ ዜማው አንጀቴን ሰርስሮ የገባ ነበር፡፡ አገሬ ጠያይም ቆንጆ ልጆችሽ በነፃነትና በእኩልነት እንዲኖሩብሽ አልማለሁ፡፡ይህ የኔ ኢትዮጵያዊ ሕልም ነው፡፡   
ትምህርት ሁለት
ሁለተኛው ትምህርት በተግባር የተደገፈነው፡፡ በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት የተሰሩ የሰብዐዊ መብት አያያዝ ሪፖርቶችን ማንበብ ከጀመርኩኝ ጥቂት አመታት አልፈዋል፡፡ሁሌም እንደተለመደው ኢትዮጵያ የዜጎቻቸውን ሰብዐዊ መብት ከሚጥሱ እና የማሰቃየት ተግባር የሚፈፅሙ በተለይም በተለምዶ ማዕከላዊ ተብሎ የሚጠራው የመንግስት ተቋም በዋነኝነትእንደሚጠቀስ ብዙዎቹ ሪፖርቶች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህ በመነሳት እስካሁን ድረስ የማሰቃየት ተግባርን (Torture) እኔም ሆነ ጓደኞቼ የምንረዳው እንደማንኛውም የሰብአዊ መብት ጥሰት እንዲሁ ነበር፡፡በተለይ እኔ በበኩሌ የተለየ ትኩረት እንደማልሰጠው አልሸሽግም፡፡
አሁን እነዚያ የአለማወቅ ወራት አልፈዋል፡፡ በታሪክ መጽሃፍት ላይ በዘመነ ደርግ እንደሚፈጸሙ ያነበብናቸው አስከፊ ተግባራት አሁንም በሃገራችን እንደሚፈፀሙ ህያው ምስክሮች ሆነናል፡፡ ከስነ ልቦናዊ የማሰቃየት ተግባር አንስቶ የተለያዩ የማሰቃያ ቁሳቁስ በመጠቀም እስከሚፈፀሙ ዘግናኝ ተግባሮች በእኛና በሌሎች ላይ ሲፈፀም ተመልክተናል፡፡በከፍተኛ ድብደባ እግሮቹ የሚወላከፉ፣ መራመድ አቅቶት በሸክም ወደ ማረፊያ ቤት የሚመለስ፣ በግርፋት ብዛት ጀርባው ብዙ ሰንበርየተጋደመበት፣ ብልቱ ላይ ሁለት ሌትር ውሃ በመንጠልጠሉ ምክንያት ሽንቱን መሽናት የተቸገረ፣ ጆሮው በጥፊ ደንቁሮና አፍንጫው የሚደማሰው መመልከት የየዕለት ተግባራችን ሆነ፡፡ በኤሌክትሪክ ሾክ የተደረጉና ‹ወፌ ላላ› ተገልብጠው እንደተገረፉ የሚናገሩ ተጠርጣሪዎችም አጋጥመውኛል፡፡ ስድብ፣ ዛቻውና የማዋረዱ ተግባር አእምሮ ሊቆጣጠረው የሚችል አይደለም፡፡ የቀረውን የማሰቃየት ተግባር ሲፈፀም ያዩና በራሳቸው ላይ የተፈፃመባቸው ይናገሩት፡፡   
ይህ ተቋም ባለበት ከተማ ምንም ነገር እንዳልተፈጠሩ ቆጥሬ ስራዬን እየሰራሁ እየበላሁ እና እየጠጣሁ በቆየሁባቸው ዓመታት አፈርኩኝ፡፡ በአገሬ ኢ-ዲሞክራሲያዊነት እንዲታለፍ ዲሞክራሲያዊነት እንዲጀመር ከዜሮ ትንሽ ከፍ የሚል መፍጨርጨር በማድረጌ ግን ተፅናናሁኝ፡፡ የማሰቃየት ተግባርን በንድፈ ሀሳብ ደረጃ መረዳትና  መረጃዎችን በልብ ማኖር አንድ ነገር ነው፡፡ ዘግናኝ የማሰቃየት ተግባር የተፈፀመበት ተጠቂ ማግኘትና ማናገር ሌላ አንድ ነገር ነው፡፡ የማሰቃየት ተግባርን በራስ ሰውነት ማስተናገድ ግን ከሁሉም ይለያል፡፡ ባለቅኔው ሰው የሚማረው አንድም በሳር ‘ሀ’ ብሎ አንድም በአሳር ‘ ብሎ እንዳለ ከዚህ በላይ ትምህርት ከወዴት ይገኛል!?
የፌደራል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ትልቅ ተቋም ነው፡፡ ምርመራ ደግሞ ሳይንስ፡፡ ሀገራችን የምር በሽብርና የሌሎች ወንጀሎች ስጋት ቢኖርባት ተጠርጣሪዎችን መርምሮ ለፍርድ የማቅረብ ዋና ሀላፊነት ያለበትይህ የፍትህ አካል ነው፡፡ በአግባቡ ከተከናወነ ሕጋዊነትን ባህል የሚያደርግ ነገር ግን ተጠርጣሪዎች ላይ የማሰቃየት ተግባር የሚፈፀምበት ከሆነ ደግሞ ሙሉ የፍትህ ስርዓቱን አቀጭጮ የሚያስቀር ነው፡፡ ይህንን የሰው ልጅ ማሰቃያ ስፍራ ለቀን ወደ ማረሚያ ቤት ስንወሰድ አበራ ጀምበሬ Agony in the grand palace ላይ ያሰፈረውን
Commit to the paper the suffering in that dark chamber
Announce to the world all the unbearable torture
የሚለውን ግጥም እያሰብኩኝ አንድ ተጨማሪ ህልም አለምኩኝ፡፡ ይህን ፖለቲካዊ የሀሳብ ልዩነትን መዳመጫና የህሊና እስረኞችን ደም ማፍሰሻ የሆነ ተቋም ወደ ሙዚየም ተቀይሮ ማየት ነው፡፡ ይህ የኔ ኢትየጵያዊ ህልም ነው፡፡
ትምህርት ሶሰት -የትውልድ እዳ
ሶስተኛው ትምህርት የሚገኘው መንግስት ወደ ጦማርያን እጁን እንዲሰድ ያደረገውን ተግባርና እስሩን ተከትሎ የታየውን ምላሽ በመገምገም ነው፡፡ ከዚያ በፊት ግን ቮልቴር  If you wish to converse with me define your terms እንዳለው ከዚህ በኋላ ‹‹ትውልድ›› ወይም ‹‹የትውልድ ልሂቃን›› ስንል ምን ማለታችን እንደሆነ ብያኔ ሰጥቼ እቀጥለላሁ፡፡ የነገሩን ውል ለመጨበጥ ትንሽ ወደኋላ መንደርደር አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ ትውልድ ስንል ተቀራራቢ የእድሜ ክልል ውስጥየሚገኝ መሰረታዊ ለውጥ በሌለውና አንድ ሊባል በሚችል ስርዓተ ትምህርት ያለፈ የአንድ ስርዓት(Regime) ውጤት የሆነ እና የዘመኑን መንፈስ የተሸከመ ማለታችን ነው፡፡ የትውልድ ልሂቃን ስንል ደግሞ ሰፊውን የልህቅነት ትርጓሜ ሊገኝ ከሚችለው ነገር አብላጫውን ያገኙ(those who get the most of what there is to get)የሚለውን እንወስዳለን፡፡ ይህንን ብይን መሰረት በማድረግ አንድ ሰው ያገኘውን የትምህርትና የስራ እድል የገቢ መጠንና በማህበረሰቡ ያለውን ቦታ ከጠቅላላው የሀገሪቱ ዜጋ ጋር በማወዳደር የእርሱ ስፍራ የቱጋ እንደሆነ ይረዳል፡፡
አንድ ትውልድ ዘመኑ የሚጠይቀውን ኃላፊነት በአግባቡ ካልተወጣ በዚያች ሀገር ያሉ ችግሮችን ለማስተካከል ያለው እድል እየጠበበ ይመጣል፡፡ ሳንካ መፍትሄ ሳያገኝ በዘገየ መጠን የበለጠ እየከበደ እና እየተወሳሰበ ስለሚሄድ መፍትሔ ለመስጠት አዳጋችና ብዙ ዋጋ የሚያስከፍል ይሆናል፡፡ 
የሀገራችንን የቅርብ ጊዜ ታሪክ በዚህ አውድ ስናጤን ከጣሊያን ወረራ በኋላ ሀገሪቱን የተረከበው ልሂቅ የፊውዳል ስርዓቱ ዘመኑን እንደማይመጥን እና የሕዝቡን ችግር የመፍታት አላማ እንደሌለው ተገንዝቦ ለመሰረታዊ ለውጥና ማሻሻል ከመስራት ይልቅ ስርዓቱ የፈጠረለትንና የፈቀደለትን የትምህርትና የስራ እድል በመጠቀም ስርዓቱን ማገልገል ምርጫው አድርጓል፡፡ የነዚህ አዳዲስ ምሁራን ዘመኑን ያልዋጀ ጥረት የተመለከተው ማኅበረሰብም ‹‹ከእጅ አይሻል ዶማ›› ብሎ ይጠራቸው ነበር፡፡ በዘመኑ ከነበሩት ስመጥር ቴክኖክራቶች አንዱ የሆኑት የቀድሞውብሔራዊ ባንክ ገዢ  ተፈራ ደግፌ “Minutes of an Ethiopian Century” በተሰኘው መጽሐፋቸው ይህንን እውነታ በሀዘኔታ ያስታውሱታል፡፡
‹‹The tragedy of our Post-war generationof Ethiopian elite was that we adapted an attitude of public silence and private passivity on this professional level walking away from society instead of confronting its problems››
ልሂቁ ከ1953ቱ መፈንቅለ መንግሥት በቀር ምንም ሊጠቀስ የሚችል እንቅስቃሴ ሳያደርግ ዝምታን መምረጡ ለሚቀጥለው ትውልድ ግዙፍ ያልተሰሩ የቤት ሥራዎችን እንዳስረከበው መረዳት አያዳግትም፡፡ በክፍሉ ታደሰ ስሌት መሰረት 1930ዎቹ፣ በ1940ዎቹ እና በ1950ዎቹ የመጀመሪያ አጋማሽ የተወለዱና በ1960ዎቹ እና በ1970ዎቹ ንቁ የፖለቲካ ተሳትፎ የነበረውን ልሂቅ ያቀፈው ‹‹ያ ትውልድ›› ከወታደራዊው መንግሥትና እርስ በእርሱ ብዙ ዋጋ ያስከፈለ ትግል አድርጓል፡፡እንደመሬት ላራሹ ያሉ ውጤቶች ቢገኙበትም ሕጋዊነትን ዲሞክራሲያዊነት እንዲጀመር መሰረት ባለመጣሉ በኋላ ለመጡት ሁለት አምባ ገነንሥርዓቶች መነሳት መንስዔ ሆኗል፡፡ 
ወታደራዊ መንግሥት ወድቆ የሽግግር መንግስት የተቋቋመ ሰሞን ስመ ጥሩ ኢኮኖሚስት እሸቱ ጮሌ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ማኅበረሰብ እንዲመሰረት የ1966ቱን አብዮት ለመራው ትውልድ የሰጠው እድል በወታደራዊው ኃይል መጨናገፉን በመጥቀስ ‹‹ታሪክ ሀገራችንን የምንታደግበት እና ከገባችበት አዘቅት ውስጥ ጎትተን የምናወጣበት ተጨማሪ እድል ሰጥቶናል፡፡ ለአንድ ትውልድ የሚሰጥ ሁለት እድል እንዲሁ በዋዛ የሚገኝ አይደለም፡፡ ሁለቱንም በግዴለሽነትና በሞኝነት ማባከን በቀጣዩ ትውልድ ይቅር የማይባል ወንጀል ነው፡፡››ብለው ቢመክሩም ያ ትውልድ ከራሱ ታሪክ ሳይማር ቀርቶ ዳግም አገሪቱን ወደኋላ የሚጎትት ስህተት ሰርቷል፡፡ 
በስርዓቱ አምባገነንነት የተነሳ በአገሪቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮች በንቃትመሳተፍ የነበረበት አዲስ ትውልድ (በ1980ዎቹ እና በ1990ዎቹ) ምንም ሊጠቀስ የሚችል ነገር ሳይሰራ አልፏል፡፡ ስደተኛው ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ከምርጫ 97 ጋር ከተያያዙ እንቅስቃሴዎች በስተቀር ጉልህ ድርሻ ያልነበረውን ይህንን ትውልድ ‹‹የጠፋ ወይም የባከነ›› ብሎ ጠርቶታል፡፡ ምርጫ 97ትም በቅንጅትም ሆነ በሕወሀት ኢኅአዴግ በኩል የመሪነት ሚና የተጫወቱት የያ ትውልድ አባላት በመሆናቸው ለትውልዱ ሙሉ እውቅና ለመስጠት ይከብዳል፡፡
ከዚህ ተስፋ ሰጭ ሙከራ በኋላ ስርዓቱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የግል ሚዲያውንና ሲቪል ማኅበረሰቡን አዳዲስ አፋኝ አዋጆች በማውጣት ፣ በማሰር እና በሌሎች እኩይ ተግባራት ማዳከሙ ሁላችንም የምናስታውሰው የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ በዚህ አካባቢ ነው ዞን ዘጠኝ ኢ-መደበኛ የጦማርያን ቡድን  መንቀሳቀስ የጀመረው፡፡ የመጀመሪያዋ ጦማር ‹‹የሚያገባው ትውልድ ፍለጋ›› በሚል ርዕስ የወጣች ሲሆን ይህም ዞኑ ከዚያ በኋላ ያደረጋቸውን እንቅስቃሴዎች በሙሉ የቃኘ ነበር፡፡ በአጠቃላይ ከየትኛውም ብሔር ፣ ሃይማኖትና ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ያልወጣና አማራጭ ትርክት በማቅረብ ትውልዱ በሀገሪቱ ጉዳዮች ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ማነቃቃትን አላማው ያደረገ ነበር፡፡ አቅማችን በፈቀደ መጠን ከአለፉት ትውልዶች በተለይም ከያ ትውልድ ለመማር ሞክረናል፡፡ የሀገሪቱ ችግሮች ውስብስብ መሆናቸውን በመረዳት የትውልድ አቻዎቻችንን እኛም የምንማርበት መድረክ እንዲሆን ምኞታችን ነበር፡፡ ዝምታው ተሰብሮ በኃላፊነት ውይይት እንዲጀመር ተነሳሽነቱን ወሰድን፡፡ 
የውይይቱ መንፈስም ከጽንፈኝነት የፀዳ የሀሳብ ልዩነትን የሚያከብር እና ለአካዳሚያዊ ሀሳቦች ልዕልና የሚሰጥ ለማድረግም ሞክረናል፡፡( ህገ መንግስቱ ይከበር ሰንል የወያኔን ህገ መንግስት እውቅና ሰጡ ብለው ያጣጣሉን ድምጾች ቀላል አልነበሩም) ሀገራችን ያላት ደካማ የውይይት ባህልና ሥርዓቱ በየጊዜው የሚፈጥሯቸው ወደር የለሽ ብሶቶች ዋነኛ ተግዳሮቶች ነበሩ፡፡ እኛም የዚህ ማኅበረሰብ ባህልና ታሪክ ውጤቶች በመሆናችን መፈተናችን አልቀረም ፡፡ ነገር ግን ለጫና አልባው ውይይት (endless conversation) በተለይ እርስ በርሳችን በነበረን መስተጋብር ታማኞች ነበርን፡፡
ብዙዎች እንደቂልነት ሊወስዱት ቢችሉም የውይይቱ መድረክ አፍቃሪ ኢኅአዴግ የሆኑ ሰዎችና ራሱን ስርዓቱን የሚጨምርና የማያበሳጭ እንዲሆን በተቻለን መጠን ጥንቃቄ እናደርግ ነበር፡፡ ይህንን ጥረታችንን ብዙ ሰዎች  ትንሽ ሙከራችንን በለጋስነት እንዲወስዱት አደረጋቸው፡፡ ይህ ለጋስነት በሀገር ውስጥ እና በባህር ማዶ የሚገኙ የምናከብራቸው ሰዎችንና ተቋማትን ይጨምራል፡፡ እንደጠበቅነውም ብዙ ያልሆኑ ነገር ግን በቂ ሊባሉ የሚችሉ የትውልድ አቻ ወዳጆችን አፈራልን፡፡ ዞኑም የዘጠኝ ሰዎች ብቻ መሆኑ አከተመ፡፡ ‹‹ይህንን ብታስተካክሉት›› ‹‹ይህቺን ደግሞ እንዲህ ብታደርጓት›› እያሉ ድካማችንን እና ስንፍናችንን ማየት የማይፈልጉ ብዙ ሆኑ፡፡ 
በዚህ ሂደት እኛም ብዙ ተማርን፡፡ የተወሰኑ ኢ-መደበኛ የቡድኑ አባላትም የሕይወት ውሳኔዎችን በመወሰን ስራዎችን በመተው አራማጅነትን እና ጦማሪነት ጋር የተያያዙ ሙያዎች ውስጥ ገቡ፡፡ በፊት የምናከናውናቸውን ትንንሸ ስራዎች መስራት ለእኛ የማያረካ አክባሪዎቻችንንም መናቅ ሆኖ ተሰማን፡፡ ለበለጠ ስራ እራስን ወደ ማዘጋጀት ያሉብንን የአቅምና የቁርጠኝነት ችግሮች ለመፍታት ረዘም ያሉ እቅዶችን ያዝን፡፡ 
እኛ እንዲህ እና እንዲያ እያልን እናስባለን፡፡ መንግስት ደግሞ ስልካችንን ጠልፎ ከዋልንበት እየዋለ በብዙ ጆሮዎችና አይኖች እየሰለለን ወንጀል ሳይሆን ሰበብ ፈልጎ ሊያስረን አድፍጧል፡፡ በመጀመሪያ ‹‹ለራሳችን ትክክል ያልሆነ ትልቅ ግምት ስለሰጠን ነው እንጂ መንግሥት እኛን ምን ሰራችሁ? ምንአጠፋችሁ ብሎ ያስረናል?›› ብለን አጣጣልነው፡፡ የመታሰራችን ምልክቶች ሲገዝፉ ደግሞ ከብዙ ማሰላሰሎችእና ክርክሮች በኋላ እስከአሁን ያደረግነው ‹‹ወንጀል››  ከሆነ ካቴናው በእጃችን እንዲገባ ፈቅደን ጡመራውን እንደምንቀጥል በይፋ አውጀን ተመለስን፡፡ 
ጤናማ ሕዝባዊ ተዋስኦ (Public Discourse) እንዲዳብርና ኃላፊነትየሚሰማው ትውልድ እንዲፈጠር መድከም በእኛ የተጀመረ አይደለም፡፡ ብዙዎች በእስር፣ በግዞት (በስደት) እና በሞት ዋጋ የከፈሉበትነው፡፡ የኛን ትውልድ መንፈስ ለማረቅ ያደረጉት እያንዳንዱ ነገር በህሊናችን የገነነና በታሪክ ተመዝግቦ የሚቀመጥ ነው፡፡ ማንም ሊቀይረው በማይችለው የተፈጥሮ ኡደት እኛም ባለተራ ሆነናል፡፡ አገር አገር የምንለው በግልብ ብሔረተኝነትና በአጉል አርበኝነት መንፈስ በመነሳት አይደለም፡፡ የሀገር አመሰራረት ንድፈ ሀሳብና የአለማችን ጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታ በመገንዘብ ነው እንጂ፡፡ ሀገራችን ከታሪኳ፣ከራሷና ከአሁኗ ጋር እንድንታረቅ ዋና ፍላጎታችን ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሚሆነው የመናገር ነፃነት ሳይገደብ ሁሉም የሀገሪቱ ጉዳዮች የሰለጠነ ጫና አልባ ውይይት ሲደረግባቸው እንደሆነ እናምናለን፡፡
ከትውልድ ጥቂቶችን በማሰር፣ ከሀገር እንዲወጡ በማስገድዶ በማሰደድ እና በመግደል የትውልድ ጥያቄን መቀልበስ ይቻላል ብሎ የሚያስብ ቢኖር እንዳይስት ይጠንቀቅ፡፡ የ1953ቱን መፈንቅለ መንግሥት  መክሸፍን ተመልክቶ ንጉሱ የመፈንቅለ መንግሥቱን ጠንሳሾች በማሰርና በአደባባይ በመስቀል የትውልዱን የለውጥ ጥያቄ ያዳፈኑ መስሏቸው መሰረታዊ ማሻሻል ማድረጉን እንዳይዘነጉ ከመከሩ ሰዎች ውስጥ አንዱ ደራሲ ዶክተር ሀዲስ አለማየሁ ናቸው፡፡ በዚህ ታሪካዊ ምክራቸውን ንጉሱ ከቁብ ባይቆጥሩትም‹‹ለማናቸውም ነገር መነሻ የሆነው ሥሩ እንደተደበቀ ተቀምጦ ከላይ እንደሚታየው ቅርንጫፉን ብቻ ቢጨፈጭፉትና ለጊዜውእንኳ የጠፋ ቢመስል የተመቸ ጊዜ ሲያገኝ የተደበቀው ስር ዳብሮ ተስፋፍቶ ለመጥፋትም እንደሚያስቸግር ሆኖ ይነሳል›› ብለው ተንብየው ነበር፡፡ የዚህ ዘመንም ነገር ጥቂት እድሜ የሰጠው ሰው ሲፈፀም የሚያየው ነው፡፡ 
እስር ሲታሰብ ብዙ ስጋቶች ወደ አዕምሮ ይመጣሉ፡፡ ከሁሉም የሚከብደው ግን ቤተሰብን ማንገላታትና በማረሚያ ቤት ተረስቶ መቅረት ነው፡፡ ቀበቶዬን አስረክቤ ወደማረሚያ ቤት ስወሰድ ይህንን እያወጣሁኝ እያወረድኩኝ ነበር፡፡ ያለፉት ሰባት ወራት የእስር ቆይታዬን ግን በመጠኑም ቢሆን መሳሳቴን ነግሮኛል፡፡ ማዕከላዊ ጨለማ ቤት በነበርኩኝ ጊዜ ጠያቂ ሰው ማግኘት የሚፈቀደው በሳምንት አንድ ቀን ለቤተሰብ አባላት ብቻ ነበር፡፡( እሱም ከሁለት ሳምንት “ምርመራ” በኋላ ከቤተሰብ ውጭ ጠያቂ ሲመጣ እኛን ማግኘት ስለማይፈቀድ የጠያቂው ስም በቁራጭ ወረቀት ላይ ተፅፎ ይመጣ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች ለእኔ ብዙ ትርጉም ነበራቸው፡፡ በእስር ቤት አለመረሳቴን እና ስለእኔ እስር የሚጨነቁ ወዳጆች እንዳሉኝ እዚያ ጨለማ ቤት ያለሁት ለግልጉዳዬ ሳይሆን ማኅበረሰባዊ ጉዳይ(public cause) ይዤ መሆኑ እያስታወሰ መንፈሴ ሳይሰበር ያኖረኝ ነበር፡፡ ፍርድ ቤት ስንቀርብ ከሩቅ የማያቸው ብዙ ፊቶች መንፈስን የሚያረጋጉና የሚያጽናኑ ናቸው፡፡ በሀገር ውስጥ እና በባህር ማዶ ያሉ የቅርብ ጓደኞቻችን በአካልነው እንጂ በመንፈስ ከእኛ ጋር አልታሰሩም ማለት ይከብዳል፡፡ ከከንፈር መጠጣ በዘለለ  እስሩ እንዳይከብደን እና በሕግ ፊት (ይፈተን ዘንድ ነው እንጂ የፍትሕ ስርዓቱ ብቻውን ተነጥሎ ጤናማ እንደማይሆን ለቀባሪው ማርዳት ነው) ንጽህናችንን ለማረጋገጥ የሚያስፈልገውን ከማድረግ አልቦዘኑም፡፡ 
ማንዴላ አንድ ሰው ወህኒ እስኪወርድ

Image
የተለያዩ መፈክሮችን የያዙ ፊኛዎች ወደ ተውለብለበዋል :: ፊኛዎቹ የተለያዩ መፈክሮች የተጻፈባቸው ሲሆን ከነዚህም መካከል : – ትግሉ ይቀጥላል ፍትህ ነጥፏል ፤ሂጃብ መለያችን፤ኒቃብ ውበታችን ፤ትግላችን ቀጥሏል
ፍትህን ማዘግየት ፍትህን መንፈግ ነው ፤ትግላችን እንደቀጠለ ነው ::

ፍትህ ፍትህ ፍትህ ;We Need Justice ፤Hijab Is Beauty ፤ justice Is Denied የሚሉት መፈክሮች ይገኙበታል፡፡ በርካታ ፊኛዎች የተውለበለቡና ወደ ሰማይ የተለቀቁ ሲሆን ተቃውሞው በከፍተኛ ድምቀት ተከናውኗል፡፡ መንግስት በሴኩላሪዝም ሽፋን እየፈጸመ ያለውን የሂጃብ ገፈፋ የሚያወግዝ ሲሆን በተጨማሪም በህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ እጸፈጸመ ያለውን የፍትህ መዛባት ፤ በማረሚያ ቤቱ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማውገዝ ነው፡፡ መንግስት ሙሉ በሙሉ ተቋሞውን በሃይል አስቁሚያለሁ ሲል የነበረ ሲሆን ህዝበ ሙስሊሙ ግን ድንገተኛ ተቃውሞ በማድረግ አስገራሚ ተቃውሞውን ገልጽዋል፡፡

Please wait, video is loading…

የባህዳር ነዋሪ በነቂስ በመውጣት በክልሉ ም/ቤት ፊት ለፊትና በአዲሱ ም/ቤት(ቀበሌ 10) መስቀል አደባባይ የቤተክርስያን የታቦት ማደሪያ ፣ ንብረትነቱም የቤተ-ክርስቲያን ነው ልትነጠቅ ወይም መንግስት እንደሚለው ለባለሀብት ሊሰጥ አይገባም በማለት ቁጣቸውን በማሰማት ላይ ናቸው፡፡ የባጃጅ ሾፌሮችም በየቦታው ትላክስና ጩኸት እያሰሙ ነው፡፡ የመስቀል አደባባይን መፍረስ በመቃወም በባህርዳር ከተማ የነበረው ሰልፍ ጥያቄውን አሰምቷል:: ሆኖም በአሁኑ ሰዓት በባህርዳር ከተማ በሕዝበ […]

ቁም ነገር መፅሔት ቁጥር 193 ታህሣስ 2007

ለሶደሬ

ሰሞኑን አዲስ ስያሜ ይዘህ የወደፊት መለያዮን/ፈረንጆች ሎጎ ይሉታል/ ስሩልኝ፤ የጣቢዬንም መርህ /ሞቶ/ ሰይሙልኝ ብለህ ያስነገርከውን ማስታወቂያ ተመልክተናል፡፡ እርግጥ ነው ገና ስያሜህን ቀይረህ በኢቲቪ መስኮት ብቅ ባልክበት ሰሞን አንድ ጦማር በዚሁ ገፅ ላይ መፃፋችንን…

ምርጫ በአንባገነን መንግስት ውስጥ? ምርጫ የዴሞክራሲያዊ ስርአት መገለጫ የሚሆነው ነጻ፣ ፍትሃዊና ተወዳዳሪ (free, fair and contested) ባህሪያትን የተላበሰ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ በኢ-ዴሞክራሲዊ መንግስት ውስጥ የሚደረጉ ምርጫዎች በምንም መመዘኛ የዴሞክራሲ ስርዓት መገለጫዎች አይሆኑም፡፡ በሀገራችን በአጼው፣ በደርግ እና በኢህአዴግ ዘመነ-መንግስታት ተደርገው የነበሩ ምርጫዎች የአጼውን፣ የደርጉንና የኢህአዴግን የአገዛዝ ስርዓቶች የስልጣን ዘመን ለማራዛም የተደረጉ (“mechanism of regime maintenance”) ምርጫዎች […]

ቁም ነገር መፅሔት ቁጥር 193 ታህሣስ 2007
ለሶደሬ

ስለ ሜሮን ጌትነት ግጥምና ውዝግቡ
መቼም ሰሞኑን በማህበራዊ ድረ ገፆች ላይ ህዝቡ እየተቀባበለው ያለውን ‹አትሂድ› የሚለውን የሜሮን ጌትነት ግጥም አልሰማሁም አትለኝም? ወር በገባ በመጀመሪያው ረቡዕ በራስ ሆቴል በሚቀርበው የግጥም ምሽት ላይ ያቀረበችው ግጥም የመንግስት ደጋፊና ተቃዋሚዎችን የጦፈ ውዝግብ…

Minilik Salsawi – ባሳለፍነው የትግል አመታት ውስጥ የተቃዋሚዎች እርስ በ እርስ መፈራረጅ መወነጃጀል መናናቅ ለስልጣን ጥመኝነት መሮጥ እንዲሁም ለስም እና ለዝና መትጋት ያለመደማመጥ እና ያለመከባበር ፖለቲካ ተቀራርቦ ያለመነጋገር እና ያለመመካከር ፖለቲካ ሃገራኢ ሆደሰፊነት እና መቻቻልን ያላዘለ ፖለቲካ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተረፈው ነገር ቢኖር ከጭቆን ወደ ጭቆና ማቅ ውስጥ ከመዘፈቅ ውጪ ምንም የናፈቀውን የነጻነት አየር እንዲተነፍስ አላደረግነውም። የተቃዋሚ ሃይሎች ጥንካሬ እንዲጎለብት በየድርጅቱ ውስጥ ያሉትን እንከኖች በማጥራት በጋራ እና በተመቻቸ የሃሳብ መግባባት ተቻችሉ እና ተግባብቶ የትግል ስትራቴጂን ግብ ለማድረስ ለአንድ ወጥ ህዝባዊ እና ሃገራዊ አጀንዳ ተግቶ መስራት ይጠበቅብናል።

ወያኔ የተቃዋሚዎችን እና የለውጥ ሃይሎችን እርስ በእርስ መፈነካከት በማየት አርጩሜውን ተስፋ በሚጣልባቸው ግለሰቦች እና ፓርቲዎች ላይ እያወናጨፈ ባለበት እንዲሁም የውስጥ አሰራራቸውን በመሰለል በትግሉ ውስጥ ያላቸውን ሚና እንዲኮላሽ በመስራት የውስጥ ድክመቶቻቸውን በመጠቀም እርስ በርስ እንዲፋጁ እና ተቃዋሚዎች እንዲከስሙ ጥንካሪያቸውን እንዳያገኙ ሲሰራ ይህንን እንዴት አድርገን በማሻሻል የወያኔን ሴራ ማክሸፍ አለብን የሚል አመኔታ የሚያስገኝ ሕዝባዊ ስራዎችን በመስራት ጥንካሬን ማግነት እንዲሁም ሕዝባዊ ድጋፎችን ማግኘት ግድ የሚልበት ጊዜ ላይ መሆናቸውን ተቃዋሚዎች ሊያውቁት ይገባል::ተቃዋሚዎች ካለፈው ድክመቶቻችን ተምረን ከዘለፋ እና ከስድብ እንዲሁም ከመፈራረጅ የሴራ ፖለቲካ በመውጣት ጥንካሬዎቻችንን የምናሳይበት ለውጥ የምናመጣበት አመት እንዲሆን በጋራ ጠንክረን መስራት አለብን።አንድነት ሃይል ነው የሚለው ብሂል ለሃገራዊ አጀንዳ መተግበር ትልቅ አስታውጾ አለው::ከኛ በላይ ላሳር ከኛ በላይ አዋቂ የለም የሚል አመለካከት ይዞ ከመክነፍ የህዝብን ጥያቄ መሰረት አድርጎ ተቀራርቦ በመነጋገር እና በመወያየት ሃገራጂ ማኒፌስቶ በማምጣት የጋራ ሃገራዊ አጀንዳ በመቅረጽ ለለውጥ መትጋት ግዴታ ነው::

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ይህ ሳይታለም የተፈታ እና የሁሉም የነጻነት ፈላጊ ሃይሎች ጥያቄ ነው። በሃገር ውስጥ ያሉትን ፓርቲዎች መዋቅሮቻቸውን በማጠናከር የውስጥ ድክመቶቻቸውን በመቅረፍ እንዲጠነክሩ የማድረግ ግዴታ ከለውጥ ፈላጊ ሃይሎች ይጠበቃል። መመካከር መተራረም ግድ ይላል። በውጪው አለም የሚገኙ የነጻነት እና የለውጥ ሃይሎች እንዲጠናከሩ እና ከጥልፍልፎሽ ፖለቲካ ወተው ጠንካራ ሃይል እንዲሆኑ የዲያስፖራው ሃይል ከበፊቱ በበለጠ መልኩ ሊሰራ ግድ ይለዋል። የወያኔ የጎን ውጋት እና የራስ ምታት የሆነው ዲያስፖራው የጀመረውን የትግል ስልት እና ትጋት በማስፋት ሚዲያዎችን በማጠናከር እና የነጻ አውጪ ፓርቲዎችን በመርዳት በማግባባት ጠንካራ ሰንሰለት ከሃገር ቤት ጋር በመፍጠር ሕዝብን ከጨቋኞች ነጻ ማውጣት አለበት።ዲያስፖራው በየቀኑ ወያኔ የሚፈጥረውን ተራ የቤት ስራ እና የማደናገሪያ ማዘናጊያ አሉባልታ ፊት ሳይሰጠው በለውጡ ጉዳይ ላይ በማተኮር በሃገር ቤት ያለው ሃይል እንዲስማማ የፖለቲካ ጡዘቶች ክፍተት እንዳይኖር ተቀራርቦ እንዲሰራ ትልቁን ሚና መጫወት አለበት::

የሚዲያ ተቋማት እና የድህረገጽ ውጤቶች ሕዝብን በማስተማር ሕዝብን መብቱን እና ነጻነቱን አውቆ ለሌላው እንዲያስተምር በማድረግ ረገድ አስፈላጊውን ወቅታዊ መረጃ እና መነሳሳትን በማስረጽ ግዴታቸውን ሊወጡ ይገባል። ያለፉ እና የከሰሙ ወሬዎችን እና አሉባልታዎችን ከመርጨት የወያኔ የፈጠራ አደናባሪ እና አዘናጊ አጀንዳዎችን እኝኝ በማለት ከማውራት ብሄር ተኮር ክፋፋይ ሃሳቦችን ከማርከፍከፍ አዛኝ መሳይ መርዝ ሃሳቦችን ከመናገር ተቆጥበን ሕዝቡን ስለመብቱ እና ነጻነቱን በማስተማር ረገድ መትጋት ከተያዘ ለውጥ የማይመጣበት ምንም ምክንያት የለም። ትችትን እና ሂስን ላለመዋጥ እውነትን ላለመቀበል የሚደረጉ ሩጫዎች ታጥቦ ጭቃ እንጂ የትም እንደማያደርሱ እንዲሁም ፓርቲዎችን እና ሰዎችን መፈረጅ እና መወንጀል ሃሳቦችን ማጣጣል ምንም ለውጥ እንደማያመጣ ካለፈው ተምረናል ። ያሳልፍነው የትግል ሂደት ከጭብጨባ እና ስብሰባ ያለፈ ፋይዳ እንዳሌለው ተገንዝበን የወሬ እና ሆይሆይ ትግል ስለማያዋጣ ጥንካሬን እና ለውጥን የምናመጣበትን የትግል ስልት በመመካከር እና በመወያየት ሃሳብን በማቻቻል መረጃ በመለዋወጥ ሃገራዊ የጋራ አጀንዳ ሊኖረን ይገባል እላለሁ።



ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ለአፍሪቃ አህጉር የመጀመሪያ የሆነውን መስጊድ ነው፡፡ ይህ መስጊድ የተሰራው በ641 ሲሆን የሚገኘውም በግብፅ መዲና ካይሮ ውስጥ ነው፡፡ መስጊዱ የሚጠራው በመስራቹ በ“አምር ኢብን ኣስ” ስም ነው፡፡ ይሁንና አምር እና ጓዶቹ መስጊዱን የሰሩት በአል-ፉስጣጥ እንጂ በካይሮ አልነበረም፡፡ ታዲያ መስጊዱን ወደ ካይሮ ማን ነው ያስገባው?… እስቲ የዛሬ ወጋችንን በአምር ታሪክ እንጀምርና ስለፉስጣጥም ትንሽ እናውራ፡፡
       *****
አምር ኢብን ኣስ የዐረቢያ ምድር ካበቀለቻቸው ታላላቅ ፖለቲከኞችና የጦር መሪዎች አንዱ ነው፡፡ የተወለደው በመካ ከተማ ሲሆን ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ያፈራው የቁረይሽ ጎሳ አባል ነው፡፡ አምር የጉርስምና ዘመኑን እንደ ሌሎቹ የዐረቢያ ወጣቶች በግመል ግልቢያና በፈረስ ጉግስ አላሳለፈም፡፡ የርሱ ቀልብ ወደ ንግዱ ነበር ያተኮረችው፡፡ በመሆኑም  በዘመኑ በገበያ ውስጥ ተፈላጊ የሆኑ ሸቀጦችን ለማምጣት ወደ የመንና ሻም (ሶሪያ) በብዛት ይመላለስ ነበር፡፡ ሀብቱ እየተስፋፋ ሲሄድ ደግሞ እስከ ፋርስ (ፐርሺያ)፣ መስር (ግብፅ)፣ አቢሲኒያ (ሐበሻ/ኢትዮጵያ) እና ኦማን ድረስ እየሄደ ሸቀጦችን ያመጣ ጀመር፡፡ በነዚህ ሀገራትም በርካታ የንግድ ሸሪኮችን ለመፍጠር ቻለ፡፡ በሸሪኮቹ በኩልም ከየሀገራቱ ገዥዎች ጋር በመተዋወቅ ልዩ ልዩ ገጸ-በረከቶችን ይወስድላቸው ነበር፡፡
Mosque of Amr in Old Cairo in 19th Century
ይህ በእንዲህ እንዳለ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በ610 ገደማ እስልምናን ማስተማር ጀመሩ፡፡ የዐረብ ጎሳዎች የድንቁርና ህይወታቸውን ትተው እንደ ጥንቱ ቅድመ-አያቶቻቸው እንደ ነቢዩ ኢብራሂምና እንደ ዒስማዒል ፈጣሪን ብቻ እንዲገዙ ሰበኩ፡፡ ጥቂት ሰዎች እምነቱን ተቀበሉ፡፡ አብዛኞቹ ግን “የአባቶቻችንን መንገድ ልታስተወን ነው እንዴ…?” በማለት በነቢዩ ላይ በጠላትነት ተነሱባቸው፡፡ በነቢዩ ያመኑትንም ያሰቃዩ ጀመር፡፡ ነቢዩ በተከታዮቻቸው ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሊከላከሉላቸው አልቻሉም፡፡ ስለዚህ ከተከታዮቻቸው መካከል የተወሰኑትን በሚስጢር ጠርተው ወደ ሐበሻ (ኢትዮጵያ) እንዲሰደዱ አዘዟቸው፡፡ በዚሁ መሰረት አንድ መቶ የሚሆኑ ሰዎች ወደ ሐበሻ ተሰደዱ፡፡
የቁረይሽ ባላባቶች የነብዩ ተከታዮች ወደ ሐበሻ መሰደዳቸውን ሲሰሙ “እዚያ ሄደው ሳይደራጁ በቶሎ ልናስመልሳቸው ይገባል” በማለት አንድ የልዑካን ቡድን ወደ አክሱም ሰደዱ፡፡ ቡድኑ ሁለት አባላት የነበሩት ሲሆን እነርሱም አምር ቢን ኣስ እና አብዱላህ ቢን ረቢዓ ናቸው፡፡ ያ ቡድን በሚችለው መንገድ ሁሉ ተደራድሮ የሐበሻውን ንጉሥ አርማህን (አስሓማ) በማሳመን የነቢዩን ተከታዮች ወደ መካ እንዲያስመልስ ታዟል፡፡ ነገር ግን ወደ ሐበሻው ንጉሥ ቀርቦ ድርድሩን እንዲፈጽም ስልጣን የተሰጠው ለአምር ቢን ኣስ ነው (አብዱላህ ቢን ረቢዓ “አምር” መልዕክቱን በትክክል ማድረሱን እንዲታዘብ ብቻ የተላከ ነው የሚመስለው)፡፡

አምር በንግድ ሰበብ ወደ ኢትዮጵያ በተመላለሰባቸው ዓመታት ከሐበሻው ንጉሥ ጋር ለመተዋወቅ ችሏል፡፡ ሆኖም አምር ለድርድሩ የተመረጠው በዚህ ብቻ ሳይሆን በዘመኑ ከነበሩት የመካ መኳንንት መካከል ተናግሮ በማሳመን ብቃቱ የተዋጣለት ሆኖ በመገኘቱም ጭምር ነው፡፡
       *****
አምር ከንጉሡ ዘንድ ቀርቦ ባደረገው ድርድር ያሰበው አልተሳካለትም፡፡ ንጉሡ ስደተኞቹን ለማንም አሳልፎ እንደማይሰጥ እቅጩን ነግሮታል፡፡ ይሁንና አምር በዚህ ተበሳጭቶ ወደ አክሱም መምጣቱን አላቆመም፡፡ ከድርድሩ በኋላም ቢሆን ለሁለት ጊዜያት ወደ ሐበሻ መጥቷል፡፡ ታዲያ ለመጨረሻ ጊዜ ከንጉሡ ጋር በተገናኘበት ጊዜ ንጉሡ እንዲህ ሲል መከረው፡፡
  “አምር ሆይ! አንተን የመሰለ ሰው የነቢዩ ሙሐመድን ትምህርት አልቀበልም ሲል ይገርመኛል፡፡ እናንተ ዐረቦች ከማንኛውም ህዝብ ወደ ኋላ ቀርታችኋል፤ ሙሐመድ ያመጣው ዐረቢያን ከጭለማ የሚያወጣውን አዲስ ብስራት ነው፡፡ በእርሱ ያመነ ሰው በፈጣሪ ዘንድ ከሚያገኘው ምንዳ በተጨማሪ ይህችን ዓለም ይገዛል፡፡”
ንጉሥ አርማህ አምርን እንዲህ ብሎ በሚመክርበት ጊዜ ለራሱም የነቢዩን እምነት ተቀብሏል፡፡ ይሁንና መላው የሐበሻ ህዝብ አዲሱን እምነት እንዲቀበል አዋጅ አልነገረም (አንዳንድ ጸሐፊያን “ንጉሥ አርማህ በነቢዩ ማመኑን በሚስጢር ይዞት ነበር” ይላሉ)፡፡
       *****
አምር ከሐበሻው ንጉሥ ከተለየ በኋላ በቀጥታ ወደ መካ ነው ያመራው፡፡ እዚያም ታዋቂው ጀግና ኻሊድ ቢን ወሊድ (ረ.ዐ) ወደ መዲና ለመሰደድ ሲዘጋጅ አገኘውና ከርሱ ጋር መሄድ እንደሚፈልግ ነገረው፡፡ ኻሊድም ሀሳቡን በደስታ ተቀበለው፡፡ ሁለቱ ሰዎች መዲና በደረሱ ጊዜ ነብዩ ሁለቱንም ሸሃዳ አስያዟቸው፡፡ ይሁንና ነቢዩ እነዚህን የዐረቢያ ጎምቱዎች አላሳረፏቸውም፡፡ ኻሊድን በሰሜን በኩል በነቢዩ መንግሥት ላይ አደጋ የጋረጡትን ሮማዊያንን ለመዋጋት በሚዘምተው የዘይድ ቢን ሓሪሳ ቡድን ውስጥ ቀላቀሉት፡፡ አምር ቢን ኣስ ደግሞ ወደ ኡማንና ባህሬን ሄዶ የዲፕሎማሲ ስራ እንዲሰራ አደረጉት፡፡ አምር ወደ ኡማን (ኦማን) የተጓዘው እነ አቡበከር፣ ዑመር እና አቡ ኡበይዳን (ረ.ዐ) የመሳሰሉ ታላላቅ ሰዎች የተካተቱበትን ቡድን በመምራት ነው፡፡ ነቢዩ አምር የቡድኑ መሪ እንዲሆን ያደረጉት የዲፕሎማሲ ችሎታውን በሚገባ ያውቁት ስለነበረ ነው፡፡ አምርም የዲፕሎማሲ ስራውን በደንብ ከመፈጸሙም በላይ የኦማን ሰዎች ወደ እስልምና እንዲገቡ ለማድረግ ችሏል፡፡
       *****
አምር ከነቢዩ ህልፈት በኋላም በአቡበከርና በዑመር ኺላፋዊ መንግሥት ውስጥም አገልግሏል፡፡ በጦር ግንባርም ሆነ በዲፕሎማሲ ስራ አንቱታን ያጎናጸፉትን ተግባራት ፈጽሟል፡፡ ከአምር ጋር የሁልጊዜ ተጠቃሽ ሆኖ የዘለቀው ግን ሮማዊያንን ከግብጽ በማባረር ወደ ኸሊፋዎቹ ግዛት የቀላቀለበት ዘመቻው ነው፡፡
አምር የግብጽን ዘመቻ (the conquest of Egypt) ያመነጨው በራሱ ነው ይባላል፡፡ በመሆኑም ኸሊፋ ዑመር ቢን ኸጣብ ሐሳቡን ተቃውመውት ነበር፡፡ የዑመር ተቃውሞ ዘመቻውን በመጥላት ሳይሆን “በተለያዩ ግንባሮች የተበተኑትን ወታደሮቻችንን በቶሎ አሰባስበን በዘመቻው እንዲሳተፉ ለማድረግ አንችልም” ከሚል የመነጨ ነው፡፡ ይሁንና አምር በወቅቱ በነበሩት ወታደሮች ብቻ ዘመቻውን በመጀመር ተጨማሪ ጦርን መጠባበቁን ነው የመረጠው፡፡
 
  አምር በ639 ዓ.ል በአራት ሺህ ወታደሮች የሲናይ በረሃን አቋረጠ፡፡ ሮማዊያንን በድንገተኛ ጥቃት በማራወጥ “ቢልቢስ” እና “ባቢሎን” በሚባሉት ስፍራዎች አሸነፋቸው (ይህቺ የግብጿ “ባቢሎን” የኢራቋ “ባቢሎን” አምሳያ እንድትሆን በሮማዊያን የተፈጠረች ናት)፡፡ ከጥቂት ወራት በኋላ ደግሞ በጥንቷ የኦኑ ከተማ (በፈረንጆች አጠራር Heliopolis) አጠገብ አሸነፋቸው፡፡ ከአንድ አመት በኋላ 12,000 ወታደሮች ከሶሪያ ሲመጡለትም አምር የዘመኑ የአፍሪቃ ታላቅ ከተማ የነበረችውን እስክንድርያን (አሌክሳንደሪያ) ለመያዝ ዘመተ፡፡ ሮማዊያን በከተማዋ ከሰማኒያ ሺህ የሚበልጥ ጦር የነበራቸው ቢሆንም ከነርሱ በአምስት እጥፍ በሚያንሰው የአምር ቢን ኣስ ጦር ድል ተመቱ፡፡ ግብጽም ሙሉ በሙሉ የሙስሊሞቹ ኺላፋ አካል ሆነች፡፡
ታዲያ አምር ግብፅን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመያዝ የበቃው በጦር ሃይሉ ጥንካሬ ብቻ አልነበረም፡፡ በወቅቱ የግብጽ ክርስቲያኖች ከፍተኛ እርዳታ ስላደረጉለት ጭምር ነው ታላቁን ድል ለማጣጣም የበቃው፡፡ ክርስትያኖቹ አምርን የደገፉበት ምክንያት አለ፡፡
  ግብጻዊያን ክርስቲያኖች የሚያምኑበት የ“ተዋሕዶ” እምነት “ክርስቶስ የሁለት ባህሪ ባለቤት ነው” ከሚለው የሮማዊያን ክርስትና ይለያል፡፡ በዚህም ምክንያት ሮማዊያኑ የግብጽ ክርስቲያኖችን እንደ “መናፍቃን” ያዩዋቸው ነበር፡፡ ከቁስጥንጥንያ (የአሁኗ ኢስታንቡል) ተሹመው ግብጽን የሚገዙት እንደራሴዎችም የግብጽ ክርስትያኖች እምነታቸውን እንዲለውጡ ለማድረግ በልዩ ልዩ መንገዶች ይጨቁኗቸው ነበር፡፡ አንዳንዴም ፓትሪያኮቻቸውን እያሰሩ “እምነትህን ተው” እስከማለት ይደርሳሉ፡፡ አምር ቢን ኣስ ግብጽን ለመያዝ በሚዘምትበት ዘመን እንኳ የግብጽ ፓትሪያርክ የነበሩት “አቡነ ብንያም” (ቤንጃሚን) ከሀገር ተባረው ነበር፡፡ በመሆኑም ግብጻዊያኑ ከጭቆናው ለመገላገል ሲሉ አምር ቢን ኣስን በዘመቻው በእጅጉ ረድተዋል፡፡ (በነገራችን ላይ ከ5ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ ግብጽን ይገዟት የነበሩት ሮማዊያን መቀመጫውን በሮም ከተማ ያደረገው የታላቁ ኢምፓየር አካል አልነበሩም፡፡ የሮም ኢምፓየር በ395 “ምስራቅ” እና “ምዕራብ” ተብሎ ለሁለት ተከፍሏል፡፡ የሮማ ከተማ በ476 በጀርመን ጎሳዎች ስትወረር የምዕራቡ ኢምፓየር ህልውና አክትሟል፡፡ የምስራቁ ኢምፓየር ግን እስከ 1431 ድረስ ቆይቷል፡፡ ብዙዎች የምስራቁን ኢምፓየር የሚጠሩት “ቤዛንታይን” በሚል ስም ነው፡፡ ሆኖም ዐረቦችም ሆኑ የኢምፓየሩ ነዋሪዎች ግዛቱን “ሮም” እያሉ ስለሚጠሩት እኔም ይህንን ልማድ ተከትያለሁ)፡፡  

  አምር ግብጽን በሚያስተዳድርበት ጊዜ በክርስትያኖቹ ላይ ይደርስ የነበረውን ጭቆና ሙሉ በሙሉ አስወግዷል፡፡ በህዝቡ ላይ በየምክንያቱ ይጣሉ የነበሩትን ልዩ ልዩ የታክስ ዓይነቶች በማስቀረት ሁሉም ዜጎች ዓመታዊውን “ዑሽር” (አስራት) እና “ዘካት” ብቻ እንዲከፍሉ አድርጓል፡፡ በመንግሥቱ ቢሮክራሲ ውስጥም ክርስትያኖቹን አሳትፏል፡፡ የቤተ-ክርስቲያኖች ይዞታ የሆኑ መሬቶችና ንብረቶች እንዲከበሩም አድርጓል፡፡
       *****
 አምር ቢን ኣስ ግብጽን ማስተዳደር በጀመረ በዓመቱ ነው “አል-ፉስጣጥ” የተባለችውን ከተማ የቆረቆረው፡፡ ስለ“አል-ፉስጣጥ” ምስረታና ስለሌሎች ጉዳዮች በሚቀጥለው ክፍል እናወጋለን፡፡
አፈንዲ ሙተቂ
ህዳር 3/2007
ገለምሶ-ሀረርጌ

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ፣ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በስንት ውጣ ውረድ ያገኙትን ሥልጣን ጥርሳቸውን ነክሰው ከያዙ ሁለት ዓመት ከሁለት ወርና 26 ቀን አስቆጥረዋል። በእነዚህ ወራት ውስጥም፡ ኃይለማርያም ሥልጣን የረገጡ ቀን ስለራሳቸው ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሰጡት ምስክርነትና ግምት ከዛሬው ኃይለማርያም በአያሌው የተለያዩ ናቸው። ገና መጀመሪያ ላይ ከመለስ ጀርባ ከጦር አዝማችነታቸው ወጥተው (በካድሬነታቸው) በሙቱ ማግሥት የሥልጣንን በር ሲይንኳኩ፣ […]

ከ250 አመታት በፊት ፣ 13 ኮሎኒዎች፣ ተብለው የሚታወቁት የአሜሪካ ግዛቶች በእንግሊዝ ሥር ነበሩ። አሜሪካኖቹ የግብር ጫና ስለበዛባቸው ለነጻነት መታገል ጀመሩ። በአሜሪካኖች እና በእንግሊዞች መካከል ጦርነት ተጀመረ። የአሜሪካኖች መሪ ጀነራል ጆርጅ ዋሺንግተን ነበሩ። እንግሊዞች ብዙ ጦር አሰልፈው ያመጹ አሜሪካዉያንን ለማስገበር ተንቀሳቀሱ። በኑዮርክ አሜሪካኖች ትልቅ ሽንፈት ደረሰባቸው። የእንግሊዝን ጦር መቋቋም አልቻሉም። ጆርጅ ዋሽንግተን፣ በሌሊትና በጉም ወደ 9 […]