አፈንዲ ሙተቂ
      —–
      የህንድ ፊልም ማየት የጀመርኩት በ1978 ይመስለኛል፡፡ በዘመኑ ቶማስ የሚባል የህንድ ክልስ ነበር፡፡ ይህ ሰው ፊልሞቹን ከድሬ ዳዋ ያስመጣና በሌሎች የሀረርጌ ከተሞች እያዞረ በፕሮጀክተር ያሳያል፡፡ በዘመኑ “የአሜሪካ ፊልም ውሸት ነው፤ የህንድ ፊልም እውነት ነው” የሚል አስተሳሰብ ስለነበረ የሰዎች ምርጫ በአብዛኛው የህንድ ፊልም ነበር፡፡ በመሆኑም ቶማስ ከሚያሳያቸው ፈልሞች መካከል ከመቶ ዘጠና የሚሆኑት የህንድ ፊልሞች ነበሩ፡፡ 
   በዚህም መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ ያየሁት የህንድ ፊልም “T.D” የሚል ርዕስ የነበረው ሲሆን አክተሩም “ጄተንድራ” ነው (በኋላ ላይ እንደተረዳሁት ያ ፊልም First Blood  ከሚባለው የራምቦ ፊልም የተቀዳ ነው)፡፡ ቶማስ ፊልሙን የሚያሳየው በሁለት ብርና በሶስት ብር ነው፡፡ በቶማስ ሲኒማ ስር ካየኋቸው ሌሎች የህንድ ፊልሞች መካከል Disco Dancer, Jimmy and His Elephant, Mard የተሰኙት ይታወሱኛል፡፡  
        በ1981 የአውራጃችን አኢወማ ቪዲዮ ሲያስመጣ ግን የቶማስ ሲኒማ “በጣም ውድ ነው” በሚል ተረሳ፡፡ ቶማስም ወደኛ መምጣቱን ተወ፡፡ በዚህም መሰረት Mister India, Ashanti, Kassam Paeda, Love Story, የመሳሰሉ ፊልሞችን በአኢወማ አየን፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ “ፎቶ ማወርዲ” የሚባለው ፎቶ ቤት ሌላ ቪዲዮ ማሳያ ከፈተና ከአኢወማ ጋር ፉክክር ውስጥ ገቡ፡፡ ሁለቱም በርካታ ፊልሞችን አስኮመኮሙን፡፡ በፎቶ ማወርዲ ካየኋቸው ፊልሞች መካከል “Ter Kassam”, “Maa Kassam”, “Numberi Admi”, “Khoj”, “Marry Kassam”, “My Name is Lakan”, “Tarzan”, “Coolie”, የሚባሉትን ከነ ስሞቻቸው አስታውሳቸዋለሁ፡፡ የብዙዎቹን ስም ግን አላስታውስም፡፡
*****  *****  *****
        በህንድ ፊልሞች የምናውቃቸው አክተሮች በከተማችን በትክክለኛ ስማቸው አልነበረም የሚጠሩት፡፡ አንዳንዶቹ እኛ ባወጣንላቸው ስሞች ነው ይበልጥ የሚታወቁት፡፡ ለምሳሌ “ሚቱን ቻካርቦርቲ” የሚባለው አክተር “ጂሚ” በሚለው ስም ነው የሚታወቀው፡፡ “ዳርሜንድራም” በኛ አጠራር “ሻንካር” ነው የሚባለው፡፡ “ሪሽ ካፑር” ደግሞ “ኮጅ” እየተባለ ነው የሚጠራው፡፡ እውነተኛ ስሙ “ሰኒ” የሆነው አክተር ደግሞ በኛ አጠራር “ገባር” ነው የሚባለው፡፡ “አጄይ ኩማር”ም “ላቭ ስቶሪ” ተብሎ ነበር የሚጠራው፡፡ ከነዚህ ስሞች መካከል አንዳንዶቹ (እንደ “ጂሚ” እና “ሻንካር” ያሉት) አክተሩ ታዋቂ በሆነበት ፊልም ውስጥ ከሚጠራበት ስም ነው የተወሰዱት፡፡ እንደ “ኮጅ” እና “ላቭ ስቶሪ” የመሳሰሉት ደግሞ አክተሮቹ የተወኑባቸው ፊልሞች አርዕስት ናቸው፡፡    
        ከዚህ ሌላ አክተሩ በፊልሙ ውስጥ ሲያንጸባርቀው የነበረውን ድርጊት በመመልከት የተሰጡ ስሞችም አሉ፡፡ ለምሳሌ “አኒል ካፑር” የሚባለው አክተር በአንድ ፊልም ውስጥ ያለ ማቋረጥ “ማስቲካ” ያኝክ ስለነበረ “ማስቲካ” ተብሎ ተሰይሟል፡፡ “ቆሮንዴ” ደግሞ “Sholay” በተሰኘው የአሚታብ ባችቻን ፊልም ውስጥ በአፍ የሚታኘክ ትምባሆ ስለሚጠቀም ነው እንዲህ ተብሎ የተጠራው (“ቆሮንዴ” በአፍ የሚታኘክ የትምባሆ ዐይነት ነው)፡፡ እንደ ከማል ሐሰን፣ ነስሩዲን፣ አሚታብ ባችቻን፣ ሻሽ ካፑር፣ ጄክ ሸሪፍ፣ ጎቪንዳ፣ ሳንጃይ የመሳሰሉትን ግን በትክክለኛ ስማቸው ነው የምንጠራቸው፡፡
     ታዲያ በጣም ያስገረመኝ ይህ በኛ ከተማ የምንጠቀምበት የስም አጠራር ዘይቤ ድሬ ዳዋና ሀረርን ጨምሮ በሌሎች ከተሞችም በስፋት የሚታወቅ መሆኑ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ያደረግኩት ጥናት እንደሚያመለክተው ከስሞቹ መካከል አንዳንዶቹን እኛ መፍጠራችን ትክክል ቢሆንም ሌሎቹ ስሞች ከድሬ ዳዋ ልጆች የተኮረጁ ናቸው፡፡
      በድሮው ዘመን “አክተር” የምንለው በፊልሙ ውስጥ መልካም ስብዕና የሚያሳየውን ብቻ ነው፡፡ እኩይ ባህሪ ተላብሶ የሚተውነው በኛ ቋንቋ “ሙጅሪም” ነው የሚባለው፡፡ በአንደኛ ደረጃ ከሚነሱ ሙጅሪሞች መካከል “አሻንቲ”፣ “ሻክቲ”፣ “ጃሉ”፣ “ሼራ”፣ “ቆሮንዴ”፣ “ፋሩቅ” የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ (ፋሩቅ Disco Dancer በተሰኘው ዝነኛ የጂሚ ፊልም ውስጥ የተወነው ወፍራም ሙጅሪም ነው፤ አስታወሳችሁት አይደል?)፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ከሚመደቡ ሙጅሪሞች መካከል ደግሞ “ሳምሶን መላጣ” እና “መለኪያ” የተባሉት ይጠቀሳሉ:: እነዚህኛዎቹ ሙጅሪሞች በአብዛኛው በታላላቆቹ ሙጅሪሞች እየታዘዙ ጥፋት የሚፈጽሙ ናቸው፡፡ ከማል ሐሰንም ሲያሻው ከነዚህ ጋር ይደመርና ሙጅሪም ይሆናል፡፡
      በህንድ ፊልም ውስጥ ዘወትር የሚታይ ሶስተኛ አክተር አለ፡፡ ይህ ሰው በፊልሙ ውስጥ የሚሰጠው ሚና እንደ ቤተሰብ አጫዋች ሆኖ ሰዎችን ማሳቅ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ አስቂኝ ገጸ-ባህሪ በያኔው አጠራር “ማህሙዴ” ይባላል፡፡ እጅግ ዝነኛ ከሆኑ ማህሙዴዎች መካከል “ሻክቲ” ተጠቃሽ ነው (“ሻክቲ” ሲፈልግ “ሙጅሪም”፤ ሲያሻው ደግሞ ማሕሙዴ ይሆናል)፡፡
*****  *****  *****
        የህንድ ፊልም ልዩ ገጽታው በርካታ ዘውጎችን አንድ ላይ የሚደበላልቅ መሆኑ ነው፡፡ የአክሽን ፊልም ውስጥ ኮሜዲ አለ፣ አስማት አለ፣ ሮማንስ አለ፤ ዳንስ አለ፤ በአንዱ ፊልም ውስጥ ሁሉም ነገር ይገኛል፡፡ ደግሞም አክተሮቹ ሲደንሱ ድምጻቸው አንድ ዓይነት መሆኑ በጣም ያደናግራል፡፡ የሴትም ሆነ የወንድ ድምጽ ለመለየት ያስቸግራል፡፡
      ከዚህ በተጨማሪ የህንድ ፊልም ውስጥ የሚታየው ግነት ከፍተኛ ነው፡፡ ለምሳሌ Mard በተሰኘው ፊልም ውስጥ አሚታብ ለመብረር የሚያኮበኩበውን ሂሊኮፕተር በገመድ ጠልፎ እንዳይበር ያደረገበት ትዕይንት ዘወትር አይረሳኝም፡፡ በልጅነታችን ያንን ትዕይንት እንደ ጉድ ነበር ያጨበጨብንለት፤ አሁን ቢሆን ግን “አንተ ውሸታም! ሞኝህን ፈልግ ” ብዬ ቪዲዮውን የምዘጋው ይመስለኛል፡፡
      የህንድ ፊልም ሲነሳ ዘወትር የሚታወሱኝ ሁለት ልጆች አሉ፡፡ አንደኛው ታገል ዲሪብሳ ይባላል፡፡ ሌላኛውን ልጅ ግን ስላላስፈቀድኩት ስሙን አልነግራችሁም፡፡ ታገል ምን አደረገ መሰላችሁ?.
     የጄተንድራን ፊልም እያየን ነበር፡፡ በፊልሙ መሀል ላይ ሻክቲ የተባለው ሙጅሪም የጄተንድራን እህት በመኪና ካሯሯጣት በኋላ ይገድላታል፡፡ ትዕይንቱ በጣም ያሳዝናል፡፡ በተለይ ልጅቷ በደም አበላ ተነክራ ላያት ሰው ልብ ትሰብራለች፡፡ ይሁን እንጂ ብዙዎቻችን ፊልም መሆኑን አልሳትንም፡፡ ታገል ግን ከመመሰጡ ብዛት የእውነት ትዕይንት መሰለው፡፡ እናም ጮክ ብሎ “ህግ የለም እንዴ?” አለ፡፡ በቪዲዮ ቤቱ የነበረው ሰው ሁሉ በሳቅ ፍርስ አለ፡፡
      የሁለተኛው ሰው ማስታወሻዬ ግን ከዚህ ይብሳል፡፡ በጊዜው ከነበሩት የሀብታም ልጆች ነን ባዮች መካከል አንዳንዶቹ የለየላቸው ጅላጅሎች ነበሩ፡፡ አሪፍ መኪና ሲያዩ “የዘመዳችን ናት” ማለት ይቀናቸዋል፡፡ “ነዋይ ደበበ ቤታችን ሊመጣ ነው” የሚሉም ነበሩ፡፡ እኛም ለነዚህ ጅሎች ነገር እያሟሟቅን ብራቸውን እናጫርሳቸው ነበር፡፡ ከነዚያ ልጆች አንዱ “አሚታብ ዘመዳችን ነው” እያለ ያወራልን ነበር፡፡ እኛም እያወቅን እንሞኝለታን:: አብዛኛውን ጊዜ የፊልም መግቢያ ዋጋውን የሚከፍልልን እርሱ ስለሆነ ለርሱ መሞኘታችን የግድ ነበር፡፡
      ታዲያ በብዙ ፊልሞች ውስጥ ሲሞት የማይታየው “ጀግናው” አሚታብ ባችቻን ሲያቀብጠው Sholay በተሰኘው ፊልም መጨረሻ ላይ ሞተ፡፡ ነገሩ በጭራሽ ያልተገመተ በመሆኑ ብዙዎች ተገረሙ፡፡ “ጉድ ነው! አሚታብም ይሞታል እንዴ?”… ተባባልን፡፡ እኛ እንዲህ ያልነው “አሚታብ ወክሎት የሚጫወተው ገጸ-ባህሪ ዘወትር አይሞትም” ከሚል መነሻ ነበር፡፡ ያ የኛ ስፖንሰር የሆነው ልጅ ግን እየየውን አቀለጠው፡፡ “ዘመዴ ሞቶ የት አባቴ ነው የምገባው?” እያለ አነባ፡፡ ፊልም ለመመልከት የሄደው ሰው ግራ ተጋባ፡፡ ለምን እንደሚያለቅስ ብንነግራቸው ሁላችንንም እንደ ጅል ይቆጥሩናል ብለን ፈራን፡፡ ስለዚህ ቶሎ ብለን ልጁን ደጋግፈን ወደ ውጪ ካወጣነው በኋላ እያባበልነው ከቤታቸው ወሰድነው፡፡
   ይህ ትዕይንት በአሁኑ ዘመን ይከሰታል ተብሎ የማይታሰብ ነው መቼስ! ከዛሬ ሀያ አመት በፊት ግን ተመሳሳይ ድርጊቶችን ማየት የተለመደ ነው፡፡
—–
      የህንድ ፊልም ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት በ1995 ይመስለኛል፡፡ በወቅቱ ያየሁት Kabi Ghushi Kabi Gham የሚል የሻህሩኽ ኻን እና አሚታብ ፊልምን ነው፡፡ ያየሁበት ስፍራ አዲስ አበባ በመሆኑ ግን እኛ ስናደርግ እንደነበረው “ማህሙዴ፣ ሙጅሪም፣ ወዘተ…” እያለ ስለ ፊልሙ የሚተርክ ሰው አላጋጠመኝም፡፡ ከዚያ ወዲህ እኔና የህንድ ፊልም አንተዋወቅም፡፡ ለመሆኑ አሁን ምን ደረጃ ላይ ደርሷል?… እስቲ ስለ ህንድ ፊልም ያላችሁን ትዝታችሁ አካፍሉን፡፡
ሰላም!
የካቲት 17/2006
ሸገር

IOM በሚል አህጽሮት የሚታወቀው አለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት በያዝነው ወር የሚያበቃው 2014 አም ግጭትን፣ የፖለቶካ ወከባንና የኢኮኖሚ ችግርን በመሸሽ ለሚሰደዱት ሰዎች አደገኛ አመት ሆኖ እንደቆየ አስታውቋል።

ታኀሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የውሃ፣ የመስኖና የኢነርጂ ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ ህዳር 26 ቀን 2007፣ በቁጥር ውመአሚ 1/01/67 በጻፉት ደብዳቤ ” በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች በከፍተኛ ወጪ ተገንብተው ለበርካታ ኢንተርፕራይዞች የመስሪያና መሸጫ አገልግሎት የሚውሉ ህንጻዎችና ሼዶች በኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት ችግር ምክንያት ለታለመላቸው አላማ ለማዋል ” አልተቻለም ብለዋል። “በእነዚህ ማእከላት ውስጥም በከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ የገቡና …

ታኀሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው  የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት  ቤት ቢቀርቡም ሌላ ቀጠሮ እንደተሰጣቸው ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ …

ታኀሳስ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባንኩ እንደሚለው በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባቸው አገሮች ቅርንጫፎችን በመክፈት በአመት እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚሆነውን፣ ከባንክ ውጭ የሚደረገውን ገንዘብ የማስተላለፍ ዘዴ ለመቆጣጠር አስቧል። አሜሪካ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስና ሳውድ አረቢያ በመጀመሪያው ዙር የንግድ ባንኮች ቅርንጫፎች ከሚከፈትባቸው አገራት ተርታ ተመድበዋል። ባንኮቹ መከፈታቸው ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የሚልኩትን ገንዘብ ለመጨመር እንደሚረዳም …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የፖለቲካ እንቅስቃሴ፣ ሰላማዊም የትጥቅም፣ በባህሪው ትብብርን ይጠይቃል። ሕብረተሰብ በማሳትፍ የሚደረግ የትብብር ሥራ ነውና። የኢትዮጵያ ገዥ ጥምር ድርጅት አንድ አካል የኾነው ህወሓት የፈር ቀዳጅነት ሚናውን ወስዶ የዛሬ አርባ ዓመት በትግራይ በረኻዎች የትጥቅ ትግል ጀምሮ በሚያካሂድበት ጊዜ፣ “ተወዲቡ ብጽንዓት ዝተቓለሰ ይዕወት” (ሲተረጎም፣ ተደራጅቶ በጽናት የታገለ ለድል ይበቃል) የሚል መፎክር ከአነገባቸው መፎክሮች አንዱ ነበር። በነገራችን ላይ የህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥም ኢህአዴግ እንደ መንግስት ሀገር ሲመራ የተከተለው ህዝብን አደራጅቶ እና አስትፎ የመስራት ባህልም ከዚኽ መፎክር የተወረሰ ሳይኾን አይቀርም። ለዚህም ነው ኢህአዴግ ነጥሮ በመውጣት በትጥቅ ትግሉም ሀገር በመምራቱም ወቅት ውጤታማ ሊኾን የበቃው። አሁን በፖለቲካው ተደራጅተው ሳይደራጁም እየተንቀሳቀሱ ያሉ የተቃውሞ፣ ሕጋዊ የኾኑትም ያልኾኑትም በዋናነት የዚኽ የተባብሮ መስራት ድክመት ስላለባቸው ነው ለውጤት ያልበቁት። ሲጣመሩ፣ ሲቀናጁም ኾነ ሲያብሩ፣ የአብሮ መስራት ምክንያታቸው የመላው ህዝብ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ በፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና ፖለቲካዊ ፕሮግራም ነጥሮ የወጣ ፖለቲካዊ አቋም ይዘው መስዋእት ለመክፈል ተዘጋጅተው ሳይኾን በጥላቻ እና የስልጣን ጥም ብቻ መሰረት አድርገው ነው ወደ አንድ የሚሰባሰቡት። በዚኽ አካሔድ ደግሞ ጠብ የሚለ ውጤት አላገኙም። በተለይ ለመስዋዕትነቱ የሚመርጡት ሌላ አካል እንዲኾንላቸው ይፈልጋሉ። እነሱ በአቋራጭ ስልጣን ላይ ለመፈናጠጥ እንዲያስችላቸው። ከዚኽ አንጻር የሀገራችን ተቃዋሚዎች ትጥቅ ትግል አውጀው በሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩት እና በስመ አክቲቪዝም የሚከትሏቸው (ሁለቱንም መንገድ የሚያጣቅሱ ቡድኖች) እንዲኹም በሰላማዊ ሕጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱት በተደጋጋሚ የመተባበር እና ለህዝብ መስዋዕት የመኾን መሰረታዊ ባህሪ ስለሚጎድላቸው እና የስልጣን […]

ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የአምደ መረብ ጸሓፍት ቁጥር ከአምናው በእጥፍ ማደጉን CPJ በሚል ምኅፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጠ። የCPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ተወካይ ቶም ሮድስ ኢትዮጵያ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ምርጫው ከመድረሱ አስቀድሞ ተቺዎች ድምፃቸው እንዳይሰማ እያፈናቸው መሆኑን ተናግረዋል።

«አርሶ አደሩ እያጉረመረመ ሲለዉ ከረመ፤ አርሶ በሌዉ መጣ ጠላ ሊጠጣ፤ አርሶ በሌዉ ካለ ምን ችግር አለ፤ አርሶ በሌዉ ጎፈር ማረስ መቆፈር፤ ላለዉ መንገዱን አለስልሶ ከርሞ ይመጣል ያልሞተ ሰዉ፤ እመቤቴ ያደረችበቱ እጣን ይሸታል መሬቱ» እያለ ሆ ይላል ያዜማል ፤ የኢትዮጵያ ገበሬ የዘራዉን ሰብል በታህሳስ ሲሰበስብ።

የሩስያ ማዕከላይ ባንክ የሀገሩ ገንዘብ «ሩብል» ዋጋ እያሽቆለቆለ የተገኘበትን ሁኔታ ለማከላከል በአሁኑ ጊዜ የሚቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ይገኛል፣ ይሁንና፣ የእስካሁኑ ጥረቱ አንድም የረባ ውጤት አላስገኘለትም። የሩብል መውደቅ ሩስያን ወደ ከፋው የኤኮኖሚ ቀውስ ወስጥ ይጥላት ይሆን?

የኤቦላ ተኀዋሲ በምዕራብ አፍሪቃ ፣ በተለይ በሶስቱ በበሽታው በጣም በተጠቁት ሀገራት፣ ላይቤርያ፣ ጊኒ እና ሲየራ ልዮን ላይ እያደረሰ ስላለው ማህበራዊ እና ኤኮኖሚያዊ ተፅዕኖ የተመድ በአፍሪቃ አዳራሽ ባካሄደው ጉባዔ ላይ ዝርዝር መግለጫ ሰጠ።

ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የአምደ መረብ ጸሓፍት ቁጥር ከአምናው በእጥፍ ማደጉን CPJ በሚል ምኅፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጠ። የCPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ተወካይ ቶም ሮድስ ኢትዮጵያ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ምርጫው ከመድረሱ አስቀድሞ ተቺዎች ድምፃቸው እንዳይሰማ እያፈናቸው መሆኑን ተናግረዋል።

Image

በአዳር ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት (መአሕድ) ምክትል ፀኃፊ መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ ራሳቸውን ስተው ሆስፒታል እንደገቡና ሕይወታቸው አደጋ ውስጥ እንደሆነ የፓርቲው ፕሬዝደንት አቶ ሽዋንግዛው ገ/ስላሴ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በአዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ የደረሰባቸው ሲሆን ለአምስት ቀናት ቀዝቃዛና ጨለማ ቤት ውስጥ ታስረው ቆይተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ከታሰሩበት ጊዜ ጀምሮ የስኳር በሽታ መድሃኒታቸውን በመቀማታቸውና ህክምናም ባለማግኘታቸው ታመው እንደነበር ለማወቅ መገለጹ ይታወሳል፡፡

መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በድብደባውና በስኳር በሽታ ምክንያት በአሁኑ ወቅት ዘውዲቱ ሆስፒታል የሚገኙ ሲሆን ሆስፒታል ከገቡበት ቅዳሜ ታህሳስ 4/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሰው ማናገር አለመቻላቸውን የፓርቲው ፕሬዝዳንት አክለው ገልጸዋል፡፡

Image
የሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ እያስፔድ ተስፋዬ ከሚሰራበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአዳር ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ በደረሰበት እስር ምክንያት ከስራው ታገደ፡፡ እያስፔድ ተስፋዬ በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ጨለማና ቀዝቃዛ ክፍል ታስረው ከነበሩት አመራሮች መካከል አንዱ ሲሆን ከእስር ከተፈታ በኋላ ታስሮ ስለመቆየቱ ማስረጃ ቢወስድም ለ15 ቀን ከስራ ታግዶ እንዲቆይ ተደርጓል፡፡

‹‹ታስሬ መቆየቴን የሚያሳይ ማስረጃ ወደምሰራበት ቅርንጫፍ ስወስድ ከእኛ አቅም በላይ ስለሆነ ወደ ዲስትሪክት ውሰድ ተባልኩ፡፡ ዲስትሪክት ስወስድ የንግድ ባንክ ዳይሬክተር የሰው ኃይል አስተዳደር ማመልከቻና ታስረህ የቆየህበትን ማስረጃ አስገባና እነሱ ወደ ስራ ገበታህ ተመለስ ካሉህ ነው የምትመለስ፤ እነሱ ተመለስ እስኪሉህ ድረስ ግን ወደ ስራ ገበታ መመለስ አትችልም አሉኝ፡፡ ባሉኝ መሰረትም ለሰው ኃይል አስተዳደር ደብዳቤና ከፖሊስ ጣቢያ የተሰጠህን ማስረጃ ወሰድኩ፡፡ እሱ እስኪያየው ድረስ ተብሎ አንድ ቀን ቀጠሮ ተሰጠኝ›› የሚለው እያስፔድ በቀጠሮው መሰረት ሲሄድ ጉዳዩ ለቅሬታ ሰሚ ኮሜቴ እንደተላከ፣ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አባሎች ስልጣና ላይ በመሆናቸው ለ15 ቀን ስራ መግባት እንደማይችልና ለታገደበት ቀናትም ደመወዝም እንደማይከፈል እንደተገለጸለት ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድቷል፡፡

ቀደም ሲል የሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ አቶ ወሮታው ዋሴ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የተባረሩ መሆናቸው ይታወሳል፡፡

Image

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች ለታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ተከሳሾቹ የክስ መቃወሚያ አቅርበዋል

ዛሬ ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በጠበቆቻቸው አማካኝነት የክስ መቃወሚያቸውን ይዘው ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

ሆኖም ግን 7ተኛ ተከሳሽ አቶ አብርሃም ሰለሞን የሰጠው የተከሳሽነት ቃል ከክሱ ጋር ተያይዞ ለጠበቃው አለመቅረቡን ተከትሎ ጠበቃው የክስ መቃወሚያ ለማዘጋጀት ባለመቻላቸው የተከሳሽ ቃልን የያዘውን ዶክሜንት ከጽ/ቤት ወስደው መቃወሚያቸውን እንዲያስገቡ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን ለመስጠት ለታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው በተለየ መዝገብ በመመዝገባቸው ከሌላው በተለየ ማሸማቀቅ እየተፈጸመባቸው ነው፡፡

ይህን በተመለከተ ለማረሚያ ቤቱ አቤት ቢሉም ሊሻሻል አለመቻሉን ተከሳሾቹ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ለማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታቸውን ተቀብሎ በቀጣይ ቀጠሮ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር ስለጉዳዩ ቀርቦ እንዲያስረዳ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

ሃገሪቱን የሚያሰጋት የሃይማኖት አክራሪነት/አሸባሪነት ሳይሆን የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አሸባሪነት ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ነው:: ጥላችሁን እንዳታምኑ እየተባለ ሃይማኖት መንግሥታዊ ቅርጽ ይዞ እንዲወጣ ለማድረግ መሞከር አክራሪነት ነው፡፡

«መጾም፣ መጸለይ፣ ሥርዓተ-አምልኮን መፈጸም ሃይማኖታዊ አልባሳትን መልበስ ለሃይማኖቱ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንጂ አክራሪነት ሊባል አይችልም፤»…የአክራሪ ክርስትና ወይንም እስልምና ቡድን መኖር የክርስትና እና እስልምና ተከታዮችን በሙሉ «አክራሪ» አስብሎ ሊያስፈርጃቸው አይችልም::አክራሪ ተብሎ የሚፈረጀው የሚራመዱ የፖለቲካ ጡዘቶች በሰዎች ላይ ሌላ እምነትን በመጫን በግዳጅ እና በሃይል ሊያስገድዱ ሲሞክሩ ይህ ማለት አህበሽን እና ተሃድሶን በጥንታውያኑ እስልምና እና ተዋህዶ ላይ በኢትዮጵያ እንደተሞከረው ማለት ነው::

አክራሪነት አሉታዊ ትርጉም ሲኖረው የራስን እምነትና አመለካከት በሌሎች ላይለመጫን መሞከር ነው፡፡ ሃይማኖት መንግሥታዊ ቅርጽ ይዞ እንዲወጣ ለማድረግ መሞከር ራሱ አክራሪነት ነው፡፡ አክራሪነት የፖሊቲካ ገጽታ ያለው ነው፡፡ ኾኖም ግን ሃይማኖትን ማጥበቅ አክራሪነት አይደለም፡፡ሃይማኖት ፍጹም እውነታን በፍጹም እምነት ስለሚቀበል ከሌሎች ግላዊ አስተሳሰቦች የተለየ ነው፡፡ የሃይማኖት መገለጫዎችን መጠቀም የዚያን ሃይማኖት ጥልቀት የሚያሳይ እንጂ እንደ ችግርም የሚወሰድ ወይም አክራሪነት ሊኾን አይችልም፡፡ «መጾም፣ መጸለይ፣ ሥርዓተአምልኮን መፈጸም ሃይማኖታዊ አልባሳትን መልበስ ለሃይማኖቱ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንጂ አክራሪነት ሊባልአይችልም፤» ይላሉ የዘርፉ ምሁራን፡፡

የአክራሪነትና የአጥባቂነት ፅንሰ ሐሶቦች በጥሩ ኹኔታ ተለይተው ተገልጸዋል፡፡ አንዳንድ ሰነዶች ወያኔም ለይስሙላ የገለበጣቸው ሰነዶቹ አክራሪነትንና አጥባቂነትን በአግባቡ ለይተውና ተንትነው ያስቀምጣሉ፡፡ በዚሁ መሠረት አጥባቂነትን፣ ‹‹የግል ሃይማኖትን ሃይማኖቱ በሚያዘው መሠረት ሳይንጠባጠብ ሁሉንም ትእዛዛት መፈጸም ነው፤» በማለት ሲፈታው አክራሪነትን ደግሞ፣ «ከራስ እምነት ወጥቶ ሌላውን መተንኮስና የሌሎችን ሃይማኖት መኖር አለማመንና አለመፍቀድወይም ሌሎቹን አስገድዶ የራስ እምነት ተከታዮች ለማድረግ መጣር ነው፤» ይላል፡፡ በተግባር ላይ አለመዋሉ እና በጣልቃ ገብነት መተርጎሙ ጉዳት አመጣ እንጂ::

ከዚህ ብያኔ ስንነሣ ክርስቲያንም ሆነ ሙስሊም ከርሱ ውጭ የኾኑትን የሌሎቹን መኖር የማይቀበልና ከግለሰቦቹ ፈቃድ ውጭ አስገዳጅ እስከኾነ ድረስ እርሱን አክራሪ ማለት ይቻላል፡፡መብትን መጠየቅ ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት መሸሽ አክራሪነት አይደለም:: በዚህ መልኩ አክራሪው ይህንኑ ድርጊት ሊፈጽም የተነሣውን ቡድን ብቻ እንጂ «አክራሪው ቡድን» የወጣበትን/የተገኘበትን ቤተ እምነት ሊወክል አይችልም፡፡ ስለዚህ በአለማቀፍ ደረጃ የአክራሪ ክርስትና እና እስልምና ቡድን መኖር የክርስትና እና እስልምና ተከታዮችን በሙሉ «አክራሪ» አስብሎ ሊያስፈርጃቸው አይችልም፤ ለሌላው ቤተ እምነትም እንዲሁ፡፡ ሃገሪቱን የሚያሰጋት የሃይማኖት አክራሪነት ሳይሆን የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አሸባሪነት ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ነው:: #ምንሊክሳልሳዊ

(ይህ የግሌ አስተያየት ነው!)

ምርጫ ካልተገባ ሌላኛው አማራጭ ትጥቅ ትግል ብቻ ነው ያለው ማነው? ሲጀመርስ ምርጫ የዲሞክራሲ መገለጫ ነው እንጂ ከመቼ ወዲህ ነው የሰላማዊ ትግል አካል ሊሆን የሚችለው፡፡ ሰላማዊ ትግል ዲሞክራሲ በሌለበት የሚደረግ ትግል ከሆነ ዘንዳ የዴሞክራሲ መገለጫ የሆነው ምርጫ ሰላማዊ ትግል ነው ማለትስ ምን ማለት ነው?

ሰላማዊ ትግል እኮ ሰላማዊ ትግል ያስባለው መሳሪያ የሚያስነሳ ጭቆና መኖሩ ነው፡፡
ግልፅ በሆነ መንገድ ለማስቀመጥ
በምርጫ የሚደረግ ትግል ህዝቡ የስልጣኑ ባለቤት በሆነበት ሀገር እንጂ ሁሉም ነገር በአገዛዙ መዳፍ ስር በሆነበት ሁናቴ አይደለም፡፡

ሰላማዊ ትግል ዲሞክራሲ ጨርሶውኑ በሌለበትና እየሞቱ ማሸነፍ ግድ የሆነበት የትግል አካሄድ ነው፡፡
የትጥቅ ትግልም ዲሞክራሲ ፈፅሞ በሌለበት ሀገር ውስጥ እየገደሉም እየሞቱም ለማሸነፍ የሚደረግ ትግል ነው፡፡

ከዚህ በመነሳት
1- አሁን ባለንበት ሁናቴ ምርጫ ማካሄድ የዴሞክራሲ ሂደት ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ማለት ሲሆን
2- ኢህአዲግን በፈቃዳችን እንደ መንግሰት እውቅና መስጠት ነው

ስለዚህ፡- ትግሉ ሰለማዊ ትግል ነው የምንለው ምርጫ ማድረግ የሚቻልበትን ምህዳር መፍጠር፤ ህዝቡን የስልጣኑ ባለቤት ማድረግ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በመሁኑ ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ማቸውንም የፖለቲካ ስራ በነፃነት መስራት በማይቻልበት ሁናቴ ነፃነት እንዲኖር መታገል ከሁሉ በፊት መሆን ያለበት ትግል ነው፡፡ ይህ ትግል በባህሪይው እልህ አስጨራሽ፣ ተስፋ አስቆራጭ፣ ብዙ ዋጋ የሚያስከፍል … ፍሬው ግን ዘላቂና እጅግ አስደሳች ነው፡፡ ለዛ ነው ደጋግመን ህይወታችንንም ቢሆን እስከመስጠት ድረስ ፍፁም ሰላማዊ ሆነን እንታገላለን የምንለው፡፡

ሰለማዊ ትግል ከነፍጥ ትግል የሚለየውም በዚሁ ባህሪይው ነው፡፡ በመውደቅ በመነሳት ውስጥ ማሸነፍ፤ ሳይገድሉ በመሞት ማሸነፍ፡፡ ይህ መንገድ በምርጫ ከሚደረግ የስልጣን ትግልም ሆነ መሳሪያ አንስተው በሀይል ስልጣን ለመያዝ ከሚደረግ ትግል ፍፁም የተለየ ነው፡፡ ነፃነት ትግል ይፈልጋል፡፡ ፍፁም ሰላማዊ ሆነን እናሸንፋለን!
Image

ሃገሪቱን የሚያሰጋት የሃይማኖት አክራሪነት/አሸባሪነት ሳይሆን የፖለቲካ የበላይነት የፈጠረው አሸባሪነት ጽንፈኝነት እና አክራሪነት ነው:: ጥላችሁን እንዳታምኑ እየተባለ ሃይማኖት መንግሥታዊ ቅርጽ ይዞ እንዲወጣ ለማድረግ መሞከር አክራሪነት ነው፡፡ «መጾም፣ መጸለይ፣ ሥርዓተ-አምልኮን መፈጸም ሃይማኖታዊ አልባሳትን መልበስ ለሃይማኖቱ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ እንጂ አክራሪነት ሊባል አይችልም፤»…የአክራሪ ክርስትና ወይንም እስልምና ቡድን መኖር የክርስትና እና እስልምና ተከታዮችን በሙሉ «አክራሪ» አስብሎ ሊያስፈርጃቸው አይችልም::አክራሪ ተብሎ […]


ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
  ዛሬ በወግ ሽርሽር ብዙ ሀገር አቋርጠን “ፋርስ” ገብተናል፡፡ የዑመር ኻያም ሀገር! የፊርደውሲ ሀገር! የኒዛሚ ሀገር! የጃሚ ሀገር! የሓፊዝ ሀገር! በሩባኢያትና በገዛላት ዓለምን እያስፈነደቁ ለብዙ ክፍለ ዘመናት የዘለቁ የቅኔ ጠቢባን የተገኙባት ምድር!
  
   ዛሬ ፐርሺያ ነን! ዛሬ ኢራን ነን፡፡ ዛሬ ቴህራን ነን፡፡ ዛሬ ኒሻፑር ነን፡፡ ዛሬ ጠብሪዝ ነን፡፡ ዛሬ ሂልማንድ ነን፡፡ ዛሬ ኢስፋሓን ነን፡፡ ዛሬ ሺራዝ ነን! እዚያ ትልቅ የጥበብ ድግስ ተደግሶ ይጠብቀናል፡፡ እዚያ ከመድረሳችን በፊት ግን ለውዲቷ ኢራን ይህንን “ሩበእ” ብንቀኝላትስ?!  
አንቺ ሀገረ-ፋርስ የሀገር ጥበበኛ
ሁሉንም ያበቀልሽ አድርገሽ መልከኛ
የቅኔሽ መዓዛ ጠርቶኝ መጥቻለሁ
እጅሽን ዘርግተሸ መርሓባ በይኛ!
ሞክሬዋለሁ አይደል?. አዎን! “ሩበእ” (ሩባኢያት) ማለት እንዲህ ነው፡፡ ባለ አራት መስመር ቅኔ ሆኖ ሶስተኛው ስንኝ ከሌሎቹ አፈንግጦ ሲጻፍ በፋርሲ ቋንቋ “ሩበእ” ይባላል (ከዐረብኛው “ራቢዕ” የተገኘ ቃል ነው)፡፡ አንደኛ፣ ሁለተኛ እና አራተኛ መስመሮች በተመሳሳይ ፊደል ነው የሚያበቁት፡፡ ሶስተኛው ስንኝ ግን ከነርሱ ጋር አይገጣጠምም፡፡ “ሩበእ” ነጠላ ስም ነው፡፡ ለብዙ ቁጥር “ሩባኢያት” ይሆናል፡፡ አንዳንዶች የግጥሙ ዘውግ ከዐረቢያ ነው የተወረሰው ቢሉም “ሩባኢያት” ኦሪጂናሌ የኢራን የግጥም ዘይቤ መሆኑ በምሁራን ተረጋግጧል፡፡
ኢራናዊያን በሩባኢያት በጣም ይኮሩበታል፡፡ እንደ ብሄራዊ ቅርሳቸው ያዩታል፡፡ በተለይ The Zenith of Persian Literature በሚባለው ዘመን (ከ950 እስከ 1400 ድረስ) የተጻፉ ሩባኢያቶችን ከልብ ያፈቅሩአቸዋል፡፡ እኛም እንደ ዕድል ሆኖ በተስፋዬ ገሠሠ በኩል የዑመር ኻያም ሩባኢያትን በአማርኛ ለማንበብ በቅተናል፡፡ ዳሩ ግን እኛ ካጣጣምናቸው ሩባኢያት በላይ በኢራናዊያን የሚወደዱት የነ ሩሚ፣ ሳዲ፣ ጃሚ እና ሓፊዝ “ሩባኢያ”ት ናቸው፡፡ (ኢራናዊያን ከዑመር ኻያም በጣም የሚያደንቁለት የሒሳብ ሊቅነቱን ነው እንጂ ገጣሚነቱን አይደለም)፡፡
*****
ኢራን ነፍስ የሆነች ሀገር ናት! በጣም ውብ ባህልና የዳበረ ቋንቋ አላት፡፡ ታሪኳም ከቅድመ ክርስቶስ በፊት ከነበረው ዘመን ጀምሮ ነው የሚሰላው፡፡ በዚህ ረገድ ከመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት በእድሜ እርሷን የሚቀድሙት የርሷ ጎረቤት ሀገራት የሆኑት ሜሶጶጣሚያ (ኢራቅ) እና ሶሪያ ብቻ ናቸው፡፡ ዓለምን ያስደመሙ ታላላቅ ባለቅኔዎችን በማብቀል ግን ኢራን ከሁሉም ሀገራት ትበልጣለች፡፡
ኢራን ከጥንትም ጀምሮ ትክክለኛ ስሟ “ኢራን” ነው፡፡ የርሷ ተወላጆች ሀገራቸውን በዚሁ ስም ነው የሚጠሯት፡፡ ነገር ግን አብዛኛው የዓለም ህዝብ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ “ፋርስ” ወይንም “ፐርሺያ” ይላት ነበር፡፡ ኢራናዊያኑ “ይህ ስም አንዱን ክፍለ ሀገር እንጂ ሀገሪቱን በሙሉ ስለማይወክል ሀገራችንን ፐርሺያ እንዳትሏት” የሚል ዘመቻ ከፍተው ተሳክቶላቸዋል፡፡ ዛሬ ይኸው ኢራን ትባላለች፡፡ ይሁንና ቋንቋው “ፋርሲ” ነው የሚባለው፡፡ በዚህ ላይ ኢራዊያኑ ተቃውሞ የላቸውም፡፡ እንግዲህ በዚህ የፋርሲ ቋንቋ ነበር እነዚያ ውድ ባለቅኔዎች ዓለምን በጥበብ ሲያጠምቁ የነበሩት፡፡
*****
   የጥንቷ ኢራን እንዲህ እንደ አሁኑ አልነበረችም፡፡ ዛሬ አፍጋኒስታን፣ ቱርክሜኒስታን እና አዘርባይጃን የሚባሉ ሀገራት ለብዙ ክፍለ ዘመናት የርሷ ግዛቶች ነበሩ፡፡ የዛሬው እንግዳችንም በአሁኗ አፍጋኒስታን፣ በበልኽ አውራጃ፣ “ሩማ” በምትባል ከተማ ነው የተወለደው፡፡ እውነተኛ ስሙ ጀላሉዲን ሙሐመድ ወለድ ነው፡፡ ብዙዎች እርሱን የሚጠሩት ግን በትውልድ ከተማው ስም “ሩሚ” በማለት ነው፡፡
የሩሚ አባት የታወቁ ሼኽ እና ቃዲ ነበሩ፡፡ ሩሚም መደበኛ ትምህርቱን እዚያው በአባቱ ስር መማር ጀመረ፡፡ ነገር ግን በአስራ አንድ ዓመቱ መጥፎ እጣ ገጠመው፡፡ በዘመኑ መካከለኛው እስያን ደም በደም አድርገው የነበሩት የሞንጎል ወራሪዎች ወደ “በልኽ” እየተቃረቡ መሆናቸው ተሰማ፡፡ ስለዚህ የሩሚ አባት ቤተሰቡን ይዞ በምዕራብ አቅጣጫ ተሰደደ፡፡ “ኒሻፑር” ከምትባለው ጥንታዊት የኢራን ከተማ ሲደርሱም ከዘመኑ ዝነኛ ገጣሚ ፈሪዱዲን አጣር ጋር ተገናኙ፡፡ አጣር በሩሚ ነገሮችን የማስተዋል ችሎታ ተደንቆ “ይህ ልጅ ለወደፊቱ ትልቅ ባለቅኔ የመሆን ተስፋ አለው” የሚል ትንቢት ተናገረ ይባላል፡፡
ከሞንጎል የሸሸው የሼኽ ሙሐመድ ባሀኡዲን ወለድ (የሩሚ አባት) ቤተሰብ በመጨረሻ “ኮኒያ” ከምትባለው የቱርክ ከተማ ደረሰ፡፡ ሼኽ ባሃኡዲን እዚያ ካለው መድረሳ ማስተማር ጀመሩ፡፡ እርሳቸው ከሞቱ በኋላ ደግሞ የማስተማሩ ተግባር አንጋፋ ልጃቸው ለሆነው ለሩሚ ተላለፈ፡፡ ይሁንና ልጁ በማስተማሩ ላይ ሊያተኩር አልቻለም፡፡ ተፈጥሮንና ኑሮን እያየ ይህንን ግልብጥብጥ ዓለም የፈጠረውን ፈጣሪ አፈቀረ፡፡ ለርሱ የሙገሳ ቃላትን በግጥም መደርደር ጀመረ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በኋላ ግን አንድ ያልተጠበቀ እንግዳ ወደ ሩሚ መንደር ብቅ አለ፡፡
ሙላህ ሸምሱዲን ይባላል፡፡ የጠብሪዝ ተወላጅ ነው፡፡ ኢራናዊያን “ሸምስ-ኢ-ጠብሪዚ” ይሉታል፡፡ ሩሚ በሸምሱ-ጠበሪዝ ላይ ባየው መንፈሳዊ ልቅና ተመሰጠ፡፡ እንደ መምህሩም ቆጠረው፡፡ ቤተሰቡንና ስራውን ሁሉ ትቶ ከርሱ ጥበብን መቅሰም ጀመረ፡፡ አንድ ቀን ግን ሸምስ ጠብሪዝ እዚህ ነኝ ሳይል ጠፋ፡፡ በዚህም የተነሳ ሩሚ የመምህሩን ፍቅር ተራበ፡፡ ፍቅሩ እያቃጠለው “መደድ” (የፍቅር የመጨረሻ ደረጃ) ውስጥ አስገባው፡፡  ከዚያማ ማን ይቻለው! ከመምህሩ የተማረውን በራሱ ቋንቋ ጻፈው፡፡ 30,000 “ገዛል” እና ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ “ሩባኢያት”ን ከተበ፡፡ እነዚህም ግጥሞች “ዲዋን-ኢ-ሸምሹ-ጠብሪዝ” በተሰኘ መጽሐፍ በአንድ ላይ ተሰበሰቡ (“ገዛል” የሚባለው ግጥም “ዜማ” ጭምር እንዳለው ልብ በሉ)፡፡
*****
የሩሚ የጥበብ ፍቅር አላበቃም፡፡ በሸምስ ጠበሪዝ መጥፋት የተከፋችው ነፍስ ሌላ መምህር ፍለጋ አላቆመችም፡፡ ታዲያ ሩሚ ብዙም አልተጓዘም እዚያው “ኮኒያ” ከተማ ውስጥ ተማሪው የነበረ ልጅ መምህሩ ሆኖ ተገኘ፡፡
 ሑሳሙዲን ይባላል፡፡፡ ሑሳሙዲን ከሩሚ ግጥሞች ሌላ የነ ፈሪዱዲን አጣርን፣ የነ ሰነኢንና የሌሎች ታላላቅ የፋርስ ባለቅኔዎችን ስራ አጥንቷል፡፡ እናም አንድ ቀን ሩሚን እንዲህ አለው፡፡ “መምህር! የርስዎ ግጥሞች ጉድለት ይታይባቸዋል፤ የራስዎትን ስሜት ብቻ እየተከተሉ ስለሚጽፉ በሌላው ውስጥ ጠልቆ የመግባት ሀይል ያጥራቸዋል፤ ለምን እንደ አጣርና እንደ ሰነኢ አይጽፉም” አለው፡፡
 ሩሚም “እስቲ እንዴት አድርጌ ልጻፍ?” በማለት ጠየቀው፡፡
 ሑሳሙዲንም “ከልዩ ልዩ ምንጮች የተገኙ እውነተኛ ታሪኮችን፣ ተረቶችን፣ ምሳሌዎችን፣ ተምሳሌቶችን፣ ወዘተ… እያሰናሰሉ ቢቀላቅሉባቸውና የግጥሞቹ አካላት ቢያደርጓቸው የምን ጊዜም ተወዳጅ ይሆናሉ” ብሎ መለሰለት፡፡
 የሑሳሙዲን ምክር በሩሚ ልብ ውስጥ ጠልቆ ገባ፡፡ ከዚያም ቅኔ ሲመጣለት መቀኘት ጀመረ፡፡ ሑሳሙዲንም ከሩሚ አንደበት የሚወጣውን መጻፉን ተያያዘው፡፡ ሁለቱ ሰዎች እንዲህ እያደረጉ ዛሬ ዓለም በሙሉ የሚደመምበትን “መስነቪ”ን አስገኙ (የመጽሐፉ ትክክለኛ ስም “መሥነዊ” ነበር፤ ይህም “መሥን” ከተሰኘው የዐረብኛ ግስ የተገኘ ነው፡፡ ነገር ግን የ“ሠ” እና የ“ወ” ድምጾች በፋርሲ ቋንቋ ውስጥ ስለሌሉ ኢራናዊያን “መስነቪ” እያሉ ይጠሩታል፤ የዓለም ህዝብም የነርሱን ፈለግ በመከተል “መስነቪ” ይለዋል)፡፡
*****
ሩሚ “መስነቪ”ን የደረሰው ከዛሬ 800 ዓመት በፊት ነው፡፡ ይሁንና ዛሬም ድረስ የህዝብ ፍቅር ሳይነፈገው እንደተወደደ አለ፡፡ በዘመናችን “ሩሚ”ን እጅግ ተነባቢ ከሆኑ አስር ምርጥ ገጣሚዎች ተርታ ያሰለፈውም “መስነቪ” ነው፡፡ ይህ ዝነኛ የግጥም ድርሳን ለዓለም ስነ-ጽሑፍ መዳበር ያደረገውን አስተዋጽኦ በመመዘን የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት የአውሮፓዊያኑ 2007 በዓለም አቀፍ ደረጃ የሩሚ ዓመት ተብሎ እንዲጠራ ወስኗል፡፡ በዚያው ዓመት ሩሚ የተወለደበት ስምንት መቶኛ ዓመት ተከብሯል፡፡
የመስነቪ ይዘት ሰፊ ነው፡፡ የሰውን ልጅ አዕምሮ ያመራምራል፡፡ በዚህ ትንሽ መጣጥፍ ስለርሱ ብዙ ማውራት አይቻልም፡፡ ዳሩ ግን ከመስነቪ የተቀዳ አንድ ውብ ታሪክ ላካፍላችሁ እችላለሁ፡፡ ሩሚ ታሪኩን በግጥም ነው የጻፈው፡፡ ነገር ግን ተርጓሚው በስድ-ንባብ መልሶ ጽፎታል፡፡ እኔም በስድ ንባብ የተጻፈውን ታሪክ ነው የምጋብዛችሁ፡፡
===አራቱ ሰዎችና መንገደኛው===
  አራት ሰዎች ነበሩ፡፡ እነዚያም ሰዎች ግሪክ፣ ፋርሲ (ኢራናዊ)፣ ዐረብ እና ቱርክ ነበሩ፡፡ የሚፈልጉትን ነገር ይገዙበትም ዘንድ የተወሰነ ገንዘብ ተሰጣቸው፡፡ ግሪኩ “እኔ ስታፊል አምሮኛል፤ ስታፊል ግዙልንና እንብላው” አለ፡፡
ፋርሲው “የምን ስታፊል? ኡዙም ግዙልን እንጂ ሰዎች” አለ፡፡
ዐረቡ “አረ ወደዚያ! ኢነብ ነው የምንገዛው፤ ኢነብ መግዛት አለብን” በማለት ተናገረ፡፡
ቱርኩ “እንዴ! አንጉር ነው መግዛት ያለብን፤ አንጉር እንጂ ሌላ ነገር አትግዙብን” አለ፡፡
    አራቱ ሰዎች ተከራከሩ፡፡ ተነታረኩ፡፡ በጭራሽ ሊግባቡ አልቻሉም፡፡ እንዲህ እየተወዛገቡ ሳለም አንድ መንገደኛ መጣ፡፡ “ምንድነው የሚያጨቃጭቃችሁ?” በማለት ጠየቃቸው፡፡ ጉዳዩን ነገሩት፡፡ ሰውየውም “በዚህ ፍራንክ የሁላችሁንም ፍላጎት ማሟላት ይቻላል” አላቸው፡፡ ሰዎቹም “እንዴት?” በማለት ጠየቁት፡፡ ሰውዬም ገንዘቡን እንዲሰጡት ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም እንደተባለው አደረጉ፡፡
መንገደኛው ሰውዬ በአካባቢው ከነበረ የፍራፍሬ መሸጫ ገብቶ አንዱን የፍራፍሬ ዓይነት ገዝቶ ሲወጣ አራቱ ሰዎች ተያዩ፡፡ በዚያው በሳቅ ፈረሱ፡፡ ለካስ አራቱም የአንዱን ፈራፍሬ ስም በየቋንቋቸው እየጠሩት ነበር? አራቱም “ወይን እፈልጋለሁ” እያሉ ነበር የሚከራከሩት::
*****
የታሪኩን “ማዕና” (መልዕክት) አገኛችሁት አይደል? ለኛም እንደ መንገደኛው ሰውዬ ያለ አስታራቂ ይላክልን፡፡ አንድ ውጥንና ግብ ያላቸው ሰዎች ዕድሜ ልካቸውን በአተገባበር ላይ ሲጣሉ ማየትን የመሰለ አሰቃቂ ህመም የለም፡፡ ሁሉም እይታውን ቢያስተካክል መግባባት ይቻላል፡፡ ሩሚ ይህንን ነው የመከረን፡፡
ብራቮ ጀላሉዲን ሩሚ! ብራቮ መሥነቪ!
*****
የካቲት 24/2006
*****
Afendi Muteki is a researcher and author of the ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his blog and his facebook page by clicking the following links

ኢትዮጵያ ውስጥ በልማትና አገልግሎት ላይ የተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕድገት ሲያሳዩ በመብቶች ጉዳዮች ላይ ሲሠሩ የነበሩት ግን መዳከማቸውን አንድ ጥናት አመልክቷል፡፡

በሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች አማካይነት በዚህ ዓመት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል፡፡

ወደ 20 ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ተጠቃሚ ሆነዋል – ተብሎም ተገምቷል፡፡
የዘገባውን ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤

 

ሕዝብን ያላስከተለ ትግል ዉጤት አያመጣም – ግርማ ካሳ

“ምርጫው ላይ ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጠናል።በምርጫው ልንሳተፍም ሆነ ላንሳተፍ ውሳኔ የምናሳልፈው እኛ ሳንሆን ሂደቱ ነው” ብለዋል። ” እኛ ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጥነው ምርጫ ላይ ሳይሆን የምርጫ ሂደቱ ላይ ነው” ሲሉ ደግሞ አቶ ግርማ በቀለ የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፀኃፊ፣ ቀደም ሲል ለምርጫው ቅድመ ሁኔታ አላቀመጥንም የሚለው ለማሻሻል ሞክረዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ የትብብሩ አመራሮች መልስ ለመስጠት የተቸገሩ፣ እርስ በርሳቸዉም አንድ አቋም ያልያዙ መሰለኝ። አቶ ዮናትን ቅድመ ሁኔታ ለምርጫው አስቀምጥናል እያሉ፣ የትብብሩ ዋና ጸሃፊ ለምርጫው ቅድመ ሁኔታ አላስቀመጥንም የሚሉ ከሆነ የቱ ነው ትክክለኛ የትብብሩ አቋም ? ? ? አቶ ዮናትን ወይስ አቶ ግርማ በቀለ ያሉት። በዚህ ጥያቄ ላይ “Honesty is the best policy” ይላሉ ፈረንጆች። ሰማያዊም ሆነ ትብብር በዚህ ረገድ አቋማችሁን በግልጽ ማስቀመጥ አለባችሁ። መቃረን የለባችሁም።

ሌላው ወደ ምርጫ ለመግባት ሂደቱ ይወስነዋል ይላሉ አቶ ዮናታን። ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል። አንዱ ቅድመ ሁኔታ ይመስለኛል የምርጫ ቦርድ ነጻ መሆን አለበት የሚል ነው። በዚህ ረገድ አሁን ባለው ሁኔታ ገዢው ፓርቲ ፈቀቅ ያለበት ሁኔታ የለም። ካልተገደደ በቀር አሁን ያለው ምርጫ ቦርድ ነው የሚቀጥለው።

ትዝ ይለኛል ከምርጫ ቦርድ ሰብሰባ ሰማያዎች ረግጠው ወጥተው ነበር …ምርጫ ቦርድ ግን ኢግኖር ነው ያደረጋቸው። ስራዉንም ቀጥሏል። የአንድ ወር መርሃ ግብር ብለዉም ከፖሊሶች ጋር ተጋጩ፥ ብዙዎች ለሁለት ሶስት ቀናት ታሰሩ። አሁንም ምንም ለዉጥ የለም በምርጫ ቦርድ አካባቢ።

ሁለት ሶስት መቶ ሰዎች ይዞ ሰልፍ መዉጣት አገዛዙን አያስገድድም። ይልቅ መቶ ሺሆች፣ ሚሊዮን ሕዝብ እንዲወጣና ለመብቱ እንዲጮህ ነው ማድረግ የሚያስፈለገው። ለዚህም በጋራና በትብብር መስራት ያስፈልጋል። ጠንካራ ከሚባሉ ድርጅቶች ጋር ከነ አንድነት፣ መድረክ ጋር አብራችሁ ሰላማዊ ሰልፎችን ሰማያዎች ቢጠሩ፣ አብረው መሰረታዊ የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን ቢያነሱ ብስለትና እውቀት ባለበት መልኩ ቢንቀሳቀሱ፣ ትልቅ ቫይብሬሽን መፍጠር ይቻል ነበር።

እርግጥ ነው እዚህ በዉጭ ያሉ እንዳንድ ጽንፈኞቹ ከረን አፌር ክፍል ያሉ ሰማያዎችን ፣ ሆይ ሆይ እያሏቸው ነው። ምናልባት ሁለት፣ ሶስት ቀናት በመታሰራችሁ “ጀግኖች፣ አንበሶች” ሲሏቸው፣ ያለ እነርሱ ሰው የሌለ ሊመስላቸው ይችላል።

ሆኖም ግን እዚህ በዉጭ ያሉ ጽንፈኖች ችግር ዉስጥ ነው ሰማያዎዎችን የሚከቷችሁ። አዎ ከዉጭ ድጋፍ ማግኘት ጥሩ ነው። ዉጭ ያለው ወገን የትግሉም አካል ነው። ሆኖም ዉጭ ያለው ማህበረሰብ የሚፈልገውን ሳይሆን በአገር ቤት ያለው ሕዝብ የሚፈለገውን በማዳመጥ ነው መንቀሳቀስ የሚገባው። የሰላማዊ ትግል የራሱ የሆነ ሰራዊት አለው። እርሱም ሕዝብ ነው። ሕዝብን ያላሰለፈና ያላንቀሳቀሰ ትግል ዋጋ አይኖረዉም።

አንድ ነገር ብዬህ ላቁም። ከአንድ አመት በፊት ሰማያዊ ሰልፍ ሲጠራ ወደ 70 ሺህ ሕዝብ ተገኝቶ ነበር። ከሶስት ወራት በኋላ ሰልፍ አንድነት ሲጠራ አብረው አእንዲያደረጉ ትልቅ ተማጽኖ ቢቀርብላቸውም፣ እምቢ ብለው፣ ተሽቀዳድመው ሰልፍ ጠሩ። ሰልፉ ጃን ሜዳ ነበር ግን መስቀል አደባባይ መሄድ አለብን ሲሉ ከፖሊስ ጋር ዉዝግብ ፈጠሩ። ጥቂት ፖሊሶች አፈኗችሁ።

ስድስት ወራት በኋላ፣ ሚያዚያ ላይ አንድነት ሰልፍ ጠርቶ ከአስተዳደሩ ጋር እየተነጋገረ ባለበት ጊዜ ፣ እንደ ጎህ ዝንብ ጣልቃ ገብተው፣ ሰልፍ ጠሩ። ለአንድነት አይሆንም በተባለ ቀን፣ እውቅና አገኙ። ለሰልፉም ቅስቀሳ አደረጉ። የተገኘላችሁ ሰው ሶስት መቶ አካባቢ ብቻ ነበር። ከሰባ ሺህ ወደ ሶስት መቶ መዉረድ ማለት ትልቅ የፖለቲካ ኪሳራ ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ የሰማያዊን ስትራቴጂ እንደማያደገፍ ሰልፉ ላይ ባለመገኘት ገለጸ።

ለምንድን ነው ይሄ የሆነው ብለው መጠየቅ አልቻሉም። አሁን በአንድ ወር መርሃ ግብር እንቅስቃሴያቸውም የተለየ ነገር አላየንም። እንደ ኢሳት ባሉ ሜዲያዎች ሁሉ ሳይቀር ለሌለ ማንም ድርጅት ያልተደረገ ትልቅ ቅስቀሳ ተደረገላቸው። በሶሻል ሜዲያዉም እንደዚሁም። ከአምስት ሚሊዮን የአዲስ አበባ ህዝብ፣ መቶ አይሞላም የወጣላቸው። ለምን የአዲስ አበባ ህዝብ ጥሪያቸዉን ሰምቶ እንቅስቃሴያቸዉን አልተቀላቀለም ? ይሄ መመለስ ያለበት መሰረታዊ ጥያቄ ነው።

ገዢው ፓርቲን ማስገደድ የሚቻለው ህዝቡ በነቂስ ሲወጣ ብቻ ነው። ሰማያዊቾ ትኩረት ሰጥተው መንቀሳቀስ የነበረባቸው ሕዝቡ እንዲወጣ ማድረግ የሚቻልበትን ስትራቴጂ በመንደፍ ላይ መሆን ነበረበት። ደግሜ እላለሁ ….ሰማያዊች የያዙት መስመር በጣም አደገኛና ትግሉን የሚጎዳ ነው። አላስፈላጊ ኮንፍሮንቴሽን አስወግደው፣ ሕዝቡን በማደራጀት ላይ፣ ከሌሎች ድርጅቶች ጋር አብሮ በመስራት ላይ ቢያተኩሩ ጥሩ የሚሆን ይመስለኛል። አለበለዚያ የሁለተኛ መርሃ ግብር ብለዉም የሚያወጡት ከአንደኛው የሚለይ አይሆንም።

የአንድነት ፓርቲ በፖለቲካ ፕሮግራም ተመሳሳይነት ካላቸው ጋር ፣ ሰማያዊን ጨምሮ፣ ያለ አንዳንች ቅድመ ሁኔታ በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ እየገለጸ ነው። ሆኖም የሰማያዊ አመራሮች ከአንድነት ጋር ለመስራት አለርጂክ ለምን እንደሆነባቸው ደጋፊዎቻቸው መጠየቅ ያለባቸው መስለኝ።

የሰማያዊ አቅጣጫ ስህተትና የማይጠቅም ነው – ግርማ ካሳ

አቶ እያስፔድ ተስፋዬ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ አባልና የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ ናቸው። “አቧራን ለማጥራት – ነጻነት ለምርጫ ቅድመ ሁኔታ ነው” በሚል ርእስ አንጹ ጽሁፍ አቅርበዋል። በሚከተለው ሊንክ ያገኙታል። የእኝህ ወጣት አቀራረብ በጣም ተመችቶኛል። በነጻነት ነጥባቸውን በማስቀመጥ ለምርጫ ከመገባቱ በፊት መሟላት ያለበት ቅድመ ሁኔታ እንዳለ ይከራከራሉ።

viewtopic.php?f=2&t=90558

የድርጅት አባል ባልሆነም፣ የምደገፈው ድርጅት አለ። እርሱም የአንድነት ፓርቲ ነው። ይህ ፓርቲ፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለምርጫ እንደሚሳተፍ በይፋ ለህዝብ አሳዉቆ፣ «2007 ለለውጥ»፣ «ተደራጅ ለምርጫ» በሚል መርህዎች በአገሪቷ ሁሉ መጠነ ሰፊ የምርጫ እንቅስቃሴ ጀመሯል።

የአንድነት አቋም ለምን ትክክለኛ እንደሆነ፣ በአንጻሩም ደግሞ የሰማያዊ ፓርቲ አቋም ለምን የወቅቱን ሁኔታ ያላመዛዘነ የተሳሳተና በ እወቀት ሳይሆን በስሜት ላይ የተመሰረተ አቋም እንደሆነ ለማሳየት እሞክራለሁ። የአንድነት አባል እንዳለመሆኔ፣ ከዚህ በታች የምጽፈው የግል አስተያየቴ እንደሆነ ከወዲሁ ለአንባቢያን አሳውቃለሁ።

ብዙዎቻችን በምርጫ በመግባትና ባለመግባት ዙሪያ የሚደረገው ዉይይት አካል ሆነን ሐሳቦችን ሰንዝረናል። አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫ መገባት የለበትም የሚሉ ወገኖች ፣ ከምን ተነስተው እንደዚያ እንደሚሉ እረዳለሁ። ሆኖም የነርሱን አቋም ተቃዉሜ ስጽፍ፣ ምርጫ ባለመግባት የሚገኝን ጥቅም ሊያሳዩን ባለመቻላቸው ነው።

እዚህ ዉጭ አገር ያሉ አንዳንድ በጠመንጃ ትግል እናምናለን የሚሉ ቡድኖች፣ ምርጫ እንዲገባ አይፈልጉም። (እነርሱ ዉጊያቸውን ትተው ለምን በሰላማዊ ታጋዮች ዙሪያ እንደሚጨነቁ ባይገባኝም) ምናልባት ምርጫ ከተደረገና አንጻራዊ መሻሻል ከመጣ የነርሱ ፖለቲካ ዜሮ ስለሚገባ ሊሆን ይችላል ምርጫዉን የሚቃወሙት። በመሆኑም ከነዚህ ቡድኖች በምርጫ ዘመቻ ላይ ተቃውሞ ቢሰማ ልንገረም አይገባም።

አገር ቤት በሰላም የሚታገሉ ወገኖች ግን ፣ ምርጫዉን ቦይኮት ሲያደርጉ ፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ደርጅታቸውን ወይንም ሕዝቡን የሚጠቅም መሆኑን በማስላት መወሰን ያለባቸው መሰለኝ። ይሄን ካደረጉ የቦይኮት ጥሪው ችግር ይኖረዋል ብዬ አላስብም። ነገር ግን ትንሽ ያልተመቸኝ ፣ እነ አቶ እስያስፔድ እንዲያስረዱን የምፈልገው ፣ ቦይኮት ማድረጉ ምን ጥቅም ለትግሉም ሆነ ለሰማያዊ ፓርቲ እንደሚያስገኝ ነው። ቦይኮት ተደረገ፤ ከዚያስ ? ? ትልቅ መመለስ ያለበት ጥያቄ።

እስከሚገባኝ ድረስ የሰማያዊ ፓርቲ ሆነ ትብብር በቀዳሚነት አቋማቸው በግልጽ አይታወቅም። አንዳንድ አመራሮች ያለ ቅድመ ሁኔታ ወደ ምርጫው እንገባለን ይላሉ። አንዳንዶቹ ደግሞ ተቃራኒዉን ይናገራሉ። ስለዚህ በቅድሚያ የሰማያዊም ሆነ ትብብሩ አቋም ግልጽ መሆን አለበት። አንድ የአመራር አባል ፌስ ቡክ ላይ በመጻፉ ሳይሆን፣ ደርጅቶቹ በኦፊሴል ለሕዝብ አቋማቸዉን ግልጽ ማድረግ አለባቸው።

ለዉይይት ያህል.፣ ቅድመ ሁኔታ ሳይሟላ ወደ ምርጫው አይገባም ከተባለ፣ ቀጣዩ ጥያቄ የሚሆነው ቅድመ ሁኔታዎቹ ምንድን ናቸው የሚል ነው። ከዚያ ገዚው ፓርቲ ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟላ ምን እየተደረገ ነው ? የተደረገውስ ምን ዉጤት አመጣ ? የሚሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ።

የሰማያዊ ፓርቲ አገዛዙ ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሟላ፣ ጫና ለማድረግ የአንድ ወር መርሃ ግብር አጠናቋል። ዉጤቱን ሁላችንም የምናወቀው ነው። ካለፈው የአንድ ወር መርሃ ግብር የተለየ ነገር በሚቀጥሉት መርሃ ግብሮች ምን ሊፈጠር እንደሚችል በርግጠኝነት መናገር ቢያስቸግረም፣ መገመቱ ግን ይከበዳል ብዬ አላስብም።

የሰማያዊ ፓርቲ ቅድመ ሁኔታዎች አልተሟሉም ብሎ ከምርጫው ቢወጣ፣ ገዢው ፓርቲ የሚፈራው ወይም የሚጎዳበት ሁኔታ የሚፈጥር ቢሆን ኖሮ «ቦይኮት አደርጋለሁ» በሚል ማስፈራራትና ቅድመ ሁኔታዎች ማስቀመጥ ያስኬዳል ብዬ ልቀበል እችል ነበር። ሆኖም ያደረች ባቄላ እንደሚባል፣ ገዢው ፓርቲ ሰማያዊ ምርጫ ዉስጥ ገባ፣ አልገባ ግድ አይሰጠዉም። የሰማያዊ ምርጫውን አለመሳተፍ ለነርሱ ኢንሲግኒፊካንት ነው። በመሆኑም ምርጫ አንገባም ማለት ፖለቲካ ፋይዳ አይኖረዉም።

ሌላው ቦይኮት በሚደረግበት ጊዜ ፣ ሕዝቡም ቦይኮት እንዲያደርግ ማስተባበር ያስፈልጋል። ህዝቡ ወደ ምርጫ ሄዶ ፣ ሰማያዊ ግን ብቻዋን ቦይኮት ቢያደረግ፣ እንደ ቢራቢሮ አየር ላይ የሚንሳፈፍ ድርጅት ነው የሚሆነው። ድርጅቶች በሙሉ ተባብረው፣ ተነጋግረው፣ በተቀናጀ መልኩ ቦይኮት እንዲደረግ ዘመቻ ቢያደርጉ፣ ህዝቡም የቦይኮቱ አካል እንዲሆን ቢያደራጁ፣ ከቦይኮቱ ጎን ለጎን ሰላማዊ ሰልፎችን የሥራ ማቆም አድማዎችን ቢጠሩ …ቦይኮት ሊሰራ ይችላል። ከዚያ ዉጭ ግን ቦይኮት የሚያመጣዉ አንዳች ፋይዳ አይኖርም። (እስከሚገባኝ ድረስ የሰማያዊ ፓርቲ ከነ አንድነት ፓርቲ ጋር አብሮ መስራቱ እንደ አለርጂክ እየሆነበት ነው። ከተመሰረቱ ጊዜ ጀመሮ ከአንድነት ጋር ፉክክር እንጂ የያዙት፣ በቁም ነገር፣ «በአንድ ላይ መሰባሰባች የአገርና የሕዝብ ጥያቄ ነዉ» በሚል ሂሳብ ለመንቀሳቀስ ሲሞክሩ አይታዩም)

በመጨረሻ የማነሳው ነጥብ የፕራክቲካሊቲ ነጥብ ነው። ሰማያዊ «አገዛዙ ላይ ጫና አሳድሬ፣ ቅድመ ሁኔታዎች እንዲሟሉ አደርጋለሁ» ይላል። በአራት ወራት ጊዜ ዉስጥ ምን ያህ ይሄ ግብ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል ? እዉነት እንነጋገርና በአራት ወራት ዉስጥ አገዛዙ ምርጫ ቦርድን ይለውጣልን ? ለነዚህ ጥያቄዎች መልሱ « አይችልም፣ አይሆንም» የሚል ነው።

ምርጫ ቦርድ ላይ በየምርጫ ጣቢያ ጫና ሊያደረግ የሚችለዉን ህዝብ፣ ድምጹን እንዲያስከበር ከማደራጀትና በየሜዳው ሄዶ ከመንቀሳቀስ ዉጭ ሌላ አማራጭ አይኖርም። የሰላማዊ ትግል ሰራዊት ሕዝቡ ነው። ወታደሮች ከኋላው ያላሰለፈ ጀነራል የትም እንደማይደርስ፣ ህዝቡን ከበስተኋላ ያላሰፈ የሰላማዊ ትግል መሪም ሆነ ድርጅት ሩጫ ከንቱ ነው።

«አንድነት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በምርጫው እሳተፋለሁ» ብሎ መግለጫ መስጠቱን አልቃወምም፡፡ አባላቶቼን ከወዲሁ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ይረዳኛል ብሎ ይሆናልና፡፡ ልክ እንደዚሁም ሁሉ ሌላውም የእኛን አቋም እንዲያከብርልን እሻለሁ፡፡» ሲሉም አቶ እያስፔድ ጽሁፋቸውን ያጠቃልላሉ። በመርህ ደረጃ ትክክል ናቸው። ሆኖም በዚህ ወሳኝ ወቅት የሰማያዊና የአንድነት ስትራቴጂዎች የተለያዩ በመሆናቸው ሕዝቡን የማደናገር ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። አንድነት በአንድ በኩል ለምርጫ ተመዝገቡ እያለ ለምርጫ ሲቀሰቀስ፣ ሰማያዊ ደግሞ በሌላ በኩል ቦይኮት ይደረግ እያለ የሚቀሰቅስ ከሆነ፣ በተቃራኒ ወገን ቆሙ ማለት ነው። የግድ አንድነቶች የሰማያዊ አማራጭ ትክክል እንዳለሆነ የማስተማርና የመቀስቀስ፣ በሐሳብ የማሸነፈ ሃላፊነት ይኖርባቸዋል።

ስለዚህ መከባበሩ፣ እንደተጠበቀ፣ ቢቻል ሁለቱም ወደ አንድ አቋም እንዲመጡ ቢነጋገሩና በጋራ ቢሰሩ፣ ካልሆነም ግን የግድ አንዱ ሐሳብ አሸናፊ ሆኖ መውጣት ስላለበት የፖለቲካ ክርክሮቹ በሰለጠነ፣ ከስሜትና ከስድብ በጸዳ መልኩ ቢደረጉ ጥሩ ሊሆን ይችላል።

ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት፣ ሰማያዊ የወሰደው ቅድመ ሁኔታ የማስቀመጣ ፖለቲካና አቋም ስህተተ ነው ብዬ ነው የማምነው። አንዳንዶች በምርጫው መሳተፉን «ተለጣፊ» እንደመሆን እና ለአገዛዙ ሌጂቲመሲ(እውቅና) እንደመስጠት አድርገው የሚቆጥሩ አሉ። እነዚህ ወገኖች አንድነት ወደ ምርጫ በመግባቱ «ተለጣፊ» ሆኗል የሚል አስተሳሰብ ካላቸው፣ መለስ ብለው የሚሊዮኖችን ንቅናቄ እንዲመለከቱ እጋብዛቸዋለው። በአሁኑ ጊዜ የሕዝብን ትርታ የያዘ፣ በሆያ ሆዬ ላይ ሳይሆን፣ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ የሚያራምድ ፣ በሁሉም ክልሎች መዋቅር ያለው የፖለቲካ ድርጅት አንድነት ብቻ ነው። ሂዱ አርባ ምንጭ፣ ሂዱ ጂንክ፣ ሂዱ ወሊሶ፣ ሂዱ ጊምቢ፣ ሂዲ ጎንደር፣ ሂዱ አሳሶ፣ ሂዱ አዳማ፣ ሂዲ ሶዶ፣ ሂዱ ደሴ …አንድነትን በዚያ ታገኛላችሁ።

ለአገዛዙ ሌጂቲመሲ መስጠት ነው ለሚሉት ደግሞ ሌጂቲመሲ ሰጭው ማን እንደሆነ ቢነገሩን ጥሩ ነበር። በዉጭ ኃይሎች ዘንድ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሌጂቲሚስ ያገኛል የሚል ፍርሃት ከሆነ ያላቸው፣ በጣም የዲፕሎማሲ እወቀት ዴፊሸንሲ አለባቸው ማለት ነው። እነአሜሪካ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴጎች አምባገነን፣ በሕዝብ ያልተመረጡ፣ ድምጽ ሰርቀው ስልጣን ላይ ጠመንጃ ስለያዙ ብቻ፣ እየገደሉና እያሰሩ እንደሚገዙ ያውቃሉ። ሆኖም እውቅና ሰጥተዋቸው ዋይት ሃዉስ ድረስ ጠርተው እያስተናገዷቸው ነው። ለምን ሌላ፣ የተሻለ፣ ጥቅማቸውን የሚያስጤብቅ ኃይል ስለሌለ። እቅጩን እንወቅ፣ ቦይኮት ተደረገም አልተደረገም፣ ምርጫ ተገባም አልተገባም፣ አሜሪካም ሆነ አዉሮፓዉያን በአገዛዙ ላይ ያላቸውን አቋም አይለዉጥም። እነ አሜሪካ የፖሊሲ ለዉጥ የሚያደርጉት፣ ፊታቸውን ከሕወሃት/ኢሕአዴግ የሚያዞሩት፣ ተቃዋሚዎች ምርጫዉን ቦይኮት በማድረጋቸው ሳይሆን፣ ሕዝቡን አደራጅተው በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን ማነቃነቅ ከጀመሩ ብቻ ነው። ለዚህም ነው ምርጫ ከተገባ ሕወሃት/ኢሕአዴግ ሌጂቲማሲ እንዲያገኝ እናደርገዋለን የሚለው አስተያየት ዉህ የማይቋጥርና በእወቅት ላይ ያልተመሰረተ ነው የምለው።

ለጊዜው አበቃሁ !

* የገቡት ይወጣሉ ፣ የወጡት ተመልሰው ይመጣሉ * የሳውዲ መንግስት “ህገ ወጦችን” የማጽዳቱ ዘመቻ ቀጥሏል * ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎች ከሞት ጋር ተፋጠው እየተሰደዱ ነው * የሳውዲ መንግስት ማስጠንቀቂያና እርምጃ … የሳውዲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውንና ህጉ በማይፈቅደው መንገድ የመኖሪያ ፈቃዳቸው ካለው ሙያ ውጭ የሚሰሩ የማናቸውንም ሀገር ዜጎች በመላ ሀገሪቱ ለማጽዳት የተደራጀ ዘመቻ ከተጀመረ ወር […]

አዲስ አበባ ህዳር 26/2007 አዲሱ የአዋሽ ወንዝ ድልድይ ግንባታ በመጠናቀቁ ዛሬ ለትራፊክ ክፍት መሆኑን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ።

የኢትዮ-ጅቡቲ መስመር 90 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ገቢና ወጪ ንግድ የሚስተናገድበት መንገድ ሲሆን በቀን ከ20 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችንም…

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሰማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች በትብብሩ ውስጥ የታቀፉ ፓርቲዎች በጠሩት የአዳር ሰልፍ ላይ የወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የተወሰደውን አሳፋሪ እርምጃ ሰምቻለሁ፡፡ እርምጃው ሁለት ነገሮችን በጉልህ ያሳዬ ነበር፡፡ አንደኛ የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሽንፍትን ያሳየ ነው፤ ሁለተኛው ደግሞ ሰላማዊ ትግሉ እየተጠናከረ መምጣቱን ያመላከተ ነው፡፡ አንተ ባዶ እጅህን መብትህን ለመጠየቅ ስትንቀሳቀስ፣ መሳሪያ ወደታጠቀ አካል በሰላም ስትገሰግስ […]

ታኀሳስ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በከፍተኛ ዝግጅት ይከበራል የተባለው የህወሃት 40ኛ አመት በአል ወጪ የሚሸፈነው ከመንግስት ካዝና መሆኑ በአባል ድርጅቶች መካከል መነጋገሪያ አጀንዳ እየሆነ መምጣቱን የሚናገሩት የኢህአዴግ ምንጮች፣ ከመንግስት ካዝና ለሚወጣው ገንዘብ የተሰጠው ሰበብ  ገጽታ ግንባታ የሚል መሆኑን ገልጸዋል። ህወሃት በአሉን ከድርጅቱ ካዝና በተለይም የአገሪቱን ሲሶ ሃብት ከተቆጣጠረው ኢፈርት ካዝና መጠቀም እየቻለ፣ ወጪውን …

ታኀሳስ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ መንግስት የሃማኖት፣ የእድር፣ የአፎቻ መሪዎችን፣ የአገር ሽማግሌዎችንና ታዋቂ ግለሰቦችን በራስ መኮንን የህዝብ አዳራሽ ታህሳስ 5 ቀን 2007 ዓም ሰብስቦ ባወያየበት ወቅት ፣ ከ1990-2004 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ የተሰሩ ቤቶች በሰነድ አልባ ቤትነት የተመዘገቡ እና ከከተማው ማስተር ፕላን ጋር የማይጋጩ ከሆነ ህጋዊ ይደረጋሉ፣ ከ2004 ዓም እስካሁን ካርታና ፕላን …

ታኀሳስ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን እንደ ሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች በነዳጅ አቅርቦት ሲቸገሩ የቆዩት የባህርዳር የታክሲና ባጃጅ አሽከርካሪዎች ዛሬም ድረስ ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን ለዘጋቢያችን ተናግረዋል። በትናንትናውና በዛሬው እለት በከተማዋ ካሉት ከአስር በላይ ማደያዎች በአንዱ ብቻ ነዳጅ የሚገኝ መሆኑን የተናገሩት አሽከርካሪዎች ፣ በዚህ ነዳጅ ማደያ ለመቅዳት እስከ ሁለት መቶ ሜትር ተሰልፈው ለሰዕታት እንደሚቆዩ ተናግረዋል፡፡ …

ታኀሳስ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለአንድ አመት ያክል ተቋርጦ የነበረው የደቡብ ሱዳንን የሰላም ስምምነት እንደገና ለማስጀመር እንቅስቃሴ መጀመሩን የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስዩም መስፍን አስታውቀዋል። ድርድሩ የተጀመረው በአዲስ አበባ ነው። ሁለቱ ተፋላሚ ሃይሎች በተለያዩ ጊዜያት ለድርድር ቢቀመጡም እስካሁን ይህ ነው የሚባል መፍትሄ ሊያመጡ አልቻሉም። የኢሳት የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደሚሉት በደቡብ ሱዳንና በኢትዮጵያ መካከል ያለው …

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

Image

ተስፋዬ ገ/ኣብ በየሄደበት ሁሉ መርዝ መርጨቱን ኣያቆምም፡፡ በቅርቡ የኦሮሞ ልጅነትን (ፎርጅድ) አግኝቻለሁ በማለት ተናግሮ ሳይጨርስ ነጻ ሆኖ ይንቀሳቀስ የነበረዉን የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) አደጋ ውስጥ ጨምሮታል፡፡ OMN ከተመሰረተ እንኳ አንድ አመት ሳይደፍን ይኸዉ ከሁለት መከፈሉን የተለያዩ ሚዲያዎች እየነገሩን ነዉ፡፡
ይህ የሚዲያ ተቋም የሰዉ ሀይል ችግር ኖሮበት አይመስለኝም፡፡ እነ በፈቃዱ ሞረዳ ከዚህም በላይ መስራት የሚችሉ ሰዎች ናቸዉ፡፡ በፈቃዱ በተደጋጋሚ ባደረጋቸዉ ቃለ መጠይቆች ወገንተኝነትን የማይፈልግ ፍጹም የጋዜጠኛነት ሙያ የሰረጸዉ ሰዉ መሆኑን አስመስክሯል፡፡
በእኔ እምነት ችግሩ ተስፋዬን ወደ ህብረታቸዉ ማስጠጋታቸዉ ነዉ፡፡ ተስፋዬ ገብረ አብ በማንኛዉም መንገድ ለኦሮሞም ሆነ ለሌላዉ ኢትዮጵያዊ ህብት እንደማይፈልግ እነ በፈቃዱና ሌሎችም የተረዱት አልመሰለኝም፡፡ እናም ይኸዉ አንድ አመት ሳይደፍን ከጆሀር መሀመድ ጽንፈኝነት ጋር ተጨማምሮ ሚዲያዉን ህልዉና ተፈታተነዉ፡፡
viewtopic.php?f=2&t=90612

Image

ከጥቂት ወራት ወዲህ አንድ የተደበቀ ነገር ግልፅ እየሆነ መጥቷል። ይኸዉም በርካታ ትላልቅ ኩባንያዎች እና የንግድ ድርጅቶች ለመንግሥት በሕጉ መሠረት ገቢ ማድረግ የሚገባቸዉን ግብር ላለመክፈል በስዉር ያሸሻሉ ተብለዉ በብዙ ሃገራት ተከሰዋል።

ፍጥረተ -ዓለም ፣ ለመከሠት የበቃበትንና ሥርዓት የያዘበትን ሁኔታ ተመራምሮ ለመገንዘብ መጣር ከዋናዎቹ የሳይንስ ተግዳሮቶች አንዱ ነው። ምንም ያህል ምርምር ያድርጉ፣ የሥነ ፈለክ ጠበብት እስካሁን ከዚህ እስከዚያ የሚባል አጽናፍ ስለሌሉት ሕዋ የሚያውቁት እጅግ ውስን እንደሆነ አይክዱም።

መፍትሄ ያጣውን የደቡብ ሱዳን ጦርነትለማስቆም ተፋላሚ ኃይላትን ሸምጋይ የሆነው የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን- ኢጋድ ሰሞኑን ደቡብ ሱዳን ውስጥ ባለፈው አንድ ወር ገደማ ተፈፀመ ያለውን ጥቃትና የስምምነት ጥሰት የሚገልፅ ዘገባ አውጥቷል።

በፓኪስታን የታሊባን ታጣቂዎች በጅምላ ከገደላቸው ከገደሏቸው 141 ሰዎች መኻከል አብዛኞቹ ተማሪ ልጆች እንደነበሩ ተዘግቧል። ጥቃቱ የተፈፀመው ማክሰኞ ታኅሣሥ 7 ቀን 2007 ዓም የኪቤር ፓክቱንክህዋ ግዛት መዲና በሆነችው ፔሻዋር ውስጥ በሚገኝ አንድ የወታደር ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ ነበር።

‹‹በሰላማዊ ሰልፈኛ ላይ ዱላ መሰንዘር ሽንፈት ነው›› እስክንድር ነጋ

ሰማያዊ ፓርቲ እና ሌሎች በትብብሩ ውስጥ የታቀፉ ፓርቲዎች በጠሩት የአዳር ሰልፍ ላይ የወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የተወሰደውን አሳፋሪ እርምጃ ሰምቻለሁ፡፡ እርምጃው ሁለት ነገሮችን በጉልህ ያሳዬ ነበር፡፡ አንደኛ የኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሽንፍትን ያሳየ ነው፤ ሁለተኛው ደግሞ ሰላማዊ ትግሉ እየተጠናከረ መምጣቱን ያመላከተ ነው፡፡

አንተ ባዶ እጅህን መብትህን ለመጠየቅ ስትንቀሳቀስ፣ መሳሪያ ወደታጠቀ አካል በሰላም ስትገሰግስ ባለመሳሪያው ዱላውን ከሰነዘረብህ አሸናፊው አንተ ሰላማዊው ታጋይ ነህ፡፡ በትብብሩ ሰልፍ ላይ የሆነው ይኸው ነው፡፡ አሁን ሰላማዊ ትግሉ ፍጹም ሰላማዊነቱን እንደጠበቀ መጠናከር ነው ያለበት፡፡ ሰላማዊ ትግል ላይ ልብ ማለት ያለብን ነገር አለ፤ እሱም ሰላማዊ ሆኖ መዝለቅ የሚለው ጉዳይ ነው፡፡

ሰላማዊ ታጋይ ይሰደባል፣ ይደበደባል፣ ይሞታልም፡፡ ግን ደግሞ ሰላማዊ ታጋይ አይሳደብም፣ አይደባደብም፣ አይገድልም፡፡ ይህ ከሆነ ሰላማዊ ትግል ያሸንፋል፡፡ አምባገነኖች ሰላማዊ ታጋዮችን በተለያየ መንገድ ከሰላማዊነታቸው እንዲወጡ ሊገፋፏቸው ይሞክራሉ፤ ስሜት ውስጥ በመክተትም የኃይል በትራቸውን ለማሳረፍ ይቋምጣሉ፡፡ ይህ ሴራ ሰላማዊ ታጋዮችን ሊያዘናጋቸው አይገባም፡፡

በቀደም በተደረገው ሰልፍ ላይ ድብደባው በሰላማዊ ሰዎች ላይ መፈጸሙ ለተደብዳቢዎቹ ሳይሆን ሽንፈቱ ለደብዳቢዎቹ ነው፡፡ በደረሰው ድብደባ ባፍርም፣ ባዝንም በውጤቱ ግን ደስተኛ ነኝ፤ ምክንያቱም ሰላማዊ ሰልፈኞች ሰላማዊነታቸውን አሳይተዋልና! በሰልፉ ወቅት ድብዳባ እና እስር የደረሰባቸውን የመብት ጠያቂዎች ሁሉ በርቱ ልላቸው እፈልጋለሁ፡፡ ባደረጉት ሰላማዊ እንቅስቃሴ በጣም ኮርቻለሁ፡፡ ሰላማዊና ህጋዊ ትግላችሁን ቀጥሉ ማለትም እፈልጋለሁ!

‹‹አሸናፊው ህዝብ ነው›› አንዱዓለም አራጌ

ግለሰቦች የለውጥ ሐዋርያ ሊሆኑ ይችላሉ፤ በዚያው ልክ የሚሳሳቱትም ግለሰቦች ናቸው፡፡ የግለሰቦች አስተሳሰብ ህዝባዊ ከሆነ ግን በአሸናፊው ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ይኖራቸዋል፡፡ ምክንያቱም አሸናፊው ህዝብ ነው፤ አሸናፊው ሀገር ነው፡፡ የሁላችንም አሸናፊነት የሚገለጸው ሀገር ከፍ ከፍ ስትል ነው፡፡ ስለዚህ ስራችን ሁሉ ሀገርን ከፍ ለማድረግ መሆን አለበት፡፡

በትብብሩ ፓርቲዎች በተጠራው ሰልፍ ላይ የሆነውን ሰምቻለሁ፡፡ በሆነው ነገር አዝኛለሁም፤ ኮርቻለሁም፡፡ ያዘንኩት በደረሰው ድብደባ እና እስር ነው፡፡ የኮራሁት ደግሞ መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ ሊጠይቁ በድፍረት አደባባይ በወጡት ታጋዮች ነው፡፡ በእነዚህ ታጋዮች የእውነት ኮርቻለሁ፡፡

በቀጣይ ፓርቲዎች በአጋርነት መስራት አለባቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ በተለይ በቀጣዩ ምርጫ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ፓርቲዎች ከእጩ አቀራረብ ጀምሮ ተቀራርበው መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ በተለይ ሰማያዊ እና አንድነት ተቀራርበው ቢሰሩ የበለጠ ውጤታማ የሚሆኑ ይመስለኛል፡፡ በተረፈ ግን በትብብሩ ሰልፍ ወቅት ጉዳት ለደረሰባቸው ሁሉ ጥንካሬን እንዲሰጣቸው እመኛለሁ፡፡ ትግላቸውንም አጠናክረው እንዲቀጥሉ አደራ እላለሁ፡፡

‹‹ቃላችሁን ጠብቃችኋልና ክብር ይገባችኋል፣ ኮርቸባችኋለሁም!›› የሺዋስ አሰፋ

ሰማያዊ ፓርቲ መርህ አለው፡፡ ያመነበትን ነገር ህጋዊና ሰላማዊነቱን ጠብቆ እንደሚፈጽም አውቃለሁ፡፡ ትብብሩ በጠራው ሰልፍ ላይም የሰማያዊ ወጣቶችና ሌሎችም ቃላቸውን ጠብቀው ሰልፍ ወጥተዋል፡፡ በእውነት በጣም ኮርቸባቸዋለሁ፡፡ እንደሁሌውም ቃላቸውን ጠብቀው ለህዝቡ መብት መቆማቸውን አይቼ ደስ ብሎኛል፡፡ እኔ በእስር ላይ ብሆንም ሌሎች የትግል ጓዶቼ ባደረጉት ነገር በጣም ነው ደስ የተሰኘሁት፡፡

ድብደባውና እስሩ የፈሪ ዱላ ነው፡፡ ኢህአዴግ በህዝብ ፊት ኪሳራን ነው ያተረፈው፡፡ ሰላምን እና ህግን ማስጠበቅ የሚቻለው በልምምጥ ሳይሆን ትክክለኛ መስመርን በመከተል ነው፡፡ በዚህ መሰረት የትግል ጓዶቼ ትክክለኛ መስመር ላይ እንደሆኑ ይገባኛል፡፡ በርቱልኝ ማለት እፈልጋለሁ፡፡ በዚህ መሰል ሰላማዊነት ነው አምባገነኖችን ማሸነፍ የሚቻለው፡፡ በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር