Tag: Ethiopia
ብልጽግናና ባሕል
በአምስት ዓመቱ ሕፃን ላይ የግብረ-ሰዶም ጥቃት የፈፀመው በ20 ዓመት እሥራት ተቀጣ Man who raped 5-year-old boy sentenced to 20 years
አስራ ሦስት ዓመት ባልሞላው ሕፃን ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ፈፅሟል ሲል የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተበት የ23 ዓመቱ ወጣት ሳሙኤል መርዕድ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ20 ዓመት እሥራት እንዲቀጣ የፌዴራሉ የመጀመሪያ…
ኢሳት እንደሚዲያ ጥፋት የለውም::ቦርዱ ጉዳዩን ሊያየው ይገባል:: Minilik Salsawi
ሰዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብት አላቸው::የህዝቦችን ነጻነት መጋፋት ጋዜጠኛ አያሰኝም:: ጥፋተኛው የኢሳት ኢዲቶሪያል ሳይሆን የጥቂት ግለሰቦች የማናለብኝነት እና በስሜት የመነዳት ፖለቲካ ነው:: አዎን ምናልባት አንዳንዶች በልቅ የፖለቲካ ስድነት ያሸበረቁ ግለሰቦች ስማቸውን የቀያየሩ ሰውን በየድህረገጹ የሚዘልፉ የኢሳት ጋዜጠኞች ይህ ጽሁፍ ላይመቻቸው ይችላል:: ኢሳት ገና ከጅምሩ ሲመሰረት ህዝባዊ አላማ አንግቦ እና ህዝባዊ ስራዎችን ለመስራት እንደተቋቋመ የማይካድ ሃቅ […]
መጓተቱ ይቅርና ግማሽ መንገድ መጥተን እንቀራረብ፡፡ – (በእያስፔድ ተስፋዬ)
መታሰር ክፉ ነው፡፡ የታሰረ ሰው ተስፋው ሁሉ ውጪ በቀረው ታጋይ ላይ ነው፡፡ የሀብታሙ አያሌው እና የየሺዋስ አሰፋ ልብ የሚነካ ተማፅኖ አእምሮዬን ሁሉ ተቆጣጥሮታል፡፡ ‹‹እባካችሁ ተባበሩ›› ‹‹እስቲ ቀረብ ብላችሁ ተነጋገሩ›› በየንግግራቸው መሀል እየደጋገሙ የሚያስተላልፉት መልዕክት ነው፡፡ ‹‹እኛ እኮ ከዛሬ ነገ ለውጥ መጥቶ ኑ ውጡ እንባላለን ብለን ነው የምንጠብቀው……በተናጠል ድርጅቶች ያላቸውን አቅም የምናውቀው ነው….እባካችሁ ተባበሩ›› ሀብታሙ አያሌው፡፡ […]
አል-ኸዋሪዝሚን በጨረፍታ
Ethiopia broadcasting authority undecided on whether to issue permit for private TV station ለግሉ ዘርፍ ቴሌቪዥን ቻናል የመስጠት ጉዳይ አልተወሰነም
ተጻፈ በ ውድነህ ዘነበ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለሥልጣን በተያዘው የበጀት ዓመት 15 አዳዲስ የቴሌቪዥን…
ለውጪ ሀገር የሕክምና ጉዞ የሚያማክር ተቋም ሥራ ጀመረ Medical center consults patients who wish to travel abroad seeking medical care
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር ተጠልፎ አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ
(ቃለየሱስ በቀለ) የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡ ከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡ አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን […]
ወያኔው ወልዱና የባህርዳሩ ግዮን ሆቴል
የአማራ ክልል ባለስልጣናት የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ በባህርዳሩ ግዮን ሆቴል ላይ ያለውን የባለቤትነት መብት እስካሁን ማስከበር አልቻሉም፡፡
ታኀሳስ ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፌደራል ፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ተረክቦ ቦታውን ለልማት ለማዋል ዝግጅት የጀመረው የክልሉ የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ ሆቴሉን ነጻ ለማድረግ ከህዳር 15 ቀን ጀምሮ አገልግሎቱን እንዲያቋርጥ እና በውስጡ ያሉትን የግለሰብ ንብረቶች ለማስወጣት ያደረገው እንቅስቃሴ ለአንድ ወር ያህል አለመሳካቱን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
ኤጀንሲው በቁጥር ኮቤልኤ-ዋሥ/32/1108 በቀን 16/ 03/07ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ በግቢው ውስጥ የሚገኙትን የግለሰብ ንብረቶች ከ15/03/07 ዓ.ም ጀምሮ በህጋዊ መንገድ እንዲያወጡ በመጠየቅ፣ ንብረቱ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ የማያወጡ ከሆነ በቤቱና በግቢው ውስጥ ለቆዩበት ጊዜ ሁሉ በቀን ሃያ ሽህ ብር እና ሌሎች ኪሳራዎችን የቤቱ ባለቤት የሆነው የክልሉ መንግስት ተወካይ የኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ የሚያስከፍል መሆኑን በመግለጽ ንብረቱ እንዲነሳ በመጠየቅ ሆቴሉን አሽጎ ሰራተኞችን መበተኑ ታውቋል፡፡
ለአስራ አምስት ቀናት ቢጠብቅም ምንም ውጤት ያላየው ኤጀንሲ በ01/04/07 ዓ.ም ባወጣው ድጋሚ ደብዳቤ « መንግስት በቦታው ላይ ያቀደውን የልማት ስራ እርስዎ ንብረትዎትን ባለማውጣትዎ ምክንያት ሊያቆም ስለማይገባ በግቢው ውስጥ ያለውን ንብረት ወደ አንድ ቦታ በማሰባሰብ የልማት ስራውን ለማስቀጠል ስላስፈለገ እቃው በሚሰባሰብበት ወቅት በእርስዎ በኩል በታዛቢነት የሚኖር ሰው ሰኞ ታህሳስ 8ቀን 2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ሆቴሉ መግቢያ በር እንዲገኝ እያሳሰብን የእርስዎ ተወካይ ወይም ታዛቢ ባይገኝ ሌሎች ታዛቢዎች በተገኙበት በግቢው ውስጥ ያለውን ዕቃ ወደ አንድ ክፍል የሚያሰባሰብ መሆኑን እየገልጽን መንግስት ይህንን እና ሌሎች ለስራው የሚያስፈልጉ ወጭዎችን ቀደም ሲል በተሰጠዎ ማስጠንቀቂያ መሰረት ከእርስዎ እንደሚጠበቅ አንዲያውቁት እናሳስባለን፡፡” ብሎአል።
በባህርዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት የአቶ መለስ ዜናዊ የቅርብ ዘመድ አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከ900 መቶ ሺህ ብር በላይ እንዳያገኝ ያደረገ ታክሰ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ወልዱና ቤተሰቡ ኃላፊነት የተወሰነ የግል ማህበር በእስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የምዕራብ ጎጃም ዞን የባህርዳር ምድብ ችሎት ውሳኔ ማስተላለፉን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የውሳኔ መዛግብት ዋቢ በማድረግ መዘገባችን ይታወሳል።
የምዕራብ ጎጃም ፍርድ ቤት ባህርዳር ምድብ ችሎት ወልዱና ቤተሰቡ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ እና አቶ ብስራት ወልዱ ወልዳረጋይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብስቦ ያለማሳወቅና ያለመክፈል እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ ባልሆነ ደረሰኝ ግብይት በማካሔድ ወንጀል በአመት ስድስት ነጥብ ሶስት ሚልዩን ብር መሰብሰባቸው መጠቀሱንና ከዚህም ለመንግስት መግባት የነበረበት ከስድስት መቶ ሺ ብር በላይ ለግል ጥቀማቸው አውለዋል በማለት ተከሳሽ ወልዱ ወልዳረጋይ በ7 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ አንደኛ ተከሳሽ ወልዱና ቤተሰቡ ሀላፊነቱ የግል ማህበርን በተመለከተ በህገ-ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በመሆኑ በወንጀል ህግ አንቀፅ 90/3 መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብስቦ ያለማሳወቅ፣ ያለመክፈል ወንጀልና ግብር ለመንግስት ያለመክፈል ወንጀል ክሶች እያንዳንዳቸው የብር 10 ሽህ መነሻ ቅጣት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ባልሆነ የደረሰኝ ግብይት ማካሔድ ወንጀል ክስ ደግሞ ብር 5 ሺህ ባጠቃላይ 25 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጫ እንዲከፍሉ ውሳኔ መተላለፉን ዘግበናል፡የባህርዳር ነዋሪዎች በድርጅቱና በልጅቻው ላይ የተሰጠውን ውሳኔ ቀልድ ነው ማለታቸውም ይታወሳል ፡፡
ከ10 ቀን በፊት ከባህር ዳር ማረሚያ ቤት ከገዢው መንግስት ባለስልጣናት በተሰጠ ቀጭን ትዕዛዝ የእስር ጊዜያቸውን ሳያጠናቅቁ ሳይሆን ሳይጀምሩ የተፈቱት አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ ፣ ኤጀንሲው በሰጠው ማስጠንቀቂያ መሰረት ንብረታቸውን ያላነሱ ሲሆን በኤጀንሲው ውሳኔ መሰረት ንብረታቸውን ላላነሱበትና ልማቱን ላደናቀፉበት 30 ቀናት ከ600 ሽህ ብር በላይ እንደሚጠበቅባቸው ምንጮች ገልጸዋል፡፡፡የባህርዳሩ ግዮን ሆቴልን ለረዢም አመታት በአምስት ሽህ ብር የክራይ ዋጋ ሲጠቀሙበት የነበሩት አቶ ወልዱ ወልደ አረጋይ ኤጀንሲው እንዲከፍሉ የወሰነባቸውን ገንዘብ መክፈል ሳይሆን በሌሉበት እና በህግ ጥላ ስር እያሉ በማናለብኝነት ሆቴሉ በመዘጋቱና ሰራተኞችንም በመበተኑ ላደረሰባቸው ኪሳራ የክልሉን የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲን በህግ ለመጠየቅ ከጠበቆቻቸው ጋር እየተመካከሩ መሆኑን እማኞች ለዘጋቢያችን ገልጸዋል፡፡
አቶ ወልዱ ግዮን ሆቴልን የሚያክል ድርጅት የአቶ መለስ ዜናዊ ዘመድ በመሆናቸውና በትጥቅ ትግሉ ወቅት መረጃ በማቀበል ላገለገሉበት እንደውለታ ተቆርጦላቸው እጅግ እርካሽ በሆነ መንገድ በሆቴሉ ከ20 አመታት በላይ ሲጠቀሙበት መቆየታቸው በክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ቅሬታ ያስነሳ ጉዳይ ሆኖ ቆይቷል። አሁንም ባለስልጣናት ደፍረው የፍርድ ቤት ትእዛዝ ለማስፈጸም እንዳልቻሉ ታውቋል።
የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ተካሄዷል ብለን አናምንም! – ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ምርጫ ቦርድ ነፃና ገለልተኛ እንዳልሆነ የሚገነዘብ ቢሆንም ባለፈው ታህሳስ 12/04/2007 ዓ.ም የተካሄደው የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ በሀገራችን የምርጫ ቦርድ አለ ወይ?! እንዲል አድርጎታል። የታህሳሱ 12/04/2007 ዓ.ም የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ነፃና ገልልተኛ አልነበረም ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የምርጫ ህጉን ተከተሎ ያልተካሄደ ሌላው ይቅርና የራሱ የምርጫ ቦርድ መመሪያን እንኳን ያልተከተለ ከመሆኑ አንፃር ተካሄዷል ብለን […]
በደቡብ ሱዳን ለተሰማራው የተመድ የሰላም አስከባሪ ጦር አዛዥ የነበሩት ሌ/ጄኔራል ዮሃንስ ከደቡብ ሱዳን መንግስት በቀረበባቸው ክስ ከሃላፊነት መነሳታቸው ታወቀ
ታኀሳስ ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህዳር 11 ቀን 2007 ዓም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በደቡብ ሱዳን በአቤይ ግዛት ተሰማርቶ የነበረው የሰላም አስካባሪ ቡድን አዛዥ ሌ/ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ተስፋማርያም በእኤአ ጁን 19፣ 2014 ተልእኮዋቸውን ጨርሰው በሜ/ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ገላልቻ መተካታቸውን ቢገልጽም፣ ኢሳት በዜና እወጃው አዛዡ ጊዜያቸውን ሳይጨርሱ መሰናበታቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደገለጹት ሌ/ጄኔራል …
ምርጫ ቦርድ ግንቦት 16 ቀን 2007 ሊያካሂድ ላቀደው ብሔራዊ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ምዝገባ በዛሬው ዕለት ጀመረ፡፡
ታኀሳስ ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በየምርጫ ክልሉ ጽሕፈት ቤቶች ከታህሳስ 16 እስከ ጥር 27 ቀን 2007 ዓ.ም ምዝገባ እንደሚካሄድ የሚታወቅ ቢሆንም አንድነትና መኢአድ ፓርቲዎች ከምርጫ ቦርድ ጋር ከገቡት አሰጥ አገባ ጋር ተያዞ በምርጫው የመቀጠላቸው ነገር አጠራጣሪ መሆኑ ታውቆአል፡፡ አንድነት እና መኢአድ በመጪው ምርጫ ለመወዳደር ወስነው የምርጫ ምልክት …
የአማራ ክልል ባለስልጣናት የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ በባህርዳሩ ግዮን ሆቴል ላይ ያለውን የባለቤትነት መብት እስካሁን ማስከበር አልቻሉም፡፡
ታኀሳስ ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከፌደራል ፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ተረክቦ ቦታውን ለልማት ለማዋል ዝግጅት የጀመረው የክልሉ የኮንስትራክሺንና ቤቶች ልማት ኤጀንሲ ሆቴሉን ነጻ ለማድረግ ከህዳር 15 ቀን ጀምሮ አገልግሎቱን እንዲያቋርጥ እና በውስጡ ያሉትን የግለሰብ ንብረቶች ለማስወጣት ያደረገው እንቅስቃሴ ለአንድ ወር ያህል አለመሳካቱን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ኤጀንሲው በቁጥር ኮቤልኤ-ዋሥ/32/1108 በቀን 16/ 03/07ዓ.ም በተጻፈ …
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 25, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
የጎርጎሪዮሣዊው ገና በዓል
የገና ወይም የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የጎሮጎሮሳዉያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተለዉ የክርስትና እምነት ተከታይ ዘንድ ዛሬ ተከብረ። በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ሐገራት የሐይማኖት መሪዎችና ፖለቲከኞች ለየተከታዮቻቸዉ መንፈሳዊና ዓለማዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የታህሳስ ወር ሃገራዊና ባህላዊ ትርጓሜ ክፍል ሁለት
መፀዉ ወይም መኽር ወር፤ ከመስከረም ሃያ ስድስት እስከ ታህሳስ ሃያ አምስት ይዘልቃል፤ ከታህሳስ ሃያ ስድስት ደግሞ በጋ ይጀምርና እስከ መጋቢት ሃያ አምስት ይዘልቃል። በዚህም ኢትዮጵያዉያን የገና በዓልን የሚያከብሩት ታህሳስ መጨረሻ በበጋ ወርራት ዉስጥ ነዉ።
የናቁት ያስቀራል ራቁት! የትግሬ ወያኔ ዐማራን ከመጨፍጨፍ እና ከመጥላት አልፎ ንቆታል – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት
የትግሬ ወያኔ ዐማራን ከመጨፍጨፍ እና ከመጥላት አልፎ ንቆታል፤ ይህ ደግሞ ነገ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል! አንድ ሰው ወይም ቡድን ሌላን ሰው ወይም ቡድን በጅምላ መጥላት ከጀመረ፣ የጠላውን ሰው ወይም ቡድን በቀጥተኛ እና በተዘዋዋሪ መንገድ ለማጥፋት ይጥራል። አልፎ ተርፎ ይህ ሰው ወይም ቡድን የጠላውን ሰው ወይም ቡድን መናቅ ሲጀምር እርሱን ለማጥፋት ሰበብ አይፈልግም። ንቀት ያሳደረበትን ሰው ወይም […]
ኢሳት እንደሚዲያ ጥፋት የለውም::ቦርዱ ጉዳዩን ሊያየው ይገባል:: Minilik Salsawi
ሰዎች ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብት አላቸው::የህዝቦችን ነጻነት መጋፋት ጋዜጠኛ አያሰኝም::
ጥፋተኛው የኢሳት ኢዲቶሪያል ሳይሆን የጥቂት ግለሰቦች የማናለብኝነት እና በስሜት የመነዳት ፖለቲካ ነው:: አዎን ምናልባት አንዳንዶች በልቅ የፖለቲካ ስድነት ያሸበረቁ ግለሰቦች ስማቸውን የቀያየሩ ሰውን በየድህረገጹ የሚዘልፉ የኢሳት ጋዜጠኞች ይህ ጽሁፍ ላይመቻቸው ይችላል::
ኢሳት ገና ከጅምሩ ሲመሰረት ህዝባዊ አላማ አንግቦ እና ህዝባዊ ስራዎችን ለመስራት እንደተቋቋመ የማይካድ ሃቅ ነው::ኢሳት የሰራቸው በጎ ተግባራት እንደተጠበቁ ሆነው እጅግ ሊሻሻሉ እና ሊታረሙ የሚገባቸው ጥፋቶችም በገሃድ አይተናል እያየን ነው::አብዛኛው ጥፋቶች የሚከሰቱት ዲሲ ከሚገኘው እና የግንቦት ሰባት አመራሮች በስሜት ፖለቲካቸው ከሚነዱት ስቱዲዮ መሆኑን ስንመለከት ደሞ ራሳችንን እንድንጠይቅ አድርጎናል::
ለኢሳት ስኬት አስፈላጊውን አስታውጾ እና ድጋፍ እስካደረኩ ድረስ የኢሳት ጉዳይ ያገባኛል ይመለከተኛል:: አንዳንድ ኢሳት የነሱ ብቻ የሚመስላቸው አዋቃጭ ግለሰቦች በደመነብስ የሚናገሩትን አልባሌ ቦለቲካቸውን ወደ ጎን በመተው ኢሳት ሊጠናከር የሚችለው ያለበትን ሲያርም እና በውስጡ የተወሸቁ ስሜታዊ እና ልቅ ጋዜተኞችን ሃይ ማለት ሲችል ብቻ ነው::አንድ ሳው አስተያየት በሰጠ ሰአት ሁሉ እየተነሱ የኒዛለፉ እና የሚሳደቡ ባለጌ ጋዜጠኞች እና አዋቃጭ ተባባሪዎቻቸውን ሊያርማቸው ይገባል::ጥላቻን ማራመድ በቀረበት በዚህ ስልጡን ዘመን ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያውያን ላይ ጥላቻ እንዲያራምዱ የሃገር ጉዳይ ተረስቶ ግለሰቦች እንዲዘረጠጡ በተራ አሉባልታ እና የስድብ ናዳ ጊዜ እንዲጠፋ የሚያደርጉ ሰዎችን ታቅፎ መጓዝ ከተጠያቂነት አያድንም::
የኢሳት ጋዜጠኞች በሃገር ውስጥ እና በውጪ ሃገር የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶችን ወደ አንድነት እና የጋራ አጀንዳ እንዲመጡ መስራት ሲገባቸው እየከፋፈሉ የህዝብ የለውጥ ጥያቄ እና የነጻነት ጥማት እንዲዘገይ አድርገዋል::በሃገር ቤት የሚገኙ ፓርቲዎችን አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ በማደረግ በየፕሮግራሞቻቸው እኩልነትን ባላስተናገደ መልኩ በመዝለፍ እጅግ አሳፋሪ የሆነ የጋዜጠኝነት ስራ ስውርተዋል::በስሜት የሚነዱ ጥቂቶች የህዝብ ቤት ይሆናል የተባለውን ኢሳትን የራሳቸው የስሜት ሃሳብ መጋለቢያ አድርገውታል::በውጪ ሃገር የሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶችን በማግለል የአንድ የፖለቲካ ድርጅት ስም ገኖ እንዲወጣ ተግተው ሲሰሩ በተግባር እያየን ነው::ስለዚህ ኢሳት የኔ ነው እስካልን ድረስ የኢሳት ጉዳይ ይመለከተናል እንዲታረምም ሂስ የመስጠት መብታችን የተጠብቀ ነው::ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ብዙ ማለት ይቻል ነበር ግን የኢሳት ቦርድ ሁኔታውን አይቶ ሊያስተካክል ይገባል::
መጓተቱ ይቅርና ግማሽ መንገድ መጥተን እንቀራረብ፡፡ Eyasped Tesfaye
መታሰር ክፉ ነው፡፡ የታሰረ ሰው ተስፋው ሁሉ ውጪ በቀረው ታጋይ ላይ ነው፡፡ የሀብታሙ አያሌው እና የየሺዋስ አሰፋ ልብ የሚነካ ተማፅኖ አእምሮዬን ሁሉ ተቆጣጥሮታል፡፡ ‹‹እባካችሁ ተባበሩ›› ‹‹እስቲ ቀረብ ብላችሁ ተነጋገሩ›› በየንግግራቸው መሀል እየደጋገሙ የሚያስተላልፉት መልዕክት ነው፡፡ ‹‹እኛ እኮ ከዛሬ ነገ ለውጥ መጥቶ ኑ ውጡ እንባላለን ብለን ነው የምንጠብቀው……በተናጠል ድርጅቶች ያላቸውን አቅም የምናውቀው ነው….እባካችሁ ተባበሩ›› ሀብታሙ አያሌው፡፡
አንድነት እና ሰማያዊ በትብብሩ ውስጥ አብረው መስራት ለምን አይችሉም???
አብረው መስራት የማይችሉበት ምንም ምክንያት ፈልጌ ላገኝ አልቻልኩም፡፡ ከሁለቱም በኩል በቀና እና ለውጥ ፈላጊ ልቦና ተቀራርቦ መነጋገር ከተቻለ የሚያግዳቸው ምንም ነገር አይኖርም፡፡ ሀብታሙ አያሌው እና የሺዋስ አሰፋ ቂሊንጦ ሲገቡ ተግባብተዋል፡፡ እኛም ነገ ቂሊንጦ ከገባን መግባባታችን አይቀርም፡፡ ከዛም እንደ የሺዋስ እና ሀብታሙ ውጪ ያለውን ሰው ተባበሩ እያልን እንመክራለን፡፡ በተስፋ ምግብም መንፈሳችንን በሂወት ለማቆየት እንጥራለን…..ከንቱ ልፋት፡፡
ወህኒ ሳንወርድ አሁን ላይ መግባባት ስለምን ይሳነናል???
አሁን ባለው ነባራዊ እውነታ አንድነት እና ሰማያዊ በትግል ስልታቸው ላይ መጠነኛ ልዩነት ያላቸው ይመስላል፡፡ ነገር ግን እንዲህ አይነት መጠነኛ ልዩነት አይደልም በሁለት ፓርቲ መሀል ይቅርና በአንድ ፓርቲ ውስጥም ባሉ ግለሰቦች መሀል የሚከሰት ነው፡፡ አንድነት ያለምንም ቅድመ ሁናቴ ምርጫ ውስጥ እገባለሁ ብሏል፤ ሰማያዊ ደግሞ ቅድመሁናቴ አስቀጧል፡፡ ነገር ግን ከምርጫ ሂደት ውስጥ ወጥቻለሁ ያለ የለም፡፡ በመሆኑም ምርጫውን ያለቅድመ ሁናቴ የሚሳተፈውና ቅድመሁናቴ ያስቀመጠው አካል የምርጫ ምህዳሩን ለማስፋት፤ ምርጫው አልሆን ካለ ደግሞ ለህዝባዊ እምቢተኝነት ተባብረው የማይሰሩበት ምክንያት አይታየኝም፡፡
አንድነት ወደ ትብብሩ ያልመጣበት ምክንያት ከመድረክ ከወጣሁ በኋላ እንደገና ያለጥናት በፍጥነት ወደ ሌላ ትብብር ውስጥ መግባት የለብኝም የሚል ነው፡፡ ነገር ግን አንድነት ፓርቲ ውህደት ከሆነ በማንኛውም ጊዜ ዝግጁ ነኝ ይላል፡፡ ለመዋሀድ ዝግጁ የሆነ አካል ደግሞ ለመተባበር ይከብደዋል ብዬ ማሰብ ያቅተኛል፡፡ በመሆኑም ለመተባበር ዛሬ ነገ ሳይል ቢወስን ደስ ይለኛል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ትብብሩ ውስጥ ያሉት ፓርቲዎች ግማሽ መንገድ ሄደው አንድነትን መቀበል አለባቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ አንድነት ካለው ድርጅታዊ አቅም አንፃር ታይቶ የትብብሩ ምክር ቤት አባል ብቻ ሳይሆን የትብብሩ ስራ አስፈፃሚም ውስጥ ተወካዩን እንዲያስገባ ሊፈቅዱለት ይገባል እላለሁ፡፡ ይህ ደግሞ ለአረናም ሆነ ለኦፌኮ የሚሰራ ይመስለኛል፡፡
በዚህ መልኩ ተባብረው የሚሰሩ ከሆኑ ምናልባትም አሁንም ቢሆን ጊዜው አረፈደም እና ሁሉም ፓርቲዎች በስምምነት በአንዱ ፓርቲ የምርጫ ምልክት ሊወዳደሩ ይችላሉ፡፡ ይህ እንኳን ባይሆን በእጩ አቀራረብ ላይ እየተመካከሩ ድምፅ የማይነጣጠቁበትን መንገድ መፈለግ ይችላሉ፡፡ ምርጫው ነፃ እስካልሆነ ድረስ አላስፈላጊ ነው ብለው ካሰቡም በጋራ ህዝቡን ለህዝባዊ እምቢተኝነት የሚያነቁበትን እና የሚያደራጁበትን መንገድ መፈለግ ይችላሉ፡፡
በቅርቡ አንድነት ፓርቲ በተለያዩ ክፍለሀገሮች ሰልፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ትብብሩም ሁለተኛ ዙር መርሀግብሩን አውጥቷል፡፡ እነዚህን ሁለት እንቅስቃሴዎች ማቀናጀት አስፈላጊ ነው፡፡ ለዚህም ከእንቅስቃሴዎቹ በፊት ፓርቲዎቹ አንዳች ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸው፡፡
የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እኔም ሆንኩ ሌሎች ጓዶች መታሰራችን እንደማይቀር አውቀዋለሁ፡፡ እስር ቤት ከገባሁ በኋላ ግን ውጪ ያለውን አካል እንዲተባበር መለመንን አልሻም፡፡ ‹‹ቀን ሳለ ሩጥ›› እንዲሉ ዛሬ ውጪ እያለሁ ፓርቲዎቹ እንዲተባበሩ ሙሉ ጊዜየን ሰጥቼ እሰራለሁ፡፡ ሌሎችም እንዲሰሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
ኢሳትና አንድነት
ኢሳት የሚድያ ተቋም በበርካታ ሽህ ማይሎች ርቀት ላይ የሚገኝ ላገር ያስባል ተብሎ የተቋቋመ ድርጅት ነዉ፡፡እንደሚለዉ የኢትዮጵያዉያን አይንና ጀሮ ይሆናል ብለንም አስበን ነበር፡፡የኢድቶርያል ቦርዱን ፖሊሲ ብናዉቀዉ ደስ ባለን፡፡መስራቾች ብዙ ለፍተዉና ሩቅ አልመዉ እንዳቆሙት ይታመናል፡፡አንድነትን በፖሊሲ ደረጃ እየታገሉት ከሆነ ያሳዝናል፡፡የሁለትና ሶስት ጋዜጠኞች የግል ፍላጎትና ጨዋታ ከሆነም እናያለን፡፡
እንዳለመታደል የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ሁሉ ባለብዙ ሚድያ፤ባለ ሙሉ ጦርና(ፌደራል ፖሊስ) ያገር ሃብት ይዞ ለሚያፍነን ፀረ ዲሞክራሲና አንደነት የሆነዉን ስረኣት እየታገልን ለዚህ ድርጊት የምንሸበር አንሆንም፡፡እነዚህ ጋዜጠኞች ግን የአንድነትን አወንታዊ የሰላማዊ ትግሉን እንቅስቃሴ፤የተመዘገበዉን ዉጤት ሳይሆን የእስርና እንግልት እንደሚያጎሉት እናዉቃለን፡፡ እኛ የጣልነዉን ወይ የወደቀብንን በማንሳት የኢቲቪን ስራ ሲደግሙብንም እንታዘባለን፡፡ይህንንም ከዚህ በፊት በሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት ግዜ በግብረሃይሉ ተገምግሞኣል፡፡
ብሶታችንን ብቻ ሳይሆን ያሉንን አማራጮች፤ስልተና እስትራተጂክ ግባችንን እንድናብራራ ቅርብ ያለዉ ሲዘጋብን እነሱዉ ቢከፍቱልን መላካም ነበር፡፡የሚፈልጉን ለብሶት ከሆነ ህዝቡ በቅርብ ስለሚያዉቀዉ ብዙም አያምሩንም፡፡ህዝቡ እንዲደራጅና ህገ መንግስታዊ መብቱን እንዲጠቀም ጉልበት እንዲኖረዉ ቢያስተምሩ በጎ ነበር፤እንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራርና የፓርላማ አባል ከሌላ ፓርቲ የፓርላማ አባልና የግዜዉ ባለስልጣን ተጨባበጠ ብሎ ክስ ግን ያስገምታል፡፡አንድነት የተከበሩ ዶ/ር ነጋሶን አምጥቶ መሪ፤እነ ሃብታሙ አያሌዉን ከፍተኛ አመራር… ያደረገበትን አገራዊ ፋይዳ የዘነጉት ይመስለኛል፡፡ዛሬም የአንድነት በር ወንጀለኛ ላልሆነ የኢህአዴግ አባልና ኢትዮጵያዊ ሁሉ በሩ ክፍት ነዉ፤ለዉይይትም ለትግልም፡፡
ሚድያ ናቸዉና ከሰራን ይዘግባሉ፡፡አንድነቶች በያለንበት ወደ ስራ!!! ሰላማዊ ለዉጥ እንዲመጣ የበኩላችሁን ገንቢ አስተዋፅኦ ለምታደርጉ የየትኛዉም ሚዲያ አይነት አካለት ግን በግሌ ክብር እሰጣለሁ፡፡ኢሳትና አንድነት ባላንጣም፤ወዳጆችም ሊሆኑ አይችሉም፡፡
ለለዉጥ እንደራጅ!!
የአምባሰደሩ የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉብኝት ተከትሎ የእንግሊዛዊ ቱሪስት የተቀነባበረ ግድያ ድንጋጤ ፈጥሯል::

የባህር ዳሩ ገዳይ ካለምንም ጥያቄ በቀጥታ ለፖሊስ እጁን ሰቷል:: Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ባሳለፍነው ሳምንት በአዲስ አበባ ካሳንቺስ ከቀድሞ ስድስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ጀርባ ከሚገኘው ድብቅ የደህንነት እስር ቤት ውስጥ በመገኘት በከፍተኛ የሴኩሪቲ ጥበቃ የነጻነት ታጋይ የሆነውን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር Greg Dorey እንዳነጋገሩ ሲታወቅ ከአንዳርጋቸው ጋር ያደረጉትን ቆይታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ባይገኝም በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሲገልጹ የኤምባሲው ምንጮች እንዳሉት ስለ አንዳርጋቸው መረጃ ያላቸው ለስርአቱ ቅርብ የሆኑ ክፍተኛ የደህንነት አባላት እና የአንድ ብሄር ተወላጅ የሆኑ አንድ ቋንቋ ተናጋሪዎች እንደሆኑ ገልጸዋል::እንዲሁም አመነስቲ ኢንተርናሽናል አንዳርጋቸውን በተመለከተ ከታፍነ 6 ወር መሆኑን ገልጾ ሁኔታው አሳሳቢ ነው ሲል ለእንግሊዝ መንግስት አቤት ያለበተን መግለጫ ባሳለፍነው ሳምንት መግለጫ አውጥቶ ነበር::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ በባህር ዳር ከተማ ውስጥ ድብ አንበሳ እየተባለ በሚጠራው ሆቴል አካባቢ አንድ አርሶ አድር ታጣቂ ሚሊሻ በሚመስል ጸጉረ ልውጥ ሰው የእንግሊዝ ዜግነት ያለው ቱሪስት መገደሉ ታውቋል::የአምባሰደሩ የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉብኝት ተከትሎ የእንግሊዛዊ ቱሪስት መገደል ድንጋጤ ፈጥሯል::ገዳዩ ለግድያው እንደተዘጋጀበት በሚያስታውቅ መልኩ በአከባቢው አድብቶ ሲጠባበቅ የነበረ እና ወዲያው እንግሊዛዊውን እንደገደለው ለፖሊስ ያለምንም ጥያቄ እጁን ሰቷል::በአከባቢዉም የታተቁ ፖሊሶች የነበሩ ሲሆን ግድያው ሲፈጸም ምንም ያደረጉት መከላከል አልነበረም::ግድያው የተቀነባበረ ነው ሲል የባህር ዳር ህዝብ እየተናገረ ነው::
“..እጩ ኣሸባሪ..” ሆንኩላቹ…! አምዶም ገ/ስላሴ
እኔ የዓረና-መድረክ ኣባል ከመሆኔ የተነሳ በምርጫ 2007 ዓ/ም ለፌደራል ወይም ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ እንደምሆን የራሴ እቅድ ይዤ ነበር፤ እናንተም በተመሳሳይ ግምት እንደምትጠብቁ እገምታለው። ኣሁን እየሆነ ያለው ግን “…ለምሳ ያሰቡን ለቁርስ ኣደረግናቸው..” ዓይነቱ የጓድ ሊቀ መንበር መንግስቱ ዓይነት ተግባር ህወሓት መራሹ የትግራይ መንግስት እጩ “ሽብርተኛ” ኣድርጎው ኣጭተውኛል። እም በኣቅሚቲ “..የኣሸባሪነት..” ካባ ለብሼ ቅሊንጦ ወይም […]
የፀጋዬ በርሔ ቪላ ተሸጠ – ከኢየሩሳሌም አረአያ
የቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንትና በኋላ የፌዴራል ደህንነት ዋና ባለስልጣን የሆኑት የሕወሐት ፖሊት ቢሮ ባል አቶ ፀጋዬ በርሄ በመቀሌ ልዩ ስሙ “አፕርታይድ መንደር” ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ያስገነቡት ባለሁለት ፎቅ ዘመናዊ ቪላ መሸጣቸውን ታማኝ ምንጮች አረጋገጠዋል። 10 ሚሊዮን ብር ገደማ እንደፈጀ የሚነገርለት የአቶ ፀጋዬ ቪላ ለአንድ ባለሃብት 25ሚሊዮን ብር እንደተሸጠ ቢነገረም በትክክል የተሸጠበትን ዋጋ ማወቅ እንዳልተቻለ ምንጮቹ […]
የምርጫ ፓርቲዎች ህዝቡን ወደምርጫ ሲያመጡ ለመጨረሻው ድምፅ ማስከበርም ስራ ህዝቡን ያመጡታል፡፡
የምርጫ ፓርቲዎች ህዝቡን ወደምርጫ ሲያመጡ ለመጨረሻው ድምፅ ማስከበርም ስራ ህዝቡን ያመጡታል
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት የአማርኛ ዜና – ዲሴምበር 24, 2014
የፕሮግራም መግለጫ
ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡
ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡
የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡
ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና
ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና
ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ
ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት
ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)
ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና
ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡
ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡
የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡
ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡
ኤም አይ 35 ተዋጊ ሄሊኮፕተር ይዘው የጠፉት አብራሪዎች ቤታቸው ተፈተሸ
ታኀሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የአየር ሃይል ደህንነቶች ወደ ጠፉት አብራሪዎች ቤት በድንገት በመሄድ ፍተሻዎችን ያካሄዱ ሲሆን፣ በቤቶች ውስጥ የተገኙ ሰነዶችን፣ የበረራ ማኑዋሎችን፣ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎችን፣ ትጥቆችንና ሌሎችም ቁሳቁሶች ወስደዋል። ከደህንነቶች ጋር ምንም አይነት ፖሊስ ያልነበረ ሲሆን፣ ደህንነቶች ፍተሻውን ለማካሄድም የፍርድ ቤት ማዘዣ አላሳዩም። የመከላከያ ሰራዊት ባወጣው መግለጫ ሁለቱ …
አንድ እንግሊዛዊ ባህር ዳር ውስጥ ተገደለ
ታኀሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የክልሉ ወኪላችን እንደገለጸችው ማንነቱ በውል ያልታወቀው እንግሊዛዊ ጧት ላይ ባዶ እጁን ወደ ጊዮርጊስ አካባቢ ሲንቀሳቀስ በአንድ የሚሊሺያ አባል ተገድሏል። ገዳዩ መሳሪያ በመያዝ ድብ አንበሳ እየተባለ በሚጠራው ሆቴል አካባቢ ሟቹን ሲጠባበቀው እንደነበር ዘጋቢያችን ያነጋገረቻቸው ሰዎች ገልጸዋል። በሆቴሉ አካባቢ ጫማ በመጥረግ የሚተዳደሩ ነዋሪዎች ገዳዩ መሳሪያውን ይዞ ከእነሱ ጋር …
በሽብርተኝነት መዝገብ የተከሰሱት ፍርድ ቤት ቀረቡ
ታኀሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብርተኝነት ወንጀል የተከሰሱት የሰማያዊ፣ የአንድነትና አረና አመራሮች ከሌሎች 6 ተከሳሽ ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ልደታ በሚገኘው 19ኛው ወንጀል ችሎት ቀርበው በእስር ቤት ውስጥ ስለሚደርስባቸው እንግልትና የደህንነት ስጋት ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አሰምተዋል። የተከሳሾች ቤተሰቦች እስረኞችን ለመጠየቅ በሚሄዱበት ጊዜ በተለየ መዝገብ መመዝገባቸውን በመቃወም ለፍርድ ቤት ባሰሙት …
የደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት ችግራቸውን በቶሎ እንዲፈቱ ተጠየቁ
ታኀሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደቡብ አፍሪካው መሪ ጃኮብ ዙማ ደቡብ ሱዳናዊያን ለ2 ሚሊዮን ህዝብ መፈናቀል ምክንያት የሆነውን ጦርነት በድርድር እንዲፈቱ ጠይቀዋል። በአዲስ አበባ የሚካሄደው የሰላም ድርድር ውጤት ለማምጣት በተሳነው በዚህ ወቅት፣ ደቡብ አፍሪካ ተጨማሪ ግፊት እያደረገች ነው። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሁለቱ ተፋላሚ ሃይሎች ችግሮቻቸውን የማይፈቱ ከሆነ ማእቀብ ይጣልባቸዋል ሲሉ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
የደንጉ ትኩሳት መከላከያ ግኝትና ችግሩ
የተለያዩ አራት ዓይነት የደንጉ ትኩሳት በሽታ አምጭ ተሐዋሲዎችን ለመከላከል የተገኘዉ መድሐኒት በሽታዉን ለማምከን አቅም እንዳለዉ ቢገለፅም፤ በክትባት መልክ ለተጠቃሚ ለማድረስ የሚደረገዉ ጥረት ግን ብዙ መሰናክል ተደቅኖበታል።
የገና ዋዜማ በቫቲካን
ርዕሰ-ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ ደግሞ የሐይማኖት መሪዎች፤ ፖለቲከኞችና ዲፕሎማቶች በሚገኙበት ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ቃለ-ቡራኬ ይሰጣሉ።
የኢትዮጵያ ምርጫ ዝግጅት
የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርጫ በመጪው ግንቦት ወር ይካሄዳል። ምርጫውን በበላይነት የሚያስፈጽመው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች በዝግጅት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በባህር ዳር ከተማ አንድ እንግሊዛዊ ቱሪስት ከአንድ ግለሰብ በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አለፈ

በባህር ዳር ከተማ አንድ ኢንግሊዛዊ ቱሪስት ከአንድ ግለሰብ በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አለፈ::በባህር ዳር ከተማ አንድ ኢንግሊዛዊ ቱሪስት ከአንድ ግለሰብ በተተኮሰ ጥይት ህይወቱ አለፈ።ድርጊቱ የተፈፀመው ዛሬ ረፋድ 4 ሰዓት ከ30 ደቂቃ ላይ ነው።በግድያው የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ የወንጀል ድርጊቱ እየተጣራ ነው ። የሟቹም አስክሬን በሆስፒታል እንደሚገኝ ተመልክቷል።
ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው ነበረ:: የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ ::
ሻምበል ሳሙኤል መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ሪፖርተር ![]()
” አብራሪዎቹ ከፖለቲካ ራሳቸውን ገለልተኛ ያደረጉት ባለው መንግስት ላይ ያላቸውን ጥላቻ እና ቂም ያመለክታል::በአንድ ሃገር የደህንነት ህዝባዊ ጥበቃ ስራ ላይ የተሰማራ ወታደር ከአምባገነኖች ፖለቲካ ራሱን ማግለሉ ህዝባዊ ተቆርቋሪነቱን ያሳያል:: ” Minilik Salsawi
ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው ነበረ::
የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ ::
ሪፖርተር :- የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡
ከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡
አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡
ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን ፀጋ ብርሃን ግደይ ጋር በኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር የዘወትር የልምምድ በረራ ለማድረግ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ድሬዳዋ ከሚገኘው የአየር ኃይል ቤዝ እንደተነሱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዋና አብራሪው ከአጭር ጊዜ በረራ በኋላ የበረራ ከፍታውን በመቀነስ ወደ ኤርትራ በማቅናት ሔሊኮፕተሩን አሰብ ማሳረፉን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
መከላከያ ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ ተዋጊ ሔሊኮፕተሩን ዋና አብራሪው ይዞ ወደ ኤርትራ መኮብለሉን አምኗል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው ዋና አብራሪው ቴክኒሺያኑንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን አስታውቋል፡፡
ሔሊኮፕተሩ ባለፈው ዓርብ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ጀምሮ በመደበኛ የሥልጠና ልምምድ ላይ እንደነበር ጠቅሶ፣ ሔሊኮፕተሩ ከግንኙነት ውጪ በመሆኑ ሠራዊቱ በአካባቢው ማኅበረሰብና አጋሮች ለተከታታይ ቀናት ፍለጋ ሲደረግለት መቆየቱን አትቷል፡፡ ‹‹ሆኖም ሔሊኮፕተሩ በከሀዲው ዋና አብራሪ አማካይነት ቴክኒሻንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፤›› ብሏል፡፡ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች ዋና አብራሪው የሔሊኮፕተሩ አዛዥ በመሆኑ የትም ወስዶ ሊያሳርፈው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
‹‹ረዳት አብራሪው ጀማሪ ነው፡፡ የበረራ ቴክኒሺያኑ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን መከታተል ነው፡፡ ዋና አብራሪው ረዳት አብራሪውና ቴክኒሺያኑ እያወቁም ወይም ያለነሱ ዕውቅና የፈለገበት ወስዶ ሊያሳርፍ ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው መክረማቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር መትረየስና ተወንጫፊ ሮኬቶች የተገጠሙለት ዘመናዊ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ነው፡፡ ከኋላው ስምንት ወታደሮችን ወይም ሁለት የቁስለኛ አልጋዎችን መያዝ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኤምአይ 17 እና ኤምአይ 8 የትራንስፖርት ሔሊኮፕተሮች ሲኖሩት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸው በደርግ ጊዜ የተገዙ ኤምአይ 24 ሔሊኮፕተሮችን ነበር፡፡ በግንቦት 1990 ዓ.ም. የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲጀመር አሥር ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተሮች የተገዙ ሲሆን፣ በጦርነቱ ወቅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡
የ1997 ዓ.ም. ሦስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተነሳውን ግርግር ተከትሎ ሁለት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች (ሻምበል አብዮት እና ሻምበል በኃይሉ) አንድ ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ይዘው ወደ ጐረቤት አገር ጂቡቲ መኮብለላቸው ይታወሳል፡፡ ብዙም ሳይቆይ የጂቡቲ መንግሥት አብራሪዎቹን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግሥት የሰጠ ሲሆን ሔሊኮፕተሩንም መልሷል፡፡ አብራሪዎቹ የጦር ፍርድ ቤት ቀርበው በአሁኑ ወቅት በእስር እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ወቅት በቤላሩስ በሥልጠና ላይ የነበሩ ሰባት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የኤስዩ 27 ተዋጊ ጀት አብራሪዎች ከድተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ አብራሪዎቹ በተለያዩ የምዕራብ አገሮች ጥገኝነት ማግኘታቸው ይነገራል፡፡
ቀደም ሲል ሻምበል ተሾመ ተንኮሉ የተባለ የአየር ኃይል ባልደረባ በ1995 ዓ.ም. ኤል 39 የተሰኘ የመለማመጃና ቀላል የውጊያ አውሮፕላን ለልምምድ በረራ ከመቀሌ ቤዝ ይዞ እንደተነሳ ወደ ኤርትራ ኮብልሎ ነበር፡፡
እስከ ማክሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ምሽት ድረስ የኤርትራ መንግሥት ስለተጠለፈው ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጠም፡፡
source Reporter ሪፖርተር 
የፍቅር ዳገት (ከአርአያ ተስፋማሪያም)
ከአርአያ ተስፋማሪያም
ፍቅረኞቹ አሁን የሚኖሩት አሜሪካ ነው። ተማሪ እያሉ ሳያስቡት ልጅ አፈሩ። የሁለቱን ፍቅርና መዋደድ እንዴት እነደነበረ የሚያውቋቸው ምስክር ናቸው። 6 አመት በመዋደድ የዘለቀው ፍቅራቸው በድንገት እሷ ከአገር በመውጣቷ ለጊዜው ተቋረጠ። የምትፅፋቸው ደብዳቤዎች ውብና አስደናቂ ነበሩ። ልክ እንደውጫዊና ውስጣዊ ውበቷ አይነት ነበሩ። በተለይ «..ውድ ፍቅሬ ቅድሚያ ግን እወቅልኝ፤ ዛሬም ልቤ አንድ! ፍቅሬም ዘላለማዊ ወረት የሌለበት እንደሆነ! ..ብቸኝነት ጅራፍ ነው! የእሳት ጅራፍ!…የዚህ አለም ኑሮ አክትሞልኝ ፅዋዬን እስክጐነጭ ፣ ተራ ደርሶኝ አንደበቴ ተሸብቦ እጅና እግሬ እስከሚታሰር ለአንተ ያለኝን ጥልቅ ፍቅርና መውደድ ከመግለፅና ከመተግበር ወደኋላ አልልም። አንተ ከማጣ (ልብ ተነጥቆ መኖር ከተባለ) ሞቴን እመርጣለሁ..» የሚለው አስደማሚ ደብዳቤዋ ይጠቀሳል። ከ4 አመት በኋላ ስትመጣ ግን እሱ በማያውቀውና ባላደረገው ነገር ቤተሰብ በጠነሰሰው ሴራ ለመለያየት በቁ። በተደጋጋሚ ቀርቦ ሊያስረዳት ቢሞክርም ለማዳመጥ እንኳ ፈቃደኛ ሳትሆን ቀረች። ልጃቸው ልታስታርቅ ብዙ ጥራለች፤ ግን አልሆነም ..ሌላ ሰው አፍቅራ አሜሪካ ገባች። እሱም ልጁን ይዞ ሄደ። ልጇን ለማየት እሱ ወዳለበት ከተማ ስትመጣ ሁሉንም ነገር አስረዳት። ታማኝ ሆኖ ለ4 አመት እንደጠበቃት አስረዳት። በጣም ተፀፀተች።..ጊዜው ግን አልፎ ነበር። ..በቅርቡ ልጅ መውለዷን ሲሰማ ሆስፒታል ድረስ በመሄድ ጠየቃት። የልጇን ግንባር ስሞ « እንኳን በሰላም ተገላገልሽ..ደስ ይበልሽ!» አላት። አንገቷን እንዳቀረቀረች ነበር። …እሱ አንድ እመነት አለው፤ ያፈቀርከውን ሰው ስትለያየው መጥፎውን የምትመኝ ከሆነ..መጀመሪያውኑ ፍቅር አልነበረህም ማለት ነው!..ይላል።..ደግሞም ምንም ክፋት የማታውቅ መልካም ሴት መሆኗን ይመስክርላታል።….ይህ እውነተኛ ታሪክ የእኔ ነው፤….ባለቷሪኳ ደግሞ የኢየሩስ እናት…
«..ለአይኔ ማመን ያቃተኝ ታላቅ ነገር ዛሬ ተከሰተ – ደብዳቤህ። ተመስገን አምላኬ!
በስራ የዛለ ሠውነቴ ከእረፍት አስበልጦ ከአንተ ሊያወጋ የተወሰኑ ረድፎችን መጓዙን አይኖቼ አስተዋሉ። ስቀጥል፥ ከምንም በላይ በሀገርህ ላይ ሠላምህን፣ በቤትህ ውስጥ የሠከነ ሕይወትን፣ ከሰዎች ጋር መልካም ግንኙነትን፣ ለፈጣሪህ ቅን ልቦናን፣ ለቤተሰብህ መታዘዝን፣ እምነት ማተብህን ማጥበቅን፣ ለሰውነትህ ምቾትን፣ ለአይምሮህ መረጋጋትን፣ በስራህ አስተዋይነትን፣ በማህበራዊ ህይወትህ ጥሩ ግንኙነትን፣ በሰዎች ዘንድ ተወዳጅነትን፣ እንዲያድልህ ፥ ለፈጣሪዬ – ለፈጣሪህ፣ ለአምላኬ – ለአምላክህ፣ ፃድቅም ባልሆን ለሃጢያተኞች ሲል መከራን ለተቀበለ፣ በበደሉት መጠን ቂም ለማይዝ፣ በጠሩት ጊዜ ለሚሰማ ለሕያው አምላክ – በልኡል መንበሩ ተቀምጦ አዳርህን – አዳሬን፣ ውሎህን – ውሎዬን፣ ለሚቃኝ ለሚመለከት፣ እውነተኛ ሚዛንና ፍርድን በእጁ ለያዘ ፈጣሪ አምላክ የእጁን በረከት እንዲዘረጋልህ የዘወትር ፀሎቴ ነው!!
ውድ ፍቅሬ፥ ቅድሚያ ግን እወቅልኝ፤ ዛሬም ልቤ አንድ፣ ፍቅሬም ዘላለማዊ ወረት የሌለበት እንደሆነ!! በቀዘቀዘና በሰከነ አነጋገር ክንድህን ተንተርሼ….ጠረንህን እያሸተትኩ ..አ. ፈ..ቅ..ር..ሀ..ለ..ሁ…የምልህን! በቀን የሰው አይን፣ በጠፍ ጨረቃ ጋኔን ሳልፈራ ..አንተን እያልኩ ድፍን ሰፈርህን እያሰስኩ « ፍቅሬን.. ውለዱ» እያልኩ ሳስሥህ የምከርመውን፤ ይህን ስፅፍልህም ወደኋላ በትዝታ እየተቃጠልኩ ትርሃስ ላይ ተደፍቼ እያነባሁ መሆኑን ብታየኝ.. “አዝንልሻለሁ” ከምትለኝ በላይ ዛሬ ታዝንልኝ ነበር። የሚያባብለኝ የለ፤ የሚያፅናናኝ። ብቻዬን ልብህን እያሰብኩና እየፈለኩ፣ እንዲያጫውተኝ እየዳሠስኩ – ፍቅርን ከትርሃስ ጋር በእንባ ሌሊቱን በመገላበጥ አነጋለሁ፤ ናፈቅከኝ!!…በካፊያ ዝናብ ከአንተ ጋር መሆን ምን ያህል እንደሚያስደስተኝ አንተም ታውቃለህ፤ ምን ብዬ ልንገርህ!?…ቢያንስ ያንተ ይሻላል- ቤተሰብን አይቶ መፅናናት ቀላል ነገር እንዳይመስልህ!! ብቸኝነት ጅራፍ ነው፤ የእሳት ጅራፍ!!!..ከስራ መልስ አረፍ ባልኩ ቁጥር ቀልቤ አዲስ አበባ….ሰፈር ልቤ ከአንተ ጋር በምናብ ሲጨዋወት ያመሻል።
« …የምወድህ ፍቅሬ፥ አጀማመራችን እኮ ብንተማመን – ልንፋቀር፣ ብንዋደድ ልንዛለቅ፣ ብንተሳሰብ ልንስማማ፣ ብንከባበር ላንናቆር፣ ብንቀያየም ላንለያይ ነበር። ታዲያ ዛሬ ማዶና ማዶ ሆነን እየተሰቃየን ተግባብተን ላንስማማ በየራሳችን ሃሳብ እየተጓዝን የፍቅራችንን መንገድ አጣመምነው። ሃላፊነቱን በእኔ ላይ ብቻ እንደማትጥልብኝ አምናለሁ፤ እንዲሁም የጥፋተኝነትን ፅዋ። ካጠፋሁ ይቅርታ! ግን ጥፋቴ ምን እንደሆነ አልታየኝም። እዚህ ያለሁበትን አጣብቂኝና ፈተና፣ ስቃይ፣ ችግር፣ መከራ ብትመለከት እንኳን ቅያሞት ሃዘን ይገልህ ነበር። እኔ አንተን የማልቀየምህ ለምን መሰለህ?..ሁሉን ነገር ስለማታየው፣ የስደትን ኑሮ በሰው ሃገር ስላልተረዳህልኝ፣ እኔም ኢትዮጲያ እያለሁ እዚህ ችግር ያለ ስለማይመስለኝ፣ አንተም ከእኔ የተለየ አስተሳሰብ ስለሌለህ፥ ለዚህ ነው ብዙም ያላመረርኩብህ። ተስፋ ነበረኝ ከአንድ ከ8 ወራቶች በኋላ አይንህን የማየት፤ ሁሉን ነገር ተወያይተን አምላካችንን በመሃከላችን አኑረን ቃሌን ልሰጥህ፣ ቃልህን ልቀበልህ!! በቃ ተስፋዬ ተሟጠጠ፤ የጓጓሁለትም የመምጫዬ ጊዜ አጠራጠረኝ። ገላዬ እኮ ከምንም በላይ ይናፍቅሃል! እውነተኛ ፍቅር በልቤ ስለመኖሩ መሀላና ምስክር የምትሻ አይመስለኝም። እወድሃለው እኮ! አልተለወጥኩም! ኑሮ አስመርሮኝ፣ ጤና ማጣት ማንነቴን እየተፈታተነ መኖር ስላስጠላኝ እንጂ በአንተም የጨከነ አንጀት ኖሮኝ አይደለም። አንተን ከማጣ ፍቅርህን በልቤ እንደሰነቅኩ ወደ መቃብሬ መውረድን እመርጣለሁ!!..የማይካድ እውነታ ተለያይተን ላንረሳሳ ትልቅ ምሰሶ የብረት ማገር በመካከላችን ጋርደን (ቃልን) በትዝታ እየተንገላታን ማዶና ማዶ ሆነን <ነበረን> መጨዋወት ከጀመርን ሁለት አመታት ተቆጠሩ። ወደ ኋላ ትንሽ ልመልስህ፥ በአብሮነት የፍቅር ጊዜያችን በአንተ ያለወጥኩት ፍጥረት አልነበረም፤ ቢኖር እንኳ አንድ እናቴ ብቻ ነች። ከተጣላኸው ተጣልቼ፣ ከተቀየምከው ተቀይሜ፣ የወደድከውን ወድጄ፣ ያቀረብከውን አቅርቤ፣ አንተን መስዬ ሣይሆን ሆኜህ አብሬህ ዘልቄ ነበር ፍፃሚያችን ያምር መስሎኝ – በተስፋ ጓጉቼ!! ከሁሉ ጋር እንደ ሺህ ዘመን የርስት ባላጋራ የጐሪጥ ስተያይ ኖሬያለሁ። የፍቅር ሃይማኖተኛ ባህታዊ መሆኔና መገዛቴ ጥሩ ባሪያ ተብዬ ያስመሰግነኛል እንጂ አያስንቀኝም! በጥሩ አፍቃሪነቴም እኮራለሁ እንጂ አላፍርም! አንተም ብትሆን እንደማትጠላኝ አውቃለሁ!..»
« .. ውድ የሆንከው ፍቅሬ ሆይ፥ የዚህ አለም ኑሮ አክትሞልኝ ፅዋዬን እስክጎነጭ፣ ተራ ደርሶኝ አንደበቴ ተሸብቦ እጅና እግሬ እስከሚታሰር፣እስትንፋሴ እስከቆመበት፣ በድኔ ወደከርሰ መቃብር ወርዶ የዘላለም እረፍቱን እስካገኘበት እለት የመጨረሻ ደቂቃና ሰኮንድ ድረስ አንተን ከማድነቅና የሕይወቴ እስትንፋስ መሆንህን ከመናገር ወደኋላ አልልም!! እወድሃለሁ! አፈቅርሃለሁና የሚደርስብኝን ችግር፣ የሚገጥመኝን ፈተና አንተን በማስታወስ ፍቅር ትዕግስቱን ሰጥቶኝ በደስታ ለማሳለፍ የቆረጥኩት ዛሬ አይደለም። ወደኋላ ሳስብ “አንተን አፍቅሬ የተሰቃየሁበት፣ በቤተሰቤ የደረሰብኝ የስድብ ናዳ …ሁሉም ትዝታ ሆኖ፥ እንዳያልፍ የለም አለፈ። ያንተ ፍቅር ግን ምንግዜም በልቤ ውስጥ የማይቀልጥ የዘላለም ሻማውን እንዳበራ ይኖራል። መቼም ቢሆን የማይለወጥ ቃል ኪዳኔ ነው!! ከአምላኬ በታች ያመለኩህ አንተን ብቻ ነው!! ብትጠላኝ ላልጠላህ፣ ብትክደኝ ላልከዳህ፣ ብትርቀኝ ላልርቅህ፣ ብትሰድበኝ ብትንቀኝና ብታዋርደኝ፣ ላልሰድብህ ላልንቅህ ላላዋርድህ፣ ከትእዛዝህ ውጭ ላልወጣ “እሺ” ከማለት በቀር መጥፎ ቃላት ላልሰነዝር..ፍቅር ሸብቦ የያዘኝ የአንተው ምርኮኝ ነኝ!! ልቤ ፍቅርህን ከማሽበልበል ውጭ መርዝ አይተፋም። አንደበቴ ፍቅርህን( አንተነትህን) ከማድነቅ በቀር ሬት አይተፋም!! ፍቅርህ ጣፋጭ ነው!! ቁጣህ አስደንጋጭ – ንግግርህ አስፈሪ፣ ቁልምጫህ አጥጋቢ – ፀብህ መራራ፣ ልብህ የዋህ – አስተሳሰብህ ጠንካራ (አስተዋይ)፣ ተክለቁመናህ ማራኪ – ቁም ነገር አዋቂ፣ አላማህ ተወዳጅ – ለችግር ፈጥኖ ደራሽ፣ በአጠቃላይ አምላክ ሲፈጥርህ ከሁሉም ነገር አድሎሃል። እወድሃለሁ! ልቤ ንፁህ ነው፤ ያንተን ፍቅር ብቻ የሚያስተናግድ!! አንደበቴ ቁጥብ ነው፥ አንተን ብቻ የሚያደንቅ!! ለእኔ ምንጊዜም ቢሆን ውድ ነህ!! ከማንም – ከምንም በላይ አፈቅርሃለሁ፤ እወድሃለሁ!! ”አፈቅርሃለሁ” ለሚለው ቃል መተኪያ ባገኝለትና የልቤን ብገልፅልህ ምንኛ ደስ ይለኝ ነበር መሰለህ!?..
ፍቅሬ ሆይ፥ ሁልጊዜ እሰጋለሁ፣ እጨነቃለሁ። አንተ ከእኔ ጋር የመኖር አላማ የሌለህ ስለሚመስለኝ ኑሮዬ የስጋት፣የጭንቀት፣ የብስጭት ይሆናል። ሌላ ምንም አያሳስበኝም። ደግሞም ከአንተ ተለይቼ ከምኖር (ልብ ተነጥቆ መኖር ከተባለ) ሞቴን እመርጣለሁና አደራ የገደል ላይ ሳር የሆነውን ሕይወቴን ነፍስ ዝራበት፤ በደመነፍስ የሚመራ ሕይወቴን፣ አላማቢስ የሆነብኝን ጭንቅላቴን፣ በጭንቀት የሚሸማቀቅ አካላቴን፣ አዝናናው፣ አበረታታው፣ ደባብሰው፣ ነፍሴ በአንተ ትለምልም፤ ካለአንተ ማን አለኝ፤!? አገር ቤት እያለሁ የሰራህልኝን ውለታ እስከ እለተ ሞቴ የማልረሳው ትልቅ ሸክም ነው። < ሸክም ነው ያለኩህ> ከፍዬ ስለማልጨርሰው ነው!! የእኔ ፍቅር አንድ ነገር ልንገርህ?፤ እኔን የአሜሪካ ኑሮ የሚያስደስተኝ፣ እዚህ ያለው ብልጭልጭ ነገር የሚያዘናጋኝ አይደለም። …አንድ ነገር ልብ በል፤ እየፃፍኩልህ ያለሁት ከሌሊቱ 7፡30 በኢትዮ.ሰዓት አቆጣጠር እንደሆነ እወቅ። ከእንቅልፌ ሠአት ላይ ቆጥቤ ነው በድቅድቅ ሌሊት የምፅፍልህ፤ እንጂ ቀንማ ትንፋሽም የለኝ። ምን ያክል ስለፋ እንደዋልኩ ፈጣሪ አይቷል!! የድካሙ ነገር አይነሳ.. እስቲ ተከድኖ ይቀመጥ፤ ስደትን ያየ ይፍረደኝ!?….ግን ዛሬ ደግሞ ደስ ያለኝ ነገር አንተ ማንንም እንዳልተላመድክ ገለፅክልኝ፤ ጥሩ ጌታ ያፅናህ! እኔስ ፀንቻለሁ በአካልም፣ በልብም፣ በመንፈስም። አምንሃለሁ! ባላምንህ ኖሮ መልስ አልፅፍልህም ነበር። አንተስ ታምነኛለህ?..እንደድሮው?..
ውድ ፍቅሬ፥ መኝታዬ ክፍል ጥግ ላይ ተቀምጬ እንባዎቼ በጉንጬ ላይ እየተሽኳለሉ ዱብ.. ዱብ..ዱብ ይላሉ። ፎቶዎችህን አስተውላቸዋለሁ፤ ድብዳቤዎችህን መላልሼ አነባቸዋለሁ፤ ደግሞ እፅፋለሁ። ልቤ ግን ድም -ድልቅታውን አያቋርጥም፤ የመገናኘት ምኞቴን በደውሉ ያስተጋባልኛል!! ያሳለፍነው እኮ እንኳን በነዚህ አመታት ቀርቶ መቼም የሚረሳ አይደለም፤ አይረሳም። አንተ ትረሳለህ ወይ?..ሰሞኑንማ ከመስሪያ ቤትህ ጀምሮ አዘውትረን እናድርበት የነበረው ..ሆቴል ድረስ ጣፋጩ ትዝታ በአእምሮዬ ይመላለሳል። ትዝ ይልህ እንደሆነ በዛ ሰሞን ፍቅር በዝቶ ቅብጥብጥ ሲያደርገን « ውዴ ፍቅር በዛ፤ ልንለያይ ነው መሰለኝ » ስትለኝ እኔም < እባክህ ፍቅሬ እንደዚህ አትበለኝ?> ብዬ አንገትህ ስር ሽጉጥ የምለው፣ በደረትህ የምንፈላሰሰው፣ አትዩብኝ የምለው አይንህ፣ አትንኩብኝ የምለው እጅህ…አረ ስንቱን…ስንቱን ልዘርዝረው!?…ውድ ነህ፣ እንቁ ነህ!
ውድ ፍቅሬ ሆይ፥ ግን አንድ ነገር የማልደብቅህና ከዚህ በፊት ደግሜ ደጋግሜ የፃፍኩልህ፣ በህልሜም ተደጋጋሚ ነገር ስላየሁ ሰጋሁ። አንተን በርግጥ ልመንህ?..እንዴት ነው ልቤ ያምንሃል፤ ህልሜ ግን አስፈራኝ። ስለዚህም ጉዳይ ገልፀህ ፃፍልኝ። ኩርት ያልክ ሁንልኝ!! ልክ እንደቀድሞህ። እንዲያ ከሆንክ ስመጣ አይኔን ለማየት አታፍርም። ከምንም በላይ ደግሞ ሕሊናህ ነፃ ይሆናል!! ካልሆነ ግን ከእኔ ይበልጥ እራስህን ሰላም ታሳጣለህና ጠንቀቅ፣ ሰቅጠጥ በል!! “ምነው ይህቺ ልጅ ጨቀጨቀችኝ” እንደማትለኝ ነው!?..ፍቅር የወለደው የስጋት ጭንቀት ነውና አትፍረድብኝ። ..ቦሌ ላይ ስትሸኘኝ አንድ ጥያቄ ጠይቀኸኝ ነበር፤ < አንቺ ግን ቃልሽን ጠብቀሽ፣ አስችሎች ሌላ ሳትላመጂ እንገናኛለን? > ስትለኝ እኔም “ራሴን የምፈትንበት ጥሩ አጋጣሚ ይሆናል፤” ብዬህ ነበር። አዎ! አንተን ካላሰብኩ በቀር ገላዬ ፈተናውን በቅጡ ተወጥቷል። በፈጣሪ እርዳታ!! …በብዙ ፈተና ተፈትኜ አለፍኩ፤ ማለፍ ያቃተኝ ግን የልቤን ፈተና ነው። ጊዜ ይፈታዋል!!…አሁን ላበቃ ጥቂት መስመሮች ቀርተውኛል። የደስታ ብስራት ላቋድስህ፤ ከ6 ወራት በኋላ ልመጣ ነው..» አበቃ።…..ይህ እውነተኛ ታሪክ ሲሆን የፍቅር ሴረኞች ለያዩዋቸው። ባለታሪኮቹ….
በነ ሀብታሙ አያሌው የክስ ጉዳይ የተሰየመው ችሎት ‹አስገራሚ› ውሎ ‹‹ዘረፋ›› ተፈጽሞብናል ብለዋል
በነ ሀብታሙ አያሌው የክስ ጉዳይ የተሰየመው ችሎት ‹አስገራሚ› ውሎ
∙ተከሳሾቹ ‹‹ዘረፋ›› ተፈጽሞብናል ብለዋል ∙‹‹ለማን አቤት ይባላል?›› ሀብታሙ አያሌው
በላይ ማናዬ : ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮችን ጨምሮ 10ሩም ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛው ወንጀል ምድብ ችሎት ቀርበው ነበር፡፡ የሰማያዊ፣ የአንድነትና የአረና ፓርቲዎች አመራሮች የሆኑት አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ እንዲሁም አንደኛ ተከሳሽን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች ተሟልተው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል፡፡
ችሎቱ የተሰየመው ታህሳስ 9 ቀን 2007 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ወቅት ተከሳሾች በቀረበባቸው የሽብር ክስ ላይ የሰጡትን መልስ በተመለከተ 7ኛ ተከሳሽ መልስ በዕለቱ ባለማቅረባቸው አሟልተው እንዲቀርቡ ነበር፡፡ በተጨማሪም ተከሳሾች በእስር ላይ ባሉበት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሊጎበኟቸው የሚሄዱ ቤተሰቦቻቸውና ወዳጆቻቸው ወደ እስር ቤቱ ሲገቡ በተለየ መዝገብ እንዲመዘገቡ እየተደረጉ መሆናቸውን ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ስለነበር ይህን በተመለከተ ማረሚያ ቤቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ በታዘዘው መሰረት ማብራሪያውን ለመስማት ነበር፡፡
የተከሳሾች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች በጥየቃ ወቅት በተለየ መዝገብ ይመዘገባሉ የተባለውን አቤቱታ በተመለከተ፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በደብዳቤ መልስ መስጠቱ የተገለጸ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ‹‹ማረሚያ ቤቱ በሰጠው መልስ እስረኞች ከሌሎች በተለየ የደረሰባቸው ችግር የለም›› ማለቱን ገልጾ ይህንኑ መልስ ሙሉ ለሙሉ መቀበሉን አስታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በዛሬው የችሎቱ ውሎ ላይ ተከሳሾች ለየት ያለ አቤቱታ በጠበቆቻቸው በኩል አቅርበዋል፡፡ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ለችሎቱ እንዳስረዱት ደንበኞቻቸው ከሌሎች በተለየ መልኩ ከፍተኛ በደል እየተፈጸመባቸው ነው፡፡ አቶ ተማም አባቡልጉ በታህሳስ 12 ለ13 ቀን 2007 ዓ.ም አጥቢያ ሌሊት ስምንት ሰዓት ጀምሮ ደንበኞቻቸው ላይ ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጎ የግል ማስታወሻዎቻቸው፣ ገንዘብ እና በተከሰሱበት ጉዳይ ላይ እያዘጋጁት የነበረው መቃወሚያና መከራከሪያ ተወስዶባቸዋል ብለዋል፡፡
‹‹ደንበኞቼ ላይ እየተደረገ ያለው ጉዳይ ለህይወታቸውም የሚያሰጋቸው ነው፡፡ በማረሚያ ቤቱ በሌሊት ፍተሻ ያደረጉባቸው ሰዎች ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ‹ህገ-ወጥ› ተግባራት ሲፈጽሙባቸው የነበሩ የፌደራል ፖሊስና የደህንነት አባላት ሰዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ሰዎች ደንበኞቼ ያውቋቸዋል፡፡ ስለሆነም ፍተሻው የተከናወነው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አልነበረም ማለት ነው፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው የተለየ የስም ዝርዝር ተይዞ ከሌሎች በተለየ መልኩ ነው፡፡ ለአብነት ደንበኞቼ አቶ አብርሃ ደስታና በሌላ የክስ መዝገብ የተከሰሰው አብዱራዛቅ አክመድ ላይ የሆነው ከሌሎቹ በተለየ መልኩ ነው፡፡ ፍተሻው ስለት ነገር አልያም ሌላ ህገ-ወጥ ቁሳቁስ ለመያዝ የተደረገ አለመሆኑን ከተወሰዱት ንብረቶች ማየት ይቻላል›› ሲሉ አቶ ተማም ለፍርድ ቤቱ በደንበኞቻቸው ላይ የተፈጸመውን ድርጊት አስረድተዋል፡፡
ይህን በተመለከተ አስተያየት የሰጡት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ በበኩላቸው፣ ‹‹ማረሚያ ቤቱ መንግስት ዜጎች ታንጸው እንዲወጡ ያሰራው ነው፡፡ ይህን አሰራር ለመጠበቅም የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የተለያዩ ስራዎችን ሊሰራ ይችላል፡፡ እየቀረበ ያለው አቤቱታም ከዚህ አኳያ መታየት ያለበት ነው›› ብለዋል፡፡
ጠበቃ ተማም የደንበኞቻቸውን አቤቱታ ከህግ አንጻር ያስረዱ ሲሆን፣ ‹‹በመሰረቱ ፍተሻ ሊካሄድ መቻሉ ላይ አይደለም አቤቱታው፡፡ የተካሄደው ፍተሻ ግን ህገ-ወጥ ነው፤ ምክንያቱም ፍተሻው የተከናወነበት ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ባለው ጊዜ ሳይሆን ሌሊት 8 ሰዓት ጀምሮ ነው፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ነው፡፡ በሌላ በኩልም ፍተሻው በማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች አይደለም የተከናወነው፡፡ በደህንነቶችና የፌደራል ፖሊሶች ነው ፍተሻው የተደረገው፡፡ ይህም ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎቱም ሆነ ብቃቱ እንደሌለው ያሳያል፡፡ ስለሆነም ፍርድ ቤቱ ይህን መሰል ድርጊት የፈጸሙት አካላትና በማን ትዕዛዝ እንደተፈጸመ ምርመራ እንዲካሄድ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን›› ብለዋል፡፡
ጠበቃ ተማም በተጨማሪ ከደንበኞቻቸው ላይ በፍተሻው ወቅት የተወሰዱባቸው ንብረቶችና ማስታወሻዎች እንዲመለሱላቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው አመልክተዋል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ ‹‹የተለየ ከፍተኛ በደል ደርሶብኛል›› በሚል ለፍርድ ቤቱ እንዲያስረዱ ዕድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው የነበሩት 3ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሺ የጠየቁት የመናገር እድል ሳይፈቀድላቸው ቀርቷል፡፡
በጠበቆቹ አማካኝነት የቀረበው አቤቱታን በተመለከተ ችሎቱ አስተያየት የሰጠ ሲሆን በተለይ ጠበቃ ተማም አቤቱታውን ባቀረቡበት ወቅት ‹‹ማረሚያ ቤቱ ደንበኞቼን ለመጠበቅ ፍላጎትም ብቃትም የለውም›› ያሉት አገላለጽ ተገቢ ስላልሆነ እንዲታረሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ይህንኑ ጉዳይ በቃል የገለጹት የመሐል ዳኛው፣ ‹‹እንዲህ አይነት አገላለጽ ማረሚያ ቤቱ የበቀል እርምጃ እንዲወስድ የሚገፋፋ እንዳይሆን…›› በማለት ሌላ አስገራሚ መነጋገሪያ ከፍተዋል፡፡
ይህን የዳኛውን ንግግር ተከትሎ 2ኛ ተከሳሽ አቶ ሀብታሙ አያሌው የመናገር እድል ከተደጋጋሚ ጥያቄ በኋላ ለአጭር ጊዜ ተፈቅዶለታል፡፡ እናም፣ ‹‹እርስዎ እያሉት ያለው ነገር ተገቢ አይደለም፡፡ በህይወቴ ላይ የደህንነት ስጋት አለብኝ ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ ይህንን ስጋቴን ለችሎት እያስረዳሁ ነው፡፡ ግን እርስዎ ‹የበቀል እርምጃ› እንዲወሰድብን ማሳሰቢያ እየሰጡ ነው፡፡ ይህ ተገቢ አይደለም፡፡ በእርግጥ አሁንም የበቀል እርምጃ እንደማይወሰድብን ማረጋገጫ የለንም፡፡ እሺ ለማን አቤት ይባላል? የደረሰብንን በደል ለፍርድ ቤት ከማስረዳት ውጭ ለማን አቤት እንላለን….አሁን እኮ ፍርድ ቤቱ ከማረሚያ ቤቱ ጋር መወገኑን ነው እያየን ያለነው፡፡ ፍርድ ቤቱ የእኛን አቤቱታ እየሰማ አይደለም፡፡ ከፍርድ ቤት ውጭ ለማን አቤት እንበል?›› ሲል አቤቱታውን በስሜት ውስጥ ሆኖ አስረድቷል፡፡
የሀብታሙን ንግግር አዳምጠው አንደኛ ዳኛ ‹‹እኛ ሳንሆን ህጉ ነው ይህን እንድንል የሚያደርገን›› በማለት አጭር መልስ ሰጥተዋል፡፡
በዚህ መልኩ ቀጥሎ የዋለው ችሎት በተከሳሾች በኩል የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ፍርድ ቤቱ ይህን ጉዳይ የማየት ስልጣን አለው ወይስ የለውም በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት፣ እና መደበኛ ክሱን ለማየት ለታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተጥቷል፡፡
#NegereEthiopia
የገንዘብ አቅም የፈተነው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ማኅበር
ሪፖርተር ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በዘመነ መንግሥታቸው ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት ይሰጡት እንደነበርና ለዚህም እውን መሆን ራሳቸው የትምህርት ሚኒስትር እንደነበሩ ይወሳል፡፡ ከሕይወታቸው ፍፃሜ በኋላም የእሳቸውን ጅማሬ ለማስቀጠል በስማቸው መታሰቢያ ማኅበር ተቋቁሟል፡፡ ማኅበሩም በሕይወት ዘመናቸው ትኩረት ይሰጡት ለነበረው የትምህርት ዘርፍ በተቻለ መጠን ተጠናክሮ እንዲቀጥል እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙና በአካዴሚክ ዕውቀታቸው በጣም ጠንካራ ሆነው […]
‹‹ለጋራ አገራችን በጋራ እንወያይ የሚል ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ›› ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከወራት ፀጥታ በኋላ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከሚዲያው ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተዋል፡፡ የሰሞኑ ዋና የመወያያ ርዕስ የሆነውንና አገሪቱ ወደ ዓለም አቀፉ የቦንድ ገበያ ለመግባት ያደረገችውን ጥረት እንደተጠበቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያብራሩት ዋናው ጉዳይ ነበር፡፡ ‹‹አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያው ገንዘብ ለማግኘት ብቁ ሳትሆን ቆይታለች…›› በማለት ጉዳዩን ያስረዱት አቶ ኃይለ ማርያም፣ በስኳር […]
እነ ሀብታሙ አያለው ላይ ሌላ ተለዋጭ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው: ዳኛውም ጠበቃ ተማም አባቡልጉን አስጠነቀቁ
እነ ሀብታሙ አያለው ዛሬ ታህሳስ 15 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የዛሬ ቀጠሯቸው መቃወሚያ ለማቅረብ የነበረ ቢሆንም ታህሳስ 12 ቀን 2007 ዓ.ም በደረሰባቸው ድርጊት ፍርድ ቤቱ ሌላ ቀጠሮ ለመስጠት ተገዷል፡፡ በለቱ ሌሊት 8፡00 ላይ የእስር ቤቱ የስራ ባልደረባ ያልሆኑ የደህንነትና የፖሊስ አባላት ለዛሬው ቀጧሯቸው የሚሆን የመቃወሚያና የመከራከሪያ ሰነዶቻቸውን ወስደውባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ገንዘባቸው እንደተወሰደባቸው ጠበቃቸው ተማም […]
እስላማዊ ኪነ-ህንጻ እና “ሲናን”ን በጨረፍታ
አስመራ የገቡት ፓይለቶች ከቤተ መንግስቱ ወደ ሆቴል ተዘዋወሩ:: የድሬደዋ አየር ሃይል መምሪያ በግምገማ ታመሰ::

– የድሬደዋ አየር ሃይል መምሪያ በግምገማ ታመሰ::
– መጭውን ውህደት የሚያሳፈጽሙ የአርበኞች ግንባር አባላት ከአውሮፓ እና አውስትራሊያ ተወከሉ::
http://ireport.cnn.com/docs/DOC-1200173
አርብ እለት ከድሬዳዋ ተነስተው በደቡባዊ ኤርትራ አሰብ ዘልቀው የገቡት የወያኔው አየር ሃይል አብራሪዎች እና ቴክኒሺያኖች በደህና ሁኔታ ውስጥ ሲገኙ በኤርትራ የአየር ክልል የተቀበላቸው እና በ1987 አመተምህረት በወያኔ እና የደርግ መኮንኖች የሰለጠነው የሻእቢያ ኮማንዶ ጦር አጅቧቸው ወደ አስመራ ቤተመንግስት ከገቡ በኋላ በቤተ መንግስቱ ውስጥ ለሁለት ቀን በእንግዳ ማረፊያ ክፍል ውስጥ ቆይተው ወደ ሆቴል መዘዋወራቸውን ከአስመራ የተገኙ ምንጮች ጠቁመዋል::
በቤተ መንግስት ቆይታቸው አስፈላጊ ጥያቄዎች እና ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ከደምህት ጦር ጋር በመቀላቀል እየተገነባ ባለው ዘመናዊ አየር ሃይል ውስጥ አገልግሎት እንዲሰጡ የተጠየቁ መሆኑን ምንጮቹ ሲናገሩ አብራሪዎቹ ግን ወደ አውሮፓ ለመጓዝ ፍላጎቱ እንዳላቸው እና አውሮፓ ሆነው ትግሉን መርዳት እንደሚችሉ ሲናገሩ ተደምጠዋል::አብራሪዎቹ እጃቸውን የሰጡትም ሆነ የተቀላቀሉት ከኤርትራ መንግስት ጋር እንጂ ከሌላ አካል ጋር እንዳልሆነ ምንጮቹ አረጋግጠዋል::
ከደብረዘይት አየር ሃይል አከባቢ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በድሬዳዋ ያለው የአየር ሃይል ካምፕ ሃላፊዎች ላይ ከፍተኛ ግምገማ ተደርጓል::በዚህም መሰረት የሃገሪት የአየር ክልል ሳይቀር ከራዳር ውጪ ነው የሚል ጉዳይ ተነስቶ መነጋገሪያ እና መገማገሚያ ሆንዋል::እርስ በርስ መወነጃጀል እንኳን ባልተደፈረበት ግምገማ ላይ እያንዳንዱ መኮንን ሃላፊነቱን ወስዶ ዋጋ ሊከፊል ዪገባዋል ሲሉ ከፍተኛ አዛዦች በቁጣ ተናግረዋል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ በመጪዎቹ ሳምንት በሚካሄደው የግንቦት ሰባት እና የአርበኞች ግንባር ውህደት ላይ እስካሁን ወኪል ያላከው የአርበኞች ግንባር አንድ ሰው ከአውሮፓ አንድ ሰው ከአውስትራሊያ በመምረጥ ለእህደት ስብሰባው ማስትላለፉን ምንጮቹ ተናግረዋል::የተመረጡት አስመራ እንደደረሱ በውህደቱ ዙሪያ ንግግር እንደሚጀመር እና የፊርማው ውህደት እንደሚጸድቅ ኮሎኔል ፍጹምን ዋቢ ያደረጉ ምንጮች ጠቁመዋል::
ብሄራዊውን ምርጫ የቀለም አብዮት ለመቀስቀስ እየተጠቀሙበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ከሰሱ።
ኒዮሊበራል ሀይሎች በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ምርጫ ከ 10 አመታት በፊት እንደሞከሩት ሁሉ የቀለም አብዮት ለመቀስቀስ እየተጠቀሙበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሰሱ።
አየር ሃይል እየታመሰ መሆኑን ምንጮች ገለጹ
ታኀሳስ ፲፬(አስራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአየር ሃይል ባልደረባ የሆኑት ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝ ከበረራ ቴክኒሻኑ ጸጋ ብርሃን ግደይ ጋር በጋራ በመሆን የሚያበሩትን ሄሊኮፕተር ይዘው ከጠፉ በሁዋላ የአየር ሃይል አዛዦች አስቸኳይ ግምገማ ከተጠሩ በሁዋላ እርስ በርስ እየተገማገሙና ከእነዚህ ሰዎች ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው የሚያስቡትን የአየር ሃይል አባላት ለማሰር እንቅስቃሴ መጀመራቸውን …





