ነሀሴ 14/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከተከሰሱበት የሽብርተኝነት ክስ ነጻ ናችሁ ያላቸው የፖለቲካ አመራሮች የሆኑት አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ እንዲሁም በተመሳሳይ መዝገብ ተከሶ ነጻ የተባለው አብርሃም ሰለሞን ላይ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኙን ለማሰማት ለመስከረም …

ከተከሰሱበት የሽብርተኝነት ክስ ነጻ ናችሁ ያላቸው የፖለቲካ አመራሮች እስከ መስከረም 21 በእስር ላይ እንዲቆዩ ተወሰነ Read more »

በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ባለ ሃብቶች በትግራይ ክልል ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተደረገላቸው ቅስቀሳ በክልሉ ውስጥ ያለው ስር የሰደደ ብልሹ የአስተዳደር ሁኔታመጀመሪያ ይስተካከል ማለታቸውን ተገለፀ። በምንጮቻችን መረጃ መሰረት- በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ ባለሃብቶች ያላቸውን ሃብት በትግራይ ክልል እንዲያሰማሩ ይርዳው በተባለ ከፍተኛ የህወሃት ካድሬ ነሓሴ 3/2007 ዓ/ም በተካሄደው ቅስቀሳ የተሞላበት ስብሰባ በብልሹ አሰራራችሁ የተጨማለቀውን አሰራራችሁ […]

በሶማሊያ ሀገር  እየተላኩና ህይወታቸው እያለፈ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ከቀን ወደ ቀን ቁጥራቸው እየጨመረ እንደሆነ ከተለያዩ ያገራችን አካባቢዎች የደረሰን መረጃ አስታወቀ።በሶማሊያ ሃገር እየሞቱ ያሉትን የኢትዮጵያ ወታደሮች ቁጥራቸው ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የሟቾቹ ቤተሰብ በየግዜው በቴለፎን መርዶ እየደረሳቸው እንደሆነ የገለፀው መረጃው በተለይም የኦሮሚያ ክልል ህዝብ ለምንድነው ስልጣን ላይ ያለው ስርዓት የሞቱት ልጆቻችን የማይነግረን በመሰረቱ […]

ህወሀት ቴዲ አፍሮን ከልክ በላይ እየገፋው ነው:: ለቴዲ የህወሀት ኢትዮጵያ አላስቀምጥ ብላዋለች:: ምናልባትም ቴዲ ከሀገር ተሰደደ የሚል መራር ዜና ልንሰማ የምንችልበት ጊዜ እየቀረበ እንደሆነ ይሰማኛል:: በግሌ በተለይ ሰሞኑን የሚደርሱኝ መረጃዎች የህወሀትን የዕብሪት ለከት ማጣት የሚያሳዩ ቴዲንም ከሚወደው ህዝብና ከሚሳሳላት ሀገሩ እንዲለያይ የሚገፋፉ ናቸው:: ቴዲ መሰደድ እንደማይፈልግ የትኛውንም በደል ተቋቁሞ በሀገሩ መኖር ለምርጫም የማይቀርብ ጉዳይ እንደሆነ […]

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) እስክመቼ ድረስ እያወራን እንደምንኖር አላውቅም::ይህን ሰሞን የሕወሓትን ስብሰባ ተከትሎ አስር ጊዜ የባለስልጣኖቹን ስም በመጥራት ወሬ እያጣፈጡ የሚነግሩን ተቃዋሚ ነን ባዮች በተገኘበት አብሮ መውቀጥ በነፈሰበት አብሮ መንፈስ ለምን? እስከመቼ? ልላቸው ወደድኩ::አሁን ጊዜው የአርከበ ምንቸውት ገባ የአዜብ ምንቸት …

በተገኘበት አብሮ መውቀጥ ለምን ? በነፈሰበት መንፈስ እስከመቼ ? በሚገባቸው ቋንቋ እናናግራቸው!!! (ምንሊክ ሳልሳዊ) Read more »

የቴዲ አፍሮ ጉዳይ እያነጋገረ ነው::የደህንነቶች ጫና በርትቷል:: የእውቁ እና ተወዳጁ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በሕወሓት የሚደረግበት ጫና ኢትዮጵያ ውስጥ መነጋገሪያ መሆኑን ለመኖሪያ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ያላኩት መረጃ ይጠቁማል:ቴዲ አፍሮ በተለያየ ጊዜ በመገዱ ላይ እና በመኖሪያ ቤቱ አከባቢ የተመደቡ ደህንነቶች …

የቴዲ አፍሮ ጉዳይ እያነጋገረ ነው::የደህንነቶች ጫና በርትቷል:: Read more »

በእስር ላይ የምትገኘው እየሩሳሌም ተስፋው በድንገተኛ ህመም ወደ ሆስፒታል ከተወሰደች በሁዋላ ሀከም ተብየዎቹ የተከሰሰችበት “ሽብር” የሚል መሆኑን አይተው ራሱዋን እንደሳተች ወደ እስር ቤት አስመልሰዋታል! ይህ በእንዲህ እንዳለ እየሩስ ትጠቀምበት የነበረውና የተያዘባትን ስልክ ማንነቱ ያልታወቀ ሰው እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ደውለን ማረጋገጥ ችለናል:: …

እየሩሳሌም ተስፋው ሕክምና ተከለከለች:: Read more »

የፌድራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ የወንጀል ችሎት ክስ ባልተነሳላቸው የዞን ዘጠኝ አምደኞች ጉዳይ ዛሬ ብይን ይሰጣል፤ ተብሎ ቢጠበቅም ለሌላ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል። ተከሳሾች የተለያዩ አቤቱታዎችን ለችሎቱ አቅርበዋል።

በሌላ ዜና በዚሁ ችሎት ብይን ከእስር እንዲፈቱ ባለፈው ሳምንት ትዕዛዝ የተሰጠላቸው የቀድሞው የአንድነት የአመራር አባል አቶ ሃብታሙ አያሌው እና ሰባተኛው ተከሳሽ አቶ አብረሃም ሰለሞን እስከ ዛሬም ከእስር አልተፈቱም።

የፍርድ ቤቱ ብይን በአቃቤ ሕግ የይግባኝ አቤቱታ መታገዱ ነው፤ የተነገረው። በጉዳዩ ላይ የሕግ አስተያየት ባለ ሞያዎች ግን እግዱ የሕግ መሠረት የለውም ይላሉ።

ነሀሴ 14/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከተከሰሱበት የሽብርተኝነት ክስ ነጻ ናችሁ ያላቸው የፖለቲካ አመራሮች የሆኑት አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ እንዲሁም በተመሳሳይ መዝገብ ተከሶ ነጻ የተባለው አብርሃም ሰለሞን ከእስር እንዳይለቀቁ ታግደዋል። አቃቤ ህግ ይግባኝ እንደጠየቀባቸው የታወቀ ቢሆንም እንደ ህግ ባለሙያዎች ግን የአቃቤ ህግ ይግባኝ ገና ተቀባይነት ባላገኘበት ሁኔታ ከእስር እንዳይለቀቁ እግድ […]

በኢትዮጵያ 4 ነብ 5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጋር የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተያዘው አመት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ታስቦ የነበረ ቢሆንም፤ የተረጅዎች ከግምት ውጪ ላሻቀበው የተረጅዎች አሀዝ ብቻ 230 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ […]

አማሳኝ ሓላፊዎች፤ በካህናት እና ሠራተኞች ስም የሚያቀርቡት አቤቱታ ተቀባይነት የለውም ከብፁዕ ዋ/ሥራ አስኪያጁ ጀምሮ ብፁዓን አባቶች ለማስፈራራትና ለመደለል እየተሞከረ ነው “እጁ የተገኘበትን ኹሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ አሳልፋ ትሰጣለች፤ ይኼ የመጨረሻ አቋሜ ነው”                                    /ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ/  *       …

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ በ11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ ላይ እንደገለጸው፣ ለረጅም ጊዜ በአመራርነት ቆይቶ ስልጣኑን በመተካካት ሂደት ባስረከበውና ቁልፍ ስልጣኑን በተረከበው መካካል የመግባባት ችግር መኖሩን ገልጿል። ነባሩ አመራር ሁሉንም ሃላፊነት አስረክቦ ድርጅቱን የመልቀቅና ራሱን ገለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል ያለው ብአዴን፣ በዚህም ላይ ነባሩ አመራር በአዲሱ አመራር እንደማይረካና ተደጋጋሚ ቅሬታ እንደሚያቀርብም …

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ 4 ነብ 5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጋር የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተያዘው አመት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ታስቦ የነበረ ቢሆንም፤ የተረጅዎች ከግምት ውጪ ላሻቀበው የተረጅዎች አሀዝ ብቻ 230 ሚሊዮን ዶላር …

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተያዘው ክረምት በአብዛኛው ምስራቅና ሰሜን ምስራቅ የሃገሪቱ ክፍሎች የተከሰተውን የዝናብ እጥረት ተከትሎ የሰቆጣ ከተማና የአካባቢው ወንዞች በመድረቃቸው የውኃ እጥረቱ መከሰቱን ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ነዋሪዎች ፣ በዝናቡ እጥረት የተነሳ የጉድጓድ ውሃ መጠን በማነሱ የሚጠጣ ውኃ እጥረት መከሰቱን ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ “በከተማዋ በአጠቃላይ የውኃ ችግር ተከስቷል፡፡በከተማዋ የመጠጥ ውኃና ፍሳሽ ልማት ጽህፈት …

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አርሶአደሩ ፣ የመንግስት ሰራተኛውና ነጋዴው ለቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አካዳሚ ግንባታ በሚል በግዴታ ከ50 ብር ጀምሮ እንዲከፍል ቢደርግም፣ ምክንያቱ በውል ባልተገለጸ ሁኔታ ገንዘቡ ለኢህአዴግ አራት ድርጅቶች ማለትም ለህወሃት፣ ብአዴን፣ ኦህዴድና ደኢህዴን ተከፋፍሏል። ሁሉም ድርጅቶች 80 ሚሊዮን 566 ሺ 221 ብር ደርሶአቸዋል። ገንዘቡን ለመንግስት ወይም ለከፈሉት ዜጎች …

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ለሁለት ቀናት በመዲናዋ አዲስ አበባ ያደረገው ሰማያዊ ፓርቲ ኢ/ር ይልቃል ጌትነትን በድጋሜ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በድጋሜ ለቀጣዩ ሦስት ዓመታት ፓርቲውን እንዲመሩ የተመረጡ ሲሆን፣ አምስት የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን አባላትም በጉባኤው ተመርጠዋል፡፡ ጉባኤው የፓርቲውን የብሄራዊ ምክር ቤት አባላትንም መርጧል፡፡ ኢ/ር …

ነኅሴ ፲፰ (አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አርበኞች ግንቦት ሰባት የጀመረውን የነፃነት ትግል በገንዘብ ለማጠናከር በላስቬጋስ ከተማ የተጠራው የሀገር አድን ጥሪ በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎና በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን በእለቱ በተደረገው የገንዘብ ማሰባሰብ ከፍተኛ ገንዘብ መገኘቱን ለማወቅ ተችሏል፡ በዚህ ለሰማእታት በተደረገ የህሊና ጸሎት የተጀመረ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ አቶ ሙሉነህ እዩኤልና አቶ ጋሻው ገብሬ የንቅናቄው …

በብላቴናው ላይ የዘገየው ፍትህ ! ‪#‎JusticeForMohammed‬ #Ethiopia #SaudiArabia Nebiyu Sirak የብላቴናው መከራና የትጉህ እናቱ ፍትህ ፍለጋ በጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ አዋዜ ሲወሳ ! (VIDEO) [youtube http://www.youtube.com/watch?v=P4TLDM9F_C8]     እግዚአብሔር ካንች ጋር ይሁን ሃሊማ !! (አሌክስ አብርሃም) ይሄ ድንቡሸ ህፃን መሃመድ ይባላል …

እግዚአብሔር ካንች ጋር ይሁን ሃሊማ !! …. በብላቴናው ላይ የዘገየው ፍትህ Read more »

ዝም ብዬ ሳስበው… Yohanes Molla ባጋጣሚ፣ ባለቀ ሰዓት በተገኘ ዕድል ሾልካ የግል ጥረቷንና ውጤታማነቷን ባታሳይ ኖሮ፥ መሰረት ደፋር የምትባል ልበ ሙሉ ጀግና አትኖርም ነበር። አክስቷ ደራርቱ ቱሉ ቀድማት ጀግንነቷን ባታስመሰክርና እህቷ በቀሉ ዲባባ ቀድማ ሩጫው ውስጥ ባትቀላቀል ኖሮ፥ ጥሩነሽ ዲባባ …

ዝም ብዬ ሳስበው… ፌደሬሽኑ ራሱን ይፈትሽ ዘንድ ግድ ነው! Read more »

‹‹እንደሚታረድ በግ ዘቅዝቀው ገርፈው ነው ያሳመኑኝ››  Getachew Shiferaw .. … .. ዳኛው፡- ‹‹ስራ?›› ተከሳሽ፡- ‹‹ጫኝና አውራጅ!›› ዳኛው፡- ተከሳሽ ክሱ እንደደረሰው ካረጋገጡ በኋላ ማንበብ ጀመሩ፡፡ ‹‹በ1996 የወጣውን —— ህግ በመተላለፍ የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት ወይንም ለሌላ ሰው ለማስገኘት ሲል ከወይዘሮ—- 700 ብር …

‹‹እንደሚታረድ በግ ዘቅዝቀው ገርፈው ነው ያሳመኑኝ›› ዛሬ ነሃሴ 18/2007 ዓ.ም በአራዳ ምድብ ችሎት የታዘብኩት Read more »

ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ሳዑዲ አረቢያ በሃኪም ቤት ዉስጥ ከሰመመን ሳይነቃ የተኛዉ ኢትዮጵያዊ እናት ለተፈጠረዉ የሕክምና ስህተት እንዲከፈላቸዉ የታዘዘዉን ካሳ እንደማይቀበሉ አስታወቁ። 2.4 ሚሊዮን ሪያል ወይም 13 ሚሊዮን በላይ ብር የካሳ ክፍያ የተወሰነላቸው እናት ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል።

አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ግድያ ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት እነ ማቲያስ መኩሪያ ለነሃሴ 27/2007 ዓ.ም ተቀጠረባቸው፡፡ ፖሊስ በጊዜ ቀጠሮ ወቅት ‹‹የቪዲዮ ማስረጃም አለን›› በማለቱ ተከሳሾቹ ‹‹ቪዲዮው ይቅረብልን፡፡ የቪዲዮ ማስረጃው ለእኛም የመከላከያ ምስክርነት ይጠቅመናል›› ብለው ጠይቀው የነበር በመሆኑ፤ ፍርድ ቤቱ የቪዲዮ ማስረጃው መቅረብ እንዳለበትና እንደሌለበት ብይን ለመስጠት ለነሃሴ 5/2007 ዓ.ም […]

የበረኪና ሽብር ? ( ሄኖክ የሺጥላ ) ======= ድሮ ድሮ ፣ ሕይወት ብርቅ በነበረበት ጊዜ ፣ አባት እና አናትን ማክበር እንዲህ እንደዛሬው ቀልድ ሳይሆን ፣ ያኔ ከጋብቻ በፊት ማርገዝ እንደ ትልቅ ነውር ይታይ በነበረበት ዘመን ፣ ድሮ ማለቴ ነው፣ ያኔ …

የበረኪና ሽብር ? ( ሄኖክ የሺጥላ ) Read more »

–   የዘረኝነት ወረርሽኝ ለኢትዮጵያ አስፈሪ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ። እርስበርስ፣ “አንተ ነህ ዘረኛ”፣ “አንቺ ነሽ ዘረኛ” እያሉ ይወነጃጀላሉ። ብዙዎቹ የሚያቀርቧቸው አማራጮች ግን፣ በቅፅል ብቻ የሚለያዩ የዘረኝነት መልኮችን ነው። .   ኢህአዴግ፣ ተቃዋሚዎቹን ያወግዛል – “የሁለት ተማሪዎችን ፀብ፣ የብሔረሰብ ፀብ አስመስለው ያራግባሉ” …

“ዲሞክራሲያዊ ወይም ልማታዊ ዘረኝነት”፣ “አገራዊ ወይም ነፃ አውጪ ዘረኝነት” … የዘረኝነት መልኮች ( ዩሃንስ ሰ. ) Read more »

H.I.M. Haile Selassie I Emperor of Ethiopia address to the General Assembly - 1963.

በመጪው ጥቅምት የ70ኛ አመት የምስረታ በዓሉን የሚያከብረው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፤ ኢትዮጵያና የቀድሞው የአገሪቱ መሪ ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ በድርጅቱ መስራች አባልነት ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚዘክርና የበዓሉ አካል የሆነ ልዩ ፕሮግራም ማካሄዱን ታዲያስ መጽሄት ዘገበ፡፡ ኒውዮርክ ሲቲ ውስጥ በሚገኘው የተመድ ዋና ጽህፈት ቤት …

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያንና የቀዳማዊ ኃ/ስላሴን አስተዋጽኦ ዘከረ :: Read more »

Politics is a dirty game የሚለውን የፖለቲካን ቆሻሻነት የሚነግሩን ብዙ ሰዎች አሉ። ይህን ከሚያወሩት ዋናዎቹ እኛ ወደ ፖለቲካ እንዲች ብለን እንዳናይና ስለ ፖለቲካ እንዳናወራ በሚፈልጉ ነውረኛ ፖለቲከኞች የሚነዛ ቧልት ሲሆን ሌላው ደግሞ ብዙ የፖለቲካ ብልግናን የሚፈጽሙ ባለጌ ፖለቲከኞችን ያዩና የተመለከቱ …

ፖለቲካ ቆሻሻ የሚሆነው ቆሻሻ አእምሮ ያላቸው ሲነኩት ነው! (የትነበርክ ታደለ) Read more »

የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከተከሰሱበት የሽብርተኝነት ክስ ነጻ ናችሁ ያላቸው የፖለቲካ አመራሮች የሆኑት አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ እንዲሁም በተመሳሳይ መዝገብ ተከሶ ነጻ የተባለው አብርሃም ሰለሞን ከእስር እንዳይለቀቁ ታግደዋል፡፡ አቃቤ ህግ ይግባኝ እንደጠየቀባቸው የታወቀ ቢሆንም እንደ ህግ …

ፍርድ ቤት ከተከሰሱበት የሽብርተኝነት ክስ ነጻ ናችሁ ያላቸው የፖለቲካ አመራሮች እገዳ ተጣለባቸው Read more »

እነ ማቲያስ መኩሪያ ለነሃሴ 27 ተቀጠረባቸው :: ……….. ‹‹ያለ ፍርድ እየተጉላላን ነው፡፡›› ………. በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር ,,,………. በቀጠሮ ማሸት አዲሱ ስልት…… አይ ኤስ አይ ኤስ በኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ግድያ ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት እነ ማቲያስ መኩሪያ ለነሃሴ …

መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ለነሃሴ 27/2007 ዓ.ም ተቀጠረባቸው፡፡ Read more »

ሰላም ጤና ይስጥልን አድማጮችና ተመልካቾቻችን ይህ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ነው።#Ethiopia ሳምንታዊ ዜናዎችን መጣጥፎችን እና መንፈስን የሚያድሱ ሙዚቃዎችን አሰናድተን ወደናንተ መጥተናል ያዳምጡት:: [youtube http://www.youtube.com/watch?v=M-YZdqBnECM]

ሊባኖስ (ቤሩት) ከአንድ አመት በላይ ያለፕሬዘዳንት ኖራለች በዚህች ሀገር መንግስቱ እየተልፈሰፈሰ የሚገኝ ሲሆን የከተሞችን ቆሻሻ እንኳ በቅጡ መሰብሰብ አቅቶታል ነው የሚባለው ይህን ተከትሎ ከተሞቻችን በቁሻሻ ተወረሩ ያሉ ሊባኖሳዊያን ትናንትናና ሰሞኑን ከባድ አመጽ ማስነሳታቸው ነው የተነገረው አመጹ ዛሬ ጋብ ቢልም ከፖሊስም ሆነ ከተቃዋሚዎቹ ወገን የበርካታ ሰዎችን መቁሰልና መጎዳትን ማስከተሉ ነው የተነገረው እናንት ቁሻሾች በተባለው ሊባኖወሳውያኑ በዚህ […]

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ለመከላከል ወይም ሳይከላከሉ በነፃ ለመሰናበት ውሳኔ ዛሬ ለ35ተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት አራቱ በእስር የሚገኙት ጦማርያን በድጋሚ በተለዋጭ ቀጠሮ ተሸኝተዋል። በዛሬው ውሎ ችሎቱ ያልተሰየመ ሲሆን ተከሳሾች እና ጠበቆች በቢሮ ተጠርተው ዳኞች ተሟልተው ስላልተገኙ ችሎቱ ለመሰየም አለመቻሉን ዶክመንቶችን ማየትና ውሳኔውን ፅፎ ማጠናቀቅ አሁንም እንዳልቻሉ በመግለፅ ዳኛ ዘሪሁን ለጷግሜ 2 ተለዋጭ ቀጠሮ […]

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ (Update) #Freezone9bloggers በዛሬው እለት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የወያኔ ካንጋሮ ፍርድ ቤት ቀርበዋል::አራቱ ጦማርያን በፍቃዱ:ናትናኤል:አቤል:እና አጥናፍ በጥቁር ሱፍ ደምቀው በፍርድ ቤቱ ተገኝንዋል::ንጽሕናቸውን በተለያየ መንገድ እየገለጹ ያሉት እና የፍርድ ቤቱን ነጻ አለመሆን በተግባር ያሳዩት ጦማርያን በራስ …

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የፍርድ ቤት ውሎ – የካንጋሮ ፍርድ ቤቱ ድራማ – ቀጠሮ ለ36ኛ ጊዜ ጳጉሜ 2 2007 Read more »

አንድ አገር ሰላሟና ብልፅግናዋ ዘላቂና አስተማማኝ የሚሆነው የሕግ የበላይነት በተግባር ሲረጋገጥ ብቻ ነው፡፡ ዜጎች በሕግ ፊት እኩል መሆናቸውን ሲያምኑ፣ ሕግም ለሁሉም ዜጎች እኩል ጥበቃ ሲያደርግ፣ ፍትሕ ለሁሉም ተደራሽ ሲሆንና የፍትሕ ሥርዓቱ በነፃነት ሲንቀሳቀስ የሕግ የበላይነት መኖሩ ይረጋገጣል፡፡ ‹‹አንድን ንፁኅ ዜጋ …

አንድ አገር ሰላሟና ብልፅግናዋ ዘላቂና አስተማማኝ የሚሆነው የሕግ የበላይነት በተግባር ሲረጋገጥ ብቻ ነው፡፡ Read more »

በገዢው ስራዓት የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ እየተካሄደ ባለው ሰፊ የዓመቱ ግምገማ “የተቃዋሚዎች ሬድዮ መስማት” እንደዋነኛ መገምገሚያ ነጥብ ሆኖ መነሳቱን ተገለፀ።በምንጮቻችን መረጃ መሰረት- በሁሉም የስርዓቱ መከላከያ ሰራዊት ውስጥ እየተካሄደ ያለውን መጠነ ሰፊ የዓመቱ ግምገማ ወታደሩ ያለማቋረጥ እየፈረሰ በመጥፋት ላይ ያለው የትጥቅ ትግል እያካሄዱ በሚገኙ ድርጅቶች የሚሰራጨውን ሬድዮ መስማት ዋናው ከሆኑ ምክንያቶች አንዱ ስለሆነ ለምን ታዳምጣላችሁ፤ እነማን ናቸው የሚያዳምጡት መታወቅ አለባቸው በማለት እየተካሄደ ባለው ስብሰባ የሰራዊቱ አዛዦች ራሳቸው […]

ኢትዬጲያዊያን ሙስሊሞች አሁን በሃገራችን ያለንበት ተጨባጭ ይህን ይመስላል አቡ ዳውድ ኡስማን ወደፊት ለመጓዝ አሁን ያለንበትን ተጨባጨ መመዘን ተገቢ ነው፡፡ የተጋረጠብንን ችግሮችም ለመጋፈጥ እና ችግሩን ጥሶ ለማለፍ ያሉትን ችግሮች ማወቁም ተገቢ ነው፡፡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ 3 ቀላል ጥያቄዎችን ለመንግስት አቅርቧል፡፡ ይህም ጥያቄዎች …

ኢትዬጲያዊያን ሙስሊሞች አሁን በሃገራችን ያለንበት ተጨባጭ ይህን ይመስላል :: (አቡ ዳውድ ኡስማን ) Read more »

ኤልሳ ብስራት ገንዘብ አምጡ ክፈሉ ባዩ ግንቦት 7 ቡድን በዋሺንግተን፤ ሲያትልና ዳላስ ያከሄደውን ዝርፊያ በሎንዶንም በመቺው እሁድ ሊያከናውን ተዘጋጅቷል። የሚሞኝ ዳያስፖራ ሞልቷልና በአስቸኳይ እንብላው ነው ዘመቻው። የጦር ስምሪቱ ወሬ ነፍሶበታልና፤ ውሸት መሆኑን የቡድኑ ደጋፊዎች ራሳቸው እየተረዱት ነውና ቶሎ ቶሎ ዝርፊያው …

ግንቦት 7ና አሜሪካ — ከመጋረጃው በስተጀርባ Read more »

– የወያኔው ጉባኤ ጥበቃና ጸጥታ ውዝግብ አስነስቷል – የወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በካድሬዎች እየተተቸ ነው – ሱማሊያ ውስጥ ሰርገኞችን የገደሉ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል አባላት ለፍርድ ቀረቡ – በደቡብ ሱዳን የመገናኚያ ብዙሀን አባላት የዜና ማእቀብ አድማ አደረጉ – በሰሜን …

የወያኔው ጉባኤ ጥበቃና ጸጥታ ውዝግብ አስነስቷል:: የወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በካድሬዎች እየተተቸ ነው Read more »

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በድጋሜ የሰማያዊ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በድጋሜ የሰማያዊ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ያደረገው ሰማያዊ ፓርቲ ኢ/ር ይልቃል ጌትነትን በድጋሜ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል፡፡ ትናንት ነሀሴ 16/2007 ዓ.ም ጉባኤውን የጀመረው ፓርቲው በዛሬው ሁለተኛና የማጠቃለያ …

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በድጋሜ የሰማያዊ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ Read more »

‹‹ታግዬ ለውጥ ማምጣት እችላለሁ!›› የሚል ትውልድ አይሸነፍም! የአስተሳሰብ የበላይነት የትግል እና የድል መሰረት ነው! እሁድ ነሐሴ 17/2007 ማንኛውም የመብት ትግል የሚጀምረው በበደል ነው፡፡ አምባገነኖች በደልን የሚያደርሱት እጅግ ስልታዊ በሆነ መንገድ በመሆኑና ለዚህ በደልም ሽፋን ስለሚያደርጉለት ብዙዎች የሚበደሉት እየተበደሉ መሆናቸውን ሳይረዱ …

ታግዬ ለውጥ ማምጣት እችላለሁ!›› የሚል ትውልድ አይሸነፍም! – ድምፃችን ይሰማ Read more »

ዛሬ እንደወትሮዬ አብርሀ ደስታን ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ አምርቼ ነበር። ታዲያ አብርሀን ሆነ መሰሎቹን ለመጠየቅ እንዲህ በቀላሉ የሚቻል አይደለም። በጥብቅ ከሚጠበቀው ቃሊቲ ውስጥ ለመጠየቅ የሚፈቀደው ከ 6:00 – 6:30 ያለችን 30 ደቂቃ ብቻ ስትሆን እሱም በር ላይ ቆመው የአይንህ ቀለም አላማረንም …

አመክሮ ካልታሰበ አብርሃ ደስታ ጥቅምት 24 2008 የሽዋስ እና ዳንኤል ነሃሴ 30 ይፈታሉ:: Read more »

በሁለተኛው ቀን ውሎ የሰማያዊ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ ቀጣይ የፓርቲውን እንቅስቃሴ አስመልክቶ የጉባኤው አባላት አጠቃላይ ውይይት እየተደረጉ ይገኛል፡፡ በቀጣይም የብሄራዊ ምክር ቤት፣ የኦዲትና ምርመራ ኮሚሽን አባላት እና የፓርቲው ሊቀመንበር ጥቆማ እና አስመራጭ ኮሚቴ አባላት ምርጫ ይደረጋል፡፡ ጠቅላላ ጉባኤው ቀጣዩን የሰማያዊ ፓርቲ …

የሰማያዊ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በሁለተኛው ቀን ውሎ Read more »

#Ethiopia ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ በሳተላይት የሚሰራጭ የራዲዮ ፕሮግራም (EPRP’s Satellite Radio transmissions to Ethiopia and Horn of Africa.) የነሐሴ 15 ቀን 2007 ዓ.ም.ዜና (August 21, 2015 News) – ወያኔ ውስጥ ውስጡን እርዳታ እየጠየቀ ነው – የወያኔ ምክር ቤት ስብሰባ …

ከኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ በሳተላይት የሚሰራጭ የራዲዮ ፕሮግራም Read more »

‹‹መጠየቅ ካለብኝ በክልል እንጂ በፌዴራል አይደለም›› አቶ ወንድሙ ቢራቱ

ለመንግሥት መግባት የነበረበትን ተጨማሪ እሴት ታክስና ሌሎች የመንግሥት የግብር ገቢዎች በማጭበርበር በግላቸውና በዘመዶቻቸው ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ በማካበት በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩት፣

የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ወንድሙ ቢራቱ ሰው በመግደል ወንጀል መጠርጠራቸው ለፍርድ ቤት ተገለጸ፡፡

ነሐሴ 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በቁጥጥር ሥር ውለው ነሐሴ 4 ቀን 2007 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው 11 ቀናት ለተጨማሪ ምርመራ ተሰጥቶባቸው የነበሩት አቶ ወንድሙ፣ በሰው መግደል ወንጀል የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽኖች ያደረጉት የምርመራ መዝገብ ቀርቦ እየተጣራባቸው መሆኑ ተነግሯል፡፡ 

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ነሐሴ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ተጠርጣሪውን አቅርቧቸዋል፡፡ ቀደም ብሎ በተፈቀደለት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ 13 ሚሊዮን ብር የተንቀሳቀሰበት ሰነድ ከባንክ ተፈልጐ መሰባሰቡን፣ በፌዴራልና በክልል ባሏቸው ቤቶች ብርበራ መካሄዱን፣ ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የሲዲ መረጃ መሰብሰቡንና የሁለት ምስክሮችን ቃለ መቀበሉን መርማሪ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ አስረድቶ፣ የሚቀረው ምርመራ እንዳለ በመግለጽ ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቋል፡፡

መርማሪ ቡድኑ ተጨማሪ ቀናት የጠየቀበትን ምክንያት ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዳው፣ ከአዲስ አበባና ከፌዴራል ፖሊስ የነፍስ ግድያ ወንጀል ምርመራ መዝገብ መጥቶለት፣ ምርመራው በደንብ መካሄዱን መገምገም ከፌዴራልና ከክልል የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ተጨማሪ የሰነድ ማስረጃዎች መሰብሰብ፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ የተለያዩ ሰነዶችን መሰብሰብ፣ ከኦሮሚያ ገቢዎች የኢንስፔክሽን ሪፖርት መሰብሰብና ሌሎች ተጠርጣሪዎችን መያዝ እንደሚቀረው አስረድቷል፡፡ 

በተጠርጣሪው ዘጠኝ ቤቶችና በአራት ከተሞች የተደረገውን የብርበራ መረጃ መተንተን፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ ያሰባሰቡትን የመሬትና የቤት ባለቤትነት ሰነድና  ከተለያዩ ባንኮች ገንዘብ የተቀባበሉባቸውን ደረሰኞች ማስረጃ መሰብሰብ እንደሚቀረው፣ ቡድኑ ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት የተጠየቀው ተጨማሪ የምርመራ ቀን እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡

አቶ ወንድሙ በበኩላቸው ባቀረቡት ተቃውሞ፣ መርማሪው የፈለገውን ሰነድም ሆነ ሌላ ነገር ማግኘቱን ገልጸዋል፡፡ መርመሪዎች እሳቸውን ካሰሩ በኋላ መኖሪያ ቤታቸው በመሄድ የአምስት ዓመት ሕፃን ልጃቸው ላይ ሽጉጥ በመደቀን ያደረጉትን ማስፈራራት አምርረው ተቃውመዋል፡፡

ከታሰሩበት ዕለት ጀምሮ ማንም ቤተሰብ እንዳልጠየቃቸው፣ ምክንያቱ ደግሞ መርማሪዎቹ እንዳስፈራሯቸው መስማታቸውን ተናግረዋል፡፡ እሳቸው የክልል ተሿሚና የካቢኔ አባል መሆናቸውን በመግለጽ፣ መጠየቅ ካለባቸውም በክልል እንጂ በፌዴራል አለመሆኑን አስረድተዋል፡፡ ኮሚሽኑ በመገናኛ ብዙኃን ስማቸውን እያጠፋ መሆኑን በመግለጽ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡

የኮሚሽኑ መርማሪ በበኩላቸው አቶ ወንድሙ ያቀረቡትን አቤቱታ የሰሙት በዕለቱ ለችሎቱ ሲያስረዱ መሆኑን ገልጸው፣ እሳቸው እንዳሉት ሆኖ ከተገኘ ኮሚሽኑ በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ አሳውቀዋል፡፡ ሥልጣኑ የክልል ነው ስለመባሉ ግን፣ የግብር ጉዳይ የፌዴራሉ ጭምር መሆኑን በመጥቀስ አስረድተዋል፡፡ የቫትንና የጉምሩክ ቀረጥን በሚመለከት የማየት ሥልጣን የፌዴራል ፍርድ ቤቶች መሆኑንም አክለዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ አቶ ወንድሙ ያቀረቡትን አቤቱታ በሚመለከት በሰጠው ትዕዛዝ ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው መከበር እንዳለበት አሳስቦ በቤተሰብ፣ በዘመዶቻቸው፣ በሃይማኖት አባትና በሕግ አማካሪያቸው የመጐብኘት መብት እንዳላቸው በመግለጽ ኮሚሽኑ ተግባራዊ እንዲያደርግ አዟል፡፡ 

በሕፃን ልጃቸው ላይ ተደረገ የተባለው እውነት ከሆነና ማስረጃ ከቀረበ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቆ፣ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በሕግና በአግባቡ መመርመር እንዳለበት፣ ከዚያ ውጪ የሆነ በግዳጅና በኃይል የሚገኝ መረጃን ውድቅ እንደሚያደርግ በማሳሰብ፣ መርማሪ ቡድኑ ለጠየቀው ተጨማሪ ምርመራ አሥር ቀናትን ፈቅዷል፡፡ 

 

አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ከአክሰስ ቦርድ ሰብሳቢነታቸው ተነሱ

‹‹መንግሥት አክሲዮን ማኅበሩን ለማፍረስ በሚደረግ እንቅስቃሴ ላይ ጥብቅ ዕርምጃ ይወስዳል›› አቶ ኑረዲን መሐመድ፣ የቴክኒክ ኮሚቴ ሰብሳቢ

በድንገት ከአገር ወጥተው በተባበሩት ኤምሬት ዱባይ ከተማ ለሁለት ዓመታት ከቆዩ በኋላ ከመንግሥት ጋር ባደረጉት ድርድር ከለላ ተሰጥቷቸው ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣

አገር ውስጥ ከተመለሱ በኋላ ቀድሞ ወደነበሩበት የአክሰስ ሪል ስቴት አክሲዮን ማኅበር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተሾሙ ቢሆንም፣ ‹‹ምንም ዓይነት ሥራ አልሠሩም›› ተብለው ከሰብሳቢነታቸው ተነሱ፡፡

የቦርድ አባላት ነሐሴ 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ባደረጉት አስቸኳይ ስብሰባ አቶ ኤርሚያስን ከቦርድ ሰብሳቢነታቸው ያነሷቸው፣ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ከተሾሙ ከመጋቢት 26 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በእሳቸው ሰብሳቢነት በርካታ ስብሰባዎችን ያደረጉ ቢሆንም፣ በሥነ ሥርዓት ጉዳዮችና አሉባልታ ወሬዎች ላይ ከመነታረክ ያለፈ ምንም ዓይነት ቁምነገር አለመሥራታቸውን የቦርዱ አስቸኳይ ስብሰባ ቃለ ጉባዔ ያስረዳል፡፡ አቶ ኤርሚያስ በሕግና በሥርዓት ሊሠሩ ባለመቻላቸው፣ ቦርዱ የኩባንያውን ችግር ለመፍታት በመንግሥት ለተቋቋመው የቴክኒክ ኮሚቴ በማሳወቁ ኮሚቴው መመርያ ሰጥቶ እንደነበርም በቃለ ጉባዔው ተገልጿል፡፡ ኮሚቴው በሰጠው መመርያ ቦርዱ ስለ አክሰስ ሪል ስቴት አካሄድ ፍኖተ ካርታ እንዲያቀርብ አዞ የነበረ ቢሆንም፣ ጥቃቅንና የትም የማያደርሱ ድርጅቱን ሥጋት ላይ የሚጥሉ ነገሮች ከመነሳታቸው ባለፈ ፋይዳ ያለው ነገር ሊሠሩ ባለመቻላቸው ከቦርድ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን የቦርዱ ቃለ ጉባዔ አስታውቋል፡፡ አክሰስ ሪል ስቴት በአቶ ኤርሚያስ ሲመራ ወደ ድርጅቱ ካዝና መግባት ያለባቸውን ተሰብሳቢ ሒሳቦች ከማንሳት ይልቅ ዕዳ መቀበልን እንዲያስቀድም መደረጉን ቦርዱ ገልጿል፡፡ ድርጅቱን ከውድቀት ሊያነሳ የሚችል ብዙ ተሰብሳቢ በሕጋዊ ሰነድ የተያዘ ገንዘብ ቢኖርም፣ በእሱ ጉዳይ ላይ ውይይት አለመደረጉንም ጠቁሟል፡ 

አቶ ኤርሚያስ ወደ አገር ቤት የተመለሱበት ዓላማ እንዲያሳካ በሚል ቦርዱ ብዙ ነገሮችን እያየ እንዳላየ ማለፉን ጠቁሞ፣ አሁን ግን ሥጋው መሬት ላይ እያለ የደረቀ ቋንጣ እያወረደ መሆኑን በመገንዘብ ዕርምጃውን ለመውሰድ መገደዱን ገልጿል፡፡ አቶ ኤርሚያስ ያለ ቦርዱ ተሳትፎ በራሳቸው ለተለያዩ ድርጅቶች ደብዳቤ መጻፋቸው፣ ቅጥር ማካሄዳቸውና ‹ፒንግል ሪል ስቴት› ከተባለ የቻይና ኩባንያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውን ቦርዱ ጠቁሞ፣ ነገር ግን ኩባንያው በሕይወት ይኑር አይኑር የሚታወቅ ነገር እንደሌለ አስታውቋል፡፡ በአጠቃላይ አቶ ኤርሚያስ ከነሐሴ 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ከቦርድ ሰብሳቢነታቸው ተነስተው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩት ወ/ሮ መብራት ወልደ ትንሳዔ በሰብሳቢነት እንዲመሩ በመስማማት መወሰኑን አስታውቋል፡፡ 

አቶ ኤርሚያስ መሥራችና የቦርድ ሊቀመንበር ከነበሩበት አክሰስ ሪል ስቴት፣ በአገር ውስጥና በተለያዩ አገሮች የሚኖሩ ከ2,000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች የቤት ግዢ የፈጸሙ ቢሆንም፣ እስካሁን ድረስ ቤትም ሆነ ገንዘባቸውን አለማግኘታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ አቶ ኤርሚያስ በድንገት ከአገር ሲወጡ ቤት ገዢዎቹ የተለያዩ ተቃውሞዎችን ሲያቀርቡ ከርመው፣ በመጨረሻ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ከአቶ ኤርሚያስ ጋር በመደራደር ለተለያዩ ግለሰቦች ቆርጠውት በነበረ ደረቅ ቼክ ምክንያት እንደማይታሰሩ ዋስትና ተሰጥቷቸው፣ በየካቲት ወር 2007 ዓ.ም. ወደ አገር ቤት ተመልሰዋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ በወቅቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ከየካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ሥራ እንደሚጀምሩና ማንኛውም ቤት ገዢ የፈለገውን ማለትም ቤቱን ወይም ገንዘቡን ከነወለዱ እንደሚመልሱ ቃል መግባታቸው በወቅቱ ተዘግቧል፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ቤት ገዢዎች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አቶ ኤርሚያስ እንኳን ገንዘብ ሊመልሱና ስለቤት ሊያናግሯቸው ቀርቶ በአካል አይተዋቸው እንደማያውቁ እየገለጹ ነው፡፡ መንግሥት የሰጣቸውን ተስፋም ማየት ባለመቻላቸው ተስፋ እየቆረጡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ተብሎ ላለፉት ስድስት ወራት ምንም ነገር አለማየታቸውን አስረድተዋል፡፡ 

የአቶ ኤርሚያስ ፍላጐት በተለያዩ መንገዶች ነገሮችን በማጓተት ድርጅቱ እንዲፈርስና ከተጠያቂነት ለመዳን ስለሆነ፣ ቃል የገባው መንግሥት በነገሩ ላይ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ 

በቦርዱ ጽሕፈት ቤት ለሚሠሩ 13 ሠራተኞች የሰኔና የሐምሌ ወር ደመወዝ መክፈል ሳይቻል ቀርቶ ቴክኒክ ኮሚቴውና ከቤት ገዢዎች ለተለያዩ ወጪዎች ከሰበሰበው ገንዘብ አክሲዮን ማኅበሩ ተበድሮ መክፈሉን አስረድተዋል፡፡ ይኼ የሚያሳየው ድርጅቱ ችግር ውስጥ መሆኑን እንደሆነ አስረድተው መንግሥት አስቸኳይ ውሳኔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ 

የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ የንግድ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ኑረዲን መሐመድ ግን በቤት ገዢዎቹም ሆነ በቦርዱ ሐሳብ አይስማሙም፡፡ እሳቸው እንደሚሉት ሰው የፈለገውን ቢያወራ ኮሚቴው መሥራት የሚችለውን እየሠራ እንደሆነና በሥራውም ውጤታማ መሆኑን ነው፡፡ 

ከየአቅጣጫው እየጮሁ የሚገኙት ከቤት ገዢዎቹ አሥር በመቶ የማይሆኑትና አቶ ኤርሚያስ ሲነኩ የሚነኩ ሰዎች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ የሕግ ከለላ የተሰጣቸው ሥራዎች ተስተካክለው እንዲሄዱ እንጂ ከሕግ ተጠያቂነት ለማዳን አለመሆኑን የገለጹት አቶ ኑረዲን፣ በአቶ ኤርሚያስ በኩል ስላሉ ሰዎች መረጃ መጠየቅ ሲጀመር የእሳቱ ወላፈን የሚነካቸው ሰዎች ብዙ ነገር ለማድረግ እየጣሩና እየተወራጩ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ከአንድ ወይም ሁለት ሳምንት በኋላ በተለይ አምቼ አካባቢ ያለው ፕሮጀክት ይፋ እንደሚደረግና ሥራ እንደሚጀመር የጠቆሙት ሰብሳቢው ቦርዱ፣ የቦርዱ አባላትና አስፈጻሚው የየራሳቸው አጀንዳ ስላላቸው ምንም ነገር እንዳልተሠራ የሚያስወሩት ወሬ እንደሚቆም ተናግረዋል፡፡ ሁሉም የሚሮጠው የራሱን መብት ለማስከበር መሆኑን ጠቁመው መንግሥት ግን ተረጋግቶና ሁሉንም ነገር በአግባቡ በመሥራት እያንዳንዷን ነገር ማስተማሪያ ማድረግ እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡ 

አክሲዮን ማኅበሩ ከፈረሰ ተጠያቂነት ስለማይኖር በንግድ ሚኒስቴር የአክሲዮን ማኅበራት ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት የመጀመሪያ የቤት ሥራው ጥንቃቄ አድርጐ ጅምሩን ዳር ማድረስ መሆኑንም አቶ ኑረዲን አስረድተዋል፡፡ አክሲዮን ማኅበሩን ለማፍረስ የሚደረግ እንቅስቃሴ ከታየ መንግሥት ጥብቅ ዕርምጃ እንደሚወስድም አስረድተዋል፡፡ የሆነ ያልሆነ መረጃ ወጥቶ ቤት ገዢውን ተስፋ የሚያስቆርጥ ወሬ እንደሚሰማ የገለጹት አቶ ኑረዲን፣ መንግሥት አቶ ኤርሚያስ ሳይኖሩ ኃላፊነት መውሰዱን ቤት ገዢው መዘንጋት እንደሌለበት አስታውሰዋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ ወደ አገር ቤት እንዲመጡ የተደረገው ሥራ እንዲሠሩ፣ ሚስጥሮችን እንዲያወጡና ሦስተኛ ወገኖችን እንዲታገሉ መሆኑን የገለጹት አቶ ኑረዲን፣ ቦርዱ ራሱ ሾሞ ራሱ እንዳወረዳቸው መግለጹ አግባብ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌላ መሾምም ሆነ መነሳት ካለባቸው በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤት የፀደቀ ሰነድ መኖር እንዳለበት ተናግረዋል፡፡ ይኼ ባልሆነበት ሁኔታ ስለሚካሄደው ነገር የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸዋል፡፡ አሁን በቦርዱም ሆነ በጥቂት ቤት ገዢዎች እየተደረገ ያለው ነገር ሥራውን የሚያስትና የሚያደናቅፍ አለመሆኑን አቶ ኑረዲን ተናግረዋል፡፡     

ቦርዱ ባሳለፈው ውሳኔና ቤት ገዥዎች እያቀረቡት ስላለው ተቃውሞ ምላሽ እንዲሰጡ አቶ ኤርሚያስን ሪፖርተር ቢሮቸአው ድረስ በመሄድና በስልክ ጭምር ለማግኘት ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡    

 

እነ ሃብታሙ አያሌውን ለመፍታት/ከበር መልሶ ለመያዝ/ የደህንነት ቢሮ ትእዛዝ እየተጠበቀ ነው:: የቀረበባቸው ክስ ከጥርጣሬ ባለፈ በሽብርተኝነት ላይ ተሳትፎ አላደረጉም በሚል በነጻ እንዲሰናበቱ ከተደረጉት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን ለመፍታት የደህንነት ቢሮ ትእዛዝ እየተጠበቀ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በፍርድ ቤት መዳፈር ወንጀል ተለጥፎባቸው እዛው …

እነ ሃብታሙ አያሌውን ለመፍታት/ከበር መልሶ ለመያዝ/ የደህንነት ቢሮ ትእዛዝ እየተጠበቀ ነው:: Read more »