የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆኑት አቶ መኳንንት ብርሃኑ መኖሪያ ቤታቸው ተክብቦ በፖሊስ እየታደኑ መሆኑንን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አመልክተዋል፡፡ የአቶ መኳንንት ቤት በፌደራል ፖሊስ መከበቡ የታወቀ ሲሆን፣ አቶ መኳንንት ግን ለሳምንት ያህል ቤታቸው እንዳልገቡ ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል፡፡ ቤታቸው የካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ አካባቢ የሚገኘው አቶ መኳንንት ብርሃኑ፣ መኖሪያ ቤታቸው እሳቸውን ለመያዝ በታዘዙ ፖሊሶች ተከብቦ ይገኛል ተብሏል፡፡ ፖሊስ አቶ […]

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው እየታየ የሚገኙት የዞን 9 ጦማርያን ዛሬ ሐምሌ 13/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ሐምሌ 1/2007 ዓ.ም ‹‹ክሳችሁ ተቋርጧል›› በሚል ከእስር ከተፈቱት ተለይተው በእስር ላይ የሚገኙት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አቤል ዋበላ ዛሬ ለ31ኛ ጊዜ […]

አገዛዙ 11ኛዋ ሰአት ላይ በደጋፊወቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑ ተሰማ! የወያኔ ስራ አስፈጻሚዎች በደጋፊዎቹ ክፉኛ እየተሞገተ መሆኑን ከውስጥ አወቅ ምንጮች ያገኘናቸው የግምገማ መርጃወች አመላከቱ።የስር አቱ ደጋፊዎችና ታማኝ የሚባሉ ካድሬወች ያነሱት ነጥብ ሲጨመቅ እንደሚከተለው ቀርቧል። “በተለይ ለእኛ ስለ ወቅታዊ ሁኔታወች ስውር የሆነብን ምክንያት ምንድን ነው፧ እኛም የፓርቲያችን እና የአገራችን ጉዳይ ያገባናል። እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ ዜናወችና መረጃወችስ እንዲደርሱን […]

የአሜሪካው ፕ/ት ባራክ ኦባማ ይህን የተናገሩት ” በአሜሪካና በኤርትራ የሚገኙ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን ለመወጋት የምታደርገውን ጥረት እያደናቀፉ በመሆኑ የእርስዎ መንግስት የኢትዮጵያን መንግስት ለመርዳት ምን ያክል ዝግጁ ነው ተብሎ ከኢቢሲ ጋዜጠኛ ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው። ጋዜጠኛው የድርጅቱን ስም በግልጽ ከመግለጽ ቢቆጠብም፣ ፕ/ት ኦባማ የሰጡት መልስ ፣ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ምክትል ሃላፊ […]

‹‹የታሰርኩት ቤተሰቦቼን በእሳት አቃጠሉብኝ ብዬ ስለከሰስኩ ነው›› አቶ አንጋው ተገኝ በእነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን የክስ መዝገብ በሽብርተኝነት የተከሰሱት 16 የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ለሀምሌ 17/2007 ዓ.ም ለብይን ተቀጠሩ፡፡ አመራሮቹ ሀምሌ 1/2007 ዓ.ም በጠበቆቻቸው በኩል የክስ መቃወሚያና የዋስትና ጥያቄ አቅርበው የነበር በመሆኑ ዛሬ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም አቃቤ ህግ ለጥያቄው መቃወሚያ እንዲያሰማ ቀጠሮ ተሰጥቶት የነበር ቢሆንም ሳይቀርብ […]

. የትጥቅ ትግሉ ያሰጋው ወያኔ የጎንደር ህዝብን እያሰቃየ መሆኑ ተነገረ፡፡ . ‹ባራክ ኦባማ ሲመጣ ሰልፍ ለመጥራት እያደራጁ ነው በሚል የተከሰሱት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ጉዳይ ፍርድ ቤቱ ለሶስተኛ ጊዜ አላይም ማለቱ . አንድ ሣምንት የዘለቀው የልኳንዳ ቤቶች አድማ እደቀጠለ ነው፤ . የስዊድን ጠቅላይ ሚኒስትር  ከአዲስ አበባ መልስ ወደ ሆስፒታል አመሩ። . የወያኔ መንግስት በአሜሪካ ፍርድ ቤት  ተከሰሰ አሰግድ […]

Minilik Salsawi በዛሬው እለት ከእስር ባልተፈቱ አራቱ የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ላይ ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ሲሆን በቦታው የጦማርያኑ ቤተሰቦች እና ጓደኞቻቸውን ጨምሮ ዲፕሎማቶች እና ጋዜጠኞች በካንጋሮው ፍርድ ቤት ተገኝተዋል::እንዲሁም በቅርቡ የተፈቱት ጋዜጠኞች እና ጦማርያን ርእዮት አለሙን ጨምሮ በፍርድ ቤቱ …

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን የልደታ ካንጋሮ ፍርድ ቤት ውሎ ለ32ኛ ጊዜ ለሓምሌ 22 ተቀጠረ:: Read more »

የቀድሞው የኢትዮጵያ ቴሌኮሙዩኒኬሽን ኮርፖሬሽን (ኢትዮ ቴሌኮም) ዋና መሥሪያ ቤት ዋና መሐንዲስና የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ሁለት ሥራ አስኪያጆች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው፣ ሰኔ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 18ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የመሠረተባቸው ተጠርጣሪዎች፣ የዋናው መሥሪያ ቤት ዋና መሐንዲስ የነበሩት አቶ ተክለ ማርያም ለአከ ተክለ ማርያም፣ የኮርፖሬሽኑ የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ምክትል ሥራ አስኪያጅና የማርኬቲንግ ኃላፊ የነበሩት አቶ መስፍን ሙርጋና የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ጌታቸው ተረፈ አየለ ሲሆኑ፣ በግል ሥራ የተሰማሩ አቶ ግርማ ተስፋዬ የተባሉ ግለሰብም በክሱ ተካተዋል፡፡ 

ተከሳሾቹ የማይገባ ጥቅም ለማግኘትና ለሌላ ሦስተኛ ወገን ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ፣ በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡ ክሱ እንደሚያስረዳው፣ አቶ ተክለ ማርያም ያላቸውን የቴክኖሎጂ ዕውቀት፣ ልምድና ክፍተት በመጠቀም በግል ሥራ ከሚተዳደሩት አቶ ግርማ ጋር ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ (ናዝሬት) ይሄዳሉ፡፡ አዳማ እንደደረሱ ለሕገወጥ ዓላማ ማስፈጸማያ የሚውል ቤት በደላላ አማካይነት አቶ ታደሰ ጅማ ከሚባሉ ግለሰብ ይከራያሉ፡፡ የቤቱን ውል ከመፈጸማቸው በፊት ቤት አከራዩ አቶ ታደሰ ጂማ 30 ቀጥታ የስልክ መስመሮችን ከቴሌ ማስገባት እንዳለባቸው ይስማማሉ፡፡ አቶ ተክለ ማርያም አብረዋቸው የሚሠሩ የውጭ አገር ዜጎች እንዳሉም ለአከራዩ አቶ ታደሰ እንደነገሯቸው ክሱ ያብራራል፡፡ 

ከውጭ አገር የሚመጡት ኢንቨስተሮች በመሆናቸው ለስልኩ ወጪ ክፍያ ምንም ሥጋት እንዳይገባቸው ለአቶ ታደሰ ተነግሯቸው፣ የስልክ መስመሮቹ ከገቡ በኋላ ኅዳር 21 ቀን 1995 ዓ.ም. በንግድ ሥራ የሚተዳደሩት ሁለተኛ ተከሳሹ አቶ ግርማ ተስፋዬና አቶ ታደሰ የቤት ኪራይ ውሉን መፈጸማቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ አቶ ተክለ ማርያም ሳተላይት መቀበያ መሆኑን እያወቁ ከአቶ ግርማ ጋር በመመሳጠር በተከራዩበት ቤት ዲሽ በመትከል፣ አገሪቱ ከዘርፉ ልታገኝ የሚገባትን ገቢ እንድታጣ በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ 

አቶ ግርማ የተባሉት ተከሳሽ ቤት አከራዩን አቶ ታደሰን በዜግነት ጥቁር አሜሪካዊ እንደሆኑ በመግለጽ ከተዋወቋቸው በኋላ፣ አብረዋቸው ከነበረ ኤም ዴቪድ ከሚባል ነጭ አሜሪካዊ ጋር ያስተዋውቋቸዋል፡፡ ወደ ተከራዩት ቤት በመውሰድ በአከራይ ተከራይ ውል ላይ ካስፈረሟቸው በኋላ፣ ስልክ ላስገቡበት 16,500 ብር ለቴሌ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት እንደከፈላቸው ክሱ ይገልጻል፡፡ 

ለሕገወጥ ድርጊት የሚውሉ ዘመኑ ያፈራቸውን ዕቃዎች በኤርፖርት ታክሲ ጭነው አዳማ በመውሰድ፣ በታኅሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ዲሹን መትከላቸውንም ክሱ አክሏል፡፡ በመሆኑም በወንጀሉ በመሳተፍ በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን የዓቃቤ ሕግ ክስ ይገልጻል፡፡ 

የቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅና የማርኬቲንግ ኃላፊ የነበሩት አቶ መስፍን ሙርጋም፣ ቤት ያከራዩት አቶ ታደሰ 30 ቀጥታ መስመር እንዲገባላቸው ጥያቄ ሲያቀርቡ፣ የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ተረፈ ማኅተም ሳያደርጉ የመሩትን ደብዳቤ ‹‹ለምን?›› ብለው ምክንያቱን ሳያረጋግጡ የቀረበውን ጥያቄ በማፅደቃቸው፣ በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን ክሱ ይገልጻል፡፡ አቶ ጌታቸውም ኮርፖሬሽኑ ያወጣውን የደንበኞች አገልግሎት አፈጻጸም መመርያ በመጣስ፣ ስልኮቹ ለምን ዓላማ እንደሚውሉ ሳይጠይቁና ሳያጣሩ በተዋረድ ላሉ ኃላፊዎች በመምራትና በማፅደቃቸው፣ በሕዝብና መንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስና አላግባብ ሥልጣንን መገልገል ወንጀል እንደተከሰሱ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ 

ሁሉም ተጠርጣሪዎች በሕዝብና በመንግሥት ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ በግብረ አበርነት በፈጸሙት ሥልጣንን ያላግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በሌሉበት ስለተከሰሱ፣ ኮሚሽኑ ተከሳሾቹን አፈላልጎ ለሐምሌ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. እንዲያቀርብ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 18ኛ ወንጀል ችሎት አዟል፡፡ 

 

በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረውን የሳንቲም እጥረት ለመሸፈን እየተደረጉ ያሉ ሙከራዎች ሁሉ ባለመሳካታቸው ከፍተኛ ውጥረት እንደፈጠረበት ታውቋል!ህዝበ ሙስሊሙ የመገበያያ ሳንቲሞችን ከገበያ በማስወጣት መንግስት ላይ ኢኮኖሚያዊ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደረበት የሚገኝ ሲሆን አሁንም ይኸው መርሀ ግብር እየተከናወነ በመሆኑንና መንግስት እየደረሰበት ላለው ችግር ምላሽ …

በኢትዮጵያ የተፈጠረው የሳንቲም እጥረት ከፍተኛ ውጥረት ፈጥሯል::የውጪ ብድር እዳ ኢኮኖሚውን በዜሮ ድምር ውስጥ ከቶታል:: ምንሊክ ሳልሳዊ Read more »

በኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጠረውን የሳንቲም እጥረት ለመሸፈን እየተደረጉ ያሉ ሙከራዎች ሁሉ ባለመሳካታቸው ከፍተኛ ውጥረት እንደፈጠረበት ታውቋል!ህዝበ ሙስሊሙ የመገበያያ ሳንቲሞችን ከገበያ በማስወጣት መንግስት ላይ ኢኮኖሚያዊ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደረበት የሚገኝ ሲሆን አሁንም ይኸው መርሀ ግብር እየተከናወነ በመሆኑንና መንግስት እየደረሰበት ላለው ችግር ምላሽ …

በኢትዮጵያ የተፈጠረው የሳንቲም እጥረት ከፍተኛ ውጥረት ፈጥሯል:: የውጪ ብድር እዳ ኢኮኖሚውን በዜሮ ድምር ውስጥ ከቶታል:: ምንሊክ ሳልሳዊ Read more »

በታኅሳስ ወር 2007 ዓ.ም. ኢትዮ ቴሌኮም ኤሪክሰን ለተባለው የስዊድን ኩባንያ ሰጥቶ ከነበረው የቴሌኮም ማስፋፊያ አራት ፕሮጀክቶች መካከል፣ መዘግየት አይቼበታለሁ ያለውን የአንዱን ፕሮጀክት (ሰርክል) ውሉን ሰርዞ ሁዋዌ ለተባለው የቻይና ቴሌኮም ኩባንያ መስጠቱን አስታወቀ፡፡ 

ኤሪክሰን ከማስፋፊያ ፕሮጀክቶች መካከል አራት ‹ሰርክሎች›ን ለመሥራት ተዋውሎ የነበረ ቢሆንም፣ በተለይ ደቡብ ደቡብ ተብሎ በተለየው የማስፋፊያ ፕሮጀክት አንዱን ‹ሰርክል› በውሉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ማጠናቀቅ ባለመቻሉ መነጠቁን፣ የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ አብዱራሒም አህመድ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

አቶ አብዱራሒም ለሁዋዌ በቀጥታ የተሰጠውን ፕሮጀክት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ ሁዋዌ ከዚህ በፊት የወሰዳቸውን ፕሮጀክቶች በፍጥነትና በተሻለ አፈጻጸም ተግባራዊ ማድረግ በመቻሉ ከኤሪክሰን ተነጥቆ የተሰጠው መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡ 

‹‹ሁዋዌ በአዲስ አበባ ያከናወናቸውን የማስፋፊያ ሥራዎች ከውሉ ቀድሞ መጨረስ በመቻሉ፣ በቀጥታ እንዲሰጠው ተወስኗል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

የኤሪክሰን ፕሮጀክትን አስመልክተው አቶ አብዱራሒም ሲገልጹ፣ ፕሮጀክቱ በሰኔ ወር መጨረሻ ላይ አጠናቆ ማስረከብ ባለመቻሉ፣ የመጀመርያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አካል የነበረውን የቴሌኮም ማስፋፊያ ሥራ ማጓተቱን ጠቁመዋል፡፡ 

‹‹ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ሁዋዌ ስድስት ‹ሰርክሎች›ን እያከናወነ ሲሆን፣ በእስካሁን አፈጻጸሙ በጣም አመርቂ የሚባል ውጤት እያየንበት ነው፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡ እነዚህም የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች የሰሜን፣ የሰሜን ምሥራቅ፣ የሰሜን ምዕራብ፣ የምሥራቅና የአፋር ቀጣናዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በመላ አገሪቱ የሞባይል አገልግሎት ኔትወርክ ተደራሽነትን  ለማስፋፋት ባወጣው ጨረታ፣ ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች ሁዋዌና ዜድቲኢ ያሸነፉ ቢሆንም፣ ዜድቲኢ በስምምነቱ መሠረት እንቅስቃሴ ባለመጀመሩ ከወሰዳቸው ስድስት የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች አራቱ ለስዊድኑ ኤሪክሰን የቴሌኮም ኩባንያ መተላለፋቸው  በወቅቱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ታኅሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል ኢትዮ ቴሌኮምና ኤሪክሰን ባደረጉት የቬንደር ፋይናንሲንግ ፕሮጀክት ማስፋፊያ ስምምነት፣ የቻይናው ዜድቲኢ ቴሌኮም ኩባንያ ከአገሩ አቻው ሁዋዌ ቴሌኮም ኩባንያ ጋር ከተካፈለው የ800 ሚሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ውስጥ፣ አራቱ ለኤሪክሰን መሰጠታቸውን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

ዜድቲኢና ሁዋዌ በመላው ኢትዮጵያ ያሉትን 13 ‹ሰርክሎች› ወይም የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ሲካፈሉ፣ ሁዋዌ አዲስ አበባን ጨምሮ ሰባት ‹ሰርክሎች›ን ሲወስድ ዜድቲኢ ስድስት ‹ሰርክሎች›ን ለመሥራት መዋዋሉ ይታወሳል፡፡

 

የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ማውጫ ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉ ተጠቆመ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. 40/60ን ጨምሮ 40 ሺሕ የሚሆኑ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ እንደሚያወጣ የገለጸ ቢሆንም፣ የዕጣ ማውጫውን ቀን ላልተወሰነ ጊዜ ማስተላለፉ ተጠቆመ፡፡ 

ዕጣ ይወጣላቸዋል ከተባሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች በተለይ ለመጀመሪያ ጊዜ በዕጣ ይከፋፈላል የተባለው 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት፣ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት አለፍ ብሎ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊትና ሰንጋ ተራ የሚገኙት ሕንፃዎች ግንባታ የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ አብረው መጠናቀቅ የነበረባቸው መሠረተ ልማቶች ባለመጠናቀቃቸው የዕጣ መውጫው ጊዜ እንዲራዘም መደረጉን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ 

የአስተዳደሩ ካቢኔና ቦርድ ተሰብስቦ ውሳኔ አለማሳለፉም ለዕጣው አለመውጣት ሌላው ምክንያት መሆኑን የጠቆሙት ምንጮች፣ የአስተዳደሩ ከፍተኛ ሹማምንት በሕዝብ መገናኛ ብዙኃን ሳይቀር ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚተላለፉ ቤቶች እንዳሉ ሲገለጽ ከርሞ፣ ቃላቸው አለመጠበቁ ‹‹ለምን?›› የሚል ጥያቄ እያስነሳ መሆኑንም አክለዋል፡፡

የመሠረተ ልማት አለመሟላት እንደ ምክንያት ሊወሰድ እንደማይችል የሚናገሩት ምንጮች፣ በአሥረኛው ዙር ዕጣ ከወጣባቸው 35 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች መካከል የአብዛኞቹ ሳይቶች መሠረተ ልማታቸው ገና ያልተጀመረ በመሆኑ ነው፡፡ 

ለሪፖርተር አስተያየት የሰጡ የተወሰኑ የ40/60 ተመዝጋቢዎች፣ ሙሉ በሙሉ ክፍያ የፈጸሙ ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው ገልጸው፣ አሁን ግን ዋጋው በጣም ሊጨምር ስለሚችል ሙሉ በሙሉ የከፈሉም ቢሆኑ ተጨማሪ ክፍያ እንደሚጠየቁ መስማታቸው አሳስቧቸዋል፡፡ በሌላ በኩል ሁሉም በዕጣው ተካተው ዕድለኞች በዕጣ እንደሚያገኙ፣ የቤቶቹን መገንባት ያዩ ሌሎች ተመዝጋቢዎች በመሀል ሙሉ በሙሉ መክፈላቸውም ስላሳወቁ፣ ሲጀመር አጠናቀው ከከፈሉት ጋር ሊቀላቀሉ መሆኑንና ሌሎች ወሬዎችን እየሰሙ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተባለው ጊዜም ዕጣ አለመውጣቱ እንዳሳሰባቸው ይናገራሉ፡፡

የ20/80 ተመዝጋቢዎች በበኩላቸው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ዕጣው ሰኔ 30 እና እስከ ነሐሴ መጨረሻ ድረስ ወጥቶ ዕድለኞች የቤት ባለቤት እንደሚሆኑ የተነገረበት ወቅት የምርጫ ጊዜ በመሆኑ፣ ሕዝቡን ለመያዝ ነው የሚል ግምታቸውን ዕውን እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ ይህ ባይሆን ኖሮ ዕጣው በተባለው ጊዜ መውጣት ነበረበት ሲሉም ይከራከራሉ፡፡ 

ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ዕጣ እንደሚወጣ በአስተዳደሩ ከፍተኛ ሹሞች ከገለጹ በኋላ ለምን ዕጣውን እንዳላወጡ ወይም ያልወጣበትን ምክንያት እንዲገልጹ፣ የአዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትንም ሆነ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲን ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡ 

ነገር ግን አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ባልደረባ እንደሚሉት፣ ዕጣው ያልወጣው በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ የመጀመሪያው የአስተዳደሩ ካቢኔና ቦርድ ተሰብስቦ ውሳኔ ባለማስተላለፉ ሲሆን፣ ሌላው በታሰበበት ወቅት ይጠናቀቃሉ የተባሉ መሠረተ ልማቶች ባለመጠናቀቃቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዋናነት የ40/60 የቤት ፕሮግራም የመጀመሪያ ከመሆኑ አንፃር ሁሉም ነገር ተጠናቆ፣ ዕጣው በወጣበት ዕለት ለባለዕድለኞች ወዲያውኑ ቁልፍ ለማስረከብ በመታሰቡ መሆኑን አክለዋል፡፡

   

 

በአልሸባብ ተመልምለው የሕዋስ (ሴል) አባላት ናቸው የተባሉ ኢትዮጵያ ውስጥ በተመረጡ ቦታዎችና በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ላይ የሽብር ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር የዋሉ የተባሉ አምስት ተጠርጣሪዎች፣ ኢትዮጵያውያን፣ ሐምሌ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32 (1/ሀ)ን በመተላለፍ በዋና ወንጀል ተካፋይ በመሆን፣ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 38 (1 እና 2) በመተላለፍ ወንጀል ለመፈጸም አድማ በማድረግና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ (4)ን በመተላለፍ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም የማቀድ፣ የመዘጋጀት፣ የማሴርና የማነሳሳት ሙከራ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል ብሎ ክስ የመሠረተባቸው፣ በድሪ የሱፍ ሮባ፣ አነስ ኡስማን ዑመር፣ አህመድ ኑር ሳኒ፣ መሐመድ አህመድ ኡስማንና እስማኤል አደም መሐመድ ናቸው፡፡

ዓቃቤ ሕግ ለፌዴል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ እንደሚያስረዳው፣ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡ 

ተከሳሾቹ ከአልሸባብ ጋር በመስማማትና አባል በመሆን ከሶማሊያ ግዛት ወደ ኢትዮጵያ የሚላኩ ተቀጣጣይ ፈንጂዎች መሥራት የሚችሉ የአልሸባብ የፈንጂ ሥራ ባለሙያዎችን ለመቀበል፣ ለፈንጂ መሥሪያ የሚሆን ቤት ለመከራየት ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡

በድሪ የሱፍ ሮባ የተባለው ተጠርጣሪ በሽር ቱሬ በሚባል የአልሸባብ አመራር በ1999 ዓ.ም. በአባልነት ከተመለመለ በኋላ፣ ሞቃዲሾ ውስጥ በሚገኘው አቡሐረሬ ተብሎ በሚጠራው መስጊድ ውስጥ ለስድስት ወራት ወታደራዊና የፖለቲካ ትምህርት ሥልጠና መውሰዱን ክሱ ያስረዳል፡፡ ተጠርጣሪው በ2002 ዓ.ም. ወደ መቋዲሾ በመሄድ ለአልሸባብ አባል የሚሆኑ ወጣቶችን በመመልመል ለሥልጠና እዚያ እንዲሄዱ ሲያዘጋጅ እንደነበርም በክሱ ተጠቁሟል፡፡ 

ግለሰቡ ጥቃት ለመፈጸም ከሞቃዲሾ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት የሚመጡትን የህዋስ አባላት መኖሪያ ቤት ተከራይቶ ለማስቀመጥ፣ የተመለሱትን ወጣቶች በኃላፊነት ለመምራት፣ መረጃ እየሰበሰበ ለአልሸባብ አባላት እንዲልክ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ዘርዝሯል፡፡

አብዱልአዚዝ አልዩ (አቡ ያሲን) የተባለ የአልሸባብ አመራርና የፈንጂ ባለሙያ በ2006 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ገብቶ ባሌ ሮቤ ከተማ ውስጥ መልምሎ በህዋስ ያራጃቸውን ስድስት አባላት፣ አንደኛ ተከሳሽ እንዲመራቸው ኃላፊነት መውሰዱንም ክሱ ያስረዳል፡፡

ሻሸመኔ ከተማ ውስጥ ‹‹ቁርዓን አስተምራለሁ ወይም የቁርዓን መምህር ነኝ›› በሚል ሽፋን አባላትን መመልመልና ማደራጀት እንዳለበት በሽር ቱሬ ከሚባለው የአልሸባብ አመራር ተልዕኮ መቀበሉንም ዓቃቤ ሕግ በክሱ ጠቅሷል፡፡ አገር ውስጥ ባሉ የተለያዩ ባንኮችም ገንዘብ ይላክላቸው እንደነበር የገንዘቡን መጠንና የባንኮቹን ስም ጠቅሶ ዓቃቤ ሕግ በክሱ አካቷል፡፡

በኅዳር ወር 2007 ዓ.ም. በጊኒር በኩል ወደ ኢትዮጵያ ይገባል ለተባለው የአልሸባብ አመራር አብዱላዚዝ፣ በነገሌ ቦረና በኩል በታኅሳስ ወር 2007 ዓ.ም. ፈንጂ ይዘው የሚገቡትን አባላት አንደኛ ተከሳሽ ሻሸመኔ በሚገኘው ቤቱ አሳርፏቸው ፈንጂ የሚሠራበትን ማቴሪያል እንዲያዘጋጅና የማፈንጃ ዒላማዎችን እንዲያጠና ተልዕኮ ተቀብሎ ይንቀሳስ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ ሻሸመኔ፣ አሰላና ባሌ ሮቤ ከተሞች ውስጥ ባንክ ቤትና ፖስታ ቤት መኖር አለመኖሩን አጥንቶ እንዲቆይም ትዕዛዝ ተሰጥቶት እንደነበር አክሏል፡፡ ተጠርጣሪው የሽብር ቡድኑ አደራጅና አመራር በመሆን ተሳታፊ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በዝርዝር ገልጿል፡፡ 

ሁለተኛው ተጠርጣሪ ተከሳሽ አነሰ ኡስማንም እንደ አንደኛ ተከሳሽ በተለይ ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ ውስጥ በመንቀሳቀስ አባላት በመመልመል፣ በተለይም አራተኛና አምስተኛ ተከሳሾችን መልምሎ ወደ ሶማሊያ ሥልጠና ሊልክ ሲል በቁጥጥር ሥር መዋሉን የዓቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ ሦስተኛ፣ አራተኛና አምስተኛ ተከሳችም በሁለተኛ ተከሳሽ ከተመለመሉ በኋላ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሥልጠና ለመውሰድ ወደ ሶማሊያ ለመሄድ በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው በክሱ ተገልጿል፡፡

ተከሳሾቹ ክሱ በችሎት ከተነበበላቸው በኋላ በራሳቸው ጠበቃ ማቆም እንደማይችሉ በመግለጻቸው፣ የተከላካይ ጠበቃ ጽሕፈት ቤት ጠበቃ እንዲመደብላቸው ትዕዛዝ በመስጠት ፍርድ ቤቱ ለሐምሌ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

 

በምስራቃዊ ኢራቅ ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን በጣለው የቦምብ ጥቃት ቢያንስ 120 ሰዎች መገደላቸውንና 130 የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸው ተገለፀ። ከኢራቅ ዋና ከተማ 35 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውና የሺዓ እስልምና ተከታዮች በሚኖሩባት የካን ባኒ ሳድ ከተማ በመኪና ላይ የተጫነው …

ኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድ በአይሲስ የቦምብ ጥቃት 120 ሰዎች ተገደሉ Read more »

(ክንፉ አሰፋ ቶሮንቶ) ሰብለ (ሚሚ) ዲትሪች ለመጨረሻ ግዜ የታየችው እ.ኤ. አ. ጁላይ 10 2014 (ባለፈው አመት) ነበር። የሶስት ልጆች እናት የነበረች የዚህች ኢትዮጵያዊት በድንገት መሰወር ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ ሰንብቷል። ለአመት የጠፋችው ይህች ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሴት በህይወት እንደማትኖር በርካቶች ቢጠረጥሩም፣ ማንንም ሳታማክር በድብቅ ወደ ሃገርዋ ገብታለች የሚሉ አልጠፉም። አለም አቀፍ ፖሊስ በአለም ዙርያ ፍለጋውን ተያያዘው። ሰብለ-ቀብር […]

ጌታቸው በቀለ፣ ጉዳያችን ብሎግ ኢትዮጵያ የገባችበት ብድር ከፍተኛ ቢሆንም የመሰረታዊ ፍላጎቶችን በዋና ከተማ ደረጃም ማዳረስ አልቻለችም በቢልዮን የሚቆጠር ዶላር የት ገባ? አንዲት ሀገር ከጠቅላላ ምርቷ 30 ከመቶው ከለጋሽ ተቋማትና ሃገራት የሚገኝ ብድር ላይ ከተመሰረተ ከፍተኛ የዕዳ ቀውስ ውስጥ እየገባች መሆኗን …

ሀገራችን ከመሸጧ በፊት መድረስ የዜጎች ግዴታ ነው! Read more »

ወንድሜ ሆይ ይህን ለኢትዮጵያ ህዝብ አድርስልኝ።ነገሩ እንዲህ ነው። ምንአልባት አጋዚ ስለሚባል ልዬ ሃይል ሰምተህ ይሆናል። አጋዚ ማለት ከትግራይ ገጠር ቦታወች የሚመለመሉ ወጣቶች ስብስብ ነው። እኒህ ወጣቶች ገና የስምንት አመት እድሜ እያሉ ነው የሚመለመሉት። ከትግረኛ ውጭ ምንም አይነት ሌላ ቋንቋ አይናገሩም። …

የአጋዚ ጦርና የወያኔ ሴራ በውስጥ አወቅ ሲጋለጥ! (የውስጥ መልዕክት) Read more »

**የኦባማ ጉብኝት ለውይይት እንጂ ወንጀለኛን መንግስት ለማጽደቅ እንዳልሆነ አስረዱ ** “የተፈቱት የዞን ዘጠኝ ጋዜጠኞች ፓስፖርታቸው እንኳን እንዳልተመለሰ እናውቃለን:: መጀመርያውኑ መታሰር እልነበረባቸውም:: ሲፈቱም አፈታታቸው ሙሉ አይደለም” ዛሬ እዚህ ዋሺንገተን ዲሲ ላይ ጠንካራ ውይይት ሲካሄድ ነበር:: ውይይቱ የኦባማን የምስራቅ አፍሪካ ጉዞ በተመለከተ ሲሆን : አሜሪካኖቹ መራር መልሶችን ሲመልሱ ተደምጠዋል:: የኦባማ ጉብኝት ለአምባገነኖች ሽፋን መስጠት ሳይሆን ሌሎች በርካታ […]

ለሃያ ስምንት ዓመታት ካገለገሉበት ተቋም ያለአግባብ መባረራቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሣይንስ እና የዓለምአቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር መረራ ጉዲና ተናገሩ።

የሜክሲኮው አደጋኛ የእጽ አዘዋዋሪ ከጥብቁ እስር ቤት እንዴት አመለጠ? በዚህ ቪዲዮ ይመልከቱት አደገኛው የእጽ ነጋዴ ጆአኪም ጉዝማን (ኤልቻፖ) ከፍተኛ ጥበቃ ከሚደረግበት ከሜክሲኮ እስር ቤት ባለፈው ቅዳሜ ምሽት ማምለጡ አይዘነጋም፡፡ ይህ ሲናሎአ የተባለውን የእጽ ዝውውር ወንጀል መረብን የሚመራና በመላው አለም ግዙፍ መረብና የዘረጋ ወንጀለኛ በእስር ክፍሉ ሻወር ቤት አካባቢ በተከፈተ አነስተኛ ጉድጓድ በመጠቀም መሬት ለመሬት ተሸሎክሉኮ […]

የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ወሰነ፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር በአካል ተገናኝታችኋል›› የሚል ክስ የመሰረተባቸው ተከሳሾቹ ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝታችኋል ከተባለ አቶ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ …

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ወሰነ – ነገረ ኢትዮጵያ Read more »

*በደቡብ ክልል ጋሙ ጎፋ ዞን አስተዳደር የህወሓት አሻንጉሊት ባለስልጣናት መካከል መከፋፈል ተፈጠረ፡፡ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የሚከተለው ከቅኝ ገዥዎች የተወረሰ ህዝብን በመከፋፈል ለረዥም ጊዜ የመግዛት ፀረ ኢትዮጵያዊ አንድነት የሆነ የበሰበሰ አውዳሚ ፖለቲካዊ ቀመር ከጎሳዎች አልፎ በመንደርና ቤተሰብ ውስጥ ገብቶ ስር በመስደድ ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በደቡብ ክልል ጋሙ ጎፋ ዞን አስተዳደር የህወሓት አሻንጉሊት ባለስልጣናት መካከል መንደርንና […]

‹እጄን ወደ ላይ አስረው ብልቴ ላይ ሀይላንድ አንጠልጥለውበታል፡፡ ሴቶቹ ሀይላንዱን የሚበቃቸውን ያህል ያወዛውዙታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆኗል፡፡ የዘር ፍሬየን ከጥቅም ውጭ አድርገው ዘሬን እንዳልተካ አድርገውኛል፡፡ ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም፡፡›› አበበ ካሴ እኔ አበበ ካሴ እባላለሁ፡፡ የሰሜን ጎንደር ተወላጅ ነኝ፡፡ በማዕከላዊ እስር ቤት ከ5 ወር በላይ ታስሬለሁ፡፡ ከዚህ መካከል 4 ወር ከ25 ቀናት በጨለማ ቤት ተቆልፎብኝ […]

የአሜሪካው ፕሬዘዳንት የኢትዮጵያ ጉብኝት ሰርግና ምላሽ በኢትዮጵያ ከወዲሁ የተወሰኑ እስረኞችና በመፍታትና ብዛት ያላቸውን የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን በማሰር ወደ ቀኑ እየገሰገሰ ይገኛል፡፡የሰማያዊና የቀድሞው አንደነት አመራሮችና አባላት ኦባማ ወደ አገራችን ሲመጡ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እያሴራችሁ እንደሆነ ደርሰንበታል በማለት ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ባሳለፍነው ሐሙስ የሞያ አጋሮቹ መፈተታት የፈጠረበትን ደስታ አጣጥሞ ሳይጨርስ በቁጥጥር ስር የዋለው ጋዜጠኛ ሐብታሙ ምናለ ከአምስት […]

ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ከተከናወነው አምስተኛውን ዙር ጠቅላላ ምርጫ በኋላ፣ በአባላት፣ በአመራሮችና በምርጫ አስፈጻሚ ግለሰቦች ላይ በተጠናከረ ሁኔታ እየደረሰ ያለውን ወከባ፣ እስራትና ግድያን በተመለከተ ጠቅላላ ጉባዔ በመጥራት፣ በጉዳቱ ላይ ቁርጠኛ ውሳኔ ለመስጠት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ …

መድረክ የአባላቱ እስራትና ሞት ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ Read more »

በተለያዩ ፊልሞችና የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ በመተወን የምትታወቀው ተዋናይት ቤዛዊት መስፍን እና ግብረ አበሯ በእስራት ተቀጡ። በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራንዮ ነዋሪ የሆኑት ተከሳሾቹ በእስራት የተቀጡት ከታዘዘላቸው ውጭ ተጨማሪ ገንዘብ ከባንክ ቤት በማውጣት ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው ነው። የ22 አመቷ ተዋናይት ከግብረ አበሯ ጋር በመሆን በተሰጣቸው የ4 ሺህ ብር ቼክ ላይ ከፊት ለፊቱ ሁለት ቁጥርን በመጨመር ያልተፈቀደላቸውን […]

በናይሮቢ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከደላሎች ጋር እንደሚሰራ ብዙዎች በምሬት ይገልጻሉ ‹‹ወተትና ማር ታፈልቃለች››ወደሚሏት ደቡብ አፍሪካ ለመሻገር በተለይ ከደቡብ ኢትዮጵያ በመነሳት በሞያሌ በኩል ወደ ኬንያ በመግባት ረዥሙን ጉዞ ለመያያዝ ራሳቸውን በሚያዘጋጁበት ቅጽበት እየተያዙ ወህኒ የሚወርዱ ወጣቶች ቁጥር በኬንያ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ በኬንያ ለመቆየት፣ስራ ለመስራት አልያም የሽብር ተግባር ለመፈጸም የመጡ እንዳልሆኑ ቢታወቁም በአገሪቱ ፖሊሶች […]

ቄራዎች ድርጅት በልኳንዳ ነጋዴዎች ምክንያት አገልግሎቱ መስተጓጎሉን አስታወቀ

የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ ጠየቀ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቄራዎች ድርጅት የዘንድሮው ሰኔ ፆም ሲፈታ አንድ ቀን ሲቀረው በልኳንዳ ነጋዴዎች ምክንያት አገልግሎቱ እንደተስተጓጎለበት አስታወቀ፡፡

ለ2,800 እንስሳት የዕርድ አገልግሎት ለመስጠት አቅዶ እንደነበር፣ ለእርድ አገልግሎት የቀረቡት ግን 900 እንስሳት ብቻ እንደሆኑ፣ ይህም ለሕገወጦች በር መክፈቱንና መንግሥትም ከአገልግሎቱ ማግኘት የሚገባውን ገቢ ማጣቱን  የድርጅቱ ዋና ሥራ አቶ ኤፍሬም ደሳለኝ አስኪያጅ አስታውቀዋል፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ ይህንን የገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ በቁም እንስሳት ንግድ አዋጅ በከተማው ክልል ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ ባዘጋጀው የተግባር ምዕራፍ ላይ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመወያየት ሐምሌ 2 ቀን 2007 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ላይ ነው፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ ይህ ዓይነቱ ድርጊት ገቢ በማሳጣት ላይ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን ኅብረተሰቡ ጤንነቱ ያልተመረመረ ሥጋ በመብላት ለተለያዩ በሽታዎች እንዲጋለጥ ማድረጉ መታወቅ ይኖርበታል ብለዋል፡፡ 

ድርጅቱ ዕቅዱን ያላሳካው የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ከደረሰኝ ጋር በተያያዘ ችግር ሳቢያ እንስሳቱን ከመግዛት በመቆጠባቸው፣ በዚህም የተነሳ የንግድ ቤቶቻቸውን ዘግተው ለኅብረተሰቡ የሽያጭ አገልግሎት መስጠቱን እርግፍ አድርገው በመተዋቸውና በዚህም ምክንያት የሥጋ እጥረት በማስከተሉ ነው፡፡

 ከዚም በተጨማሪ ቄራዎች ድርጅት ለዕርድ አገልግሎት የ2,000 ብር ዋጋ ጭማሪ እንዳደረገ የተነዛው አሉባልታ፣ ለልኳንዳ ንግድ ቤቶች መዘጋትና ነጋዴዎቹም እንስሳቱን ላለመግዛት ለማንገራገራቸው ተጨማሪ ምክንያት እንደሆነ ነው የተናገሩት፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቄራዎች ድርጅት ለዕርድ አገልግሎት የሚያስከፍለው በአንድ እንስሳ 230 ብር ብቻ እንደሆነ፣ ይህም የተመረተውን ሥጋ በተሽከርካሪ እስከ ልኳንዷ ቤቶች ድረስ የማጓጓዙንም ሥራ እንደሚያካትት፣ ከዚህ ውጪ ግን ምንም ዓይነት ጭማሪ እንዳላደረገ በመገናኛ ብዙኃን ጭምር ማስታወቃቸውን ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

‹‹ድርጅቱ አገልግሎቱን የሚሰጠው የንግድ ፈቃድ ላላቸው ብቻ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የተቋቋመው ጤናማነቱ የተረጋገጠ የዕርድ አገልግሎት ለከተማው ነዋሪዎች መስጠት ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ለተለያዩ ጉዳዮች ማለትም ሠርግ፣ ተዝካር፣ ወዘተ ላላቸው ወገኖች አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ይህ ዓይነቱ አሠራር እንዲቀጥል እናበረታታለን፡፡ ከክፍያ አንፃር ግን ከነጋዴው የተለየ ጭማሪ ሳይደረግ ነው የዕርድ አገልግሎቱን የሚያገኙት፤›› ብለዋል፡፡

በተረፈ ለድርጅቱም ደረሰኝ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው፣ በተለይ እንስሳት ከገበያ ወደ ቄራ በሚጓጓዙበት ጊዜ ሲሞት ካሳ የሚከፈልበት አሠራር እንዳለ፣ በዚህም የተነሳ ደረሰኝ ላይ የሚታወቅ ሁኔታ ካለ በዚያው ልክ እንደሚከፈል፣ ይህ ባለመሆኑ የተነሳ ግን አንዳንድ ጊዜ ከዋጋው በላይ እየተጠየቀ ድርጅቱን ላላስፈላጊ ወጪ እንደተዳረገ አልሸሸጉም፡፡

የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አየለ ሳህሌ ከደረሰኝ ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ሁኔታ አስመልክተው እንዳብራሩት፣ የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ባለፈው ሳምንት ማዘጋጃ ቤት አካባቢ ስብሰባ አድርገው ልኳንዳ ነጋዴዎች ለገዙት በሬ ደረሰኝ እንደማይፈልጉ፣ ምክንያቱ ደግሞ ያለደረሰኝ መሸጥ ስለሚፈልጉ ነው የሚል መረጃ በተባራሪ ልኳንዳ ነጋዴዎች ጆሮ ይደርሳል፡፡ 

ይህ ጉዳይ ተጋግሎ እየመጣ ረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ደረሰኝ ካላገኙ ከብት እንደማይገዙ በልኳንዳ ነጋዴዎች ዘንድ ጎልቶ ታየ፡፡ በዚህም ብቻ ሳይወሰኑ የማኅበሩ ቢሮ ድረስ እየመጡ ‹የሠራችሁልን ነገር የለም፣ በመብታችን ትደራደራላችሁ፡፡ እንዲያውም ማኅበሩን እናፈርሳለን› የሚል አቋም እንደያዙ ነው ምክትል ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት፡፡

በዚህም ምክንያት ልኳንዳ ነጋዴዎች ደረሰኝ ወይም ለሕጋዊነታቸው ማረጋገጫ ካላገኙ እንስሳት መግዛት አንችልም በማለት በራሳቸው መንገድ ንግድ ቤታቸውን እንደዘጉ፣ ማኅበሩም እስከ ፆም ፍቺው ዕለት ድረስ የማረጋጋት ሥራ ቢያከናውንም ሊሳካለት እንዳልቻለ አቶ አየለ ጠቅሰው፣ ‹‹በዚህም ምክንያት የአዲስ አበባ ልኳንዳ ነጋዴዎች ማኅበር ለተፈጠረው ችግር የከተማይቱን ሕዝብ ይቅርታ ይጠይቃል፤›› ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አለባቸው ንጉሴ ‹‹በዓለም አቀፍ ደረጃ በተዘጋጀ ጉባዔ 5,000 የሚሆኑ እንግዶች እየተስተናገዱ ባሉበት፣ የሰኔ ፆመኞች ፆማቸውን ሲፈቱ የልኳንዳ ንግድ ቤቶችን መዝጋት በማንኛውም ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ሕገወጥ ተግባር ነው፡፡ ምንም ዓይነት ችግር ቢኖርም መዝጋቱ መፍትሔ አይሆንም፡፡ የታወቅንበት መቻቻል፣ ሰላምና ፍቅር ደፍርሶ ሌላ ነገር እንዲከስት ያደርጋል፤›› ብለዋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሺሰማ ገብረ ሥላሴ የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማኅበር ስብሰባ ስለማድረጋቸው ለቢሮው የደረሰ ምንም መረጃ እንደሌለ ገልጸዋል፡፡ በተረፈ በቁም እንስሳት የገበያ ማዕከላት ውስጥ በጉልበት የታጀበ ጣልቃ ገብነትንና ሕገወጥነትን እንዲቀር ለማድረግ እንታገላለን፡፡ ለዚህም ዕውን መሆን ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር መተጋገዝ ያስፈልጋል ብለን እናምናለን፤›› ብለዋል፡፡ 

 

በዚህ ወር መጨረሻ የአባታቸውን ሀገር ለሁለት ቀናት ይጎበኛሉ ተብለው የሚጠበቁት ባራክ ኦባማ ወደ ኬኒያ ምድር ሲመጡ በግብረ ሰዶማውያን ጉዳይ ላይ አንዳችም ነገር እንዳይናገሩ በከፍተኛ ሁኔታ ሲያስጠነቅቁ ሰንብተዋል። የተለያዩ እምነት መሪዎችና የፓርላማ አባላት ጭምር ደብዳቤዎችን ለዋይት ሀውስ አስገብተዋል። የኬኒያ ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው “ይህ የአፍሪካውያን ባህል ካለመሆኑም በላይ ድርጊቱ የሀይማኖታችንን ህግ የሚጥስ ነው።” በማለት ተችተዋል። አንድ የቤተክርስትያን […]

ኢትዮጵያዊ ስለሆንን? (የኢትዮጵያ ከ20አመት በታች የሴቶች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን እሁድ እለት ከካሜሮን አቻው ያለግብ ከተለያየ በኋላ ወደ ሀገሩ ሊመለስ ሲል በረራ ተሰርዟል ተብሎ እንዲህ ነበር የሆነው። ምስል፦ ኢ/ያ እ.ፌ. የህዝብ ግንኙነት ወንድኩም አላዩ) ኢትዮጵያዊ ስለሆንን? ቆንጅት ተሾመ አውቃለሁ…. ሀገራቸውን ወክለው ካሜሮን የሄዱ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በረራ ተሰርዟል ተብሎ በአየር ማረፊያ ውስጥ በየጥጋ ጥጉ..በየመቀመጫው […]

ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው ሰማያዊ ፓርቲ ከ2007 ሀገራዊ ‹‹የውሸት ምርጫ›› ማግስት በገዥው አካል እየተወሰደ የሚገኘው ግድያ፣ እስር፣ ከስራ ማፈናቀል፣ ማሸማቀቅና ድብደባ በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ ፓርቲው ዛሬ ሐምሌ 7/2007 ዓ.ም ‹‹የወለደውን የረሳ ብሶት የወለደው ስርዓት! የዘመቻ እስርና ግድያ ተጠናክሮ ቀጥሏል!›› በሚል በጽ/ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እዳመለከተው፣ ምርጫው ከተጠናቀቀበት ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም ማግስት በምርጫው በንቃት ይሳተፉ […]

የትጥቅ ትግሉ በአራቱም አቅጣጫ ተጠናክሮ ቀጥላል  የወያኔም ስጋቱ አይላል፤ ተባላ አርበኞች ግንቦት 7 በተለያዩ ግንባሮች በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት ተከትሎ ከወያኔ ጎራ የተምታቱ ዜናዎች እየተደመጡ ነው። የቴፒው ትንቅንቅ አሁንም ቀጥሏል። ርዕዮት ዓለሙና የዞን 9 ጦማሪዎች በድንገት መፈታት እያነጋገረ ነው የሚኒስትር-ሬድዋን ሁሴን-አማካሪ-መኮብለላቸው ተሰማ እግዚአብሔር 10ቱን ለሙሴ የተሰጡትን ትእዛዝ እንዳሻሽላቸው አዞኛል “” የሮማው ካቶሊክ ጳጳስ ፍራንሲስ   አሰግድ […]

ከአንድ ዓመት በፊት ሚያዝያ 26 እና 27 ቀን 2006 ዓ.ም. በድንገት ተይዘው ከታሰሩ በኋላ፣ በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ ተመሥርቶባቸውና የሰነድና የሰው ማስረጃ ቀርቦባቸው፣ ለብይን የተቀጠሩበትን ቀን እየተጠባበቁ ከነበሩት አሥር ተከሳሾች መካከል አምስቱ በድንገት ሐምሌ 1 እና 2 ቀን 2007 ዓ.ም. መፈታታቸው እያነገጋገረ ነው፡፡

  የሸዋሮቢት ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርና የቀድሞው አንድነት አባላት ዛሬ ከ3:00— 4:00 ሰአት በታጠቁ የመንግስት ሀይሎች ከያሉበት ታድነው በመታሰር ላይ መሆናቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በዚህም መሰረት እስካሁን ድረስ 1 አቶ ዘነበ ደሳለኝ (የተወካይ ም/ቤት እጩ የነበረ። 2 አቶ ቴዎድሮስ ሀብቴ (የቀድሞ አንድነት አባል የነበረ።) 3 አቶ መንግስቱ ደባይ 4 አቶ በቀለ (የአባት ስም ያልተገለፀ) […]

ዛሬ ሐምሌ 4 2007ዓ.ም ረፋዱ ላይ አቶ መርከቡ ሃይሌ ሰሞኑን ሲከታተሉት በነበሩ ደህንነቶች እና ፖሊስ ታፍኖ ለጊዜው ወደአልታወቀ ቦታ ተወስዷል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ትናንት በኢህአዴግ የታሰረው አቶ ደብሬ አሸናፊ ዛሬ ረፋዱ ላይ ቤቱ በከፍተኛ የታጠቁ ሃይሎች ተከቦ ፍተሻ የተካሄደበት ሲሆን አሁን በጉለሌ አካባባቢ ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ እንደሚገኝ ተረጋጧል፡፡ በሌላ በኩል ትናንት ታፍነው የታሰሩት በሰሜን ሸዋ […]

Ali Sirajየኢፌዲሪ ንግድ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን እያገለገሉ የቆዩት አቶ አሊ ሲራጅ በድንገት አረፉ፡፡ አቶ አሊ ሲራጅ በድንገት ያፉት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓ/ም ማለዳ በአዳማ በኦህዴድ ስብሰባ ላይ አንዳሉ በድንገት ህመም ተሰምቷቸው ወደ ሆስፒታል እየሄዱ እንዳለ ሆስፒታል ሳይደርሱ ህይወታቸው ሊያልፍ እንደቻለ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ አቶ አሊ ሲራጅ የ 46 አመት ጎልማሳ ሲሆኑ በቅርቡ በተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ኦህዴድ/ኢህአዴግን ወክለው በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተወዳድረው ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

የሮማው ካቶሊክ ጳጳስ ፍራንሲስ ሰሞኑን በላቲን አሜርካ ባደረጉት የስራ ጉብኝት በኢኮዶር በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የካቶሊክ እምነት ተከታዮች አዲስ መልእክት አስተላልፈዋል:: ጳጳስ ፍራንሲስ ካስተላለፉት አዳዲሶቹ መልእክቶች ዋናዎቹ እግዚአብሔር 10ቱን ለሙሴ የተሰጡትን ትእዛዝ እንዳሻሽላቸው አዞኛል:: ከ10 ትእዛዛት ውጪ 2 ሌላ አዲስ የእግዚአብሔር ትእዛዛት በ10ቱ ትእዛዛት ውስጥ በተጨማሪ የሚካተቱ መሆኑን ጳጳስ ፍራንሲስ አስታውቀዋል:: ከሚጨመሩት እና ከሚሻሻሉት ከ10ቱ አዳዲስ ትእዛዞች […]

የወያኔው ሬድዋን ሁሴን ፣ እነ ርዮት አለሙ የተፈቱት መንግስት ማግናኒመስ (ትልቅ) ስለሆነ ነው እያለን ነው፣ ድርጅታችውን መልአካዊ አድርጎ ለማቅረብ ሲሞከር። ሆኖም፣ የገዢውች ማንነትን፣አ አዉሬነትን አሁን በአገሪቷ ዙሪያ ሁሉ ካሉ የቶርቸር ቻምበሮች (ክፍሎች) የሚሰሙ የሰቆቃ ጩኸቶች በትልቁ እያጋለጡ ነው። ባልሰሩትና ባልፈጸሙት ወንጀል፣ ቢያንስ ሃያ ዘጠኝ የሚሆኑ በእሥር የሚማቁ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችን አባላት አሉ። ፍርድ ተነፍገው […]

        በጥብቅና ሙያ የሚተዳደሩት አቶ ተማም አባቡልጉ አባዲኮን ከስነ ምግባር ጋር በተያያዘ በሚል ለ፩ አመት ከሰባት ወር የጥብቅና ፍቃዳቸውን ታግዳል። አቶ ተማም አባቡልጉ በግፍ ለታሰሩት ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጥብቅና በመቆም የወያኔን መሰሪ አሰራር ለአለም በማጋለጥ የሚታወቁ ሲሆን የካንጋሮ ፍርድ ቤት ፍርደ  ገምድልነት ቁልጭ ብሎ እንዲታይ ያደረጉ የሀገር አብት ጠበቃ ናቸው። ይህ ያልተመቸው […]

በሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት ውስጥ የከረረ ተቃውሞ በፖሊስ አባላቱ በመነሳቱ በርካታ ቁጥር ያላቸው ፖሊሶች መታሰራቸው ተሰማ፡፡ ቅዳሜ ዕለት ሰኔ 27 2007 ዓ.ም ዳባት ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት በተካሄደው ስብሰባ ላይ የከረረ ተቃውሞ የተነሳ ሲሆን ተቃውሞውን ተከትሎ የበርካታ ፖሊስ አባላት እስር እና ከአካባቢው መሰወር ተከስቷል፡፡ በስብሰባው ላይ የተነሳው ተቃውሞ ዋነኛ ምክንያትና ሰበብ የፖሊስ ፅ/ቤቱ ዋና […]

በሽብር ወንጀል ተፈርዶባት በይግባኝ በአምስት ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥታ በማረሚያ የነበረችው ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ትናንት የአመክሮ ጊዜዋ ተጠናቆ ከእስር ተለቀቀች። በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ የወንጀል ችሎት ግለሰቧ በእነ ኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሶስት የሽብ በይግባኝ ባደረገችው ክርክር የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የጋዜጠኝነት ሙዋየዋን በመጠቀም የሽብር ቡድንን ደግፋለች በሚል ወንጀል ብቻ ጥፋተኛ ናት በማለት የ14 ዓመቱን […]

የ2007 የኢትዮጵያ ምርጫ ተጠናቆ ሙሉ ውጤቱ ይፋ ከሆነ እነሆ ሳምንታት አለፉ። የምርጫው ሂደት ያስነሳው የፖለቲካ ትኩሳትና አቧራ በርዶ ፤ የምርጫው ተዋናዮች ግርግርና አስረሽ ምቺው ሰክኖ ምርጫ 2010 ከሰበር ዜናነት ወደ ታሪክ ማህደርነት የሚተላለፍበት ደረጃ ላይ እንገኛለን። የዚህን ምርጫ ታሪካዊ አንድምታና በታሪክ መዝገብ ውስጥ የሚኖረው ስፍራ በታሪክና ሶሻል ሳይንስ ተመራማሪዎች ወደፊት የሚለካ ሲሆን ይህ ጽሁፍ የዚህን ምርጫ ሁለት ለየት ያሉ ባህርያት ላይ ትኩረት በመስጠት ለመቃኝትና ለመዳሰስ ይሞክራል። በመጀመሪያ ይህን ምርጫ ካለፉት ምርጫዎች የተለየ የሚያደርገው ለምርጫ የወጣው ህዝብ ብዛት (turn out) ሲሆን ከተመዘገበው 36.8 ሚሊየን ህዝብ 34.8 ሚሊየን ህዝብ በነቂስ ወጥቶ በምርጫው ተሳትፏል። በዚህም በኢትዮጵያ ታሪክ ታላቁ ቀጥተኛና ነጻ የሆነ  ህዝባዊ ተሳትፎ የታየበት የፖለቲካ ክስተት ያደርገዋል። ይህን መሰል ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር የታየበት ምርጫ በአገራችን ብቻ ሳይሆን በብዙ አገሮች ከሚታዩት የህዝብ የምርጫ ተሳትፎዎች ጋር ሲንጻጸር ከፍተኛ አሃዝ ከተመዘገበባቸው አንዱ የሚያደርገው ሲሆን ይህም የምርጫውን የዲምክራሲያዊ መሰረት ያሰፋ፤ ፉክክራዊ ባህርይውን ያጎለበትና ለተአማኒነቱንም ዋስትና እንዲኖረው ካደረጉት ምክንያቶች እንደ አንዱ ሆኖ ሊጠቅስ የሚያስችል ነው። ከሁሉ በላይ ግን ለምርጫ ከወጣው የህዝብ ቁጥር አሃዝ ጀርባ ያለው ዋናው ቁምነገርና ይህንን ምርጫ ካለፉት ምርጫዎች በይዘት የተለየ የሚያደርገው ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የስልጣን ባለቤትነት መብቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ በስፋትና በጥልቀት እየተረዳ መምጣቱ የተንጸባረቀበት፤ ለዲሞክራሲ ስርአት ያለው ፍላጎትና ቁርጠኝነት እየሰፋና እየጎለበት መምጣቱን በግብር ያረጋገጠበት ምርጫ መሆኑን ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫን የማይገሰስና የማይቀለበስ ቋሚ ባህሉ […]

(አዲስ ከድሬዳዋ) መንግስት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ በማድረግና በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም ኢንቨስትመንቶችን በማስተናገድ ኢኮኖሚው እያደገ ነው፡፡ ዋነኛው የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽና የስራ እድል ፈጣሪ መንግስት በሆነበት ሁኔታ በመንግስት ሜጋ እና ትናንሽ ፕሮጄክቶች አማካኝነት ወደገበያው እየተለቀቀ ያለው ገንዘብና ከገበያው የሚሰበሰበው የገንዘብ መጠን ልዩነቱ ሰፊ በመሆኑ የግሽበት ተጋላጭነታችን ከፍተኛ ነው፡፡ ባንድ ወቅት ከ40 ፐርሰንት በላይ ደርሶ የነበረው የሀገራችን የዋጋ ግሽበት አሁን ወደ ባለአንድ አሀዝ ግሽበት(ከ10 ፐርሰንት በታች) መውረዱ እንደትልቅ ስኬት እየተነገረ ነው፡፡ ለመሆኑ ቀድሞ ነገር ኢንፍሌሽኑ እንዴት ጀመረ፣ አሁንስ እንዴት ሊቀንስ ቻለ ኢንፍሌሽኑ የጀመረው በተደጋጋሚ እንደሚነገረው መንግስት በሚያስተገብራቸው በርካታ ፕሮጀክቶች አማካኝነት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ወደገበያው እየለቀቀ ስለሆነ ነው፡፡ በኢኮኖሚስቶች የሚመከረውና መንግስት ኢንፍሌሽኑን ለማረጋጋት መውሰድ ያለበት እርምጃ በዋናነት ወደገበያው እየለቀቀው ያለውን ገንዘብ መቀነስ ነው፡፡ መንግስት ግን ይህ ኢኮኖሚያዊ እድገቱን ያቀዘቅዝብኛል በሚል ተመራጭ እርምጃ አድርጎ አልወሰደውም፡፡ አንድ አመት በከፊል ሞክሮት የነበረ ቢሆንም ቀጣይነት ግን አልነበረውም፡፡ መንግስት ይልቁንም በገበያው ላይ ያሉ ተጫዋቾች ላይ ቁጥጥሩን በማጥበቅ፣ ቁጠባን በማበረታታትና የግብር መሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግ ጥረት በማድረግ ነው ችግሩን ለመፍታት የሞከረው፡፡ በእርግኑን ይህንን አማራጭ በመከተሉ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገቱ ሳይቀዛቀዝ ኢንፍሌሽኑን በእጅጉ መቀነስ ችሏል፡፡ ሆኖም ለዚህ የተወሰኑ ዜጎች ያለአግባብ ዋጋ እንዲከፍሉም ተደርጓል፡፡ ሁለቱን ልጥቀስ የመንግስት ሰራተኞች፡- በ1994 ዓ.ም. የነበረው 400 ብር የመግዛት አቅም በ2004 ከነበረው 1000 ብር ጋር ተመጣጣኝ በሆነበት ሁኔታ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ በእነኚህ አስር አመታት 250 ፐርሰንት ሊያድግ ይገባ ነበር፤ […]

‹‹ሁላችንም በአንድ ነገር ላይ ዕምነት ነበረን – ከዚህ በኋላ ያለው የእስራቸው ጊዜ ጊዜ አጭር ሊሆን እንደሚችል፡፡ ማን ያውቃል …›› ሰኔ 05 ቀን 2005 ዓ.ም (ከ25 ቀናት በፊት) እነተስፍሽን በቂሊንጦ በጠየኳቸው ቀን ይህንን አውግተን ነበር፡፡ ዛሬ እውነት ሆነ! ደስስስስ! ——————-የዞን 9 ጦማሪ ዘላለም ክብረት፣ ጋዜጠኞቹ ተስፋለም ወልደየስ እና አስማማው ሃይለጊዮርጊስ ከእስር ተፈቱ። ‹‹…ተስፍሽ፣ በፍቄና አጥናፍ መጡ፡፡ […]

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የተመሰረተባቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ሌሎች በተመሳሳይ መዝገብ የተካተቱ ተከሳሾች ላይ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለዛሬ ተከሳሾች በነጻ ይሰናበቱ ወይስ ይከላከሉ በሚለው ላይ ብይን ይሰጣል ተብሎ ተጠብቆ የነበር ቢሆንም ብይኑ ሳይሰጥ ተቀጥሯል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ፣ የአንድነት እና የዓረና ትግራይ አመራሮች የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ሀብታሙ አያሌው እና […]