በኢንዶኔዥያ የዛሬ አስር ዓመት የደረሰዉን ከፍተኛ ማዕበል የደረሰዉን ጥፋት በማሰብ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በህንድ ዉቅያኖስ ዳርቻ በመገኘት በከፍተኛ የፀሎት ሥነ-ስርዓት አስቡ።

የገና ወይም የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል የጎሮጎሮሳዉያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተለዉ የክርስትና እምነት ተከታይ ዘንድ ዛሬ ተከብረ። በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ሐገራት የሐይማኖት መሪዎችና ፖለቲከኞች ለየተከታዮቻቸዉ መንፈሳዊና ዓለማዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።

መፀዉ ወይም መኽር ወር፤ ከመስከረም ሃያ ስድስት እስከ ታህሳስ ሃያ አምስት ይዘልቃል፤ ከታህሳስ ሃያ ስድስት ደግሞ በጋ ይጀምርና እስከ መጋቢት ሃያ አምስት ይዘልቃል። በዚህም ኢትዮጵያዉያን የገና በዓልን የሚያከብሩት ታህሳስ መጨረሻ በበጋ ወርራት ዉስጥ ነዉ።

የተለያዩ አራት ዓይነት የደንጉ ትኩሳት በሽታ አምጭ ተሐዋሲዎችን ለመከላከል የተገኘዉ መድሐኒት በሽታዉን ለማምከን አቅም እንዳለዉ ቢገለፅም፤ በክትባት መልክ ለተጠቃሚ ለማድረስ የሚደረገዉ ጥረት ግን ብዙ መሰናክል ተደቅኖበታል።

ከ100 000 ሺ በላይ ስደተኞች አውሮጳ በተለይ ኢጣሊያ መግባታቸው፣ የቀኝ አክራሪዎች-የውጭ ሃገር ዜጎች ጥላቻ መባባስ፣ ብሎም በአውሮጳ ምክር ቤት አሸናፊ ሆነው መውጣት እንዲሁም ሌሎች አበይት ነጥቦች በዛሬው አውሮጳ እና ጀርመን ጥንቅራችን ተካቷል።

የዓለም የምግብ እና የእርሻ ድርጅት በተገባደደዉ ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት የተሻለ የሰብል ምርት መገኘቱን በቅርቡ ይፋ አድርጓል። በተቃራኒዉ በመላዉ ዓለም ወደ805 ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ በቂ ምግብ እንደማያገኝም ጠቁሟል። ከአየር ንብረት ለዉጥና ከለዉጡ መዘዞች በመታገል የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጥረቶች በተለያዩ ሃገራት እየተሞከሩ ነዉ።

«የምዕራብ ፀረ-እስልምና የአውሮፓ አርበኞች» በጀርመንኛ ምህፃሩ ፔጊዳ የተሰኘዉ ኅብረት ፤ የጀርመን ዋና የመነጋገሪያ ርዕስ ከሆነ ሰነበተ። ህብረቱ ተቃውሞ ቢገጥመውም ትናንት 10ኛውን የተቃውሞ ሰልፍ በድሬስድን ከተማ አካሂዷል።

የኢቦላ ተሐዋሲን ጨምሮ በአፍሪቃ የረሀብ አደጋም ስጋት እንደፈጠረ ተገለጠ። ከአፍሪቃ ጋር የሚደረግ የንግድ ግንኙነት ኅብረተሰቡን በማይጎዳ መልኩ መሆን እንደሚገባው የጀርመን መራሒተ-መንግሥት የአፍሪቃ ልዕክ ተገልጧል። የምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ኢቦላን ለመዋጋት ለሚያደርጉት ጥረት ጀርመን የምትሰጠው ድጋፍ እንደሚቀጥል አስታውቃለች።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የደቡብ ሱዳንን ቀውስ ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ማዕቀብ የመጨረሻው አማራጭ ሊሆን እንደሚችል አመለከቱ። ከዚህም ሌላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አገራቸው ተጨማሪ ጦር ወደ ሶማሊያ ለማዝመት ዝግጁ እንደሆነች መግለፃቸዉንም የፈረንሳይ ዜና ወኪል ዘግቧል።

በባህር ዳር ከተማ ዓርብ ታኅሣሥ 10 ቀን 2007 ዓም ድንገት በተቀሰቀሰ ግጭት ከሦስት እስከ አምስት ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተሰማ። በርካቶችም መቁሰላቸው ተጠቅሷል። ሆኖም የደረሰዉን የጉዳት መጠን በትክክል የሚያረጋግጥልን የመንግስት አካል አላገኘንም።

ለዋሽንግተን ሐቫና ግንኙነት አሮጌዉ ዓመት አዲስ ተስፋ ፈንጥቋል። ከአፍሪቃ በስተቀር የሌላዉን ዓለም አበይት ክንዉኖች በሁለት ክፍሎች ቃኝተን፤ የማላላን ገደኛ፤ የማሌዥያን ፈሪሰኛ ግን ጉደኛ ዓመት እንሸኘዉ፤

እስካሁን ሦስት ተከታታይ አልበሞችን አሣትሟል። በቅርቡ ለአድናቂዎቹ ጆሮ ያደረሰው ሲዲ «አስታራቂ» ይሰኛል። ዜማ እና ግጥም ደራሲ፣ የሙዚቃ አቀናባሪ፣ መሣሪያ ተጨዋች እና ድምፃዊ ነው። አርቲስት አብነት አጎናፍር።

የዚያኑ ያክል ሕገ-መንግሥቱ የፀደቀበት ሃኛ ዓመት ከመከበሩ ከአንድ ቀን በፊት አዲስ አበባ ዉስጥ ለተቃዉሞ ሠልፍ አደባባይ ለመዉጣት የሞከሩ የከተማይቱ ነዋሪዎች፤ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችና አባላት በፀጥታ አስከባሪዎች መደብደብ፤መዋከብ፤ በጅምላ እየታፈሱ መታሰራቸዉ ተዘግቧል።

ዬኤስ አሜሪካ ጓንታናሞ ኪዩባ በሚገኘዉ ወታደራዊ እስር ቤቷ የያዘቻቸዉን አራት የአፍጋኒስታን ዜጎች በነፃ ለቃ ወደ ሃገራቸዉ መላክዋን ዋሽንግተን የሚገኘዉ የዩኤስ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።

2014 ዓም የዓለም አቀፉ ትኩረት በአፍሪቃ ላይ ያረፈበት ዓመት ነበር። ዓመቱ አራተኛው የአውሮጳ ህብረት እና የአፍሪቃ ጉባዔ፣ የመጀመሪያው የዩኤስ እና የአፍሪቃ መሪዎች ጉባዔ የተካሄደበት፣ ከፍተኛ የአፍሪቃ ባለሥልጣናት

የኬንያ መንግሥት ፤ ሽብር ፈጠራን በገንዘብ ይደጋፋሉ ያላቸውን 15 ቡድኖች ጨምሮ ባጠቃላይ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ የመንግሥት ያልሆኑ ድርጅቶች በሕግ የተመዘገቡትን ደንብ ሽሯል።

በኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራትን ሁኔታ የዳሰሰ ጥናትና ዉይይት መካሄዱ፤ ዴንማርክ ስለኤርትራ ስደተኞች ያወጣችዉ ዘገባና ማስተባበያዉ፤ ኬንያ፤ የመንግሥት ባልሆኑ ድርጅቶች ላይ የወሰደችዉ ጥብቅ ርምጃ እንዲሁም ጀርመን የተባበረችበት የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኞች ስልጠና…

የዴንማርክ መንግሥት ስለ ኤርትራ ስደተኞች የሚከተለዉን መርሕ እንዲቀየር ሃሳብ የሚያቀርበዉን የሐገሪቱን የስደተኛ ጉዳይ ዘገባ «ጥልቅ ስህተት ያዘል ዘገባ ሲል» የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት «HRW» አጣጣለ።

ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የአምደ መረብ ጸሓፍት ቁጥር ከአምናው በእጥፍ ማደጉን CPJ በሚል ምኅፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጠ። የCPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ተወካይ ቶም ሮድስ ኢትዮጵያ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ምርጫው ከመድረሱ አስቀድሞ ተቺዎች ድምፃቸው እንዳይሰማ እያፈናቸው መሆኑን ተናግረዋል።

«አርሶ አደሩ እያጉረመረመ ሲለዉ ከረመ፤ አርሶ በሌዉ መጣ ጠላ ሊጠጣ፤ አርሶ በሌዉ ካለ ምን ችግር አለ፤ አርሶ በሌዉ ጎፈር ማረስ መቆፈር፤ ላለዉ መንገዱን አለስልሶ ከርሞ ይመጣል ያልሞተ ሰዉ፤ እመቤቴ ያደረችበቱ እጣን ይሸታል መሬቱ» እያለ ሆ ይላል ያዜማል ፤ የኢትዮጵያ ገበሬ የዘራዉን ሰብል በታህሳስ ሲሰበስብ።

የሩስያ ማዕከላይ ባንክ የሀገሩ ገንዘብ «ሩብል» ዋጋ እያሽቆለቆለ የተገኘበትን ሁኔታ ለማከላከል በአሁኑ ጊዜ የሚቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ይገኛል፣ ይሁንና፣ የእስካሁኑ ጥረቱ አንድም የረባ ውጤት አላስገኘለትም። የሩብል መውደቅ ሩስያን ወደ ከፋው የኤኮኖሚ ቀውስ ወስጥ ይጥላት ይሆን?

የኤቦላ ተኀዋሲ በምዕራብ አፍሪቃ ፣ በተለይ በሶስቱ በበሽታው በጣም በተጠቁት ሀገራት፣ ላይቤርያ፣ ጊኒ እና ሲየራ ልዮን ላይ እያደረሰ ስላለው ማህበራዊ እና ኤኮኖሚያዊ ተፅዕኖ የተመድ በአፍሪቃ አዳራሽ ባካሄደው ጉባዔ ላይ ዝርዝር መግለጫ ሰጠ።

ኢትዮጵያ ውስጥ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የአምደ መረብ ጸሓፍት ቁጥር ከአምናው በእጥፍ ማደጉን CPJ በሚል ምኅፃረ-ቃል የሚጠራዉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጠ። የCPJ የምሥራቅ አፍሪቃ ተወካይ ቶም ሮድስ ኢትዮጵያ ውስጥ ገዢው ፓርቲ ምርጫው ከመድረሱ አስቀድሞ ተቺዎች ድምፃቸው እንዳይሰማ እያፈናቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ከጥቂት ወራት ወዲህ አንድ የተደበቀ ነገር ግልፅ እየሆነ መጥቷል። ይኸዉም በርካታ ትላልቅ ኩባንያዎች እና የንግድ ድርጅቶች ለመንግሥት በሕጉ መሠረት ገቢ ማድረግ የሚገባቸዉን ግብር ላለመክፈል በስዉር ያሸሻሉ ተብለዉ በብዙ ሃገራት ተከሰዋል።

ፍጥረተ -ዓለም ፣ ለመከሠት የበቃበትንና ሥርዓት የያዘበትን ሁኔታ ተመራምሮ ለመገንዘብ መጣር ከዋናዎቹ የሳይንስ ተግዳሮቶች አንዱ ነው። ምንም ያህል ምርምር ያድርጉ፣ የሥነ ፈለክ ጠበብት እስካሁን ከዚህ እስከዚያ የሚባል አጽናፍ ስለሌሉት ሕዋ የሚያውቁት እጅግ ውስን እንደሆነ አይክዱም።

መፍትሄ ያጣውን የደቡብ ሱዳን ጦርነትለማስቆም ተፋላሚ ኃይላትን ሸምጋይ የሆነው የምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለስልጣን- ኢጋድ ሰሞኑን ደቡብ ሱዳን ውስጥ ባለፈው አንድ ወር ገደማ ተፈፀመ ያለውን ጥቃትና የስምምነት ጥሰት የሚገልፅ ዘገባ አውጥቷል።

በፓኪስታን የታሊባን ታጣቂዎች በጅምላ ከገደላቸው ከገደሏቸው 141 ሰዎች መኻከል አብዛኞቹ ተማሪ ልጆች እንደነበሩ ተዘግቧል። ጥቃቱ የተፈፀመው ማክሰኞ ታኅሣሥ 7 ቀን 2007 ዓም የኪቤር ፓክቱንክህዋ ግዛት መዲና በሆነችው ፔሻዋር ውስጥ በሚገኝ አንድ የወታደር ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ ነበር።