የተተቸው የፓኪስታን ጸረ-ሽብር ዕቅድ

በፓኪስታን የታሊባን ታጣቂዎች በጅምላ ከገደላቸው ከገደሏቸው 141 ሰዎች መኻከል አብዛኞቹ ተማሪ ልጆች እንደነበሩ ተዘግቧል። ጥቃቱ የተፈፀመው ማክሰኞ ታኅሣሥ 7 ቀን 2007 ዓም የኪቤር ፓክቱንክህዋ ግዛት መዲና በሆነችው ፔሻዋር ውስጥ በሚገኝ አንድ የወታደር ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ ነበር።