ኢትዮጵያና ሱዳን የኤሌክትሪክ መሥመር ከፈቱ
አልበሽር ለኅዳሴ ግድብ ድጋፍ ሰጡ፡፡
አልበሽር ለኅዳሴ ግድብ ድጋፍ ሰጡ፡፡
ላሳለፈነው ሰኞ ተቀጥሮ የነበረው በእሥር ላይ የሚገኙት የሙስሊሙ ኅብረተሰብ ጥያቄ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የእነ አቡበከር አሕመድ ጉዳይ ለፊታችን ታኅሣስ 3/2006 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡
ወያኔ የካደው እና ግንቦት ሰባት የተነፈሰው የእንደራደር ጥያቄ የአናጎሜዝን የአዲስ አበባ ቆይታ ተከትሎ የወጣ ጉዳይ ነው::

ምንሊክ ሳልሳዊ :-ይህን ሰሞን በሃገር ውስጥ እና በውጪው ሃገር ኢትዮጵያውያን ዘንድ የመወያያ ርእስ የሆነው እና ይየወያኔ ካድሬዎችን ቀልብ የገፈፈው እና ከሰል ያለበሳቸው ወያኔ ለግንቦት ሰባት ያቀረበው የድርድር ጥያቄ ነው::በስፋት አሁንም እየተከራከሩበት ያለው ይህ ጉዳይ አገሩን በጡዘት አምሶት የሃገሪቱ የፖለቲካ ሂደት አንድ ተስፋ የሰጠ ሁኔታ እንደሚታይ እየተተነበየ ነው::
ወያኔ በእርግጥ በማይጥም የፖለቲካ እሰጥ አገባ የተጠመደ ቢሆንም የወያኔ ፕሮፓጋንዳ ለላውን ከማዘናጋት ውጪ ምንም አይነት ፋይዳ እንዳሌለው እና ራሱን እየፈተሸ እንደሆነ ያጋለጠ ጉዳይ ነው:: የድርድር ጥያቄ አላቀረብኩም ያለው ወያኔ እንደለመደው ከኦነግ ከኦብነግ ከሻእቢያ ጋርም እየተደራደረ ጥያቄውን እራሱ እያቀረበው ሲክድ የቆየ ሲሆን በቅርቡ እንኳን በኬንያ ከኦብነግ በጀርመን ከሻእቢያ ጋይ ያደረጋቸውን ድርድሮች እየታከካቸው አልፏል::
ወያኔ የካደው እና ግንቦት ሰባት የተነፈሰው የእንደራደር ጥያቄ የአናጎሜዝን የአዲስ አበባ ቆይታ ተከትሎ የወጣ ጉዳይ ነው:: በእርግጥ በተለያዩ ጊዜያት ለወያኔ እና ለግንቦት ሰባት የቅርብ ርቀት የሆኑ ሰዎች ይህንን ጉዳይ በግል አንስተውት የሆነ ቢሆንም ባይሆንም ግን የአና ጎሜዝ የአዲስ አበባ ምላስ ተከትሎ ግንቦት ሰባት ለህዝብ ይፋ ያደረገው ጉዳይ አሁንም ሚዛኑ ወደ ግንቦት ሰባት እንዲሆን አድርጎታል::
እንቅልፍ የነሳቸው የወያኔ ባለስልታናት የቀን ተቀን የስብሰባ መቀመጫቸው ግንቦት ሰባት ነው:; በወታደሩ በደህንነቱ እና በታማኝ ካድሬው ዙሪያ ውይይቱ ምስጢሩ ግንቦት ሰባት ነው:: እነዚህ የሚስጥር ተወያዮች እንደሚጠቁሙት ሲሰበሰቡ በውይይት ወቅት ግንቦት ሰባትን አሸባሪ ብለው አይጠሩትም:; አሸባሪ የሚለውን ቃል የሚጠቀሙት ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታቸው አደባባይ ላይ መሆኑን በይፋ የተረጋገጠ መረጃ ይጠቁማል::
በቅርቡ ከአባቱ ሻእቢያ ጋር ጀርመን ላይ የተወያየው ወያኔ ግንቦት ሰባት የራስ ምታት ስለሆነበት እንዲያደራድረው አሊያም እንዲገላግለው ተማጽኖ ቢሆንስ??? ወይኔ ሻእቢያ የሚፈልጋቸውን ተቃዋሚ ኤርትራውያንን እያፈነ እንደሚሰጥ የህን ሰሞን ሃተታዎች እየጠቆሙ ነው እንዲሁም በሱዳን በኩል እያሽከረከረም እንደሚያስረክብ::ነገሩ የጨነቀው እርጉዝ ያገባል አይነት ነው ….
የአቶ ታምራት ላይኔም ወደ ፖለቲካው ለመቀላቀል ማቆብቆብ እኮ የዚሁ የድርድር አንዱ አካል ነው:; ብኣዴን ታምራት ላይኔን ይፈልገዋል:: አገሬ በፈለገችኝ ሰአት ለማገልገል ተዘጋጂቻለሁ የሚለው ታምራት ጠጋ በል እየተባል መሆኑስ የወያኔ አንድ የጭንቀት ምልክት አይደል?! … ወደ ሚዲያዎች አያሰገገ መምጣቱ ሌላ ምስጢር የለውም::
አና ጎሜዝ ከአዲስ አበባው ቆይታቸው ሁለት ንግግሮችን ከአንደበታቸው ሰምተናል:: አንዱ “ከባለስልጣናት ጋር ያደረኩት ውይይት በጎ እና ገንቢ ነው መልካም ምላሽ እንዳገኙም በእርካታ ተናግረዋል:; በመተማመን ስሜት ደሞ “አዲስ ንፋስ አለ” ሲሉ ተስፋቸውን አብርተዋል:: ይህንን የፖለቲካ ስሜታቸውን ያልተረዱ የደፈናው ጋዜጠኞች የወያኔን የሞተ እስትንፋስ ሊያበረቱ ቢሞክሩም የሚሳካ ካለመሆኑም ሌላ ወያኔም …ጌታ….ተላላኪ…;;እያለ ቢዘላብድም ታምኝነት ሊያገኝ አልቻለም:: አና ጎሜዝ ይህንን ሲናገሩ ከባለስልጣናት አንደበት የሰሙት እና የተላኩት መልእክት እንዳለ ይጠቁማል:: አና ጎሜዝ ወደ ግንቦት ሰባት ብቻ ሳይሆን ለተለያዩ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን የለውጥ ጠያቂዎችም የብሄራዊ ድርድርን ጉዳይ አስረግጠው አዋይተዋል:;በእርግጥ ስለግንንቦት ሰባት ባያነሱም ይህ የእንደራደር ጥያቄ የመልስ ምቱን ወያኔ ለማወቅ ፈልጎ ያደረገው ሊሆን የሚችል የማጭበርበሪያ የፖለቲካ ስልት ቢሆንም የድርድሩ ጥያቄ ግን የአና ጎሜዝን የአዲስ አበባ ቆይታ እና የአዲስ ነፋስ ምልክታን ተከትሎ መነገሩ እውነታውን ያጎላዋል:; ይህ የሚያሳፍረው ወያኔን ቢሆንም ወያኔ ግን ምንተእፍረቱን አይኑን በጨው አጥቦ ቢክድም አሁንም ግንቦት ሰባትን እንዲያደራድሩት ከትን እንዲያደበጀርባ እየተለማመጠ እንደሚገኝ ለማስገንዘብ እወዳለሁ:: #MinilikSalsawiምንሊክሳልሳዊ
News, Cultural Mosaic, Kebele Lives and Environment or Tech
ጋዜጠኞቹ በኤርትራ ከሚደርስባቸው ጫና በመሸሽ በተሰደዱበት ኡጋንዳ በጀመሩት United Hearts በተባለ ድረ ገፃቸው ጠንካራ ዘገባዎች በማቅረባቸውና ቡና ልዩ ልዩ ሃሳቦችንም በነፃነት በማስተናገዳቸው ለሽልማት በቅተዋል ።
ወታደሮቻቸውን አፍጋኒስታን ያዘመቱት የሰሜን አትላንቲክ የጋራ መከላከያ ቃል ኪዳን ድርጅት በምህፃሩ NATO አባል ሃገራት ካርዛይ ውሉን በአስቸኳይ ካልፈረሙ ሃገሪቱ የሚሰጣት የእርዳታ ገንዘብ ይቋረጣል ሲሉ እየዛቱ ነው ። የሃገሪቱ የፀጥታ ጥበቃም አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ማስጠንቀቃቸውን ቀጥለዋል ።
ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን እንዳስታወቀዉ ከትናንት ሌሊት ጀምሮ ዛሬም በቀጠለዉ ዉጊያ የተገደሉ የአስራ-ስድስት ሰዎች አስከሬን በከተማይቱ በሚገኙ ሁለት ሆስፒታሎች ተከማችቷል።
በያዝነዉ ሳምንት ህዳር 24፤ የዓለም የአካል ጉዳተኞች ቀን ለ22 ኛ ግዜ ታስቦ ዉሎአል። የተመድ ያወጣዉ ዘገባ እንደሚያመላክተዉ በዓለም ከሚኖሩ ህዝቦች መካከል 15 ከመቶዉ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳተኞች ናቸዉ። በኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ላይ የሚደርስዉ ተፅኖ እና በተለያዩ ዘርፎች ያላቸዉ እንቅስቃሴ ምን ይመስላል?
ባኩ-አዘርባጃን ዉስጥ በመካሄድ ላይ ባለው 8 ተኛው የዓለም ህልናዊ ባህላዊ ቅርሶች ጉባኤ ላይ የተለያዩ ሃገራት 30 ህሊናዊ ቅርሶች እንዲመዘገቡላቸው አቅርበው ነበር ። የመስቀል በዓል አከባባር በባለሞያዎች ተገምግሞ በዚህ ጉባኤ ተቀባይነት ካገኙት ህሊናዊ ቅርሶች አንዱ ነው ።
እነ ሌኒን በሚሉት መልኩ ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የሚባለው አገራችን ውስጥ የለም፡፡ የስታሊን ጠባብ ብሄርተኝነት፣ የምዕባራዊያኑ ‹‹ካፒታሊዝምና ዴሞክራሲ›› በስም ደረጃ፣ የአልባኒያና የቻይና አምባገነንነት፣ የሻዕቢያና አረብ አገራት ጥላቻ፣ የሞሶሎኒ ፋሽዝም……ተደባልቀው የተሰራ ውጥንቅጡ የጠፋበት ‹‹ርዕዮት ዓለም›› ነው፡፡ የአሁኑ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ከሁሉም ጎን የወሰደው መጥፎ ጎናቸውን እንጅ መልካሙን አይደለም፡፡ እነዚህ የየዘመኑን ትውልድ ያሰከሩ አስተሳሰቦችን መጠናቸውን ሳያውቅ የደባለቀው አብዮታዊ ዴሞክራሲ ከአልኮንነትም አልፎ መርዝ ወደመሆን ደርሷል፡፡ አልኮል ብቻውን ከሚወሰደው በላይ ሲደባለቅ ያሰክራል፡፡ ያሳብዳልም፡፡
ፋሽስቶች ለኢትዮጵያውያንና ለሌሎች ካልሆነ በስተቀር ለአገራቸው ህዝብ ክብር ነበራቸው፡፡ እነ ሌኒንም ቢሆን ለአገራቸው አንድነት እንጅ ተገንጣይነት አልሰሩም፡፡ አረቦቹ ለአገራቸው ጥቅም ሲሉ ነው ኢትዮጵያን ይጠሉ የነበሩት፡፡ የአስተሳሰባቸው መርዝነት ለእኛ እንጅ ለራሳቸው ህዝብ አልነበረም፡፡ ምንም ያህል ቢያብዱና ቢሰክሩ ለአገራቸው ህዝብ ክብር ነበራቸው፡፡ ለብሄራዊ ጥቅማቸው ይጨነቁ ነበር፡፡
ድብልቅልቁ የወጣው ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ግን ኢህአዴግን ጨርቁን አስጥሎታል፡፡ ለዛም ነው ይህን ያህል ያበዱት የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የአልኮል መጠን ስንት ቢሆን ነው?›› ብየ የጠየቁት፡፡ ከወራት በፊት ለግራዚያ ሲቆም አብዮታዊ ዴሞክራሲ ምን ያህል እንደሚያሰክር፣ እንደሚያሰብድ አሰይቶናል፡፡ ይህ ከእነ ሞሶሎኒ የተወሰደው የአልኮል ክፍል መሆኑ ነው፡፡ ከሳምንታት በፊት ኢትዮጵያውያንን በአረብ ዱላ ገረፈ፡፡ ይህኛው ከአረቦቹ ጥላቻ የተዘነቀው የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አልኮል ነው፡፡ አሁን ደግሞ የአጤ ምኒልክን ሙት አመት አታከብሩም ብሎ ከልክሏል፡፡ ይህኛው የሁሉም ውጤት ነው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ መጨረሻ ቀላቅሎ ያለ አቅሙ አይኑን ጨፍኖ የተጎነጨው ይህኛውን አልኮል ነው፡፡ ጸረ ኢትዮጵያውይነት! የአሁኑ ጣሊያኖች የምኒልክ ታሪክ እንዳይወደስ የሚፈልጉበት ምንም አይነት ምክንያት የለም፡፡
በግራዚያኒ ላይ የጣሊያን ግራ ዘመም ፓርቲዎች በነጻነት ተቃውሞ አሰምተው በሰላም ገብተዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ግንወገኖቻቸው በተጨፈጨፉበት ጎዳና እንደገና ተደብድበዋል፡፡ ታስረዋል፡፡ ይህ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ የተለከፈ መንግስት ከያኔው ጨፍጫፊዎችም በላይ ይሆንብኛል፡፡ ስካር ሱስ ነው፡፡ በሽታም ጭምር፡፡ እንዲህ የጠደባለቀ መርዛማ አልኮል መጎንጨትን ልማዱ ያደረገ ድሮ ሰክሮ የሚሰራውን ጉዳይ ምሎና ተዘክሮ እተዋለሁ ቢልም የሚሰራው ግን ያው የስካሩን፣ የእብደት ተግባሩን ነው፡፡ ለግራዚያኒ የቆመው ኢህአዴግ ከውስጥም ከውጭም ተቃውሞ ሲገጥመው ስህተቱ ስካሩ መሆኑን ሳይረዳው ቀርቶ አይደልም፡፡ ግን ለሳውዲዎች ቆሞ ደገመው፡፡
አሁን ደገሞ ለድሮዎቹ፣ አድዋ ላይ ለተሸነፊት ጣሊያኖች ቆሞ ከለከለ፡፡ ኢህአዴግ ከአረቦቹ፣ ከፋሽስቶቹ፣ ከእነ ስታሊን….የደባለቀውን የውስጡን ጥላቻ በአብዮታዊ ዴሞክራሲው አልኮል አወጣው፡፡ ይህን ታዲያ ከስካርና ከእብደት ውጭ ምን ይሉታል? እኔ ይህን ናላ አስቶ፣ ጨርቅ አስጥሎ በአገር ህዝብ ላይ የሚያዘምት፣ ህዝብ ላይ የሚያስጨክን፣ ብሄራዊ ጥቅምን የሚያስጠላ ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የአልኮል መጠኑን መገመት አልቻልኩም፡፡ ከመጠን በላይ መሆኑን፣ መርዛማነቱ ማመዘኑን ከመገመት ውጭ! ግን ኢህአዴግ እስከመቼ እንዲህ ጨርቁን ጥሎ ይዘልብናል?
(ሪፖርተር፤ ኅዳር ፳፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) ኄኖክ ያሬድ የኢትዮጵያው የመስቀል ክብረ በዓል በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ዩኔስኮ አስታወቀ፡፡ ዩኔስኮ የመስቀል ክብረ በዓልን (Commemoration feast of the finding of the True Holy Cross of Christ) በዓለም ቅርስነት መመዝገቡን ኅዳር 25 ቀን ይፋ ያደረገው፣ በኢንታንጀብል (መንፈሳዊ) ባህላዊ ቅርሶች ጥበቃና ክብካቤ ላይ የሚሠራው ኮሚቴው ስምንተኛውን ጉባኤ እያካሄደባት ካለው የአዘርባጃኗ …![]()
ሴራ የአምባገነኖች ዋነኛ መሳሪያ ነው፡፡
ህዝብን ለማወናበድመ ትኩረት ለማስቀየር፣ ለመከፋፈል በአጠቃላይ ዋነኛ መግዢያ መሳሪያ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ምንም ይሁን ምን ሴራ ካልሰሩ ስልጣን ላይ የሚኖሩ አይመስላቸውም፡፡ አምባገነኖች የሴራ ሱስ ጠጠቂዎች ናቸው፡፡ ከወራት በፊት ነው፡፡ ኢቲቪ ስለ ስደት ተደጋጋሚ ዘገባዎችን፣ ዶክመንተሪዎችን ማሳየት ተያይዞት ነበር፡፡ ከዛም የሳውዲ አረቢያ መንግስት ስደተኞች እንዲወጡ ትእዛዝ ማስተላለፉ ተሰማ፡፡ ይህን ተከትሎ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት በህጋዊ መንገድ የሚሄዱትንም ጭምር አገደ፡፡
ለባለስልጣናት እንደ ምትታለብ ላም የሚቆጠሩት ኤጀንሲዎችም ሳይቀር ስራ እንዲያቆሙ ተነገራቸው፡፡ በጊዜያውይነትም ታገደ፡፡ ብቻ እዚህ ላይ የኢትዮጵያ መንግስት አንድ ያሳሰበው ነገር እንዳለ ማየት ይቻላል፡፡ ለስደተኞች አዝኖ እንዳልሆነ በስተመጨረሻ የደረሰውን ሰቆቃና ሰቆቃው ሲደርስ የወሰደው የረባ እርምጃ አለመኖሩ ያስረግጣል፡፡ እኔ በበኩሉ አንድ ሴራ ይታየኛል፡፡ በዓረቡ አለም የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ልክ በአሜሪካና አውሮፓ እንደሚኖረው ዲያስፖራ የተቃውሞ ምንጭ መሆን ጀምረዋል፡፡ እንዲያውም በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ድህረ ገጽ የሚንቀሳቀሱት በአረቡ አለም የሚገኙት ወገኖቻችን ናቸው፡፡ አብዛኛዎቹ ደግሞ የአይበገሬው ‹‹ድምጻችን ይሰማ!›› አባላት ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የዚህን ቡድን ድምጽ ሲሰማ ይበርክካል፡፡ ጭንቅ ይለዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ‹‹አማካሪ›› ነን ባዮች የኢትዮጵያን ስደተኞች የድምጻችን ይሰማን ጨምሮ የተቃውሞ ጎራውን የሚያጠናክሩ መሆናቸውን አምነዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ ግን መንግስት የሚወቅሰውን አክራሪነት መሳሪያ ሊሆኑ ይችላሉ ብለው አስበዋል፡፡ ያው ‹‹አማካሪ›› ነን ባዮቹ የሚናገሩት መንግስት ሊሰማ የሚፈልገውን ነውና የሚፈሩትን ለጥፈውባቸዋል፡፡ ሳውዲዎች ደግሞ ስራ አጣን ብለው እያማረሩ ነው፡፡ በኢትዮጵያውያን ላይ ያላቸው ጥላቻ እና ከመንግስቱ ጋር ያላቸው ግንኙነት አንድ ያደርጋቸዋል፡፡ መንግስትም ሆነ የሳውዲ መንግስት ስደተኞቹን እንደ ጠላት ያዩዋቸዋል፡፡ ያም ሆኖ ኢትዮጵያውን ከስደታቸው አልቆሙም ነበር፡፡ እናም አንዳች ነገር መደገስ ነበረባቸው፡፡ ስደተኞቹ በተለይም የመንግስት አማካሪ ነን ባዮች ‹‹አክራሪዎች›› ይፈለፈሉባታል ከሚሏት ሳውዲ ‹‹አይቀጡ ቅጣት›› ተቀጥተው እንዲመሰሉ ማድረግ፡፡ ሌሎች እንዳይሄዱ ‹‹ትምህርት›› መስጠት፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ለተመላሾች በሚያደርገው ‹‹ድጋፍም›› የሆነች ጥቅም እንደሚያገኝበት ገምቷል፡፡ ታዲያ ኢትዮጵያውያን ላይ ብቻ ይህ ሁሉ ሰቆቃ ለምን ደረሰ? በሳውዲ መንግስት ላይ ምንም አይነት ጫል አልተደረገም? መንግስት ለምን ትክክለኛ እርምጃ ለመውሰድ ተደናረ? ለምንስ ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርጉትን ደበደበ? የሀይለማሪያም ደሳለኝ ዝምታስ? ሌላ ሴራ ከትናንትና በፊት መቀሌ ከአንዴም ሶስቴ መንደዷን ሰማን፡፡ ከዛም መርካቶ፡፡ አሁንም ቢሆን ይህ ለኢህአዴግ መቀመጫ የነሳው ሙስሊም የሚበዛበት አካባቢ ነው፡፡ መርካቶ የእንቅስቃሴው መሰረት ነው፡፡ አዲስ አበባ ላይ ብቻ ቢደርስ ትኩረት ሊስብ ይችላል በሚል መቀሌን ቀድመው ያነደዷት ይመስለኛል፡፡ ደግሞ በሁለቱም ከተማ የወደሙት ሱቆች ናቸው፡፡ ለምን? የንግዱን ማህበረሰብ ለማሸበር? ትኩረትን ከጅጅጋ ወደ አዲስ አበባና መቀሌ ለማስቀየስ? ‹‹አክራዎችን ገቢ ለማሳጣት››? ማን ያውቃል ‹‹አማካሪዎቹ›› የማይዘይዱት አይኖርም፡፡ ሁሉም ድራማ ነው፡፡
እሳቱ በቁጥጥር ስራ ሳይውል በቁጥጥር ስር ዋለ ማለቱን ለምን አስፈለገ? በቅርቡ ኢህአዴግ ከአማካሪዎቹ ‹‹49 በመቶ በላይ የኑሮ ውድነት ይከሰታል፡፡›› ተብሎ እንደተነገረው ተሰምቷል፡፡ በክርክር ላይ ናቸውም ተብሏል፡፡ የኑሮ ውድነቱ ምክንያት ከተባሉት መካከል ደግሞ ‹‹ከ39 አይበልጡም!›› የሚባሉት የመርካቶ ነጋዴዎች ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ እነዚህ ነጋዴዎች ‹‹ድምጻችን ይሰማ››፣ በኑሮ ውድነትም ይከሷቸዋል፡፡ ብቻ ሴራው ይታየኛል፡፡ አምባገነኖች ከገቡበት ማጥ ለመውጣት ሴራን ዋናው ስልታቸው ያደርጋሉ፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ውጤትና ምክንያቱን ሳይመዝኑ የተለከፉበትን ሴራ ይሸርባሉ፡፡ በተራ ግለሰባዊ ጠብ፣ በጥላቻ አገርና ህዝብ ያቃጥላሉ፡፡ ይወራሉ፡፡ ጦርነት ያስጀምራሉ፡፡ በሽታ እንዲቀሰቀስ ያደርጋሉ፡፡ ዞረው የመፍትሄው አካል መስለው ይታያሉ፡፡ ይለምኑበታል፡፡ የዜጎቻችን ሰቆቃና የከተሞቻችን ቃጠሎ ሴራ ሴራ ይሸተኛል፡፡ ይህ መንግስት እኮ ሀውዜንን ማስጨፍጨፉን የቀድሞ አባላቱ ተናግረዋል፡፡ የአበበች ደራራን አባት መግደሉን ካድሬዎቹ መስክረዋል፡፡ የደሴውን ሸክ መግደሉን ህዝብ እየተናገረ ነው፡፡ አንድ ቀን የሚወጣ ይሆናል፡፡
ግርማ ካሳ
“የኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ለግንቦት ሰባት የእንደራደር ጥያቄ አቀረበ” ሲል ኢሳት ሰበር ዜና አሰማን። ዶ/ር ብርሃኑ ነጋንም በማቅረብ በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ እንዲሰጡም አድርጓል። ምንም እንኳን የቀረበውን ዘገባ ከሌላ ምንጭ ማጣራት ባይቻልም፣ ዜናው እውነት ሊሆን የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ግን ይሰማኛል። አገዛዙ ከኦብነግ፣ ኦነግ ከመሳሰሉ ጋር ድርድር እየጀመረ፣ የማቋረጥ ልማድ እንዳለው ታሳቢ በማድረግ። የግንቦት ሰባት “እንደራደር” ጥያቄም ከዚያ የተለየ አይሆንም።
እሳት አደጋ ሰራቶኞች 50000 ብር ግቦ ተቀብለዋል ::
ከቀኑ በስምንት ሰአት የጀመረ እስከ ምሽቱ ሶስት ሰአት ድረስ አልተቆጣተሩትም ::
የእሳቱን ጪስ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ በያለበት በሀዘን ሲመለከተው ነጋዴዎች ንብረታቸው መቃጠሉ ሳያንስ በዱላ ተደብድበዋል ፡፡
የእሳት አደጋው መንስኤ በገለልተኝ አካላት አስኪጣራ ምንም ከማለት መቆጠቡ አስፈላጊ ቢሆንም ሀላፊነት የሚሰማው ለህዝብ መሰዋትመት የሚከፍል የድንገተኝ አደጋዎችን የሚቆጣጠር የመንግስት አካል አለሞኖሩ ህብረተሰባችንን በጣሙን ያሣዘነ ሆኖ አልፏል ፡፡ የእሳትና ድንገተኝ አደጋ ሰራተኞች እሳቱ ልክ ከቀኑ በ 8 ሰአት እንደተቀሰቀሰ መረጃው ቢደርሳቸውም ቦታው የደረሱት 9 ሰአት ላይ መሆኑ ያበሳጫቸው የአካባቢው ነዳዴዎች እቃቸውን ለማሸሽ በሚያደርጉት ትግል ብዙዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል::
በተጨማሪም በቦታው ቀደም ብለው የደረሱ የፌደራል ፖሊሶች እሳቱን ለማጥፋት ህብረተሰቡን ከማስተባበርና ይበልጥ ጉዳት እንዳያደርስ ከመከላከል ይልቅ የአካባቢውን ነጋዴዎችና
እሳቱን ለማጥፋት የሚረበረቡትን በዱላ እየደበደቡ ሲያባርሩ ተስተውለዋል ፡፡ ከዚህ በባሰ መንግስት የለም ወይ የሚያስብለው የእሳትና የድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች እቦታው ደርስው መኪናቸው ውስጥ
ዝም ብለው ሲቀመጡ በንዴት ንብረጃቸውን ለማሸሽ ተንደርድረው ወደሱቃቸው የገቡትን ነጋዴዎች በውሃ ገፍትረው የጣሉዋቸው ሲሆን እነዘህም ነጋዴዎች በተክላሀይማኖት ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ ፡፡
ብር ካልተሰጣቸው እንደማያጠፉ የተረዱት 2 ነጋዴዎች ሀምሳ ሺህ ብር አዋጥተው እንደሰጦቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ለአደጋው መባባስ በመጀመሪያ ደረጃ ተጠያቂው የመንግስት አካላት መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው ፡፡ስምንት ሰአት ሙሉ መርካቶ በቃጠሎ ውስጥ የነበረች ሲሆን የሁለት ብሎኮች ንብረቶችም ሙሉ በሙሉ ወድመዋል ፡፡የእሳቱን ጪስ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ በያለበት በሀዘን ሲመለከተው አምሽቷል፡፡ እሳቱን ማቆም የተቻለው ከምሽቱ ሶስት ሰአት ላይ መሆኑንም
አየይን እማኞች አክለው ገልጸዋል ፡፡
ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ)
በአረብ አገር በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሠራተኞች ላይ የሚደረገው ህገወጥ የማሰቃየት እርምጃ በአስቸኳይ ይቁም! በአሁኑ ወቅት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን/ት ስደተኛ ሰራተኞች ላይ በሪያድና በአዲስ አበባ ከተሞች ባሉ ገዥ አካሎች እየተፈጸመ ያለው የሰብአዊ መብት እረገጣ ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ ለጉዳዩ ልዩ የሆነ ትኩረት እንዲሰጡትና ለወገኖቻቸው የማያቋርጥ ድጋፍ እንዲያደርጉ ምቹ አጋጣሚን ፈጥሯል።
ለጥናታዊ ውይይቱ÷ ካህናት፣ የአብነት መምህራን፣ መዘምራን፣ ሰባክያነ ወንጌል፣ የሰንበት ት/ቤት ተጠሪዎች እና ምእመናን የሚወከሉበት ቁጥር ተወስኗል፡፡ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች÷ ተሳታፊዎቹ በአገልግሎት ድርሻቸው እና በተወሰነላቸው ቁጥር መሠረት መወከላቸውን የማረጋገጥ ሓላፊነት ተጥሎባቸዋል፡፡ ሀ/ስብከቱ የተሳትፎ ጥሪ ያስተላለፈበትን ደብዳቤ በማፈንና የተለያዩ ሰበቦችን በመደርደር ጥናታዊ ውይይቱን ለማኮላሸት አሻጥር የሚሠሩ የለውጡ አደናቃፊዎች (አንዳንድ አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች) በጥንቃቄ ተለይተዋል፤ በጸጥታ አካሉ […]![]()
ተመስገን ደሳለኝ – ከአዲስ አበባ
…አውሮፕላኑ ቅዳሜ ጠዋት ሶስት ሰዓት ላይ ድሬዳዋ አየር ማረፊያ ደርሶ ከተርሚናሉ ስወጣ፣ ተጠራጥሬ ሰዓቴን ተመለከትኩ፤ የድሬ የጠዋት ፀሐይ ከተለመደው ንዳዷ ጋር የአዲስ አበባን የቀትር መራራ ፀሀይን ታስከነዳለች፤ እናም አጥበርባሪ ጨረሯን ያለምህረት ስትለቅብኝ፣ ጓደኛዬ መኪና ይዞ እቦታው እስኪደርስ መጠበቁ በገዛ ፍቃድ መለብለብ ስለመሰለኝ፣ በቀጥታ ከተደረደሩት ታክሲዎች አንዱን ይዤ ወደ ከዚራ አመራሁ፤ ድሬ የሄድኩት በዋናነት ከማህበራዊ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ምክንያት በመሆኑ ሊቀበለኝ የተዘጋጀውን ጓደኛዬን ደውዬ ከማውቃቸው የአንዱን ሆቴል ስም ጠቅሼ እዚያ እንድንገናኝ ነገርኩት፡፡
Ethiopian migrant workers, Saudi Arabaia, UNHCR, HRW
Ginbot Sebat, negotiations, Ethiopian, Government
ህዳር ፳፭(ሃያ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው ወር ጀምሮ ህጋዊ ወረቀት የላቸውም በሚል የውጭ ዜጎችን ማባረር የቀጠለችው ሳውድ አረቢያ፣ ከአለማቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድርጅት ትችት ቢደርስባትም፣ ዜጎችን ማስወጣት እንደምትቀጥል አስታውቃለች። አረብ ኒውስ እስካሁን በተወሰደው እርምጃ 126 ሺ ሰዎች ከአገሪቱ መውጣታቸውን ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ 90 ሺ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው መግባታቸውን ገልጸዋል። አረብ ኒውስ አንድ ባለስልጣንን …
ህዳር ፳፭(ሃያ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በደብረማርቆስ ከተማ ተደርጎ በነበረው የህዝብ ስብሰባ ላይ ነርካታ ነጋዴዎች በታክስ መማረራቸውን ገልጸዋል። መቶ አለቃ ስመኝ መኩሪያው እንዳሉት መንግስትን አክብረን በቫት ብንገባም በአንድ አነስተኛ የንግድ ሱቅ በየወሩ እስከ 73 ሺ ብር ተጠይቀን ፤ መንቀሳቀስ አልቻልንም የምንነግደውን ሊወርሰን የሚሽከረከረው መንግስት ሚዛኑ የሚጥልብን ግብር አስመርሮናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ “የምንሰራውን ስራ በማቋረጥ …
ህዳር ፳፭(ሃያ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቦንብ ተራና እና ጆንያ ተራ የሚባሉት አካባቢዎች ዛሬ ቀን ላይ በከፍተኛ የእሳት አደጋ የተጠቁ ሲሆን የከተማዋ የእሳት አደጋ በጊዜው ባለመድረሱም በነዋሪዎች ከፍኛ ተወቅሷል። የመስተዳድሩ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ የህዝብ ግኑኝነት ሰራተኛ አቶ ንጋቱ ማሞ በ10 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረው ጥሪው የደረሳቸው አደጋው ከደረሰ ከ45 ደቂቃ በሁዋላ መሆኑን ተናግረዋል። …
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen
የሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኛ ሠራተኞች ላይ እንደደረሱ በስደተኞቹ የሚገለፁ የሰብዓዊ መብቶች ረገጣዎችን የሣዑዲ አረቢያ መንግሥት እንዲያጣራ የመብቶች ተሟጋች ቡድኑ ሂዩማን ራይትስ ዋች ጠየቀ።
ቡድኑ ኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች በሳዑዲ ደረሱብን ያሏቸውን የመብቶች ረገጣዎች በዝርዝር አስቀምጦ፤ ጉዳዩ ተጣርቶ የድርጊቱ ፈፃሚዎች ለህግ እንዲቀርቡ ጠይቋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር – ዩኤንኤችሲአር ከሳኡዲ አረቢያ እየተመለሱ ላሉ ኢትዮጵያዊያን የፍልሰት ሠራተኞች ሰብአዊ እርዳታ ማድረግ መጀመሩን ገልጿል።
እርዳታው ከኮሚሽኑ ግዴታ ውጭ ቢሆንም ሰብአዊ ቀውስ ሲከሰት በዝምታ ማለፍ እንደማይቻልም አመልክቷል።
ይህ እርምጃ በቅርቡ አንዲት የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣን ሰጡ…
News, Ethiopians in America, Americana, Democracy and Women and Family
በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ ትላንት እና ዛሬ በደረሱ የእሳት አደጋዎች ከፍተኛ ንብረት መውደሙ ተሰማ።
የኣይን እማኞች እንደሚሉት ትላንትና ለሊት በከተማይቱ ቀበሌ 06 የኢንዱስትሪ ዞን ተብሎ በሚታወቅ ስፍራ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ በትንሹ 70 ያህል የማምረቻ ተቐማት ሙሉ በሙሉ ወድሟል።
በአውሮጳ ፣ በዩኤስ አሜሪካ እና በመካከለኛ ምሥራቅ የሚኖሩ አፍሪቃውያን በትውልድ አገሮቻቸው የሚኖሩ ዘመዶቻቸውን መርጃ በያመቱ በብዙ ሚልዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ይልካሉ።
ሰው ፣ ለኅልውናው ፣ ለጤንነቱ እጅግ የሚያስፈልገው ነገር ካለ ፣ በጥሞና አስቦበት፣ ያን ለማግኘትም ሆነ ለመፈልሰፍ ፣ ማትኮሩ ፤ መጣሩና እንዲያም ሲል ማሳካቱ አይቀርም። የአንድ ነገር ግኝት ፣ ምንጩ የአንድ ነገር ተፈላጊነት ነው። በእንግሊዝኛ (
በምዕራብ አፍሪቃዊቷ ሀገር ማሊ የጸጥታ ሁኔታዉ የቱዋሬግ አማፅያን በሰሜን የተኩስ አቁም ካወጁ በኋላ እየተጠናከረ መሄዱ ነዉ የሚነገረዉ። አካባቢዉ ለእስላማዊ ታጣቂዎቹ ተታኩሰዉ የሚያፈገፍጉበት እንደመሆኑ በየጊዜዉ ከባድ ጥቃት ይደርስበታል።
የዩክሬን መንግሥት ከአውሮፓ ህብረት ጋር ልዩ የንግድና የፖለቲካ ትብብር ውል ላለመፈረም በመወሰኑ የተነሳው ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል።በዋና ከተማይቱ በክዬቭና በሌሎችም ከተሞች አደባባይ የወጡ ተቃዋሚዎች የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ቪክቶር ያኑኮቪችና መንግሥታቸው ሥልጣን እንዲለቁ መጠየቃቸውን ቀጥለዋል።
የኑሮ ውድነት 40% ይጨምራል የሚል ጥናት ለጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ ቀረበ::
በሃገሪቱ የኢኮኖሚ ውንብድና ተስፋፍቷል::
የስራ አጦች መስፋፋት ሃገሪቱን የወንጀል መናኸሪያ እያደረጋት ነው::
የኢሕኣዴግ ኢኮኖሚስቶች በወረደላቸው መመሪያ በጋራ እና በተናጠል ባደረጉት ጥናት መሰረት በአገሪቱ በተለይ በከተሞች አከባቢ የኑሮ ውድነት በ40% ይጨምራል ሲሉ ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የፖሊሲ ጥናት ቡድን የጥናት ሪፖርታቸውን ያቀረቡ መሆኑን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ተናግረዋል::
የጥናት ሪፖርቱን ያቀረቡት የወያኔው ኤክስፐርቶች መንግስት የኢኮኖሚ ፖሊሲ በድጋሚ እንዲፈተሽ እና ማሻሻያዎች እንዲደረጉ ሲያሳውቁ በአገሪቱ የተንሰራፋው የሙስና እንቅስቃሴ ዋነኛው የኢኮኖሚው ማነቆ ከመሆኑም በላይ የፍትህ እና የንግድ ስርኣቱ መላሸቅ የኢኮኖሚ ቁጥጥሩን ስላላው ለዋጋ ንረቱ መንስኤ ናቸው ብለዋል::መንግስት ለግሉ ዘርፍ ያለው አመለካከት ደካማ መሆኑ እና ከፖለቲካ ባለስልጣናት ጋር ቁርኝት ያላቸው ነጋዴዎች ለመክበር የሚያደርጉት ሩጫ የህዝቡን የኑሮ ውድነት ጣራ እንዲነካ አድርገውታል::እንዲሁም የኢኮኖሚ ውንብድና በሃገሪቱ ላይ እየተፈጸመ ነው::የስራ አጦች ቁጥር መጨመር ሃገሪቱን የወንጀለኞች መናኸሪያ እያደረጋት ነው::
በአላቂ እቃዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ንረት ይከሰታል በሃገር ውስጥ ምርቶች ላይም ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ በሚቀጥለው አንድ አመት ይመጣል ያለው ጥናት የግሉ አምራች ዘርፍ ጥሬ እቃዎችን ወደ ሃገር ውስጥ በሚያስገባበት ጊዜ የተወሰነ የቀረጥ ክፍያ አለመኖሩ እና የመንግስት ባለስልጣናት እንዳሰኛቸው በየጊዜው እየቀያየሩ የህገር ውስጥ ምርቶች እንዲጎዱ የማኑፋክቸሪውም ዘርፍ እንዲዳከም በማድረግ ችግር እንዲፈጠር አድርገዋል::
ጥናቱ የባንኮችን መዳከም የስራ አጥነትን የስደትን የፖለቲካ ተጽእኖን የህዝቡን አስተያየት እና የገበሬውን ምሬት አጠቃሎ የያዘ መሆኑ የጠቆሙት ምንጮቹ መንግስት በሞኖፖል ንግዱን ይዞታል የውጪ ዜጎች ህገወጥ የኢኮኖሚ ስርኣት ዘርግተዋል ከፍተኛ ብዝበዛ በሃገሪቱ ምጣኔ ሃብት ላይ እየተደረገ ነው የሚሉ ዝርዝር ጥናቱን አቅርቧል:: ጥናቱ ይፋ ለውይይት ይቅረብ አይቅረብ የሚለው ገና ያልተወሰነ ሲሆን የጥናቱን ዝርዝር መረጃው ከምንጮቻችን እንደደረሰን የምናቀርበው መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን::
በእስራኤል ሃገር በአቶ ፋሲል ለገሰ የሚመራው IETV ወይንም ሁለተኛው ETV ሲመሰረት አላማው ኢትዮ-እስራኤሎችን በሙሉ ልቡ ህብረተሰብ ነክ ችግሮችን በማካተት ለህብረተሰቡ ይጠቅማሉ ብሎ ዓላማ ያደረጋቸውን ለምሳሌ፤- እኛ ኢትዮ-እስራኤሎችን እንዴት ከሰለጠነው ህብረተሰብ ጋር ማቀራረብ እንዳለበት እንዲሁም ባህላችንና ቋንቋችን ለ እስራኤል ህብረተሰብ በቀላሉ እንደ ድልድይ ሁኖ ለማገልገል በ እስራኤል መንግስት አመታዊ በጀት ተመድቦለት ጣቢያው አየር ላይ ከዋለ እንሆ ሦስት አመታትን አሳልፏል።
ነገር ግን ዓላማውን ስቶ ለኢትዮጵያ መንግስት ፕሮፖጋንዳነት በማዋል ጭራሽ የኢትዮጵያን አምባሳደር በየሳምንቱ እያቀረበ ስለ ኢትዮጵያ “ግምታዊ” እድገት ስለ አምስት አመቱ ትራንስፎርሜሽን ስለአባይ ግድብ እና ግንቦት 7 የአሸባሪ ቡድን እንደሆነ እነሱን ከቀረብን የኢትዮጵያ መንግስት ለፍርድ እንደሚያቀርበን ፡እንደነዚህ አይነት ገደብ የለሽ ፕሮግራሞች ይቀርቡልናል ። አቶ ፋሲል ለገሰ በመጀመሪያ ይህን አስተሳሰብዎትን መቀየር መቻል ይኖርቦታል። አንድ ህብረተሰብ ወስዶ እንደህፃን ልጅ ዋ.. ብሎ የሚያስፈራሩባት ያሻዎትን የሚያደርጉበት ኢትዮጵያ አይደለችም ። እስራኤል ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሃገር ውስጥ ነው ያለነው፡ ምንም እንኳን የፓርቲው ደጋፊና አቀንቃኝ እንደሆኑ የታወቅ ቢሆንም ጋዜጠኛ በሚለው ሙያ ላይ ጋዜጠኛ ለመባል ከሚያስፈልጉት ነገሮች ውስጥ ትንሾችን ለማድረግ ይሞክሩ።
ስለዚህ እኔ በግሌ የምሰጥዎት አስተያየት ቢኖር ነገሩ ለኢትዮ-እስራኤላውያን በቅቷል ። ይመለሱና ህብረተሰቡን ቃል በገቡበት መሰርት ያገልግሉ አዎ ህብረተሰቡ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ አያገባህም ከተባለ እስዎም አያገባዎትም ። ወይንም ለሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ድርጅቶች እና ፓርቲዎች በእኩልነት አገልግሎት ይሰጥ።
የፊታችን ታህሳስ 3 የእምዬ ምኒልክን 100ኛ እረፍት በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት እንደሚዘክር የታወቀ ነዉ፡፡ በፕሮግራሙ ላይም በርካታከሀገር ዉስጥና ከዉጪ ሀገር ምሁራን ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ይገኛሉ ተብሉ ይጠበቃል፡፡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ሰማያዊ ፓርቲ ለዝግጅቱ በሚያስፈልጉ ጉዳዩች ላይ ስራ እየሰራ ይገኛል! በስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ አዋጅ መሰረትም ስብሰባ እንደሚያደርግ ለስብሰባና ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ደብዳቤ በትናንትናዉ እለት ያስገባ ሲሆን ዘሬ በደብዳቤ የተመለሰዉ መልስ እጅጉን አስቂኝና አጠያያቂ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡

በደብዳቤዉ ላይ ለምታደርጉት ስብሰባ እዉቅና ልነሳጥችሁ አንችልም ምክንያቱም የፖሊስ ጥባቃ መመደብ አንችልም የሚል ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ደግሞ የፅፈት ቤቱ ሀላፊ ተብዬዉ አቶ አሰግድ በንቀት ደግሞ ማናችሁና ምኒልክ ምናምን የምትሉት ደግሞ ምኒልክ ማነዉ በሚል በእብሪት የመለሰዉ መልስ ነበር፡፡
እንኳን ድንኳን ጥሎ ለመሰብሰብ ይቅርና ጎዳና ሙሉ ህዝብ በመላበት የሩጫ የሰልፍ መሰል የገዢዉ ፓርቲ መልካም ፈቃድ ያገኙ ፕሮግራሞች ከህዝቡ እኩል ፌደራል ፖሊስ ለጥበቃ እንደሚታዘዝላቸዉ እየታወቀ ፤ በሌላ መልኩም በድፍረት እንወጣለን ብለን በተለያየ ምክንያት በተጠሩ ሰልፎች ላይ ለድብደባ የሚላከው ቁጥር ስፍር የሌለዉ የፀጥታ ሀይል አሁን ምን ቢውጠው ነዉ የጥበቃ የሚሆን የሰዉ ሀይል ልናስተባብር አንችልም ስለዚህ ዝግጅታችሁን እዉቅና አንሰጠዉም መባሉ??? ይህ ከእብሪት በላይ ምን ሊሆን ይችላል!!!?
ያም ሆነ ይህ ዝግጅቱ በታቀደለት ምልኩ እንደሚፈፀም በተለመደ ቁርጠኝነት ላይ ነን! ሲፈልጉ ለጥበቃ የከለከሉትን ሀይል ለድብደባ ይላኩት!!! እኛ የምንዘክራቸዉ ፍርሃት ካልፈጠረባቸዉ ሞተዉም መንፈሳቸዉ ካልተለየን እምቢ ባይ አባቶቻችን ተወልደናል፡፡
ድል ለኢትየጵያ ህዝብ!!!
‹‹ስደተኞችን በእንግድነት ተቀብለን እየተከባከብን አኑረናል፤ ሸኝተናል፡፡ እኛ ስደተኞች ኾነን እየተደበደብንና እየተገደልን መገኘት የለብንም፤ አይገባንም›› /ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሳዑዲ ዓረቢያ በመመለስ ላይ ለሚገኙ ወገኖች ማቋቋሚያ የሚኾን የሁለት ሚልዮን ብር ጊዜያዊ ርዳታ አበረከተች፡፡ ትላንት፣ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ከቀትር በፊት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ በተጠራ ጉባኤ ላይ …![]()
#MinilikSalsawi
‹‹መጀመሪያ በ‹‹አማራው›› ላይ መጡ ምንም አልተናገርኩም ምክንያቱም ‹‹አማራ›› አልነበርኩም፡፡ ቀጥለው ‹‹በኦሮሞ›› ላይ መጡ ምንም አላልኩም ምክንያቱም ‹‹ኦሮሞ›› አልነበርኩም፡፡ በመቀጠል ‹‹በሶማሊው፣ በጋምቤላው፣በትግሬው….ላይ መጡበት ምንም አልተናገርኩም ምክንያቱም ከአንዳቸውም አልነበርኩም ከዚህ በመቀጠል በሙስሊሙ ላይ መጡ አሁንም ምንም አላልኩም ምክንያቱም ሙስሊም አልነበርኩም በመቀጠል በክርስቲያኖቹ ላይ መጡ ምንም አልተናገርኩም ምክንያቱም ክርስቲያን አልነበርኩም በስተመጨረሻ በእኔ ላይ መጡብኝ አሁን ለእኔ የሚቆምልኝ ማንም አልቀረም፡፡ ብቻዬን ነኝ!››
ይህ በናዚዎች ስር የነበረው ህዝብ ታሪክ ነው፡፡ በአምባገነኖች ስር ያለና የነበረ ህዝብ ታሪክ ነው፡፡ የእኛው የኢትዮጵያውያን የወቅቱ ችግር ነው፡፡ኒይሞለር በአንደኛው የዓለም ጦርነት የተሳተፈና የናዚ ቀንደኛ ደጋፊ የነበር የፕሮቴስታንት ፓስተር ነበር፡፡ ጨፍጫፊው ናዚ ለጀርመናውያን እቆማለሁ ቢልም በሀሳብ የተለዩትን ጀርመናዊያን ላይ ግን ጠንካራ ብትሩን አሳርፎባቸዋል፡፡ እናም ኮሚኒስት፣ ሶሻሊስት፣ ቤተ እስራኤላዊያን፣ የሰራተኛ ማህበራት….ሌላም ሌላም ከናዚ አስተሳሰብ የሚቃረኑት በሙሉ በየተራ እርምጃ ተወሰደባቸው፡፡ በዛ ዘመን አንዱ ላይ እርምጃ ሲወሰድ ሌላው ዝም በማለቱ ናዚዎች የሚፈልጉትን ሁሉ በግፍ ጨፍጭፈዋል፣ አስረዋል፣ አሰቃይተዋል፡፡
በዚህ ወቅት የፕሮቴስታንቱ ፓስተር ማርቲን ኒይሞለር የሂትለርና የናዚ ደጋፊ ነበር፡፡ ምክንያቱም ኮሚኒስት፣ ሶሻሊስት፣ ቤተ እስራኤላዊያን፣ የሰራተኛ ማህበራት… የሚባሉት መካከል ብዙዎቹ ከፕሮቴስታንት ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው እንደ ጠላት አይቷቸዋል፡፡ ፓስተሩ ሂትለር ኮሚኒስቶቹን ሲያዝር፣ ሲገድል፣ ሲያግዝ ‹‹እግዚያብሄር አይወደውም፣ እነሱም ጀርመናውያን ናቸው፣ ይቅር ተባባሉ፣ ተቀራረቡ›› ከማለት ይልቅ እግዚያብሄር የማይወደውን እግፍ በአይኑ እያየ ዝምታን መረጠ፡፡
ናዚ ያልዳሰሰው የህብረተሰብ ክፍል፣ ካድሬ ለማድረግ ያልጣረው ጀርመናዊ፣ ከጎኑ ለማሰለፍ ያልሞከረው መሪ አልነበረምና በስተመጨረሻ ወደ እምነት ተቋማት ማምራቱ የግድ ነበር፡፡ እናም ፕሮቴትታንትም ቤተ ክርስቲያንም ከመጽሃፍ ቅዱስ ይልቅ የናዚን ‹‹ዶክትሪን›› እንድትቀበል ተገደደች፡፡ ልክ እንደኛው ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ማለት ነው፡፡ ናዚን አድንቆ የገባውን ካድሬ ‹‹የእምነት አባት›› እነ ሂትለር እጃቸውን ዘርግተው ተቀበሉት፡፡ በእምነታችን ጣልቃ ሊገባብን አይገባም ያሉት ግን አይቀጡ ቅጣት ተቀጥተዋል፡፡
ማርቲን ኒይሞለር የናዚን ‹‹ዶክትሪን‹‹ አልቀበልም ካሉት ‹‹አባቶች‹‹ መካከል አንዱ ነበር፡፡ ናዚ ሲያሰቃያቸው ዝም ብሎ ያያቸው ቤተ እስራኤላዊያን፣ ኮሚኒስቶች፣ ሶሻሊስቶች፣ የንግዱ ማህበራት…..የደረሰባቸው እጣ ፈንታ አሁን እሱ ጋ ደርሳለች፡፡ ከሌሎቹ ጋር ባለመተባበሩ ብቻውን ቀረ፡፡ ናዚዎች አስረው ሲያሰቃዩት ኖረው የተፈታው ጥምር ጦሩ ከአሸነፈ በኋላ ነው፡፡ ሆኖም ይህ ፓስተር ከስቃዩ በኋላ በእጅጉ ተጸጽቷል፡፡ እ.ኤ.አ እስከ 1984 ድረስ ስለ ሰላም ሰብኳል፡፡ ይህ ሰው ከሚታወቅባቸው መካከል ዝምታ አንድ በአንድ እንደሚያስጨርስ በእስር ዘመኑ የተናገረውና መግቢያየ ላይ ወደ እኛው ሁኔታ አጠጋግቼ የጠቀስኩት ወርቃማ አባባል ነው፡፡ እሱ ቃል በቃል ያለው እንዲህ ነበር፡፡
‹‹First they came for the communists, and I didn’t speak out because I wasn’t a communist. Then they came for the socialists, and I didn’t speak out because I wasn’t a socialist. Then they came for the trade unionists, and I didn’t speak out because I wasn’t a trade unionist. Then they came for me and there was no one left to speak for me.››
ይህ አባባል ከሌላ ብሄር፣ እምነት ወይንም ሌላ ማንነት ውስጥ ነኝ ብሎ በሌሎች ላይ የሚደረጉትን ጥቃቶች በቸልታ ለሚያልፍ አሊያም ከላይ የተጠቀሱት ‹‹ማንነቶች›› ውስጥም ሆኖ ግድ ለማይሰጠው ሰው ሁሉ የሚያገለግል ነው፡፡ በሌሎች ላይ የሚደረግን በዝምታ ሲያልፍ ኖሮ በስተመጨረሻ አብሮት የሚቆም አጥቶ በብቸኝነት ለሚጨቆን ሁሉ የተነገረ ነው፡፡
በእኛ አገር በአንዱ ቋንቋ ተናጋሪ ላይ ችግር ሲደርስ ሌላኛው ዝምታን ይመርጣል፡፡በእምነትም ቢሆን ተመሳሳይ ነው፡፡ ሙስሊሙ ሲነካ፣ ኦርቶዶክሱ ስለ መርህ፣ ስለመብት አብሮ አይጮህም፡፡ ሙስሊሙ፣ ፕሮቴስታንቱምና ካቶሊኩም የሚያደርገው ተመሳሳይ ነው፡፡ በተቃዋሚዎቻችን ሰፈር ደግሞ ይብሳል፡፡
በአገራችን ከሚነገሩት አሉታዊ አባባሎች መካከል ዝምታን የሚያበረታቱት በግንባር ቀደምነት ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ሌሎች በሚደርስባቸው ችግር ይቅርና በራሳችን ጉዳይ ዝምታን በመምረጥ ኢትዮጵያውያን ባህላችን አድርገነዋል፡፡ ዝምታ ወርቅ ነው፣ ዝም አይነቅዝም፣ ዝም ባለ አፍ ዝንብ አይገባበትም፣ ዝምን ማን ወሰደው፣ ብንናገር እናልቃለን…. እና በርካቶች ዝምታን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ ከመናገር ይልቅ ዝምታን የሚመርጠው ይህ ባህላችን ‹‹መቻል!›› የሚባል ቃልንም በምሳሌነት፣ በስምነትና በሌላም መልኩ በስፋት ይጠቀምበታል፡፡ ገዳይ ባህል!
የጀርመኑ ፓስተር የናዚ ቀንደኛ ደጋፊ ነበር፡፡ መጨረሻ ግን የሂትለር ዱላ ያመራው ወደሱው ነው፡፡ እንዲያውም ስቃዩን በወጉ የሚያይለት፣ ለዚህ ስቃዩ የሚቆረቆርለት አላገኘም፡፡ ደጋፊ፣ ካድሬ…..ም ቢሆን ስለ አንድ ብሄር፣ እምነት፣ ቋንቋ፣ ሙያ፣ አሊያም ስለ ራሱ ከዚህም ወረድ ሲል ፈርቶ ዝም ቢል የመጨረሻው መዓት እሱ ላይ ማረፉ የማይቀር ነው፡፡ የአሁኑን ጨምሮ ከገዥው ጋር የተሰለፉ ፖለቲከኞች፣ ካድሬዎች፣ ደጋፊዎችና ሌሎች አካላትም በስተመጨረሻ በትሩ ያረፈው እራሳቸው ላይ ነው፡፡
በቃ! የዝምታችን አባዜ ይህ ነው ትርፉ፡፡ ልክ እንደዚያ ቄስ፣ ልክ እንደኛ ፖለቲከኞች፣ ልክ እንደአገራችን የእምነት ተቋማት፣ እንደ ማህበራት፣ ምሁራን፣ ልክ የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪዎች የተለመደ ተግባር ዝምታ፣ ‹‹ምን አገባኝ!››፣ የፖለቲካ እሳትነት ብቻችን ያስበላናል፡፡ አስበልቶናልም፡፡ ማንም ስቃያችን ሳያይልን፣ ማንም ሳይጮህልን፣ ማንም ሳይቆምልን ያስፈጀናል፡፡ ያስጨርሰናል፡፡ ዝምታ ከወርቅ ይልቅ እንደሚያበሰብስ፣ እንደሚነቅዝና እንደሚያነቅዝ የምናውቀው ብቻችን እጣ ፈንታችን ሰንጎነጫት ነው፡፡ በጣም እጅግ በጣም ከመሸ!
“ኢሕአዴግ ሃገሪቱን ወደ እርስ በርስ ጦርነት እንዳይከታት እሠጋለሁ” ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር ናቸው፡፡ ላለፉት 30 ዓመታት በአሜሪካ ኖረዋል፡፡ የየትኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆኑና ሆነውም የማያውቁት ዶ/ር ዳኛቸው በሀገሪቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ግን ምሁራዊ አስተያታቸውን በየጊዜው ይሰጣሉ፡፡ ከዶ/ር ዳኛቸው ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሎሚ አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ያደረገው ቆይታ ይህንን ይመስላል፡-
በሳውዲ የተነሳው የወገን ሰቆቃ ገና አልበረደም። ስቃዩ የበለጠ ሲከፋ እንጂ ሲቀንስ አላየንም። ለውጭ ምንዛሪ ማግኛ ሲባል ልክ እንደ ባርያ ንግድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ በኩል የተላኩት ምስኪን ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በገዥው ፓርቲ እንደታሰበው አልሆነም። እንዲያውም ሌሎች መዘዞችን አስከትሎ መጥቷል። ዲያስፖራው እንደገና ተነሳ። ለቦንድ ግዢና ለግንቦት ሃያ በዓላት የሚሰባሰቡትም ጭምር ገዢው ፓርቲን ማውገዝ ጀመሩ። የስደተኛው ጎርፍም እንደሱናሚ ማእበል […]
“እነ አቶ ልደቱ የፖለቲካ መጠቀሚያ ነው ያደረጉን”
ዶ/ር ኃይሉ አርአያ
ዶ/ር ኃይሉ አርአያ በኢዴፓ በኋላም በቅንጅት አመራርነት አገልግለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአንድነት ፓርቲ ምክር ቤት አባል ናቸው፡፡ የ”ሎሚ” አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ከዶ/ር ኃይሉ አርአያ ጋር ሰፊ ቃለመጠይቅ አድርጓል፡፡ በሃገር ቤት የሚታተመውን ሎሚ መጽሄት በውጭ ሃገር ለማታገኙት ወገኖች ቃለምልልሱን ዘ-ሐበሻ ትካፈሉት ዘንድ አስተናግዳዋለች።
ሎሚ፡- እርስዎ ያዘጋጁዋት የነበረችው “ፕሬስ ዳይጀስት” ለዲፕሎማቲኩ ማህበረሰብ ኢትዮጵያን በተመለከት መረጃ የሚሰጥ “ታብሎይድ” ነበር፡፡ የትንሿን ጋዜጣ ዝግጅት ለምን አቋረጡት?
ዶ/ር ኃይሉ፡- ጋዜጣዋ አሁንም እየተዘጋጀች ነው፡፡ እኔ ግን ያቋረጥኩት ጋዜጣዋ የምትፈልገውን ጊዜ እና ጥረት ማበርከት ባለመቻሌ ነው፡፡ በአጭሩ ብዙ ጊዜ ይጠይቃል፡፡ ዝግጅቱ ብዙ ጊዜ የመጠየቁን ያህል ደግሞ ብዙ ጥቅምም አያስገኝም፡፡ ከዚያም ባሻገር ስራው የሦስት ሰዎች ስራ ነበር፡፡ ግን የሦስት ሰዎችን ጥረት የሚጠይቅ ስራ አልነበረም፡፡ በዚያን ጊዜ ሌላ የምሰራው ስራ ስላልነበረ ሁላችንም ትንሽ ትንሽ እየሰራን ነበር የምናሣልፈው፡፡ የአንድ ሰው ስራ ነው፡፡ የአንድ ሰውም የሙሉ ጊዜ ስራ አልነበረም፡፡ ስለዚህ ጊዜ ከማባከን ያንን ለአንድ ሰው ትቶ ሌሎቻችን ሌላ ስራ ብንሰራ ይሻላል በሚል ነው የተውነው፡፡
ሎሚ፡- በደርግ ዘመን “የብሔረሰብ ጥናት ኢንስቲቲዩት” ኃላፊ እርስዎ እንደነበሩ ይታወሳል፤ ኢንስቲቲዩቱ ምን አስተዋጽኦ አበረከተ? አሁን የብሔረሰብ መብት ተከብሯል ከሚባለው ጋር ሲያነጻጽሩት “የብሔረሰብ ጥናት ኢንስቲቲዩት” ሰርቶታል የሚሉትን አብይ ጉዳይ ሊገልፁልን ይችላሉ?
ዶ/ር ኃይሉ፡- በመጀመሪያ የኢንስቲቲዩቱ ኃላፊ አልነበርኩም፡፡ ኢንስቲቲዩቱ ራሱ ኃላፊ ነበረው፡፡ እንደውም ኃላፊው የሚኒስትር ማዕረግ ነበረው፡፡ በኢሠፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ የብሔረሰቦች ጉዳይ መምሪያ በሚባለው ቦታ በምክትል ኃላፊነት ነበር የምሰራው፡፡ ያ መምሪያ ነው ተቋሙን ያቋቋመው፡፡ ብዙ የሚሰሩ ስራዎች ነበሩ፤ ጥናቶች ነበሩ፤ ሕገ መንግስቱን ለማዘጋጀት ብዙ ጥናቶች መደረግ ነበረባቸው፡፡ የኢሠፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ የነበረው የኛ መምሪያ ብዙ ስራ ሊሰራ ስለማይችል የግዴታ ራሱን ችሎ ለመንቀሣቀስ “ኢንስቲቲዩቱን” መመስረት አስፈላጊ ነበር፡፡ ስለዚህ “የብሔረሰቦች ጥናት” ኢንስቲቲዩት ተቋቋመ፡፡ ነገር ግን በመምሪያችን ስር ነበር፡፡
የእኛ መምሪያና ኢንስቲቲዩቱ አብረው ነበር የሚሰሩት፡፡ ጥናቶች ሲካሄዱ አብረን ሁላችንም እንሳተፋለን፤ አመራር የሚሰጠው ግን ከመምሪያው ነበር፡፡ በሁሉም ዘርፍ ለአምስት ዓመት ያህል ነው ኢንስቲቲዩቱ ጥናት ያካሄደው፡፡ በዛን ጊዜ የተሰሩ ስራዎች ኢህአዴግም ከመጣ በኋላ ብዙ ጠቅሞታል ብዬ ነው የምገምተው፡፡ ያኔ የህግ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት ሰው አሁን በሚኒስትሮች ምክር ቤት ያሉ ይመስለኛል፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የህግ አማካሪ ናቸው፡፡ ሌሎችም በሀገሪቱ አሉ የተባሉ ምሁራን ተሰባስበው ከፍተኛ ጥናት አካሂደዋል፡፡ በጣም ጠቃሚ የሆኑ ጥናቶች ናቸው የተካሄዱት፡፡ ጥናቶቹ አልባከኑም ብዬ አምናለሁ፡፡ በርግጥ የተፈለገው ሕገ መንግስት በተደረጉት ጥናቶች መሠረት ተቀርጿል፡፡ መቅረፅ ብቻም አይደለም፤ ስራ ላይም ውሏል፡፡ በተለይ በብሔረሰቦች ላይ የተደረገው ጥናት በዝርዝር ነው የተካሄደው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የብሔረሰቦች መብት ምን ያህል ተከብሯል የሚለው የትኩረት መጠን ካልሆነ በስተቀር ያኔ የተደረገው የብሔረሰቦች ጥናት እና የተሰጠው የብሔረሰቦች ትኩረት በጣም ከፍተኛ ነበር፡፡ የኢህአዴግ መንግስት ስለ ብሔረሰቦች መብት መከበር እንደ አዲስ የጀመረ በማስመሰል ሲናገር ስሰማ በጣም አዝናለሁ፡፡ በዛን ጊዜ የነበረውን ነገር አልተከታተለውም፤ ውጊያ ላይ ስለነበር ሊከታተልም አይችልም፡፡ ውጊያ ላይ እያለ ባይከታተልም ስልጣኑን እና ኢንስቲቲዩሹኑን ከተረከበ በኋላ በዛን ጊዜ የነበሩ ሰነዶችን መመርመር ይችል ነበር፡፡ ሰነዶቹ አሁንም ይኖራሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡ ኢህአዴግም ተጠቅሞባቸዋል ብዬ ነው የምገምተው፡፡
“የብሔረሰቦች መብት” ኢህአዴግ እንደ አዲስ የጀመረው ጉዳይ አይደለም፡፡ በባህላቸው፣ በቋንቋቸው…በሌላውም አቅጣጫ ኢህአዴግ እንደ አዲስ እንደጀመረ አድርጐ ነው የሚያወራው፡፡ ይህንን ትዝብት መቼም ለታሪክ እንተወዋለን፡፡ የደርግ ስርዓት ሌሎች ድክመቶች ሊኖሩበት ይችላል፡፡ የብሔረሰቦችን ጉዳይ በተመለከት ግን መሠረቱን ያስቀመጠው የደርግ ስርዓት ነው፡፡ ኢህአዴግ ምናልባት አጠናክሮታል፣ አስፋፍቶታል ማለት ይቻላል፡፡ አንደ አዲስ ጀመርኩት የሚለው ነገር ግን ከእውነት የራቀ ነው፡፡ ይህ ሊስተካከል ይገባል፤ ምክንያቱም ታሪክ ራሱ ቁጭ ብሎ የሚመሰክርበት ጉዳይ ስለሆነ በዝምታ ማለፍ ነው የሚሻለው፡፡ የብሔረሰቦችን ጉዳይ በተመለከተ እንዲሁ ለይስሙላ ከሚደረግ በስተቀር ነፃ የሆነ ለውጥ ተደርጓል ብዬ አልገምትም፡፡ ምናልባት በጥቅም፣ በሀብት አከፋፈል በጀትን በተመለከተ ለብሔረሰቦች የሚመደበው ገንዘብ አሁን በከፍተኛ መጠን ጨምሯል፡፡ ሌላው የቅርፅ ጉዳይ ነው፡፡ ብሔረሰቦች የሕገ-መንግስት ባለቤት ሆነዋል፡፡ ህገመንግስትን መስርተዋል፤ ሕገ መንግስት አላቸው፤ ሰንደቅ አላማም ያውለበልባሉ…እነዚህ ከቅርፅ አኳያ ለውጦች ናቸው፡፡ እነዚህ የቅርፅ ለውጦች በተግባር ቢደገፉ ጥሩ ይሆኑ ነበር፡፡ ነገር ግን አልተደገፈም፡፡ ምክንያቱም ብሔረሰቦች አሁንም መሠረታዊ የሆኑ ችግሮች አሉባቸው፡፡ መሠረታዊ የምላቸው በኔ በኩል የህግ መከበር ነው፡፡
ህጐች ይጣሳሉ፤ መብቶች ይደፈራሉ፤ ምን ያህል ነፃነት እንዳላቸውም እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ምንም እንኳን ስርዓቱ ፌዴራል ቢሆንም ቅርፁ ፌደራላዊ ቢሆንም በተግባር ግን “አሃዳዊ” ነው፤ ምክንያቱም በደርግ ጊዜ መንግስት “አሃዳዊ” ነበር፡፡ ክልሎች የአስተዳደር መብት ነበራቸው፡፡ ያም ቢሆን በሚገባ ተግባራዊ አልሆነም፡፡ ከይዘት አኳያ በደርግ አሃዳዊ መንግስትና በኢህአዴግ ፌደራላዊ መንግስት መካከል ልዩነት አለ፡፡ “ደርግ” የነበረው የውስጥ አስተዳደር ነው፤ የኢህአዴግ ግን ፌዴራል ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ብሔረሰቦች ሕገ መንግስት አላቸው፣ የራሣቸው መንግስትና ባንዲራ….አላቸው፡፡ በዛን ጊዜ የነበረው ኢሠፓ መዋቅሩን ታች ድረስ አውርዶ ሀገሪቱን የሚያስተዳድረው ኃይል እርሱ ነበር፡፡ ኢህአዴግ ምንም እንኳን በቅርፅ “ፌደራላዊ” ቢባልም ሀገሪቱን ጠርንፎ በአሃዳዊ መልክ ነው የሚያስተዳድረው፡፡ በሁለቱ መካከል የይዘት ልዩነት የለም፡፡ ለውጡ ምንድነው? ብትለኝ ጥቂት ነው፡፡ እምቢልታና መለከት የሚያስነፉ አይደሉም፡፡ አሁንም ብሔረሰቦች ይጨቆናሉ፡፡
የሚጨቁኗቸው ደግሞ የራሣቸውን ቋንቋ የሚናገሩ የራሣቸው ወገኖች ናቸው፡፡ ስለዚህ አሁንም ከጭቆና እና ከችግር አልወጡም፡፡ ፌደራላዊ ስርዓት ጥሩ ሆኖ ከአሃዳዊ ሲለይ አልታየም፡፡ ሕዝቡ ቢጨቁነኝም ይጨቁነኝ፣ ቢረግጠኝም ይርገጠኝ፣ የኔን ቋንቋ እስከተናገረ ድረስ የሚል ከሆነ ሌላ ነገር ውስጥ ነው የሚገባው፡፡ ለኔ ቋንቋ አይደለም ትልቁ ነገር:: ከዛ ባለፈ ሕግ መከበር አለበት፤ ፍትህ መከበር አለበት፤ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት መከበር አለበት፡፡ እውነተኛ ነፃነት መኖር አለበት፡፡ አሁን የብሔረሰቦች ቀን ተብሎ “በዓል” ይከበራል፡፡ ሰባት ዓመት ሙሉ ተከብሯል መሰለኝ፡፡ ስምንተኛው በዓል በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ነው የሚከበረው፡፡ በአንድ በኩል ይህ ጥሩ ነው፡፡ ምክንያቱም በብሔረሰቦች መካከል ያለውን ስሜት በማጠናከር እና በራስ መተማመንን ለማምጣት የሚረዳ ነገር ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ እንዲሁ ዘፈንና ጫጫታ ሆኖ መሠረታዊ ጉዳዮች ሣይደረጉ ሲቀሩና እዛው በቦታው ሲመለስና እንደ ድሮው የሚጨቆን ከሆነ ምንድነው ትርጉሙ? የሰው ልጅ ፍላጐት ከዛ ያለፈ ነው፡፡ ይሄ ግን እየተመለሰ አይደለምና ከዳንሱና ከጭፈራው ጐን ለጐን የብሔረሰብ ነፃነት ሊከበር ይገባል፡፡ ሊሰሩ የሚችሉበት ነፃነት ይኑራቸው፡፡ ትምህርትን፣ የጤና አገልግሎትን ያየን እንደሆነ ተስፋፍቷል፡፡ “በቁጥር” ተስፋፍቷል፤ “በጥራት” ግን ገና ነው፡፡ መስፋፋቱ ጥሩ ነው፤ ግን ቁጥር ብቻ በቂ አይደለም፡፡ ይሄ መንግስት አሁን እየጠቀሰልን ያለው ቁጥር ነው፡፡ ይህን ገንብቻለሁ እያለ በሁሉም ዘርፍ ይገልፃል፡፡ ያ ብቻ በቂ አይደለም፡፡ በጥራት መሻሻል አለበት፡፡ ቁሣዊና ሰብአዊ ልማት አለ፡፡
መንግስት እየተገበረ ያለው ቁሣዊ ልማትን ነው፡፡ ሰብዓዊ ልማት የለም፡፡ ሰብዓዊ ልማት ያለ ነፃነት፣ ያለፍትህ፣ ያለ ዴሞክራሲ ይሄን ያህል ጠቃሚ አይደለም፡፡
ሎሚ፡- በሚያዝያ 1983 ዓ.ም. ደርግ ባቋቋመው ሸንጐ የመጨረሻ ስብሰባ ላይ አባል እንደመሆንዎ ተገኝተው ለኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም የተናገሩትን ለዚህ ትውልድ መረጃ እንዲሆን ቢያስታውሱን?
ዶ/ር ኃይሉ፡- ጊዜው በጣም አስቸጋሪ ነበር፡፡ ሀገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ነበረች፡፡ ሀገሪቱን እመራለሁ፣ ግንባር ቀደም ነኝ የሚለው የፖለቲካ ድርጅት (ኢሠፓ) በየጊዜው እየተሰባሰበ የሀገሪቱን ሁኔታ እየገመገመ ሕዝቡ ምን እንደሚልና በሚለው መሠረት ምን መደረግ እንዳለባቸው ማወቅ ነበረበት፡፡ ግን ሳያደርግ ቀረ፡፡ ስብሰባዎች እንዲካሄዱ ነበር ብዙ ጊዜ የምንጐተጉተው፡፡ ከዛ ከፓርላማ ስብሰባው በፊት ኢሠፓ ተሰብስቦ የዚህችን ሀገር ሁኔታ እንዲገመግም፣ መፍትሄ እንዲፈልግና ተግባራዊ እንዲያደርግ በየጊዜው በሚደረጉ የመሠረታዊ ድርጅት ስብሰባዎች እንከራከር ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም አይነት ውጤት አልተገኘም፡፡ ነገሮች እየተባባሱ ሄዱ፡፡
በመጨረሻ የተደረገው ተስፋ የመቁረጥ ዓይነት ሙከራ ነው፡፡ ሙከራው ቢዘገይም ከሚቀር ይሻላል፡፡ ምንም ካለማድረግ የተወሰነ ነገር ማድረግ ጥሩ ነው፡፡ ይሄ የግል ስሜቴ ነው፤ የግል ስሜቴን ለመግለፅ ነው የሞከርኩት፡፡ ግን አሁን መለስ ብዬ ያለንበትን ሁኔታ ሳይ ደግሞ ያን ያህል ጊዜ መዘግየት አልነበረብንም እላለሁ፡፡ ጊዜ መስጠት አልነበረብንም የሚል እምነት አለኝ፡፡ አሁን ደግሞ ለዚህ ስርዓት አላግባብ ተገቢ ያልሆነ ጊዜ እየሰጠን ነው፡፡ በስልጣን በቆየ ቁጥር እየበሰበሰ ነው የሚሄደው፡፡ በተፈጥሮው ስልጣን ያሞስናል፤ ያበሰብሳል፡፡ አንድ ወገን፣ አንድ ኃይል ስልጣን ላይ ከሚፈለገው በላይ በቆየ ቁጥር እየበሰበሰ ይሄዳል፡፡ ይሄ እኮ የተፈጥሮ ሂደት ነው፡፡ ሌሎች ሀገሮች የፕሬዚዳንትና የጠ/ሚኒስትር (በተለይ “የፕሬዚዳንት”ን) የስልጣን ቆይታ የቱንም ያህል ጥሩ ቢሆን ከስምንት አመት በላይ አያልፍም፡፡ ስለዚህ ሀገሪቱን ትጐዳለህና ቦታ ልቀቅ ነው የምትባለው፡፡ የኛ መንግስት እስካሁን ድረስ ብዙ ቆይቷል፡፡ 22 ዓመት ብዙ ነው፡፡ በኔ እምነት መበስበስ ከጀመረ ቆይቷል፡፡ የመበስበሱ ምክንያቶች በየጊዜው እየታዩ ናቸው፡፡ መቀጠል የለበትም ብለን መናገር አለብን እንጂ ዝም ማለት የለብንም፡፡ ከዚህ በፊት ዘግይተን ከነበረ እናዝናለን፡፡ በስንፍናችን እናዝናለን፤ እንቆጫለን፡፡ ነገር ግን ከዚያ ተምረን ያ መደገም የለበትም እንላለን፡፡ የሀገራችን ጉዳይ መፍትሄ ማግኘት አለበት፡፡ ገደብ የሌለው ስልጣን መፍትሄ ማግኘት አለበት፡፡ እነሱ ሥልጣን ላይ የተቀመጡት ሕዝብ ስለፈለጋቸው አይደለም፡፡ በእንዴት ዓይነት ሁኔታ ስልጣን ላይ እንደወጡ የኢትዮጵያ ሕዝብም እነሱ ራሣቸውም ያውቁታል፡፡ አዲሱ ትውልድ በተለይ ወጣቱ ትውልድ መናገር መቻል አለበት፡፡ ለመብቱ ለነፃነቱ መቆም መቻል አለበት፡፡ አስፈላጊ ከሆነም ደግሞ መስዋዕትነት መክፈል አለበት፡፡
ሎሚ፡- በዚያ ወቅት በትግራይ ተወላጆች ላይ ግድያ ሲፈጸም የድፍረት ንግግር ለመናገር የገፋፋዎት የተለየ ምክንያት ምን ነበር?
ዶ/ር ኃይሉ፡- በወቅቱ ካለፈው ታሪኬ የተነሣ እንደ አደገኛ ሰው የታየሁ አልመሰለኝም፡፡ ፍራቻም አልነበረኝም፡፡ እንዲያውም የትግራይ ተወላጅ መሆኔን
ያስታወስኩት እኮ ዘግይቼ ነው፡፡ ጐሣ፣ ጐጥ… እየተነሣ ሲመጣ ነው ይሄ ነገር
መጉላት የጀመረው፡፡ እንጂ በፊት እኔ የዚህ ተወላጅ ነኝ፣ የዛ ተወላጅ ነኝ የሚል
ነገር አልነበረም፡፡ ስሜቱም አልነበረኝም፤ ትግራይ ነው የተወለድኩትና በተወለድኩበት አካባቢ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ነው ያደግኩት፡፡ በአጋጣሚ ትግራይ ማይጨው ራያ ተወለድሁ፡፡ የተወለድኩበትን አካባቢ እቀበላለሁ፡፡ ግን እዚያ ትግራይ በመወለዴ ልዩ ነገር ይገባኛል የሚል አመለካከት የለኝም፡፡ እዚያ መወለዴም ስጋት አላሳደረብኝም፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ ሰው ነኝ፤ ከዛ በኋላ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ በዛ ምክንያት እንዲህ እሆን ወይ ጉዳት ይደርስብኝ ይሆን ወይ ብዬ አላስብም፡፡ እንደውም በዛን ጊዜ ኮ/ል መንግስቱ ፊት እንደዛ ስናገር ሰዎች በጣም ደንግጠው ከአካባቢው ለመራቅ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ በኋላ ደግሞ ታስታውስ እንደሆነ ኮ/ል መንግስቱ በፃፉት ጽሁፍ /እኔ እንኳን መፅሐፉን ሣይሆን በቴፕ ነው የሰማሁት/ “ዶ/ር ኃይሉ እንደዛ የተናገረው ምናልባት ዘመዶቹ አምቦ ስለደረሱ ይሆናል፤ /ሣቅ/ ነው፤ ለኔ እንዲህ ዓይነት ስሜት ነው የፈጠረብኝ” ብለው ነበር፡፡ በጣም አሣዘነኝ፤ ምናቸው ነው ለኔ ዘመድ የሚያደርጋቸው?… በጣም አዘንኩ፤ የማንነት ጉዳይ አንዳንዴ ብወድም ባልወድም ብልጭ ማለቱ አይቀርም፡፡ ትኩረት የምሰጠው ነገር ግን አይደለም፡፡ ፍርሃት አልነበረብኝም፡፡ ያኔ የትግራይ ተወላጆች ብቻ አይደለም የሚገደሉት፤ ማንም ያንን መስመር የሚቃወም ሁሉ ነበር የሚገደለው፡፡
ሎሚ፡- ኮ/ል መንግስቱ እንደዛ ከተናገሩ በኋላ ቤትዎ ገብተው በሰላም አደሩ?… ሌሊቱን የት አሣለፉ? የኮ/ል መንግስቱ የደህንነት ሰዎች ምላሽስ ምን ነበር?
ዶ/ር ኃይሉ፡- ምንም ችግር አልደረሰብኝም፡፡ ሰዎች ወስደው የት እንዳሳደሩኝ አላስታውስም፡፡ ብቻ የሆነ ቦታ ነው የወሰዱኝ፡፡ የተለየ ነገር አልገጠመኝም፡፡ አስታውሳለሁ፤ ኮ/ል ተስፋዬ ወ/ስላሴ /የደህንነት ኃላፊው/ “ጐሽ ጥሩ ነው ያደረግከው” ብሎ መለስ ቀለስ እያለ እየፈራ እየቸረ ነው ያናገረኝ፡፡… /ረዥም ሳቅ/፡፡… በኋላ ጡረታ እንድወጣ ደብዳቤ ተፃፈ፡፡ በነገራችን ላይ ቀደም ብዬ ነበር ጡረታ እንድወጣ የጠየቅኩት፡፡ ነገር ግን በተለያየ ምክንያት ጥያቄዬ ተግባራዊ ሳይሆን ቆይቶ ነበር፡፡ ወዲያው የተወሰደውን እርምጃ ሰዎች ነግረውኛል፡፡ …ኮ/ል መንግስቱ በጣም ተቆጥተው ነበር፡፡ ነገር ግን ብዙዎቹ ለምነን አባብለን ነው ያስታገስናቸው ብለውኛል፡፡ አንደኛው የማውቀው ወዳጄ “እንዲያውም እግራቸው ላይም እስከመውደቅ ደርሰናል“” ሲል ነበር የነገረኝ፡፡ ይህ ምን ያህል እውነት እንደሆነ አላውቅም፡፡ መናደዳቸው አያከራክርም፤ እግዚአብሔር ይመስገን የከፋ ነገር ግን አልደረሰብኝም፡፡ በእሣቸው የደህንነት ሰዎችም የደረሰብኝ ነገር የለም፡፡
ሎሚ፡- እንግዲህ ውይይታችን ሰፊ ነውና ወደኋላም ወደፊትም እያልን ጥያቄ እናንሳ፤ ወደ ቅርብ ጊዜው እንመለስና ወደ ቅንጅት (ምርጫ 97) ግርግር እንምጣ፡፡ በወቅቱ አቶ ልደቱ የነበረው አቋም በእርግጥም የኢዴፓ ውሣኔ ነበር? በቅርቡ አቶ ልደቱ ከመፅሔታችን ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ “የስልጣን ጥያቄ ስላልነበረን የበሰሉ ሰዎች ቢመሩት ይሻላል ብለን ነው ዶ/ር ኃይሉ አርአያን እና ዶ/ር አድማሱን ከቤታቸው አምጥተን ስልጣን እንዲይዙ ያደረግነው” ብሏል፡፡ ይሄን እንዴት ይመለከቱታል?
ዶ/ር ኃይሉ፡- በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ብዙ መናገር አልፈልግም፡፡ ይሄ በእኔና በአንተ ቃለ መጠይቅ ላይ ብቻ ተገልፆ የሚያልቅ አይደለም፡፡ በጣም ሰፊ የሆነ ታሪክ ነው፡፡ ግን መናገር ካለብኝ አንድ ወጣት (ታምራት ታረቀኝ) የሚባል መፅሐፍ ፅፎ ነበር፡፡ ምናልባት እዚያ ላይ ያለውን ብደግመው በቂ ይሆናል፡፡ ተጠቅመውብናል ማለት እችላለሁ፡፡ በዛን ጊዜ የነበሩ የኢዴፓ አመራር /እነ አቶ
ልደቱ/ ተጠቅመውብናል፡፡ ከተጠቀሙብን በኋላ ጊዜው ሲመጣ እኛን ወደ ጐን ለማግለል ሞክረዋል፡፡ አቶ ልደቱ ብዙ ውይይት የሚከፍት ሰው ነው፡፡ መጠቀሚያ አደረገን እንጂ በምሁርነቴ ጠርቶ ይሄ ቦታ ይገባሀል ብሎ አይደለም ቦታ የሰጠኝ፡፡ በኔ ውስጥም የሚሰማኝ ይሄ ነው፡፡
ሎሚ፡- አቶ ልደቱ “ዶ/ር ኃይሉ አርአያ ከቅንጅት ጋር የትም አንደርስም” ብሎ
ይከራከር ነበር ሲልም ገልጿል፤ ይሄስ እውነት ነው?
ዶ/ር ኃይሉ፡- ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው፡፡ በተቃራኒው ነው እሱ የገለፀው፡፡ ከቅንጅት ጋር አብሮ ስለመስራት ነበር የኔ ክርክር የነበረው፡፡ አቶ ልደቱ በወቅቱ ብዙ ነገር የተወሳሰበና የተተበተበ ነገር ነበር የሚያነሣው፡፡ እንዲያውም “ቅድመ ሁኔታዎች” በሚል ይከራከር ነበር፡፡ በኔ በኩል በቅንጅት ዙሪያ መግባባት አለብን የሚል አቋም ነው የነበረኝ፡፡ በአቶ ልደቱ የተገለፀው የተገላቢጦሽ ነው፡፡
ሎሚ፡- ኢዴፓ ያንን አጋጣሚ አክሽፏል ብለው ያምናሉ?
ዶ/ር ኃይሉ፡- አዎ! አምናለሁ! በሁለት ምክንያት፡፡ አንደኛ ከምርጫ በኋላ የቅንጅት አመራር የአራቱ ፓርቲ አመራር ከልደቱ በስተቀር ለመዋሃድ ውሣኔ ሲያሳልፍ እና መሪዎቹ ፊርማቸውን ሲያሳርፉ በስምምነቱ ላይ አቶ ልደቱ በኢዴፓ ሰነድ ላይ ማህተም ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ማህተሙ ሳያርፍ ቀረ፡፡ ይሄ የሆነው ማህተሙን የሙጥኝ ብሎ በመያዙ ነው፡፡ ሁለተኛ ለምርጫ ቦርድ በቅንጅት የተጠየቀው የውህደት ጥያቄ ተግባራዊ እንዳይሆን የሚል ደብዳቤ በማስገባቱ ያለጥርጥር ያንን ዕድል አክሽፎታል ብዬ አምናለሁ፡፡ ይሄን ስል ግን ሌሎችም ችግሮች አልነበሩም ማለቴ አይደለም፡፡ ሌሎችም ችግሮች ነበሩ፡፡ ቀሪዎቹ የፖለቲካ ድርጅቶች ራሣቸው አስፈላጊውን ጉባኤ አካሂደው ማሟላት ያለባቸውን ነገሮች አሟልተው አንድ መሆን ሲገባቸው ሣይችሉ ቀርተዋል፡፡ ያ ብቻም ሣይሆን ያከሸፈው ሌሎች የውስጥ ችግሮችም ነበሩ፡፡
ሎሚ፡- በወቅቱ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ሲመረጡ በአቶ ልደቱ ላይ ምን ዓይነት ስሜት ነበር የታየው?
ዶ/ር ኃይሉ፡- ብርቱካን በተመረጠችበት ጊዜ አቶ ልደቱ መበሣጨቱ ምንም የሚያከራክርና አንድና ሁለት የሚባል ነገር አይደለም፡፡ በጣም በጣም ተበሣጭቷል፡፡ በግል የተመለከትነው ነገርም ነው፡፡
ሎሚ፡- ከእርስዎ ጋር በኢዴፓም ሆነ በቅንጅት ውስጥ ሲሰሩ የነበሩት ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ ከፖለቲካ የራቁበት ምክንያት ምንድን ነው?
ዶ/ር ኃይሉ፡- ይህንን ጥያቄ መመለስ የሚገባው እሱ ዶ/ር አድማሱ ነው፡፡ እንደው ስገምተው ግን አንደኛ የትምህርትና የስራ ዕድልም ስላገኘ ይመስለኛል፡፡ ለባለቤቱም ጭምር ነው ይህ ዕድል የመጣው፡፡ ምክንያቱም የኛን ሃገር የመሰለ ፖለቲካ በሩቅ የሚከናወን አይደለም፡፡ ምናልባት አንድ ቀን ይመለስና የጀመረውን ትግል ይቀጥልበታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ሁለተኛ ደግሞ የዚህ ሀገር ተቃዋሚዎች ሁኔታ ደግሞ የሚያበረታታና ተስፋ የሚያጭርም አይደለም፡፡ ብዙ ችግሮች አሉ፡፡ አሁን አንዳንድ መሻሻሎችና መስተካከሎች የሚኖሩ ይመስላሉ፡፡ ምናልባት እነዚህ የ33ቱ ፓርቲዎች የመሰባሰብና አንድ ላይ ለመስራት የመወሰን ጉዳይ የሚያበረታታ ነው፡፡ ነገር ግን የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራችን በፊትም ቢሆን እንኳን ሩቅ ላለና እዚህ ሀገር ውስጥ ላለም የሚያበረታታ ተስፋ የሚሰጥ አይደለምና አልፈርድበትም፡፡ እንዲህ እግዚአብሔር ሲፈቅድ ወደሀገሩ ጠቅልሎ መጥቶ እገባበታለሁ ካለ መልካም ነው፡፡ ውስጡ ግን ማሰቡና መጨነቁ አይቀርም፡፡
ሎሚ፡- አቶ ልደቱ በሕይወትህ ምን የሚፀፅትህ ነገር አለ ለሚለው ጥያቄጠይቄው ነበር፡፡ ሲመልስም “በሕይወቴ ከሚፀፅተኝ ነገር አንዱ ምሁራንን ማመኔ ነው፡፡ ለምሁራን የነበረኝ ግምትና አስተሳሰብ ነው የሚጸጽተኝ” ብሏል፤ አባባሉን እንዴት አዩት?
ዶ/ር ኃይሉ፡- በመጀመሪያ ደረጃ ማንን አመነና ነው፡፡ ምንስ ተጓደለበት ነው የኔ ጥያቄ፡፡ ሣልፈልግ ወደዚህ የማልወደው ነገር ውስጥ እያስገባኸኝ ነው፡፡ የሚፀፅተኝ ሊል አይገባም፤ ምንም የሚፀፅት የተፈጠረበት ነገር የለም፡፡ የእሱን ተወውና በራሴ ግን በምሁራን ዙሪያ ከተባለ “ምሁራን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ንቁ ተሣታፊ አለመሆናቸው ነው የሚያሣዝነኝ፡፡ የማመንና ያለማመን ጉዳይ አይደለም፡፡ አምነናቸው ጉድ አደረጉን፤ አሳልፈው ሰጡን የሚል መንፈስ ያለው
ይመስላል አባባሉ፡፡ በምን ጉዳይ ምንድን ነበር የጠበቀው? ምንስ ቀረበት?
አንድ፣ ኢሳት ፣ ኢህአዴግን እና ግንቦት7ትን የተመለከተ ዘገባ ካቀረበ በሁዋላ አንዳንዶች ዜናውን ሲጠራጠሩት ተመልክቻለሁ፣ ያሽሟጠጡም አልታጡም። መጠራጠርም፣ ማሽሟጠጥም የሰውልጅ ባህሪ በመሆኑ አልገረመኝም። ትንሽ የገረመኝ አንዳንድ “ጋዜጠኞች” መረጃውን ካገኙ በሁዋላ በራሳቸው መንገድ አጣርተው ሀቁን ማውጣት ሲችሉ እነሱም እንደሌላው መልሱን በማንኪያ እንዲቀርብላቸው መፈለጋቸው ነው። ጋዜጠኛ “ጥቆማ” ከተሰጠው ተመራምሮ፣ የምርምር ስራውን ይጽፋል እንጅ እንደ አንባቢ መልሱ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብለት አይጠብቅም፣ ጥያቄ መጠየቅማ ማንም ይጠይቃል፣ ጋዜጠኛን ጋዜጠኛ ወይም ተመራማሪ የሚያደርገው ለጠየቀው ጥያቄ ላይ ታች ብሎ መልስ ማቅረብ ወይም በአሰባሰባቸው መረጃዎች ላይ ተንተርሶ ትንተና መስጠት ሲችል ነው ( በሁለተኛው መስፈርት መሰረት ተመስገን ደሳለኝን እና በእስር ላይ የሚገኘው ውብሸት ታየን አደንቃለሁ)።
ሁለት፣ ዜናውን እንደሰማሁ መጀመሪያ የመጣልኝ ጥያቄ “እና ምን ያስገርማል?” የሚለው እንጅ፣ “ድርድሩ የተጠየቀው መቼና በእነማን በኩል ነው?” የሚለው አልነበረም። የአለም የፖለቲካ ታሪክ በግጭትና በድርድር የተሞላ ነው። “ድርጅቶች ይጋጫሉ፣ ይደራደራሉ፣ ምን ያስገርማል?”፣ በፖለቲካ ትግል” በመቃብሬ ላይ ..” የሚባል ነገር የለም። “ለምን ሰበር ዜና ሆነ ታዲያ?’ እንዳትሉኝ፣ ሰበር ዜና ማለት አስገራሚ የሆነ ዜና ማለት አይደለም ።
ሶስት፣ ቀጥሎ የመጣልኝ ጥያቄ “ኢህአዴግ ከግንቦት7 ጋር መደራደር ለምን ፈለገ?” የሚለው ነው። ይህን ጥያቄ ለመመለስ ” የፖለቲካ ድርጅቶች የእንደራደር ጥያቄ የሚያቀርቡት መቼ ነው?” የሚለውን ማየት ነበረብኝ። የፖለቲካ ድርጅቶች በአብዛኛው ለድርድር የሚቀመጡት ህልውናቸውን ለማቆየት ወይም ተደራድሮ የሚገኝ ጥቅም ሳይደራደሩ ከሚገኝ ጥቅም ( ጉዳት) የተሻለ ሆኖ ሲያገኙት ነው። በዚህ ንድፈሀሳብ ላይ ተመስርቶ ኢህአዴግ እና ግንቦት7 አሁን ያሉበትን ቁመና መፈተሽ ይገባል። ኢህአዴግ ከመለስ በሁዋላ ኢህአዴግ አለመሆኑ ይታወቃል።ሊቀመንበሩ ድርጅቱን ይዞ ለመቀጠል ተቸግሯል፣ (ምናልባትም በቅርቡ ይፋ የሚሆኑ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከፍተኛ የገንዘብ ችግር አጋጥሞታል)፣ የ ህዝቡ ልብ እንደሸፈተ አውቋል፣ ወጣቱ ለውጥ እንደሚፈለግ ተረድቷል፣ ሰራዊቱ የሚተማመንበት ሀይል እስኪያገኝ እንጅ እንደሚከዳው ተገንዝቧል። በአጠቃላይ መጪው ጊዜ ለኢህአዴግ ብሩህ አለመሆኑን ግንባሩ ጠንቅቆ ያውቃል። በዚህ አደጋ ውስጥ ሆኖ ጊዜ ለመግዛትና ድርጅቱን ለማጠናከር የድርድር ጥያቄ ቢያቀርብ አይገርምም።
ግንቦት7 ለኢህዴግ “አጣዳፊ ጠላት” (immediate threat) ሆኗል እያልኩ አይደለም፣ ነገር ግን እምቅ ጠላት ( potential threat) መሆኑን አልጠራጠርም ። አንድ ድርጅት ለሌላው ድርጅት አጣዳፊ ጠላት የሚሆነው ፣ አሁን ባለበት ሁኔታ፣ ከተቃራኒው ድርጅት የበለጠ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የሀይል ሚዛን ሲኖረው ነው። ግንቦት7 ኢህአዴግን ዛሬውኑ ለማስወገድ አይችልም ምክንያቱም ከኢህአዴግ የሚበልጥ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ ሀይል የለውምና ፤ ነገር ግን በጊዜ ሂደት እንደሚያስወግደው መገመት ይቻላል፣ ከመለስ በሁዋላ ያለውን ሁኔታ ብታጠኑ የኢህአዴግ የሀይል ሚዛን ወደ ታች እየወረደ፣ በአንጻራዊ መልኩ የግንቦት 7 የሃይል ሚዛን ደግሞ ወደ ላይ እየወጣ ነው፣ የ ግንቦት7 መሪዎች በዚህ አመት የሀይል ጥቃት እንደሚጀመሩ አስታውቀዋል፣ በዚህ አመት ቀርቶ በሚቀጥሉት 3 አመታት ጥቃት ከፈጸሙ እያደጉ መሆኑን የሚያሳይ ነው ( 4 ፓይለቶች መክዳታቸውንም አንዘንጋ)። የፖለቲካ ሳይንቲስቶች እንደሚሉት ሁለት አይነት ሀይል አለ። አንዱ መቺው ሀይል ( hard power) ሲሆን ሌላው ደግሞ መለስተኛው ሀይል ( soft power) ነው። መቺው ሀይል የሚባለው ወታደራዊው ሀይል ነው። በዚህ በኩል ኢህአዴግ ከግንቦት7 በብዙ እጅ የሚልቅ ጉልበት አለው። ነገር ግን ግንቦት7ትም በዚያው ጎዳና እየተጓዘ መሆኑን መርሳት የለብንም።
መለስተኛ ሀይል (soft power) የሚባለው ደግሞ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያዎችን፣ ጥራት ያለው የሰው ሀይልን ( መሪም ተከታይም)፣ ህዝባዊ ድጋፍ ፣ የካፒታል አቅም ፣ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት የመሳሰሉትን ያካትታል። ግንቦት7 በዚህ በኩል ከፍተኛ ጉልበት መገንባቱን መመስከር ይችላል። ከኢህአዴግ ተመጣጣኝ የሆነ ካፒታል ባይኖረውም፣ ከሌሎች ድርጅቶች የተሻለ ካፒታል( ገንዘብ)እንደሚኖረው ከስራዎቹ መገመት ይቻላል ። የተማሩ ሰዎችን በመያዝ በኩልም፣ ከኢህአዴግ ቢበልጥ እንጅ አያንስም። በፕሮጋንዳውና በህዝብ ድጋፍ በኩልም እንዲሁ። እንዲያውም የግንቦት7 የፕሮፓጋንዳ ማሽኖች ከኢህአዴግ የተሻሉ ለመሆናቸው ብዙ አስረጅ አይጠይቅም፣ የግንቦት7 ራዲዮና ዌብሳይት እስከዛሬ ሳያቋርጥ እየሰራ ነው፣ ጠንካራ የፓልቶክ ደጋፊዎችም አሉት። ኢህአዴግ ራሱ የሚሰራላቸው ፕሮፓጋንዳም ቀላል አይደለም። ኢህአዴግ ቢያንስ በውጭ ያለውን ድጋፉን፣ በተለይም ለጀመራቸው የአባይ እና ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ገንዘብ ለመለመን ሲል ግንቦት7ን ለድርድር ቢጠይቀው አይገርምም። ኢሳት የግንቦት7 ነው ብሎ ስለሚያስብም፣ ኢሳትን እንዲያስቆምለት ልደራደርህ ቢል አሁንም አይገርምም። (በኢሳት ላይ እንኳ ቀልድ የለም፣ መደራደር ከፈለገ ከኢሳት ጋር እንጅ ከግንቦት7 ጋር ሊሆን አይችልም፣ ምክንያቱም ግንቦት7 ስለኢሳት ምንም የሚያገባው ነገር የለምና፣ ከኢሳት ጋር ድርድር ከተጀመረም ለኢሳት የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ዙሪያ እንጅ፣ ከስራው ጋር የተያያዘ እንደማይሆን መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ)
አራት፣ ኢህአዴግ ከግንቦት7 ጋር ብቻ ነው ወይ ድርድር የመረጠው? እኔ ባለኝ መረጃ ኢህአዴግ በእነ ፕ/ር ኤፍሬም ይስሀቅ በኩል ላለፉት 4 ወራት ከእነ አቶ ሌንጮ ለታ ድርጅት ጋር ሲነጋገር ነበር። ይህን ጠንቅቄ አውቃለሁ። ከኦብነግ ጋርም እንዲሁ ተደጋጋሚ የድርድር ጥያቄዎች ቀርበዋል። እነዚህ ድርጅቶች በፓርላማ “አሸባሪ” የተባሉ ናቸው። እና ለግንቦት7 ጥያቄ ቢያቀርብ ምን ይደንቃል? ፖለቲካ እኮ ፊት ለፊት የምትናገርውና በውስጥ የምታደርገው የተለየ ነው። That is politics. በነገራችን ላይ ” አንደኛው የአለም ጦርነት የተጀመረው በድብቅ በሚካሄድ ፖለቲካ የተነሳ ነው” ተባለና ፖለቲካ ግልጽነት እንዲኖረው ተብሎ አዲስ አስተሳሰብ ለረጅም ጊዜ ተራመደ። ፖለቲካ ግን ዛሬም ፊትና ጀርባ እንደያዘ ቀጥሎአል።
አምስት፣ “ጥያቄው በእነማን በኩል ቀረበ?’ የሚለውንም ለራሴ አንስቻለሁ። የድርጅቱ መሪዎች መልሱን ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፣ ነገር ግን የራሴን ግምቶች አስፍሬአለሁ። አንድ፣ በቅርቡ በእነአቦይ ስብሀት የተመራ ቡድን አሜሪካ ከርሞ ሄዷል። ሁለት፣ ፕ/ር ኤፍሬም አሜሪካ ከርመዋል፣ ኦነጎችን ለማስታረቅም ላይ ታች ሲሉ ከርመዋል። ሶስት፣ በቅርቡ የአውሮፓ እና የካረቢያን አገሮች ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፣ ብዙ ዲፐሎማቶችም አዲስ አበባ ነበሩ። አራት፣ ኖርዌይና ሆላንድ ሁሌም ተቃዋሚዎችን ለማቀራረብ ይሰራሉ። ይዋል ይደር እንጅ ትክክለኛውን መልስ እናገኛለን። መልሱ ግን ከጠቀስኳቸው ሰዎች ወይም አገሮች በአንዱ ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ። የእንደራደሩ ጥያቄ ለመቅረቡ ግን መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ። እስከዛው እንደ ጋዜጠኛ መላ ምት በማስቀመጥ ምርምራችን መቀጠሉ ተገቢ ነው።
ስድስት፣ ግንቦት7 ለምን ይህን ድርድር ይፋ ማድረግ ፈለገ? ኢህአዴግ አስቀድሞ በኢቲቪ ” ከግንቦት7 ጋር ሲያደርግ የነበረው ድርድር ከሸፈ” ብሎ መግለጫ ቢሰጥ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስቡት? የግንቦት7 ደጋፊዎች የድርጅቱን መሪዎች በጥሩ አይን የሚያዩዋቸው አይመስለኝም፤ ግንቦት7ትም ውስጥ አለመተማመን ይፈጠርና ድርጅቱን ከሁለት ሊከፍለው ይችል እንደነበር መገመት ይቻላል፣ ዲሞክራሲያዊ ነኝ የሚል ድርጅት ከአባሎቹና ከህዝቡ የሚደብቀው ነገር መኖር የለበትም። ግንቦት7 በመግለጫው “ድርድር መደረግ ካለበት ከሁሉም ድርጅቶች ጋር ነው፣ ሁሉንም ነገር ግልጽ እናደርጋለን የምንደብቀው የለንም” ብሎአል። ትክክል ነው። እውነተኛ ድርድር ሲጀመር ለጊዜው ይፋ የማይወጡ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ፣ ድርድር ተጠየቅሁ ብሎ መግለጫ መስጠቱ ግን የሚገርም አይመስለኝም። ግንቦት7 መረጃውን ከኢህአዴግ ቀድሞ ይፋ ማድረጉ ድርጅቱን ከመከፋፈል ማዳን ብቻ ሳይሆን ንቅናቄው ከኢህአዴግን አንድ እርምጃ ቀድሞ የ ሚያስብ መሆኑን ለማሳየትም ጠቅሞታል።
በአገር ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞች በኢህአዴግ በኩል ያለውን መልስ ይዘውልን እንደሚቀርቡ ተስፋ እናድርግ።
ክንፉ አሰፋ
በሳውዲ የተነሳው የወገን ሰቆቃ ገና አልበረደም። ስቃዩ የበለጠ ሲከፋ እንጂ ሲቀንስ አላየንም። ለውጭ ምንዛሪ ማግኛ ሲባል ልክ እንደ ባርያ ንግድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ በኩል የተላኩት ምስኪን ኢትዮጵያውያን ጉዳይ በገዥው ፓርቲ እንደታሰበው አልሆነም። እንዲያውም ሌሎች መዘዞችን አስከትሎ መጥቷል። ዲያስፖራው እንደገና ተነሳ።
በሳዑዲ ዐረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አስመልክቶ “ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ” ሊቀመንበር አቶ ኦባንግ ሜቶ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር አድሃኖም ገብረየሱስ የጻፉትን ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ልከውልናል።
ለልጅ ተክሌ የተሰጠ ምላሽ
ሥርጉተ ሥላሴ
አረሙ ወያኔ በየትኛውም መስፈርት ኢትዮጵያዊነትን የመቀማት ሞራሉም ሆነ አቅሙም የለውም – በጣም በእርግጠኝነት!
ጤና ይስጥልኝ ሞገደኛው ተክሌ እንደምን ሰነበትክ? ደህና ነህ ወይ? የብዕር አጣጣልህ እንደ አቤ ቶኬቻው ውብ ስለሆነ ለረጅም ጊዜ እያደንኩ አነባለሁ። ጠረባህንም አክሎ። በጠረባህ ዙሪያ አንድ ቀን የምለው ይኖረኛል … ዛሬ ግን ልታገሰው ስላልቻልኩት ማለት ፈለግኩ … በሦስት ነገሮች ዙሪያ … እንዲህም እላለሁ … እኔው …
የማለዳ ወግ፦ የጅዳ ሸረፍያ እስከ ሽሜሲ የተሰማው የወገን ዋይታና እዚህ ያደረሰን መንገድ!
ነቢዩ ሲራክ
ፈታኙን ወቅት ለማለፍ …
የሳውዲ የምህረት አዋጅ አልቆ በሪያድ መንፉሃ ላይ አለምን ያሳዘነ ሰቆቃ ተፈጸመ … ስጋት ነግሶ፣ ኑሮ ከብዶን ጨንቆን ጠቦን ከርመናል! በዚህ ክፉ ቀን ወገን ወገኑን ለመርዳት ደፋ ቀና በማለቱ ረገድ የሃገሬ ልጅ ከጫፍ እስከ ጫፍ በቁጭት ስሜት ሲንቀሳቀስ የፖለቲካው ትኩሳት ወላፈን እያጓተተን አልሰነበትንም አይባልም።
Ethio-telecom, fraud
ህዳር ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚኖሩ ዜጎች በስልክ እየሰጡ ባለው አስተያየት ግንቦት7 ከኢህአዴግ ጋር መነጋገሩን አይደግፉም። አብዛኞቹ የሚሰጡት ምክንያት ደግሞ “ኢህአዴግ ተዳክሟል፣ ኢህአዴግ የሚታመን ድርጅት አይደለም” የሚሉ ናቸው። በዚህ ዙሪያ ኢትዮጵያውያን የሰጡት አስተያየት የሚከተለውን ይመስላል በሌላ በኩል ደግሞ የተወሰኑ ኢትዮጵያውያን የድርድሩ ዜና መልካም ወሬ መሆኑን ለኢሳት በላኩት የኢሜል መልክት አስታውቀዋል። …