የናይጀርያ ገዥዉ ፓርቲ የህዝባዊ ዲሞክራቲክ ፓርቲ በእንጊሊዘኛ አፅህሮቱ PDP አዲስ የፖለቲካ ፈተና ገጥሞታል። የገዥዉ ፓርቲ አባላት የነበሩ ሰባት ሀገረ ገዥዎች ከፓርቲያቸዉ አፈንግጠዉ፤ All Progressives Congress (APC በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ) ከተሰኘዉ ዋና ተቃዋሚ ፓርቲ ጋር የጋራ ፓርቲ መስርተዋል።

ህዳር ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ የሚታየው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው ዜጎች። ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያን በእስር ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቀናቸውን ይጠባባቃሉ። የኢትዮጵያ መንግስት በመቶ ሺ የሚቆጠረውን ስደተኛ ለማስተናገድ የመደበው የሰው ሀይል 40 ብቻ ነው። የሳውድ አረቢያ መንግስት ደግሞ በተዘዋዋሪ መንገድ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ …

ህዳር ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባል እና የኢትዮጵያን የ1997 ምርጫ የታዘቡት ወ/ሮ አና ጎሜዝ ይህን የተናገሩት አዲስ ስታንዳርድ ለተባለ የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ነው። በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ባለው የአውሮፓ፣ አፍሪካና ካረቢያን አገሮች የፓርላማ ጉባኤ ላይ የተገኙት ወ/ሮ አና የአምባገነን ምንጭ የሆነው መለስ ዜናዊ ቢሞትም፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ፖለቲካዊ ለውጥ አለመምጣቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ተለውጣለች …

የሶማልያው ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ሙሐመድ ጠ/ሚንስትር አብዲ ፋራህ ሺርዶን ሥልጣን እንዲለቁ በመጠየቃቸው ገና በሁለት እግሮችዋ መቆም ያልቻለችውን ሀገር ለሌላ ዙር ቀውስ እንዳይዳርጋት አሥጋቷል። የሁለቱ መሪዎች አለመጣጣም ሰበብ ምን እንደሆነ በትክክል

ባለፈው አንድ ዩኒቨርሲቲ ሄጄ አንድ ጓደኛዬ የነገረኝ አሳዛኝ ነገር ነበር፡፡ የአማርኛ መምህር ለመቅጠር የተሰጠው ፈተና ዩ፣ ዪ፣ ዬ እና ዮ ን መጻፍ ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው ግን ከተፈተኑት አምስት የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው መምህራን አንዱ ብቻ አሟልቶ ጽፏቸዋል፡፡ ወደፊት አማርኛን ማንበብና መጻፍ የሚችል ሰው ለማግኘት ሥዕለት ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡ እስኪ ይኼንን ማስታወቂያ ተመልከቱት ‹ይከላከላል› ወይስ ‹ይከሳከሳል› – ተከላካይ ነው ቦክሰኛ?

ከአስተዳዳሪው ጋራ የጥቅም ግንኙነት ያላቸው የቅ/ላሊበላ ደብር ሰበካ ጉባኤ አባላትና የአስተዳደር ሠራተኞች፣ ለመኪና ‹ሽልማቱ› ከግማሽ ሚልዮን ብር በላይ (በአንዳንድ ምንጮች መረጃ እስከ ብር 800,000) ከደብሩ ካዝና ወጪ ማድረጋቸው ተጠቁሟል፡፡ ‹‹መነኩሴ ቢሸለም መስቀል እንጂ መኪና ምን ያደርግለታል?›› የሚሉ የቅ/ላሊበላ ደብር ካህናትና ምእመናን፣ ‹‹አባ ገብረ ኢየሱስ በሕግ መጠየቅ እንጂ ሽልማት አይገባቸውም›› በሚል ኅዳር ፲፮ ቀን ፳፻፮ ከቀትር …

እስካሁን ባሉት አመልካች ሁኔታዎች ከተሄደ ኢትዮጵያ በመጪው አስር ዓመታት ጊዜ ዉስጥ መካከለኛ ገቢ ያላት አገር የመሆን ግባቸው እንደሚሳካ የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ።

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዛሬ አዲስ አበባ ዉስጥ በተከፈተዉ የአፍሪቃ ንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤቶች ስብሰባ ላይ ባደረጉት የመክፈኛ ንግግር ነው አገራቸው በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉ ነዳጅ አምራች ያልሆኑ አገሮች አንዷ መሆኗን የተናገሩት።

“ፖሊሲዎቻችንና ስታራቴጂዎቻችን ብቃትና ጥራታቸዉን አረጋግጠዋል። እናም አሁን ያሉትን አመልካቾች ከተከተልን፥ ኢትዮጵያ በመጪዎቹ አስር ዓመታት ጊዜ ዉስጥ መካከለኛ ገቢ ያላት አገር የመሆን ግባችንን እናሳካለን፤” ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ እምነታቸውን ገልጠዋል። የዛሬውን ጉባኤ ያዘጋጀዉ ከአርባ በላይ አገሮች ብሔራዊ ምክር ቤቶች አባል የሆኑበት የፓን…

ህዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደገለጹት ስትርሀ እየተባሉ በሚጠሩ የማጎሪያ ካምፖች ውስጥ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛሉ። በውሀ እና በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ እርጉዝ ሴቶች፣ ህጻናትና እናቶች አሁንም የድረሱልን ጥሪያቸውን እያሰሙ ነው። በማጎሪያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያዊን ምግብ እና ውሀ ለመግዛት ወጣ ሲሉ እንደሚገደሉ ጓደኞቻቸው የተገደሉባቸው ኢትዮጵያውያን …

ህዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግለሰቡ የተገደለው ባለፈው ሳምንት ሲሆን፣ ገዳዮችም ከመንግስት ጋር ባላቸው ቅራኔ የተነሳ ጫካ የገቡ ሰዎች ናቸው ተብሎአል። ከአካባቢው ነዋሪዎች ባገኘነው መረጃ መሰረት በጅማ ዞን ኪሼ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው በለጣ ጫካ ውስጥ በመደበቅ አልፎ አልፎ ጥቃት የሚሰነዝሩ የአኮረፉ ነዋሪዎች ቻይናዊውን የገደሉት ፎቶ ግራፍ ለማንሳት በሚሞክረበት ወቅት ነው። ቻይናዊው …

ህዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ጅጅጋን በማስመልከት በተላለፉ ዜናዎች ላይ አንዳንድ ማስተካከያዎች እንድናደርግ የከተማዋ ነዋሪዎች ጠይቀውናል። ኢሳት በብሄር ብሄረሰቦች በአል ምክንያት የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ እንደተዘጋ አድርጎ ያስተላለፈው ዜና ስህተት ያለበት ሲሆን የተዘጉት የጅጅጋ ነርሲንግ ማሰልጠኛኮሌጅ እና የጅጅጋ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም እንጅ ዩኒቨርስቲው አለመሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። የአቶ መለስ ዜናዊ ሀውልት እንደፈረሰ ተደርጎ በቀረበው …

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ ዋና አማካሪ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው ተሾሙ፡፡ በዛሬው ዕለት የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው የተሾሙት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ÷ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ከ፲፱፻፺፫ …

ባለፈው መስከረም በኬንያ መዲና በናይሮቢ ፤ የሶማልያው አክራሪ እስላማዊ ድርጅት (አሸባብ)WESGATE በተሰኘው ዐቢይ የገበያ አዳራሽ፣ አደጋ በመጣል ከ 60 በላይ ሲቭሎች መግደሉ የሚታወስ ነው። እ ጎ አ በ 2006 የሶማልያ የሸሪያ ፍርድ ቤቶች ሕብረት

ባለፈዉ ሳምንት ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ የተገደሉበትን 50ኛ ዓመት ዘክራ ዉላለች። እንደ ጎርጎረሳዉያኑ ህዳር 22 ፤ 1963 ዓ,ም ቀትር ላይ በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በጥይት የተገደሉት ፕሬዚደንት ኬኔዲ ሰለባ የሆኑት ስልጣን ላይ ከወጤ ሶስተኛ ዓመታቸ ን ሊይዙ ትንሽ ወራቶች እንደቀራቸዉ መሆኑን ዘገባዎች ያሳያሉ።

በ1997 ኢትዮጵያ ዉስጥ የምርጫ ሒደት የተከታተለዉ የአዉሮጳ ሕብረት የታዛቢዎች ቡድንን የመሩት እና የኢትዮጵያ መንግሥትን አጥብቀዉ የሚተቹት የአዉሮጳ ሕብረት እንደራሴ ወይዘሮ አና ጎሜሽ በትናንቱ ጉባኤ በነበረዉ ክርክር ዋና ተሳታፊ ነበሩ

ባህር ዉስጥ ከመስጠም የተረፉ ሶስት ኢትዮጵያዉን ተገን ጠያቂዎች ከትናንት በስተያ የቤልጂየም ጦር ሠራዊት ላይ ክስ መሠረቱ። ከሁለት ዓመታት በፊት በጀልባ የተጫኑ አፍሪቃዉያን ስደተኞች ወደጣሊያን ሲጓዙ ለአደጋ መጋለጣቸዉን ከተመለከቱ በአካባቢዉ ከነበሩ ኃይሎች ርዳታ ባለማግኘታቸዉ 63ቱ ህይወታቸዉ አልፏል።

ቴዎድሮስ አድሃኖም Tewodros Adhanomኤፍሬም ማዴቦ
የኢትዮጵያ ህዝብና እናስተዳድረዋለን የሚሉት አምባገነን ገዢዎቹ ተስማምተውና አንዱ ሌላውን አክብሮ የኖረበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ የለም። የእስከዛሬው ታሪካችን ምዕራፍ በጥቅሉ ሲታይ ታሪካችን የሚቋጨው ህዝብ ተረገጠ፤ ተጋዘ፤ ገዢዎች ደግሞ ረገጡ፤ ገዙ፤ አሰሩ፤ አጋዙ እየተባለ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አሸናፊ ንጋቱ
በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ መንግስት የዛሬ 22 ዓመት አንግቦት የነበረውን የዲሞክራሲ መፈክር በማየት ዲሞክራሲ የጠማው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ጮቤ በመርገጥ ነበር የተቀበለው። ነገር ግን ይህ መፈክር ድራማ መሆኑ እየዋል እያደረ ነበር እየተጋለጠ የመጣው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም፣ ትርጉም፦ ነጻነት ለሀገሬ

ባለፉት አስርት ዓመታት በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች በአገራቸው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አህጉር በተለየ መልኩ ተንሰራፍቶ እየተፈጸመ ካለው ጭካኔና ርህራሄ የጎደለው አምባገነናዊ ስርዓት ለማምለጥ ሲሉ እግራቸው ወዳመራቸው አገር በመሰደድ ላይ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አበራ ሽፈራው ከጀርመን
በተለይም ባለፉት 22 ዓመታት በሀገራችን ለተከናውኑት አበይት ችግሮች ሁላችንም እጆቻችንን ወደ ህወሓት እየቀሰርን ለችግሮቻችን መፍትሔ መስጠት አቅቶን ይባሱኑ ለከፍተኛ ስቃይና መከራ መዳረጋችንና፤ መፍትሔውን ከህወሓት እየጠበቅን ለችግራችን መባባስ አስተዋጽኦ በማድረጋችን ችግራችን እየተባባሰ ቀጥሏል። በምን መልኩ ነው አስተዋጽኦ አደረግነው?

ሙሉውን አስነብበኝ …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በርካታ ተስፋ የቆረጡ ኢትዮጵያውያን መዲናህ ከተባለው መጠለያቸው  ግንብ እየዘለሉ  ወደ ታይባን ዩኒቨርስቲ ካምፓስ እንደገቡ የአገሪቱ ፖሊስ አስታውቋል። ብርጋዴር ፋህድ ቢን አሚር አል ጋናም እንደገለጹት 15 ኢትዮጵያውያን ወደ ዩኒቨርስቲው ግቢ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ሀይሎች ኢትዮጵያውያኑን በመያዝ ወደ ማጎሪያ ካምፓቸው ልከዋቸዋል። ኢትዮጵያውያኑ በሰዎች፣  በመኪኖች ወይም ህንጻዎች ላይ ጉዳት እንዳላደረሱ …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሶማሌ ክልል 8ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ታከብራለች መባሉን ተከትሎ የክልሉን ዋና መቀመጫ ጅጅጋን  አርቲስቶች እና የመንግስት ባለስልጣናት በየጊዜው እየጎበኙዋት ነው። ለበዓሉ ዝግጅት የተመደበለትን 31 ሚልዩን ብር ከዝግጅቱ በፊት ቀድሞ ያጠናቀቀው የሶማሌ ክልል መንግስትን ለበአሉ ማክበሪያ እና ማድመቂያ በማለት ተጨማሪ 14 ሚሊዮን ብር ጠይቋል። ለበዓሉ ማስተናገጃ የሚሆን ስቴዲየም …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአህጉሪቱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ተንከባካቢ አካል ነው የተባለው ኮሚሽን፣ ኢትዮጵያ ለስኳር ልማት በሚል በታችኛው ኦሞ አካባቢ የሚገኙ ዜጎችን በማፈናቀል እየፈጸመችው ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በፍጥነት እንድታቆም ጠይቆ፣ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እንደሚያደርግም ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በአካባቢው በሚኖሩ ብሄረሰቦች ላይ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ግርፋት እና እስራት መፍጠሩን …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዩጵያ የቴሌቪዥን ድራማ ታሪክ በረዥምነቱ ቀዳሚውን ቦታ በመያዝ የሚታውቀው ሰው ለ ሰው ተከታታይ ድራማ 109 ክፍሎች ያህል ከተላለፈ በኃላ፣ ሰዎች በማህበራዊ ድህረ ገጾች የድራማው ተዋንያን የሆነውን በትወና ስሙ አስናቀ የተባለውን  ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር  በማመሳስል ገጸባህሪውና ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለስልጣናትን በገንዘብ …

ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት መረጃ አገልግሎት ማግኛ ድር (WWW)የተሰኘው ድርጅት መሥራች፣ ብሪታንያዊው ሳይንቲስት፣ ሰር ቲሞቲ በርነርስ ሊ፤ ይኸው በይፋ መረጃ አቅራቢ የሆነው የኢንተርኔት «ድር» ቁጥጥርና ቅድመ ምርመራ እያየለ መምጣቱ ለወደፊቱ

ጥንታዊ ስልጣኔን ለታሪክ ትተን ከድህነት ወለል በታች ከሚፈረጁት የዓለማችን ኣገራት ተርታ ተሰልፋ የምትገኘው ኢትዮጵያ ግን ደግሞ ይህ ነው የማይባል የተፈጥሮ ሀብትም እንዳላት ይታወቃል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከዓለም እጅግ ደሐ የሚባሉ ሐገራትን የምጣኔ ሐብት ይዞታን የገመገመበትን ዘገባ ባለፈዉ ሳምንት ይፋ አድርጓል።ዓለም አቀፉ ድርጅት እጅግ ደሐ ብሎ ከፈረጃቸዉ 49ኝ ሐገራት ዉስጥ 34ቱ የአፍሪቃ ሐገራት ናቸዉ።

የኢትዮጵያ መንግስት ከስዑድ አረቢያ ከሃምሳ ሺህ የሚበልጡ ዜጎች ወደሀገር ቤት መመለሳቸዉን አስታወቀ። የመንግስት ቃል አቀባይ ለዶቼ ቬለ እንደገለፁት ለዚሁ ተግባር በጀት ተመድቦ በሚካሄደዉ ዘመቻም በየዕለቱ ወደስምንት ሺህ ገደማ የሚሆኑት እየገቡ ነዉ።

የለውጡ ቀንደኛ ተገዳዳሪዎች፣ ‹‹ጠላቶች ነበርን፤ ዛሬ የሰማነውና ያየነው ጥናት ግን መልካም ኾኖ አግኝተነዋል፤›› ሲሉ ራሳቸውን ሒስ አድርገዋል፤ ‹‹ቤተ ክርስቲያኒቱ የተወለደችው ዛሬ ነው፤›› ሲሉም የመዋቅርና አሠራር መመሪያ ጥናቱን አድንቀዋል፤ ጥናታዊ ውይይቱ በላቀ የለውጥ መነሣሣት ቀጥሏል፤ ከፍተኛ አመራሩ የተሳተፈበት የቀዳማይ ዙር ጥናታዊ ውይይት መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡

እሥራኤልን ዐርባ ዓመት በበረሃ የመራ፣ ፈርዖንን ድል የነሣ፣ የኤርትራ ባሕርንም ለሁለት እንደ ድንጋይ የከፈለ ሰው ነው ሙሴ፡፡ እርሱን በተመለከተ አያሌ መጻሕፍትን ጽፈዋል፣ ፊልሞችን ደርሰዋል፣ ብዙዎችም በእርሱ ስም ተጠርተዋል፡፡ ሕዝብን ከባርነት የማውጣት፣ ለሕዝብ ብሎ የመከራከር፣ ለሕዝብ ብሎ ራስን የመሠዋት፣ ሕዝብን ከራሱ በፊት የማስቀደም፣ ሕዝብን በትዕግሥትና በጥበብ የመምራት፣ ለሕዝብ ብሎ ተከራክሮ ድል የማድረግ ተምሳሌት ነው – ሙሴ፡፡
ሙሴ ከወገኖቹ ጋር የኖረው ከተወለደ እስከ ሦስት ወር እድሜው ብቻ ነው፡፡ ያ ጊዜም ቢሆን ወገኖቹ በግብጻውያን እጅ ከባርነት በከፋ ስቃይ ውስጥ ገብተው የሚንገበገቡበት ጊዜ ነው፡፡ እንኳን ሌላውን ዓይነት ነጻነት ቀርቶ ልጅ ወልዶ የማሳደግ መብት እንኳን አልነበራቸውም፡፡ በተለይም ልጁ ወንድ ከሆነ፡፡ በምድርም ላይ እነርሱን ሊመለከት፣ ሊታደግና ሊራዳ የሚችል አንዳችም ኃይል አልነበረም፡፡ ዓለም እንደ ወስከንቢያ በላያቸው ላይ ተደፍታባቸው ነበር፡፡

ሙሴ ለዐርባ ዓመታት ያህል የኖረው በፈርዖን ቤተ መንግሥት ውስጥ የፈርዖን ልጅ ተብሎ፣ ግብጻዊነቱ እየተነገረው ነው፡፡ የተማረው የግብጽን ጥበብ፣ የበላው የግብጽን ምግብ፣ የሚያውቀው የግብጽን ቋንቋ፣ የኖረው ከግብጻውያን መኳንንትና መሳፍንት ጋር፣ የሚያየው የግብጻውያንን አማልክት፣ የተወዳጀው ከግብጻውያን ጠንቋዮችና አስማተኞች ጋር ነበር፡፡

ሙሴ የኖረበት የኑሮ ደረጃ ወገኖቹ ከነበሩበት የኑሮ ደረጃ እጅግ ከፍ ያለ ነበር፡፡ እርሱ በመኳንንት ወግ፣ በቤተ መንግሥት፣ ችግር የሚባል ነገር ሳይነካው፣ ግፍ የሚባል ነገር ሳይደርስበት፣ መብቱ በሚገባ ተጠብቆ፣ ከቅንጦትና ከድሎት አንዳች ሳይጎድልበት፣ የፈርዖን የልጅ ልጅ እየተባለ የኖረ ሰው ነበር፡፡ በተቃራኒው ወገኖቹ ደግሞ ሰው ሊደርስበት የሚችለውን የመጨረሻ መከራ እየተቀበሉ፤ ካሉት በታች ከሞቱት በላይ ሆነው ነበር የሚኖሩት፡፡ ህልውናቸው በሌሎች ፈቃድ እየተወሰነ፣ ፈንግል እንደያዘው ዶሮ ሞታቸው የሰዓታት ጉዳይ እየሆነ፣ መኖር ራሱ ቅጣት ሆኖባቸው ነበር የሚንገፈገፉት፡፡

ሙሴ እንዲህ በምቾትና በቅንጦት፣ ችግርን በጆሮው እንኳን ሳይሰማት አድጎ፣ የቤተ መንግሥቱን ቅምጥል አጣጥሞ፣ በፈርዖን ዕቅፍ ተቀምጦ – በዐርባ ዓመቱ ግን የወገኖቹ ነገር ያንገበግበው፣ ግፋቸው ይሰማው፣ መከራቸው ያመው፣ ስቃያቸው ያቃዠው፣ ሕመማቸው ያንቀጠቅጠው፣ ሞታቸው ዕረፍት ይነሣው ጀመር፡፡ እርሱ በቤተ መንግሥት ቢቀመጥም ልቡ ግን ከቤተ መንግሥቱ ወጥቶ ግፍ ከሚደርስባቸው ወገኖቹ ጋር ግፍ ይቀበል ጀመር፤ እርሱ ከፈርዖን ማዕድ ቢሰለፍም፣ ልቡ ግን ከወገኖቹ ጋር ይራብ ጀመር፡፡ እርሱ በሐር ልብስ ቢሞቀውም፣ ኅሊናው ግን ከወገኖቹ ጋር ተራቁቶ ይበርደው ነበር፤ እርሱ በሥልጣን ላይ ቢቀመጥም፤ ኅሊናው ግን ከወገኖቹ ጋር ለባርነት ተላልፎ ተሰጥቶ ይገረፍና ይታሠር ነበር፡፡ እርሱ ንጉሣዊ ሕይወትን ቢያጣጥምም፣ ልቡ ግን ከወገኖቹ ጋር ይሞት ነበር፡፡

ለዚህም ነበር አንድ ቀን ወደ ወገኖቹ ሲወጣ አጋዥ አልባ መሆናቸውን ያየ፣ ለግፍ ተላልፈው የተሰጡ መሆናቸውን ያጠና፣ የእነርሱ ሕይወት እንደ ጢንዚዛ ሕይወት ባለቤት የለውም ብሎ ያሰበ ግብጻዊ አንዱን ዕብራዊ ሲመታው ያየው፡፡ ለተመታው ዕብራዊ እርሱ አመመው፡፡ እርሱ የዚህ ግፍ የሚፈጸምበት ማኅበረሰብ አካል መሆኑን አመነ፡፡ ስለዚህም ታዳጊ ለሌለው ታዳጊ ለመሆን ወሰነና በራሱ ላይ ሞት ፈርዶ ያንን ግብጻዊ መታው፡፡ ልቡ ዐርባ ዓመት ከኖረበት ቤተ መንግሥት ሸፍቶ ሦስት ወር ወደኖረበት የእሥራኤላውያን የድህነት መንደር ገባ፡፡

እንዴት? ነው ጥያቄው፡፡ እንዴት?

ሙሴን ማን ነው ያስሸፈተው? ማንነቱን ሳይረሳ ዐርባ ዓመት በፈርዖን ቤተ መንግሥት ያኖረው ማነው? ከድሎቱ ይልቅ የወገኖቹን ስቃይ እንዲመርጥ ያደረገው ማነው? ሰዎች ለአንድ ዓመትና ለሁለት ዓመት ከሀገርና ከወገን ርቀው ባህላቸውንና ቋንቋቸውን ይረሳሉ፣ ማንነታቸውንም ይጥላሉ፡፡ እርሱ ግን ዐርባ ዓመት በፈርዖን ቤተ መንግሥት ሲኖር ለምን ማንነቱን ጠብቆ ኖረ? አንዳንድ ሰዎች ምቾትና ድሎትን ካገኙ፣ ከከበሩና ከተሾሙ ሀገራቸውን፣ ሕዝባቸውንና ወገናቸውን አሳልፈው ለመስጠት ዝግጁ ናቸው፡፡ ሙሴ ግን እምቢ አለ፡፡ እነርሱ ከበሉ ሕዝባቸው የበላ፣ እነርሱ ሲሾሙ ሕዝባቸው የተሾመ፣ እነርሱ ሲያገኙ ሕዝባቸው ያገኘ የሚመስላቸው ባለ ሥልጣናት ብዙ ናቸው፡፡ ሙሴ ግን ከወገኑ ተለይቶ ያገኘው ክብርና ምቾት፣ ሥልጣንና ሀብት ቆረቆረው እንጂ አልተስማማውም፤ ከእርሱ ድሎት ይልቅ የወገኑን መከራ መረጠ፡፡

መንግሥቱ ለማ፡-

የተለመደ ነው የመጣ ከጥንት

ከተጠቂው መራቅ አጥቂን መጠጋት

እንዳሉት የሀብታም፣ የባለ ሥልጣን፣ የታዋቂ ሰው፣ የባለ ጊዜ፣ የከበረ ወገን፣ የሚፈራና የሚከበር ሕዝብ ወገን ነኝ፣ ዘመድ ነኝ፣ አባል ነኝ ማለት ከጥንትም የነበረ ነው፡፡ የአጥቂው ወገን ሆኖ ከተጠቂው ጋር መቆም፣ የጨቋኝ ወገን ሆኖ ከተጨቋኝ ወገን መቆም፣ የክቡራን ወገን ሆኖ ከተዋረዱ ጋር መሰለፍ፣ የገፊዎች ዘመድ ሆኖ ከተገፊዎች ጋር መወገን፣ የሀብታሞች አካል ሆኖ ከድኆች ጋር መሰለፍ፤ የሹመኞች ቤት ሆኖ ለተራው ሕዝብ ዘብ መቆም ግን ብዙም የማይገኝ እንደ አልማዝ ብርቅ የሆነ ነገር ነው፡፡ ታድያ ሙሴ ይህንን ከየት አገኘው?

የሙሴ እናት ሙሴን በቤቷ ለመደበቅ የቻለችው ለሦስት ወራት ብቻ ነው፡፡ በዚያ ዘመን ሲወለድ ወንድ መሆኑ የታወቀ ዕብራዊ ሁሉ እንዲገደል በፈርዖን ዐዋጅ ወጥቶ ነበርና፡፡ የጨነቃት እናት መላ አታጣምና ዓባይ ወንዝ ወስዳ በሳጥን አድርጋ ጣለችው፡፡ የጣለችበት ቦታ የፈርዖን ሴት ልጅ ገላዋን የምትታጠብበት ቦታ ነበርና የፈርዖን ልጅ ሳጥኑን አየችው፡፡ ስትከፍተው የሚያምር ወንዝ ልጅ አገኘች፡፡ አምላክ የሰጠኝ ነው ብላ ወሰደችው፡፡ የሙሴ እናት ብልሃትና ጀግንነት ከዚህ ይጀምራል፡፡ እርሷ ባትኖር ኖሮ ሙሴ ከእነዚያ ሁሉ ሟች ሕጻናት ተለይቶ ባልተረፈ – በኋላም ታሪክ ባልሠራ ነበር፡፡

እናቱ ሙሴን ዓባይ ወንዝ ላይ ሰትጥለው እኅቱ መጨረሻውን እንድታይ ልካት ነበር፡፡ የፈርዖን ልጅ ሙሴን ከባሕር አውጥታ(‹ሙሴ› ማለት ከባሕር የወጣ ማለት ነው) ሞግዚት ስትፈልግ የሙሴ እኅት እናቱን ሞግዚት አድርጋ አመጣችላት፡፡ እናቱም ሞግዚት ሆና ሙሴን አሳደገችው፡፡ በፈርኦን ቤተ መንግሥት ውስጥ በእናቱ ሞግዚትነት ነበር ያደገው፡፡ ሁለተኛው ብልሃቷ ይሄ ነው፡፡ ሙሴ ሲያድግ እናቱ እውነቱን እየነገረችው ነው ያደገው፡፡ ‹‹አንተ በፈርዖን ቤተ መንግሥት ብትኖርም ግብጻዊ ግን አይደለህም፤ አንተ በምቾት ብትኖርም፣ የሚሰቃዩት የእሥራኤላውያን ወገን ነህ፤ አንተ የግብጽን ቋንቋ ብታጠናም ቋንቋህ ግን ዕብራይስጥ ነው፡፡ እዚህ ያገኘኸውን ልምድና ዕውቀት፣ሥልጣንና ክብር፣ ከሞት የመትረፍ ዕድል ወገኖችህን ነጻ ለማውጣት ተጠቀምበት፡፡ ይህ የምታየው ሕዝብ እንዲህ አልነበረም፡፡ ታላቅ ሕዝብ ነበር፣ ታላቅ ሕዝብም ነው፡፡ የአሁኑን መደኽየት፣ የአሁኑን መዋረድ፣ የአሁኑን መገፋት፣ የአሁኑን መጨቆን አትይ፡፡ ነገ ታሪክ ይለወጣል፡፡ አንተ ዛሬ ይህችን ክብርና ሥልጣን፣ ምቾትና ድሎት አገኘሁ ብለህ ከወገንህ ብትርቅ ታሪክ የተለወጠ ዕለት አንተም ስትረገም፣ ስትዋረድና ስትወቀስ ትኖራለህ፡፡ አንት ባታየው ዐጽምህ ይዋረዳል፡፡ ዛሬ ግን ከተገፉትና ከተዋረዱት ወገን ሆነህ ታሪክ ሲለውጥ አብረህ ብትሠራ ስምህ በወርቅ ቀለም ይጻፋል› – እያለች አስተማረችው፡፡

ሙሴ የእናቱ ውጤት ነው፡፡ ሰውነቱን ፈርዖን ሲያሳድገው ልቡን እናቱ ናት ያሳደገችው፤ ምግቡን ፈርዖን ሲሰጠው ጥበቡን እናቱ ናት የሰጠችው፡፡ አካን ቤተ መንግሥቱ ሲቀርጸው የሀገርና የወገን ፍቅር፣ ጽናትንና ብርታትን፣ ለወገን ሲሉ መሥዋዕት መሆንን የተማረው ከእናቱ ነው፡፡ የጥንቱን ታሪክ እየነገረች ልቡ በወገኑ ፍቅር እንዲቃጠል ያደረገችው እናቱ ናት፡፡ ያንን ታሪክ የመመለስ፣ ይህንን ሕዝብም ታላቅ የማድረግ ድርሻ ያንተ ነው ያለችው እናቱ ናት፡፡ ሙሴን ነጻ አውጭ እንዲሆን አድርጋ የሠራችው እናቱ ናት፡፡ በሙሴ ውስጥ ያለችው፣ ከፈርዖን ጋር የተከራከረችው፣ ቤተ መንግሥቱን ጥሎ ለወገኑ ሲል በረሃ እንዲንከራተት ያደረገችው፣ ባሕር እንዲክፍል ያበቃችው፣ የሕዝቡን ስድብ፣ ማጉረምረም፣ ሐሜትና ዐመጽ ችሎ ሕዝቡን እንዲመራ ያደረገችው እናቱ ናት፡፡ ‹ሕዝቤ ከሚጠፋ እኔን ከሕይወት መጽሐፍ ደምስሰኝ› ያሰኘችው እናቱ ነች፡፡

እንዲህ ያለች እናት በሌለችበት፣ እንዲህ ያለ ሙሴ መፈለግ ጉም መዝገን ይሆናል፡፡ እኛ የምንለፋው ሙሴን ለማግኘት ነው፡፡ የሚበጀን ግን ጀግናዋን የሙሴን እናት ማግኘት ነው፡፡

የሙሴ እናት የት ነው ያለሽው?

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

እሁድ ኖቨምበር 24 ቀን 2013 (እ.ኤ.አ.) በፍሎሪዳ ስቴትስ በምትገኘው ታምፓ ቤይ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባላት በሳዑዲ ዐረቢያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ኢሰብዓዊ በደል ከልብ እንዳስቆጣቸው ገልጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …