ህዳር ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጅጅጋ በማንኛውም ሰአት ዜጎች ቤታቸው በጸጥታ ሀይሎች ይፈታሻል። የጸጥታ ሀይሎችም ከሞባይል ስልክ ጀምሮ እስከ ላፕቶፕ እንዲሁም ገንዘብ ይወስዳሉ። የቀበሌ መታወቂያዎችን ሳይዙ ከሄዱ ደግሞ ተጠርጥረው ይያዛሉ። የከተማዋ ነዋሪዎች እንደሚሉት ጅጅጋ ለኢትዮጵያውያን ከሳውድ አረቢያ በላይ የስቃይ መሬት ሆናለች ። አንድንድ ምንጮች እንደሚሉት ችግሩን የተወሳሰበ ያደረገው አልሸባብ  በጅጅጋው ፕሬዝዳንት የግል ሞባይል …

ህዳር ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ቅዳሜ በከንባታ ጠንባሮ ዞን በዱራሜ ከተማ ገበያ ላይ በተነሳው ተቃውሞ አንድ ታዳጊ ሲገደል ሁለት ፖሊሶች ደግሞ ቆስለዋል። በርካታ ገበያተኞችም ጉዳት ደርሶባቸዋል። ግጭቱ የደረሰው የከተማው ግብር ሰብሳቢዎች አነስተኛ ነጋዴዎች ቡና መሸጥ እንዲያቆሙ ማስገደዳቸውን ተከትሎ ነው። አርሶአደሮች የተወሰኑ ኪሎ ቡናዎችን ወደ ገበያ በመውሰድ  የመሸጥ የዘመናት ልማድ ያላቸው ሲሆን፣ የከተማው …

ቅዱስ ዮሃንስ

ትምህርት ዜጎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ በመቅረጽ ለራሳቸው፣ ለማህበረሰባቸውና ለሀገራቸው ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ የሚያግዝ የእውቀት ማሸጋገርያ ስልት ነው። ዛሬ በስልጣኔ የገሰገሱ የአለም ሀገራት የዕድገታቸው ዋነኛ መነሻ ትምህርት ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ይሄይስ አእምሮ

ከጥቂት ሣምንታት ወዲህ በተለይ የኢትዮጵያን የወያኔ መንግሥት በሚቃወሙ የሚዲያ ማዕከላት ዘንድ ዋና መነጋገሪያ ሆኖ የሚገኘው በሳዑዲ የኢትዮጵያውያን መንገላታትና መሰቃየት እንዲሁም ከኢሰብዓዊነትም በወረደ ሁኔታ በግፍ መጨፍጨፍ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ገቢዬን ከሌቦች ጋር እየተጋራሁ ነው ሲል ያማረረው ኢትዮ-ቴሌኮም በተለይ ከውጭ ሃገር ወደ ኢትዮጵያ የሚደወሉት ስልኮች በሕገ ወጦች በኩል የሚያልፉበት ሁኔታ መኖሩን አስታውቋል።

ከውጭ ሀገር በሚደወሉ ስልኮች ላይ የጥራት ችግር የሚያጋጥመውም በዚሁ የተነሣ መሆኑን የኢትዮ-ቴሌኮም የኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽንስ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዱራሂም አህመድ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ አብራርተዋል።

አቶ አብዱራሂምን ያነጋገራቸው እስክንድር ፍሬው ያጠናቀረውን ዘገባ የያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ኤችአይቪ ኤድስን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገቧን በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሣደር ፓትሪሽያ ሃስላክ ገለፁ፡፡

ምናልባትም ሃገሪቱ ከኤድስ ነፃ ትውልድ በመፍጠር ጎዳና ላይ እንደምትገኝ ጠቁመዋል፡፡

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ለኤድስ አጣዳፊ ድጋፍ መርኃግብር – ፔፕፋር አሥረኛ ዓመትም አዲስ አበባ ላይ በአሜሪካ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተከብሯል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በዚሁ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያን መንግሥት ወክለው የተገኙት የኤችአይቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ፅ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ፈይሣ የተገኘው ውጤት ሊቀለበስ እንደማይችል ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

የመካከለኛው ምስራቅሀገሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ በሙስና እየተዘፈቁ መምጣታቸውን ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሺናል የተባለ ኣንድ የጥናት ተቐም ኣስታወቀ። መቀመጫውን በጀርመን ሀገር ያደረገው ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሺናል ዛሬ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርቱ በተለይ

የዓለም የጤና ድርጅት ከጎርጎሪዮሳዊዉ 2011ዓ,ም አንስቶ የዓለም የኤድስ ቀን ሲታሰብ፤ ማንም በቫይረሱ የማይያዝባት ዓለምን የመፍጠር መርህ ነዉ ያስቀደመዉ። ዘንድሮም እንዲሁ ዕለቱ ሲታሰብ በተለይ ታዳጊ ወጣቶች ለHIV ቫይረስ የማይጋለጡበት መንገድ ተጠናክሮ ትኩረት እንዲደረግበት የሚለዉ አፅንኦት ተሰጥቶታል።

ከሳሽ እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በሠፈራ መርሐ-ግብሩ በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማፈናቀል፥ ማሰደዱን የብሪታንያ መንግሥት እያወቀ ለኢትዮጵያ መንግሥት በተለይም ለፀጥታ አስከባሪዎች ማሰልጠኛ ርዳታ መስጠቱ ለተፈፀመዉ በደል አባሪ ተባባሪ መሆኑን አመልካች ነዉ።

http://www.goolgule.com/we-shall-arise-again/

ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር፡፡ መቸም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር፡፡ ህጉ የሚለው ግን ማስፈቀድ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡ በተቃራኒው መንግስት በተለያዩ ጉዳዮች ሳቢያ በእለቱ ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ከለላ መስጠት የማይችልበት ሁኔታ ከገጠመው ሰልፉን ለጠራው አካል ችግሩን ገልጾ ቀኑ እንዲተላለፍለት ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም ይህን መሰል ጥያቄ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ለፓርቲያችን ባለመቅረቡ በሙሉ ልብ ቅድመ-ዝግጅት ማድረጉን ተያያዝን፡፡ ሁሌም ቢሆን መንግስት ሰበብ ፈልጎ ሊወነጅለንና ከመስመር ሊያስወጣን እንደሚፈልግ በሚገባ እናውቃለንና በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ሳይቀር ጥንቃቄ እናደርጋለን፡፡ ለሚመለከተው መስሪያ ቤት ባሳወቅን በአስራ ሁለት ሰአታት ውስጥ ምላሽ ስላልመጣ ሙሉ በሙሉ ህጋዊነታችንን አረጋግጠናል ማለት ነው፣ እነሱ ደግሞ ጠብ-መንጃ በእጃቸው አለና የፈለጉትን ሁሉ ማድረግ ይችላል፡፡

አቶ ሽመልስ ከማል ለሚዲያወች የሰጡትን ፍጹም ከእውነት የራቀ ውንጀላና ሰበብ አዳምጨዋለው፡፡ “ሰላማዊ ሰልፉን ያገድንበት ምክንያት ጸረ-አረብ መፈክሮች ስለነበሩ ነው” ብለዋል፡፡ መጀመሪያ ደረጃ ሰልፉ ገና ከግቢው ፈቅ ሳይል ነው ያፈኑት፣ ሆኖም የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም አንድ በአንድ እየሆንን ወደ ሰላማዊ ሰልፉ መዳረሻ ለመሄድ ስንሞክር የተወሰኑ አመራሮችን አራት ኪሎ አካባቢ ያዙን፣ እነሱ ቀድሞውኑ ሰልፉ እንዳይካሄድ ስለወሰኑ ነው እንጅ ትንሽ እንኳ ተንቀሳቅሶ የሰልፉን ባህሪ ለመገምገም ምንም እድል አልሰጡንም፡፡

ለምሳሌ ሰልፉን እንደምናደርግ ይፋ ባደረግን ማግስት ከራዲዮ ፋና ተደውሎ አንዳንድ ጥያቄዎች ተጠይቄ ነበር፡፡ በቃለ-መጠይቁ ሰላማዊ ሰልፉ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰውን በደል በመቃወም እንደምናደርግ ተናግረናል፡፡ ጋዜጠኛው ለሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች መልዕክት ካለ ብሎ በጠየቀኝ ወቅት የሳውዲ አረቢያ ሰንደቅ አላማ ላይ ያለው ምልክትና ጽሁፍ ሀይማኖትን የሚመለከት በመሆኑ ዜጎች በስሜታዊነት ባንዲራ እንዳያቃጥሉ፣ እነሱ ቢያዋርዱንም እኛ ግን ክብር ያለን ዜጎች ስለሆንን ተቃውሟችንን ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ማካሄድ እንዳለብን ተናግሬ ነበር፡፡ ከሰላማዊ ሰልፉ በፊት በዚህና በተለያየ መንገድ በማያሻማ ሁኔታ መልዕክት ባስተላልፍም እነሱ ግን ይህን በመቁረጥ አላስተላለፉትም፡፡ እነዚህና ሌሎች ምክንያቶች ሲደመሩ የአቶ ሽመልስ ከማል ንግግር ነጭ ውሸት መሆኑን ያስገነዝባል፡፡

ሁለተኛ የአንድ ሀገር መንግስት ዜጎቹ እየተደፈሩ፣ በማጎሪያ ካምፕ በረሀብና በውሃ ጥም፣ ሌላው ቢቀር መጸዳጃ ቤት እንኳ ተከልክለው ፍጹም ከሰውነት ክብራቸው ወርደው እየተበደሉ፣ እየተገደሉ ባለበት ወቅት ገና ለገና ተቃዋሚ ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ላይ በሚንጸባረቅ ጥላቻና ተቃውሞ የዲፕሎማሲ ግንኙነቴ ይበላሽብኛል ብለን መናገር እንችላለን? ሌላው ይቅር አንድ ክፉና ደጉን የለየ ሰው የሚያስበው ጤነኛ ሃሳብ ነው ማለትስ ይቻላል?

ከእገዳው ባሻገር የሚደንቀው ነገር ደግሞ በፓርቲያችን አመራሮችና አባላት ላይ የተደረገው ድብደባ ነው፣ የሆነ ማስተላለፍ የፈለጉት ነገር ያለ ይመስላል፡፡ የጭካኔያቸውን መጠን እንድናውቅ የሚደበድቡት አቅመ-ደካሞችን፣ ሽማግሌዎችንና ሴቶችን እየመረጡ በፍጹም አረመኔነት ነበር፡፡ ይህን ተግባራቸውን ስመለከት የደረሱበትን የዝቅጠት ደረጃ መታዘብ ችያለው፡፡ ከፖለቲካ ልዩነትም፣ ከአምባገነንነትም በላይ ሰዎቹ እንደታመሙ ነው ለመረዳት የቻልኩት፣ስር የሰደደ የቁስ ሰቀቀንና የስልጣን ጥም የተጣባቸው፣ ለዚያ ሲሉም የትኛውንም አይነት ውርደት ለመቀበል የቆረጡና የሞራል ልዕልናቸውን ሙሉ በሙሉ ያጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ስነ-ልቦናቸው ክፉኛ ተቃውሷል እንጂ ሀገር እመራለው የሚል ቡድን እንዲህ ያለ ተግባር ይፈጽማል ለማለት እቸገራለው፡፡ በአባላቶቻችን ላይ ክፍኛ ድብደባ ተፈጽሟል፣ እስከዛሬም እግሮቻቸው መራመድ የማያስችላቸው፣ የሚያነክሱ ሰዎች አሉ፡፡ እውነት ለመናገር ይሄ እብደት ነው፡፡ አንዲት እራሷን መከላከል የማትችል ሴትን ለሶስት መደብደብን ከዚህ በተሻለ ልገልጸው አልችልም፡፡

አንድ ማስገንዘብ የምፈልገው ነገር ለኛ ዋናው ጉዳይ የዜጎቹ ህጋዊነት ወይም ህጋዊ ያለመሆን ጉዳይ አይደለም፡፡ በምንም አይነት መንገድ ሴቶች እየተደፈሩ፣ ወንዶች በየስርቻው እንደ ውሻ ተቀጥቅጠው እየተገደሉ እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች ታጉረው ይህን ሁሉ መከራ መቀበላቸውን ልንታገሰው፣ ወይም ከህጋዊነት አንጻር እየተራቀቅን ልንመለከተው አንችልም፣ ስለ ህግም ከተወራ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ጭፍጨፋው ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ባላቸው ላይ ጭምር ሲፈጸም እንደነበር አምኗል፡፡

ባለንበት የግሎባላይዜሽን ዘመን የአንዱ ሀገር ዜጋ ካለ ሀገሩ መገኘት አገር ይያዝ የሚያስብል አይደለም፡፡ መውጣት ካለባቸው ጊዜ በመስጠት፣ ከመንግስታቸው ጋር በመነጋገር በዘዴ ነገሩን መከዎን እየተቻለ አንድ ሀገርና መንግስት በሰዎች ላይ እንዲህ የጭካኔ ጥግ የሆነን አቋም ይዘው መንቀሳቀሳቸው ፍጹም ኢ-ሰብአዊነት ነው፡፡
ለኢትዮጵያውያን እንዲህ ያለ አስከፊ ጊዜ የለም፣ እውነቱን ለመናገር ለአገዛዙ ሰዎች የነበረኝ ጭላንጭል ተስፋም አፈር ተደፍቶባታል፣ እንዲህ ግልጽ የሆነ ጭፍጨፋ እየደረሰብን እንኳ በድፍረት ለመናገር አልፈለጉም፡፡ ስለ ኢትዮጵያውያን መገደል ለማውራት ሲፈልጉ ሌላ ሀገር ይጠቅሱና እነሱም እኮ እየተገደሉ ነው ይላሉ፣ ወገን ከምንለው የማህበረሰባችን አካል ይሄን መስማቱ ከጥቃቱ ይበልጥ ያማል፡፡

ለምሳሌ ኢቲቪ ስለ ጉዳዩ ሲያወራ ህገ ወጥ ሊባል የሚችል ድርጊት ተፈጽሟል በማለት ነው፡፡ ተመልከቱ! እንዴት ያለ ባዕድነት ነው? ኢትዮጵያውያን በድህነትም ውስጥ እንኳ ለክብራችን የመሞት ባህሪ አለን፣ ይሄ ከቀደሙት አንጡራ ኢትዮጵያውያን የወረስነውና ዛሬም ያለን ሀብታችን ነው፡፡

ትናንት ፍየል ጠባቂ የነበረ በረኸኛ ይህን ክብራችንን ገፍፎ እንደውሻ ቀጥቅጦ ስርቻ ሲጥለን ያልተቆጣ መንግስት ኢትዮጵያዊ ነው? ከዜጎቹ የወጣና ለህዝቡ የቆመ እውነተኛ መንግስት ከዚህ የበለጠ የሚቆጣበት ጉዳይ ከወዴት ይመጣል? እውነተኛ መንግስት ቢሆን ኖሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሳውዲ ካምፓኒዎችን በሰአታት ውስጥ ማባረር፣ ኤምባሲውን ዘግቶ አምባሳደሩን ማሰናበትን የመሳሰሉ ውሳኔዎችን ያሳልፉ ነበር፡፡ የሆነው ግን በተቃራኒው ነው፣ የዲፕሎማሲ ግንኙነቴ ሊበላሽ ይችላል ብሎ እኛ ድምጻችን እንዳናሰማ ደበደበን፣ አፈነን፡፡ በግልጽ እንደሚታየው የጥቅም ትስስሩ ነው አፋቸውን ያዘጋቸው፣ ይህች ጥቅማቸው እንዳትቋረጥ በዜጎች ህይዎት መደራደርን መርጠዋል፡፡

ስነ ልቦናቸው የተቃወሰ በመሆኑና ተራ ስስታሞች በመሆናቸው እንጂ ኢንቨስትመንትም ሆነ ዲፕሎማሲ ግብአትነታቸው ለሰው ልጅ ነው፣ እንደ አህያ ሲያፈጋ ከርሞ ሬሳቸውን ለላከ መንግስት እንዴት ተመጣጣኝ ምላሽ ለመመለስ ይገዳል?እንዴት እንደ ኢትዮጵያ ያለች ታሪካዊትና ለአፍሪካ የነጻነትና የኩራት ተምሳሌት የሆነች ሀገርን እየመሩ እንዴት ትናንት የነዳጅ ዘይት ባቆማቸው እረኞች ስትዋረድ ዝም ይላሉ?!::

እንዴት!

በዜጎች ህይወት የተደራደረው አገዛዝ ማለፉ አይቀርም፣ ለዚህ ጥርጥር የለኝም፡፡ ታሪክ ለመጥቀስ ብዙ ርቀት መሄድ አያስፈልግኝም፡፡ የቅርብ የሰሜን አፍሪካ አምባገነኖች የከፋ ፍጻሜ አለና፡፡ ኢትዮጵያውያን ፍቅርም ጸብም እናውቃለን፣ ሳውዲዎችም የፈጸሙትን ግፍ ማወራረዳቸው አይቀርም፡፡ በዚህ ክፉ ጊዜ ስለሰብአዊ መብት ቆመናል የሚሉ አለም አቀፍ ተቋማት ዝምታን መምረጣቸው እውነተኝነታቸውን ለመመርመር ጥሩ እድል ይሰጠናል፡፡

መንግስት ቢኖረን ኖሮ ይሄ ሁሉ ውርደት ይፈጸምብን ነበር ብየ አላስብም፡፡ በዚህ ሰአት ርዕሰ-መንግስት ብሆን ኖሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትልቅ ድርጅት እንደመሆኑ፣ ወደየትኛውም ሀገር የሚደረገውን ጉዞ አቋርጨ ዜጎቸን ማስወጣትን አስቀድም ነበር፡፡ ያሄ ጥቂት ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ሊያመጣብን ቢችልም ከከፋው የዜጎች ስቃይ ጋር ግን በአንድ ሚዛን ላይ አይቀመጥም፡፡ የአደጋ መከላከያና ዝግጁነት ኮሚሽን የሚባል ድርጅት አለ፡፡ በዜጎቻችን ላይ ጎርፍና ድርቅ ሲመጣ ብቻ ነው የሚንቀሳቀሰው? ይሄም ሰው ሰራሽ አደጋ ነው ሙሉ ሀይሉን ወደዚህ አዙሮ ሊንቀሳቀስ ይገባው ነበር፡፡

እርግጥ ነው ባቀድነው መሰረት ሰላማዊ ሰልፉ ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዳይሆን አድርገውታል፡፡ ጩኸቱ ግን ይቀጥላል… ባለን አቅም ሁሉ አፈናውንም፣ ወከባውንም ተቋቁመን ለዜጎቻችንና ለኢትዮጵያዊነት እንታገላለን፡፡ አገዛዙ ይሄን ሰላማዊ ሰልፍ ሲያፍን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንድ መልእክት አስተላልፏል፣ ይህን መልእክት እንዲያስትላልፍ ማስገደዳችንም ለኛ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ የሳውዲ መንግስት ያሻውን ያደርግ ዘንድ የፈቀድኩት እኔ ነኝ፣ በመሆኑም እሱን በመቃወም ግንኙነቴን አታበላሹ ብሎ እርምጃ በመውሰዱ ህዝቡ የነገሩ ቁልፍ የት እንዳለ፣ የአጥቂወቹ በራስ መተማመን ምን ላይ እንደቆመ በጠራ ሁኔታ ለመመልከት እንዲችል ሆኗል፡፡

ይሄ ሁሉ ነገር እየተፈጸመ የተስተዋለ አንድ ነገር አለ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዝምታ እውነተኛ ማንነታቸው፣ እውነተኛ በአገዛዙ ውስጥ ያላቸውን ቦታ ያሳየን ክስተት ነው፡፡ እንደሚታወቀው እሳቸው በኢህአዲግ እንጂ በኢትዮጵያ ህዝብ የተመረጡ አይደሉም፡፡ ኢህአዲግ የሚናገረው ከሌለ እርሳቸው የሚሉት አይኖርም፡፡ እንደ አንድ ሀገርና ህዝብ መሪ ግን የመኮነንም ሆነ የማጽናናት ቃል ይጠበቅባቸው ነበር፡፡

ባሉበት ቦታ ያስቀመጣቸው ህወሀት ነው፤ ድርጅቱ ደግሞ ይሄን አቋም አልወሰደም፡፡ ስለዚህ እንደሚቆጣቸው ስለሚያውቁ ዝምታን መረጡ፣ ቸልታንም አስበለጡ፡፡ በሀገርም ሆነ በግለሰብ ደረጃ ከዚህ በላይ ሽንፈት ያለ አይመስለኝም፡፡

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር

(ይህ ጽሁፍ በፋክት መጽሄት ተስተናግዷል፣ ነገር ግን መጽሄቱ ላልደረሳቸው ሰዎች ይደርስ ዘንድ እዚህ ለማስተናገድ ወደድኩ፡፡)

ሳውዲ አረቢያ ጎዳና ላይ የኢትዮጵያውያን ደም ብቻ ነው የሚፈሰው፡፡ የሚያለቅሱትም ኢትዮጵያውያን ሆነዋል፡፡ ኦጋዴን ታነባለች፤ ጋንቤላ ውስጥ ተወላጆቹ ለአረቦቹ እትብታቸው የተቀበረበትን መሬት ትተው እየሸሹ ነው፡፡ በኦነግ ስም መታሰር አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ቀድሞ የታሰሩትንም ማዕከላዊ፣ ዝዋይ፣ቃሊቲ….እየማቀቁ ነው፡፡ ከየ አካባቢው ኢትዮጵያውያን መሬታችሁ አይደለም ተብለው ያፈሩትን ተነጥቀው እየተባረሩ ነው፡፡ ሙስሊሞቹ ታስረዋል፡፡ መስጊድ ውስጥ ፖሊስ ገብቷል፡፡ ገዳማት ለሸንኮር አገዳ ተከልለዋል፡፡ ወጣቱ ስራ አጥቷል፡፡ ተቃዋሚዎችና ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪዎች›› ተብለው እየተሰቃዩ ነው፡፡ ህገ መንግስቱን ጠቅሶ መብትን ማስከበር ያስደበድባል፡፡ ያሳስራል፡፡

ኢትዮጵያ እንዲህ ሆነች፡፡ እምነት ምኑም ባይሆን በኢኮኖሚው ያስለቅሱታል፡፡ ከእነሱው ተጠግቶ ለኢኮኖሚው ግድ ባይኖረው በእምነቱ ይመጡበታል፡፡ ይህንም ቢሆን ‹‹ዝም›› ብሎ ቢያልፍ እህቱ ሳውዲ ውስጥ ተደፍራ ስትሞት ‹‹ህገ ወጥ ስለነበረች ነው›› ይሉታል፡፡ ለዚህ ሰቆቃ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ይደበደባል፡፡ ይታሰራል፡፡ ብቻ በአንድም ሆነ በሌላ ኢትዮጵያ ታነባለች፡፡ የሚያሳዝነው ግን እንዲህ እያነባች መጨፈሯ ነው፡፡

አንድ የአማርኛ ፊልም ላይ ነው፡፡ ተዋናዮቹ ‹‹ጥሮ ግሮ›› የሚለውን ቃል ወደ እንግሊዘኛ ለመተርጎም ሞክረው መጣር መጋር በኢትዮጵያ እንጅ ሌላ አገር እንደሌለ አምነው ይተውታል፡፡ እንደ እኔ ኢትዮጵያ እያነባች የምትዳንስ ብቸኛዋ አገር ትመስለኛለች፡፡ እያነቡ እስክስታ የእኛው ብቻ መገለጫ ይመስለኛል፡፡ ሰቆቃ ተለይቷት የማታውቀው አገር እያረረች ትስቃለች፣ እያነባች እስክስታውን ታስነካዋለች፡፡ ይህ የሚደረገው በገዥዎቿ ትዕዛዝ ቢሆንም የሚያለቅሱትም የሚዳንሱትም ግን ምስኪኖቹ ህዝቦቿ ናቸው፡፡

በአሁኑ ወቅት ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ለህዳር 29 ዳንስ እየተለማመዱ ነው፡፡ ይህ ሁሉ በሆነበት ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› የሚባሉት በተድላና በደስታ እንደሚኖሩ ሲነገር ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን እየራጠራለሁ፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ህቡዕ ይሆኑብኛል፡፡ መቼም ብሄር ብረሰቦችና ህዝቦች የሚባሉት ሳውዲ፣ ኦጋዴን፣ ጉራፈርዳ፣ ነቀምት፣ አዲስ አበባ……ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰቃዩትን ውጭ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ሳውዲ ውስጥ እህቱ የሞተችበት እንባውን በቅጡ ሳይጠራርግ ይጨፍራል፡፡ መሬቱን የተነጠቀው፣ ወንዱሙ የታሰረበት፣ ከክልል የተባረረ…..እርር ድብን እያለም ቢሆን በትዕዛዝ እስክስታውን ይመታል፡፡ እያረረ ይስቃል፡፡

ህዳር 29ኝም ሆኑ ሌሎቹ በዓላት ለእኔ እንደዚህ ናቸው፡፡ ቋንቋህ ተከብሮልሃል ተብሎ መብቱን በአፍ መፍቻው መናገር ሳይጀምር ሰቆቃ የደረሰበት ህዝብ፣ የብሄርን መብት ተከብሮልሃል ተብሎ ከስም ያላለፈ ጥቅም ያላገኘ ‹‹ብሄርና ብሄረሰብ›› ከልቡ የሚያከብረው በዓል ሊሆን አይችልም፡፡ አዎ ህዳር 29 መብገኛ፣ እያረሩ የሚጨፈርበት፣ ህገ መንግስታዊ መብት ከጭፈራና ማስመሰል ያለለፈበት እያረሩ የሚስቁበት ቀን ነው፡፡

Image

ኢትዮጵያ ግራ በሚያጋባና ሊተነበይ በማይችል የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ መገኘቷን ያመኑ የህወሃት ሰዎች መካካል የእርቅ ሃሳብ ላይ ለማተኮር እቅድ እንዲያዝ ሃሳብ ማንሳታቸው ተሰማ። ኢህአዴግ የቀድሞው የአፈና ገመዱ መንተቡን የሚያሳዩ ምልክቶች መታየታቸውና አለመተማመን መንገሱ ተጠቆመ።

ለጎልጉል መረጃ በመስጠት የሚታወቁ የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራርና ዲፕሎማት እንዳሉት ህወሃት ውስጥ “እርቅ አስፈላጊ ነው” በሚል እቅድ እንዲያዝና እንዲሰራበት ሃሳብ ቀርቧል። በድርጅቱ ውስጥ በተፈጠረ አለመተማመን ሳቢያ ስጋት የገባቸው የህወሃት ሰዎች የእርቅ ሃሳብ እንዲሰራበት ያቀረቡት ሃሳብ ግን በመደበኛ ስብሰባ አይደለም።

በህወሃትና ህወሃት በሚያዛቸው አቻ ፓርቲዎች መካከል ያለው የመከባበርና የመገዛት ስሜት ከመለስ ሞት በኋላ መበላሸቱ፣ በኢህአዴግም ሆነ በህወሃት ደረጃ የተፈጠረው ልዩነትና በሙስና ስም የተጀመረውን ዘመቻ ተከትሎ የተነሳው አለመግባባት አደጋ እንዳያስከትል ተፈርቷል። የመረጃው ምንጭ እንደሚሉት በጣም ጥቂት ካልሆኑ በስተቀር ከሙስና የጸዱ አለመኖራቸው “ማን ንጹህ ሆኖ ማንን ይጠይቃል?” የሚል ቅሬታ አስነስቷል።

ህወሃት ባሰበው በሁሉም መንገድ የበላይ ሆኖ ሊቀጥል እንደማይችል ከየድርጅቶቹ በቀጥታና በተዘዋዋሪ በስፋት እየተነገረ መሆኑንን ያነሱት እኚሁ ሰው፣ ይፋ ባልሆነ መንገድ የቀረበው እርቅን የመቀበል ጥያቄ በኦርቶዶክስ ሃይማኖት የሲኖዶስ ጉባኤ ላይ የተነሱት አስደንጋጭ ችግሮች ተከትሎ መሆኑን አልሸሸጉም።

ሊታመን በማይችልና ባልተለመደ መልኩ የሃይማኖት አባቶች ኢህአዴግን አንደበታቸውን ከፍተው በግልጽ ማውገዛቸውን፣ “አገሪቷን ገደላችኋት” በማለት መኮነናቸውን ተከትሎ በኢህአዴግ ዘንድ መደናገጥ እንደተፈጠረ ለማወቅ ተችሏል። የእምነት ጉዳይ ጥንቃቄ የሚያሻው በመሆኑ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት የተቆጠቡት ዲፕሎማት “ኢህአዴግ በቀድሞው ፓትሪያርክ ፈቃድና ውዴታ ያደርግ እንደነበረው አሁንም በደኅንነት ሃይሎች ቤተክርስቲያኒቱን መቆጣጠርና አመራሮቹን አንደበታቸውን ማፈን የማይችልበት ደረጃ መድረሱን አምኖ ተቀብሏል። በዚህ ላይ ደግሞ እስካሁን ምላሽ ያላገኘ የድምጻችን ይሰማ ጉዳይ አለ” ኢህአዴግ እንደተምታታበት አመላክተዋል።

ሲኖዶሱ በጉባኤው ያነሳቸው ነጥቦች ኢህአዴግ ነገሮች ቀስ በቀስ ከእጁ እንደወጡበት የሚያሳይ እንደሆነ ያመለከቱት የኢህአዴግ ሰው “ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የኢህአዴግ አባላት በልብ ከድርጅቱ ጋር እንደሌሉ ሪፖርት ቀርቧል። አብዛኛው አባልና ደጋፊ ባለሃብቶች የሚባሉትን ጨምሮ ሰላማዊ ለውጥ እንዲካሄድ ኢህአዴግ ወደ እርቅ መንገድ እንዲሄድ ይፋ (ኦፊሴላዊ) ባልሆነ መልኩ ያነሳሉ” በማለት ድርጅቱ የገባውን ስጋትና መሸርሸር ያስረዳሉ።

እርቅ ከተፈለገ ለምን በግልጽ አይቀርብም በሚል ለቀረበላቸው ሃሳብ ዲፕሎማቱ ምላሽ ለመስጠት አልፈለጉም። ይሁን እንጂ “ከማን ጋር ነው የምንታረቀው? እነማንን ነው ለእርቅ የምንጋብዘው? እርቅ ጠያቂ መሆን ያለበትስ ማን ነው?” የሚሉት በግልጽ ባይቀርቡም ተመሳሳይ የስጋት ጥያቄዎች እንዳሉ ሳይገልጹ አላለፉም።

በቅንጅት ጊዜም በተመሳሳይ የዕርቅ ፍላጎትና “ሥልጣን እናስረክብ” የሚል አቋም ተነስቶ እንደነበር ያስታወሱት ምንጫችን፤ በወቅቱ ሃሳቡ ተግባራዊ ያልሆነው “ወያኔዎችን ወደመጡበት ጠራርገን እንመልሳቸዋለን” በማለት አንድ የቅንጅት አመራር ለሕዝብ መፈክር ሲያወርዱ ከተሰማ በኋላ ነበር፡፡

በመከላከያ አዛዦችና በደህንነት የተለያዩ መምሪያዎች የሃላፊዎች ለውጥ እያካሄደ ያለው ኢህአዴግ ከአቻ ፓርቲዎች ጋር ውህደት በማድረግ ብሔራዊ ፓርቲ ለማቋቋም በሁለት ጉባኤዎች ሃሳብ ቢቀርብም ተግባራዊ አላደረገውም። ፓርቲው ህብረ ብሔር ከሆነ ህወሃት የገነባቸው የንግድ ድርጅቶችና በሞኖፖል የያዘውን ቁልፍ ስልጣን እንዲያጣ ስለሚያደርገው ጊዜ ሲያጓትት መቆየቱን ያመለከቱት የመረጃው አቀባይ “ይህ ፍርሃቻ አሁንም ሆነ ወደፊት ለሚፈለገው በሃሳብ ደረጃ ያለ እርቅ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል የውስጥ ለውስጥ ሃሜት አለ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል። ሆኖም እጅግ የተወሳሰበ የፖለቲካ ትወና ውስጥ ያሉት ካልሆኑ በስተቀር በማናቸውም መልኩ እርቅን ለመቀበል የማያቅማሙ እንደሚበዙ ግን አልሸሸጉም፡፡

በኢህአዴግ ውስጥ አለመተማመን መንገሱን የሚናገሩ ወገኖች “ለራሳቸው መተማመን ያቃታቸው ክፍሎች እንዴት ሌላውን አስማምተው ይመራሉ” በማለት መጠየቅ ከጀመሩ ቆይተዋል። በተለይም አዲሱ ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ወደ መንበሩ ከመጡ በኋላ አገሪቱ በደቦ መመራቷ የኢህአዴግን መሽመድመድ የሚያሳይ እንደሆነም እየተቹ ነው።

sebhat negaሁሉም ሰላም ነው፤ ልማት ነው፤ ዕድገት ነው፤ ህዳሴ ነው … በማለት አንድም ችግር የሌለበት ለመምሰል የሚሞክረው ህወሃት ደግሞ በውስጡ የመከፈል አደጋ አጋጥሞት እንደማያውቅ ምንነታቸውና የስራ ደርዛቸው በውል በማይታወቀው አቶ ስብሃት አማካይነት እያስታወቀ ነው። እሳቸው እንደሚሉት ችግር የህወሃት “ሰማያዊ ስጦታውና በረከቱ ነው” አቶ ሃይለማርያምም በበኩላቸው “ኢህአዴግ መካከል መከፋፈል አለ የሚሉ የዋሆች ናቸው” ሲሉ አንድነት የሰፈነበት አመራር እንዳለ ለማስተጋባት ሞክረዋል።

የእርቅ ሃሳብ ተሰንዝሯል በማለት መረጃውን የሰጡን ዲፕሎማት ግን ይህንን አይቀበሉም። “በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሚታይ ነው። አንዱ እኔ ነኝ። ሌሎችም አሉ። ብዙዎች ሰላማዊ ህይወት ናፍቆናል። የተወሳሰበውን አገራችንን ፖለቲካ አካሄድ ለመተንበይ ተቸግረናል። መፍትሔው የእርቅ ሃሳብ ብቻ ነው” በሚል ተከራክረዋል።

በድርጅታቸው ውስጥ የበላይና የበታች መጥፋቱን፣ የበታቹ የበላዩን እንደሚያዘው፣ አንዳንዴ የበላይ መስለው ምንም ዓይነት የውሳኔ ሰጪነት ሚና የሌላቸው ክፍሎች መኖራቸው የአደባባይ ምስጢር እንደሆነ የሚናገሩት እኚሁ ሰው፣ “እርቅና ዋስትና የሚሰጥ አግባብ ቢያገኝ የመጀመሪያው ስምምነት ፈራሚና ደጋፊ ስብሃት ነው። ቀሪውን የጡረታ ዘመኑንን በትዝታ ያለውን እየበላ መኖር ይፈልጋል። እሱ ብቻ ሳይሆን ብዙዎች ተመሳሳይ ፍላጎት አለን። አስከማውቀው ድረስ ችግሩ ከራስ ምግባርና ከድርጅት ተልዕኮ በመነጨ የተሰሩት ጥፋቶችና ሃጢያቶች መብዛታቸው ከለውጥ በኋላ የሚያመጣቸው የተጠያቂነት ጣጣዎች ናቸው” ብለዋል፡፡

በኢህአዴግ ውስጥ ንጹህ ሰዎች አሉ ለማለት የማይቻልበት ደረጃ መደረሱን የሚያመለክቱት ዲፕሎማት፣ ህወሃትም ሆነ ኢህአዴግ አሁን የጋራ ነጠብ የሌላቸው፣ የርስ በርስ ትስስራቸው የላላና የተለያየ፣ አንዱ ሌላውን ለመንካትና ለመገምገም የሞራል ብቃት ያጣበት፣ እርስ በርሱ በወንጀል የሚጠቋቆምበት የውድቀት ጫፍ ላይ መድረሱን የውጪ አገር ወዳጆቹም ተረድተውለታል፤ አሁን ለእነርሱም ችግር የሆነባቸው ቁጭ ብለው ሥልጣን ላይ የሰቀሉትን ህወሃት አሁን ቆመው እንዴት ማውረድ እንደሚቻል መቸገራቸው ነው ብለዋል። የእርቅ ሃሳቡ ከውጪ አገር ወዳጆቻቸው ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ ግን ፍንጭ አልሰጡም።

በህወሃትም ሆነ በኢህአዴግ ደረጃ የውስጥ ስጋት ቢኖርም “ሕዝብ እስኪ ዛሬን ልደር” በሚል የሞራል ውድቅት ውስጥ በከተተው ድህነት የተመታ በመሆኑ ለጊዜው ያምጻል የሚል ግምገማ አለመኖሩን ዲፕሎማቱ አመልክተዋል። ይሁን እንጂ ህዝብ በኢህአዴግ ደስተኛ አለመሆኑ፣ የጥበቃና የቁጥጥር መረቡ እንደወትሮው ትጋት ማጣቱ፣ የአካባቢ ስሜትና “ወገኔን ለምንና እስከመቼ አሳልፌ እሰጣለሁ?” የሚል አስተሳሰብ መበራከቱ፣ አጋጣሚ ተቃውሞ ቢነሳ መቋቋም እንደማይቻል፣ ረብሻ ከተነሳ የስርዓቱ ባለሟሎች ህልውና ጉዳይ አስጨናቂ እንደሚሆን ግንዛቤ ስለመኖሩ አላስተባበሉም። በማያያዝም እሳቸው በዚህ ደረጃ ስርዓቱን ከገመገሙና ችግሩን ከተረዱ በይፋ የማይከዱበትን ምክንያት ተጠይቀው “ለጊዜው በምስጢር ጠባቂነት የዝግጅት ክፍሉ ቃሉን ይጠብቅ። የቀረውን ወደፊት እናየዋለን” የሚል ድፍን መልስ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሰጥተዋል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

ውዱ ጣፈጠ (ዶ/ር)

ታሪክ ትም/ ክፍል

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ

በሀገራችን ውስጥ ለኦርቶዶክስ ክርስትና መስፋፋትና መደርጀት ትልቁን ሚና የተጫወቱት ሀገራዊ ቅዱሳን ካህናትና የሃይማኖት መሪዎች ናቸው፡፡ በተለይም በመካከለኛው ዘመን መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን በአንድነት ሁነው አብረው ሰርተዋል፡፡ ነገሥታቱና ካህናቱ አብረው የሰሩትን ያህል በመካከላቸውም አንዳንድ ከሃይማኖት ጋር የሚጋጩ ነገሮች እየተከሰቱ ሲያጋጩዋቸውና ሲያጣሉዋቸው ኑረዋል፡፡ በመካከሉም እርቅ እተፈጠረ የተለመደ ስራቸውን ሰርተዋል፡፡ ያለ ውህደታቸውም የመንግሥትና የቤተ-ክርስቲያኗ  መስፋፋት በጥንካሬ ሊቀጥል አይችልም ነበር፡፡

ኢትዮጵያውያን ካህናት ከዛጉዌ ስርወ-መንግሥት ጀምሮ የሃይማኖት መÍህፍትን ከቅብጥ፤ ከአረብኛ፤ ከጽርእ በመተርጎም ለሃይማኖት ስራ እንዲዉሉ አድርገዋል፡፡ በጊዜውም የግእዝ kk ትልቅ የሥነ ጽሑፍ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ጥረዋል፡፡ የገድል መÍሕፍት በብዛት ተጽፈዋል፡፡ የሀገራቸውን ቤተ ክርስቲያን አሰራር የተመቸ ለማድረግ አዳዲስ ነገሮች እንዲለመዱና እንዲaaሉ ለውጥም እንዲመጣ ጥረዋል፡፡ በጣት ከሚቆጠሩ አንዳንድ የቤተ-ክርስቲያኗ የቅብጥ (ግብፅ) ጳጳሳት በስተቀር ለቤተ-ክርስቲያኗ ለውጥ እዲጀመር ጥረት ያደረጉ የቅብጥ ጳጳሳት የሉም፡፡

ኢትዮÉያውያን ቅዱሳንን ከዘመኑ ነገስታት ጋር ሲያጋጭ የኖረው ነገስታቱ ለውጥንና አንዳንድ Bይማኖታዊ ትችቶችን ለመቀበል ባለመፈለጋቸው ነበር፡፡ ቅዱሳኑና  ነገRታቱ መጋጨት የጀመሩት በመካከለኛው ዘመን የኢትዮÉያ ታሪክ ዘመን ነግሶ ከነበረው ከአÑðአምደ Òዮን ዘመነ መንግRት ጀምሮ ነበር፡፡

      ዛሬ የሚመረቀው የዲያቆን ዳንኤል ክብረት የገድላት የአማርኛ ትርጉም መÎÙ ግልÎየሚያደርገው እነዚህ የመካከለኛው ዘመን ቅዱሳን ለBይማኖታቸውና ለሀገራቸው የሰሩትን kሚ ስራ፤ Bይማኖታዊ ተጋድሎና መንፈሳዊ Òናት ቆልጭ አድርጎ የሚያሳየን ነው፡፡ አሁን ባለንበት ዘመን ገድላትን፤ ታሪከ-ነገስታትን እንዲሁም ሌሎች የታሪክ ድርሳናትን ወደ አማርኛም ይሁን ወደ ሌላ ሀገራዊ kk ተርጎሞ ለማቅረብ ራእይ ያለው ጠንካራ የስራ ሰው ለማየት ብርቅ በሆነበት ጊዜ እነዚህ ድንቅ Bይማኖታዊ  ገድላት በዲያቆን ዳንኤል ክብረት ወደ አማርኛ ተተርጉመው መቅረባቸው ይበል፤ እጅ ይባርክ፤ በለመደ ጣትህም ሌሎቹን ለመተርጎም እንድትበቃ እግዚአብሄር ይርዳህ ከሚል ማበረታቻ ቃላት ጋር መሆን አለበት፡፡

ባለፉት ጥቂት አመታት ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ከግእዝ ወደ አማርኛ የተረጎሙት የደቂቀ እስጢፋኖስ በህግ አምላክ የሚልና የአባ ባሕርይ ድርሰቶችን አስነብበውናል፡፡ አቶ አለሙ ኃይሌ የአፄ ገላውዴወስን፤ የአፄ ሰርፀ ድንግልንና የአፄ ሱስንዮስን ታሪከ ነገሥታት አሳትመው ለአንባቢ አቅርበዋል፡፡

        ይህንን አራቱ yያላን የሚለውን ደጎስ ያለ መÎÙ (ከመታተሙ በፊት እንዳነብለት ጠይቆኝ ሳነበው በሶስት ቅÎ የተዘጋጀ ነበር) ተመልክቸ አስተያት እንድሰጠው በጠየቀኝ ጊዜ ስው መቸም ብርቱ ነው በሚል የግርምት ህሳቤ ነበር የተቀበልኩት፡፡ ወቅቱ የአመቱ የትምህርት ማጠቃለያ ስለነበርና ሌሎች አጣዳፊ ነገሮች ስለነበሩብኝ፡፡ ቀስ እያልኩ ማንበብ ስጀምር ግን እንዳነብ ስለ ሰጠኝ እድል እያመሰገንኩት ጭምር፡፡

ይህ አራቱ yያላንበሚል ርእስ ወደ አማርኛ የተተረጎመው መÎÙ የአቡነ  በÐሎተ-ሚካኤል፤ አቡነ ፊልÊስ፤ አቡነ አኖሪዎስና አቡነ አሮን ገድል ነው፡፡ እነዚህ አራቱ yያላን ለBይማኖታቸው መስፋፋት ወደር የማይገኝለት ታሪክ የሠሩ፤ Bይማኖትን ያስፋፉ፤ ብዙ ደቀ መዛሙርት ያስተማሩና ያፈሩ፤ ገዳማትን የመሠረቱ፤ Bይማኖታዊ ክርክር አንሥተው በጊዜው ከነበሩ ነገሥታት ጋር ፊት ለፊት የተፋለሙ፤ የደረሰባቸውን ቁጣ፤ ግርፋት፤ እንግልት፤ ስቃይና መከራ፤ እንዲሁም ስደትና ግዞት ለBይማኖታቸው  በጸጋየተቀበሉና ማንኛውንም መስዋእትነት በBይማኖታቸው በጽናት የተወጡ ናቸው፡፡

      ሌሎች የታሪክ መÑህፍትም እንደሚያስነብቡን ክርክሩ የተጀመረው በአÑððአምደ Òዮን ዘመነ መንግስት ጊዜ ነው፡፡ እነዚህ ቅዱሳንና ሌሎች የBይማኖት ወንድሞቻቸው ወደ መንግስቱ መቀመጫ ተጉዘው Bይማኖታችን የሚያዘውን ነገር አልፈÐምክም በማለት ለምመከርና ለመመለስ በሄዱበት ወቅት ነበር፡፡ የነገሩ ጭብጥ “ለምንት አውሰብከ ብእሲተ አቡከ – ለምን የአባትህን ሚስት አገባህ” የሚል ነበር፡፡ የክሱ ጨብጥ  Bይማኖታዊ ህግን ጥሰሀል የሚል ነበር፡፡ በጊዜው ንጉሱ ይህንን ተቃውሟል፡፡ የምትጠቅሱት አባቴ አይደለም በሚል፡፡ ንጉሱን በአደባባይ እንደወቀሱት በትእግስት ሊያሰናብታቸው አልፈለገም፡፡ በአደባባይ እንዲገረፉ ከዚያም በግዞት ወደ ትግራይ እንዲሄዱ ተደረገ፡፡

      ከጥቂት አመታት በ|ላ ተመልሰው በመምጣት ሌላ ጥያቄ አነሱ፡፡ በገዳም ውስጥ በአንድነት የሚኖሩ ወንድና ሴት መነኮሳት መቀመጫ ተለይቶ እዲወሰን ጠየቁ፡፡ በጊዜው ወንድና ሴት መነኮሳት በአንድነት ይኖሩ ነበር፡፡ ቀደም ብሎ በትግራይ ውስጥ የመነኮሳት መኖሪያ የተለያ ቦታ ነበርና ይህ ጥያቄ ወዲያውኑ ተቀባይነትን አገኘ፡፡ ከዚያም በሸዋና በሌሎች አካባቢዎች ተግባራዊ እንዲሆን ተደረገ፡፡

      በሶስተኛ ደረጃ የቅብጡ ሊቀ-ጳጳስ የቅስናና የዲቁና ማዕረግ ለመስጠት ገንዘብ ይቀበላል (simony) የሚል ክስ አቀረቡ፡፡ ምክንያቱም እነዚህን የክህነት ማዕረጋት ለመስጠት ገንዘብ ማስከፈል በሐዋርያት የተወገዘ ነበርና፡፡ ንጉሱ  ይህንን ክስ አልተቀበለውም፡፡ የቅብጡ ጳጳስም ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው ሁሉ እኔም ተቀብያለሁ ስህተት የለበትም በሚል ክሱን በማጣጣል ካህናቱን አወገዘ፡፡ እነዚህ ካህናትም በግዞት ወደ ዝዋይ ሀይቅ እንዲጋዙ ተደረገ፡፡ በሀካባቢው የእስልምና የመስፋፋት ችግር ስለነበር በዚያ በኩል ለመኖር አይችሉም ይቀጣሉ በሚል እሳቤ፡፡ ነገር ግን ለጥቂት አመታት በዝዋይ አካባቢ ከኖሩ በ|ላ የአባይን ወንዝ እየተሻገሩ ክርስትናን ለማስፋፋት ወደ ጎጃምና ወደ ጣና ሀይቅ አካባቢ አገሮች በስደት ራቅ ብለው ሄዱ፡፡

      ይህ ክርክር በአÑðð አምደ Òዮን ዘመነ መንግስትና በልጁና በወራሹ በአÑððሰይፈ አርእድ ዘመነ መንግስታት ጊዜ ተጠናክሮ ቀጠለ፡፡ ሰይፈ አርእድ ወደ ስልጣን በመጣ ጊዜ በአንዲት ሚስት ተወስኖ ለመኖር አስቀድሞ ቃል የገባ ቢሆንም ቃሉን አክብሮ አልኖረም፡፡ በዘመኑም እነዚህ ቅዱሳን ወደ መቀማጫ ከተማው እየመጡ ከስህተቱ ለመመለስ ሞከሩ፡፡ ነገር ግን አልተሳካላቸውም፡፡ እንዲያውም እንግልቱ፤ ቅጣቱና መጋዙ እተባባሰ ሄደ፡፡ ከዚያም እነዚህ አበው ቅዱሳን ወደ ሩቅ ሀገር፤ በጣም ሞቃታማና ቆላማ ወደ ሆነ ሀገር ተጋዙ፡፡ በረሀብና በጥም እንደዚሁም በስቃይ ሲጠበሱ ከእንደዚህ አይነት ድርጊታቸው ይቆጠባሉ በሚል፡፡

      በመÒኃፉ ውስጥ እንደምታነቡት አበው ቅዱሳኑ የደረሰባቸው ቅጣት፤ ግርፋትና እንግልት በዘመናችን ካየነው የደርግ ዘመን ተመሳሳይና በጣም ኢሰብአዊ የሆነ ድርጊት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ አንዱ በሃይማኖት ሌላው በፖለቲካ ሰበብ የተፈፀመ፡፡ እንዲያው ለቅንጣት ምሳሌ ያክል ክብራቸውን ለማዋረድና መሳለቂያ ለማድረግ በንጉሱ መቀማጫ ከተማ በአደባባይ ልብሳቸውን አውልቀው እርቃናቸውን እንዲዘዋወሩ ተደረገ፡፡ ረ ስንቱ ይነሳል፡፡ እነርሱ ግን በአቋማቸው Ðንተው የሀይማኖታቸውን ስነ-ምግባር አጥብቀው ያዙ፡፡ ባላቸው ሀይማኖታዊ Òናት ግፉና መከራውን እንዲሁም ግርፋቱንና ስቃዩን በፍስሀ ተቀበሉት፡፡ ስደቱንና ግዞቱን እንደ ቀላል ችግር ተጋፈጡት፡፡ በደረሰው አለማዊና ዘግናኝ ቅጣት የወደቁትንና መስዋዕት የሆኑትን ብዙሀኑን የሀይማኖት ወንድሞቻቸውንና እህቶቻቸውን አርማ ተሸክመው እስከመጨረሻው ድረስ Ðንተው መንከራተቱንና ስቃዩን በአምላክ ስም አሸነፉ፡፡

      በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የምናገኘው ነገር አቡነ ያእቆብ በተባሉ የቅብጥ ሊቀ-ጳጳስ ዘመነ ፕትረክና ሀይማኖትን ለማስፋፋት ሲባል ኢትዮጵያ በአስራ ሁለት አገረ ስብከታት መከፋፈሉዋንና መምህራን መመደባቸውን ነው፡፡ ይህ ሊቀ ጳጳስ የአቡነ ተክለ-ኃይማኖትን አስራ ሁለት ደቀ መዝሙራትንና የደብረ ሊባኖስ ገዳም ምሩቃንን በመመደብ አገሪቱን ከፋፍሎ እንዲስተምሩ አሰማራቸው፡፡ በዚህ የለውጥ እንቅስቃሴና ቅዱሳኑ በተደረገባቸው መጋዝ ቤተ ክርስቲያንዋ ተስፋፋች፡፡ የሀገረ-ስብከት መከፋፈልም መሰረት ተጣለ፡፡ በቅብጡ ሊቀ ጳጳስ የተፈለመው ብቸኛ የለውጥ መንፈስ ከቅብጥ ከሊቀ ጳጳሳት መካከል ይህ ሊቀ ጳጳስ ብቻ ስሙ በበጎ ሲዘከር የሚኖር ነው፡፡

      በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ከምናገኛቸው አያሌ ቁም ነገራት መካካል በጣም ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡ የሀገራችን ገድላት፤ ታሪከ ነገስታትና ሌሎች ጥንታዊ Òሁፎች በግእዝ የተÑፉትን ወጣቱ ትውልድ ምን እንደተሰራ ለማወቅ ይቸግረዋል፡፡ የሀይማኖት ታሪክን፤ ድርሳናትን፡ ገድላትንና አለማዊ የጥንት ታሪከ ነገስታትን የማንበብና የመመርመር ፍላጎት በአእምሮው ካልሰረÐ በስተቀር፡፡ በቅርቡ ልናገኛቸው የምንችላቸው ገድላት፤ ወይንም በሌላ የውጭ kk ተተርጉመው የሚገኙና እኛ ግን በቅርብ የማናገኛቸው፤ እንዲሁም የት እንደሚገኙ ለማናውቅ ሁሉ ዘለግ ያለ እድሜና ብርታት ለዲያቆን ዳንኤል ክብረት ይድረሰውና እነሆ ይህንን መÒኃፍ በእጃችን መዳፍ ውስጥ  አስገባልን፡፡ ለመንፈሳዊ ተማሪዎች፤ ለሃይማኖትና ለታሪክ፤ በተጨማሪም ለሌሎች ምሁራን፤ እንዲሁም አግባብነት ላላቸው ሌሎች የትምህርት ዘርፎች የሚረዱ ዋቢ መጻሕፍት ያልተተረጎሙትንና በእጃችን ያልገቡትን ስራዎች የሚችሉ ሁሉ ተርጉመው እንዲያቀርቡልን ይህ ስራ ያበረታታል፡፡                      

      ባለፉት ክፍለ ዘመናት በሀገራችን በደረሰው የፖለቲካ ምስቅልቅል፤ ጦርነትና የህዝብ ፍልሰት በመካከለኛው ዘመን የጥንት የቦታ ስያሜዎች አንድም ተረስተዋል፤ ጠፍተዋል ወይንም በሌላ አዲስ ስም ተተክተዋል፡፡ የጥንቱን ዋና የመረጃ መጻሕፍትን ለሚያነብ ተመራማሪ እነዚህን የጥንት ስያሜዎች የት አካባቢ እንደነበሩ ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል፡፡ ትልቅ የራስ ምታትም ነው፡፡ እነሆ በዚህ መፅሀፍ ዲያቆን ዳንኤል ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል የጥንቱን ስያሜ ይዞ ታሪኩ ተፈፅሞባቸዋል በሚባሉት አካባቢዎች ተዘዋውሮ የአብዛኞቹን ቦታዎች የጥንት አካባቢ ሊደርስባቸው ችሏል፡፡ አብዛኞቹም ስማቸው ተቀይሮ በሌላ ተተክቷል፡፡ አንዳንዶቹም ትንሸ ለወጥ ብሎ ሙሉ ለሙሉ ሳይጠፉ ተገኝተዋል፡፡ ይህን ለማድረግ ለብዙ ቀናት ሳይሰለች አቀበትና ቁልቁለት፤ ሸለቆና ወንዝ ሳይበግረው የጥንቱን አካባቢ ሊለይ በመቻሉ አድናቆት ይገባዋል፡፡ በግርጌ ማስታዎሻ ሰፋ ካለ ማብራሪያ ጋር አቅርቦልናል፡፡ ስሞቹ የተገኙበትን ሌሎች መረጃዎችንም አካቶልናል፡፡ በአገራችን ጥናቱ ስለተደረገበት ዘመንና ለሌላም ነገር የፖለቲካ ካርታ የሌለ ቢሆንም ይህንን ስራ ይዘው ለመቀጠል ለሚፈልጉ ጎዳናውን አስቀድሞ ጠርጎ መንገዱን አመቻችቶላቸዋል፡፡

      እነዚህ አበው ቅዱሳን የደረሰባቸው ስቃይና እንግልት፤ እስራትና ግዞት ምን ያህል ስር የሰደደ እንደነበር በግልፅ ያስተምረናል፡፡ ለመሆኑ የእግዚአብሄርን ስም አንግበው የሃይማኖት ስራ ሲሰሩ ህይወታቸውን ሁሉ ለተንገላቱ አበው ቅዱሳን በክርስቲያኑ መንግስት ይህ ስቃይ ይገባቸው ነበርን ብለን ታሪኩን በጥልቀት እንድንመረምር ይረዳናል፡፡ አሁን በቅርቡ በተለያዩ ሀገራት የእኛንም ጨምር በፖለቲካ ጉዳዮች ዜጎች የደረሰባቸውን መጎሳቆልና መንገላታት ስናጤን አበው ቅዱሳን አባቶቻችን ያለፉበትን የስቃይ ዘመን እንድንገመግም እንገደዳለን፡፡ ሌላው ቀርቶ አሁን በቅርቡ በደርግ መንግስት ያለቁትን የቀይና የነጭ ሽብር ሰለባዎችን ስናስብ ወጣቱ ትውልድ በስንት አይነት ጣእርና ስቃይ ተለብልበው እንዳለቁ ለመገንዘብ ይረዳናል፡

      ሌሎች ተመራማሪዎች አዲስ መረጃ በማግኘታቸው ሰፊና ጥልቅ ምርምር አካሂደው ታሪኩን አገናዝበው እንደሚያስነብቡን አልጠራጠርም፡፡ በዚህ አጋጣሚ የደቂቀ እስጢፋኖስ ተከታዮች የደረሰባቸውን እልቂትና ጭፍጨፋ ከጥቂት አመታት በፊት ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ከግእዝ ተርጉመው ያቀረቡልንን መፅኃፍ ያነበባችሁት ስለሆነ ነገሬን እዚሁ ልkጭ፡፡

      ዲያቆን ዳንኤልን ሊያስመሰግነው ከሚገባው ስራ መካከልም በብዙ ድካም የግርጌ ማስተወሻውን ፅፎ ማካተቱ ነው፡፡ በግርጌ ማስታወሻ የተዘረዘሩት ማብራሪያና መግለጫ እጅግ አድካሚ ስራ ነው፡፡ ይሁንና ስራውን ምን ያህል አድቅቆ እንደሰለቀው ግልፅ ያደርግልናል፡፡ በተጨማሪም ተካቶ የቀረበው የቦታና የሰው ስም መዘርዝር እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ ይህም አታካችና አድካሚ ሲሆን በምንም ሁኔታ ሰሞች እንዳይረሱ ሳይፃፉ እንዳይቀሩ ለማድረግ በተደጋጋሚ የተደረገውን የአርትኦት ትኩረት ነው፡፡ ሰለ አንድ ነገር ለማወቅ የሚፈልግ ሰው መፅሀፉን ገፅ በገፅ አንብቦ የሚፈልገውን ስም በቶሎ ለማግኘት የሚረዳ በመሆኑ ስራን ያቃልላል፡፡ የህትመት ስራ የናረ ባይሆን ኖሮ የግእዙ ፅሁፍ ቢካተት ጥሩ ነበር፡፡

      ይህ ጥልቅ ስራ ሌሎች ተመራማሪዎች የርሱን አርአያነት ተከትለው እንዲህ አይነቱን የትርጉም ስራ ለመስራት ያነሳሳቸዋል፡፡ በሀገራችን የተደረሱ ብዙ ስራዎች እንዲሁም ከተለያዩ የውጭ kk ወደ ግእዝ የተተረጎሙ የብዙ መጻሕፍት ትርጉም ስራ ገና አልተነካም፡፡ ይህ የማንቂያ ደወል በብዙ ሰዎች ጆሮ ላይ ሊደውል ይገባል፡፡ በተለይም የቤተ-ክርስቲያናችን ካህናትና ምሁራን – ከሊቅ እስከ ደቂቅ – ይህንን የትርጉም ስራ ስራየ ብለው እንዲጀምሩት ይሞግታቸዋል ያበራታታቸዋልም ብየ እገምታለሁ፡፡ በተለይም ጠቅላይ ቤተ-ክህነትም ሆነ የባህል ሚኒስቴር ሊያስቡበት ይገባል፡፡ ምንም እንኳ የተጠናከረ ድርጅትና የስራ ተነሳሽነት የሚያስፈልገው ቢሆንም በተለይ ጠቅላይ ቤተ-ክህነት እኔ አለሁ ብሎ ብእሩን ሊያነሳ ይገባል፡፡

      ስራው መበረታታት ያለበት ከግእዝ ወደ አማርኛ kk በመተርጎሙ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ ወደ ሌሎች የብሄረሰብ kkዎች ቀስ በቀስና በጊዜ ሂደት ስራው መጀመር ያለበት መሆኑ ጭምር ነው፡፡ በጊዜ ሂደት ከታሰበው መድረስ ስለሚቻል አቢይ ቁም ነገሩ ለመጀመር ቆርጦ መነሳሳቱ ላይ ነው፡፡

      ለማጠቃለል ያህል ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ስለ ሰራኸው ስራ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ የድካምህን ዋጋ ባለቤቱ ይክፈልህ፡፡ ሌሎች ሰራዎችህንም አሁን የተወጠኑት ጨምሮ በተከታታይ እድታስነብበን በትህትና እመኛለሁ፡፡ ቅዱሳን አበውን የባረከ አምላክ አንተንና ቤተሰብህን ይባርክ፡፡

አመሰግናለሁ፡፡           

                      

ምንሊክ ሳልሳዊ :- ወገኖቼ መቸም የወያኔን እኩይ ምግባር የቱን ጥለን የቱን አንስተን እንደምንናገር አናውቅም ሙሉ ሰውነቱ በመጥፎ የፖለቲካ ፈንጂዎች እና በቀሎች የተሞላ በማዘናጋት እና በማደናበር በማጭበርበር የተሞላ መሆኑ ሳይታለም በይፋ የተፈታ እውነት ነው::

የዛሬ ትኩስ ወሬ የሆነው የወያኔው ጁንታ ከግንቦት ሰባት ጋር እንደራደር የሚለው ጥያቄ እጅም አስገራሚ የማይደንቅ ሆኖም በጭንቅ ሰአት የተጠበቀ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ አሊያም ማጭበርበር ሲጨመርም ማዘናጋት የታከለበት ጠማማ አክሄድ መሆኑ ለማንም አይጠፋውም:: ወያኔ ከበረሃ ጀምሮ በአባቱ ሻእቢያ በኢሕኣፓ በደርግ በኢሕዴን እና ተመሳሳይ አንጃዎች ላይ ሲሰራ የነበረው የማጭበርበር እና የማዘናጋት ፖለቲካ አልፎ እስከ ሽብር ተግባር ድረስ የሚፈጽም አደገኛ አሸባሪ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል::ወያኔ በአሲምባ ኢሕኣፓን በሮም እና ሎንዶን ደርግን እንዲሁም በበረሃ ሻእቢያን እና ኢህዴንን… ከዛም የሽግግር መንግስት ከተባለ ጀምሮ እንደ ኦነግ ኦብነግ የመሳሰሉ ድርጅቶችን በድርድር ስም ሲያጭበረብር የነበረ ከመሆኑም በላይ በትልቁም የኢትዮጵያን ሕዝብ ያጭበረበረ እና እያጭበረበረ እያዘናጋ ያለ ቅስም ለመስበር የሚራውጥ የሽብር ጀሌ ነው::

ወያኔ አሸባሪ ብሎ ከፈረጀው ግንቦት ሰባት ጋር ለመደራደር ያቀረበው ጥያቄ አንድም ቀልድ ነው አንድም ማዘናጊያ ስልት ነው:: ወያኔ በሃገር ውስጥ ያለውን ሕዝብ እና ከሃገር ውጪ ያለውን ዲያስፖራ ለማዘናጋት እና ከገባበት አጣብቂኝ ለመውጣት የመጀመሪያውን ዳገት በመቧጠጥ ላይ ይገኛል::የወያኔው ጁንታ ያቀረበው የድርድር ጥያቄ ወጥሮ የያዘውን ከፍተኛ አደጋ ለመወጣት ሲሆን ከዚህም መሃል

-በሃገሪቱ ይከሰታል ተብሎ የሚሰጋው እና በጥናት ሪፖርት የቀረበበት የኑሮ ውድነት
-በሰራዊቱ እና በደህንነቱ ተቋማት ውስጥ እየተነሱ ያሉ ህገመንግስታዊ ጥያቄዎች
-በተለያዩ ሃገሮች በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሱ ያሉ ብሄራዊ ውርደቶች
-የሃይማኖት መሪዎች ወቀሳ እና የሃይማኖት ነጻነት ጥያቄ
-በሃገሪቱ እየተስፋፋ የመጣው የትውልዱ ስራ ማጣት እና ስደት
-የፖለቲካ ምህዳኡ መጥበብ ያስነሳው አለማቀፍ ጫና
-በየእስር ቤቱ ያሉ የፖለቲካ እና የሕሊና እስረኞች ይፈቱልን ጫና
-እንዲሁም ተመሳሳይ የሆኑ የዲሞክራሲያዊ መብቶች እና የፖለቲካ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ለውጦች ጥያቄዎች ወያኔን አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሲሆን በየጊዜው በሚነዙ ፕሮፓጋንዳዎች እና በማይገናኚ የሃሰት እይታዎች የሚዲያ ፍጆታ የፖለቲካ ውሸቶች ሕዝብ በጁንታው ላይ ያለውን እምነት በማጣቱ እና ተስፋው በመሟጠጡ ወያኔ በውጥረት ውስጥ በመሆኑ ይህንን ለማዘናጋት እና የፖለቲካ ማጭበርበር ለመፈጸም የድርድር ጥያቄዎች ማቅረቡ ምንም አዲስ ነገር ካለመሆኑም በላይ የሚጠበቅ እና የማዘናጊያ ደውል ነው:; ከዚህ ቀደም ተደራደርኩ ካላቸው ድርጅቶች ላይ ያመጣው ታጣ እና ውጤት ቢኖር ስደት እና ሞት ለድርጅቶቹ አባላት እንዲሁም አሸባሪ የሚል ታርጋ መለጠፍ ብቻ ነው::

በግንቦት ሰባት ውስጥ ያሉ ታጋዮች በኢህኣፓ በኢሕኣዴግ በቅንጅት እና በተለያዩ ፓርቲዎች ውስጥ በመሆን የተለያዩ እውቀቶችን እና ልምዶችን የቀሰሙ እንደመሆናቸው ለወያኔ የማዘናጊያ እና የማጭበርበሪያ ደውል መልስ አይጠፋቸውም ትግሉም ስልጠናውንም ሃገር እና ወገን የማዳን ስራውም ከበፊቱ በበለጠ መልኩ እየተጠናከረ እንደሚሄድ እንተማመናለን::
‪#‎MINILIKSALSAWI‬
ለወያኔ የማደናበሪያ እና የማዘናጊያ ስልቶች የሚራራ ልብ የለንም!! ድል ለተጨቆኑ ሕዝቦች!!እናቸንፋለን!!!

Image

ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የገነባዉ ሥርዓት በከፍተኛ ችግሮች የተወጠረ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የመሪው ሞት በወያኔ መሀል ያስከተለው ቀውስ፤ የሕዝብ ሁለገብ ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበት መሄድ የፈጠረበት ስጋት እና ምርጫ በደረሰ ቁጥር የሚደርስበት ጭንቀት መጨመር ተደማምረው ውጥረቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እያደረሱት መሆኑን የሚያሳዩ በቂ ምልክቶች አሉ። የእስካሁኑ ተሞክሮዓችን እንደሚያሳየው ወያኔ ውጥረት ሲበዛበትና መዉጪያና መግቢያዉ ሲጠፋዉ ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችን “እንወያይ፣ እንደራደር” በማለት ለውጥረት ማስተንፈሻ ጊዜ የሚገዛ መሆኑን ነው። ሰሞኑን በወያኔ አገዛዝ መልዕክተኞች በኩል የደረሰንን “የእንደራደር” ጥያቄ ንቅናቄያችን በዋናነት ያየው ወያኔ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም እየሞከረ መሆኑን ነው።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘው ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በሰላማዊ መንገድ በሚደረግ ትግልና በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረጉ ዉይይቶች ቢመጣ የግንቦት 7 ምርጫ መሆኑን ንቅናቄያችን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። ግንቦት 7ን ሁለገብ ትግል ውስጥ እንዲገባ ያስገደደው የወያኔ እምቢተኝነትና እብሪት ብቻ ነው።

የግንቦት 7 ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰሞኑ የወያኔ የእንደራደር መልዕክት እንደደረሰው በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ባጠቃላይ እንጂ ግንቦት 7ን ብቻ የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነ ከድምዳሜ ላይ ደርሷል። ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ከሚያደርገው ትግልና እየከፈለ ካለው መስዕዋትነት ጋር በቀጥታ ግንኙነት አለው። በመሆኑም፤ ለቀረበልን ጥያቄ ግልጽ መልስና፤ ድርድር ስለሚባለው ጉዳይም ያለንን አቋም ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከተው የኢትዮጵያ ሕዝብና የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ ለማቅረብ የሚያስችል ተጨማሪ አጋጣሚ አድርገን ወስደነዋል። በዚህም መሠረት ለቀረበልን ጥያቄ የሰጠነዉን መልስና አቋማችንን በድርጅታችን ድረ ገጽ ላይና በሌሎች መገናኛ ብዙሀን በኩል በይፋ ለመግለጽ ወስነናል።

በድርድር ስለሚመጣ ለውጥ ያለን የመርህ አመለካከት:

ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንዳደረግነው ድርጅታችን ከምሥረታው ጀምሮ የትግል ስልቱን ሲወስን እምነቱ አድርጎ የተነሳው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በሀገራችን በሰላማዊ መንገድና በድርድር ቢመጣ በእጅጉ የሚፈልገውና የሚመኘው መሆኑን ነው:: ድርጅታችንን ወደ ሁለንተናዊ ትግል የገፋው በመግቢያው ላይ እንደገለጽነው የወያኔ እብሪት ብቻ ነው:: የቀረበልን ምርጫ በባርነትና በውርደት መኖር ወይም ለነፃነት እየታገልን መሞት ቢሆን ኖሮ ንቅናቄያችን የሚመረጠው ምን ግዜም ለነፃነትና ለአገር አንድነት ታግሎ በክብር መሞት መሆኑን በተደጋጋሚ ለሕዝብ ግልጽ አድርገናል። ይህ የማይናወጥ አቋማችን ደግሞ ለይምሰል የተቀመጠ አቋም ሳይሆን ከልባችን የምናምንበትና ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አባላቶቻችንን ያሰባሰብንበት አቋም ነው። ዛሬ በትግሉ ግንባር የምንንቀሳቀሰውና ወደ ግባችን የሚወስደንን ተጨባጭ እርምጃዎች እየወሰድን ያለነውም በዚሁ አቋማችን ዙሪያ ነዉ።

ይህ አቋማችንና እምነታችን በአንድ ላይ ጎን ለጎን የሚሄዱ ሁለት መርሆችን አጣምሮ የያዘ ነዉ። አንደኛው፣ ሂደትን በሚመለከት ሁሌም ለድርድር ክፍት መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ፣ ይህ የድርድር ሂደት እንዲያው ለለበጣ የሚደረግ ሳይሆን ወደሚፈለገው ነጻነት በአነስተኛ መስዕዋትነት ሊያደርስ ይችል ከሆነ በሩን ላለመዝጋት እንጂ፣ በምንም አይነት ዋና ውጤቱን፤ ማለትም ኢትዮጵያን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሀገር ማድረግን፤ የሚቀይር ወይንም ከዚያ ያነሰ ውጤትን ለመቀበል መፍቀድን ፈጽሞ የማያመለክት መሆኑን ነው::

በእኛ በኩል ድርድሩን አስፈላጊና ጠቃሚ የሚያደርጉት መነሻ የፖለቲካ እሳቤዎችም ከእነኝሁ ሁለት መንታ ገጽታዎች የሚመነጩ ናቸው:: በድርድር ለሚገኝ ፍትሀዊና እውነተኛ ውጤት ክፍት መሆናችንን ሁሌም እናሳያለን፤ ነገር ግን ይህን የምናደርገው የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባትን ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚጠይቀውን ማንኛውንም መስዋዕትነት መከፈል አለበት የሚለውን መሠረታዊ የአካሄድ መርህ በመመርኮዝ እንጂ መርሀችንን ለድርድር ለማቅረብ እንዳልሆነ በግልጽ መታወቅ ይኖርበታል::

ስለዚህም:

ሀ) የድርድሩ ውጤት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ያረጋገጠ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በአስቸኳይ እውን ማድረግ መሆን ይኖርበታል:: ይህ ዋናው ግብ ሆኖ ከዚህ በመለስ የሚኖሩ በሂደት የሚገኙ አነስተኛ ግቦች ሊኖሩ ይችላሉ (ለምሳሌ የፖለቲካ እስረኞች ማስፈታት…ወዘተ):: ሆኖም በምንም አይነት ለእነኝህ መለስተኛ ግቦች ተብሎ ዋናውን ግብ የሚያሳጣ ወይንም ጊዜውን ያላግባብ የሚያስረዝም ድርድር፣ ድርድር ነው ብሎ ድርጅታችን አይቀበልም። ስለዚህም ዋናው የድርጅታችን ዓላማና ግብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ፣ በፍጹም ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም:: በሥልጣን ላይ ባለው ኃይል በኩል ወደዚህ ግብ ለመድረስ ቁርጠኝነቱ በሌለበት ሁኔታ በሚደረግ ማንኛውም አይነት ድርድር ውስጥ ግንቦት 7 አይሳተፍም::

ለ) በግንቦት 7 እምነት ማንኛውም ድርድር ወያኔ ከግንቦት 7 ጋር በተናጠል የሚያደረገው ሳይሆን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሁሉንም የፖለቲካ ኃይሎች ያካተተ መሆን ይኖርበታል:: ድርጅቶችን በተናጠል እየለያዩ “እንደራደር” ማለት በራሱ ጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ስሌትን የያዘ እሳቤ እንጂ፣ በዘላቂነት አገሪቱን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ አገር ለማድረግ መፈለግን አያመለክትም:: ለአንድ ድርጅት ለብቻው የሚመጣ ወይም የሚጠቅም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የለም:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመፍጠር ፍላጎት ያለው ድርድር በአገሪቱ ያሉትን የተለያዩ የፖለቲካም ሆነ የሲቪክ ኃይሎችን ያካተተና ያመኑበት መሆን ይኖርበታል:: የሚደረገው ድርድርም ማን በስልጣን ላይ ይውጣ ወይንም የፖለቲካ ስልጣንን ባሉት ኃይሎች መሀከል እንዴት እናከፋፍለው የሚል የስልጣን ቅርምት ድርድር ሳይሆን፤ ሕጋዊና የሕዝቡን የሥልጣን ሉዓላዊነት ባረጋገጠ ሁኔታ የፖለቲካ ስልጣን እንዴት እንደሚያዝ ፍትሀዊ የሆነ ሂደትን ለማስጀመር የሚደረግ ድርድር መሆን አለበት::

ሐ) ቀደም ብለን እንደጠቀስነው ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አንድን ድርጅት ወይንም የፖለቲካ ድርጅቶችን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ነው:: ይህ እስከሆነ ድረስ እንዲህ አይነት ድርድር ከሕዝቡ በተደበቀ ሁኔታ በሚስጥር የሚካሄድበት ምንም ምክንያት የለም::

2) ከዚህ በፊት ከወያኔ ጋር ከተደረጉ ድርድሮች ያገኘናቸው ተመክሮዎችና ከዚህ በመነሳት ወደፊት በሚደረጉ ምንም አይነት ድርድሮች እንዳይደገሙ ለመጠበቂያ የሚሆኑ ከአሁኑ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች

ከማንኛውም ወገን ጋር የሚደረግ ድርድር የተደራዳሪዎቹ ምንነት፤ ውስጣዊ ባህርያቸውን፤ ከተለምዶ ተግባራቸው ያላቸውን ተአማኒነትና ወደዚህኛው ድርድር ያመጣቸውን ምክንያቶች በበቂ ከመገንዘብ ጋር ተያይዞ የሚታይ ጉዳይ ነው:: ቃሉን አክባሪና ተዓማኒ ከሆነ ሰው ጋር የሚደረግ ድርድርና ያለፈው ታሪኩ ምንም አይነት የተዓማኒነት ባህርይ ከማያሳይ ቡድን ጋር የሚደረግ ድርድርም ሆነ ለድርድሩ የሚደረግ ዝግጅት ለየቅል ናቸው:: ይህ ማለት ግን ተዓማኒነት ካለው ኃይል ጋር ብቻ ነው ድርድር የሚካሄደው ማለት አይደለም:: በፍጹም ተዓማኒ ካልሆነ ኃይል ጋር የሚደረግ ማንኛውም ድርድር ግን ድርድሩ በእርግጥም ተግባራዊ ሊሆን የሚችል መሆኑን የሚያሳዩ ጠንካራ መጠበቂያዎች (System of Verification) እንዲሁም ግልጽ የመተግበሪያ ሥርዓቶች (Implementation Mechanism) ሲደረጉለት ብቻ ነው ከምር ሊወሰድ የሚችለው:: ከዚህም ባሻገር ግን መጀመሪያውኑ ወደ ድርድር የሚመጣው ለጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ሳይሆን በእዉነተኛ መንፈስ ከድርድር የሚመጣውን ውጤት በመፈለግ መሆኑን የሚያሳዩ “የመተማመኛ” ምልክቶች ሲያሳይ ነው በእርግጥም ወደ ድርድር የመጣው ከልቡ ድርድሩንና ከድርድሩ የሚመጣዉን ዉጤት ፈልጎ መሆኑን ለማመን የሚያስችለው::

ወያኔ ከተቀናቃኝ ወገኖች ጋር “ድርድር” ሲያደርግ የመጀመሪያ ጊዜዉ አይደለም:: እኛ እስከምናውቀው ድረስ ምናልባት በኃይል ይበልጡኛል ብሎ ከሚያምናቸው ወገኖች ጋር ካልሆነ በስተቀር፣ በረሃ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ በማንኛውም ጊዜ ለቃሉ ታማኝ፤ ለመርሁ እውነተኛ፤ ለደረሰበት ስምምነት ተገዢ ሆኖ አያውቅም:: ይልቁንም ሶስተኛ አደራዳሪ ወገኖችን በሚያሸማቅቅና በሚያሳፍር መልኩ ውሸትን እንደ አዋቂነት፤ ማጭበርበርን እንደ ብልጠት፤ የተስማማበትን በገሀድ ማፍረስን እንደ የአመራር ብልሀት አድርጎ የሚያይ፤ ምንም እፍረትና ጨዋነት የሚባል ነገር ያልፈጠረበት እኩይ ኃይል ነው:: ከራሱ የድርጅት ጥቅምና በስልጣን ከሚገኝ የዝርፊያ ሀብት ማካበት ባሻገር፤ ለአገር ዘላቂ ጥቅም ብሎ የራሱን ጥቅም አሳልፎ የሚወስደው ምንም እርምጃ እንደሌለ በተግባር በተደጋጋሚ ያረጋገጠልን ኃይል ነው:: በግንቦት 7 ውስጥ ያለን ወገኖች ይህንን የወያኔ ባህርይ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ ሌሎች ጽፈውት ያነበብነው ሳይሆን፣ እራሳችን በተግባር በተሳትፈንበት ሂደት ያገኘነው ጥልቅ ግንዛቤ ነው:: ይህንን ደግሞ በአንድ አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን ከድርጅቱ ታሪክ ጋር የተጣበቀ፤ በአመራር አባላቱ ላይ እንደ ግል ባህርይ የሰረጸ መሆኑን እስክንገነዘብ ድረስ በተደጋጋሚ የተመለከትነው ነው:: ስለዚህም ከዚህ ኃይል በኩል የሚመጣን የ “እንደራደር” ጥያቄ ከዚህ በፊት እንዳደረገው ለገባበት የፖለቲካ ውጥረት ማስተንፈሻ፣ ለውሸት ፕሮፓጋንዳው መጠቀሚያ፤ ለጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ መሰብሰቢያ፤ የዴሞክራሲ ታጋዮችን ትጥቅ ማስፈቺያና ወኔ መስለቢያ አድርጎ እንዲጠቀምበት በፍጹም አንፈቅድለትም:: ስለዚህም ከላይ በመርህ ደረጃ ከጠቀስናቸው ሶስት ጉዳዮች በተጨማሪ ምንም ዓይነት ድርድር ከመደረጉ በፊት ወያኔ ጉዳዩን ከምር የወሰደው መሆኑን የሚያሳዩ “የመተማመኛ” እርምጃዎች መውሰድ አለበት ብለን እናምናለን::

እነኝህም፣

ሀ) ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች፤ ጋዜጠኞች፤ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት:: ይህ ደግሞ በግልጽ የሚታወቁ እስረኞችን ብቻ ሳይሆን በድብቅ የተቋቋሙ ማጎሪያና ማሰቃያ ቤቶች ያሉትን ሁሉ ማጠቃለል አለበት።

ለ) በሕዝብ በተለይ በተቃዎሚ ኃይሎች ላይ ወያኔ በየቀኑ እያካሄደ ያለውን ወከባና እንግልት ባስቸኳይ ማቆም፣ ሰብዓዊና የዜግነት መብታቸውን ማክበር አለበት።

ሐ) በፖለቲካ ምክንያት ከዚህ በፊት የተወሰዱ ሁሉም ዓይነት ፍርድ ተብዮ ውሳኔዎች እንዲሻሩ ማድረግ፤ በሂደት ላይ ያሉ ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ምንም አይነት ክሶችን ማቋረጥ አለበት።

መ) ሕዝብን በፍርሃትና በስጋት ለማቆየት ሆነ ተብለው የወጡ አፋኝ ህጎችን በአስቸኳይ ማንሳት አለበት።

ሠ) ማንኛውም ድርድር ገለልተኛ የሆኑ ሶስተኛ ወገኖች ባሉበት፤ የድርድሩ ሂደት በምስልና በድምጽ ተቀርጾ በገለልተኛ ወገኖች እጅ ብቻ የሚቀመጥ፣ የድርድሩ ቦታም የተደራዳሪ ወገኖች በጋራ በሚስማሙበት ቦታ መሆኑን መቀበልና ይህንንም በግልጽ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ አለበት።

እነኝህ ከላይ ያስቀመጥናቸው በወያኔ በኩል የሚወሰዱ “የመተማመኛ” እርምጃዎች ለተቃዋሚዎች ተብሎ የሚወሰዱ እርምጃዎች አይደሉም:: ወያኔ እነዚህን እርምጃዎች ለመውሰድ ቁርጠኝነት ሳይኖረው ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት የሚደረግ ድርድር ላይ ከምር ይሳተፋል ብለን ማመን በፍጹም ስለማንችል ነው ::

እስከዚያው ድረስ ግን ግንቦት 7ም ሆነ ሌሎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት በቁርጠኝነት የምንታገል ኃይሎች፣ ወያኔ እነኝህን የመተማመኛ እርምጃዎች እስኪወስድና ቀደም ብለው በተቀመጡት መርሆች መሠረት በሚደረግ ድርድር በተግባር ሊመነዘር የሚችል ስምምነት፣ አልፎም ለምንም አይነት ማጭበርበርና መንሸራተት እድል የማይሰጥ ጠንካራ መጠበቂያዎች መኖራቸው እስኪረጋገጥ ድረስ፣ የጀመርነውን ትግል ይበልጥ አጠናክረን የምንገፋበት እንጂ በምንም አይነት ለአንድ አፍታም ቢሆን በድርድር ስም የማንዘናጋ መሆኑን አበክረን እናስታውቃለን::

የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ፣

ኅዳር 23፣ 2006 ዓ:ም
http://www.ginbot7.org/2013/12/02/%E1%8 … %E1%89%80/

ህዳር ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እንደገለጹት ኢህአዴግ የእንደራደር ጥያቄውን በሁሉት ወር ጊዜ ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ ማቅረቡ ነው። ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ኢሳት ላቀረበው ጥያቄ በሰጠው የጽሁፍ መልስ “የእንደራደር” ጥያቄ እንደቀረበለት አምኖ፣ “ይሁን እንጅ ንቅናቄው በዋናነት  ወያኔ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም” ያደረገው ነው ብሎአል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘውም …

ህዳር ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሂውማን ራይትስ ወች ባወጣው መግለጫ የሳውዲ የጸጥታ ሀይሎችና የሳውዲ ዜጎች በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የሀይል እርምጃ በመውስድ ጉዳት አድርሰዋል። በኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ላይ ለተፈጸመው ጥቃት የሳውድ አረቢያ መንግስት አስፈላጊውን  ምርመራ በማድረግ በአጥፊዎቹ ላይ ተገቢውን እርምጃ ሊወስድ ይገባል ያለው ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በቶሎ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ …

የዚህ ቀን በዓ/ዓቀፍ ደረጃ ታስቦ መዋሉ በተመድ መግለጫ መሰረት ከሰው ልጅ ታሪካፍ ፈተናዎች ኣንዱ የነበረው የባርያ ንግድ የተወገደበትን ኣሉታዊ ኣሻራ ለማስታወስ እና ከዚሁ ጎን ለጎን ዘመናዊ ባርነት እየተባሉ የሚታወቁትን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ለመታገል ነው። ታህሳስ 2 ይላል ዛሬ የ ተመድ ዋ/ጸኃፊ ኮፊ ኣናንን ጠቅሶ የወጣው የድርጅቱ

ከአፍሪቃ ሕብረት-እስከ አረብ ሊግ፥ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እስከ አዉሮጳ ሕብረት የሚገኙ አሐጉራዊ፥ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶች ያወደሱ፥ ያደነቁ፥የሚደግፉ፥ የሚረዱት መንግሥት ሹማምንታት ግን ከቀማዎቻቸዉ ብዙ የተለዩ አይመስሉም።

ከስዑዲ ዐረቢያ የሚመለሱ ኢትዮጵያውያን፣ መንግሥት መልካም አቀባበል እያደረገላቸው ነው ቢባልም፤ ካለው የኑሮ ውድነት አንጻር፣ ሥራ የማግኘቱ ነገር ትስፋ ሰጪ አይመስልም አሉ።

እንደመግቢያ፤ የፋና ነገር 1. ፋና፤ ኢትዮጵያዊ ካናዳዊት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፡፡ እሱዋ እንደምትለው ከሆነ ፖለቲካ አትወድም፡፡ በአባይ ቦንድ ሽያጭና በመሰል የመንግስት መርሀ ግብር ዝግጅቶች ላይ ግን ቀድማ የምትገኝ ጎበዝ ነች፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች መፈክር ይዘው በኢህአዴግ ላይ ሲሰለፉ ስትመለከት ግን ደምዋ ይፈላል፡፡ ሰሞኑን በዚህ በሳኡዲአረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ግፍ ስላሳዘናት፤ ሳውዲዎችን ልክ ልካቸውን ልትነግራቸው […]

ሣምንታት ወዲህ በተለይ የኢትዮጵያን የወያኔ መንግሥት በሚቃወሙ የሚዲያ ማዕከላት ዘንድ ዋና መነጋገሪያ ሆኖ የሚገኘው በሳዑዲ የኢትዮጵያውያን መንገላታትና መሰቃየት እንዲሁም ከኢሰብኣዊነትም በወረደ ሁኔታ በግፍ መጨፍጨፍ ነው፡፡ ዜጎቻችን በአካፑልኮ ቤይ የመዝናኛ ሥፍራ ሲንሸራሸሩ ከርመው የመጡ ይመስል ይህ ምስል በኢትዮጵያው የወያኔ ሚዲያ በአስደሳች መልክ እየቀረበ ቢሆንም ትክክለኛውን መረጃ ከአማራጭ የዜና ምንጮች እንደወረደ እንደምንከታተለው ከሆነ ግን ከሀገርና ከሕዝብ ኅልውና […]

ፈታኙን ወቅት ለማለፍ … የሳውዲ የምህረት አዋጅ አልቆ በሪያድ መንፉሃ ላይ አለምን ያሳዘነ ሰቆቃ ተፈጸመ …ስጋት ነግሶ ፣ ኑሮ ከብዶን ጨንቆን ጠቦን ከርመናል ! በዚህ ክፉ ቀን ወገን ወገኑን ለመርዳት ደፋ ቀና በማለቱ ረገድ የሃገሬ ልጅ ከጫፍ እስከ ጫፍ በቁጭት ስሜት ሲንቀሳቀስ የፖለቲካው ትኩሳት ወላፈን እያጓተተን አልሰነበትንም አይባልም። ግልጥልጥ አድርግን እናውራ ካልን የኑሮ ውድነት እና […]

የእፎይታ ጊዜው የኮሚቴዎቻችንን የፍርድ ቤት ውጤት ተምርኩዞ እንደሚያበቃ ድምፃችን ይሰማ አስታወቀ::

መንግስት በኮሚቴዎቻችን ላይ የጥፋተኝነት ብይን የሚሰጥ ከሆነ የእፎይታ ጊዜው እንደሚያበቃ እና በአዲስ ጉልበት ሰላማዊ ተቃውሞው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ድምፃችን ይሰማ አስታወቀ፡፡

ሙሉውን መግለጫ ከዚህ በታችን እንደሚከተለው ይቀርባል፡

ከዒደል ፊጥር አስቀድሞ የታወጀው የእፎይታ ግዜ ማብቂያ ከኮሚቴዎቻችን የፍርድ ሂደት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ይኖረዋል፡፡ በርካታ መስዋእትነት በከፈልንበት ሰላማዊ ትግላችን ውስጥ ኮሚቴዎቻችንን ነፃ ማውጣት አንዱ ጥያቄያችን መሆኑም ይታወቃል፡፡

ህዝበ ሙስሊሙ ደጋግሞ እንደገለፀው ለዚህ ጥያቄው መሪዎቻችንን በነፃ ከማሰናበት ውጪ ምንም አይነት መልስ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ መሪዎቻችንን በቀጠሮ ዳግም ማጉላላት ወይም በሃሰት ተመስርቶ መፍረድ በእፎይታ ጊዜው ርዝመት እና ከዚያ በኋላ በሚኖረው ትግላችን ጥልቀት ላይ ግልፅ ተፅእኖ ይኖረዋል፡፡ ይህ ማለት ግን ከእፎይታ ጊዜው በኋላ ለሚኖረን ረጅም ጉዞ የመንግስትን እግር እየተከታተልን መሪዎቻችንን በመያዣነት እንዲጠቀምባቸው እንፈቅዳለን ማለት አይደለም፡፡

በእፎይታ ጊዜው ሰላማዊ ትግላችን በሚገባ ተገምግሟል፡፡ ብዙሃኑ የተሳተፈበት የቀጣይ አቅጣጫ ቀረፃ እና የአካሄድ ስልትም ተነድፏል፡፡ በዚህ ረገድ የእፎይታ ጊዜው ለተገቢው ስልታዊ ጥቅም ውሏል፡፡ በዚህ ወቅት የተከናወኑ አበይት ተግባራት በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚገለፁ ይሆናሉ፡፡ ቀጣይ አቅጣጫችን እና የትግል ስልታችን የእፎይታ ጊዜው ማብቂያ እስከሚታወጅ ድረስ ይፋ ባይሆንም በነዚህ ጊዜያት መንግስት እየመረጠ ያለው አካሄድ የህዝቡም አቅጣጫ ምን ሊሆን እንደሚችል ፍንጭ የሚሰጥ ነው፡፡

በቀሪው ጊዜ የመሪዎቻችን የፍርድ ሂደት እንደመጨረሻ ግብአት ተወስዶ የእፎይታ ጊዜው ማብቂያ እና የቀጣዩ ጉዞ ጅማሬ ይሆናል፡፡ የመሪዎቻችን የፍርድ ሂደት ላነሳናቸው ጥያቄዎች መፍትሄ የማፈላለጉ ሂደት ቀጣይ ጉዞ ወይም በጥያቄዎቻችን መልስ ማጣት ማግስት የሚጠነሰሰው ሌላው ትግል መጀመሪያ ይሆናል፡፡

ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የግለሰቦች ጥርቅም እስከሆኑ ድረስ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ጽንፈኛ፣ አሸባሪ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ ተላላኪ፣ ኒዮ ሌንራል፣…….የሚባሉት መለጠፊያዎች እየተሰጧቸው አሳራቸውን የሚበሉት ‹‹ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ናቸው፡፡

ምንም ያህል ልዩነት ቢኖረው የአንድን አገር ህዝብ የማይለወጠው የጋራ ማንነቱ ዜግነቱ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከሌሎች ህዝቦች ይልቅ የሚያመሳስሉን፣ የምንጋራቸው በርካታ እሴቶች አሉን፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያውይነታችን (ዜግነታች) የጋራችን ነው፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰብ፣ ህዝብ ተብሎ በጅምላ ዜግነት ሊሰጠው አይችልም፡፡ አንድ ሰው ኢትዮጵያዊ ለመሆን መደራጀት አይጠበቅበትም፡፡
በሚሊዮን የሚቆጠሩ ግለሰብ ኦሮምኛ ተናጋሪዎችን ‹‹ኦሮሞ››፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን ግለሰብ አማርኛ ተናጋሪዎች ‹‹አማራ››፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ግለሰብ ሶማልኛ ተናጋሪዎን ‹‹ሶማሊ››…….እያሉ ነው ኢትዮጵያውያንን ‹‹ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› በሚል አዲስ ማምነት የሚደረድሩን፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰብ፣ ህዝብ የሚባለው ከግለሰቦች እንጅ ከምንም የመጣ አይደለም፡፡ የብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበር ካለበት መጀመሪያ መቅደም የሚገባው የስሪታቸው የግለሰቡ መብት ነው፡፡
‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ትግሬ….› እየተባሉ የተቦደኑት ህዝቦች አንድ አይነት አይደሉም፡፡ እንዲያውም ኦሮምኛ ተናጋሪው ‹‹ኦሮሞ›› ከሚባለው ውጭ ከአማርኛ ተናጋሪው ጋር የሚጋራው በርካታ ማንነቶች ይኖሩታል፡፡ አማርኛ ተናጋሪው ‹‹አማራ›› ከተባለው ይልቅ ከኦሮምኛ ተናጋሪው ጋር የሚያመሳስሉት በርካታ ማንነቶች ይኖሩታል፡፡ ለአብነት ያህል ትግርኛ፣ አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ሶማሊኛ፣ ….ተናጋሪው ህዝብ ከቋንቋውም በላይ አንዱ የሌላውን ድንበር ተሸግሮ ከሌላኛው ቋንቋ ተናጋሪ ጋር በእምነት፣ በፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ሌሎች ገመዶች ይገናኛል፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የአንድ ብሄር ሰዎች አይደሉም፡፡ የሙስሊሙ እንቅስቃሴ እንዲህ እስካሁን በጥንካሬ የዘለቀው በድንበር ተሸጋሪው ማንነቱ እንጅ በጠባብ ‹‹የብሄር›› ማንነት ታጥሮ አይደለም፡፡ ኦርቶዶክሶቹ፣ ፕሮቴስታንቶቹ፣ ካቶሊኮቹ በ‹‹ብሄር›› የታጠሩ አይደሉም፡፡
የአንድ ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› የእምነት፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ…መብቱ በግለሰብ ደረጃ ካልተጠበቀለት በስተቀር የ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ…›› መብት ሊጠበቅ አይችልም፡፡ ችግሩ የ‹‹ብሄርና›› ሌሎች ማንነቶችን የሚጠቀሙ የፖለቲካ ቡድኖች ከግለሰብ ማንነት ይልቅ ጥቅል ማንነትን የሚያስቀድሙት ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ መሆኑ ነው፡፡ በ‹‹ኦሮሞ፣ አማራ፣ ትግሬ፣ሶማሊ…….›› ስም በጅምላ ከመነገድ ያለፈ ስለ እያንዳንዱ ህዝብ አያስጨንቀቃቸውም፡፡ 30 ወይንም 40 ሚሊዮን የአንድ ‹‹ብሄር›› ህዝብ በአንድ ጉዳይ ሊከፋ አይችልም፡፡ ቢያንስ ከገዥዎች ጋር ሆኖ የሚጠቀም አይጠፋም፡፡
ከፊሉን በእምነቱ፣ ከፊሉን በኢኮኖሚው፣ ከፊሉን እናከብርልሃለን በሚሉት ቋንቋው፣ ከፊሉን በነጻነቱ…. እያሉ ግን ሁሉንም ይጨቁኑታል፡፡ ሁሉንም ይጎዱታል፡፡ መስፈርቱ በብሄር ሳይሆን በግለሰብ ቢሆን ግን የሚድበሰበስ ነገር አይኖርም፡፡ ሁሉም የግለሰብ መብቶች እስከተከበሩ ድረስ የአገሪቱ ህዝብ መብት ይከበራል፡፡ የግለሰብ መብት ካልተከበረ ግን የማንም መብት ሊከበር አይችልም፡፡ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የግለሰቦች ጥርቅም እስከሆኑ ድረስ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ግንቦት ሰባት፣ ጽንፈኛ፣ አሸባሪ፣ ኪራይ ሰብሳቢ፣ ተላላኪ፣ ኒዮ ሌንራል፣…….የሚባሉት መለጠፊያዎች እየተሰጧቸው አሳራቸውን የሚበሉት ‹‹ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች›› ናቸው፡፡
Getachew Shiferaw

Image

ጥሪው የማህጸን ነበር። ምላሹም የዕትብት ሃዲድነት ነበር።

ጤና ይስጥልኝ ሞገደኛው ተክሌ እንደምን ሰነበትክ? ደህና ነህ ወይ? የብዕር አጣጣልህ እንደ አቤ ቶኬቻው ውብ ስለሆነ ለረጅም ጊዜ እያደንኩ አነባለሁ። ጠረባህንም አክሎ። በጠረባህ ዙሪያ አንድ ቀን የምለው ይኖረኛል …. ዛሬ ግን ልታገሰው ስላልቻልኩት ማለት ፈለግኩ ….. በሦስት ነገሮች ዙሪያ …. እንዲህም እላለሁ …. እኔው ….

ሳውዲ አረብያ ላይ ለደረሰው ውርደት ተጠያቂው አረሙ ወያኔ ነው። የወያኔ ፖሊሲ ነው ለዚህ የትውልድ ፍልሰት በይፋ የፈቀደው። ሙጃው ወያኔ የተመሰረተበት ይህ ነውና። እኛ ጊዜ እዬጠበቀ ወያኔ በሚያፈነዳው ፈንጅ ዙሪያ ጥቃቱን ለመመከት ዕለታዊ ሰልፍ ስለምነደርግ ነው እንጂ የወያኔ መሰረታዊ ፍጥረት ትውልድን ከማፍለስ ላይ በመሆኑ መርዙ የማይነካውና የማያካተው አንዳችም ነገር የለም። ይህ የጥፋት አዟሪት የሚነሳው ኢትዮን ቅኝ ለማደረግ ህልማቸው ካልተሳከ ሀገሮች ምኞት ነው። ስለሆነም ዒላማችን ሊነሳ የሚገባው ከጥንስሱ መሰረት ላይ መሆን አለበት እላለሁ እኔ። ይህን መሰረት ያያዘ የኢትዮጵያዊነት የጥላቻ ፖሊሲ ከሥሩ ለመንቀል ደግሞ ከበቀለበት ማንፌስቶ ነው የትግሉ ወላፈን መነሳት ያለበት የሚል ጠንካራ አድምታ ነው ያለኝ በግሌ። መዳህኒቱም የወያኔ ማንፌስቶ ግብዕተ – መሬት ሲፈጸም ብቻ ነው። የፈውሱ ፍሬ ነገር ከሃርነት ትግራይ ህልፈት ላይ ነው። እያንዳንዱን የወያኔ የጥፋት ሆነ የቅጣት የበቀል እርምጃ በሥርዓት በተጠና ሁኔታ ቢመረመር ቢተነተን – ቢነበብ – ቢፈታታሽ ድርጀቱ ከተፈጠረበት እንቁላል አስኳል ውስጥ ይመነጫል።

ለማንኛውም በሳውዲ ላይ የተሰነዘረብን የጥቃት እርምጃ ለመቃወም እልፎችን ያስቆጣው ሰላማዊ ሰልፎች ወያኔ ኢትዮጵዊነትን የቀማበት ወይንም የነጠቀበት አልነበረም። በጭራሽ።“ኢትዮጵያዊያንን ለማስተባበርና ሳኡዲዎችን ለመጀንጀን የምናቁዋቁመውን ኮሚቴ መለየት ያለብን ይመስለኛል፡፡ሰልፎቹንግንተቀምተናል፡፡ ከልጅ ተክሌ ጹሑፍ የተወሰደ”

ልጅ ተክሌ …. ምን አልባት አንተ በላህበት ሀገር ሆኖ ከሆነ ከተጠያቂዎቹ ውስጡ አንዱ ትሆናለህ። ከማንም በተሻለ ተደማጭነቱም፤ ተቀባይነቱም አለህና! ሁልጊዜ አንተ ታንከባላለህ ድክመቶችን ወደ ሌሎች። …. አንተ እኮ ምርጥ፤ ልዑቅ ከሚባሉ ኢትዮጵውያን ውስጥ አንዱ ነህ። የፖለቲካ ተንታኝ …. በታኝ፤ ጋዜጠኛ፤ አክቲቢስት፤ ሃያሲ፤ የምትፈልገውን ጽፈህ ተከብረህ የሚወጣለህ፤ ያልታገድክ፤ ገድብ ያልተሰረባህ፤ አንቱ የተባልክ ሚሊዮኖች በምታገኘው መድረክ ሁሉ በአክብሮት የሚያዳምጡህ ዕድለኛ ወጣት ነህ …. እና ካናዳ ላይ ወያኔ ኢትዮጵያዊነት ለመቀማት መድረክ ሲያገኝ አንተ የት ነበርክ? ምንስ ትሰራለህ? ….. እራስህን ጠይቅ።

እኔ ሲዊዘርላንድ ነው የምኖረው። ሰላማዊ ሰልፉን ማን እንደጠራው አላወቅም። ከኢሳት ሰምቼ ነበር የሄድኩት። እንዲህ ዓይነት ሰላማዊ ሰልፍ ሲዊዘርላንድ ውስጥ አላዬሁም። እጅግ በጣም ብዙ ሰው ነበር። ቁጭቱ፤ እልሁ፤ እንባው፤ መቃጠሉና መንደዱ … የነጠረው ሰንደቅዓላማ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ካለምንም ቅይጥ በነፍስ ወከፍ ተይዞ ነበር …. እኔ በሰዓቱ እጠረት ነድጃለሁ። ምክንያቱም እዛው ባድርም አልጠግብኩትም ነበርና። ወንድምዓለም ጊዜው ከኖረህ እንዲህ ሰርቸዋለሁ አዳምጠው www.lora.ch.tsegaye ዬ 21.11.2013 ወይንም … በዚህኛው ሊንክም ይቻላል ….

…. ይገርማል። ለመሆኑ ለዛውም ውጭ ሀገር ወያኔ በምን ሞራሉና አቅሙ ነው እኛነታችን፤ ማንነታችን፤ ውስጣችን የመቀማት አቅሙስ ሞራሉስ የሚኖረው። ወንድሜ ሆይ! በአባይ ቦንድ ምን ያህል አረሙ ወያኔ እንዴት እንደ ተራገፈ አላዬህንም? አይታሰብም! ተዎው እኛን ወያኔ ከመጠበት ዘመን ጀምሮ የተወለዱት አዲስ ፈርጦች እኮ ናቸው የኢትዮጵያዊነት መሪና አደራጅ የሆኑት። ይህ ከድንቅ በላይ ነው። ኢትዮጵያዊነት እኮ ገና በሥነ – ምርምር ብዙ የፈካ ተግባር ከፊት ለፊቱ የሚጠብቀው የሰማይ ጥበብ ነው። ተቀማን? አፈርኩልህ ስለቃሉ ….. አኔ የብዕርህ ፍቅረኛ። ጥሎብኝ ደግሞ ድምጽህንም እወደዋለሁ።

ሳውዲ ላይ ለዛውም የውጭ ዜጋ በሳውዲ መሬት ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሲደርግ እኮ ሰማዕት ኢትዮጵያውያኑ የመጀመርያ ናቸው። በማይቻልበት ቦታ ችለው ግን የተሰውበት የተጋድሎ ልዩ ታሪክ …..። የበቀል አምላክ እንደሚበቀለው የሳውዲን መንግስት ቀን ይናገራል …. አምላካችን እንደ ቻይነቱ ቁጡ ነውና።

ሰላማዊ ሰልፉ በመላ ዓለም የኢትዮጵውያን የአትንኩን አኅታዊ ድምጽ … ደመ – ነፍሱን ወያኔን ያራጋፈ፤ ያደናበረ፤ ከእንቅልፉ የቀሰቀሰው፤ ያተራመሰው፤ ከእንሰሳነት፤ ከአራዊትንት አስተሳሰቡ ተግ ብሎ ሰው ስለመሆኑ እራሱን እንዲጠይቅ ያፋጠጠበት፤ ወያኔ ከዛቀጠበት አርንቋ ለመውጣት እፍ ግብ ያለበት በፍጹም ሁኔታ የተዋረደበትና ማንነቱ ያጋለጠበት ነበር ማለት ይቻላል። እውነቱን ልንገረህ ትናንት የተቋቋመው ሰማያዊ ፓርቲ ከወያኔ አስተዳደራዊ ተቋም በላቀ ሁኔታ ዕውቅና ያገኘበት። ኢትዮጵያዊነት የወያኔን የ40 ዓመት ሴራ አክሽፎ የተሞሸረበት – የተመሳጠረበት ታላቅ አብነታዊ የኢትዮጵውያን የወል የጥሪት ውጤት ነበር። ካፒታላችን ቅርሳችን ነው ለዛሬ። ለነገ ደግሞ ትውፊታችን …..

ሌላው አንተ እንዳትቀማ በራስህ ላይ ማተኮር እንዳለብህ የሚያመለክት ነገርም ከጹሑፍ አዬሁ …. እንዳላዬሁ ሆኜ ላላፈው አልፈለግሁም። ምን? ምን አልክ ወንድምዓለም …. „„…የበለጠ የሚያሳስበው ደግሞ፤ ከዚህ ከሳኡዲ ችግር ጋር በተያያዘ ያቁዋቁዋምነው አለማቀፍ ኮሚቴም፤ አስር ሀያ አመት ከምናደርግበት የትግል ስልት ብዙ ፈቀቅ ያለ አይመስልም፡፡ የኮሚቴው ሙሉ ዝርዝር ባይኖረኝም፤ የሶስቱ ሰዎች ስም እንደሚያሳየው ከሆነ፤ ኮሚቴው ዘመኑን ያልዋጀ፤ የአንድ ብሄር ስብስብ ነው የሚመስለው፡፡ ስብስቡ አለማቀፍም አገርአቀፍም ደረጃውን እንዲጠብቅ አልተደረገም፡፡ “ …. „ብንቀበለውም ባንቀበለውም፤ በአደባባይ እንደዚያ ብለን ባናውጅም፤ ይሄንን የሳኡዲን ግፍ ለማለስለስና ለማስቀልበስ የምናቋቁማቸው ተቁዋማትና ስብስቦችም ሁኑ ሌሎች መሰል ፖለቲካዊና ሲቪክ ማህበራቶቻችን፤ በተዘዋዋሪ ይሄንን የሀይማኖትና የብሄር ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገቡ መሆን አለባቸው፡፡ ከልጅ ተክሌ ጹሑፍ የተወሰደ” ዬት የት እዬተጓዝክ ነው እናትዬ …. አዬህው በወያኔ የጎጥ ፖሊሲ ምን ያህል እንደ ሰመጥክ፤ እዬተጠቃህም እንደሆነ …. እጅም እንደ ሰጠህ። „እናስተውል“ ይላሉ አባቶቻችን …. እኔ ስለተደራጀው ግብረኃይል እራሱ በነፍሱ ስላለ የሚለውን ይበል ….

ነገር ግን እንደ አንተ ዓይነት ወንድም ግን በብሄረሰብ ስብጥር ላይ ማተኮሩ በጣም መውረድ ነው። ይህ የሚመችህና የሚደላህ ከሆነ ከቶ ስለምን ተሰደደክ? አልገባኝም። የእኔ እናት ጎሰኝነት፤ መንደርተኝነት እኮ ኋላቀርነት ነው። ኋላቀርንት በኢኮኖሚያዊ ስሌቱ ያልተመጣጠነ እድገት ማለት ነው። በአስተሳሰብ ስሌት ስንሄድም ያው ያልተመጣጠነ እድገት ነው …. በ21ኛው ምዕተ ዓመት ከቤተሰብ ቀጥሎ ካላው ጎሳ ላይ መቆም ምን ሊሉት ይቻላል ከኋላቀርነት ውጪ

እባክህ እያንዳንዱን ነገር በዚህ ዝርዝርና ምንዛሬ አታሰባጠረው …. ከዚህ መጠራቅቅ መውጣት አለብህ። አዎና! በአንድ ወቅት አንድ ቅዱስ አባታችን ከዚህዓለም ስደት ላይ እንዳሉ ሲያርፉ ዬእምነት ልዩነት ሳይኖር ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቀብር ሥርዓቱ ላይ መገኘቱ ብቻ ሳይሆን ስሜቱን አድንቀህ ተከታታይ ጹሑፎች በኢትዮ ዛሬ ላይ አስነብበህን ነበር። ያን ጊዜ ስትጽፍ ጎሰም አድርገህ የጻፍካት ነበረች። ሊቀ ሊቃውንቱን ብታገኛቸውና ልምዳቸውን ቢያካፍሉህ ግን ሸንቆጥ አድርገህ ያለፍካት ነገር „ላም ባለወለበት መሆኑን ትረዳ በነበረ“ ለማንኛውም ሁላችንም ….. በዚህ ስሌት ከተጓዝን …. ምን አልባት ያን የፍቅር ቤት ደርመሾቹ እኛው ሆነን እናርፋለን። የወያኔን የተጠያቂነት ጠቀረማ ዘመንም የመሸከም ግዴታ ሊኖርብን ነው። በዚህ የፋደሰ መንገድ ከተጓዝን። ከወያኔም እንሻል ቢያንስ እኛ …. በስተቀር ግን ዛሬም ጭቃ ነገም ረግረግ …. መዛገጥ … መዝገጥም – ኪሳራ መከዘን ይሆናል ዕጣ ፈንታችን።

ሌላው ያነሳህው …. እንዲህ ላሉ ድንገተኛ ችግሮች ቋሚ አካላት አለመኖራቸው …. እንዳሳዘንህም ጽፈኃል። አንተ እንዲህ ያለ የቀደመ ሃሳብ ከነበርህ ባለህበት ሀገር ማቋቋም ትችል ነበር አኮ። ማን ጌታ አለብህ። አቅሙ እንዳለህም አስባለሁ። በሌላው ድርጅት ላይ ካለይሉኝታ የምትሰንዝራቸው ወቀሳዎች እዳይደገሙ ጥርት ያለ ብቁ ተቋም። ከስህተት የጸዳ፤ ምርጥ ዘር የሚያፈራ፤ ፍጽምና ሸማው የሆነ ድርጀት የማቋቋም ሙሉ መብት ነበረህ። አለህም። እንዲህ በዬጊዜው እርር ድብን ከምትል …. ልጅ ተክሌ የአንተ ጹሑፍ አምልጦኝ አያውቅም፤ ቃለ ምልልሶችህም ከሌላ ድርጀቶች ጋር አንተ የደረካቸውም ሆነ አንተም በኢሳት ባለህ ቦታ …. ከሌሎች ጋር ያደረከውም …..

እኔ እንደማስበው ወያኔ ብዙ ቢፈታታነውም የኢትዮጵያ ሰብዕዊ መብት አስከባሪ ጉባኤ በፕሮፌሰር መስፍን ይመራ የነበረው፤ እስረኞችን ለመታደግ ውጭ ሀገር የተቋቋመው፤ የአዲሱቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ፤ ሌሎቹም … በተጨማሪም በኢሳትም ሰብዕዊ መብት በሚመለከት ራሱን ያቻለ መመሪያ መኖሩ …. ጅምሩ መልካም ነው። በዬጊዜው እስር ቤት የሚማቅቁት ጋዜጠኞች፤ ከዚህም ባለፍ ሥምና ዝና የማይፈልጉ፤ ድምጻቸውን አጥፈተው ከዬሀገሮችም ሆነ በድንበር ዘለልም ከዓለም ዓቀፍ የሰብዕዊ መብት ድርጅቶች ጋር የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን እንዳሉም አውቃለሁ። ይደክማሉ። ይሰራሉ።

እኔ በምኖርበት ሲዊዘርላንድ የሰብዕዊ መብት ረገጣ በኢትዮጵያ የቆረቆራቸው ወጣቶች ሶሎቶርን በሚባል ከተማ በ2010 የመሰረቱት አንድ ግብረኃይል አለ። ጥቅምት 12/2012 አቶ ኦባንግ ሜቶ ከአዲሲቱ ኢትዮጵያ የክብር እንግዳ የነበሩበት፤ ከግንቦት 7 ዶር. ታደሰ ብሩ፤ አቶ ወንድምአገኝ ጋሹ ከኢሳት በተገኙበት በዙሪክ የተሳካ ህዝባዊ ስብሰባ

አካሄዶም አይቻለሁ። ስብሰባው ጥሩ መንፈስ ነበረው። ሃሳቦች በሚገባ ተንሸራሽረዋል። ከጀርመን ሙንሽን የመጡ ወገኖችም ነበሩ። …

…. እኔ እንደ አንተ ሃያሲ ስለሆንኩ ከልብ የተደሰትኩበት ስብሰባ ነበር … ማለት እችላለሁ። ያው አልጻፍኩትም። ልመናው ሆነ ድጅ ጥናቱ ገደለኝ። በዬድህረ ገፆች አውጡልኝ በማለት መንከራተት እንጂ …. ያን የመሰለ የወጣቶች ጥረት ወሼኔ ተብሎ በተፃፈለት ነበር። በሌላ የሚዲያ ሽፋን ማግኘቱን ባላውቅም …. እኔ ግን በጸጋዬ ራዲዮ ፕሮግራሜ በዜና ሰርቸዋለሁ ….. ከዚህ ጋር በተያዬዘ መልኩ በሰብዕዊ መብት ዙሪያ ጠንከር ያሉ ተግባራት በሲዊዲንም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ እንዳለ ይሰማኛል።

…. በተጨማሪ በዬሀገሩ የሚስማሙ፤ የሚግባቡ፤ የሚደማመጡ ሰዎች የራሳቸውን የግልና የወል ጥረት እንደሚያደርጉም አስባለሁ። ሌላው ቀደም ባላው ጊዜ አዲስ ድምጽና የሲዊዲን እንዲሁም ሌሎች የነፃነት ትግሉ ቤተኛ የሆኑ የኮሚኒቲ ራዲዮኖች ሆነ ማህበራዊ ድሀረ ገፆች በርካታ ተግባራትን ከውነዋል በዚህ ዙሪያ ። እንዲሁም የኢትዮጵውያን የመወያያ ሩሞች የራሳቸውን ሁለገብ ተግባር ሲከውኑ ቆይተዋል። የትኛው የአፍሪካ ሀገር ነው እንደ ኢትዮጵውያን በሀገሩ ጉዳይ ትርጉም ያለው ተግባር ውጭ ሀገር የሚከውነው። እውነት ለመናገር ተጽፎ አያልቅም ….

ልጅ ተክሌ … ችግራችን ከቁጥር በላይ ነው። በሁሉም ቦታ ሁሉም ሊሆን ስላማይቻል ክፍት ቦታ እዬፈለጉ ቀዳዳ መሸፈን የእኔም የአንተም ግዴታ ነው። ሲናሪዮ ሆነ ፕሮቶኮል የማይጠይቁ ብዙ የተግባር መስኮች አሉና። ሌላው ግን እኛም ስደተኞች ነን። ብዙ መከራና ፈተና በግል ህይወታችን እዬፈተለን ነው። ይህም ሆኖ ውጪ ያለነው ኢትዮጵውያን ሁሉንም ሆነናል በአቅማችን ልክ። ከነድክመቶቻችን ለበርካታ ነገሮች በባለቤትነት ስሜት የምንችለውንም አድርገናል እያደረግነም ነው።

ስለሆነም በማናቸው ጊዜ በድንገተኛ የእናት ሀገር የእማ ጥሪ፤ ጠሪም ተጠሪም ወቃሽም ተወቃሽም የለም። ሊኖርም አይገባም። መወቀስ ካለብን ሁላችን። መመስገን ካለብን ደግሞ ሁላችን። ቁስሉም ህምሙም ስቃዩም እኩል ነው። በእናት ሀገር የችግር ቀን የድረሱልኝ ጥሪ አንዱ የክት ሌላው የዘወትር፤ አንዱ ልጅ ሌላው የእንጀራ ልጅ ሊሆን አይችልም …. ከወያኔ በስተቀር …. ወያኔ ይህን ለማጥፋታ 40 ዓመት ቢሰራበትም ንጉሥ ዳዊት በወጣትነቱ ማህልዬን፤ በጎልማሰነቱ ምሳሌን በእርጅና ዘመኑ ደግሞ ሁሉም ኖሮት ዓለምን ፈትሾና አይቶና መርምሮ ከመንፈስ ቅዱስ በተሰጠው መክሊት ከንቱነትን አመሳጠረ …. በሳውዲ የኢትዮጵያዊነት መከራ የወያኔን ከንቱነት ያነበበ፤ የተረጎመና ያመሳጠረ ነበር ዓይንም ህሊናም የለውም እንጂ …. ሙጃው ወያኔ።

እናሳርገው …. በወሳኝ ጉዳይ። …. አንድ ነገር ኢህድግ …. የሚባል ኑሮ ያውቃልን? ከዚህ የወያኔ ሸንኮፍ ተጠቂነትም መውጣት ያለብን ይመስለኛል። የልጅ ተክሌ ጹሑፍ ለወያኔ የጥፋት ሴራ ዕውቅና የሰጠ መሰለኝ። ሀገር ትውልድ ታሪክ ባህል እምነት ያጠፋ ወያኔ ነው። መነሻው መድረሻውም ተልዕኮውም በመሆኑ …. ቅርጽ ነው ኢህድግ ይዘቱ TPLF ነው ትናንትም ዛሬም …. በሌለ ነገር ላይ ምስክርነት …. መስጠት —- ትዝብት ነው … ይበቃኝ። ጨረስኩ።

እኔ እኔ ነኝ የምለው፤ እኔ በእኔ ውስጥ ሳይሾልክ እኔን ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው።

እኔ እኔ ነኝ የምለውም የጠላቴ ዒላማ ተጠቂ አለመሆኔን በፍጹም ሁኔታ በእኔ ውስጥ ሳረጋግጥ ብቻ ይሆናል።

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

Image
ሥርጉተ ሥላሴ


ሰዎችን ለማድነቅ የምንጠቀምበት ቃል ‹ወንድ› ወይም ‹ወንዳታ› በሆነበት ማኅበረሰባዊ አስተሳሰብ የምትደነቅ ሴት ማብቀል ይከብዳል፡፡ የምትደነቅ ሴት ብትበቅል እንኳ የማኅበረሰቡ ውጤት ነው ማለት አይቻልም ባይ ነኝ፤ የግል ጥረቷ ውጤት ነው የምትሆነው!
ቋንቋ፣ አባባሎች እንዲሁም ተረትና ምሳሌዎች ማኅበረሰቡ አባላቱን የሚያሳድግበትን (nurture የሚያደርግበትን) መንገድ ያሳብቃሉ፡፡ ያልዘራነውን አናጭድም፤ ስለዚህ አጋጣሚውን ተጠቅመን ከቃላት አጠቃቀማችን ጀምሮ ራሳችንን መገምገም መጀመር ሊኖርብን ነው፡፡

ለመሆኑ የአማርኛ ተረትና ምሳሌዎቻችን ስለሴት ምን ይላሉ?
  1. ሴት ሲበዛ ጎመን ጠነዛ
  2. ሴትና ዶሮ ዱር ከሄዱ ቤታቸውን ይክዳሉ
  3. ሴት ከወንድ፣ እህል ከሆድ
  4. ሴት ለቤት፣ ወፍጮ ለዱቄት
  5. ሴትና መሬት የማይችሉት የለም
  6. ሴት ማገዶ ሲቸግራት ምሰሶ ትነቅላለች
  7. ሴት በማጀት፣ ወንድ በችሎት
  8. ሴት በጳጳስ፣ ኳደሬ በንጉስ
  9. ሴት ብታውቅ፣ በወንድ ያልቅ
  10. ሴት ሲያፏጩላት፣ ያረሱላት ይመስላታል
  11. ሴት አማት የመረዘው፣ ኮሶ ያነዘዘው
  12. ሴት አግብተው ሴት ቢወልዱ፣ የት አለ ንግዱ
  13. ሴት ከጠላች፣ በቅሎ ከበላች አመል አወጣች
  14. ሴት ካልወለደች ቋንጣ አትጠብስም
  15. ሴት ያመነ ጉም የዘገነ
  16. ሴት ያመጣው ጠብ አይበርድም
  17. ሴት ይወዷል ማጀት ያንጎዳጉዷል
  18. ሴትና ቄስ ቀስ
  19. ሴትና በቅሎ እንደገሪዋ ነው
  20. ሴትና አህያ ዱላ ይወዳል
  21. ሴትና ድመት ወደ ሞቀበት
  22. ሴትና ድስት ወደ ማጀት
  23. ሴትና ዶሮ ሳያብድ አይውልም
  24. ሴትና ፈረስ እንደኩሬ ውሀ እያደር ማነስ
  25. ሴትና ፈረስ የሰጡትን ይቀምስ
  26. ነፍስ በፈጣሪዋ፣ ሴት ባሳዳሪዋ
  27. ወጭትና ሴት ሲከናነቡ ይሻላል
  28. ወንድ ልጅ ለፈረስ ሴት ልጅ ለበርኖስ
  29. የመንገድ ዳር እሸት ባል የሌላት ሴት
  30. ዝናብ ካልጣለ ሁሉ ቤት፣ እንግዳ ካልመጣ ሁሉ ሴት

ተረትና ምሳሌ፤ የእምነት-እውነት
ተረትና ምሳሌዎች እንደባሕላዊ እሴት ወይም ብልሐት (wisdom) የተለመደ ነው፡፡ በሙግት ለመርታት ብዙ ተረት መቻል በቂ ሊሆን ይችላል፡፡ እነዚህ ተረትና ምሳሌዎች፣ ልክ እንደሌሎቹ ሁሉ የተገነቡት በተጠራቀመ የማኅበረሰብ የእምነት-እውነታላይ ነው፡፡ አሁን፣ አሁን ከከተማ እየተመናመኑ ቢሆንም በብዙኃኑ ገጠሬ እና ጥቂት በማይባሉ ከተሜዎችም ውስጥ ስር የሰደደ እምነት የተጣለባቸው አፍራሽ ተረቶች ናቸው፡፡ ደግነቱ፣ ተረት በተጠራቀመ ዕውቀት ተረትም፣ በተረት ይተካል፡፡
ለተረትና ምሳሌዎቻችን ትንሽ ጥብቅና ለመቆም ያክል፣ እጅግ በጣም ጥቂት ቢሆኑም በሴቶች ዙሪያ ገንቢ የሆኑ ተረትና ምሳሌዎችም አሉን፡፡ እንደምሳሌ ‹‹ሴትና ጭስ መውጫ አያጣም›› የሚለውን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይህንኑ ይዘው ይመስለኛል ብዙዎች ‹‹ሴት አይደለሽ እንዴ መላ አምጪ እንጂ!›› የሚሉት፡፡ ተረትና ምሳሌዎች በጊዜ ብዛት በሰዎች ልቦና ውስጥ የእምነት-እውነትየመፍጠር አቅም አላቸው፡፡

ማርክ ትዌይን ‹The Awful German Language› ባሰኘው ጽሑፉ ‹‹በስርዓተ ጾታ ጉዳይ እንደጀርመኖች አዳላጭ ቃል የለም›› ይልና እንደምሳሌ በጀርመን ቋንቋ ዛፍ ወንድ ይሆንና ቅርንጫፎቹ ግን በሴት ይጠራሉ ይላል (ገጽ 16)፡፡ ማርክ ትዌይን ይህንን ያለው እኛን ስለማያውቀን ነው እንጂ አማርኛን ቢያውቅ ኖሮ ቢያንስ ለጀርመኖች ተፎካካሪ ያደርገን ነበር፡፡ በአማርኛችን ግዙፍ፣ ጠንካራ ነገሮች ጾታቸው ‹ወንድ› ነው፤ ትንናሽና እና ደካማ ግዑዝ ነገሮች ግን ‹አንቺ› እያልን ነው የምንጠራቸው፤ ምናልባት ከጀርመኖቹ የምንለየው ጾታ-አልባ ስያሜ ስለሌለን ብቻ ነው፡፡ ‹‹የአበበ ቤት ትልቅ ነው፣›› ወይም ‹‹የአበበ ቤት ትንሽ ነች፣›› እንላለን እንጂ አናገላብጠውም፡፡ እዚህጋ በተገላቢጦሽ ይባል፣ አይባል የሚል መውጫ የሌለው ሙግት ውስጥ መግባት አልፈልግም፡፡ ነገር ግን አባባሉ የተፈጠረው ከምን ዓይነት ማኅበራዊ እሳቤ ነው የሚለውን አውቀን እንግባበት ነው የምለው፡፡

ምንሊክሳልሳዊ-በሰራዊቱ ውስጥ የተነሳውን ሕገመንግስታዊ ጥያቄ ተከትሎ የቀድሞ የኢሕዴን እና የኦሕዴድ ባለስልጣናት ከመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ እንደሚቀነሱ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቁመዋል:: በየቀኑ ለስብሰባ የሚቀመጠው ሕወሓት መራሹ የጄኔራል መኮንኖች የአንድ ብሄር ቡድን ተጠንቷል ባለው እና የተወያየበት ሰነድ እንደሚያመለክተው በሰራዊቱ ውስጥ የሚነሱ ማንኛቸውም ጥያቄዎች የሚፈጠሩት ከአማራው እና ከኦሮሞው ወገን ከሆኑት መኮንኖች ሲሆን ይህንንም የሚመሩት የውስጥ መዥገር የሆኑት የብኣዴን እና የኦሕዴድ መኮንኖች ስለሆኑ ከሰራዊት ውስጥ በመቀነስ በተለያዩ መንገዶች በወንጀል ለማጥመድ እና ከነማን ጋር እንደሚገናኙ አስፈላጊውን የደህንነት ክትትል ማድረግ ይገባል ሲል ተነጋግሮበታል::

እነዚሁ የለውጥ ጥያቄ ያነሱት የሰራዊቱ መኮንኖች ከተለያዩ የታጠቁ የጠላት ሃይሎች እና የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር በመገናኘት የመንግስትን ህልውና እየተፈታተኑት ከመሆኑም ባሻገር የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ከቀድሞ ስርኣት የተወረሱ እና ለዲሞክራሲው እና ለልማቱ እንቅፋት ስለሆነ አስቸኳይ እርምጃ ሊወሰድ ይገባል ተብሏል::ከግንቦት ሰባት እና ከተቃዋሚ ዲያስፖራዎች ጋር በመገናኘት በሰራዊቱ ውስጥ ያለነበሩ እና ሊከሰቱ ይችላሉ ተብለው የማይገመቱ አፍራሽ እንቅስቃሴዎች በመፍጠር ለሃገሪቱ የሚጠቅሙ ሰዎችን በማስኮብለል መረጃ በማቀበል እንዲሁም አለመተማመን እንዲኖር በመስራት ከፍተኛ ደንቃራ ሆነዋል::

የውስጥ አዋቂ ምንጮቹ እንደገለጹት የቀረበው ሰነድ ለጄኔራል መኮንኖቹ ያልተበተነ ሲሆን የስብሰባው መሪ የሆኑት ኢታማጆር ሹሙ እጅ በመሆን ሰነዱ እየተነበበ የተወያዩበት እና ይህም የሚያመለክተ በሕወሓት ጀኔራሎች መካከልም መተማመን አለመኖሩን ያሳያል ብለዋል::በሙስና ከአስተዳደርዊ ባለስልጣናት በበለጠ የተዘፈቁት የሕወሓት ጄኔራሎች በስብሰባ እና አብዛኛው ንብረቶቻቸን በተዘዋዋሪ በመሸጥ ስራ ላይ እየተንቀሳቀሱ ሲገኝ በሱዳን በኢምሬት እና በአውሮፓ አገሮች እንዲሁም በአሜሪካ በቤተሰቦቻቸው ስም የተለያዩ ንብረቶችን በመግዛት ላይ መሆናቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮሽ ጨምረው ገልጼዋል::

ኢትዮጵያ በሳውዲ ካለ ይኖሩ የነበሩ ከ50,000 የሚበልጡ ዜጎችዋን ወደ ሀገራቸው መመለስዋን በያዝነዉ ሳምንት መጀመርያ ማስታወቁ ይታወቃል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ችግር ያጋጠማቸውን ዜጎቹን የመመለሱን ተግባር ሲጀምር ቁጥራቸው 10,000 ይሆናል ብሎ ገምቶ ነበር።

Image

ምርጫ 97ን ተከትሎ የአውሮፓ ኅብረትን የምርጫ ታዛቢ ቡድንን የመሩት አና ጐሜዝ ምርጫውን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ በኢትዮጵያ መንግሥትና በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ላይ የሰላ ትችትና ወቀሳ በመሰንዘር ይታወቃሉ፡፡

ከዘጠኝ ዓመታት ቆይታ በኋላ በ26ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያን፣ ፓስፊክ እና የአውሮፓ ኅብረት የጋራ የፓርላማ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ የመጡትን አና ጐሜዝን በዴሞክራሲ፣ በእስረኞች አያያዝ፣ በሰብአዊ መብት አጠባበቅ እንዲሁም በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ነአምን አሸናፊ አነጋግሯቸዋል፡፡

ሪፖርተር፡- ምርጫ 97ን ተከትሎ በእርስዎና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል ያለው ግንኙነት ጥሩ የማይባል ነው፡፡ በዚህ የተነሳ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ያቀረቡት የቪዛ ጥያቄ እንዴት ነበር? ቪዛ መስጠት ያለመፈለግ አልያም ሌላ ነገር አጋጥሞዎታል?

አና ጐሜዝ፡- በፍጹም፡፡ ምንም ዓይነት ክልከላ ወይም እምቢታ አላስተናገድኩም፡፡ ለነገሩ የአውሮፓ ኅብረት የሰብአዊ መብተት ንኡስ ኮሚቴ ባለፈው ሐምሌ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ነበር፡፡ በዚያን ወቅት በአውሮፓ ኅብረት የኢትዮጵያ አምባሳደር እኔም መሄድ እፈልግ እንደሆን ጥያቄ አቀረበልኝ፡፡ እኔም መሄድ ብፈልግም ባልፈልግም ቪዛ አትሰጡኝ ምን ያደርጋል አልኩት፡፡ እርሱ ግን የለም እንሰጥሻለን አለኝ፡፡ እሺ ለአሁን የሥራ ባልደረቦቼ ይጓዙ የእኔ ጊዜው ሲደርስ አመለክታለሁ አልኩ፡፡ ስለዚህ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የአፍሪካ ፓስፊክ ካሪቢያንና የአውሮፓ ኅብረት ጥምር ስብሰባ ላይ ለመካፈል የቪዛ ጥያቄ አቀረብኩ፤ እነርሱም ያለምንም ቅድመ ሁኔታና ያለምንም ችግር ቪዛውን ሰጥተውኛል፡፡ በዚህም በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር በማለፋቸው የተለየ የፖለቲካ አተያይ እየተፈጠረ እንደሆነ የሚያሳይ ነገር ነው፡፡ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ለውጥ ለማምጣት ጥረት እያደረጉ እንደሆነም ተረድቻለሁ፡፡ በተለይ ሙስናን በመዋጋት የጀመሩት ዕርምጃ ከፍተኛ የሥርዓቱን ባለሥልጣናት ሳይቀር ወደ እስር ቤት አስገብዋል፡፡ ይህም መልካም ጅምር ነው፡፡

ነገር ግን በኢትዮጵያ ከፍ ያለ ለውጥ ማየት እሻለሁ፡፡ ይህ የእኔ ብቻ ፍላጐት አይደለም፣ የኢትዮጵያውያንም ጭምር እንጂ፡፡ እዚህ በመምጣቴ ከስብሰባው ጐን ለጐን ሌሎች ሰዎችን በማናገር ለውጡ በእንዴት ያለ ሒደት ላይ እንዳለ ለመመልከትም እሞክራለሁ፡፡

ሪፖርተር፡- የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድንን በመምራት በ1997 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ውስጥ ስለነበሩ የአገሪቱን የምርጫ የዲሞክራሲና ሰብአዊ መብትንና የመሳሰሉ ጉዳዮችን ያውቋቸዋል፡፡ አገሪቱ አሁን ያለችበትን ሁኔታ እንዴት ይገመግሙታል?

አና ጐሜዝ፡- እንደሚመስለኝ ድኅረ ምርጫ 97 በኢትዮጵያ ያለው ዲሞክራሲያዊ ምህዳር ጠቧል፡፡ ከምርጫ 97 በፊት ከነበረበት ገጽታ አንፃር ብሶበታል፡፡ ምርጫውን ተከትሎ እልቂቶችን አይተናል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሲታሠሩ አይተናል፣ ለሲቪል ማኅበራት ምህዳሩ ሲጠብ አይተናል፡፡ እንደሚመስለኝ በበጐ አድራጐት ማኅበራት ላይ የወጣው ሕግ አሉታዊ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ አላግባብ ጥቅም ላይ ሲውል አስተውለናል፡፡ ሕጉ እጅግ የተለጠጠ ትርጓሜ እየተሰጠው የተለየ ሐሳብ ያላቸውንና የሚቃወሙ ግለሰቦችን ለማጥቃት አገልግሎት ላይ ለማዋል እየሞከረ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ የተነሳ ሁኔታው የባሰበት ነው፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ምርጫ 2002 በቀዘቀዘ ሁኔታ ተከናውኖ አልፏል፡፡ የሥራ ባልደረባዬ ቴስ በርማን ምርጫውን ለመታዘብ በአውሮፓ ኅብረት ተወክሎ ነበር፡፡ ምርጫው መቀዛቀዙን ገልጿል፡፡ ምክንያቱም በምርጫ 97 ኅብረተሰቡ በስፋት ከመሳተፉ በተጨማሪ በምርጫው ለውጥ ይመጣል የሚል ተስፋ ነበረው፡፡ ይህ ተስፋውም እስከ ድምፅ ቆጠራው ድረስ የዘለቀ ነበር፡፡ ነገር ግን ሕዝቡም ሆነ እኔ ምርጫው መጭበርበሩን ተረድተናል፡፡ ስለዚህ በምርጫ 2002 ኅብረተሰቡ በአብዛኛው ወደ ምርጫ አልሄደም፡፡ እኩለ ቀን ላይ ሁሉም ነገር የተጠናቀቀበት የምርጫ ጣቢያዎች ነበሩ፡፡

የአውሮፓ ኅብረትን የወከለው ቴስ በርማን የምርጫውን ሪፖርት ለማቅረብ እንኳን ወደ አዲስ አበባ መመለስ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ሪፖርቱ ሒስን የያዘ ስለሚሆን ነው፡፡ ሒሱ ግን ገንቢ ነው፡፡ ቢሆንም ግን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ይህን ከልብ የመነጨና ቀና ሒስ መቀበል አልፈለጉም፡፡

እንደሚመስለኝ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ካለፉ በኋላ ነገሮች በሚገርም ሁኔታ ተለውጠዋል፤ የሚለወጡም ይመስለኛል፡፡ ይህም የመነጨው አመራሩ በመለወጡ ነው፡፡ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ለውጥ ለማምጣት እየሠሩ ይመስለኛል፡፡ ነገሮች ተጠናክረው እንዲጓዙ እንፈልጋለን፡፡ በፀረ ሙስና ላይ የተጀመረው ትግል፣ የዲሞክራሲያዊ ምህዳሮች መስፋፋት፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብቶች እንዲስፋፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንዲጠናከሩ፣ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ማየትን እንሻለን፡፡

እርግጥ ነው በተደጋጋሚ በመንግሥት በኩል የሚነገር መከራከሪያ አለ፡፡ ይህም እነዚህ ግለሰቦች የታሰሩት ጋዜጠኞች በመሆናቸው ሳይሆን በሽብርተኝነት ወንጀል ነው ይላል፡፡ እኔ ግን ይህን አልቀበለውም፡፡ ምክንያቱም አሁን አሁን ሽብርተኝነት የሚለው ሐሳብ የተለየ ሐሳብ ያላቸውን ግለሰቦችም ሆነ ቡድኖች ዝም ለማሰኘት እያዋሉት ነው፡፡

ከአሁን በፊት በአገሬ የነበረው አምባገነን መንግሥት ይጠቀምበት የነበረው ቃል አመፀኛ የሚል ነበር፤ አሁን ግን ቃሉ ሽብርተኛ ሆኗል፡፡ እንደሰማሁት እነዚህ ሽብርተኛ የተባሉ ግለሰቦች ያለፉበት የፍትሕ ሥርዓቱ ፍትሐዊ አልነበረም፡፡ ግለሰቦቹ የሽብር እንቅስቃሴን ማድረጋቸው የሚያስረዳ በቂ መረጃ አልቀረበም፡፡ ለኢትዮጵያ ለውጥ እንዲመጣ ጥሪ ማስተላለፍ ፈጽሞ የሽብር ተግባር ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ የትኛውም ዲሞክራሲ ሊጠብቀው የሚገባ እውነተኛ የዲሞክራሲ መገለጫ ነው፡፡

ሪፖርተር፡- ድኅረ ምርጫ 97 ኢትዮጵያን አሁን ካለው የኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር እንዴት ያነጻጽሩታል?

አና ጐሜዝ፡- አዲስ አበባ የቆየሁት ከመጋቢት ጀምሮ እስከ ምርጫው ድረስ እንደሆነ ማስታወስ ጥሩ ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ጥቂት ተስፋ ሰጪ ነገሮች ነበሩ፡፡ መንግሥት በተወሰነ መልኩ የፖለቲካ ምህዳሩን ክፍት ለማድረግ ይሞክር ነበር፡፡ ከሁሉም በላይ ግን የብዙኃኑን ሐሳብ ተቆጣጥሮት የነበረው ለአምስት ጊዜያት በቀጥታ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተላለፈው የፓርቲዎችን ክርክር ነው፡፡ ይህ ክርክር የሕዝቡን ሐሳብ ተቆጣጥሮት የነበረ ሲሆን፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ያንን በመፍቀዳቸው እንደ ተጸጸቱ እገምታለሁ፡፡ ምክንያቱም ኅብረተሰቡ አማራጮችን በአግባቡ የተረዳበት ክርክር ነበርና፡፡

ድኅረ ምርጫ የተፈጠረውን ሁኔታም አስታውሳለሁ፣ በምርጫው ዕለት ምሽት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያለምንም በቂ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጁ፡፡ ይህም ምን ያህል እንደ ተሸበሩ የሚያሳይ ነበር፡፡ ምርጫው በአጠቃላይ በሰላምና በሥርዓት ተካሂዷል ብሎ የሚያምን ከሆነ እንዲህ ያለ ውሳኔ ለምን አስፈለገ? ለምን ሕዝቡን አያማክሩም ነበር፡፡ ምክንያቱ ግልጽ ነው፣ ምርጫውን ለማጭበርበር በመታሰቡ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ መሠረት አሁን ያለውን የኢትዮጵያ ሁኔታ የማወዳድረው ከቅድመ 97 ሁኔታ ጋር ነው፡፡ በዚያን ወቅት ቢያንስ በርካታ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በፓርላማ ውስጥ መቀመጫ ነበራቸው፡፡ አሁን ግን በፓርላማው መቀመጫ ያለው ተቃዋሚ አንድ ብቻ ነው፡፡

እርግጥ ነው አንዳንድ የማውቃቸው ግለሰቦች የሚዲያው ዘርፍ በትንሹም ቢሆን እየተከፈተ እንደሆነ ገልጸውልኛል፡፡ ነገር ግን እየተከፈተ ያለው የሚዲያው ዘርፍ ዋናው ሳይሆን አማራጭ የሆኑት ማኅበራዊ ሚዲያዎች ናቸው፡፡ እርሱም የሚመነጨው ደግሞ ሕዝቦች ከቴክኖሎጂ ጋር ባላቸው ቅርርብም ጭምር ነው፡፡ በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ የቴክኖሎጂ አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡ አሁን ያለውን ቴክኖሎጂ ለማገድ ከአውሮፓም ይሁን ከእስራኤል የምታመጣው ባለሙያ ለመቆጣጠር የሚሆንለት አይሆንም፡፡ በምትቀጥራቸው ባለሙያዎች ፌስቡክንም ሆነ ትዊተርን መቆጣጠር እጅግ አዳጋች ነው የሚሆነው፡፡ በዚህ የተነሳ ባለሥልጣናቱም ወደ እዚያው ለመቅረብ እየሠሩ ይመስለኛል ምክንያቱም መንግሥት ሚዲያውን በሥነ ሥርዓት ካልከፈተው ሕዝቡ የራሱን መንገድ ይፈልጋል፡፡

ሪፖርተር፡- ዲሞክራሲን፣ የሰብአዊ መብት አያያዝን እንዲሁም ስለ እስረኞች ጉዳይ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል?

አና ጐሜዝ፡- አዎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሆኑት አባዱላ ገመዳ ምሳ ጋብዘውኝ ነበር፡፡ ከእርሳቸውም ጋር አቶ ተሾመ ቶጋ ነበሩ [የቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች አፈ ጉባኤ፣ በአሁን ሰዓት በብራሰልስ የኢትዮጵያ አምባሳደር] ከእነዚህ ባለሥልጣናት ጋር በጣም ግልጽ የሆነ ውይይት ከማድረጋችን በተጨማሪ በግልጽ ያሉኝን ጥያቄዎች፣ ቅሬታዎችና ሒሶች ሰንዝሬያለሁ፡፡ ምንም ግለሰባዊ ችግር እንደ ሌለብኝም አስረድቻለሁ፡፡ በግሌ የማገኘው ምንም ዓይነት ኢኮኖሚያዊም ሆነ ሌላ ጥቅም የለኝም፤ ሥራዬን ግን በቁርጠኝነትና በትጋት እሠራለሁ፡፡ ስለዚህም ያየሁትንና የሰማሁትን የመናገር ግዴታ አለብኝ፡፡ በዚህም መሠረት ውይይታችን እጅግ በጣም ግልጽና ገንቢ ነበር ማለት ይቻላል፡፡

ሪፖርተር፡- ከባለሥልጣናቱ ያገኙት መልስ ምን ይመስላል?

አና ጐሜዝ፡- ይህን እንኳን በዝርዝር አልነግርህም፡፡ የውይይታችን አንዱ ጠቀሜታም በግል መያዙ ነው፤ ምክንያቱም ውይይታችን የተካሄደው በግል ስለነበር፡፡ ነገር ግን ላረጋግጥልህ የምፈልገው ነገር ቢኖር ውይይታችን የፖለቲካ ምህዳሩን ስለማስፋት፣ የታሠሩ የፖለቲካ እስረኞችን ስለማስፈታት፣ ለበጐ አድራጐት ማኅበራት ምቹ ሁኔታን ስለመስጠትና ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ማጠናከርና መሰል ጉዳዮች የተዳሰሱበት ከመሆኑም በተጨማሪ ግልጽና ገንቢ ነበር ማለት ይቻላል፡፡

ሪፖርተር፡- ከባለሥልጣናቱ ባገኙት መልስ ረክተዋል?

አና ጐሜዝ፡- እንደሚመስለኝ እኔን ለመስማት መፍቀዳቸውና መወያየታችን አንድ ጥሩ ምልክት አድርጌ እመለከተዋለሁ፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት ጉዳዮች በሙሉ የኢትዮጵያ ጉዳዮችና ሒደቶች ናቸው፡፡ የትኛውም አካል ምንም ዓይነት ተፅዕኖ ማሳደር አይችልም፡፡ ነገር ግን ከእኔ ጋር ለመወያየትና እኔን ለመስማት መፍቀዳቸው እንደ ጥሩ ጐን አድርጌ እመለከተዋለሁ፡፡

ሪፖርተር፡- በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ መንግሥትን ከሚወቅሱበት ጉዳይ አንዱና ዋነኛው የእስረኞች ሁኔታ ነው፡፡ እዚህ በመጡበት ወቅት ወደ ቃሊቲ ተጉዘው እስረኞችን ለመጠየቅ ጥያቄ አቅርበዋል?

አና ጐሜዝ፡- ጥያቄ አቅርቤያለሁ፡፡ ጥያቄዬ ግን በግለሰብ ደረጃ ሳይሆን የጋራ ስብሰባው የፖለቲካ ኮሚቴ ወደ ስፍራው ተጉዞ እስረኞችን እንዲጐበኝ ባለፈው ቅዳሜ ጥያቄ አቅርቤያለሁ፡፡ (ይህ ኢንተርቪው የተካሄደው ሰኞ ዕለት የነበረ ሲሆን ረቡዕ ዕለት በሌዊ ሚሽል የተመራ ቡድን እስረኞችን ጐብኝቷል)

ከእስረኞች ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ በኢትዮጵያ መንግሥት በኩል የሚደመጥ ነገር አለ፡፡ እነዚህ ግለሰቦች የታሰሩት ጋዜጠኛ ወይም ሌላ ስለሆኑ አይደለም፡፡ ይልቅስ አሸባሪ በመሆናቸው ነው የሚለውን አስተሳሰብ የሚጋሩ የአውሮፓ ተወካዮችም እንዳሉ ለመታዘብ ችያለሁ፡፡ እኔ ግን በዚህ አስተያየት ፈጸሞ አልስማማም፡፡ ምክንያቱም የስዊድን ዜግነት ያላቸው ሁለት ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ተከሰው መለቀቃቸው ይታወሳል፡፡ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ በበርካታ ወንጀሎች ክስ ተመሥርቶባትና ተፈርዶባት መፈታቷ ይታወሳል፡፡ የእነዚህ ሰዎች ጉዳይም የተለየ አይደለም፡፡ የታሰሩት ግለሰቦች የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ምልክቶች ናቸው፡፡ የወጣቱ ትውልድ ምልክቶች ናቸው፤ ምናልባትም ያቋቋሙት የፖለቲካ ሥርዓትም የላቸውም፡፡

ሪፖርተር፡- መንግሥት በሽብርተኝነት ነው ያሰርኳቸው የሚለውን የሚያምኑ ከሆነና እነዚህ ሰዎች አሸባሪ አይደሉም ብለው የሚያስቡ ከሆነ የእርስዎን ሐሳብ የሚያጠናክር ምን መረጃ አለዎት?

አና ጐሜዝ፡- ኢትዮጵያ ከሽብርተኝነት ጥቃት ሥጋት ነፃ ነች እያልኩ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያና የአውሮፓ አገሮች ከሽብርተኝነት ጥቃት ሥጋት እንዳለባቸው አምናለሁ፡፡ ነገር ግን በስመ ሽብርተኝነት የዲሞክራሲ ምህዳሩን ማጥበብ፣ የተለየ ሐሳብ ያላቸውንና ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን የሚጠይቁ ግለሰቦችን ፀጥ ማሰኘት፣ ሽብርተኝነትን መታገል አይደለም፡፡ ይህ እንዲያውም ግለሰቦችን በይበልጥ ወደ ሽብር ተግባር እንዲሰማሩ መመልመል ነው፡፡

በኢትዮጵያ ያለውን የሽብር ሥጋት ደረጃ ለማሳነስ እየሞከርኩኝ አይደለም፤ ነገር ግን የታሳሪዎቹን የፍርድ ሒደት የታዘቡ ግለሰቦች እንደነገሩኝ የፍርድ ሒደቱ ፍትሐዊ ካለመሆኑም በተጨማሪ የቀረቡት ማስረጃዎች የግለሰቦቹን የሽብርተኝነት ተግባር የሚያሳዩ አልነበሩም፡፡ ለዚህ ነው እነዚህ ሰዎችን አሸባሪ ብሎ መጥራትን የማልቀበለው፡፡

ሪፖርተር፡- ይህ የሰጡኝ ማብራሪያ ትክክል እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሁነኛ ትንታኔ ሊሰጡኝ ይችላሉ?

አና ጐሜዝ፡- አላውቅም፡፡ እኔ እኮ ታሳሪዎቹን በግል አላውቃቸውም፡፡ ለምሳሌ የብርቱካን ሚደቅሳ ጉዳይን ያነሳህ እንደሆነ በግል እንተዋወቃለን፡፡ እንዲሁም ከብርሃኑ ነጋ ጋር የግል ትውውቅ አለን፡፡ እነዚህ እስረኞች ግን በግሌ አላውቃቸውም፡፡

ሪፖርተር፡- በቅርበት እንደሚያውቋቸው ከገለጹት ግለሰቦች መካከል አንዱ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ናቸው፤ እርሳቸው ያቋቋሙት የፖለቲካ ድርጅት በኢትዮጵያ መንግሥት እንደ አሸባሪ ይቆጠራል፡፡ እሳቸውም ሥርዓቱን ለመለወጥ ከምርጫ የተለየ መንገድ ያስፈልጋል እያሉ ነው፡፡ እርሳቸው አቅጣጫቸውን ይቀይራሉ ብለው አስበው ያውቃሉ?

አና ጐሜዝ፡- ብርሃኑ ነጋን የማውቀው በምርጫ 97 ወቅት ነው፡፡ ቅድም የገለጽኩት በቀጥታ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተላለፈው የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክር የተነሳ በአገር አቀፍ ደረጃ ተቃዋሚ ጐራ ወኪል እንዲሆን አስችሎታል፡፡ በክርክሩ የተነሳ በአገር አቀፍ ደረጃ ተቃዋሚ ጐራውን በመወከል ስሙ የሚነሳ ግለሰብ ቢኖር ብርሃኑ ነጋ ነበር፡፡ እርግጥ ነው በየምርጫ ወረዳቸው የታወቁ ግለሰቦች ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ አቶ ቡልቻ ደመቅሳና ወዘተ፡፡ በነገራችን ላይ ብርሃኑ ነጋ በምርጫ 97 ወቅት ባይታሰር ኖሮ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ይሆን ነበር፡፡ ከእስር እንደተፈታም ወደ ስደት አመራ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች አቅጣጫውን እንዲቀይር ያደረጉት ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም በአገሪቷ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ ሊኖረው የሚችለው ሚና በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሥርዓት በመበላሸቱ የተለወጠ ይመስለኛል፡፡

ሪፖርተር፡- እርስዎ በስፋት የሚታወቁት የኢትዮጵያ መንግሥትንና የአውሮፓ ኅብረትን ከዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፋፋት ጋር ባለባቸው ችግር በተደጋጋሚ ሲወቅሱ ነው፡፡ አሁን በእርስዎ ላይ የተፈጠረ የአቋም ለውጥ አለ?

አና ጐሜዝ፡- ኢትዮጵያን በተመለከተ ከፍተኛ ትችትና ሒስ እሰነዝራለሁ፡፡ አውሮፓ ኅብረት ላይ የምሰነዝረው ሒስ ደግሞ የባሰ ነው፡፡ የአውሮፓ ኅብረትን በተለያዩ ጉዳዮች እተቻለሁ፡፡ በተለይ በኅብረቱና በኢትዮጵያ ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ትችት እሰነዝራለሁ፡፡ ምክንያቱም የአውሮፓ ከፍተኛና ጠንካራ ተፅዕኖ ማሳረፍ ሲችልና በኢትዮጵያ ጉዳይ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣት ሲችል ዝምታን ይመርጣል፡፡ ይህን አይቻለሁ፡፡

አንዳንድ ሰዎች የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲ የተሻለ እንደሆነ ይገልጹልኛል፡፡ እርሱን እጠቀምበታለሁ፤ እንዴት ጥቅም ላይ እንደሚውልም አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ከፍተኛ ጫና የማሳደር ዲፕሎማሲ (ሜጋፎን) መጠቀም ይኖርብናል፡፡

ባልደረባዬ ሊዊ ሚሸል ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ሁለት የስዊድን ዜግነት ያላቸውን ጋዜጠኞችን አስፈትቶ ስለ ኢትዮጵያውያን እስረኞች ጉዳይ አንዳች ሳይሠራ ወደ አውሮፓ በመመለሱ በጣም ተናድጄ ነበር፡፡ በተለይ ለኢትዮጵያውያንና በአጠቃላይ ለአፍሪካውያን የምናስተላልፈው መልዕክት ምንድነው? እኛ የምንጨነቀው ለዜጐቻችን ብቻ ነው፡፡ ይህ ተግባር ተራና ማዳላት ያለበት ነው፡፡

ሪፖርተር፡- በአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ በነበሩበት ወቅት ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ጋር ጥሩ የሚባል ግንኙነት እንደነበሮት ይታወሳል፤ እዚህ ከመጡ ያገኟቸው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች አሉ?

አና ጐሜዝ፡- እስከ አሁን ያገኘሁት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የለም፡፡ ነገር ግን እንደማገኛቸውም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ከዚህ በላይ ግን በኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የትውልድ ችግር አለ፡፡ በግሌ በተቃዋሚ ፓርቲና በውጪ አገሮች ባሉ ኃይላት መካከል ግንኙነት ቢፈጠር መልካም ይመስለኛል፡፡ ይህም ለፖለቲካው ምህዳር መከፈትና ለውይይት መዳበር ጠቃሚ ይመስለኛል፡፡ ይህ ደግሞ እውነተኛ ለሆነ የዲሞክራሲ ግንባታ እጅግ አስፈላጊ ከመሆኑም በላይ መጠላላትን አስወግዶ ወደ ፊት ለመጓዝ ይረዳል፡፡

ሪፖርተር፡- ምርጫ 97ን ተከትሎ ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጋር በተደጋጋሚ ውዝግብ ውስጥ ገብተው ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እንዴት ይገልጿቸዋል?

አና ጐሜዝ፡- ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እስከ ምርጫው ድረስ የነበረኝ ግንኙነት መልካም የሚባል ነበር፡፡ ከእርሳቸው ጋር ግልጽ የሆኑ ብዙ ውይይቶች አካሂደናል፡፡ ተለዋዋጭ ባሕሪ እንዳላቸው ለመታዘብ ችዬ ነበር፡፡ በግንኙነታችን መጀመሪያ አካባቢ አምናቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ቀስ በቀስ ሊያሞኙኝ እየሞከሩ እንደሆነ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ እርሳቸው በጣም ክፉ ነበሩ፡፡ በጣም ክፉ የሆነ አእምሮ የነበራቸው ናቸው፡፡ ብልህ ናቸው ግን ክፉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያን ሔራልድ ጋዜጣ ላይ የጻፉትን የምንጊዜውም ረዥሙን ርእሰ አንቀጽ አልረሳውም፡፡ መጨረሻ ላይ ግለሰባዊ ጥቃት በመሰንዘር ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ገንዘብ ተቀብላለች የሚል ዘመቻ ጀመሩ፡፡ ፈጽሞ ተራ የፈጠራ ውሸት ነው፡፡

እኔ በግሌ ከእርሳቸው ጋር ምንም ዓይነት ችግርም፣ ጸብም ባይኖረኝም እኔን በመክሰስና በመዝለፍ ጉዳዩን ግለሰባዊ አደረጉት፡፡ እርግጥ ነው ያኔ በጣም በጣም ብናደድባቸውም አሁን ግን የሉም፤ ሄደዋል፡፡
reporter amharic

ተክለሚካኤል አበበ (ቶሮንቶ-ካናዳ)

የሳኡዲ ግፍና የኛ ሰልፍ፤

እንደመግቢያ፤ የፋና ነገር

1.         ፋና፤ ኢትዮጵያዊ ካናዳዊት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፡፡ እሱዋ እንደምትለው ከሆነ ፖለቲካ አትወድም፡፡ በአባይ ቦንድ ሽያጭና በመሰል የመንግስት መርሀ ግብር ዝግጅቶች ላይ ግን ቀድማ የምትገኝ ጎበዝ ነች፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች መፈክር ይዘው በኢህአዴግ ላይ ሲሰለፉ ስትመለከት ግን ደምዋ ይፈላል፡፡ ሰሞኑን በዚህ በሳኡዲአረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ግፍ ስላሳዘናት፤ ሳውዲዎችን ልክ ልካቸውን ልትነግራቸው ቆርጣ ተነስታለች፡፡ ስለዚህም በመጪው አርብ መሰል ጉዋደኞችዋን ይዛ ሰልፍ ልትወጣ ተፍ ተፍ ትላለች፡፡ በፋና እምነት በሳኡዲ በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …