ህዳር ፲፫(አስራ ሦስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳዑዲ ዓረቢያ ኢትዮጵያዊያን በአስከፊ ሁኔታ እንዲባረሩ ከተደረገ በኃላ  መንግስት በሳዑዲ ስፖንሰርነት ያጓጓዛቸውን ከ10ሺ በላይ ተመላሾች በካድሬዎች ማሰልጠኛ በሆነው የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በማሳረፍ ባለሃብቶች እንዲረዱዋቸው በመማጸን ላይ ነው። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ለተመላሾቹ ማቋቋሚያ መንግስት 50 ሚሊየን ብር  መመደቡን፣ ገንዘቡ ሊያድግ እንደሚችልና በማቋቋም ረገድ ችግር እንደሌለ …

ህዳር ፲፫(አስራ ሦስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ መስተዳድር ትናንትና ዛሬ በቡራዩ አካባቢ ከ1 ሺ ያላነሱ ቤቶችን ማፍረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል። ነዋሪዎች እንደሚናገሩት መስተዳድሩ ምንም አይነት መጠለያ ሳያዘጋጅ እና ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ እስከ ሙሉ የቤት እቃዎቻቸው ቤቶቻቸውን በድንገት በማፍረሱ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀዋል። አለማየሁ የተባለ አንድ ወጣት የወላጆቹ ቤት ሲፈርስ በማየቱ ስሜቱን መቆጣጠር ተስኖት፣ …

ህዳር ፲፫(አስራ ሦስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዩኒሴፍ ባወጣው ሪፖርት እንደማለከተው ይህን ችግር ለመቅረፍ የኮሚኒቲ አስተባባሪዎች ከፍተኛ  ሚና መጫወት አለባቸው። ኤርትራ ውጭ ላይ መጸዳዳትን በማስቀረት ከፍተኛ ድል ማስመዝገቡዋን ዩኒሴፍ ጠቅሷል። በመላው ኤርትራ ውጤታማ ስራ በመሰራቱ አገሪቱ ውጭ ላይ መጸዳዳትን ያስቆመች አገር የሚል ሰርተፊኬት እንደሚሰጣት ድርጅቱ ገልጿል። በአለም ላይ 34 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች ንጹህ የመጸዳጃ …

ጀርመን እንድትቀበላቸው ያመለከቱ ተገን ጠያቂዎች ማመልከቻቸው ተቀባይነት እስኪያገኝ ረዥም ጊዜ በሚወስድ ሂደት ውስጥ ማለፍ አለባቸው ። ጉዳዩ የሚመለከታቸው የፌደራል ጀርመን የውጭ ዜጎችና የስደተኞች ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረቦች አመልካቾቹን ስለ ሃገራቸው ሁኔታ ና የፖለቲካ ክትትል ይደረግባቸው እንደሆነ ይጠይቋቸዋል ።

እጨጌ ዕንባቆም የመናዊ
ልዩ መርሐ ግብር በደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት(መርካቶ) አዳራሽ

                                 ቀን –  ኅዳር 22 ቀን 2006 ዓም

                                 ሰዓት-  ከቀኑ በ8 ሰዓት


                               የመግቢያ ካርዱን ይውሰዱ


  • ከየመን በ16ኛው መክዘ መጥቶ የደብረ ሊባኖስ አበ ምኔት ስለሆነውና አያሌ መጻሕፍትን ስለደረሰውና ስለተረጎመው እጨጌ ዕንባቆም የመናዊ ልዩ ዝግጅት በተለያዩ ሊቃውንትና ምሁራን ይቀርባል

  • በመርሐ ግብሩ ላይ ለመሳተፍ የመግቢያ ካርዱን 
  • ለም ሆቴል ማትያስ ሕንጻ ከሚገኘው አግዮስ መጻሕፍት መደብር፣ 
  • ከደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት(መርካቶ) ሰንበት ትምህርት ቤት ጽ/ቤት እና 
  • ከማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት ፊት ለፊት ከሚገኙ የመጻሕፍት ማከፋፈያ ሱቆች(የአርከበ ሱቆች) ማግኘት ይችላሉ፡፡
  • አስቀድመው የመግቢያ ካርዱን በመውሰድ አብረን ሊቃውንቱን እናስብ
አዘጋጆች

  • ምክሐ ደናግል ሰንበት ትምህርት ቤትና ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

ሕጋዊ ፈቃድ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ላይ የሚደርሰውን ችግር እና ጥቃት በመቃወም በተለያዩ ሀገራት ሰሞኑን የተቃውሞ ሰልፍ ሲካሄዱ ሰንብተዋል። ዛሬም በበርሊን እና በፓሪስ የሚገኙ ዜጎች አደባባይ ወጥተዋል።

‹‹ዘረኝነት›› እና ኢትዮጵያ ምን አገናኛቸው? /Minillik Salsawi/

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በፌስ ቡክና በሌሎች አጋጣሚዎች ታዋቂና አንቱ የተባሉ ፖለቲከኞች ሳይቀር በኢትዮጵያ ያለውን ልዩነት ‹‹ዘር፣ ዘረኝነት፣ ዘረኛ›› እያለ ሲገልጹ ማየትና ማንበቤ ነው፡፡ ለመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹ዘር፣ዘረኝነት፣ዘረኛ›› አሉ? ለሰው ልጅ አመጣጥ ሳይንሳዊ አሊያም መለኮታዊ አመጣጥ ይሰጠዋል፡፡ አንደኛው ሰው ከዝንጀሮ መሰል እንሰሳ መጣ ሲል ሌላኛው አሁን ያለውን አካል ይዞ ነው የተወለደው በሚል ‹‹አምላክ ሰውን በአምሳያው ፈጠረ!›› ይለናል፡፡ የዓለም ህዝብ ከዝንጀሮ መጣ የሚሉት መነሻውን ወደ አፋር ሲጎትቱት በመለኮታዊው ግምገማቸው ወደ መካከለኛው ምስራቅ የተጠጋ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በሁለቱ አመለካከቶች መሰረት የሰው ‹‹ዘር›› ምንጩ አንድ መሆኑንእንረዳለን፡፡ ግን ሰዎች በዚህ አልተወሰኑም፡፡ ሰውን ለመነጣጠል የሚያስችል ፖለቲካ ጨመረበት፡፡ በቆዳ ቀለሙ፣ በአኗኗሩ፣ በሰውነትና አካል ቅርጹ፣ እና በመሳሰሉት አናሳ ወይንም የበላይነቱ! ይህን መሰረት በማድረግ በ18ኛው ክፍለዘመን ጆሃን ብሉሜንባች የተባለ ጀርመናዊ የህክምና ባለሙያ አምስት ዋና ዋና የሰው ‹‹ዘር›› አይነቶችን አስቀምጦ ነበር፡፡ አውሮፓን ማዕከል አድርጎ የምዕራበዊያንን ነጮች ካውካሳይድ ብሎ ጠራቸው፡፡ የኤሲያዎቹን ‹‹ብጫ›› ህዝቦች ሞንጎሎይድ ብሎ አንድ ‹‹ዘር›› ውስጥ አስቀመጣቸው፡፡ አውስትራሊያና ኦሺኒያን ደግሞ ማሌዠያ የሚል ስያሜ ሰጣቸው፡፡ አሜሪካኖቹን አሜሪካውያን በሚል ሰየማቸው፡፡ ጥቁር አፍሪካውያንን በሙሉ ደግሞ ኢትዮጵያውያን የሚል ‹‹ዘር›› ውስጥ አስቀመጣቸው፡፡ ይህን አምነን እንቀበል ብንል እንኳ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ አፋር፣ እና ሌሎች አፍሪካውያን አንድ ‹‹ኢትዮጵያ›› የሚባል ‹‹ዘር›› ውስጥ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ከቀለም፣ የቅርጽና ሌሎች ፖለቲካ ያልተላቀቀው ‹‹ታሪክ›› የሚያስተምረው ሶስት የሰው ‹‹ዘር›› አሉ ብሎ ነው፡፡ ነጮቹን በድፍን ካውካሳይድ ይሏቸዋል፡፡ ጥቁሮቹን ኔግሮይድ ብለው ይሰይሙታል፡፡ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ከዚህ ውስጥ እንገኛለን፡፡ ሞንጎሎይድ የሚሉት ደግሞ ወደ ቢጫ ይጠጋል የሚሉትን የኤሲያ ህዝብ ነው፡፡ ዘር ምን ያህል እውነት ነው? ………… በዘመናችን ‹‹ዘረን›› ከፖለቲካ መቀስቀሻነት ባለፈ ‹‹ሳይንሳዊ›› ትንታኔው የሚሰጡት ባይጠፉም በቆዳ ቀለም፣ አካላዊ ቅርጽና በመሳሰሉት የሚለየዩ ሰዎች በስነ ህይወታዊ ይህ ነው የሚባል የጎላ ልዩነት እንደሌላቸው የሚከራከሩት ተበራክተዋል፡፡ ለአብነት ያህል ዘር ከስነ ህይወታዊ በተለይም ከዘረመል ጋር የረባ ግንኙነት የሌለው መሆኑን በርካታ ጥናቶች አረጋግጠዋል፡፡ ለፖለቲካ መቀስቀሻም ቢሆን በአይን ቀለሙ ለማመሳሰል የተሞከረ ህዝብ በቆዳ ቀለሙ አይገናኝም፡፡ አሊያም በአፍንጫው፣ ወይንም በሌላው ነገሩ ይያያል፡፡ በመሆኑም ፖለቲከኞች አሊያም ሰውን የሚከፋፍሉት ‹‹አጥኚዎች›› ‹‹ዘር›› ብለው ሲመድቡ ለራሳቸው አስተሳሰብ ወይንም ጥቅም ቅርበት ያለውን በማጠጋጋት ብቻ ነው፡፡ በምዕራበዊያን አገራት ከእናቱ ወይንም ከአባቱ አንዱ ጥቁር የሆነው ጥቁር ይሉታል፡፡ ከዚህ በኋላ የእሱ የልጅ ልጆች ምንም ያህል ከነጭ ጋር ቢወላለዱና ነጭ ቢመስሉም ‹‹ኔግሮ›› የሚል ዘር ውስጥ መመደባቸው የግድ ነው፡፡ የኦባማ ልጆች ምንም ያህል ከነጭ ጋር ቢወላለዱ የልጅ ልጆቻቸው ጥቁር እንጅ ነጭ አይባሉም፡፡ ይህም የበላይ ነን የሚሉት ነጮች ለጥቁር ህዝብ ባላቸው የተሳሳተ አለመካከት የመጣ እንጅ የቀለም፣ የቆዳ አጠቃላይ የአካል ቅርጽ እንዳልሆነ የሚያሳይ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ የሚያሳየን አብዛኛዎቹ ዘር ጥቃቅን ስነ ህይወታዊ ጉዳዮችን በማጋነን የመጣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ፈጠራ መሆኑን ነው፡፡ ዘር የፖለቲካ ፈጠራ በመሆኑ ፓስተር፣ ቄሱ፣ ሹሁና ሌላው የ‹‹ሀይማኖት›› አባት የሰው ልጅ ከአንድ አዳምና ሄዋን መጣ ብሎ ሳይጨርስ ስለተለያዩ ‹‹ዘሮች›› ፖለቲካዊ ትርጉም ያወሩልናል፡፡ ስለ ጥንታዊ ሰው የሚያጠናው ሳይንቲስት የሰው ዘር መገኛ ‹‹አፍሪካ ነች›› ብሎ ሳያበቃ ፖለቲካው በጎተተው መጠን ስለተለያዩ ዘሮች ከማውራት አይቆጠብም፡፡ እንደ አብዛኛዎቹ የወቅቱ ሀቀኛ ምሁራን ከሆነ የቆዳ ቀለም ልዩነትን ለመፍጠር ከዘረመል ይልቅ የአየር ንብረት ትልቅ ቦታ አለው፡፡ በአፍሪካ በርሃማ ቦታዎች የሚኖርና በአውሮፓ ግግር በረዶማ ቦታዎች የሚኖር ህዝብ አንድ አይነት የቆዳ ቀለም ሊኖረው አይችልም፡፡ ሆኖም በሂደት ተላምዶዊም ሆነ በሌላ ምክንያት ዘረመልም በቆዳ ቀለምና በመሳሰሉት ምንም አስተዋጽኦ የለውም ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንስ የቆዳ ቀለምንና የመሳሳሉትን ልዩነት በመፍጠር ሚና የሚኖረው ዘረመል በጣም ጥቂትና በሰዎች መካከል ለመሰረታዊ ልዩነት መነሻ የሚሆን አለመሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ ‹‹ተመሳሳይ›› በሚባሉ ህዝቦች መካከል ያለው ስነ ህይወታዊ ልዩነትም በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ ከደም አይነት ጀምሮ ከቤተሰብ፣ ከጎሳና ብሄር፣ እንዲሁም ዘር የሚባለው በሙሉ የተለያዩ ናቸው፡፡ የአሜሪካን አንትሮፖሎጅ ማህበር እ.ኤ.አ በ1998 ባወጣው ጥናት ‹‹የሰውን ዘር በስነ ህይወታዊ ጥናት ድንበር ለይቶ መከፋፈል አይቻልም፡፡ 94 በመቶ ያህል የሰዎች ስነ ህይወታዊ ልዩነት አንድ ‹ዘር›› ውስጥ ናቸው በሚባሉት ውስጥም ይከሰታል፡፡›› የሚል መደምደሚያ ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ማለትም አብዛኛው ልዩነት አንድ ዘር በሚባሉትም መካከል እንዳለ ነው፡፡ በተለያዩ ወቅቶች ‹‹ዘር›› ለሚባለው የተሰጠውም ይህንኑ ጥላቻ አዘል ፖለቲካ የሚያሳይ ነው፡፡ ለአብነት ያህል በ18ኛውና 19ኛው ክፍለ ዘመን በነጮቹ ዘንድ ጥቁር ግማሽ እንሰሳ እንደሆነ ሁሉ ይታመን ነበር፡፡ በ19ኛው እና 20ኛው ክፍለ ዘመን ለዚህ አሉታዊ አስተሳሰብን የሚቃረን የማርክሲዝም አስተሳሰብ ብቅ ብሏል፡፡ በ20ኛው ክፈለ ዘመን በተለይም በ1930 ጀምሮ ደግሞ ዘር ለጦርነት ምክንያት ሲሆን አካላዊ ሳይሆን ፖለቲካዊና በፖለቲከኞች ፈጠራ የመጣ ልዩነት መሆኑን አስመስክሯል፡፡ ይህም ዘር የሚባለው ‹‹ፈጠራ›› መሆኑን እንደሚያሳይ በርካቶች በመከራከሪያነት ያቀርቡታል፡፡ ኢትዮጵያና የዘር ጉዳይ ………… ዘር መኖሩን አምነው በጉዳዩ ጥናቶችን የሚያደርጉ ‹‹ምሁራን›› ዘርን የሚያስቀምጡት ከጎሳና ብሄር በላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ጎሳ የሚባለው ‹‹አንድ አይነት አኗኗር፣ ስነ ልቦናዊ ሁኔታ፣ አለባበስ፣ ቋንቋ›› ውስጥ ከሚገኝ ‹‹ብሄር›› ከተባለው ማንነት በታች የሚገኝ ማንነት ነው፡፡ ሆኖም በርካቶች ዘርን ከጎሳና ከብሄር ጋር በማቀላቀል የቃሉን አውድ ሲያዛቡ ይስተዋላል፡፡ ፖለቲከኞች ዘር ሲሉ ምክንያቱን ስነ ህይወታዊ ምክንያት ይሰጡታል፡፡ እነ ሂትለር በጸጉር፣ በአይን ቀለም ጀርመናዊያንን ከሌሎቹ ሲያነጻጽሩ እንደነበሩት ማለት ነው፡፡ አሊያም ነጮቹ ራሳቸውን ከአፍሪካውያን፣ ከአረቦቹ አሊያም ከህንዶቹ ወይንም ከደቡብ አሜሪካውያን ጋር አነጻጽረው ልዩ እንደሚያደርጉት፡፡ ይህ ዘርን ከጎሳና ከብሄር ጋር የመቀላቀል አባዜ በኢትዮጵያም ከተለመደ ሰነባብቷል፡፡ በብሄር አሊያም በጎሳ የሚያምኑ የፖለቲካ ሀይሎችን የትኛውንም የፖለቲካ ጥበት ‹‹ዘረኝነት›› ብሎ መፈረጅ ለኢትዮጵያውያን አዲስ አይደለም፡፡ የኢህአዴግ መንግስት በሚያራምደው የብሄር ፖለረቲካ ‹‹በዘረኝነት›› ይወቀሳል፡፡ ሌሎችም ይህን የፖለቲካ ስልት በራሳቸው መልክ ይዘው ብቅ ሲሉ ‹‹የዘር ፖለቲካ›› ብለው የሚፈርጁት በርካቶች ናቸው፡፡ በአገራችን ከብሄርና ጎሳም ወረድ ሲልም ከእናት፣ አባትና ቤተሰብ የሚሳብን ዝምድና እና የ‹‹ደም›› ትስስር ለመግለጽ ‹‹ዘር›› ብሎ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም ዘር፣ ዘረኝነት.. የሚባለው ፖለቲካዊ ፍች ከቤተሰባዊ ትስስር ይልቅ ‹‹race›› ከተባለው ጥቅል (ግን የተሳሳተ የፖለቲካ ፈጠራ) ማንነት የመጣ ነው፡፡ በእርግጥ ይህ በኢትዮጵያ ውስጥ የሰረጸው ጣሊያን ካደረሰችው ምስቅልቅል ጋር ተያይዞ እንደሆነ በርካቶች ይገልጻሉ፡፡ ጣሊያኖች ኢትዮጵያ ውስጥ በራሳቸው የሰለጠነ ልዩ ዘርና በኢትዮጵያ ኋላ ቀር ዘር መካከል ከፈጠሩት ንቀት አዘል ክፍፍል ባለፈ ኢትዮጵያውያንን በ‹‹ብሄርና ጎሳ›› ከፋፍለዋል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ውስጥ የብሄር ፖለቲካ አዋጭ መሆኑን የሚያምኑት አካላትን ከጣሊያኑ ከፋፋይ ስርዓት ጋር በማዛመድ ‹‹ዘረኛ፣ ዘር፣ የዘር ፖለቲካ›› ብለው ይፈርጇቸዋል፡፡ ‹‹ዘር›› ፈጠራ መሆኑን ለጊዜው ረስተን ከአገራችን ህዝብ አኳያ ብንገመግመው ሰህተት መሆኑን እንረዳለን፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ብሄር አሊያም ጎሳ የሚባለው የቋንቋ ልዩነት ሲጠቀስ በዘር መክፈልም ሆነ ጎሰኛ አሊያም ጠባብ ብሄርተኛን ‹‹ዘረኛ›› ማለት የተሳሳተ ነው፡፡ የሚገርመው ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹በየዘረኝነት›› ስም የሚያወግዙት አካላት ኢትዮጵያ በጠባብ ማንነት መከፋፈል የለባትም የሚሉ ናቸው፡፡ ሆኖም ‹‹ዘር፣ዘረኛ፣ ዘረኝነት ፖለቲካ›› አለ የሚሉ ከሆነ በአካልም ቢሆን እጅጉን የተለያየ ነን ወደሚል እጅግ የሚቃረንና የተሳሳተ አመለካከት ያደርሳቸዋል፡፡ በጸጉር፣ በአይን ቀለም፣ በቆዳ ቀለም፣ በቁመት እጅጉን የተለያየን ነን እንደማለት ነው፡፡ ይህ ግን ስህተት ነው፡፡ የስርዓቱን ከፋፋይነት ለመግለጽ ከተፈለገ እንኳ ከጠባብ ብሄርተኝነት፣ጎሰኝነትና ጎጠኝነት ያለፈ ስም ሊሰጠው አይችልም፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ አማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ብሎ በዓይን ቀለም፣ በጸጉር፣ በአፍንጫ፣ በቆዳ ቀለም፣ በቁመት፣ በቅርጽ….መለየት አይቻልም፡፡ አሊያም አማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬ… የሚባለው ህዝብ ውስጥ ተመሳሳይ የዓይን ቀለም፣ የቆዳ ቀለም፣ የአፍንጫ ርዝማኔና ቅርጽ…..ብቻ አካላዊ ማንነት አይኖርም፡፡ እንደ ሁመራና መተማ ያሉ በርሃማ አካባቢዎች የሚኖረው ህዝብ በአለባበስ፣ በአመጋገብና በአካል ገጽታ ከደጋው ትግርኛና አማርኛ ተናጋሪ ህዝብ ይልቅ በቆላማው አካባቢ ከሚኖረው የአፋርና የሶማሊ አካባቢ ህዝብ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ በደጋው አካባቢ የሚኖረው ኦሮምኛ፣ አፋርኛ፣ሶማሊኛ፣ ትግርኛ፣ አማርኛ…..ተናጋሪ ህዝብ ተመሳሳይ ቋንቋ ከሚናገው ቆለኛ ህዝብ ይልቅ ሌላ ቋንቋ ከሚናገረው ደገኛ ህዝብ ጋር ተመሳሳይ ገጽታ፣ የኑሮ ዘይቤ፣አለባበስ…..ያለው ነው፡፡ ዘር ከፖለቲካ ፈጠራው አልፎ የደም ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ኦሮምኛ ተናጋሪው አንድ አይነት ደም፣ አማርኛ ተናጋሪው ከኦሮምኛ ተናጋሪው የተለየ ሌላ የደም አይነት በኖረው ነበር፡፡ በዓለም ደረጃም ቢሆን ተመሳሳይ ነው፡፡ ዘር የተሳሰተ የፖለቲካ ቀመር ነው፡፡ ይህን የተሳሳተ የፖለቲካ ቀመር እንጠቀም ካልም ደግሞ ‹‹ዘርን›› ካመጡት ‹‹ምሁራን›› ምድብ ልንወጣ አንችልም፡፡ ስለሆነም ኢትዮጵያውያንን የግድ በዚህ በተሳሳተ ቀመር እንክፈላቸው ከተባለ በጥቁር ማንነት ስር እኩል ከጋና፣ ከሞዛምቢክ፣ ከኬንያ፣ ከአንጎላ፣ ከጥቁር አሜሪካና ጃማይካኖቹ ጋር ይመደቡ ይሆናል እንጅ ሌላ ‹‹ዘር›› አይገኝላቸውም፡፡ እንዲያውም ጆሃን ብሉሜንባች የተባለው ጀርመናዊ ለመላው ጥቁር ህዝብ ‹‹ኢትዮጵያዊ›› የሚል ዘር ነው የሰጠው፡፡ ከዚህ ባለፈ ኢትዮጵያውያንን በቋንቋና ሌሎች ጥቃቅን መሰረቶች ‹‹ዘር›› ብሎ መፈረጅ ግን በጥላቻ ከተሞላው ጀርመናውይም በላይ እንድንሳሳት ያደርገናል፡፡ እናም በበኩሌ ፖለቲከኞቻችን ስለ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ሲወራ ‹‹ዘር›› የምትባለዋ ቋንቋ የተሳሳተች መሆኗን ተረድታችሁ ባትጠቀሙባት ይሻላል እላለሁ፡፡ ካልሆነ ግን ኦሮምኛ፣ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ ሶማሊኛ፣ አገውኛ፣ አርጎብኛ…..ተናጋሪው አንዱ ከሌላው በአይን ቀለሙ፣ በጸጉሩ፣……….እንደሚለይ መረጃ ልታቀርቡልን የግድ ነው፡፡ ዝም ብሎ መከፋፈል አለ እንዴ?

http://66.147.244.58/~theethio/harartub … %E1%8A%93/

Abraha Desta
November 19
“ከህወሓት የባስክ ትሆናለህ” አሉኝ
———————————–

“ጨቋኝ ስርዓት አልፈልግም” ብዬ በፃፍኩት ላይ አንድ የፌስቡክ ወዳጄ “አንተ ራስህ ስልጣን ብትይዝ ከህወሓት የባስክ አምባገነን ትሆናለህ” አለኝ።

እኔም እላለሁ፣

ከህወሓት የተሻልኩ እንደምሆን እርግጠኛ አይደለሁም (ራሴ ለግዜው እንደ ፓርቲ ልቁጠር)። ስለ አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ። እኔ ሰለማዊ ታጋይ ነኝ። ስልጣን የምይዘው በህዝባዊ ምርጫ እንጂ በጠመንጃ አይደለም። የምወዳደረው በሐሳብ እንጂ በሃይል አይደለም።

ስለዚህ ስልጣን ስይዝ የራሴ ወታደር፣ ፖሊስ፣ ዳኛ ወዘተ ይዤ አልመጣም። ስልጣን የምይዘው በሕገመንግስት መሰረት እስከሆነ ድረስ በኔና በወታደሮቹ ያለ ግንኙት ሕገመንግስታዊ ይሆናል። ስለዚህ ወታደሮቹ እንደፈለኩ የግሌ የስልጣን ጥም ለማርካት አላዝዛቸውም። ዳኞችም ነፃ ይሆናሉ።

ስለዚህ እኔ ስልጣን ከያዝኩ በኃላ ከህወሓት ካልተሻልኩ በህዝብ ምርጫ እንደወጣሁ ሁሉ በሚቀጥለው በህዝብ ምርጫ ከስልጣን እወርዳለሁ። ከስልጣን ላለመውረድ ምንም ዓቅም የለኝም፤ ምክንያቱም በምርጫ ስልጣን የያዘ አካል የግሉ ወታደርና ፖሊስ የለውም። የስልጣን መሰረቴ የህዝብ ድምፅ ከሆነ በስልጣን ለመቆየት ስል ህዝብን አልጨቁንም። ከጨቆንኩ ደግሞ ህዝቡ ያወርደኛል።

የኢህአዴግ መንግስት ሰለማዊ ትግልን አጨልሞብኝ በትጥቅ ትግል ስልጣን ከያዝኩ ግን አምባገነን የመሆን ዕድል አለኝ። ምክንያቱም የስልጣን ምንጬ ጠመንጃ እንጂ ህዝብ አይደለም። ለህዝብ ታማኝና አገልጋይ የምሆንበት ዕድል ይጠባል። ስለዚህ በምርጫ ስልጣን የያዘ መንግስት ቢያበላሽ እንኳ በምርጫ ይወርዳል። አሁን የቸገረን በጠመንጃ የመጣ መንግስት ነው።

ዓላማችን ስልጣን መያዝ ብቻ ሳይሆን ስልጣን በጠመንጃ ከመያዝ በምርጫ የምያዝበት ስርዓት መገንባት ጭምር ነው።

(ስልጣን የመያዝ ዕቅድም ፍላጎትም የለኝም። የኔ ፍላጎት በነፃነት የፈለኩትን ማድረግ ነው። እኔ የሌሎችን መብት ሳልዳፈር የፈለኩትን የማድረግ ነፃነት እንዲኖረኝ የህዝብ መንግስት ወይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት አለበት። ስልጣን መያዝ ነፃነትን ይገድባል)።

It is so!!!

“የኢትዮ-ኤርትራ ችግር መፍትሄ፣ ድንበር ማስመር ሳይሆን ድንበር ማፍረስ ነው”
——————————–

ኤርትራዊው ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ እንዲህ ተጠየቀ;

አዲስ አድማስ ጋዜጣ : የኤርትራ ህዝብ አሁን ያሉበትን የነፃነት ሁኔታ ከቀድሞው ጋር ሲያስተያዩት ምን ትርጉም ይሰጥዎታል?

ተከስተ ነጋሽ: እኔ እኮ በመጀመሪያም ኤርትራውያኖች ከማን ነው የሚገነጠሉት የሚል አቋም ነው ያለኝ። ማነው ከማን የሚገነጠለው? የደቡብ ወይም የኦሮሞ ህዝቦች እንገነጠላለን ቢሉ ኖሮ ምክንያት ነበራቸው፡፡ የኤርትራ የነፃነት ጥያቄ በተነሳበት ወቅት ኤርትራውያኑና ከላይ የጠቀስኳቸው ህዝቦች በኢትዮጵያ ውስጥ ያገኙትን እድል (Comparative advantage) ስናይ፣ ኤርትራውያኑ በጣም ተጠቃሚ ነበሩ፡፡ (በጣሊያን፣ በእንግሊዝ፣ በፌዴሬሽኑ ዘመን) በ1960ዎቹ የአዲስ አበባ ሀብታሞቹ እነሱ ነበሩ። በትምህርት መስክ ሃያ አምስት በመቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ኤርትራውያን ነበሩ። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችንም ካየሽ 25 በመቶ የሚሆኑት ኤርትራውያን ነበሩ፡፡ ከተማረው ሰላሳ አምስት በመቶው ክፍል ኤርትራውያን ነበሩ፡፡

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት በደረሰው አስተማማኝ መረጃ መሰረት   በሳውድ አረቢያ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ለትምህርት ቤት መገንቢያ እና ለችግር ግዜ ይሆነናል በማለት ከግል ኪሳቸው እያወጡ በደረግ ዘመን ሲያጠራቅሙት የነበረውን ገንዘብ የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በሰጡት ትእዛዝ ገንዘቡ ተወርሶ በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲና የአምባሳደሩ መኖሪያ እንዲሁም ጅዳ የሚገኘው የቆንስላ ጽህፈት ቤት እንዲሰራበት …

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘግይቶም ቢሆን ችግረኛ ኢትዮጵያውያንን ከሳውድ አረቢያ ማስወጣት የጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት፣ እስካሁን ድረስ የተመላሾችን አሀዝ በተመለከተ የሚሰጠው መግለጫ ግን ህዝቡን ጥርጣሬ ላይ መጣሉን የኢትዮጵያው ዘጋቢያችን ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስተሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም በቲውተር ወደ አገር ቤት የተመለሱት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 10 ሺ 707 ነው በማለት ገልጸዋል። ይሁን እንጅ የእርሳቸው …

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሰኞ ኖቬምበር 25፤ 2013 ከ ጠዋቱ 8:30 ጀምሮ ሚድራንድ በሚገኘው ፓን አፍሪካ ፓርላማ ፊት ለፊት ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያዘጋጁ ለኢሳት ተናግረዋል። በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በመገኘት ድምጻቸውን እንዲያሰሙ ተማጽነዋል።

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት አቶ መላኩ ፈንታ ክሳቸው በየትኛው ፍርድቤት ይታይ የሚለውን ጉዳይ ፥ የህገመንግስት ትርጉም ያስፈልገዋል በሚል ለሕገመንግስት አጣሪ ጉባኤ መምራቱ አንዳንድ ከፍተኛ የኢህአዴግ ሹማምንትን እንዳላስደሰተ ታውቋል። ሰኞ ህዳር 10 ቀን 2006 ዓ.ም በነበረው የችሎት ውሎ አቶ መላኩ ፈንታበሚኒስትር ማዕረግ ተሸመው ሲያገለግሉ እንደነበሩና …

ህዳር ፲፪(አስራ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዛሬው እለት የአዲስ አበባ መስተዳድር በቡራዩ አካባቢ በወሰደው እርምጃ፣ ከ500 በላይ ቤቶችን ያፈረሰ ሲሆን በርካታ ቤተሰቦች ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ለኢሳት ገልጸዋል። አመዲና ጎጥ በተባለ አካባቢ የሚኖር አንድ መስፍን የተባለ ወጣት ወላጆቼ በሰሩት ቤት መኖር ካልቻልኩ ምን ህይወት አለኝ በሚል ራሱን ማጥፋቱም ታውቋል። የቀበሌው ሊቀመንበር ህዝቡን ሰብስቦ ለማነጋገር …

ወደ አሥራ ሦስት ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን እስከአሁን ከሣዑዲ አረቢያ አዲስ አበባ መግባታቸውን የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ተመላሾቹን ለማቋቋም በፌደራል መንግሥቱና በክልል አስተዳደሮች የትብብር ሥራ እንደሚከናወንም መሥሪያ ቤቱ አመልክቷል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ተፈፅሟል የሚል ዜና ከወጣ ጀምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን እያሰሙ ነው፡፡

ዛሬ፣ ሐሙስ፣ ኀዳር 12 / 2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደጅና ጀርመን ዋና ከተማ በርሊን ውስጥ ደግሞ በሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሰልፎች ተደርገዋል፡፡

ባለፉ ጥቂት ቀናት ውስጥም በእንግሊዝ፣ በጣልያን፣ በአውስትራሊያ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ደግሞ በዳላስ፣…

ሕጋዊ ፈቃድ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ላይ የሚደርሰውን ችግር እና ጥቃት በመቃወም በተለያዩ ሀገራት ሰሞኑን የተቃውሞ ሰልፍ ሲካሄዱ ሰንብተዋል። ዛሬም በበርሊን እና በፓሪስ የሚገኙ ዜጎች አደባባይ ወጥተዋል።

Image
ልሂቃን ለስልጣናቸው ሲሉ ሊሰብሩት የሚጥሩትን ድልድይና ገመድ አጠናክረነው በሰላም አብረን መኖር የምንችለው፡፡

በእርግጥ እኛም ከኤርትራውያን የምንሻልበት ደረጃ ላይ አይደለንም፡፡እነሱም እንደኛው ናቸው፡፡ መከራ ውስጥ ሆነውም ቢሆን ግን በሳውዲ አረቢያ ሰቆቃ የደረሰባቸውን ዜጎች ድምጽ ከጎናችን ሆነው አሰምተዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ዋንጫ ከጎናችን ሆነው የአገራችን ቡድን አበረታትተዋል፡፡
ድሮም ቢሆን ህዝብ በራሱ ተሳስቶ አያውቅም፡፡ ህዝብን የሚያወናብዱት ልሂቃን ናቸው፡፡ ኤርትራ በጣሊያን እጅ በነበረችበት ወቅት በርካቶቹ ወደ እናት አገራቸው ጠፍተው ገብተው በከፍተኛ ስልጣን አገራቸውን አስተዳድረዋል፡፡ እነ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስግዶም ስለ እናት አገራቸው መስዋትነት ከፍለዋል፡፡ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌደራል ስርዓት ስትቀላቀል ጨፍረዋል፣ ደስታቸውን በእምባ ሳይቀር ገልጸዋል፡፡ ይነሱም ይብዙም ኤርትራውያን በኢትዮጵያ መከራ ጊዜ ከጎናችን እርቀው አያውቁም፡፡
አጼ ኃይለስላሴ ፌደሬሽኑን ሲያፈርስ በኢትዮጵያውያን ድጋፍ ወይንም ግፊት አልነበረም፡፡ መንግስቱ ኃይለማሪያም በኤርትራውያን ላይ እርምጃ ሲወስድም ቢሆን እንዲሁ፡፡ ጀብሃና ሻዕቢያ በአረብ አገራት ድጋፍ ኤርትራን ለመገንጠል የጣሩት በህዝቡ ትዕዛዝና ግፊት አሊያም ድጋፍ አልነበረም፡፡ እንዲያውም ይህንን ተገንጣይነት ኤርትራውያን ‹‹እናት አገር ወይንም ሞት›› ብለው ተዋግተውታል፡፡ በኢትዮጵያ የነበሩት አስተዳደሮችም ሆነ ‹‹ወንበዴዎቹ›› ስህተት ግን ሁለቱን ህዝቦች መካከል ያለውን ድልድይ ለመስበር ሳይታክቱ ሰርተዋል፡፡
ህወሓትና ሻዕቢያ ስልጣን ከያዙ በኋላም ቢሆን የሁለቱ ህዝቦች ትስስር እንደፈለጉት ሊበጠስላቸው አልቻለም፡፡ የሻዕቢያና የህወሓት ካድሬዎች ሁለቱን ህዝቦች እየደበደቡ፣ እየዘረፉ፣ እያሰቃዩ ከአስመራና አዲስ አበባ ሲያስወጡ ህዝብ የተለያየው በእንባ ነበር፡፡
በእርግጥ የመንግስታት ፕሮፖጋንዳ፣ ካድሬዎች የሚፈጥሩት መከራና ኢኮኖሚያዊ ወይንም ሌላ ግንኙነት በመቋረጡ ምክንያት ህዝቦች ሊቆራረጡ ይችላሉ፡፡ ሁለቱ ህዝቦች መካከል ያለውን ግንኙነት ለመስበር የተደረገው ሙከራ ግን አልተሳካም፡፡ አዎ! ኤርትራውያን የአገሪቱ ‹‹መንግስት›› ሰላማዊ ሰልፈኞቹን ባሰረበትና በደበደበበት ወቅት ከጎናችን ሆነው ገመዱ ኃይለስላሴ፣ መንግስቱ ኃይለማሪያም፣ ኢሳያስ፣ መለስ፣ ህወሓት፣ ሻዕቢያ ሊበጥሱት የማይችሉ የደም ገመድ መሆኑ በድጋሜ አሳይተውናል፡፡
እናም እንደነሱው ከጎናቸው መቆም ይገባናል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢሳያስ ጠፋ፣ ታመመ እየተባለ ነው፡፡ አምባገነን መሪ ሲሞት፣ ሲታመም፣ ወይንም አምባገነኑ ስርዓት ምክንያት ስርዓት ሲናጋ የሚጎዳው ሀብትና ጥበቃ የሌለው ምስኪን ህዝብ ነው፡፡ ሀብት ያላቸው የኤርትራ ባለስልጣናት በፈለጉት አገር ሄደው ይኖራሉ፡፡ ጥበቃ ያላቸው አገር ውስጥም ቢሆን አንጻራዊ ሰላም ይኖራቸዋል፡፡ ድሃውና ሲጨቆን የነበረው ህዝብ ግን አምባገነኑ እያለም ሆነ ሞቱ ስጋት ውስጥ ነው፡፡ የአገር አደጋ አደጋ የሚሆነው ለድሃው ነው፡፡
ኢትዮጰያውያን መለስ ዜናዊ ጠፋ፣ ታመመ፣ ሞተ በተባለበት ወቅት አምባገነንነቱን ረስተን ‹‹አገር ትፈራርሳለች›› ብለን ተጨንቀናል፡፡ ኤርትራውያንም አሁን ተመሳሳይ ስጋት ውስጥ ናቸው፡፡ ሁለቱ ህዝብ በተለያየ ጊዜ ይከሰቱ እንጅ ተመሳሳይ መከራ፣ ስጋት ውስጥ ናቸው፡፡ ችግራቸው መሰረት ተመሳሳይ ነው፡፡ እናም እነዚህን ችግሮች መፍታት የሚችሉት አንዱ ከአንዱ ጎን በመቆም ብቻ ነው፡፡
ለችግሮቻቸው መፍትሄ ማምጣት እንኳን ባንችል ልክ እንደወትሮው፣ ልክ እንደባህላችን፣ ልክ እነሱ እንዳደረጉት ከጎባቸው መሆናችንን ማሳየት አለብን፡፡ ሲሆን ታሪክ፣ ደም፣ አምሮ መኖር በደመነፍስ እያነጋኘን እንደሆነ በቅርቡ አይተነዋል፡፡ የሁለቱ አምባገነን ስርዓቶች ፕሮፖንዳና መሰሪነት በርካቶቹን እሴቶቻችን ሸርሽሮት አብሮ መስራት እንደማይቻል የሚያስብ የዋህ (ካድሬ ቢኖር እንኳ) ጎረቤቶች ነን፡፡ የኤርትራ ችግር መቼም ቢሆን የኢትዮጵያውያን ችግር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ችግር የኤርትራውያን ችግር ነው፡፡ ከሁለቱ አገራት መካከል አንዱ እንደ ሰው ተሰዶ ወይንም ሸሽቶ፣ አሊያም አጥሮ መኖር አይችልም፡፡ የሶማሊያና የሱዳን ችግር እንኳን ችግራችን ሆኗል፡፡
እናም በችግራቸው ጊዜ አብረናቸው መቆማችን ለእነሱ ብቻ ሳይሆን ለእኛም ጥቅም ነው፡፡ ስለሆነም ከኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን ጎን አብረን መቆም ይኖርብናል፡፡ እንዲህ ሲሆንም ነው ልሂቃን ለስልጣናቸው ሲሉ ሊሰብሩት የሚጥሩትን ድልድይና ገመድ አጠናክረነው በሰላም አብረን መኖር የምንችለው፡፡ — with Getachew Shiferaw and 2 others.

በጦርነቶች እና በግጭቶች ምክንያት ከመኖሪያ ቦታቸው የተፈናቀሉ ወጣቶች የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራው የአውሮጳ ህብረት የልጆች የሰላም ፕሮጀክት የአንድ ዓመት የስራ ክንውን እና ውጤት ብራስልስ ቤልጅየም

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች በአንዳንድ የአፍሪቃ ሃገራት በመገናኛ ብዙሃንና በሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ላይ ተጠናክሮ የቀጠለው ጥቃት እንዲቆም እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ብራሰል ቤልጂግ ውስጥ ለተካሄደው የአፍሪቃና የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽኖች የሰብዓዊ መብቶች የጋራ መድረክ አሳስቧል ።

አዉሮጳን እርሱ ፤ ብሩህ ተስፋ እና ተስፋ የሚገኝበት አዲስ አበባ ነዉ ይሰኛል ባለፈዉ ወር መገባደጃ ላይ ዲ ቬልት የተሰኘዉ የጀርመን አንጋፋ ጋዜጣ ያስነበበዉ ርዕስ፣ በጀርመንኛ መጠርያዉ ዲ ቬልት ፤ ማለትም «ዓለም» በመባል የሚታወቀዉ ዕለታዊ የጀርመን ጋዜጣ በጎርጎረሳዉያኑ 1964 ዓ,ም ሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት እንዳለቀ ጀምሮ የሚታተም ነዉ።

በውጪ ሐገር በስደት ላይ በሚገኘው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራው የካምፓላ መካነሰላም መድሃንያለም ቤተክርስትያን በዩጋንዳ የህዳር ሚካዔልን የንግስ በዓል ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አንዳከበሩት በስፍራው የነበረው የፔን ዘ ኢትዮጵያ ዘጋቢ ገለፀ።
ከለሊቱ አስራአንድ ሠዓት ጀምሮ በማህሌት የጀመረው ክብረ በዓል በደብሩ መሪጌታ ይህይስ ዓለሙ ያሬዳዊ ዝማሬ ቀርቧል።<ውእቱ ሚካዔል መልዓከ ኃይለ ልዑል።ውእቱ ልዑለ መንበር ይስአለነ……>
በዕለቱ ቅዳሤ በርካታ ምዕመናን የታደሙ ሲሆን ከማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ አስራ ስምንት ከቁጥር አስራአምስት እስከ ሃያ አንድ በቆሞስ አባ ኃይለማርያም ተነቧል። ስርዓተ ቁርባን ከተከናወነ በኋላም በቆሞስ አባ አብዩ የዕለቱን በዓል በማስመልከት ኦሪት ዘፀአት ምዕራፍ አስራ አራት ከቁጥር አስራ ዘጠኝ ጀምሮ ያለውን ቃል በተመለከተ የወንጌል ማዕድ ቀርቧል።
የቅዳሤ ስርዓቱ እንዳበቃም ታቦተ ህጉ በካህናትና ምዕመናን ታጅቦ በክብርና በምስጋና ዜማ ታጅቦ በአውደ ምህረቱ ላይ መሪጌታ ይህይስ <አንተኑ ሚካዔል መና ዘአወረድከ።ወአንተኑ ለእስራዔል መና ዘአወረድከ።>በያሬዳዊ ዜማ ወረብ አቅርቧል።
የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ፀሐይ ደስታ በበዓሉ ፍፃሜ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እግዚአብሔር አምላክ እስራዔላዊያንን ከግብፅ የባርነት ቀንበር ነፃ የወጡበትን ዕለት በመዘከር ይህንን ታላቅ በዓል ቤተክርስትያን በድምቀት እንደምታከብረውና በዓሉ የስደተኞች በዓል ሊባል እንደሚችል ጠቁመው ስደተኞች ሁላችን እግዚአብሔር አምላክ እስራዔላዊያንን ከግብፅ የፈርዖን አገዛዝ እንዳዳናቸው ሁሉ እኛንም ለሐገራችን ያብቃን ሲሉ ቃለ ምዕዳን ሰጥተዎል።
በመጨረሻም የአምልኮ ነፃነት በተረጋገጠባት ዩጋንዳ ኤርትራዊያንና ኢትዮጵያዊያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የፖለቲካ ድንበር ሣያግዳቸው በአንድ ደብር ፈጣሪያቸውን ሲያመሠግኑ የዚህ ዜና ዘጋቢ ተመልክቷል።
Pen Ethiopian

Image

በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ጥቃት እና የፈዘዘው ስርኣት የፖለቲካ ክስረት
መፍትሄው ኢሕኣዴግ የማይደፍረው ስር ነቀል ለውጥ ነው::

ምንሊክ ሳልሳዊ:-ኢትዮጵያውያን በመካከለኛው ምስራቅ በስፋት መሰደድ የጀመሩት ባለፈው 20 አመታት የወያኔው ጁንታ መንግስት ስልጣኑን ተቆጣጥሮ በህዝቦች ላይ በተለየ መልኩ የፈጠረውን አደገኛ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ቀውስ ተከትሎ መሆኑ እሙን ነው::ይህ ቀውስ የደረሰባቸው ወገኖቻችን ከተሰደዱባት ሃገር አንዷ ሳኡዲ አረቢያ ተጠቃሽ ናት::ሳኡዲ አረቢያ ከሃብቷ ብዛት የመጣ የስራ ፍቅር ባሌለው ወጣት ዜጋ የተሞላች እና ፔትሮ ዶላር ባሰከራቸው ቱጃሮች የምትተዳደር አገር መሆኗ እና የዜጎቿ የስራ አለመስራት የስራ እድሎችን ስላሰፋ የወያኔ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጠቂዎች ወደዚሁ መሰደድን መርጠዋል:: ይህንን ተከትሎም ይህን ሰሞን የአለም ዋና አጀንዳ የሆነው የኢትዮጵያውያን በሳኡዲ አረቢያ እየደረሰባቸው ያለ ስቃይ ነው::

ሰቆቃው ያደረሰው የሰብኣዊ መብት ጥያቄ ከሳኡዲ መንግስት ላይ ይልቅ ወደ ወያኔው ጁንታ ላይ እንዲተኮር ያደረገ ሲሆን የወያኔው ጁንታ ለከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ተዳርጓል::በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው አስደንጋጭ እና ሰብኣዊነትን ያለፈ ድርጊት በመንግስት ባለስልጣናት መሃከል የፈጠረው መረበሽ እስከአለመግባባት አድርሷቸዋል::ይህንን የወያኔን አቋም የተመለከተችው ሳኡድ አረቢያ በአለም አቀፍ ደረጃ የፖለቲካ የበላይነት ተቀናጅታለች::በከፍተኛ ደረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ባሉ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ዘንድ ከፍተኛ የሆነ አትኩሮት አግኝቶ የአለም ጎዳናዎች ሳኡዲን እና ወያኔን በሚቃወሙ በሰላማዊ ሰልፍ እየተጥለቀለቁ ነው::ህገመንግስታዊ መብቶችን አለመከበሩን እና ለዜጎች አለመቆርቆርን በማሳየቱ በአለማቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያውያንን ቁጣ ቀስቅሷል::ሚዲያዎች ከዜጎች የሳኡዲ ሰቆቃ ይልቅ በኢትዮጵያውያኑ ሰልፎች ላይ አትኩሮት ሰተዋል::

ከወያኔው መንግስት የሚንጸባረቁ አጀንዳዎች ለዘብተኛ አቋሞች በስህተት እንደተፈጠሩ ወቅታዊ ሁኔታኦች እያሳዩ ሲሆን ስርኣቱ አጣብቂኝ ውስጥ እና የፖለቲካ ኪሳራ ውስጥ እንደገባ ተረጋግጧል:: የሌላ ሃገር እምባሲዎች ዜጎቻቸውን በመጠበቅ ላይ ሲያተኩሩ የወያኔው ዲፕሎማቶች የዜጎች ንብረት የሆነውን ኤምባሲ በመዝጋት አገልግሎት አቁመዋል::
የደረሰውን ሰቆቃ ተከትሎ ስርኣቱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር ለሉአላዊ የዜግነት ክብር መነሳሳት ሲኖርበት እና ህዝብን ማቀፍ ሲኖርበት ለብሄራዊ ውርደት ዜጎችን ዳርጓል::የፖለቲካ ፓርቲዎች የጠሩትን ሰልፍ በሃይል እና በደብዳቤ በትኗል::የወያኔው ስርኣት የህዝቡን ቁጣ ባለማንበቡ በችኮላ ያልበሰለ ሃሳብ በማራመዱ የፖለቲካ ኪሳራውን አስፍቶታል::ህገመንግስታዊ መብቶችን አለመከበሩን እና ለዜጎች አለመቆርቆርን በማሳየቱ በአለማቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያውያንን ቁጣ ቀስቅሷል::ሚዲያዎች ከዜጎች የሳኡዲ ሰቆቃ ይልቅ የወያኔን ስርኣት ጋጥወጥነት አትኩሮት ሰተውታል::

ለዚህ ሁላ ችግር መንስኤው ስርኣቱ በልማት ሽፋን የሚከተለው የፖለቲካ እና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ችግሮች እንደሆኑ አግጥጦ ገሃድ ከመውጣቱም በላይ የአደባባይ ሃቅ ሆኖ ለለውጥ እንትጋ የሚሉ ድምጾች በመላው ሃገሪቱ ተንጸባርቀዋል:; የወያኔ ስርኣት ህዝብን የሚያሳትፍ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ እስካልተከተለ ድረስ እና አሁን ባለው ሂደት ላይ ለውጥ እስካላደረገ ድረስ የስደት ችግሩ በስፋት እየቀጠል ይሄዳል:;ዛሬ ሳኡዲ ላይ የደረሰው ሰቆቃ ነገ በሌሎች ሃገራትም ይቀጥላል::ይህ ብሄራዊ ውርደት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ ነው:;ኢትዮጵያውያን ከቀድሞው ጀምሮ በፖለቲካ ቢሰደዱም እንደዚህ አይነት ውርደትን አስተናግደው አያውቁም::የአሁኑ ውርደት ያለው ስርኣት ለዜጎቹ ደንታ ቢስ በመሆኑ የተወለደ ችግር ነው::በሃገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ተመዘገበ ከመባል ውጭ የተባለው እድገት ምንም አይነት ህዝባዊ ጠቀሜታ እንዳላሳየ በይፋ አስመስክሯል::የተማረው እና የሚሰራው ሃይል መሰደዱ ኢኮኖሚው እንደኮላሸ እንጂ እንዳደገ አያሳይም::የዚህ ሁላ መንስኤው ስርኣቱ የሚከተለው አፋኝ የፖለቲካ እና የእኮኖሚ ፖሊሲ ስለሆን ድጋሚ ሊከለስ እና ሊፈተሽ ይገባዋል::

የነቃ እና የተደራጀ አዲስ ፖሊሲ አስፈላጊ መሆኑ እሙን የሆነበት ጊዜ ላይ ደርሰናል::ስርኣቱ የሚከተለውን ፖሊሲ በአስቸኳይ ካልቀየረው የሚመጣው አደጋ ከፍተኛ ነው::በሃገሪቱ በልማት ስም እና በፖለቲካ ባላንጣነት በዜጎች ላይ የሚደርሰው ችግር የሙስና መንሰራፋት ሚዛናዊነት የጎደለው የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ የግሉን ሴክተር የማዳከም ውስጣዊ ሴራ ዘር ተኮር የሆነ ፖለቲካ እና አድሎኣዊ አሰራር የትምህርት ጥራት መውረድ እና የስራ አጡ ቁጥር እንዲስፋፋ የሚደረጉ ደባዎች ዜጎች ምንም አይነት ጥያቄ እንዳያነሱ የሚደረጉ የፖለቲካ ዱላዎች ለድህነት መፈጠር እና የስደት መስፋፋት ምክንያት ሆነዋል::የህዝብ ቁጥርን ተከትሎ የሚደረግ የእድገት ፖሊሲ አለመመጣተን የሃገሪቱ ዜጎች ተዘዋውረው እንዳይሰሩ የተደረገ የጎሳ ፖለቲካ የተማሩ ዜጎችን የስራ እድል አጥብቦታል::አለ ተብሎ የሚወራለት የኢኮኖሚ እድገት ጥቂት የስርኣቱን ካድሬዎች ተጠቃሚ ያደረገ በመሆኑ ማንኛውም ነገር በካድሬዎች ዙሪያ እና በፓርቲ ስራዎች ዙሪያ ያተኮረ በመሆኑ ዜጎች በሃገራቸው ላይ ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓቸዋል::

ያለው ስርኣት ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት ፖሊሲዎቹን እና የደረሱ የዜጎችን ችግር ከስሩ መሰረቱ መመርመር አለበት:: በፓርቲው አመራር ደረጃ ያሉ የስርኣቱ ባለስልጣናት ለስርነቀል ለውጥ ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው::በግል የንግድ ተቋማት ላይ ስርኣቱ ያለው አቋም ከመጀመሪያ ለውጦች አንዱ ነው የግል የንግድ ተቋማት መዳከም ምክንያቱ የስርኣቱ መራሽ የንግድ ድርጅቶች እና አድሏዊነት የፈጠረው የኢኮኖሚ ችግር ሲሆን መፍትሄውም የተዳከመውን የግሉን የንግድ እንቅስቃሴ እንዲያንሰራራ ማድረግ እና ለዜጎች በርካታ የስራ እድሎች እንዲከፍት ማበረታታን አንዱ ሲሆን የተለየ የፖለቲካ አቋም ያለው ዲያስፖራው በሃገሩ ጉዳይ እንዲሳተፍ እድሎችን ማመቻቸት እንዲሁ ለፖሊሲ ለውጥ ጅማሮ ሊሆን ስለሚችል ስደትን በስፋት ለመቀነስ እና ዜጎች ከሃገራቸው እንዳይወጡ ለማድረግ ይችላል::

በአሁን ሰአት ስርኣቱ እየተተቀመበት ያለው የኢኮኖሚ ፖሊሲ በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ የተገነባ ከመሆኑም ባሻገር ባልተማሩ እና ባልሰለጠኑ የፖለቲካ ታማኞች ስለሚተገበር በአግባቡ እየተተረጎመ ባለመሆኑ ውድቀትን አምጥቷል::የሃገሪቱ አጠቃላይ ሃብት እና የኢኮኖሚ ምሶሶ በጥቂት የፓርቲ ድርጅቶች እና ባለስልጣናት እጅ በቁጥጥር ስር ስለሆነ የግሉ ኢንቨስትመት በመዳከሙ እና ስርኣቱ ከዚህ አይነት የንግድ እንቅስቃሴ ካልወጣ በቀር ምንም አይነት ለውጥ መምጣት እንደማይቻል እሙን ሲሆን መፍትሄው የተቆጣጠረውን እና በግል መያዝ ያለባቸውን የንግድት ተቋማት እና የአገልግሎት ዘርፎች መልቀቅ ካልቻለ ችግሩ እየከፋ ዜጎችን ምንም ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ያደርጋል::በአለም አቀፍ ደረጃ እንደሚታየው መንግስታት ህግ የማውጣት እና የማስፈጸም አቅም እንጂ ከትልቅ እንስከተራ ንግድ ድረስ እጃቸውን አስገብተው ሲሰሩ አይታይም::ያለው ስርኣት ወደ ቸርቻሪ ነጋዴነት በመቀየሩ ለዜጎች የስራ እድሉን አጥብቦታል::

ኢኮኖሚውን ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎች እና የፓርቲ የንግድ ድርጅቶች በሞኖፖል ስለተቆጣጠሩት ዜጎች በስርኣቱ ፖለቲካ ካልተጠመቁ ድረስ ስራ የማግኘት እድል የላቸውም::ይህ ኢኮኖሚውን የመቆጣጠር የፖለቲካ ጭብርብሮሽ የኢንቨስትመት ሂደቱን ከማዳከሙም በላይ ዜጎች በሃገራቸው እና በስርኣቱ ላይ እምነት እንዲያጡ አድርጓል::ስርኣቱ ከነጋዴነት መውጣት ሰፊ የስራ እድሎች እንዲፈጠሩ እና ስደት እንዲቀንስ የሚረዳ ሲሆን ዜጎች በሃገራቸው ተሳፋ እንዳይቆርጡ ያደርጋል:: እንዲሁም የመንግስት የመገናኛ ቡዙሃን በሃሰት የተሞሉ መሆናቸው እና አስፈላጊውን መረጃ መስጠት አለመቻላቸው ሌላኛው የኢኮኖሚ ድቀት እና የስደት መንስኤ ናቸው:: በነጻነት የማይሰሩት እና ለፖለቲካው የእድሜ ማስረዘሚያ የሆኑት የመገናኛ ብዙሃን ቀረጥ የሚከፍላቸውን ህዝን እንዳያገለግሉ ከመደረጉም በላይ በሃሰት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ወንጀሎችን በመፈብረክ የታወቁ ሆነዋል::

ሕዝቡ ስርኣቱ እስካልተመቸው ድረስ ስደትን ማቆም አይቻልም ጊዜአዊ እገዳውም ውጤታማ አይሆንም:: ሀገሪቱ ብዙ ሴቶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሊሰደዱባት የቻለውም ከሴቶች እኩልነት ጋር በተያያዘም ችግር በመኖሩና ብዙ ስራ አለመሰራቱን የሚያሳይ ነው::በዚህ ዙሪያ የሚሰሩ ድርጅቶችም በነፃነት አለመቋቕውማቸው ሴቶችም እንደሰው አለመታየታቸው ነው::የፓርቲ ፖለቲካ መስበክ ሳይሆን በሴቶች እኩልነት እና ተሳትፎ ዙሪአ ኢኮኖሚው መዳበር ሲኖርበት አስፈላጊውን ኦረንቴሽንም መስጠን የስርኣቱ ግዴታ ነው::አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ስራ የሚገባውን ወጣት የሚሸከም ኢኮኖሚ አልተፈጠረ:: የግል ሴክተሩም በርካታ ዜጎች እንዳይፈጥር ሆኖ እየሞተ መሆኑን ከዓለም ባንክ ሪፖርቶች ማየት ይቻላል::በዓለም ደረጃ በመንግስት ኢንቨስትመንት ኢትዮጵያ በዓለም ሦስተኛ ስትሆን፤ በግል ኢንቨስትመንት ከመጨረሻዎቹ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ነን። ስለዚህ የግል ሴክተሩ ካልተስፋፋና ካላደገ ስራ ሊፈጠር አይችልም። በየዓመቱ ከዩኒቨርሲቲ የሚመረቀው ወጣት በዓመት ወደ መቶ ሺህ ሊጠጋ ነው። ይሄንን ኃይል መጦ የሚያስቀር የሚያደርግ ኢኮኖሚ መፈጠር የሚቻለው የግል ሴክተሩ ሲነቃቃ ነው። አሁን የግል ሴክተሩ በኮንስትሪክሽን ዘርፍ ላይ ውር ውር እያለ ነው። ይሄም ሴክተር ቢሆን፤ የቀን ሰራተኛ ከመሳብ ባለፈ ሙያተኛውን መቅጠር አልቻለም። ለዚያውም ትንሽ ሲሚንቶ መለሰን ሲጀምሩ ወደ መካከለኛው መስራቅ በተከበረ ወርሃዊ ደመወዝ ሲቀጠሩ ይታያል። ሀገሪቱ የተማረ የሰው ኃይል የላትም። ያሉዋትም ለባዕድ አገር እያገለገሉ ነው። በአንፃሩ የአገሪቱን የባቡር መንገድ እና ግድብ የሚሰሩት ቻይናና ሕንድ ናቸው። ስኳር ፋብሪካውንም የሚሰሩት ሕንዶች ናቸው። በሚያሳዝን መልኩ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የተማሩም ሆነ ያልተማሩ ችሎታቸውን እየሸጡ ያሉት ለባዕድ ሀገር ነው። ከአፍሪካ እስከ ደቡብ ሱዳን፣ ቦትስዋና እና ደቡብ አፍሪካ ሳይቀር በርካታ ኢትዮጵያውያን ችሎታቸውን በጥሩ ዋጋ እየሸጡ ነው። ይሄን አሳዛኝ ታሪክ ለመቀየር የግል ሴክተሩ ማደግ ወሳኝ ነው ።

የግል ዘርፉ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይረከብ ማለት ግድብ ይገንባ፣ የባቡር መንገድ ይዘርጋ ማለት አይደለም ነገር ግን የግል ዘርፉ ሊሰራቸው የሚችሉ ስራዎች ተለይተውና ተጠንተው መሰራት አለባቸው። የኅብረተሰብ ችግርም እየተበራከተ ስለሆነ ችግሩን መመርመር ያስፈልጋል ። የግል ዘርፉ ከካፌና ሆቴል ላይ ብቻ የሚሯሯጠው ለምንድነው? የቀጥታ የውጪ ኢንቨስትመንት ችግር በገፍ የማይመጣው ለምንድነው፣ አነስተኛና ጥቃቅን አደረጃጀት ምን ያህል ውጤት አምጥቷል? የተደራጀ ጠንካራ የግል ዘርፍ መፍጠር ነው ወይስ አነስተኛ ጥቃቅን ድርጅቶች የሚለው መታየት አለበት። የትኛው ነው ብዙ ኀሳብ የሚያመነጩት፣ የገበያ ሁኔታስ? ባንኮች አካባቢ ያለው ችግር ምንድነው? ለምን አያበድሩም ይሄ ሁሉ መፈተሽ አለበት ።የኢትዮጵያ የአረብ ገረድ አምራች ሆና መቅረት የለባትም ።

http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … st_21.html

የወረዳው ሊቀ መንበር ለስብሰባው በሚገባ መዘጋጀታቸው ሲወራ ነው የሰነበተው፡፡ ሕዝቡን ለፀረ ሽብርተኛት ዘመቻ በሚገባ ማንቀሳቀስ አለብኝ ብለዋል አሉ፡፡ አንድም ሰው ከዚህ ስብሰባ መቅረት እንደሌለበት በየሰፈሩ ሲወራ ነበር፡፡

የስብሰባው ቀን ሕዝቡ እግር ኳስ የሚያይ መስሎ አዳራሹን ሞላው፡፡ ቦታ የጠበባቸውም በመስኮት በኩል ጉርድ ፎቶ የሚነሡ ይመስል አንገታቸውን ብቻ አስግገው ያጮልቃሉ፡፡ እስካሁን ማንም ሊቀ መንበር ያልተናገረውን ንግግር ሊያደርጉ ነው ስለተባለ ሰው ምን እንደሚናገሩ ለመስማት ጓጉቷል፡፡ በተለይ አንዳንዱ የወረዳው ነዋሪ እንደ ክትባት ለሁሉ የታዘዘ የሚመስል ተመሳሳይ ንግግር መስማት ሰልችቶታል፡፡ ተናጋሪዎች እንደ ኮካኮላ ጠርሙስ አንድ ዓይነት ሆነው  እንደ ተመረቱ ሁሉ እንኳን ቃሎቻቸው ሳሎቻቸው እንኳን ስለሚመሳሰሉ አንዳንዱ ‹ይህንን ንግግር የት ነበር የሰማሁት›› እስከማለት ደርሷል፡፡ አሁን የኛ ወረዳ ሊቀ መንበር ይህንን እንደ ኮንዶሚንየም መልክ የተመሳሰለ ንግግር ሰብረው ሪኮርድ ሊያስመዘግቡ መሆኑን ስንሰማ ተገልብጠን መጣን፡፡

አንድ በስብሰባው ውስጥ ያገኘሁት ሰው ‹‹እነዚህ ባለ ሥልጣናት ግን አንድ ዓይነት ቃላት ከየት ነው የሚያገኙት?›› ብዬ ስጠይቀው ምን እንዳለኝ ታውቃላችሁ ‹‹የባለ ሥልጣናት መዝገበ ቃላት›› የሚባል ያልታተመ መጽሐፍ አለ፡፡ከዚያ ብቻ ነው ቃላት መምረጥ የሚችሉት፡፡ እዚያ ውስጥ የንግግር ቅጽ አላቸው፡፡ ወረዳውን፣ ቀኑን፣ የተሰብሳቢዎቹን ዓይነትና የበዓሉን ስም ብቻ ትቀይርና ንግግሩን ትወስዳለህ›› ብሎ ቀለደብኝ፡፡

አሁን ሊቀ መንበሩ እየገቡ ነው፡፡ ሕዝቡ አጨበጨበ፡፡ ፕሮግራሙን የሚመራው ሰው ማይክራፎኑን ያዘና ‹አሁን ስብሰባችንን የምናከናውንበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡›› ሲል ሕዝቡ አጉረመረመ፡፡ ግራ ገባው፡፡ ‹ይህ ሕዝብ ባይገባው ነው›› ብሎ አዘነልን፡፡ ‹‹ወረዳችን በዕድገት እመርታ ላይ መሆኗን ታውቃላችሁ፡፡ ልዩ ልዩ ጽሕፈት ቤቶችና አጋር አካላት ተሳልጠው በመሥራታቸውና ሙስናንና ብልሹ አሠራን አስወግደን ልማታዊ አስተሳሰብን በማምጣታችን …›› ሕዝቡ ትዕግሥት አጣ፤ አንድ ጎረምሳ እንዲያውም ‹‹ይህንነን ንግግር የዛሬ ሦስት ዓመት ሰምተነው ነበር፡፡›› ሲል ተሰብሳቢው ሳቀ፡፡

አንደኛዋ ወይዘሮማ ‹‹ምነው መንግሥት በየቦታው ተዋንያኑን ብቻ ነው እንዴ የሚቀይራቸው? የፊልሙን ስክሪፕትስ ለምን አይቀይረውም፡፡ ያ ይሄዳል ይሄ ይመጣል፤ ፊልሙ ያው ነው፡፡›› ሳቅና ጭብጨባ አጀባቸው፡፡ ሰውዬው ግራ እንደገባው ነው፡፡ ‹‹ይህ ንግግር ከራሴ የወጣ ነው፡፡ ይህንን ማን ተናግሮት ነው የዛሬ ሦስት ዓመት የሰሙት›› አለ ተገርሞ፡፡ ‹‹ባክህ ሃርድ ዌሩ ነው እንጂ ሶፍት ዌሩ ያው ነው፡፡ ወይ አብዴት አድርጉት ወይ ቀይሩት››  ወጣቱ ሲናገር በዐዋቂነቱ ተጨበጨበለት፡፡

የወረዳችን ሊቀ መንበር አዝማሚያው ስለገባቸው ማይክራፎኑን ከፕሮግራም መሪው ተቀበሉት፡፡ ‹‹ወደ መጣንበት ጉዳይ ብንገባ ይሻላል፡፡›› ሲሉ አንድ ካህን ድምጻቸውን ከፍ አደረጉና ‹‹ልክ ነው ከተአምሩ መቅድሙ ረዘመብንኮ›› አሏቸው፡፡ ሊቀ መንበሩ ፈገግ ብለው ወረቀታቸውን ከቦርሳቸው አወጡ፡፡ አሁን ስፒል ቢወድቅ የሚሰማበት ዝምታ ተፈጠረ፡፡ የሰው ጆሮ እንደ ዲሽ ተዘረጋ፡፡

ሊቀ መንበሩ ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡ ‹ፈጣሪ በቸርነቱ እስካሁን ሀገር አስፍቶ ጠላት አጥፍቶ አኑሮናል› ብለው ሲጀምሩ ሕዝቡ ቀጣዩን እንኳን ሳይሰማ አጨበጨበ፡፡ የተከበራችሁ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ የድርጅት ኃላፊዎች፣ የሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የወጣት ሊግ አመራሮች፣ የሴቶች ሊግ አመራሮች፣ የአነስተኛና ጥቃቅን አመራሮችና አባላት፣ የበጎ አድራጎት ድርጅት ኃላፊዎች፣ የአደረጃጀቶች ኃላፊዎች….. እያሉ እንደ ስም ጠሪ መምህር ወይም እንደ ሙሾ አውራጅ ሲዘረዝሩ ሊውሉ ነው ተብሎ ነበር የተጠበቀው፡፡

‹‹ድርጅታችንም እስካሁን በፈጣሪ ቸርነት፣ በታጋዮች መሥዋዕትነት፣ በአመራሩ ብስለትና በሕዝቡም ይሁንታ ይህንን ሀገር እየመራ መጥቷል፡፡›› ሲሉ ከጎኔ የነበሩት አንድ ሽማግሌ ‹‹ይኼ ነገር የሆነ የሆነ ነገር ሸተተኝ›› አሉኝ፡፡ በዚህ እድሜያቸው የሆነ ነገር ለማሽተት መቻላቸውን አደነቅኩና ‹‹ምን ሸተተዎት›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ቆይ እስኪ ቀጣዩን እንስማው›› አሉ፡፡ እንደ ሬዲዮ አንቴና አንገታቸውን ወደ ላይ መዝዘው፡፡

ሊቀመንበራችን እንደ ቀጠሉ ናቸው ‹‹ደግሞም ሕዝባችን እስካሁን አሳፍሮን አያውቅም፤ ከእንግዲህም ያሳፍረናል ብለን አናምንም›› ሲሉ ጭብጨባው ቀለጠ፡፡ እኒያ ሽማግሌ ግን ወደ ላይ የዘረጉትን የአንገታቸውን አንቴና ወደ ውስጥ ሰበሰቡት፡፡ ከዚያም ራሳቸውን ወደ ቀኝና ግራ ወዘወዙ፡፡ ‹‹ይኼ የተከተፈ ንግግር ነው›› አሉ፡፡ በግራ በቀኝ፣ በፊት በኋላ የተቀመጡት ተሰብሳቢዎች ዘወር ዘወር እያሉ አዩዋቸው፡፡ ሊቀ መንበራችን ግን ቀጠሉ፡፡ ‹‹አሁን ግን አገር የሚያጠፋ፣ ገጽታ የሚለውጥ፣ ዕድገት የሚገታ፣ የሕዝብን ሰላም የሚያናጋ ጠላት መጥቶብናል›› ሽማግሌው አንገታቸውን አውልቀው መጣል ይፈልጋሉ መሰል ከአመድ እንደተነሣች አህያ ያርገፈግፉታል፡፡

‹‹እኛም ብሔር ብሔረሰቦች ፊታቸውን ወደ ልማት ማዞራቸውን፣ ሀገራችንም በአንጻራዊ ሰላም ላይ መሆኗን ተመልክተን፤ ዐቅማችንንም ለልማት እንጂ ለሌላ ነገር ማዋል የለብንም ብለን ዝም ብንለው፤ ደግሞ እያለፈ እንደ ዘንዶ አደጋ ማድረስ ጀመረ››፡፡ ሽማግሌው የአንገታቸው አልበቃ ብሏቸው በጫማቸው መሬቱን ይፎግሱ ጀመር፡፡ ‹‹አሁን ግን ሕዝባችንን አጋዥ አድርገን ሀገራችንን አሳልፈን አንሰጥም በማለት ተነሥተናል፡፡ ሕዝባችን ሆይ እስካሁን የበደልንህ አይመስለንም፡፡ አንተም አልበደልከንም፡፡ ዐቅም ያለህ በዐቅምህ እርዳን፤ ዐቅም የሌለህ ለሚስትህ/ለባልሽ፣ ለእምነትህ ስትል መረጃ በመጠቆም እርዳን፡፡›› አሁን ሽማግሌው እጃቸውን ከእጃቸው ጋር ማፋተግ ጀመሩ፡፡ ሊልጡት ነው እንዴ፡፡ ‹‹ወስልቶ ከዚህ ዘመቻ የቀረ ካለ ግን ይጣላናል፡፡ አንተወውም፤ ድርጅታችንን፤ እንምረውም››

‹‹ኦህ›› አሉ ሽማግሌው፡፡

‹ለዚህ አማላጅ የለንም፡፡ ፀረ ሽብር ዘመቻችን ተጀምሯልና የሀገራችን ሰው በዚሁ ወቅት በየራስህ ከትተህ እናግኝህ፡፡››

ሕዝቡ አጨበጨበ፡፡ ጭብጨባውም ረዘመ፡፡

ሽማግሌው ማንም ሳይቀድማቸው ተሥፈንጥረው ተነሡ፡፡

‹‹እሽ አባቴ›. አሉ ሊቀመንበሩ፡፡ ሽማግሌው ወኔ ይዟቸው የተነሡ መስሏቸው፡፡

‹‹ይህ ንግግር የማን ነው?›› አሉ፡፡ እየተንቀጠቀጡ፡፡ ሰው አጉረመረመ፡፡

‹‹እንዴት ማለት›› አሉ ሊቀ መንበሩ፡፡

‹‹ይህ ንግግር ዐፄ ምኒሊክ ለዐድዋ ዘመቻ ከተናገሩት ንግግር የተወሰደ አይደለም?›› አሉ ሽማግሌው፡፡

‹‹ነው›፡፡ ግን ሬሚክስ አድርጌ በአዲስ አቀራረብ ነው ያመጣሁት፡››

‹‹ምኑን ነው ሬሚክስ ያደረጉት››

‹‹ከዓላማዬ ልጀምርልዎት፡፡ የቀድሞ መሪዎችን ንግግር እንዲህ ሬሚክስ እያደረግን ካላቀረብነው ይረሳሉ፡፡ ትውልዱ አያስታውሳቸውም፡፡ ይህንን ያደረግኩት ለምኒሊክ ክብር ብዬ ነው፡፡ አላዩም ዘፋኞቻችንን፤ የቀድሞ ዘፋኞችን ዘፈን ሬሚክስ እያደረጉ በአዲስ አቀራረብ ሲያቀርቡ፡፡ እኔም እንደዚያው ነው ያደረግኩት፡፡ ሬሚክስ ያደረግኩት ደግሞ የምኒሊክን ባላባታዊ አስተሳሰብ ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰብ ጋር ነው፡፡ በአዲስ አቀራረብ ያልኩት ንግግሩን ልማታዊ፣ ሕዝባዊ፣ ፌዴራላዊ፣ ብዝኃነትን የያዘ አድርጌ ነው ያቀረብኩት፡፡›› አሉ ሊቀ መንበሩ፡፡

‹‹እና ዐፄ ምኒሊክን በአዲስ አቀራረብ አቀረቧቸው ማለት ነው›› አሉ ሽማግሌው፡፡

‹‹አዩ አባቴ ማዘመን ማለት ይኼ ነው፡፡ ታሪክን ማረም ይገባል፡፡ አዲስ መፍጠር ካልተቻለ የነበረውን ሬሚክስ እያደረጉ በአዲስ አቀራረብ ማቅረብ ነው፡፡ ሕዝቡም የሚወደው ይኼንን ነው›› አሉና ወደ ሕዝቡ ሲመለከቱ ጎረምሶቹ ‹‹ሼባው አቦ ተወና፣ እኛ ተመችቶናል›› አሏቸው ሽማግሌውን፡፡

ሽማግሌውም ‹‹በጦርነት ያልጠፋች ሀገር በሬሚክስ መጥፋቷ ነው በሉኛ›. ብለው ተቀመጡ፡፡ በአዲስ አቀራረብ በሬሚክስ ላስደሰቱን ለሊቀ መንበራችን ግን ጭብጨባው ቀለጠላቸው፡፡

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

ህዳር ፲፩(አስራ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የላቸውም በሚል የሳውዲ ፖሊሶች እና ወጣቶች በኢትዮጵያውያን ሴቶች፣ ህጻናትና ወንዶች ላይ የፈጸሙትን የሰብአዊ መብት ጥሰት በመቃወም በተለያዩ የውጭ አገራት የሚካሄዱት የተቃውሞ ሰልፎች እንደቀጠሉ ሲሆን ፣ በዛሬው እለት በስዊዘርላንድ በርን በተካሄደው ተቃውሞ ኢትዮጵያውያኑ ስሜታቸውን ለመቆጣጠር ተስኖአቸው ታይተዋል። ኢትዮጵያውያኑ የሳውዲን መንግስትና የኢትዮጵያን መንግስት የሚያወግዙ …

ህዳር ፲፩(አስራ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጦር ፍርድ ቤቱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው በቅርቡ በኦጋዴን የተፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በተመለከተ፣ የክልሉ የወጣቶች ሊቀመንበርና የፕሬዚዳንቱ የግል ዌብሳት ማኔጀር እና አማካሪ የነበረው ወጣት አብዱላሂ ሁሴን በኦጋዴን የጦር ወንጀልና የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መፈጸሙን የሚያሳይ ማስረጃ ለፍርድ ቤቱ አቃቢ ህግ ማቅረቡን ተከትሎ ነው። የጦር ፍርድ ቤቱ ዋና …

ተመስገንደሳለኝ

በረዥሙ የኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ታሪክ፣ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ አንድም ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ሁሉም መንግስታት የተወገዱት በአመፅ አሊያም በተፈጥሮ ሞት ነውና፡፡ በ1983 ዓ.ም ወርሃ ግንቦት በጠብ-መንጃ ኃይል ሥልጣን የተቆናጠጠው ኢህአዴግ-መራሹ መንግስትም ቢሆን፣ በቀድሞዎቹ ገዥዎች ‹የብረት ጫማ› ውስጥ ተከልሎና ተደላድሎ ዕለተ-ስንብቱን በመጠባበቅ ላይ ያለ ይመስለኛል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነብዩሲራክ

ትናንት እንደ ቀልድ …
በያዝነው የፈረንጆች 2013 ዓም በወርሃ መጋቢት አጋማሽ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ” ህጋዊ ሰነድ ያልያዙትን አስወጣለሁ !” ብላ አወ ች ። ቀጠለና አፈሳ አሰሳው ተከተለ! አስፈሪው ያ ክፉ የጭንቅ ቀን በሳውዲው ንጉስ ሌላ የምህረት አዋጅ ተተክቶ ህገ ወጥ የተባሉትን ህጋዊ በሚያደርግ ህግ ተተካና የምህረቱ አዋጅ በያዝነው ህዳር መባቻ እንደሚያልቅ በተጠቆመው አዲስ የምህረት አዋጅ ተተካ !

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወደብ ኣልባዋ ኢትዮጵያ ለወጪ እና ገቢ ሸቀጧ ከሞላ ጎደል የምትጠቀመው በጂቡቲ ወደብ እንደሆነ ይታወቃል። ከዚሁ የተነሳ በጂቡቲ ወደቦች ከሚስተናገዱት ገቢና ወጪ ምርቶች ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውም የኢትዮጵያ ሸቀጦች እንደሆኑ ይገመታል።

የአየር ንብረት መለዋወጥ ዓለምን እያሰጋ ያለ ጉዳይ መሆኑ ይታወቃል። በከባቢ ሙቀት መጠን መጨመር ምክንያት ፤ የጎርፍ፤ የአዉሎ ነፋስ፤ የባህር ላይ ማዕበል አደጋዎች፤ በዓለማችን በተለያዩ ቦታዎች መከሰታቸዉ ነባራዊ ሁኔታ ነዉ። እነዚህን አደጋዎች ለመከላከል፤ እንዲሁም

ውዝግብ ከሚታይባቸው አካባቢዎች በሚወጣ የአልማዝ ማዕድን ንግድ አንፃር የተጀመረውን ትግል የማጠናከር ዓላማ የያዘው በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ « ኬ ፒ ሲ ኤስ » በመባል የሚታወቀው « የኪምበርሊ ፕሮሰስ ሰርቲፊኬሽን ስኪም »

የስዑድ አረቢያ መንግስት ያለ ሕጋዊ ፈቃድ በግዛቱ ይኖሩ የነበሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዉጭ ሀገር ዜጎች ፈቃዳቸዉን እንዲያስተካክሉ የሰጠዉ የምህረት ጊዜ ካለቀ በኋላ ባጠናከረችዉ አሰሳ በሺዎች የሚቆጠሩትን ወደየመጡበት መመለሱን ተያይዛዋለች።

ዐረቢያ፥ ረቢያ፥ የቄዳር ግፊያና ግፍ።
ኅዳር ፱ ቀን ዓ. ም.
ከእስልምና እምነት መምጣት በፊት ዐረቦች የሚኖሩት መካ፣ ያትሪብ፣ መዲና ወዘተ ተብለው ይጠሩ
በነበሩ ሠፈሮች አካባቢ ነበር። ዐረቦች የአስተዳደር ሥርዓት ፣ የህግ ሥርዓት ወይም የእደ ጥበብ
ስምሪት አልነበራቸውም። መንግሥትና መንግሥታዊ አስተዳደር የሚባል ነገርም አያውቁም ነበር።1
ቁሬሺ፣ ባኑ ሃሺም፣ ባኑ ኡማያ ወዘተ በሚባሉ ጎሳዎች ተለያይተው ግን ይጣሉ ነበር።2 ጣዖት
አምላኪዎችም ነበሩ። ካባ የተባለ ድንጋይም ያመልኩ ነበር። እስከ አራት መቶ ዓ.ም. አካባቢ ዐረቦች
ለሚናገሩት ቋንቋ መፃፊያ ፊደል አልነበራቸውም። ከእስልምና መምጣት አስቀድሞ በንግግር ግጥም
መፎካከር የዐረቦች ባህል ነበር።3 እጅግ በጣም ግጥም የሚገጥመውን ሰው መጅኑን እያሉ ይጠሩት ነበር። ዐረቦች
ከእስልምና በፊት የነበረውን ዘመን ጃሂሊያ ወይም የድንቁርና ዘመን ብለው ይጠሩታል።
በዚህ ጊዜ ነበረ አንድ ሙሀመድ የሚባል ዐረብ መካ አጠገብ በሚገኜው የሂራ ኮረብታ ላይ ሳለሁ ጅብሪል ነገረኝ
ብሎ አዲስ እምነት በአቅራቢያው ላሉ ሰዎችና ለዘመዶቹ የሰበከው። በልዩ ልዩ የምዕራባዊ ትረካዎች እንደሚነገረው
ሙሀመድ በሂራ ኮረብታ ላይ ጅብሪል ነገረኝ ካለበት ጊዜ በፊት እሱ በሚኖርበት አካባቢ ክርስትናን ለማስፋፋት
ክርስቲያኖች ብቅ ይሉ እንደነበረ ይነገራል። ከነዚህም ውስጥ ዋናዎቹ ኢትዮጵያውያን ነበሩ። ከኢትዮጵያውያንም
መካከል የሂመራ (የየመን) ንጉሥ አብርሃ ዐረቦች ወደ ሰንዓ መጥተው በሰንዓ የተገነባውን ትልቁን የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በግቢው ተደብቀው በመጸዳዳት ባረከሱ ጊዜ ዐረቦቹን ለመቅጣትና የመካን የካባ
ጣዖት ለማፍረስ ሥንቅ በዝሆኖች ጭኖ ያደረገው ዘመቻ ይታወሳል።4 ሙሀመድ ይዞት ለተነሳው እምነት መሠረተ
ሃሳቡን ያገኘው ክርስትናን ለማስፋፋት እሱ ወደሚኖርበት አካባቢ ከሄዱ ኢትዮጵያውያን የወንጌል አስተማሪዎች
መሆኑን በእስልምና እምነት በተለይም በቁርአን ውስጥ ያሉ ጭብጦች ያመለክታሉ።
የእስልምና እምነት ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ “ኢሳ” የሚባል ስም ነው የተሰጠው። በሌሎች አገሮች የነበሩ
ወንጌላውያን ኢየሱስ ክርስቶስን፥ “የሽዋ” ወይም “ሄሱስ” ወይም “ጀሽዋ” ወይም “ጂሰስ” ወይም “አየሱስ” እያሉ
ነበር የሚጠሩት። በእስልምና ውስጥ ላለው “ኢሳ” ለሚለው ቃል በጣም የሚቀርበው የግዕዙ “ኢየሱስ” ሲሆን
ቀጥሎም የግሪኩ “አየሱስ” ነው። ሙሀመድ ቃሉን ከግዕዙ ወይም ከግሪኩ መውሰዱን ለመለየት ቀላሉ ማነጻጸሪያ
ሙሀመድ “ማርያም” የሚለውን ቃል ከየት እንዳገኜው መለየት ነው። በእስልምና “ማርያም” የሚለው ቃል ድንግል
ማርያምን ለመጥራት የሚጠቀሙበት ሲሆን ቃሉ በግሪክ “ማሪያ” የሚል ሲሆን በግዕዝ ደግሞ “ማርያም” ነው።
ለድምዳሜ በቂ ባይሆኑም ከዚህ አጠራር በቀላሉ ሙሀመድ ቃሉን ከግዕዝ ሰዎች እንዳገኘው መንገዱን ያሳያል።
እብራይስጥና ግዕዝ ተቀራራቢ በመሆናቸው ምክንያት አጋጣሚውን በመጥለፍ አንዳንድ ታሪክን ለመሠሪ ዓላማ
ለመጠቀም የተነሱ ምዕራባውያን እና አይሁድ ነን ባዮች ሙሀመድ የእስልምና እምነትን መሠረተ ሃሳብ ያገኘው
ከአይሁዶች ነው ለማለት ይቃጣቸዋል። ነገር ግን ሙሀመድ ሃሳቡን ከአይሁዶች እንዳላገኘው ብዙ ማስረጃወችና
አመልካቾች አሉ። በመጀመሪያ አይሁድ በኢየሱስ ክርስቶስ አያምኑም። ስሙንም አይጠሩም። እንኳን አምላክ ነቢይ
ነውም አይሉም። ቅድስት ድንግል ማርያምንም በእምነታቸው አያውቋትም። በተጨማሪ “ኤልያስ” የሚለውን
መጠሪያ እስላሞች የሚጠሩት እንደ ግዕዙ “ኤልያስ” ብለው እንጂ እንደ እብራይስጡ “ኤልያሁ” ብለው
አይደለም። በተለይም ደግሞ የእስላሞች ቁርአን መጠሪያው “መጽሐፍ” ተብሎ ነው። “መጽሐፍ” የዐረብኛ ቃል
አይደለም ከግዕዝ ውጭ በሌላ ቋንቋ ውስጥም አይገኝም። እስልምና ይህን ቃል የወሰደው ከግዕዝ ነው።
ከሁሉም በላይ ደግሞ አዲሱን እምነቱን እንዳያስፋፋ በመካና በመዲና ተቃውሞ ሲያጋጥመውና በዳሩል ናድዋ
የተሰበሰቡት የቁሬሺ ጎሳ ባላንጣዎቹ ተከታዮቹን ሊገድሉ ሲያሳድዷቸው ፥ ሙሀመድ ለተከታዮቹ፣ “ፍትህን
ሳያጓድል የሚያስተዳድር ደግ ንጉሥ በእውነት ምድር በሐበሻ አገር ይገኛልና ወደ እርሱ ሂዱ። ያስጠጋችኋል።”5
አላቸው። ተከታዮቹም ወደ አክሱም ተሰደዱ። ንጉሠ ነገሥቱም ተቀብለው አስትናገዷቸው። እዚህ ላይ ትኩረት
የሚያስፈልገው “የሐበሻው” ንጉሥ ደግ መሆናቸውን ማን ነገረው? ፍትሕን ሳያጓድሉ የሚፈርዱ መሆናቸውንስ
እንዴት አወቀ? የሚለው ጥያቄ ነው። ከአይሁድ ወይም ከግሪክ ወይም ከፋርስ ወደ ዐረብ አገር የሚመጡ ሰዎች ስለ
“የሐበሻ” ንጉሥ ደግነት ሊነግሩት አይችሉም። ስለ ኢትዮጵያ ንጉሥ ደግነት ለሙሀመድ ሊነግሩ የሚችሉት
ከኢትዮጵያ ወደ ዐረቦች ሠፈር የሄዱ ኢትዮጵያዊ የክርስትና ተከታዮች ወይም የወንጌል መምህራን ናቸው።
እንግዲህ እነዚህ መረጃዎች የሚያሳዩት ሙሀመድ እስልምናን ለወገኖቹ ለመስበክ መነሻ የሚሆነውን ትምህርት
ያገኘው ከኢትዮጵያውያን መሆኑን ነው።
2
የሙሀመድ ተከታዮች አክሱም እንደደረሱ መልካም መስተንግዶ እንደተደረገላቸው የዐረብ ተራኪዎች
እራሳቸው ዘወትር ይመሰክራሉ። በተለይም ደግሞ ቁሬሺ የሚባሉት የሙሀመድ ተቃዋሚዎች አክሱም ድረስ
ለንጉሠ ነገሥቱ እጅ መንሻ ይዘው በመምጣት በሽሽት የመጡት የሙሀመድ ተከታዮች ወንጀለኞች ናቸውና
ስጡን፣ ወደ ዐረብ አገር መልሰን እንውሰዳቸው ብለው ሲጠይቋቸው ንጉሠ ነገሥቱ የሁለቱንም ወገን ቃል ካዳመጡ
በኋላ ስደተኞቹን አሳልፌ አልሰጥም ማለታቸው እስካሁን ይነገራል። እነዚህ የሙሀመድ ተከታዮች የሆኑ ስደተኞች
ወደ ዐረቦች አገር ቢመለሱ አደጋ ላይ እንደሚወድቁ ያዩት ነጉሠ ነገሥቱ ስደተኞቹ በሂመራ (የመን) እንዲሠፍሩና
እንዲኖሩ ፈቀዱላቸው። አሁንም እዚህ ላይ ከላይ የተጠቀሱት ነዳጅ ፈላጊ ሃሰተኛ ምዕራባዊ ተራኪዎችና አይሁድ
ነን ባዮች ከእስልምና በፊት የመንን ፋርሶች አጥቅተው ይዘዋት ነበር የሚል ሃሰት ይተርካሉ። ከነሱ የሃሰት ትረካ ሌላ
እነሱ ለሚሉት ነገር ጭብጥ ማስረጃ የለም። የመን የኢትዮጵያውያን ምድር እንደነበረችና በውስጧም
ከኢትዮጵያውያን በቀር ዐረብ የሚባል ጎሳ እንዳልነበረባት፣ ዐረብኛ ቋንቋም እንዳልትነገረባት፤ ይልቁንስ የሂመራ
ሰዎች የሚናገሩት ቋንቋ፣ የሚጽፉትም ጽሁፍ ግዕዝ እንደነበረ፣ ባህላቸውም “የሐበሻ” እንደነበረ የሚያረጋግጡ
በጣም በርካታ ማስረጃዎች አሉ። የሙሀመድ ተከታዮች በኢትዮጵያ ከተሰደዱ በኋላ ጊዜው ሲረጋጋ አንዳንዶቹ
እየተመለሱ እስልምናን አስፋፉ። ከሞት አፋፍ ላይ ደርሶ የነበረው እስልምና በኢትዮጵያው ንጉሥ ደግነት ምክንያት
እንደገና አንሰራራ።
እንግዲህ ይህን የመሰለ መስተንግዶ የተደረገላቸው ዐረቦች ግን እስልምናቸውን ሲያስፋፉም ሆነ ሲገድሉ፣ በመሬት
ንጥቂያም ላይ ሲሰማሩ ርኅራኄ ያደረገችላቸውን ኢትዮጵያ በርኅራኄ ዐይን አይተዋት አያውቁም። ብዙ ዐረቦች
“ኢትዮጵያ ስላስጠጋቻችሁ እሷን አትንኩ” ብሎ ሙሀመድ ተናግሯል ሲሉ ይደመጣሉ። ይሁንና ከእስልምና በኋላ
ዐረቦች ኢትዮጵያን ሳይነኩ የሰነበቱበት ዘመን የለም። ከእስልምና ማንሰራራት በኋላ ኢትዮጵያ በእስልምና
የደረሰባትን ውድቀት ሲመለከቱ ንጉሠ ነገሥቱ ለነዛ ለተሰደዱ ዐረቦች ያደረጉላቸው መስተንግዶ ከደግነትም አልፎ
የየዋህነት እንደነበር አዙሮ ለሚያይ ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል። ንጉሠ ነገሥቱ እጃቸውን ዘርግተው ዐረቦቹን
መቀበላቸው ለኢትዮጵያ ተናዳፊ እባብን እጅ ዘርግቶ እንደመቀበል ነው የሆነባት።
የመንን ወሰዱ። ኢትዮጵያውያንን አረዱ። የቀሩትንም መንገድ ላይ ጣሏቸው።
ከተደረገላቸው ከዚህ ሁሉ ቸርነት በኋላ ዐረቦች እስላምናን
ለማስፋፋትና የሌሎችን መሬቶች ለመንጠቅ ሲሰማሩ የመጀመሪያ ሰለባ
ያደረጉት የኢትዮጵያን አውራጃ ሂመራን (የመንን) መውረርና የራሳቸው
ማድረግ ነበር። ዐረቦች በሂመራ ኢትዮጵያውያን ላይ የሠሩት ግፍ
ምዕራባውያን አፍሪካውያንን በባርነት ቀንበር ከገዙበት ግፍ ቢበልጥ
እንጂ አያንስም። ዓረቦች ሂመራን (የመንን) ሲወሩ መጀመሪያ በሰንዓ
የሚገኘውን እጅግ የተዋበውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ህንፃ
ቤተክርስቲያን ነበር ያፈረሱት። ክርስቲያኖችንም አረዱ። የቀሩትን
ኢትዮጵያውያን አስገድደው አሰለሟቸው። በባርነትም ገዟቸው።
የመንንም አጥለቀለቋት። እጅግ የሚዘገንኑ ግፎችንም በኢትዮጵያውያን ላይ ፈጸሙባቸው። ልጆቻቸው
ታሪካቸውን እንዳያውቁ አደነቆሯቸው። የሚበሉት፣ የሚጠጡትና የሚለብሱትም አሳጧቸው። አክሃዳም
(ጠራጊወች) የሚል ስምም አወጡላቸው። አክሃዳሞች ከሽንት መጥረግና ከጫማ ማጽዳት ውጭ ሌላ ሥራ
አይፈቀድላቸውም፡፤ ልጆቻቸውም አይማሩም። ዐረቦች “እቃህን ውሻ ቢነካው እጠበው፤ አክሃዳም ከነካው ግን
ጣለው”¶ የሚል ፈሊጥ አወጡላቸው። ዐረቦች አክሃዳም እያሉ የሚጠሯቸውን ሥራና ትምህርት ብቻ ሳይሆን
የከለከሏቸው ሰው መሆንን ጭምር ነው።
ከየመን ወረራ በኋላ ዐረቦች እስልምናን በማንገብ የሌሎች ሰዎችን
መሬቶች ለመንጠቅ ወደ ሰሜን አፍሪካ፣ ወደ መካከለኛው
ምስራቅና ወደ ፋርስ ዘመቱ። የተከላከሏቸውን በጎራዴ እያረዱ
ገደሉ፣ የቀሩትን እስላም አደረጓቸው፣ መሬታቸውንም ሁሉ
ወሰዱ። በተለይ ጥቁሮችን በማጥፋት ከሲሶ በላይ የሚሆነውን
የአፍሪካ መልክዓ ምድር በንጥቂያ ወሰዱ። ኢትዮጵያን በዙሪያዋ
ከበቧት። በግድም በውድም ብዙ ኢትዮጵያውያንን አሰለሙ። በዳር ድንበርም በማህል አገርም ያሉ
ኢትዮጵያውያንን ካሰለሙም በኋላ የክርስቲያን መንግሥት ስለሆነ ለመካከለኛው መንግሥት አትገዙ፣
ጎጦቻችሁንም ከመካከለኛው መንግሥት ገንጥሉ የሚሉ ፋትዋዎችን በመደንገግ ሙስሊም የሆኑትን
3
ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ላይ ለጦርነት በማነሳሳት ኢትዮጵያን በአመጽ ለብዙ መቶ ዓመታት አስጨነቁ።
የባህር በሮቿንም ያዙ።
ዐረቦች ቆስጠንጥኒያ ተብሎ የሚጠራውን አገር በንጥቂያ ከወሰዱ በኋላ ኦስማንየ የሚባል የቱርክ የእስልምና
መንግሥት ተቋቁሞ እሱም በመስፋፋትና እስልምናን በማስፋፋት ብዙ የዓለም ክፍሎችን ይቆጣጠር ጀመር።
ኦስማንየ የተባለው የእስልምና ቀንበር ጫኝ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን መሣሪያ
በማስታጠቅ ኢትዮጵያን ለብዙ አመታት በአመጽና በጦርነት አደቀቁ። በተለይም አህመድ ግራኝ በመባል
የሚታወቀውን ሙስሊም በማስታጠቅ ከምሥራቅ ኢትዮጵያ እስከ ሰሜን ኢትዮጵያ ድረስ በጦርነት አመሷት።
አብያተ ከርስቲያናትን አወደሙ። ቅዱሳን መጻሕፍትን አቃጠሉ። ካህናትን እና ምእመናንን አረዱ። የኢትዮጵያ
ንጉሠ ነገሥት የዐረብ ስደተኞችን ካስተናገዱ ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በችግር፣ በጦርነትና በሰላም ማሳጣት
ዐረቦች እንዳመጡት እስልምና ኢትዮጵያን ያዎካት የለም። የዐረቦች እስልምና አዋኪነቱ በማበጣበጥ ብቻ የተገታ
አይደለም። ታሪክንም በመበረዝ ጭምር ነው።
በተለይ ባለፉት ሃምሳ አመታት በዐረባዊው በግብጽ መንግሥትና ካይሮ በሚገኘው የዓለም ሙስሊሞች
እንዲከተሉት የእስልምና መመሪያ ወይም ፋትዋ ማፍለቂያ ማእከል በሆነው በአል አዛር ተቋም አበረታችነት
በኢትዮጵያ የተኪያሄዱት ሁከቶች ኢትዮጵያን ትልቅ አደጋ ላይ የጣሉ ነበሩ። ይህ የዐረቦች የአመጽ ጥንስስ
በኢትዮጵያ ብዙ ደም ካፈሰሰ በኋላ “ኤርትራ” ተብላ የምትጠራውን የኢትዮጵያ አካል ከነነዋሪዎቿ ከኢትዮጵያ
ገንጥሏል። በእስልምና ስም የሚመጣው የዐረቦች የብጥብጥ እርሾ በማሀል አገር፣ በምሥራቅ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ
ኢትዮጵያ፣ በሶማሊያ ወዘተ እስካሁን ድረስ ጥፋቱን እንደቀጠለ ነው።
ዐረቦች እስልምናን ተጠቅመው በሚፈጥሩት ሁከት ምክንያት ኢትዮጵያ በመታመሷና ድህነትም ላይ በመውደቋ
በተለይ ባለፉት አርባ አመታት ውስጥ ብዙ ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ኢትዮጵያን ትተው በመሰደድ በተለያዩ
የዓለም አገሮች ተበታትነዋል። ከነዚህም ውስጥ ጥቂቶቹ ወደ ዐረቦች አገር ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ ተሰድደው በዛ እስከ
አሁን ይኖራሉ። ሆኖም ግን ከዚህ ቀደም በታህሳስ ወር &frac12; ዓ.ም. ሰላሳ አምስት የሚሆኑ የኢትዮጵያ
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምእመናን የክርስቶስን ልደት በቤታቸው ተሰብስበው ስላከበሩ የሳዑዲ ዐረቢያ መንግሥት
እነዚህን ክርስቲያኖች በእሥራትና በድብደባ ካንገላታቸው በኋላ ክሳዑዲ ዐረቢያ አባሯቸዋል።6 ዐረቦች
የመጀመሪያው ሂጅራ እያሉ በሚያስታውሱት ስደታቸው ከዐረብ አገር ተሰድደው ወደ ኢትዮጵያ መጥተው
ኢትዮጵያውያን ላደረጉላቸው አቀባበል፣ የተሰደዱትንም ችግር እንዳያገኛቸው በኢትዮጵያ እንዲኖሩ መልካም
መኖሪያ ለሰጧቸው ኢትዮጵያውያን የከፈሉት ውለታ እነሆ ኢትዮጵያውያን በዐረቢያ በተሰደዱ ጊዜ ዱላ፣
እሥራትና ካገር ማባረር ሆነ። ዛሬም እንደትናንትናው ዐረቦች
ኢትዮጵያውያንን የማጥቃትና የማዋረድ ሥራቸውን
ቀጥለውበታል። በተለይ ሰሞኑን በሳዑዲ ዐረቢያ
ኢትዮጵያውያንን እያሳደዱ በመያዝ እየደበደቡ አጉረዋቸዋል።
አንዳንዶችንም ገድለዋቸዋል። ኢትዮጵያውያን ሴቶችን
ከቤታቸው እያወጡ አስራ አምስት እና ሃያ እየሆኑ ሰብአዊነት
በሌለው ሰይጣናዊ ሁኔታ ደፍረዋቸዋል። ከቤታቸውም
ከተሰደዱበትም ቦታ እያወጡ ጥለዋቸዋል። የርኅራኄ መስተንግዶ
የተደረገላት ቄዳር ግፍን መለሰች። በቄዳር ድንኳኖች ውስጥ
ያላችሁት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኢትዮጵያውያን
ወንድሞቻችሁንና እህቶቻችሁን ተመልከቱ። ሰላምን ከሚጠሉ ጋር ነፍስ ብዙ ጌዜ ኖረች። ኢትዮጵያ ማረፊያ ሰጥታ
ሰላምን ለቄዳር ልጆች ሰጠች፣ የቄዳር ልጆች ግን ስላምን ነሷት። መኖርያቸው ለራቀ፣ በቄዳር ድንኳኖች ላደሩ
ወዮ፥ እግዚአብሔር ተናግሯልና እንደ ምንደኛ ዓመት በአንድ ዓመት ውስጥ የቄዳር ክብር ሁሉ ይጠፋልና።
እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
1 Muller, Herbert J.: The Loom of History, 1958
2 Grunebaum, G. E.: Classical Islam – A History 600-1258 – 1970
3 Margoliouth, D.S.: Mohammed and the Rise of Islam, 1931
4 Discover True Islam: free-minds.org
5 Safieddine, Shahnaze: Migration to Abyssinia & Wikipedia, the free encyclopedia
6 Nazret.com: Saudi Arabia Deports 35 Ethiopian Christians for Praying, August 4, 2012

ሳውዲ አረቢያ በተለይም በመንፉሃ ሪያድ የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ መረጃዎችን ስንለዋዎጥ ባጅተናል ። አሰቃቂውን የወገን ጉዳት አብረን አውግዘን ፣ ወገኖቻችን ደራሽ ያገኙ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ በመላ አለም ያሰማነው ድምጽ ፍሬ አፍርቷል ! ደስ ሲል … በሁከቱ የተፈጠረውን ችግር ፣ የፈሰሰውን እንባና ደም የአይን ምስክሮችን በአካል ላነጋገረና ህመሙን ሲታመም ለከረመ የእኔ ቢጤ ዛሬ የተገፊው ወገን […]