Amharic News 1800 UTC – ኖቬምበር 16, 2013
News, Call-in show or special interviews and Ye Musica Qana
News, Call-in show or special interviews and Ye Musica Qana
የኬንያ እና የሶማልያ መንግሥታት በኬንያ ከለላ ያገኙ ከ500,000 የሚበልጡ የሶማልያ ስደተኞችን ወደ ትውልድ ሀገራቸው ለመመለስ ከተመድ የስደተኞች ጉዳይ ተመልካች መሥሪያ ቤት፣ በምሕፃሩ «ዩ ኤን ኤች ሲ አር» ጋ አንድ ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።
የዓለም ዜና

በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው መከራ መስማት ህሊና መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኗል። ኢትዮጵያዊን እህቶቻችን ወንድሞቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ፤ አካሎቻቸው በስለት እየተቆራረጠ፤ እየተደበደቡና እየተደፈሩ ነው።
ይህ ሁሉ የሚፈፀው በሪያድ፣ ጂዳና አዲስ አበባ የሚገኙ የወያኔ ዲፕሎማቶች መልካም ፈቃድና ሙሉ ተባባሪነት መሆኑ ደግሞ ይበልጥ የሚያንገበግብ ነው። ወያኔ ለአረብ ሀብታም ሸሪኮቹ ለም መሬቶቻችንን ሰጥቶ ኢትዮጵያዊ በአገሩ ሠርቶ የእለት ጉርሱን መሸፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ አደረገው። ቀጥሎ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ልጃገረዶችና ወጣት ኢትዮጵያንን እየደለለ ከባርነት ላልተሻለ ግርድና አሳልፎ ሰጣቸው። ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ “በሏቸው፤ ቀጥቅጧቸው፤ ህገወጦች ናቸው” እያለ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ በአጋፋሪነት እያስተናገደ ነው።
በኩየት በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሊደርስ የሚችል መሆኑ ምልክቶች እየታዩ ነው። በኩዌት ያለአንዳች ምክንያት ቁጥራቸው በአንድ ሺህ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በድንገት ከሥራ ተባረዋል። እዚህም የወያኔ እኩይ እጆች እንዳሉት መረጃዎች አሉ። በሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም ሕይወታቸው በዘወትር ስጋት ላይ ወድቋል።
የኢትዮጵያዊያን እጣ ፈንታ በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ሰቆቃና እንግልት መሆኑ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያስቆጭ፤ ለመራራ ትግል የሚያነሳሳም ነው። ለአገሩ ሕዝብ የሚቆረቆር መንግሥት ኑሮን ቢሆን ኖሮ ሕይታችን እንዲህ የተመሰቃቀሰ ባልሆነም ነበር።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሳውዲ አረቢያ እና ሌሎችም የመካከለኛ ምሥራቅ አገራት መንግሥታት ለኢትዮጵያዊያን እህቶቻንና ወንድሞቻችን ሰብዓዊ ክብር እንዲሰጡ አበክረን እናሳስባለን። ሰብዓዊ መብቶችን መድፈር ዓለም ዓቀፍ ወንጀል መሆኑን ልንነግራቸው እንፈልጋለን። በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ አሁኑኑ ይቁም!!! ሰቆቃ ፈፃሚዎች ለፍርድ ይቅረቡ!!!
በተቻለው ፍጥነትና ባገኘነው እድል ሁሉ ተጠቅመን ሕይወታቸው አደጋ ላይ ላሉት ወገኖቻችን እንድንደርስ ግንቦት 7 ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ያደርጋል።
በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በዘላቂነት የሚወገደው ወያኔ ከሥልጣን ተባሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመረጠው መንግሥት ሲያስተዳድር በመሆኑ ለዚህ ታላቅ ግብ በኅብረት እንነሳ።
በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ይቁም!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
Ethiopian national soccer team – ready for away match with Nigeria’s counter part
Ethiopia, terrorism charges, ginbot 7
Semayawi Party, Medrek,Saudi, Ethiopians, demonstrations
ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz
ህዳር ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ያለው ግፍ ተባብሶ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ የሳውዲን መንግስት ለመቃወም በሳውድ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ተቃውሞዋቸውን ለመግለጽ የወጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በፌደራል ፖሊሶች ተደብድበዋል። ከ100 በላይ ሰዎች ታስረው የነበረ ሲሆን እስከ ምሽት ድረስ 40 የሚሆኑት ተለቀዋል። ሰልፉን ያዘጋጀው የሰማያዊ ፓርቲ 15 የአመራር አካላትም በእስር ላይ …
ላለፉት ሰባት ዓመታት በዐረብ ሀገር የኖረችና ከአራት ወራት በፊት ነዋሪነቷን በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገች ወጣት ኢትዮጵያዊት፣ ከኢትዮቲዩብ ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ በዐረብ ሀገር የነበራትን ቆይታ፣ በሀገር ቤትም ያለውን ችግር፣ የኢትዮጵያን ኤምባሲ በተመለከተ በግሏ የደረሰባትን ስትገልጽ ልብ ትሰብራለች። ትናንት ኅዳር 5 ቀን 2006 ዓ.ም. (ኖቨምበር 14፣ 2013 እ.ኤ.አ.) ዋሽንግተን ዲሲ በሳዑዲ ዐረቢያ ኤምባሲ በርካታ ኢትዮጵያውያኖች የተቃውሞ ሰልፍ ባደረጉበት ወቅት ነበር ኢትዮቲዩብ ያናገራት።
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ሣዑዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያዊያን ላይ “ተፈፅሟል፣ እየተፈፀመም ነው” ያለውን ግፍ በመቃወም ዕሁድ፤ ኅዳር 8/2006 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡
የሰልፍ ዕውቅና የሚሰጠው ክፍል ግን በቃል አሉታዊ መልስ እንደሰጠው አስታውቋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ሰማያዊ ፓርቲ ሳዑዲ አረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር በመቃወም የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ፡፡
አዲስ አበባ በሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አቅራቢያ በተሰባሰቡት ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ “ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እሥር ተፈፅሟል” ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ድርጊቱን አውግዟል፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር በበኩሉ ለቪኦኤ በሰጠው ቃል ሰልፉ “ሕገወጥ ነው” ብሏል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ አዘጋጆቹ “ከሚመለከተው ክፍል ፍቃድ…
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከፍበኛ መሻሻል ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ፈባጠን አካሄድ አፍሪካን አልፎ በቀሪውም ዓለም መድረክ ሊያሣትፈው የተቃረበ ይመስላል፡፡
ነገ፣ ቅዳሜ ኅዳር 7/2006 ዓ.ም ከናይጀሪያ አቻው ጋር በሚያደርገው የመልስ ግጥሚያ አስፈላጊውን ሁሉ አሟልቶ ካሸነፈ በመጭው ሰኔ ብራዚል በምታስተናግደው የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ አህጉሪቱን ከሚወክሉ አምስት የአፍሪካ ብሔራዊ ቡድኖች አንዱ ይሆናል ማለት ነው፡፡
ለዚህ ወሣኝ ፍልሚያ ቡድኑ “ብቃት ያለው ዝግጅት አድርጌአለሁ” ይላል፡፡
ሰሎሞን ክፍሌ የነገው የመልስ ጨዋታ ወደሚካሄድባት የናይጀሪያ ከተማ ካላባ ደውሎ የቡድኑን ዋና አሠልሐኝ ሰውነት ቢሻውንና ሌሎችም የቡድኑን አባላት አነጋግሯል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
ፌደራል አቃቢ ሕግ “የግንቦት ሰባት አባል በመሆን” ና “የሽብር ወንጀል ፈፅመዋል” ሲል በሃያ ሰዎች ላይ ክሥ መሥርቷል፡፡
ሰዎቹ መቼ እንደታሠሩ ግን አልገለፀም፡፡
ጉዳዩ እየታየ ያለው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ሲሆን ተከላካይ ጠበቃ ያቀረበው የክሥ መቃወሚያ በፍርድ ቤቱ ውድቅ ሆኗል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የአንዳንድ ተከሣሾች ጉዳይ በሌሉበት መታየት ጀምሯል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የመለስካቸው አምኃ ዘገባ ያዳምጡ፡፡
News, Community Heroes or Call-in, Crossfire and African Topics
ሐኪሞቹና ረዳቶቻቸዉ አዲስ አበባና ደብደረ ብርሐን ከተሞች በሚገኙት ሆስፒታሎች ዉስጥ በማሕፀን፥ በኩላሊትና በአይን ሕመም ይሰቃዩ ለነበሩ በሺሕ ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን የቀዶ ሕክምና ርዳታ አድርገዋል
አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።
የዓለም ዜና
ያለንን ችሎታ ማካፈል እንፈልጋለን ይላሉ። ችሎታቸውም እግር ኳስ መጫወት ነው።
ማምሻውን በደረሰን መረጃ
ሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ የደረሰውን በድል እና ስቃይ ለመቃወም አዲስ አበባ በተጠራው ሠላማዊ ሠልፍ የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሶች አሰቃቂ ድብደባና እሰር መፈፀማቸው ቀደም ተብሎ መገለፁ የሚታወቅ ነው፡፡ አሁን በደረሰን መረጃ ቁጥራቸው ወደ 100 የሚጠጉ እስረኞች የተለቀቁ ሲሆን ፤ከነዚህም መካከል ጋዜጠኞች እንደሚገኙበት ለማወቅ የተቻለ ሲሆን የተቀሩት ማለትም፡-
1ኛ. ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የፓርቲው ሊቀ/መ
2ኛ. አቶ ስለሺ ፈይሳ የፓርቲው ም/ት ሊቀ/መ
3ኛ. አቶ ወረታው ዋሴ የፓርቲው የፋይናስ ጉዳይ አላፊ
4ኛ. አቶ ጌታነህ ባልቻ የፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ አላፊ
5ኛ. አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አላፊ
6ኛ. አቶ ዮናታን ተስፋዬ የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ አላፊ
7ኛ. አቶ አብታሙ ደመቀ የብሔራዊ ም/ቤት አባል
8ኛ. አቶ ዮናስ ከድር የብሔራዊ ም/ቤት አባል
9ኛ. ዮሴፍ ተሻገር የብሔራዊ ም/ቤት አባል
10ኛ. ወጣት አቤል ኤፍሬም አባል
11ኛ. ሰለሞን ወዳጄ አባል
12ኛ. ፋሲካ ቦንገር አባል
13ኛ. መርከብ ሀይሌ አባል
14ኛ እመቤት ግርማ አባል
15ኛ. አስራት አብርሃም ደራሲና ጻአፊ (በግል)
16ኛ. ዳዊት ፀጋዬ ደራሲና ጻአፊ (በግል)
17ኛ. እየሩስ ተስፋ አባል
18ኛ. ንግስት ወንድኢፍራው አባል
ከላይ በስም ዝርዝ የተገለፁ እስካሁን መስቀል ፍላወርና ፒያሳ ማዘጋጃ አካባቢ በሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ ሲሆን ከፍተኛ ደብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሎአል፡፡ እንዲ አይነቱን ድርጊት ፓርቲው ያስቆጣው መሆኑን እየገለፀ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እንጠይቃለን፡፡
በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡
እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡
በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡

የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡
ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡
ፓርቲያችን እንዲህ አይነቱን የለየለት የመንግሥት ሕገ ወጥ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ የሚመለከተው መሆኑን እየገለፅን፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐናችን እንዲቆም በአፅንኦት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡
እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡
በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡
የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡
ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡
ፓርቲያችን እንዲህ አይነቱን የለየለት የመንግሥት ሕገ ወጥ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ የሚመለከተው መሆኑን እየገለፅን፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐናችን እንዲቆም በአፅንኦት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም

Getachew=Shiferaw-
በጧቱ ነበር ወደ ወሎ ሰፈር ለማቅናት መንገድ የጀመርኩት፡፡ መሃል ላይ አንድ ስልክ ደረሰኝ፡፡ ‹‹የሰማያዊ ፓር አመራሮችና አባላት ታግተዋል›› የሚል፡፡ ለማረጋገጥ ወደ ቢሮ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ቢሮ ስደርስ የአካባቢው ሰዎች ሰብሰብ ሰብሰብ ብለው ስለ ታሳሪዎቹ፣ ሳውዲ ውስጥ ስለሚሰቃዩት ኢትዮጵያውያን፣ ስለሰላማዊ ሰልፉ ያወራሉ፡፡
በርካታ ፖሊሶች በቢሮው አካባቢ ተሰባስበዋል፡፡ ግቢው ውስጥ ግን ማንም የለም፡፡ ቢሮው በር ላይ ሳውዲ ውስጥ ለሚሰቃዩት ወገኖች በምልክትነት የተሰቀለው ጥቁር ምልክት እንዳልተነሳ ስመለከት ፖሊሶቹ ስለ ጉዳዩ እውቀት እንደሌላቸው ገባኝ፡፡ አመራቹን በአንዳች ነገር ከሰው ብቻ እርምጃ እንዲወስዱ ተነግሯቸዋል ማለት ነው፡፡
ከሰዎች መረጃ እያሰባሰብኩ እያለ ሌላ ስልክ ደረሰኝ፡፡ ‹‹ወደ ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል›› የሚል ነው፡፡ ወደዛው መሄድ አለብኝ፡፡ አንድ ጓደኛየን አግኝቸው ከእሱ ጋር አመራሁ፡፡ ኤምባሲው ጋር የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀላቀል እየረፈደብን ቢሆን ስለ ታሳሪዎቹ መረጃ ማግኘት ነበረብን፡፡
ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ ስንደርስ ኢንጅነሩንና ሌሎች ጥቂት አመራሮችን ከርቀት አየናቸው፡፡ ሌሎቹን አስገብተው እየደበደቧቸውም ይሁን ለሌላ ጉዳይ ውስጥ ገብተው አይታዩም፡፡ ፖሊሶቹ ወደ እኛ ሲመጡ ሳውዲ ኤምባሲ ያለውን ጉዳይ ከመታሰር ብለን ታሳሪዎቹን ከእርቀት ሰላም ብለን ወደ ኤምባሲው እየተቻኮልን አቀናን፡፡
ሰዓቱ እየሄደ በመሆኑ ላንደርስ እንችላለን ብለን ሰግተናል፡፡ በእርግጥ የኢህአዴግ አንዱ ስልትም እንዲህ በተለያዩ ጉዳዮች በመወጠር ዋናውን ነገር ማሳት ነው፡፡ ወሎ ሰፈር አካባቢ ወደ 6 ሰዓት አካባ ስንደርስ ጥቁር የለበሱ ሰዎች ከኤምባሲው አቅጣጫ እየተመለሱ ነው፡፡ ሌላው ህዝብ ደግሞ በየ መንገዱ ዳር ቆሞ ይመለከታል፡፡
ይበልጥ እየቀረብን ስንሄድ የምናውቃቸውን ሰዎች አገኘን፡፡ እስካሁን አልተደበደብኩም የሚል ሰው አላጋጠመንም፡፡ አንዲት ምን አልባትም ሳውዲ ውስጥ የምታውቀው ሰው ጥቃት የደረሰበት ዘመድ ያላት የምትመስል ሴት ስቅስቀስ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ሙሉ ጥቁር ልብስ ለብሳለች፡፡ ይህች ሴት እንዲህ የምታለቅሰው ከድብደባው ይልቅ ለዜቾቻችን ክብር ያልተሰጣቸው መሆኑ ነው፡፡
ሌላኛዋ ደግሞ የምታለቅሰው በጣም በመደብደቧ ነው፡፡ አንድ ሌላ ወጣት (ጓደኛየ ጋር ይተዋወቃሉ) ሰላም ካለን በኋላ በየ ቦታው ይቀመጣል፡፡ ምኑን እንደመቱት ስንጠይቀው ኩላሊቱ አካባቢ የተገመደለ አዲስ ቁስል አሳየን፡፡ ልጁ በንዴት ይቁነጠነጣል፡፡
በርካቶች መታሰራቸውን ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የነበሩት ነግረውናል፡፡ አብዛኛው የተበተነው ወጣት እያማረረ ነው፡፡ አንደኛው ‹‹ሰላማዊ ትግል አያስፈልግም›› ይላል፡፡ ለጎኑ ካሉት ክርክር ይገጥመዋል፡፡ ሌላኛው ‹‹ ነገ ኳስ ላይም ቢሆን ይህን ጮከታችን እናሰማለን››፣ ሌላኛው ‹‹እኔ የተደበደብኩት አገሬ ውስጥ ነው ወገኖቹ ሳውዲ ውስጥ እየሞቱ ነው፡፡››፣ ሌላኛዋ ‹‹እሁድም መጥተን መደብደብ አለብ›› ……
እኔም ቢሆን ኢህአዴግ ይፈቅዳል የሚል ተስፋ አልነበረኝም፡፡ ሰማያዊዮች ሲታሰሩም ማረጋገጥ የቻልኩት ይህን ነው፡፡ ግን መታሰርም ሆነ መደብደብ አንድ ነገር ነው፡፡ ይህ ለዜጎቻችንም ሆነ ለራሳችን ያለንን ክብር የምናሳይበት ነው፡፡ ኢህአዴግ ዳግመኛ ከገዳዮቻችን፣ ከጠላቶቻችን ጎን ቆሞ፡፡ ጸረ ህዝብነቱንም አስመሰከረ፡፡
አንዳንዴ ስትደበደብ ወይንም ስትሰታሰር ይወጣልሃል፡፡ እኔ እየዞርኩ ሳይ የዋልኩት የዜጎችን ሰቆቃ ብቻ ነው፡፡ እናም ቅጥል ብያለሁ፡፡
የሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ለመሳተፍ የወጡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ታሰሩ፡፡ ከጽ/ቤታቸው ተነስተው ወደ ሰላማዊ ሰልፉ ቦታ ሲሄዱ 4 ኪሎ የኦሮሚያ ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ጎን በሚገኘው ወታደራዊ ገራዥ መታሰራቸውን ዘጋቢያችን ከቦታው አድርሶናል፡፡ ከመታሰራው ቀደም ብሎ ከፖሊስ ጋር እንሂድ አትሄዱም በሚል ጭቅጭቅ ላይ እንደነበሩ ሰምተናል፡፡ ሌሎች የፓርቲው አባላትና አመራሮች ተበታትነው ወደ ሳውዲ አረቢያ […]
ጥላቻው እያደገ ሔዷል ፣ ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞቻቸውን ድሮ ድሮ በአረቦች ዘንድ የተከበርን ፣ የታፈርን የእኛን የሃበሻ ልጆች “ጨካኞች ፣ የማይታመኑ !” እያሉ ጥላቻቸውን መገልጽ ጀምረዋል። November 14,2013 የወጣው አረብ ኑውስ Recent clashes make Saudis wary of Ethiopian maids በሚል ርዕስ ስር ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያን ሰራተኞችን ለማባረር እየዛቱ ነው ! ይህ የአረብ ኒውስ ዘገባ […]
የህግ ባለሙያው ዶ/ር ሸክስፒር ፈይሳ ንግግር ያደርጋል
አሁንም የኢትዮጵያዊያኖች የድረሱልኝ ጥሪ እየተሰማ ነው(ቪድዮዎችን ይመልከቱ)
Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም. November 30, 2013)፦ በካናዳ የንግድ መናገሻ በሆነችው ቶሮንቶ ከተማ በሳኡዲት አረቢያ በኢትዮጵያዊያኖች ላይ የሚፈጸመውን ግፍ በመቃወምና በአሰቃቂ ሁናቴ ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች የሻማ ማብራት ስነስርአት ነገ አርብ እንደሚካሄድ ይፋ ተደረገ።
Ethiopians demonstrate outside Saudi Embassy in Washington, D.C.
Qootcha people in Ethiopia and arrests
Ethiopians returning from Saudi Arabia
ህዳር ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአውሮፓና አሜሪካ የሚገኙ ኢትዮያውያን በሰልፍ ተቃውሟቸውን ሲገልፁ ውለዋል። በሳዑዲ ዐረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈፀመ ያለው ግፍ ተባብሶ መቀጠሉን ተጠቂዎቹ ለኢሳት ገለፁ። በሪያድ ወደማጎሪያ ካምፕ ውስጥ የተወሰዱ ኢትዮጵያውያን ካሉበት ስፍራ ሆነው ለ ኢሳት በስልክ እንደገለፁት፤ በትናንትናው ዕለት ብቻ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በከባድ መኪናዎች እየተጫኑ ወዳልታወቀ ስፍራ ተወስደዋል። ስደተኞቹ-ለሳዑዲ ፖሊሶች፦” ወደ …
ህዳር ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህዳር እና የታህሳስ ወራትን በሙሉ በጾም በጾሎት ምእመኑ እግዚኦታ እንዲያሰማ ቄስ አለሙ ሺጣ የኢትዩጵያውያን ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ዋና ጽሓፊ በአምላክ ስም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በኢትዩጵያ በአሁኑ ስዓት እየተሰተዋለ ላለው ችግር ፣በምስራቅ አፍሪካ እና በአፍሪካ ሐገራት እንዲሁም በአለም ለሚታየውና ለሚሰማው በደል- ሀይማኖቱ በሚጠይቀው ስርዓት እጆችን ወደ አምለክ እንድናነሳ እና እንድናለቅስ …
ህዳር ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሸንጎው ከፍተኛ የአመራር ምክርቤትቅዳሜ ጥቅምት 29፣ 2006 ባደረገው ስብሰባ በሳዑዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ በሀገሪቱመንግስት የጸጥታ ሀይሎችእየደረሰ ያለውን ህገወጥ እስራት፣ድብደባና ስቃይ በታላቅ ሀዘንና አንክሮ እንዳጤነው ገል ል። ሸንጎው ለዚህ ግፍ ሰለባዎችና ለቤተሰቦቻቸው የተሰማውን ሀዘን በመግለጽ ከጎናቸው እንደሚቆምምአረጋግጧል። በተመሣሳይ የ ኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ( ኢህአፓ) ሳውዲ አረብያ በዜጎቻችን ላይ …
በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቹ ወደሀገራቸው እየተመለሱ መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናቱም ከሳዑዲ አቻዎቻቸው ጋር እየተነጋገሩ መሆናቸውን አስታውቋል።
በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ አምባሣደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ የተመራ የልዑካን ቡድን ወደ ሪያድ መጓዙ ተገልጿል፡፡
ሰሞኑን መግለጫ እያወጡ ያሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ግን መንግሥት ለእርምጃው ዘግይቷል፥ የበለጠ ሥራም ይጠብቀዋል ይላሉ።
በጉዳዩ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ለነገ ጥሪ የበተነው መኢአድ የሌሎች አንዳንድ ሃገሮች ዜጎች መብቶች ከኢትዮጵያዊያኑ በተሻለ ሁኔታ እንደሚጠበቅና በኢትዮጵያዊያን ላይ ግፍ ሲደርስ ግን የአሁኑ የመጀመሪያ አለመሆኑን የድርጅቱ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ አመልክተዋል፡፡
ዛሬ መግለጫ ያወጣው ሰማያዊ ፓርቲ ደግሞ ነገ ዐርብ፣…
“የወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል መሪ ቃል የተጠራ የኢትዮጵያዊያን ሰልፍ ዛሬ፣ ኅዳር 5 / 2006 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የሣዑዲ አረቢያ ኤምባሲ ደጃፍ ላይ ተካሂዷል፡፡
በሰልፉ ላይ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተገኙ ሲሆን ሣዑዲ አረቢያ ለሚገኙ ወገኖቻቸው ጥበቃ እንዲደረግ፣ ሰብዓዊ መብቶቻቸው እንዲከበሩ፣ በአፋጣኝ ወደ ሃገራቸው የሚመለሱበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠይቀዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በቁጫ ወረዳ፥ ከ 20 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ከ 100 በላይ ተማሪዎች፥ መምህራንና አርሶ አደሮች መታሠራቸውም ይነገራል።
ከወረዳው ባለሥልጣናት ጉዳዩን ለማጣራት ባባለፉት ሁለት ቀናት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።
መለስካቻው አምሃ ተከታዩን ከአዲስ አበባ ልኳል።
በሐረሪ ክልል ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሰብል ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ። የአካባቢዉ ገበሬዎችና ኗሪዎች ለዶይቼ ቬለ እንደገለፁት በማሳ ላይ ያለ የስንዴና ገብስ ሰብል እየረገፈ፤ አንዳንዱ ሰብልም ማሳላ እያለ መልሶ በቅሏል።
በሌሎች ሐገሮች የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች እየተበደልን ነዉ ይሉ ይዘዋል።ስደተኞቹ እንደሚሉት የየሐገሩ ባለሥልጣናት ያስሯቸዋል፥ ያንገላቷቸዋል፥ ያስፈራሯቸዋል፥ ቀለል ሲል ደግሞ ጉቦ ይጠይቋቸዋል።በየሥፍራዉ ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎችና ለዓለም አቀፍ የርዳታ ድርጅቶች በየጊዜዉ አቤት ቢሉም እስካሁን የረዳቸዉ የለም
ኮብለር የሌሎች አማፂ ቡድናት አባላትም ትጥቃቸዉን እንዲፈቱ ጠይቀዋል።ትጥቅ ካልፈቱ ግን ዓለም አቀፉ ጦር በሐይል እንደሚያስፈታቸዉ ዝተዋል።ይሁንና የኪንሻሳና የካምፓላ ባለሥልጣናት አዲስ እሰጥ አገባ መግጠማቸዉ ምሥራቃዊ ኮንጎ «ዘላቂ ሠላም» ለማስፈን የተለፋዉን ሁሉ መና እንዳያስቀረዉ እያሰጋ ነዉ።
የዕለቱ ዜና
For me, the people of Kingdom of Saudi Arabia and #Ethiopia are two people with the same behavior. Especially, until the former have gotten the oil to become rich. Both are religious people who lived under series of regimes that used religion as a t…
ዩጋንዳ ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በሕይወት አለ?
ይህን ጥያቄ ለመመለስ ካምፓላን ማዳረስ ኣያስፈልግም።የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሚሊኒየሙ አከባበር ግዜ ነበረ። ከዛ ተሽመደመደ።ጁላይ ኢለቨን ካምፖላ በአልሻባብ አጥፍቶ ጠፊዎች አሰቃቂ ፍንዳታ በደረሠ ግዜ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አለሁ ብሎ ሲሯሯጥ ታየ።ከዛ በኋላ ነበር ኖቬምበር አስራአራት ቀን ሁለት ሺ አስር የኢትዮጵያ ኮሚኒቲን
ኖቬምበር አስራአራት ከሚሊኒየሙ በፊትና በኋላ ኮሚኒቲው ያከናወናቸውን ተግባራት የሚያትት ዝርዝር የስራና የሂሣብ ሪፖርት ቀርቦ የነበረው።ለአንድ ዓመት ያህልም በወገኖች ድጋፍ ቢሮ እስከመክፈትና የአባልነት መታወቅያም ለማህበረሠቡ አዳርሶ ነበር።ኮሚኒቲው በወቅቱ ያሣየው ፍጥነት የወያኔን ወኪሎች አስግቶአቸው ይሁን ወይም በሌላ ምክንት ቢሮውም ተዘጋ ፣አመራሩም ላይገናኙ የተማማሉ መሠለ።ከወያኔ ቆንስላ ሃላፊዎች ጋርም ምስጢራዊ ስብሰባ የተወሰኑ የኮሚኒቲው አመራሮች አደረጉ የሚል ወሬ ተሠማ።ያኔ ኮሚኒቲው ተሸረሸረ።
ዩጋንዳ ያለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ መተዳደርያ ደንቡ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ አባል መሆን እንደሚችል ስለሚገልፅ የወያኔ ቆንስላ ሠራተኞች ካሣደዱዋቸው የፖለቲካ ስደተኞች ጋር የአንድ ኮሚኒቲ አባል ለመሆን ሲመዘገቡ ታይተዋል።በየትኛውም ስፍራ የፅዋ ማህበርም ቢሆን ወያኔዋቹ በይፉም ሆነ በህቡህ ያን ማህበር ካልተቀላቀሉ፣
አልያም ካላፈረሱና ወይም በነሡ ሣንባ የሚተነፍስ ተለጣፊ ካልመሠረቱ ሞታቸው ነው።
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በዩጋንዳ ዛሬ ስሙ ከመኖሩ ባሻገር ተሽመድምዶ ያለው ፖሊዮ ይዞት አይደለም።የኮሚኒቲው አመራሮች የያዙትን ቦታ ለመልቀቅ ፈቃደኝነት ያላቸውም አይመስልም።የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ከሚሊኒየሙ በፊትም ሆነ በኋላ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የሚያደርጋቸውን ተግባራት በቅርበት ያውቃል።እንደዜጋም አቅሙ የፈቀደውን በማድረግ በወያኔ ቆንስላ ጥቁር መዝገብ በጠላትነት ተፈርጆ እንደሚገኝ የካምፓላ ሰማይ የሚያውቀው ዕውነታ ነው።
ወያኔ የሚሊኒየሙን በዓል በሱ ፊታውራሪነት ካምፓላ ላይ ለማክበር ሲሯሯጥ በወቅቱ ወያኔ ንፁሀንን እስር ቤት አጉሮ በዓሉን በጋራ እንድናከብር ሊያግባባና ሊያስፈራራ ሲሞክር የታሠሩት ይፈቱ፣ብሔራዊ ዕርቅ ይደረግ ብለን የተወሰንን ወገኖች በመናገራችንና ሚሊኒየሙን ያለወያኔ ተሣትፎ በደመቀ ሁኔታ በማሣለፋችን ነበረ የወያኔ ጥርስ ውስጥ የገባነው።
ባለፉት ሦሥት አመታት የወያኔ ቆንስላ ዩጋንዳ ካምፖላ ላይ እውነተኛ የፖለቲካ ስደተኞችንን በማሳደድ፣በማሠለልና መፈናፈኛ በማሳጣት ሕብረተሠቡን በዘር እስከማደራጀት ሠርቷል።
ኮሚኒቲውን አሽመድምዷል።ከአመራሩ የተወሠኑትን ፖስፖርት በመስጠት ከስደተኛነት አላቋል።የወያኔ ቆንስላ ቤተኛ የሆኑም እንዳሉ የአደባባይ ሚስጥር ነው።
በርካታ ወገኖች ኮሚኒቲው ባይቀበርም እንደሞተ ያምናሉ።እንደገና ለማጠናከርም ቢሞከር አሁን ካሉት የአመራር አባላት መካከል ከወያኔ ጋር በግልፅም ይሁን ውስጥ ለውስጥ የሚሞዳሞዱትን ለይቶ ለማውጣት አስቸጋሪ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።
ከሁለት ዓመት በፊት በሕጋዊው ሲኖዶስ የሚመራውን የካምፖላ መካነ ሠላም መድሐንያለም ቤተክርስትያን የወያኔ ቆንስላ ካህናትና፣ ዲያቆናት እንዲሁም መዘምራንን በስውር አደራጅቶ ያካሄደው ትርምስ በእውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ከከሸፈና የአመፁ መሪ የነበሩት የቀድሞ አስተዳዳሪ የስደተኛ እስታተሳቸውን ወርውረው በወያኔ ፖስፖርት የአምስት ኪሎውን ቤተክህነት ከተቀላቀሉ ወዲህ ነገሮች እየጠሩ መጥተዎል።
ካምፖላ ላይ የፖለቲካ ስደተኛ መታወቅያ በደረታቸው ፣የወያኔ አክቲቭ ፓስፖርት ትራሳቸው ስር ሸጉጠው ትክክለኛ ስደተኞችን የሚሠልሉና ለአደጋ የሚያጋልጡትን ሆድ አደሮች ለማጋለጥ በዩጋንዳ የሚኖሩ ስደተኞች ለህልውናቸው ሲሉ በህብረት ሊቆሙ ይገባል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጥቂት የፖለቲካ ስደተኞች ስደተኛውን ብቻ ያቀፈ የስደተኞች ማህበር ለመመስረት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ሲሆን ለስደተኛው መብት መከበር የሚሠራ ከማናቸውም የፖለቲካ ሃይሎች ተፅዕኖ ነፃ የሆነ ማህበር ለመመስረት የበኩሌን እገዛ ሳደርግ ብቆይም ለደህንነቴ ስጋት የሚፈጥሩ ሁኔታዎች በመፈጠራቸው ከማናቸውም ማህበረሠቡን ከሚመለከቱ ጉዳዮችራሴን አግልዬ እንደምገኝ ለመጠቆም እወዳለሁ።በተቻለ አቅም ስደተኛው የራሱን ማህበር ከወያኔ ሠርጎ ገቦች እንዲጠብቅ አሳስባለሁ።
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ እስከዛሬ የታመሙትን ወገን በማስተባበር ለማሣከም ያደረገው መልካም ተግባር ፣
የሟች ወገኖችን አስከሬን ከቤተሠብ ጋር መክሮ ለሐገራቸው አፈር እንዲበቁ በመስራቱ፣ምስኪን ስደተኞች ሲሞቱ በመቅበር የሠራውን ስራ በመዘከር ወደ ወያኔ ጉያ የተሸጎጠውና ፖራላይዝዱ ኮሚኒቲ እኔም ልክ የዛሬ ሦሥት አመት በተከናወነው የማሟያ ምርጫ የቦርድ አባል ሆኜ እስከዛሬ መቆየቴን እየጠቆምኩ በመላ ዓለም የምትገኙ ኮሚኒቲዎች ልምዳችሁን እንድታካፍሉኝ እንደ አንድ ዩጋንዳ ላይ በሚኖር ሐገር አልባ ስደተኛ በአክብሮት እጠይቃለሁ።
ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ሁሉ ፀሀፊው በንፁህ ህሊና እውነቱን ብቻ ለመግለፅ ህሊናው ዝግጁ መሆኑን ይጠቁማል።
ጋዜጠኛ ደረጀ በጋሻው
ከኮሚኒቲው ቦርድ አባላት አንዱ
ድምጻችንን ከማሰማት አንቆጠብ..የኢትዮጵያ መንግስት ማላገጡን በሳዑዲም ዜጋችን መሞቱ ቀጥሏል..
በግሩም ተ/ሀይማኖት
ሪያድ ውስጥ ወገኖቻችን ላይ ዛሬም ጥቃት ተፈጸመ፡፡ ብጥብጥ ተፈጥሯል እባክህ በዚህ ስልክ ቁጥር ደውልልኝ ብሎ ቁጥር አስቀምጦልኝ አገኘሁ፡፡ 9665533…አደረኩና ደወልኩ፡፡ ከወዲያ ማዶ ምላሽ ስጠብቅ ኮለል ያለ የመደፈር ጥቃት የአትንኩኝ ባይነት ግርማ ሞገስ ባለው ድምጽ ‹‹ሀሎ!›› ተባልኩ፡፡ ሰላምታዬን አደረስኩና ብጥብጡ ምንድን ነው አልኩት፡፡ ‹‹..ይሄውልህ ግሩሜ በሪያድ መንፉሃ አውራ መንገዶች ሃገራችን ውሰዱን ብለን እቃችንን ሸጠን ወጥተናል፡፡ አምባሳደሩ መጣና ምንም ችግር የለም ወደ ሀገር ትገባላችሁ ብሎ ሄደ፡፡ ዛሬ ከቀትር በኋላ ወደ ብጥብት ተነሳ….(ዛሬ የሚለው ትላንት ማታ ስላውራሁት ነው)
(እኔ እሱን ላቋርጥና የምለው ስላለኝ ቅንፌን ከፍቻለሁ፡፡ አምባሳደሩ በሉ ተብለው የታዘዙትን ነው ያሉት፡፡ ያ-ሳይሆን የሚያሳዝነው ቤታቸውን ጥለው ወጥተው አደባባይ መሆናቸውን እያዩ አላግጤ ንግግራቸውን ተናገው እና በአፍ ደልለው መሄዳቸውን ሌላ ምንጮቼ ገልጸውልኛል፡፡ ዜጋዬን..ያለው መንግስትም 25 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገር መመለሱን በዜና እወጃው አሰውቋል፡፡ የተመለሱት ሰዎችን ምንነት በዜናው ላይ ከተደረገላቸው ቃለ-ምልልስ ማወቅ ይቻላል፡፡ የኢህአዴግ ካድሬዎች ዘውትር የሚያንቆረቁሩት ስልቹ ቃላትን ሲደግሙት ለሰማ ‹‹..አሀ! የእንትን ልማት ማህበር አባል…›› ብሎ መጥራቱ አይቀሬ ነው፡፡ ይህን ጥርጣሬዬን ይዤ ለአንዱ እንዴት ነው ለመግባት ያለው ሂደት አልኩት፡፡ ‹‹.1000 ሪያል ካለህ በአፋጣኝ ትጨርሳለህ….›› በስመአብ የደነገጥኩትን አትጠይቁኝ፡፡…እኔ በአረቡ አለም ያሉት ኤምባሲዎች ኮሙኒቲ ካልተመዘገብክ የአማራ ልማት ማህበር፣ የትግራይ፣ የኦሮሞ፣የጉራጌ..ምናምን አባል ካሆናችሁ እያሉ አገልግሎት ስለማጓተታቸው ስጠይቀው ይባስ ለፈጣን አገልግሎት 1000 ሪያል ጉቦ መባሉ እንዴት አያስደነግጠኝ? አሁን ለደወልኩለት እና እያናገርኩት ላለው ልጅም ይሄን ጥያቄ አቀረብኩለት…ወደ ዘገባዬ ተመለስኩ፡፡)
ወደ ሀገራችን መልሱን የሚለው ጥያቄያችንን ለማደናቀፍ ፖሊስ ሸባቦቹን ይዞ መጣ፡፡ (ሸባብ ማለት ወጣት ነው፡፡ ፖሊስ እነዚህን የመንደር ጎረምሶች ይዞ በመዞር ነው ዜጋዎቻችን ላይ ጥቃት የሚፈጽመው) ‹‹ለምንድነው እንደዚህ የምትሆኑት ሂዱ ብላችኋል መሄድ እንፈልጋለን ብለን ነው ቤት ንብረታችንን ጥለን የመጣነው ብለን ለማረጋጋት ሞከርን፡፡ በፊት ሲመጡ አሰር (የዘጠን ሰዓት ስግደት) እየሰገድን ነበር፡፡ በተፈጠረው ግርግር ሲያሰግደን የነበረውን ልጅ በጩቤ ወጉት፡፡ ከዛ ከፍተኛ ግርግር ነበር፡፡ ወደ ታፋው አካባቢ ነው የወጉት፡፡ እንግዲህ ኤምባሲው ምንድን ነው ስራው…(ወዳጄ የኤንባሲው ስራ እናንተን ማስደብደብ እና ከሳዑዲ የሚፈልጉትን ማግኘት) እንዴት ነው በዚህ ጭንቅ ሰዓት ኤምባሲው የሚያስከፍላችሁ ነገር አለ እንዴ? አልኩና ጥያቄ በስልክ ወረወርኩ፡፡ ቀበል አለና አይ! ጉዳዩን ቶሎ እንዲጨርሱልህ ላለመጉላላት ከፈለክ 1000 ሪያል የይጠይቁሀል….(ጉቦ መሆኑ ነው ወገኖቼ በዚህ የጭንቅ ሰዓት እነዚህ የኤምባሲ ሰራተኞች ጉቦ ይበላሉ…..የወገናቸውን ደም ይጠጣሉ፡፡ ኧረ!!!!…እባካችሁ እንተዛዘን….) ሌላው አሁንም የገዚው ፓርቲ አሸርጋጆች በድርጅታዊ አወቃቀር ሳይሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊን እንደ ዜጋ በማየት ማስተናገድ እንጂ በዚህ ሰዓት አባል የሆና ያልሆነ እያላችሁ እና ከዜጋ ህይወት ገንዘብ አስበልጣችሁ ኪሳችሁን ማደለብ ስታስቡ አሁንም ወገኖቻቻንን ለእልቂት አትዳርጉ፡፡
በዙሪያው የምንገኝ የመንፉሃን ግጭት ተከትሎ በተሰጠው ወደ ሃገር የመግባት እድል ለመጠቀም በቡዙ ሺህ የሚቆጥሩ ኢትዮጵያዊ መጠለያዎችን እያጨናነቀ ነው። በመካ ያለው ከባድ ሁኔታ ቢሆንም ያለው የባሰ ያስገረመው በሁለት ኢትዮጵዊያን መካከል በተፈጠረ ግጭት አንደኛው አንዱን ደጋግሞ በጩቤ በመውጋቱ አንደኛው ኢትዮጵያው ለህልፈተ ህይወት በቅቷል፡፡ ይህ ወገን ወገኑን የሚጎዳበት ሂደት በእንደዚህ አይነት አጣብቂኝ የስቃይ ህይወት ውስጥ ሆኖም መቀጠሉ ያሳዝናል፡፡
አሁንም በሽዎች የሚቆጠሩ ወደ መጠለያ ለመግባት እየጎረፉ ነው ። በመጠለያው ትናነት አንዲት የ9 ወር እርጉዝ ሞታ ተቀብራለች ። በመጠለያው የምግብና የመጥ እጠረቱ ደግሞ ኢትዮጰያውያኑነ አጥር ሰብረው እንዲወጡ እያስገደደ ነው ተብሏል። በሳዑዲ ያለው ሁኔታ መንግስት ቀዝቅዟል በማለት በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቃል አቀባይ በኩል ቢናገርም ቢገልጽም፡፡ሁኔታው የከፋ እና ፖሊስ አሁንም ወጣቶችን ይዞ በየቦታው እየዞረ ማስደብደቡን እንደቀጠለ መሆኑን ሳዑዲያ ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ይናገራሉ፡፡ በጣም አሳፋሪ መረጃ እየሰጡ ያሉት የመንግስት ተቋማት ዛሬም ይህንኑ እየደገሙት መሆኑ አሳዛኝ ኢ-ሰብአዊነት እየፈጽሙ መሆኑን ልብ ሊባል ይገባዋል፡፡
ከከተማው አርቀው ያስቀመጧቸው ካምፐ ውስጥ የምግብ እና ውሀ እጥረት መኖሩን አንድ መረጃ ሲያቀብለኝ የከረመ ወዳጄ አድርሶኛል፡፡ ሴቶች፣ ህጸናት፣.የስኳር በሽተኞች፣ አሉ፡፡ ካምፕ ውስጥ አስገብተው ከቀን አንዴ ብቻ ነበር እህል የሚሰጠን፡፡ አሁን ድንገት ሁለት ነው ማለት ከተቻለ ሁልቴ አንዴ የምትበላውን የሚያህል ያበሉሀል፡፡ የመጠለያው ሁኔታ እጅግ አስከፊ መሆኑን ነግሮኛል፡፡ በተጨማሪም በእስር እና ከእስር ወደ እስር ቤት መቀየር ላይ አስካሁን ብቻ 5 ሰዎች መሞታቸውን ይሄው የአይን እማኝ የሆነው የመረጃ ምንጬ ገልጾልኛል፡፡ በግሩም ተ/ሀይማኖት
ሰኞ ኖቨምበር 18 በ ዋሽንግተን ዲሲ በሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ለመሳተፍ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ በጋራ ለመሄድ እንዲቻል የሚክተሉት ግለሰቦች የማስተባበር ህላፊነት የተሰተጣቸው ስለሆነ የሚከተሉትን ስልኮች በመደወል ክቅዳሜ ክሰአት በፊት ቦታ እንድትይዙ አዘጋጅ ግብረሃይሉ ይጠይቃል። 1.እዮብ 617 513 7514 2.ካሳይ 857 928 8677 3.አበራ 617 304 2584 4.አብይ 617 953 7126 5.ዮናስ 617 447 8007
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ህዳር ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሴቶች ካምፕ ያለው ሁኔታ እጅግ አስከፊ መሆኑን ኢትዮጵያውያን ሴቶች ይነጋራሉ። ቀን በጸሀይ ማታ ደግሞ በብርድ እንድናሳልፍ እየተገደድን ነው የምትለው ሌላዋ እስረኛ ሳሚራ፣ ህጻናት እና እናቶች በምግብ እጦት እየተጎዱ ለበሽታም እየተዳረጉ ነው ትላለች። ባለፉት አራት ቀናት የወለዱ እናቶች መኖራቸውን የምትገልጸው ሳሚራ፣ የሳውዲ ፖሊሶች ወላዶችን የት እንደወሰዱዋቸው እንደማታውቅ ገልጻለች። ሀብታም የተባለቸውም …
ህዳር ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆነው ወጣት ብርሀኑ ተክለያሬድ ለኢሳት እንደገለጸው ምንም እንኳ የአዲስ አበባ መስተዳድር ፈቃድ ክፍል ፣ የሰላማዊ ሰልፍ መጠየቂያ ደብዳቤውን እንደማይቀበል ቢገልጽም፣ ፓርቲው ተቃውሞውን በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ለማድረግ ወስኖ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግስት ተባብሮ ተቃውሞ ማዘጋጀት ሲገባው፣ ፓርቲው እንዳያዘጋጅ መከልከሉ እንዳስገረመው ወጣት አሬድ …
ህዳር ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጄኔራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ፣ የኢትዮጵያ ሽግግር መንግስት ካንውነስል፣ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ማህበር በደቡብ አፍሪካ፣ ሂውማን ራይተስ ሊግ በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም መድረክ ድርጊቱን የሚያወግዙ መግለጫዎችን ለኢሳት ልከዋል።
News, Ethiopians in America, Americana, Democracy and Women and Family
የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ኣስመልክቶ ላለፉት 9 እና 10 ዓመታት በተለይ ከመንግስት በኩል የሚሰማው እጥፍ ድርብ እድገት ወይንም በእንግሊዝኛው Double digit grorth ያውም ከ 11 በመቶ ያላነሰ ወይንም ከዚያ በላይ መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚዎች በዚያች ኣገር ያንን ያህል እድገት ያውም በኢህኣዲግ የእጅ ኣዙር እዝ ኢኮኖሚ የማይታሰብ ነው እያሉ
የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ኣስመልክቶ ላለፉት 9 እና 10 ዓመታት በተለይ ከመንግስት በኩል የሚሰማው እጥፍ ድርብ እድገት ወይንም በእንግሊዝኛው «ዳብል ዲጂት ግሮውዝ» ያውም ከ 11 በመቶ ያላነሰ ወይንም ከዚያ በላይ መሆኑ ይታወቃል። ተቃዋሚዎች በዚያች ኣገር ያንን ያህል እድገት ያውም በኢህኣዲግ የእጅ ኣዙር እዝ ኢኮኖሚ የማይታሰብ ነው እያሉ
ሳዉድ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ዛሬም የድረሱልን ድምጻቸዉን እያሰሙ ነዉ። የሀገሪቱ መንግስት ላለፉት ወራት ሰጥቶ የቆየዉ የምህረት ቀነገደብ ካለፈ ወዲህ በዜጎችና የጸጥታ ኃይሎች ይፈጸምብናል የሚሉት በደልም ገደብ ማለፉን ይናገራሉ።