ከሰሞኑ እየተመለሱ ወደ ትውልድ ሀገር ስለሚገቡትም በመነገር ላይ ነው። በሌላ በኩል በዚያ የሚገኙትን ግራ ያጋባ፤ ሆኖም ተጨባጭነት የሌለው የአውሮፓ መንግሥታት ተመላሾችን ለመቀበል እንደተዘጋጁ የሚናፈሰው ወሬ፤ በእርግጥ ተጨባጭነት የሌለው መሆኑም ታውቋል።

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መ ኢ አ ድ)በናዝሬት ከተማ ከ 33 የተቃውሞ ፓርቲዎች ጋር ከተደረገው የጋራ ስብሰባ በኋላ ፣ የራሱን አባላት በመጥራት የድጋፍ ፊርማ የማሰባሰብ ሥርዓት ማካሄዱ ተነገረ። በዚህ ሂደት በተለይ በደቡብ ኢትዮጵያ የወረዳ አስተዳደርና ፖሊስ ስብሰባየን አስተጓጎሉብኝ ሲል ወቀም ሆነ ስሞታ ማሰማቱም ታውቋል ።

ዓለማየሁ ዲባባ

የሳዑዲ ሕዝቦች በአንድ የታሪክ ዘመናቸው በኃይማኖት ልዩነት እርስ በእርሳቸው ተፋጅተው ወደ ኢትዮጵያ በተሰደዱ ወቅት ተቀብለናቸው አኑረናል፣ አስጠልለን መግበናል፣ አልብሰን አርዘናል። ከለላ እና ጥበቃ ሰጥተናቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የአውሮጳ ህብረት ለኢትዮጵያ ወደ 240 ሚልዮን ዩሮ የሚጠጋ የልማት ርዳታ እንደሚሰጥ አስታወቀ። ይህንኑ ርዳታ የሚመለከተው ስምምነት ትናንት በኢትዮጵያ መንግሥት እና ለጉብኝት አዲስ አበባ በገባው የአውሮጳ ህብረት የልዑካን ቡድን መሪ አንድሪስ ፒባልግስ መካከል ተፈርሞዋል።

ጥናቱ – እያንዳንዳቸው ከ50 – 122 ገጾች ያሏቸውን 15 የፖሊሲና ማኑዋል አርእስተ ጉዳዮችን ያካተተ መኾኑ ተገልጦአል፡፡ ከእነርሱም መካከል፡- የሰው ሀብት አስተዳደር፣ የሰው ኃይል ልማት፣ የፋይናንስ፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን፤ የዕቅድ፣ ክትትልና ግምገማ፤ የግዥ፣ ሽያጭና ንብረት አስተዳደር፤ የኢንቨስትመንትና ምግባረ ሠናይ፤ የቅርስና ቱሪዝም፤ የመንፈሳዊ ፍትሕ፣ የአስተዳደር እና የሥራ ክርክር ጉዳዮች ችሎቶችን የተመለከቱ ፖሊሲዎች፣ መመሪያዎችና ዝርዝር አሠራሮች ይገኙበታል፡፡ ዛሬ፣ ኅዳር …

ህዳር ፲፮(አስራ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሪያድ የሚታየው ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው ኢትዮጵያውያን። እሁድ  2  ኢትዮጵያን ሴቶች መክረይመንታ ሸባቢያ በሚባል ቦታ ላይ በወታደራዊ ተሽከርካሪዎች መገደላቸውን በአይኔ ተመልክቻለሁ ያሉ የሪያድ ነዋሪ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ሌላ ኢትዮጵያዊት ደግሞ በአካባቢው ከተሰማሩት ወታደሮች ጋር ስትነጋገር በብረት ተመትታ መሞቷን እና አንዲት ኢትዮጵያዊትም እንዲሁ የቀኝ እጇ ተቆርጦ በአካባቢያቸው …

ህዳር ፲፮(አስራ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአፍሪካ ፓርላማ  ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል። በተቃውሞው ላይ የተገኘችው የኢሳት የደቡብ አፍሪካ ተባባሪ ዘጋቢ ዝናሽ ሀብታሙ እንደገለጸችው በሰልፉ ላይ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ ኢትዮጵያውያን ታሰትፈዋል። ተቃውሞውን ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ምክትል ሊ/መንበር አቶ ንብረት ጌታሁንም ህዝቡ በተቃውሞው ላይ ተገኝቶ ስሜቱን በከፍተኛ ሁኔታ ገልጿል ብለዋል በተመሳሳይ …

ህዳር ፲፮(አስራ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የጋራ ትግል አስፈላጊ መሆኑን በፅኑ የሚያምኑት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር  እና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ  በሕዳር 13/2006 ዓ.ም በሁመራ ሉግዲ ከቀኑ    10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1፡00 ለሶስት ሰዓት ያህል በወሰደው ውጊያ የመንግስት 24ኛ ክፍለ ጦር ድባቅ ተመቷል ብሎአል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በ24ኛው …

ህዳር ፲፮(አስራ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአፍሪካ ኅብረት በዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ላይ የያዘውን አቋም እንዲደግፍ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ ጥያቄ አቀረቡ፡፡ ጥያቂያቸውን ለመቀበል አውንታዊ ምላሽ እንደገኙ በመግለጽ አፈጉባኤው ለጋዜጠኞች ቢናገሩም ጉዳዩ ተቀባነት ያገኘው ለውይይት እንጅ ለማጽደቅ አይደለም ተብሎአል። የአፍሪካ የካረቢያንና የፓስፊክ አገራት ፓርላማ 34ኛ መደበኛ ጉባዔ ትላንት በአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን …

ህዳር ፲፮(አስራ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ተማሪ አንተነህ አስፋው የተገደለው በዩኒቨርስቲው የጸጥታ ሀይሎች መሆኑ ታውቋል። ይህን ለመቃወም የወጡ በሺ በሚቆጠሩ ተማሪዎች ላይ የፌደራል ፖሊስ በወሰደው እርምጃ ከ120 በላይ ተማሪዎች እንደታሰሩ ታውቋል። የተወሰኑ ተማሪዎች ከፉኛ በመደብደባቸው ሆስፒታል ገብተዋል፣ የአንድ ተማሪ ህይወትም በአሳሳቢ ሁኔታ ላኢ እንደሚገኝ ታውቋል።

ህዳር ፲፮(አስራ ስድስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የታላቁ ሩጫ በከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ ሥር ሆኖ እሁድ ህዳር 15 ቀን 2006 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡ መነሻውን ጃንሜዳ በማድረግ ፥ በ6 ኪሎ አደባባይ ፣ በምኒሊክ ሆስፒታል፣ በቀበና ፣በ አቧሬ ፣ በእንግሊዝ ኤምባሲ ፣ በመገናኛ አደባባይ በማደረግ ተመልሶ ጃንሜዳ የተጠናቀቀው ይህ ለ 13ኛ ጊዜ የተካሄደው ውድድር ከወትሮው በተለየ ጥበቃና የፖሊስ …

ፊልጶስ
የግፍ ጽዋው ሞልቶ፣ …
ሞልቶ፣ … ሞልቶ ፈሶ
ሰው መባል በሰው፣ ስዕብናችን አሶ
ከ’ጥናፍ – እስከ – አጥናፍ፣ ደማችን “‘ረክሶ”፤
ውቅያኖስ፣ ባህሩን፣ ወንዙን አደፍርሶ
እዩት ይ’ጣለላል፣ አስፋልቱን አልብሶ።
ግን እኮ፣ … እንኳ’ ደም
ውኃ ፈሶ፣ አይቀርም
ይዘገያል እንጂ፣ በሰፈሩት ቁና፣ መሰፈር አይቀርም።
“ዓለም የም’ጠፋው፣ ሰይጣናዊ ምግባር በሚፈጽሙ ሳይሆን፤ ምንም ሳያደርጉ ቀጭ ብለው በሚመለከቷቸው ሰዎች ነው።” /አልበርት አነስታይን/

ሙሉውን አስነብበኝ …

አበራ ሽፈራው ከጀርመን
በአረቡ ዓለም ከፍተኛ ተሰሚነትና የመላው ዓለም አይን ሁሉ በተለየ መልኩ በሚያያት ሳውዲአረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ግፍና መከራ ለትውልድ የማይረሳ ክፉ ታሪክ ጥሎብናል፤ ዛሬም ሰቆቃው ቀጥሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የእሥራኤል ሚንስትሮች ም/ቤት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር የገቡ ናቸው ያላቸውን አፍሪቃውያን ስደተኞች፤ በግዴታ እንዲመለሱ ማድረግ የሚቻልባቸውን የእርምጃ ዓይነቶች ትናንት ማጽደቁ ተነግሯል። እሥራኤል የገቡ 60,000 ያህል ስደተኞች ወደ መጡበት

ኢራን ድብቅ የኑክሌር ተቋም እንዳለት ከታወቀበት ከሁለት ሺሕ ሁለት ጀምሮ በቴሕራንና በምዕራባዉያን ሐገራት ፖለቲከኞችን መካከል የደራዉ ዉዝግብ ለመጀመሪያ ጊዜ-አንድ እልባት አግኝቷል። የእስራኤል-ምዕራባዉያን ልዩነት፥ የኢራን-እስራኤል ዉዝግብስ ነዉ?-የዛሬዉ ጥያቄ

ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ የፖለቲካ አመለካከትን መተቸት አይደለም፤ ከዋና ዋና  ገራዊ አ ንዳዎች ወረድ ያሉ የጉልበታሙን ስርዓት የሥራ አፈፃፀሞችን ማብጠልጠልም አይደለም፤ የተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ስንክሳር መንቀስም… አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ (አል- በሽ) መሆን ለፈተና፣ ለመከራ፣ ለሰቆቃ… መዳረጉ የወለደው ብሶት እንጂ፤ መመረር-ማምረር ነው፡፡ …ይህ የእኛ ዕጣ ፈንታ የሆነበትን ምስጢር መመርመር ነው፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢያሱ ዓለማየሁ

የኢሕአፓ 41 ዓመት መራራና ረጅም ትግል ረጅም ትግስትን ጠይቋል። አያሌ ፈተናዎችን ተቋቁሞና አልፎ ዛሬም ህልውናውን ጠብቆ በትግሉ ሜዳ ላይ መገኘቱ በቅድሚያ የአባላቱታሪክን ገርተውና ጽፈዋት ያለፉትም ሆነ በሕይወት ያሉትን ጽናትና ቆራጥነትየሚመለከት ነው። ኢሕአፓን ለመመስረትና መስርቶም ለማታገል በተደረገው ትግል በታሪክ አጋጣሚ ዋና ተካፋይ ሆኜ በመቆየቴ የሚሰማኝ ደስታና ክብርም ወደር የለውም። ሀቁ ይህ ድርጅት ከቶም ባልተመሰረተ የሚሉት ጠላቶች እንደ ነበሩትና እንዳሉት ሁሉ (በአብዛኛው ከስርዓቶቹ ጋር የተያያዙ) ቤዛችን ነው፣ የወኔያችን መከሰቻ ነው፣ የሀገር አለኝታችን ነው ድርጅታችን ነው የሚሉ ደሞ ብዙዎች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

SHARE:

ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር፡፡መቸም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር፡፡ህጉ የሚለው ግን ማስፈቀድ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡በተቃራኒው መንግስት በተለያዩ ጉዳዮች ሳቢያ በእለቱ ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ከለላ መስጠት የማይችልበት ሁኔታ ከገጠመው ሰልፉን ለጠራው አካል ችግሩን ገልጾ ቀኑ እንዲተላለፍለት ይጠይቃል፡፡በመሆኑም ይህን መሰል ጥያቄ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ለፓርቲያችን ባለመቅረቡ በሙሉ ልብ ቅድመ-ዝግጅት ማድረጉን ተያያዝን፡፡
ሁሌም ቢሆን መንግስት ሰበብ ፈልጎ ሊወነጅለንና ከመስመር ሊያስወጣን እንደሚፈልግ በሚገባ እናውቃለንና በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ሳይቀር ጥንቃቄ እናደርጋለን፡፡ለሚመለከተው መስሪያ ቤት ባሳወቅን በአስራ ሁለት ሰአታት ውስጥ ምላሽ ስላልመጣ ሙሉ በሙሉ ህጋዊነታችንን አረጋግጠናል ማለት ነው፣እነሱ ደግሞ ጠብ-መንጃ በእጃቸው አለና የፈለጉትን ሁሉ ማድረግ ይችላል፡፡

አቶ ሽመልስ ከማል ለሚዲያወች የሰጡትን ፍጹም ከእውነት የራቀ ውንጀላና ሰበብ አዳምጨዋለው፡፡ “ሰላማዊ ሰልፉን ያገድንበት ምክንያት ጸረ-አረብ መፈክሮች ስለነበሩ ነው“ብለዋል፡፡መጀመሪያ ደረጃ ሰልፉ ገና ከግቢው ፈቅ ሳይል ነው ያፈኑት፣ሆኖም የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም አንድ በአንድ እየሆንን ወደ ሰላማዊ ሰልፉ መዳረሻ ለመሄድ ስንሞክር የተወሰኑ አመራሮችን አራት ኪሎ አካባቢ ያዙን፣እነሱ ቀድሞውኑ ሰልፉ እንዳይካሄድ ስለወሰኑ ነው እንጅ ትንሽ እንኳ ተንቀሳቅሶ የሰልፉን ባህሪ ለመገምገም ምንም እድል አልሰጡንም፡፡

ለምሳሌ ሰልፉን እንደምናደርግ ይፋ ባደረግን ማግስት ከራዲዮ ፋና ተደውሎ አንዳንድ ጥያቄዎች ተጠይቄ ነበር፡፡በቃለ-መጠይቁ ሰላማው ሰልፉ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰውን በደል በመቃወም እንደምናደርግ ተናግረናል፡፡ጋዜጠኛው ለሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊዎች መልዕክት ካለ ብሎ በጠየቀኝ ወቅት የሳውዲ አረቢያ ሰንደቅ አላማ ላይ ያለው ምልክትና ጽሁፍ ሀይማኖትን የሚመለከት በመሆኑ ዜጎች በስሜታዊነት ባንዲራ እንዳያቃጥሉ፣እነሱ ቢያዋርዱንም እኛ ግን ክብር ያለን ዜጎች ስለሆንን ተቃውሟችንን ጨዋነት በተሞላበት ሁኔታ ማካሄድ እንዳለብን ተናግሬ ነበር፡፡ከሰላማዊ ሰልፉ በፊት በዚህና በተለያየ መንገድ በማያሻማ ሁኔታ መልዕክት ባስተላልፍም እነሱ ግን ይህን በመቁረጥ አላስተላለፉትም፡፡እነዚህና ሌሎች ምክንያቶች ሲደመሩ የአቶ ሽመልስ ከማል ንግግር ነጭ ውሸት መሆኑን ያስገነዝባል፡፡

ሁለተኛ የአንድ ሀገር መንግስት ዜጎቹ እየተደፈሩ፣በማጎሪያ ካምፕ በረሀብና በውሃ ጥም፣ሌላው ቢቀር መጸዳጃ ቤት እንኳ ተከልክለው ፍጹም ከሰውነት ክብራቸው ወርደው እየተበደሉ፣እየተገደሉ ባለበት ወቅት ገና ለገና ተቃዋሚ ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ላይ በሚንጸባረቅ ጥላቻና ተቃውሞ የዲፕሎማሲ ግንኙነቴ ይበላሽብኛል ብለን መናገር እንችላለን?ሌላው ይቅር አንድ ክፉና ደጉን የለየ ሰው የሚያስበው ጤነኛ ሃሳብ ነው ማለትስ ይቻላል?

ከእገዳው ባሻገር የሚደንቀው ነገር ደግሞ በፓርቲያችን አመራሮችና አባላት ላይ የተደረገው ድብደባ ነው፣የሆነ ማስተላለፍ የፈለጉት ነገር ያለ ይመስላል፡፡የጭካኔያቸውን መጠን እንድናውቅ የሚደበድቡት አቅመ-ደካሞችን፣ሽማግሌወችንና ሴቶችን እየመረጡ በፍጹም አረመኔነት ነበር፡፡ይህን ተግባራቸውን ስመለከት የደረሱበትን የዝቅጠት ደረጃ መታዘብ ችያለው፡፡ከፖለቲካ ልዩነትም፣ከአምባገነንነትም በላይ ሰወቹ እንደታመሙ ነው ለመረዳት የቻልኩት፣ስር የሰደደ የቁስ ሰቀቀንና የስልጣን ጥም የተጣባቸው፣ለዚያ ሲሉም የትኛውንም አይነት ውርደት ለመቀበል የቆረጡና የሞራል ልዕልናቸውን ሙሉ በሙሉ ያጡ ሰዎች ናቸው፡፡ስነ-ልቦናቸው ክፉኛ ተቃውሷል እንጂ ሀገር እመራለው የሚል ቡድን እንዲህ ያለ ተግባር ይፈጽማል ለማለት እቸገራለው፡፡በአባላቶቻችን ላይ ክፍኛ ድብደባ ተፈጽሟል፣እስከዛሬም እግሮቻቸው መራመድ የማያስችላቸው፣የሚያነክሱ ሰዎች አሉ፡፡እውነት ለመናገር ይሄ እብደት ነው፡፡አንዲት እራሷን መከላከል የማትችል ሴትን ለሶስት መደብደብን ከዚህ በተሸለ ልገልጸው አልችልም፡፡

አንድ ማስገንዘብ የምፈልገው ነገር ለኛ ዋነው ጉዳይ የዜጎቹ ህጋዊነት ወይም ህጋዊ ያለመሆን ጉዳይ አይደለም፡፡በምንም አይነት መንገድ ሴቶች እየተደፈሩ፣ወንዶች በየስርቻው እንደ ውሻ ተቀጥቅጠው እየተገደሉ እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች ታጉረው ይህን ሁሉ መከራ መቀበላቸውን ልንታገሰው፣ወይም ከህጋዊነት አንጻር እየተራቀቅን ልንመለከተው አንችልም፣ስለ ህግም ከተወራ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ጭፍጨፋው ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ባላቸው ላይ ጭምር ሲፈጸም እንደነበር አምኗል፡፡

ባለንበት የግሎባላይዜሽን ዘመን የአንዱ ሀገር ዜጋ ካለ ሀገሩ መገኘት አገር ይያዝ የሚያስብል አይደለም፡፡መውጣት ካለባቸው ጊዜ በመስጠት፣ከመንግስታቸው ጋር በመነጋገር በዘዴ ነገሩን መከዎን እየተቻለ አንድ ሀገርና መንግስት በሰዎች ላይ እንዲህ የጭካኔ ጥግ የሆነን አቋም ይዘው መንቀሳቀሳቸው ፍጹም ኢ-ሰብአዊነት ነው፡፡
ለኢትዮጵያውያን እንዲህ ያለ አስከፊ ጊዜ የለም፣እውነቱን ለመናገር ለአገዛዙ ሰዎች የነበረኝ ጭላንጭል ተስፋም አፈር ተደፍቶባታል፣እንዲህ ግልጽ የሆነ ጭፍጨፋ እየደረሰብን እንኳ በድፍረት ለመናገር አልፈለጉም፡፡ስለ ኢትዮጵያውያን መገደል ለማውራት ሲፈልጉ ሌላ ሀገር ይጠቅሱና እነሱም እኮ እየተገደሉ ነው ይላሉ፣ወገን ከምንለው የማህበረሰባችን አካል ይሄን መስማቱ ከጥቃቱ ይበልጥ ያማል፡፡

ለምሳሌ ኢቲቪ ስጉዳዩ ሲያወራ ህገ ውጥ ሊባል የሚችል ድርጊት ተፈጽሟል በማለት ነው፡፡ተመልከቱ! እንዴት ያለ ባዕድነት ነው?ኢትዮጵያውያን በድህነትም ውስጥ እንኳ ለክብራችን የመሞት ባህሪ አለን፣ይሄ ከቀደሙት አንጡራ ኢትዮጵያውያን የወረስነውና ዛሬም ያለን ሀብታችን ነው፡፡

ትናንት ፍየል ጠባቂ የነበረ በረኸኛ ይህን ክብራችንን ገፍፎ እንደውሻ ቀጥቅጦ ስርቻ ሲጥለን ያልተቆጣ መንግስት ኢትዮጵያዊ ነው?ከዜጎቹ የወጣና ለህዝቡ የቆመ እውነተኛ መንግስት ከዚህ የበለጠ የሚቆጣበት ጉዳይ ከወዴት ይመጣል?
እውነተኛ መንግስት ቢሆን ኖሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሳውዲ ካምፓኒዎችን በሰአታት ውስጥ ማባረር፣ኢምባሲውን ዘግቶ አምባሳደሩን ማሰናበትን የመሳሰሉ ውሳኔዎችን ያሳልፉ ነበር፡፡የሆነው ግን በተቃራኒው ነው፣የድፕሎማሲ ግንኙነቴ ሊበላሽ ይችላል ብሎ እኛ ድምጻችን እንዳናሰማ ደበደበን፣አፈነን፡፡በግልጽ እንደሚታየው የጥቅም ትስስሩ ነው አፋቸውን ያዘጋቸው፣ይህች ጥቅማቸው እንዳትቋረጥ በዜጎች ህይዎት መደራደርን መርጠዋል፡፡

ስነ ልቦናቸው የተቃወሰ በመሆኑና ተራ ስስታሞች በመሆናቸው እንጂ ኢንቨስትመንትም ሆነ ዲፕሎማሲ ግብአትነታቸው ለሰው ልጅ ነው፣እንደ አህያ ሲያፈጋ ከርሞ ሬሳቸውን ለላከ መንግስት እንዴት ተመጣጣኝ ምላሽ ለመመለስ ይገዳል?እንዴት እንደ ኢትዮጵያ ያለች ታሪካዊትና ለአፍሪካ የነጻነትና የኩራት ተምሳሌት የሆነች ሀገርን እየመሩ እንዴት ትናንት የነዳጅ ዘይት ባቆማቸው እረኞች ስትዋረድ ዝም ይላሉ?!::
እንዴት!
በዜጎች ህይወት የተደራደረው አገዛዝ ማለፉ አይቀርም፣ለዚህ ጥርጥር የለኝም፡፡ታሪክ ለመጥቀስ ብዙ ርቀት መሄድ አያስፈልግኝም፡፡የቅርብ የሰሜን አፍሪካ አምባገነኖች የከፋ ፍጻሜ አለና፡፡ኢትዮጵያውያን ፍቅርም ጸብም እናውቃለን፣ሳውዲወችም የፈጸሙትን ግፍ ማወራረዳቸው አይቀርም፡፡በዚህ ክፉ ጊዜ ስለስብአዊ መብት ቆመናል የሚሉ አለም አቀፍ ተቋማት ዝምታን መምረጣቸው እውነተኝነታቸውን ለመመርመር ጥሩ እድል ይሰጠናል፡፡
መንግስት ቢኖረን ኖሮ ይሄ ሁሉ ውርደት ይፈጸምብን ነበር ብየ አላስብም፡፡በዚህ ሰአት ርዕሰ-መንግስት ብሆን ኖሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትልቅ ድርጅት እንደመሆኑ፣ወደየትኛውም ሀገር የሚደረገውን ጉዞ አቋርጨ ዜጎቸን ማስወጣትን አስቀድም ነበር፡፡ያሄ ጥቂት ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ሊያመጣብን ቢችልም ከከፋው የዜጎች ስቃይ ጋር ግን በአንድ ሚዛን ላይ አይቀመጥም፡፡የአደጋ መከላከያና ዝግጁነት ኮሚሽን የሚባል ድርጅት አለ፡፡በዜጎቻችን ላይ ጎርፍና ድርቅ ሲመጣ ብቻ ነው የሚንቀሳቀሰው? ይሄም ሰው ሰራሽ አደጋ ነው ሙሉ ሀይሉን ወደዚህ አዙሮ ሊንቀሳቀስ ይገባው ነበር፡፡

እርግጥ ነው ባቀድነው መሰረት ሰላማዊ ሰልፉ ሙሉ በሙሉ ስኬታማ እንዳይሆን አድርገውታል፡፡ጩኸቱ ግን ይቀጥላል……ባለን አቅም ሁሉ አፈናውንም፣ወከባውንም ተቋቁመን ለዜጎቻችንና ለኢትዮጵያዊነት እንታገላለን፡፡
አገዛዙ ይሄን ሰላማዊ ሰልፍ ሲያፍን ለኢትዮጵያ ህዝብ እንድ መልእክት አስተላልፏል፣ይህን መልእክት እንዲያስትላልፍ ማስገደዳችንም ለኛ ትልቅ ስኬት ነው፡፡የሳውዲ መንግስት ያሻውን ያደርግ ዘንድ የፈቀድኩት እኔ ነኝ፣በመሆኑም እሱን በመቃወም ግንኙነቴን አታበላሹ ብሎ እርምጃ በመውሰዱ ህዝቡ የነገሩ ቁልፍ የት እንዳለ፣የአጥቂወቹ በራስ መተማመን ምን ላይ እንደቆመ በጠራ ሁኔታ ለመመልከት እንዲችል ሆኗል፡፡

ይሄ ሁሉ ነገር እየተፈጸመ የተስተዋለ አንድ ነገር አለ፡፡የጠቅላይ ሚኒስትሩ ዝምታ እውነተኛ ማንነታቸው፣እውነተኛ በአገዛዙ ውስጥ ያላቸውን ቦታ ያሳየን ክስተት ነው፡፡እንደሚታወቀው እሳቸው በኢህአዲግ እንጂ በኢትዮጵያ ህዝብ የተመረጡ አይደሉም፡፡ኢህአዲግ የሚናገረው ከሌለ እርሳቸው የሚሉት አይኖርም፡፡እንደ አንድ ሀገርና ህዝብ መሪ ግን የመኮነንም ሆነ የማጽናናት ቃል ይጠበቅባቸው ነበር፡፡

ባሉበት ቦታ ያስቀመጣቸው ህወሀት ነው፤ድርጅቱ ደግሞ ይሄን አቋም አልወሰደም፡፡ስለዚህ እንደሚቆጣቸው ስለሚያውቁ ዝምታን መረጡ፣ቸልታንም አስበለጡ፡፡በሀገርም ሆነ በግለሰብ ደረጃ ከዚህ በላይ ሽንፈት ያለ አይመስለኝም፡፡

(ይህ ጽሁፍ በፋክት መጽሄት ተስተናግዷል፣ነገር ግን መጽሄቱ ላልደረሳቸው ሰዎች ይደርስ ዘንድ እዚህ ለማስተናገድ ወደድኩ፡፡)

የሥራ ተቋራጩ በ2 ዓመት ጊዜና በ3 ሚልዮን ብር ወጪ ግንባታውን አጠናቅቆ ማስረከብ ነበረበት፤ ይኹንና የሥራው መጠን ከ65 በመቶ በላይ ባልተራመደበትና ከውለታ ጊዜው ውጭ ለ6ኛ ዓመት በዘገየበት ኹኔታ አላግባብ በቀረበ የተቋራጩ የይገባኛል ጥያቄ ከብር 8 ሚልዮን በላይ ወጪ መከፈሉ ተጠቁሟል፡፡ ቋሚ ሲኖዶስ መስከረም ፰ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት÷ በ3 ሚልዮን ብር በ2 ዓመት ጊዜ […]

የኃያላኑ መንግሥታት ልዑካንና የኢራን ተወካዮች በኢራን የኒዩክልየር መርሃ ግብር ላይ ጄኔቫ ላይ የጀመሩት ድርድር ይሁንታ መልስን አግኝቶ መጠቃለሉ ተነገረ። አሁን የተደረሰዉ ስምምነት ከኢራን ጋር መፍትሄ ለመድረስ የሚያስችለን ዋና መሰረታዊ ጭብጥ ነዉ ሲሉ፤

የኃያላኑ መንግሥታት ልዑካንና የኢራን ተወካዮች በኢራን የኒዩክልየር መርሃ ግብር ላይ ጄኔቫ ላይ የጀመሩት ድርድር ይሁንታ መልስን አግኝቶ መጠቃለሉ ተነገረ። አሁን የተደረሰዉ ስምምነት ከኢራን ጋር መፍትሄ ለመድረስ የሚያስችለን ዋና መሰረታዊ ጭብጥ ነዉ ሲሉ፤

Image

ይህ ቀን በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 4ኛው ምድብ ችሎት በመንግስት አቃቤ ህግ በኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች ላይ የተከፈተውን የሽብር ድርጊት ፈፃሚነት ክስ የመጨረሻ ብይን የሚሠጥበት ቀን ነው፡፡

በዚህ ቀን ፍርድ ቤቱ ሲመለከት የቆየውን አቃቤ ህጉ ያቀረበውን መረጃ በማየት ኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች በቀረበባቸው የሽብር ድርጊት ፈፃሚነት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው አግኝቻቸዋለው በመሆኑም እራሳቸውን ይከላከሉ አልያም ደግሞ ጥፋተኛ ሆነው አላገኘዋቸውም በማለት በነፃ እንዲሰናበቱ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች የሽብር ክስ ተምስርቶብን ከ አንድ አመት በላይ በእስር ቤት ስቃይ ላይ እያሳለፍን ብንገኝም ለቆምንለት አላማ ግን ፍፁም በፅናት ላይ እንገኛለን፡፡

የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ የህዝብ ወኪሎች ናቸው፡፡ ኮሚቴው ማለት ኢትዬጰያውያን ሙስሊሞች ማለት ነው፡፡ ህጋዊ የሆነ ውክልና ያላቸው በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ የሚገኙ የኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች አንድ አካል ናቸው፡፤

ህዳር 23 የሚበየነወ የጥፋተኝነት ብይን በኮሚቴው ላይ ሳይሆን በኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች ላይ ነው፡ ለዚህም ነው ህዳር 23 በኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች ላይ በሽብር ድርጊት ፈፃሚነት የቀረበው ክስ ብይን የሰጥበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የምንገልጸው፡፡

ኮሚቴውን እና ህዝብን ፈፅሞ መለየት አይቻልም፡፡ ለቀሩት 10 ቀናቶች የኮሚቴዎቻችን የፍርድ ሂደት ሳይሆን መባል ያለበት የኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች የፍርድ ሂደት መባል እንደሚኖርበት እሙን ነው፡፡

በመሆኑም ኮሚቴው ማለት የኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች ማለት በመሆኑ በዚህ ክስ አንተም፣እኔም፣ አንቺም፣እነሱም መወንጀላችን በመገንዘብ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 4ኛው ምድብ ችሎት የሚሰጠው ብይን በሁሉም ኢትዬጲያውያን ሙስሊሞች ላይ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡

ፍትህ ለኢትዬጲያ ሙስሊሞች!!!
BY:- ABU DAWD OSMAN

Source Addis Admass local newspaper addis abeba

Image

ራውዳ ጀማል ትባላለች፡፡ የሃያ ዓመት ወጣት ናት፡፡ ስለራስዋም ሆነ በሳኡዲ ስላሉ ኢትዮጵያውያን ወቅታዊ ሁኔታ ስታወራ እያለቀሰችና እየተወራጨች ነው፡፡ ለማነጋገር ስቀርባት “ወንድ ከሆናችሁ ጋዜጠኞች ነን፣ የህዝብ አፍ ነን ካላችሁ፤ እዚህ ተቀምጣችሁ፣ “ሁለት ሰው ሞተ” እያላችሁ ከምታቅራሩ ሳኡዲ ሂዱና በየቀኑ ሁለት ሶስት ሰው የሚሞትበትን እልቂት ተመልከቱ፣ “ሰዎቹን ምን እየሰራችሁ ነው?” ብላችሁም ጠይቁልን” አለችኝ። መቅረፀ ድምፄን ሶስት አራት ጊዜ ያስጠፋችኝ ቢሆንም በመጨረሻ ግን ለቃለ ምልልስ ፈቃደኛ ሆነችልኝ፡፡
ስንት ዓመት ቆይተሽ መምጣትሽ ነው?
ከሁለት ዓመት በኋላ ነው የመጣሁት፡፡ እስከ አስረኛ ክፍል የተማርኩት አዲስ አበባ ቢሆንም፤ የኮምቦልቻ ልጅ ነኝ፡፡
እንዴት ነበር የሄድሽው?
በፓስፖርት… በኮንትራት ነበር የሄድኩት … ካላስ! የሰውየው ልጆች ግን “የማይሆን” ፊልም ተመልከቺ እያሉ ያስቸግሩኝ ነበር፡፡ ሲመረኝ ጠፍቼ ወጣሁ፡፡ ከዚያም ከጓደኞቼ ጋር በነፃነት ቤት ተከራይተን እየኖርን፣ በ1800 ሪያል ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩኝ፡፡ ቤተሰቤንም ገንዘብ እየላኩ እረዳ ነበር፡፡
ወደ አገርሽ እንዴት ተመለስሽ?
ውጡ ሲባል… ረብሻ ሲነሳ.. ጓደኞቻችን ሲሞቱ.. ሲደፈሩብን.. ‘ድሮም ስደተኛ ክብር የለውም’ ብዬ ተመልሼ መጣሁ..ከሚገሉኝ ከሚያበለሻሹኝ ብዬ እጄን ሰጠሁ፡፡ ብዙ ኢትዮጵውያኖች ችግር ላይ ናቸው.. እባካችሁ ድረሱላቸው፡፡ ብርዱም ፀሃዩም ሲፈራረቅባቸው.. ያሳዝናሉ፡፡ ብዙ ያልመጡ አሉ፤ መምጣት እየፈለጉ፡፡ ስቃይ ላይ ናቸው፡፡ እኔ አሁን አስራ ሶስት ቀን ታስሬ ነው የመጣሁት፡፡ እስቲ ስለ እስሩ ንገሪኝ … ሁለት ቀን ያለ ምግብ ያለ ውሃ ነው የታሰርነው። ከዛ በኋላ ግን ጥሩ ምግብ ሰጥተውናል፣ ጥሩ መኝታም አግኝተናል፡፡ ብዙዎቹ ግን ከእኛ የባሰ ችግር ላይ ናቸው፡፡ መጠለያ ያላገኙ አሉ… ኤምባሲያችንም አይሰማም እንጂ ስንት ጊዜ ደውለን ተናግረናል መሰለሽ፡፡ ግን የሚሰማ የለም፡፡ ከአገራችን ውጡ ካሉ በኋላ ትዕግስት ያጡና መልሰው ይዩዙናል፡፡ በዛን ጊዜ አበሻው፣ ሻንዛ/ጩቤ ይመዛል፡፡ ፖሊስ ራሱን ለማዳን ይተኩሳል። እኔ እንደውም ደህና ነኝ፤ እዛ ላሉት ድረሱላቸው። በምድረ ዱርዬ እየተደፈሩ ነው ያሉት /ለቅሶ/ ስንት ህፃናት አሉ የሚሞቱ፣ የሚታመሙ፡፡ ስንመጣ ደሞ፤ ሻንጣ አትያዙ ተብለን ተመናጭቀን…በጥፊ ተመትተን..መከራችንን በልተናል፡፡
ወንዶችና ሴቶች ለብቻ ነበር የተቀመጣችሁት?
የተቀመጣችሁት አትበይ! የታሰራችሁት በይ፡፡ … የሴት እስር ቤት ለብቻው ነው በሴቶችና በህፃናት ለቅሶ የተሞላ ነው፡፡ እኔ ራሴ ስድስት ያበዱ ሴቶችን ይዤ መጥቻለሁ…/ለቅሶ/
አሁን ቤተሰብ እየጠበቅሽ ነው?
ነበረ ግን ሻንጣዬ ጠፋብኝ፡፡ በርግጥ ጤነኛ ሆኖ መምጣትም ቀላል አይደለም፡፡ እዛ ያሉትን ጥለናቸው ስንመጣ እያለቀስን ነው፡፡ እስር ቤቱ ውስጥ አንድ እርጉዝ ሞታብናለች፡፡ እዛው እስር ቤት እያለን ምጥዋ መጣ፤ ግን የህክምና እርዳታ ባለማግኘትዋ ሞተች፡፡
እስር ቤት ያሉት ምን ያህል ይሆናሉ?
ሰማኒያ ክፍል አለ..በየክፍሉ ስልሳ አምስት ስልሳ አምስት ሰው ነው ያለው፡፡ መካሲመሺ እስር ቤት ይባላል፡፡ የወንድና የሴት እስር ቤት የተራራቀ ነው፡፡ በጣም ረጅም ከመሆኑ የተነሳ በመኪና እንጂ በእግር አይሞከርም፡፡ በአሁኑ ሰዓት በከተማው ያለው እስር ቤት ሞልቶ የመዝናኛና የስብሰባ አዳራሹን ሁሉ እስር
ቤት አድርገውታል፡፡ የተደፈሩት የሞቱት..ሴቶች ብዙ ናቸው፡፡ አንዷን እርጉዝ ለሶስት ሲደፍሯት ሞታለች፡፡
የሌሎች አገር ስደተኞችም እየወጡ ነው ተብሏል…
አዎ፡፡ ኢትዮጵያዊው ከበደሉ ብዛት የተነሳ እየተናነቀው እኮ ነው ግጭቱ የሚከረው፡፡
ሚስቱን እህቱን ከእጁ መንትፈው ሊወስዱበት ሲሉ ነው ጦርነት የሚነሳው፡፡ አበሻ ወንድ እየሞተ ያለው ‹‹ሴቶቻችንን አትንኩብን..›› ስለሚል እኮ ነው፡፡ ኤምባሲው ሊደርስላቸው ይገባል፡፡
አዲስ አድማስ ጋዜጣ

Written By: Kassahun Addis


The regime in Addis Ababa and its diplomatic missions around the globe spend more time bedeviling members of the Diaspora opposed to the lack of democracy in Ethiopia. While they should be working to promote the interest and safety of citizens abroad, they spend resources spying on individuals, dividing communities and fundraising. This is on top of unofficial import export business most embassy officials are engaged in.

The original picture

The photoshopped picture in the tigraionline.com article
This short piece is to put further light on how low these embassies go to achieve their goals. A picture caption of a story published on Tigraionline.com by the Public Relation head, Tsehaye Debalkew, of the embassy ask “What evidence do you want more than a picture?” (See the article written by Ato Tsehaye, an official working for Ethiopian embassy in DC, USA )

How far will the Ethiopian Embassy in Washington DC go to taint everyone opposed to the systemic and gross violation of basic human rights in the country as hate mongers, Eritrea loving, power mongers? Well, the answer is they will use basic paint program from their desktop and do amateurish Photoshop of pictures showing Ethiopians rallying against the Saudi abuse of their fellow country men and women.

Ato Tsehaye Debalkew accuses what he calls the “few Diaspora” of “character assassination.” The irony is that he, and the office he represents, manipulated a picture, or used manipulated picture, to assassinate the characters of the “few Diaspora” Then to add insult to our intelligence, he captioned it “What evidence do you want more than a picture?”

I wouldn’t have been surprised if sharing of this fake picture was only circulated in social media. Apparently there were already 50+ shares of this picture. Well, that is unregulated sphere and anyone can do anything. But coming from an official, spokesperson, of the embassy and carried by tigraionline, a semi official website, I felt obliged to put this together.

ምንሊክ ሳልሳዊ :-በወያኔ የመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ውጥረት መፈተሩን ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ተሰምቷል:: በወታደራዊ ጥቅማ ጥቅም እና በህገመንግሥቱ ዙሪአ ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ አካል መጥፋቱ እና ዝም መባሉ ዉስጥ ውስጡን እየተብላላ ያለው የመኮንኖቹ ጥያቄ እንዳይፈነዳ የተሰጋ ሲሆን ከፈነዳ ሰራዊት ለሶስት ቦታ እንደሚከፈል ለምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

መኮንኖቹ በትምህርት በስራ እና በማእረግ እድገት በቤተሰብ እንክብካቤ በደሞዝ ጭማሪ እና በሕገመንግስታዊ የህዝብ መብቶች ዙሪያ ጥያቄ ያነሱ ሲሆን ወታደራዊ ጥቅማ ጥቅሞች ለአንድ ብሄር አባላት ብቻ ተመድበው እየተሰራባቸው ነው ከተማ ውስጥ ታጥቀው የመሸጉ እና ህዝብን እያጠቁ የሚገኙት የአንድ ብሄር አባላት ናቸው እንዱሁም ከሃገራዊ ጥቅም ይልቅ የፓርቲ ጥቅም እየተስተዋለ ነው:ወታደሩ የጦር ሳይንስን እና ዲሲፕሊን በጎደለው መልኩ እየተስተዳደረ ነው በሰራዊቱ እና በሃገሪቱ ሁሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን ሽፋን እና ማዘናጊያ በማድረግ የሙስና እና የዘረፋ መስፋፋት መልስ ሊያገኝ ይገባዋል ጄኔራል መኮንኖች አላቸው የተባለው ንብረት ይጣራ በሃገሪቱ የፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች ሊመለሱ ይገባል የሚሉ እና ተመሳሳይነት ያላቸውን ጥያቄዎች ማንሳታቸው ታውቋል::የመከላከያ አባላቱ በኑሮ ውድነት እና በተቃዋሚዎች ህገመንግስታዊ መብቶች ላይ ያነሱት ጥያቄ አዛዦቹን ያስደነገጠ ከመሆኑም በላይ በአንድ ብሄር ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እስከመቼ የሚለውም ጥያቄ መመለስ አለበት በሚል የእግር እሳት እየሆነባቸው ነው::

ይህ ከዚህ ቀደም የተጀመረው እና አሁንም በሰሜን እዝ እና በምስራቅ እዝ የተከሰተው የሰራዊቱ ህገመንግስታዊ ጥያቄ እና የጥቅማ ጥቅም አቤቱታ በመላው ሃገሪቱ ተስፋፍቶ በሁሉም የሰራዊት እዞች ውስጥ ጥያቄው መነሳቱን ምንጮቹ አመልክተዋል::በተለያዩ ጊዜያት እየተንከባለለ የመጣው ይህ የሰራዊቱ አቤቱታ እጅግ አደገኛ አዝማሚያ እያሳየ ሲሆን በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አስተዳደር እንዲወገድ እና ህገመንግስታዊ መብቶች እንዲከበሩ ጥያቄዎች ገፍተው መምጣታቸው ሲታወቅ ከፍተኛ የሕወሓት ጄኔራሎች በየቀኑ ካለማቋረጥ ምስጢራዊ ስብሰባዎችን እያደረጉ ከመሆኑም በላይ ከየእዙ የሚመጣላቸው ሪፖርት መፍታት የሚቻልበትን ጉዳይ እየተወያየ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም ምንጮቹ ገልጸው ነበር::

ሌ/ጄ ሳሞራ የኑስ ጡረታ ወቶ በምትኩ የብኣዴን ሜ/ጄ አበባው ይተካሉ ሲባል ወያኔ በድንገት የመለስ የቅርብ ሰው የነበሩትን እና በአንድ ወቅት የአማር ክልል አቶ አያሌው ጎበዜን ላንቻ አከባቢ በመኖሪያ ቤታቸው ለ3 ወር አግተው ሲያሰቃዩ የነበሩት ሌ/ጄ ዮሃንስ ገብረመስቀልን በማእረግ ሾሞ ሳሞራ የኑስን ለመተካት የሚያደርገውን ሩጫ የብኣዴን አባላት መቃወማቸውን ተከትሎ ጄኔራል አባባውን ጨምሮ የብኣዴን መኮንኖችን ያገለለ የሕወሃት አባላት የሆኑ ጄኔራሎች ብቻ የተሳተፉበት በትግሪኛ የተመራ ስብሰባ መደረጉን ውስጥ አዋቂ ምንጮቹ ተናግረዋል::በስብሰባው ላይ ቀሪ ከፍተኛ ባለማእረግ መኮንኖች እና የመምሪያ ሃላፊዎች ለምን አልተሳተፉም የሚል ጥያቄ ከአንድ ስማቸው ካልተጠቀሰ ብርጋዴር ጄኔራል መነሳቱን ምንሊክ ሳልሳዊ ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ይህ ስብሰባ ዋና አትኩሮቱ የነበረው በብሄር አደና ላይ ሲሆን እንደ ምንጮቹ መረጃ በአማራ እና በኦሮሞ መኮንኖች እየተመራ ያለውን የለውጥ ጥያቄ በማክሸፉ ዙሪያ እንደነበር እና አሁንም በስፋት የሕወሓትን የፓርቲ አቋም የሚቀበሉ እና የጥቅም ተጋሪ የሆኑ ሰዎችን ለመሾም የታቀደ ሲሆን እንዲሁም ከፖለስ ሰራዊት በከፍተኛ የማእረግ ሹመት ወደ ጦር ሰራዊቱ ለማምጣት የታሰበ ሲሆን በወታደራዊ ደህንነት ዙሪያ ሌላ ተጨማሪ ሰልጣኞችን ከፖሊስ ወስዶ በማሰልጠን ወደ ሰራዊት ማዘዋወር የሚሉ ውይይቶች ተካሂደውበታል:: አሁንም ስብሰባው የቀጠለ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን እንለቃለን::

በአፍሪቃ በእስራት የሚፈለጉት እና በወቅቱ በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ ተሸሽገው የሚገኙት የዩጋንዳ ዓማፅያን ቡድን፣ በምህፃሩ የሎርድ ሬዚስተንስ አሚ፣ « ኤል አር ኤ » መሪ ጆሴፍ ኮኒ እጃቸውን ለመስጠት በማሰላሰል ላይ መሆናቸው ተሰማ።

Image

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው መጠን የለሽ የመብት ጥሰት ለመቃወም በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በየአገራቱ የሚገኙ የሳውዲን ኢምባሲዎችን በተቃውሞ እያጨናነቁ ነው። በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ባለው ዘግኛኝ በደል የተሰማቸውን ጥልቅ የመጠቃት ስሜት ኢትዮጵያን በተቃውሞ ሰልፎቹ ላይ በሚያሰሟቸው መሪር የሐዘን እንጉሮችና የቁጭት ንግግሮች እየገለፁ ነው። ከሐዘንና ቁጭት ባለፈም ለበደል ለተጋለጡ ወገኖቻችን አስቸኳይ ሰብዓዊ ርዳታ ለማድረስ እና የዲፕሎማሲ ድጋፍን ለማሰባሰብ ዓለም ዓቀፍ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ሥራውን ጀምሯል።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን ዓለም ዓቀፍ ጥረት ለመደገፍ በውጭ አገራት የሚገኙ አባላቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፏል።

ይህ ሁሉ በውጭ አገራት እየተደረገ ያለ ጥረት ነው። ኢትዮጵያዊያን ባሉበት አገራትና ከተማዎች ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ በአንድነት መንቀሳቀሳቸው የሚያስደስት ነገር ነው። ሌላው ቀርቶ በሳዉዲ ዋና ከተማ ሪያድ ውስጥ እንኳን ኢትዮጵያውያን የሳውዲን መንግሥት ተቃውመው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል።

የሳውዲ መንግሥት በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ የያዘውን ጨካኝ አቋም እና በመንግሥት እውቅና በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል መቃወም ያልተቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ!!! ይህ እጅግ ያማል፣ ልብን ያደማል።

ወያኔ የሳውዲ የንግድ ሸሪኮቹን ለማስደሰት የፈንሳይን ግማሽ የሚያህል ለም መሬት በነፃ መስጠቱ በቂ አልመሰለውም። በአገራቸው ኢትዮጵያዊያንን ሲጨፈጭፉ፣ ሲገሉና ሲደፍሩ በቸልታ መመልከቱ በቂ የወዳጅነት ስጦታ መስሎ አልተሰማውም። እናም ሸሪኮቹ የበለጠ እንዲደሰቱና ከእስከዛሬ በበለጠ ገንዘብ እንዲደጉሙት ለማበረታታት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲያቸው ፊት ለፊት ኢትዮጵያንን ደበደበላቸው።

ወያኔ ከሳውዲ ጋር ያለው ግኑኝነት “የቢዝነስ ሽርክና” ነው። ቢዝነሱም ኢትዮጵያዊያንን በቁማቸው መሸጥንም ያጠቃልላል። የወያኔ ሹማምንት እና የሳውዲም ቱጃሮች በዘመናዊ ባርነት ንግድ ውስጥ አቀባይና ተቀባይ ናቸው። ለዚህም ነው እየተነገደበት ያለው ምስኪን ኢትዮጵያዊ እጣ ፈንታ በአዲስ አበባና በሪያድ አንድ ዓይነት የሆነው። እዛ ዱላ፤ እዚህም ዱላ። እዛ እስር፤ እዚህም እስር። እዚያ ስድብ፤ እዚህም ስድብ። እዚያ ቶርቸር፤ እዚህም ቶርቸር። በባርያ ንግድ ውስጥ አቀባዩም ተቀባዩም ባርያዉን መግዛታቸው፣ መስበራቸው፣ መግደላቸው የማይቀር መሆኑ የታወቀ ነው።

ሌላው አሳዛኝ ጉዳይ ደግሞ የወያኔ ድኩማን ሹማምንት የሚሰጡት አስተያየት መስማት ነው። በሳውዲ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፍትህ ለመጠየቅ በመላው ዓለም እና በአዲስ አበባ ደግሞ በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት ወደ ጎዳና በወጡ ኢትዮጵያዊያን የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ተብየው “የፋሺሽት መፈክር አንግቦ በተጎሳቆሉ ዜጎች ስም የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መጣር ብሎም መንግሥት በዜጎቹ ግዴለሽ እንደሆነ አስመስሎ ማቅረብ” ሲል ተሳልቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተብየው ጨምሮ ሁሉም የወያኔ ሹማምንት “ሳውዲዎች በግዛታቸው ውስጥ ያሻቸውን የማድረግ “ሉዓላዊ” መብት አላቸው፤ መንግሥታችን የሳውዲ አረቢያን ሉዓላዊ መብት ያከብራል” እያሉ ይከራከራሉ። ለመሆኑ ይህንን የሚሉት ከልባቸው ነው? ፈጽሞ። ኢትዮጵያዊያንን ማሰቃየትና መግደል የቢዝነሳቸው አካል ስለሆነ ነው እንጂ የሉዓላዊነት ትርጉም ይህን ያህል ተምታቶባቸው አይደለም።

ሰብዓዊ መብቶች አገር፣ ድንበር፣ ዜግነት፣ ወይም ሌላ ማናቸው ሰው ሠራሽ ህግጋት ሊጥሷቸው እንደማይገቡ የወያኔ ሹማምንት ቢያንስ ሲነገር ሰምተው ያውቃሉ። ማንኛውም ሰው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መገደል፤ ሰቆቃ (ቶርቸር) እንዲደርስበት ማድረግ፤ ጾታዊ ጥቃት እንዲደርስበት ማድረግ እንደማይቻል ሰምተው ያውቃሉ። ሰብዓዊ መብቶች ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ ሊያገኙት የሚገባ ክብር መሆኑ በተሳተፉባቸው በርካታ ዎርክ ሾፖች ሰምተዋል። ያም ሆኖ ግን በዘመናዊው ዓለም እንስሳ እንኳን ያገኘውን ክብር ኢትዮጵያዊያን ተነፍገው በሪያድ ጎዳናዎች ሲታረዱ፤ በጭካኔ ሲደበደቡና ሲገረፉ፤ ሴቶች ሲደፈሩ፤ ሕፃናት በረሀብና በእርዛት ሲቀጡ የወያኔ ባለሥልጣኖች የበዳዮች አፈቀላጤ ሆነው የሚከራከሩት በዳዮቹ ሸሪኮቻቸው ስለሆኑ ነው።

ይህ ድርጊት በወያኔ እየደረሰብን ያለው በደል ምን ያህል ሥር የሰደደ እንደሆነ እና የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ ምንጭ የት እንዳለ አመላካች ሆኗል።

“ትግላችን የነፃነት ትግል ነው” ስንል “ከማን ነፃ ለመውጣት?” እያሉ የሚሳለቁ እንደነበሩና እንዳሉም ይታወቃል። በወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያዊያን ወደ ባርነት ማሽቆልቆላቸው ይህ ተጨባጭ ማስረጃ ነው። ከወያኔ የባርነት አገዛዝ ነፃ እስካልወጣን ድረስ ሌሎች አገሮች መብቶቻችን የሚያከብሩልን በየአገራቱ ልምድ እና ከወያኔ ጋር ባላቸው ሽርክና መጠን ነው።

ለሳውዲ መንግሥትና ቱጃሮቹ ከነዳጅ ቀጥሎ የሀብታቸው ምንጭ ከየአገሩ የሚመጣላቸው የድሀ ጉልበት ነው። የሳውዲ ቱጃሮች ድሆችን ከባርነት ባልተሻለ መንገድ ረግጠው በመግዛት ኑሮዓቸውን ያደለቡ ናቸው። ለወያኔ አገዛዝ ደግሞ ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛው የገቢ ምንጩ ዜጎቹን በመሸጥ የሚሰበስበው ነው። ለወያኔ፣ ኢትዮጵያዊያን ወንዶችና ሴቶች ትርፍ አምጪ ሸቀጦች ናቸው። ወያኔና ሳውዲ – ሻጭና ገዢ ናቸው።

ባርያ ከሻጩ ነፃ ሳይወጣ ከአንድ ገዢ ነፃ ቢወጣ ሌላ ገዢ ስለሚመጣ ዘለቄታነት የለውም። እኛም ከወያኔ ነፃ ሳንወጣ ከሳውዲ ነፃ መወጣት አይቻለንም፤ ቢቻልም ነፃነታችን ዘላቂነት አይኖረውም።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሳዉዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ በሚደርሰው ጥቃት ክፉኛ ተቆጥቷል። በዚህ የመከራና ጭንቅ ሰዓት ለወገኖቻችን ለመድረስ የሚቻለውን ጥረት ሁሉ ማድረግ እንዳለብን ያምናል። አባላቱ በነብስ አድን ርብርብ በግንባር ቀደምትነት እንዲሳተፉ መመሪያ አስተላልፏል። ይህ አጣዳፊ ሆኖም ጊዜዓዊ መፍትሔ ነው። በግንቦት 7 እምነት የችግሮቻችን ሰንኮፍ ያለው አዲስ አበባ ነው። ሰንኮፉን ሳንነቅል የሚደርስብንን ውርደት በዘላቂነት መቀልበስ አንችልም። ስለሆነም በችግር ላይ የወደቁትን ወገኖቻችን እየረዳን፤ የችግሮቻችን ምንጭ በሆነው ወያኔ ላይ የተባበረ ክንዳችንን እናንሳ ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የጋራ ላይ ፉጨት!!
//ደመቀ ከበደ – ጣና ዳር//

‹‹ሀበሽ አባ ደፋር – አባ ሰው አይፈሬ
ጫማ የለም ከእግሩ – ተሰርቶ ጎፈሬ፤
ሀበሽ አባ ሞጋች – አባ ጎበዝ ጤፉ
ጋራ ላይ ያቅራራል – በጎቹ ሲጠፉ››
የሚሉት ቀረርቶ – የሚሉት ሽለላ
ስንት ወንድ ገደለ – ስንት ጎበዝ በላ፤
‹‹ደፋር ነው እያሉ – ጀግና ነው እያሉ
የሞት ሞቱን ሲሞት – ዳር ቆመው ያያሉ፤
ተውት ይሄን ሶታ – ይሄንን ጠንበለል
ጀግና ነህ አትበሉት – እንዲያው ይንጎማለል፤››
የሚሉት የእናት ወግ – የአባት ማስፈራሪያ
ስንት ወንድ አከሸፈ – እንደ ዘመን ድሪያ፤

እኔ ግን እላለሁ፤
ተውት ይኸን ጀግና – ይውጣ ወደ ጋራ
ይሸልል ይፎክር – እንዳሻው ያቅራራ
እንዳሻው ‹‹ቡ!›› ይበል – ያሻውን ይጣራ
ሰው እንዴት ይኖራል – እያየ መከራ!!

Image


በዚህ 20 አመት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን የማይወጣ ዳገት የሆነው የኢህአዴግ ስርዓት ብቻ አይደለም፡፡ የተቃዋሚዎች መጠላለፍም ህዝብን ተስፋ ሲያስቆርጥ ኖሯል፡፡ እንዲያውም ተቃዋሚ ፓርቲዎች ገዥውን ለመቃወም ከሚያደርጉት በላይ እርስ በእርስ ለመጠላለፍ በርካታ ጊዜያቸውን የሚያጠፉ ሆነዋል፡፡

Image
ሰሞኑን ፌስ ቡክ ላይም የምናነበው ይህን መጠላለፍ ነው፡፡ ሳውዲ ውስጥ ዜጎቻችን ሰቆቃ እየደረሰባቸው ባለው ወቅት ሳይቀር ተቃዋሚዎች እርስ በእርሳቸው ይናቆራሉ፡፡ ምንም እንኳ ጭቅጭቁ ፌስ ቡክ ላይ ቢሆንም የፓርቲዎቹን አቋም ግን የሚያንጸባርቅ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ የሚያስገርመው ደግሞ የሚናቆሩት ይህ ነው የሚባል የፖሊሲም ሆነ ሌላ የሚያጨቃጭቅ ልዩነት ያላቸው ፓርቲዎች አለመሆናቸው ነው፡፡
ተጨቃጫቂዎቹ የዚህ ትውልድ ወጣቶች መሆናቸው ደግሞ ይበልጡን ያስገርማል፡፡ አብዛኛዎቹ ደግሞ ሁለቱ ፓርቲዎች የተቀራመቷቸው የባለ ራዕይ ወጣቶች አባላት የነበሩ ናቸው፡፡ በእድሜ ከገፉት ፖለቲከኞች ይልቅ ወጣቶች ከመግባባትም አልፎ ሁለቱን ፓርቲዎች ማቀራረብ ነበረባቸው፡፡ የአንድነት አባላት ሰማያዊ ፓርቲ ያደረገውን ሰልፍ ሲነቅፉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ደግሞ አንድነት መንግስትን ገፍቶ መሄድ እንዳልቻለ ይተቹታል፡፡ መተቻቸት አንድ ነገር ነበር፡፡ ሆኖም በሁለቱ አባላት መካከል የሚደረገው እሰጣ ገባ ከምክንያታዊነት ይልቅ በመጠላለፍ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ጭራሹን ጥላቻም ይታከልበታል፡፡ ከአሁኑ ካድሬያዊ ባህሪም ይታይበታል፡፡
እንደ እውነት ከሆነ ሁለቱ ፓርቲዎች አብረው ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት ነበረባቸው፡፡ ሆኖም በመካከላቸው ባለው የመጠላለፍና የመጠላላት ችግር ለየብቻቸው አድርገውታል፡፡ አንድነት ደግሞ ጭራሹን አልቻለም፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ አንድነትና ሰማያዊ ክፍተቶች ታይቶባቸው ይሆናል፡፡ ግን እነዚህ ክፍተቶች ኢህአዴግ የፈጸመውን በደል እያለ ሁለቱን መነታረክ አልነበረባቸውም፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ የመጨረሻው አይደለም፡፡ ሁለቱ ፓርቲዎች (ወጣቶቻቸውም) ሌሎች በርካታ ትግሎች ይጠብቃቸዋል፡፡ ባለፈው የታየውን ስህተት በሚቀጥሉት ማረም ይችሉ ነበር፡፡ አሁን የሚታየው ግን አንዱ የሌላውን ስህተት ሲያገን፣ አንዱ ውድቀቱን በሌላው ላይ ሲያላክክ፣ አሊያም በማይተቸው ሲተች ነው፡፡
በበኩሌ ‹‹ተባበሩ አሊያም ተሰባበሩ›› የሚለው መርህ አይመቸኝም፡፡ ቢያንስ ለገዥው ባለመተባበር ላይ ግን መተባበር የግድ ይላቸዋል፡፡ እርስ በእርሳቸው ሲናቆሩ ተስፋ የሚያስቆርጡት፣ የሚያስገዙት ህዝብን ነው፡፡ ከ97 በኋላ የተፈጠረው መከፋፈል፣ መናቆርና መጠራጠር በርካታ ዋጋ አስከፍሎናል፡፡ የፓርቲዎቹ አባላት ደግሞ ቀዳሚ ተጠቂዎች ናቸው፡፡ እናም መጠላለፉ ለገዥው ካልሆነ በስተቀር ለማንም የሚጠቅም አይደለም፡፡ ሀሳብን በነጻነት መናገር አንድ ነገር ነው፡፡ የሀሳቡን ጥቅምና ጉዳት ሳይመዝኑ መዘላለፍ፣ መናቆር ግን ፖለቲካችን በብስለት ላይ ያልተመሰረተ ለመሆኑ አመላካች ነው፡፡
በሚያስማማቸው መተባበር ቢችሉ መልካም ነገር ነው፡፡ መተባበር ባይችሉ እንኳን አንዱ ሌላውን ባለመጥለፍ ቢተባበር መልካም ይመስለኛል፡፡ አይደለም በአሁኑ ዘመን ፖለቲካ በ1970ዎቹ ታጣቂዎች ለገዥዎች ክፍተት ላለመፍጠር ልዩነታቸውን በሰላም ፈትተዋል፡፡ ሳይግባቡ ሲቀሩ እርስ በእስር ላለመጠላለፍ ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህ እንዴት በዚህ ዘመን ያቅታል?
የፓርቲዎች ድክመት ለፖለቲካ ትግሉ እንቅፋት እየሆነ ነው ከተባለ እንኳ ችግሩ መፈታት ያለበት በመጠላለፍ አይደለም፡፡ በሰከነ መንገድ ተወያይቶ መፍታት፣ ተነጋግሮ መግባባት ካልተቻ የየራሱን ትግል አጠናክሮ ትክክለኝነቱን በማሳየት የሌላው መንገድ ስህተት መሆኑን ማሳየት ይገባል፡፡
በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እያደረጉ የሚገኙት እነዚህ ሁለቱ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ኢህአዴግን መቃወም ብቻ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም፡፡ ህዝብ ተቃዋሚዎች የትግሉ ዳገት ላይ ሲደርሱ እርስ በእስር ተጓትተው እንደገና ተስፋ እንደማያስቆርጡት፣ ዋጋ እንደማያስከፍሉት፣ እንደገና ተከፋፍለው እንደማያስገዙት ካወቀ ብቻ ነው ሊከተላቸው የሚችለው፡፡ እንዲያው ቢከተላቸው እንኳ እነዚህን ስህተቶች ላለመድገም መዘጋጀት ይሆርባቸዋል፡፡ ከሁለቱም ፓርቲዎች አባል ባልሆንም ለመጠጋት ስሞክር ይች መጠላለፋቸው እምነት አሳጥጣ እንደገና ትገፈትረኛለች፡፡ ይህ ለሌሎችም ተመሳሳይ ይመስለኛል፡፡ ህዝብ ትግሉን በሙሉ ልብ ለመቃለቀል የሚፈራውም በዚህ ምክንያት ነው፡፡
በቅርብ ጊዜያት እንደምናየው መጠላለፍ ከሆነ አሁን የሚጠላለፉት ፓርቲዎች መካከል አንዱ ስልጣን ቢይዝ ከኢህአዴግ ባልተነሰነሰ ሌላኛውን ለማፈን ወደኋላ እንደማይል ነው፡፡ መሳሪያ ቢኖራቸው ደግሞ ተጨፋጭፈዋል፡፡ ህዝብ ተቃዋሚን የሚደግፈው ገዥውን ስለሚቃወም ብቻ ሳይሆን ገዥው የፈጠሩትን ስህተት የማይደግሙ ከሆኑ ብቻ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ‹‹ብሄራዊ እርቅ›› ሲወራ በኢህአዴግና በተቃዋሚዎች መካከል ስላለው አለመግባባት ነው የሚወራው፡፡ ኢህአዴግ ለብሄራዊ መግባባትም ሆነ ለሌሎች ጉዳዮች እጁን ያልሰጠው ተቃዋሚዎች መካከል ባለው መጠላለፍ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር ይህ የተቃዋሚዎች መጠላለፍ ኢህአዴግ አጋር ፓርቲዎች ከሚሰሩለት በላይ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቶለታል፡፡ ስለሆነም ከገዥው ጋር ከሚደረገው ትግል ቀድሞ ተቃዋሚዎች እርቅ፣ መግባባት…ብቻ ትግሉን ወደኋላ ከመጎተት የሚታደግ አንዳች መፍትሄ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ካልሆነ ግን እንደተለመደው በትኩሳትና ሰሞነኛ ፖለቲካ ዳገቱ ላይ ደርሶ እርስ በእርስ ተከፋፍሎ፣ ህዝብን ተስፋ አስቆርጦ፣ ገዥዎችን አጠናክሮ ከመመለስ ያለፈ ውጤት ጠብ ሊል አይችልም፡፡ ይህ ደግሞ ትውልዱን ለማይወጣው ተገዥነት አሳልፎ ይሰጠዋል፡፡