በመኪና እየተዘዋወሩ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች የደሴን ሕዝብ ሲቀሰቅሱ ዉለዋል። ከደሴ 12 ኪሎሚዕት ርቃ በትምገኘዋ የኩታበር ከተማ ተመሳሳይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ ዜጎችን ፖሊሲ አስቆሞ ለማሰር ሞክሮ የነበረ ሲሆን በአካባቢው የነበረ ሕዝቡ ፖሊስን ከቦ « አታስሯቸዉም» ምንም አይነት ችግር ሳይፈጠር ፖሊሶች ገለል እንዳሉ ከደሴ የደረሰን መረጃ ይጥቁማል። የአንድነት አመራሮች ወደ ደሴ ነገ ጠዋት ያመራሉ :: የአንድነት ከፍተኛ […]

በአዲስ አበባ፣ በዛሬው ቀን በተደረገው ቅስቀሳ ከአምሳ ሶስት በላይ አባላትና ደጋፊዎች በሺሆች የሚቆጠሩ በራሪ ወረቀቶችን ሲያድሉ ዉለዋል። ከሃምሳ ሶስቱ ወጣቶች ስድስቱ ታስረዋል። እስረኞችን ለማስፈታት ወደ ፖሊስ ጣቢያዎቹ የሄዱት የአንድነት የአመራር አባላት፣ ለምን እስረኞች እንደታሰሩ የፖሊስ አዛዦችን ሲጠይቁ « ሰልፉ የተፈቀደ ሰልፍ ስላልሆነ ፣ ነገሩን እስክናጣራ ነው እንጂ አላሰርናቸው» የሚል ምላሽ ተሰጧቸዋል። «ለሰልፍ ፍቃድ አይጠየቅም። ማሳወቅ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጉዳይ ሪፖርት አቅራቢ ፤ በኤርትራ ሳይቋረጥ የቀጠለው የሰብአዊ መብት ጥሰት በተለይም በብሔራዊ የውትድርና አገልግሎት ረገድ የሚታየው እጅግ የሚያሳስብ ነው ሲሉ ድርጅቱ ሁኔታውን እንዲከታተሉ ያሠማራቸው ወ/ት ሼይላ

«ዴሞክራሲ የለም! ሰልፍ ማድረግ አይቻልም! አርፋችሁ ተቀመጡ ! » የሚሉን ከሆነ ይንገሩን ። የአገሪቷ ሕግ የሚለው ግልጽ ነው። ዜጎች ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ሙሉ መብት አላቸው። አስተዳደሩ በይፋ ሕግ ወጥ ተግባር ነው እየፈጸመ ያለው። ሕጉ እንዲህ ነው የሚለው ፡ “ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ስፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያየት ካለውም ምክንያቱን […]

«ዩክሬን ለወደፊቱ የትልቅ ገበያ ትስፋ አላት።»ተስፋዉ በርግጥ አማላይ ነዉ። የዩክሬን እዉነታ ከሚባለዉ መቃረኑ እንጂ ቀቢፀ-ተስፋዉ። የዩክሬን ሕዝብ የነብስ ወከፍ ገቢ የሞንጎሊያን እንኳን አያክልም። 3800 ዶላር። ኢንዱስትሪዎችዋ-አሮጌ ናቸዉ። ብልጣብልጥ፤ አታላይ፤አጭርበርባሪ ነጋዴ ፤ደላላ፤ ባለሥልጣናት ከብረዉባታል።

ኬንያ በተጠርጣሪ አሸባሪዎች ላይ ዘመቻ ከፍታለች ። ፖሊስ ከዚህ ሳምንት መጀመሪያ አንስቶ በአሸባሪነት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቤት ለቤት አሰሳ እያደነ በማሰር ላይ ነው። እስከ ትናንት ድረስ ከአንድ ሺህ የሚበልጡ ሰዎች መታሰራቸው ተገልጿል።

በደቡብ ኢትዮጵያ በምትገኘው የቡታጂራ ከተማ የሚገኘው ሀኪም ቤት ከአውሮጳ ህብረት በተገኘ 40 ሚልዮን ዩሮ ርዳታ የእናቶችን እና የሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የሚያስችል ፕሮዤ ጀምሮ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። የተመ የሕፃናት መርጃ

4ኛው የአፍሪቃ መንግሥታት እና የአውሮጳ ህብረት ጉባዔ ትናንት ብራስልስ፣ ቤልጅየም በተከፈተበት ወቅት፣ ስለ ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ እና ስለ ፕሬስ ነፃነት የተመለከተ ሴሚናር በዚችው ከተማ ተካሂዶዋል። ሴሚናሩን የጠሩት እና ያዘጋጁት

የዓረብኛ ሥነ-ፅሁፍ በኢትዮጵያ በተሰኝባቀረብነዉ ዝግጅት ላይ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ቋሚ ባልደረባ አቶ አህመድ ዘካርያ በኢትዮጵያ የተገኙት የዓረብኛ ሥነ-ፅሁፎች በዓረብኛ ፊደላት ይቀመጡ እንጂ ቋንቋዉ አገርኛ እንደሆነ በዝርዝር ገልፀዉልናል።

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የእሪታ ቀን በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በተያዘለት ቀንና ቦታ እንደሚካሄድ ለመገናኛ ብዙሀን ካሳወቀበት ከትላንትናው እለት ማለትም መጋቢት 24/2006 ዓ.ም ጀምሮ ለከተማዋ ነዋሪዎች ስለሰልፉ ዓላማ የሚገልፅ በራሪ ወረቀት እያሰራጨ ይገኛል፡፡እስካሁን ድረስ ከ10.000 ሺ በላይ በራሪ ወረቀቶች ተሰራጭተዋል ፡፡ የነገውን ቅስቀሳ የአንድነት ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ እና የአዲስ አበባ […]

የሚሊዮኖች ንቅናቄ እንደዘገበው በአዲስ አበባ ቅስቀሳው ቀጥሏል። ፖሊሶች በርካታ ዜጎችን ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ እያሰሩ ሲሆን፣ አገዛዙ የዜጎችን መሰረታዊ የዉህ.፣ የኔትወርቅን የመብራትና የትራንስፖርት ችግሮችን ከመፍታት ፣ ጊዜና ጉኦልበቱን ሕግን በመናድና ዜጎንች በማሸበር ላይ ያተኮረ ይመስላል። የሚከተሉት ከሚሊዮኖች ንቅናቄ ፌስ ቡክ ገጽ የተወሰዱ ናቸው ፡ የአንድነት ወጣቶችን ቅስቀሳቸውን ቀጥለዋል:: ———————————————— አሁንም ፖሊስ እንቅስቃሴያቸውን እያወከ ይገኛል:: ———————————————— […]

የአንድነትፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን በአዲስ አበባ ለመጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ ማፊያው አስተዳደር የተለመደውን መልስ ሠጥቷል፡፡ ህግ እና ስርዓት ያፈነገጠ፡፡ በአስራ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ሶስት ያወጣው “ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ስርዓት” አዋጅ ቁ. 3/1983 የሚመለከተው አካል “ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ህዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ስፍራ ቢደረግ ይሻላል […]

የአንድነት ለዲሞክርሲና ለፍትህ ፓርቲ መጋቢት 28 ቀን በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ ለአዲስ አበባ አስተዳደር ቢያሳዉቅም፣ አስተዳደሩ ሰልፉ እንዲደረግ የታሰበበት ቦታ፣ ትምህርት ቤቶች ፣ ዩኒቨርሲቲና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ያሉበት በመሆኑ እዉቅና እንደማይሰጥ የሚገልጽ፣ ከሕገ መንግስቱ የተጻረረ ደብዳቤ መላኩ ይታወቃል። የአንድነት ፓርቲ ፣ ምንም እንኳን ቀበና ከሚገኘው ጽ/ቤታቸው እስከ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ጽ/ቤት ድረስ ሊደረግ የታሰበው ሰልፍ […]

የኮሌጁ የደቀ መዛሙርት ም/ቤት ችግሩ በአስቸኳይ እንዲጣራ ከኹለት ወራት በፊት ያስገባው ደብዳቤ ለተጠርጣሪ ደቀ መዛሙርት ሽፋን በሚሰጠውና ተጠርጣሪዎችን በቢሮው እየጠራ በሚያበረታታው የአስተዳደር ዲኑ ያሬድ ክብረት ተቀብሮ መቆየቱ ተገልጦአል፡፡ በቅ/ሲኖዶስ ከተወገዙ ግለሰቦችና ፕሮቴስታንታዊ ድርጅቶች የኑፋቄ አስተምህሮና ተልእኮ የሚሰጣቸው ኅቡእ አንቀሳቃሾች ትኩረታቸውን በአዲስ ገቢ ደቀ መዛሙርት ላይ አድርገዋል፤ በመምህራን ምደባ ተጽዕኖ እስከ መፍጠርና የማስተማር ክፍለ ጊዜዎችን በጋጠ …

የዚህ ጽሑፍ ግብ በመንግስት ስልጣን ሽሚያ የተነሳ በአንድ ወገን በዮሐንስ እና በአሉላ ትውልድ በሌላ ወገን በምኒልክ እና በጎበና ትውልድ መካከል የነበረውን የፖለቲካ ባላንጣነት፣ ለስልጣን ሲሉ የተደራረጉትን እና የፈጸሙትን ስህተት መተረክ አይደለም። በመካከላቸው የነበረው ጸብ ዙፋኑ ለእኔ ይገባ ነበር የሚል ጸብ ነበር፡፡ የስልጣን ጸብ ነበር። በእርስ በርስ ጦርነት የሚፈጸመው ስርዓት አልባው የመንግስት ሽግግር ባህላችን የፈጠረው ጸብ […]

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም;- በነጻነት ለሀገሬ

ታላቅወንድም በአንክሮ እየተመለከቷችሁ ነው! በሚስጥር፡ የሚንሾካሾከው ወሮበላ መንግስት 2014ኢትዮጵያ 

በኢትዮጵያ ያለው ሚስጥር አነፍናፊው ገዥ አካል በጉአዳ ውስጥ የተደበቁ የኢትዮጵያውያንን/ትን ሚስጥሮች መርምሮ ለማውጣት በጣም ውድ የሆኑ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን በመጠቀም የስለላ ፕሮግራሞችን በመተግበር በታላቅ ፍርሀት ውስጥ ተዘፍቆ በመንፈራገጥ ላይ ይገኛል፡፡ ከፍርሀታቸው የተነሳ ህዝቡ በእነርሱ ላይ ምን ለማድረግ እንደሚችል ስጋት ውስጥ በመውደቅ እራሳቸውን በማስጨነቅ እንቅልፍ አጥተው ሲባንኑ ያድራሉ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግፍ ከበዛበት ወህኒ የአክብሮት ስላምታየ ይድረሳችሁ! እነሆ ለሁለተኛ ጊዜ ለአፍታ ያህል እድሉን አግኝቸ ወህኒ የመውረዴን እውነታ ላስረዳችሁ ግድ አለኝ ። ዛሬ አስረግጨ የምነግራችሁ ወህኒ የመውረዴ ምክንያት ሚስጥር ግምሽ እድሜየን ህግና ስርአቷን አክበሬ የኖርኩባትን የሳውዲት አረቢያን ህግ ተላልፊ አይደለም ! የስደተኛው ጉዳይ ያገባኛል በሚል የማቀርበው መረጃ ቅበላየ የማይመቻቸው ፣ ያመማቸው ከተሰረሰውና እየተሰራ ካለው ከእገታው ጀርባ ስለመኖራቸው […]


ለነሱ (ለማ/ቅዱሳን) የተሰጠው ስም ለእኔም ይገባኛል

(ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ፤ የፓርላማ አባል)
ክቡር ሆይ
አኔ የአንድ እምነት አንድ ሀገር አራማጅ ነኝ መንግ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ዘመቻ ጀመረ በሚል እሰጥ አገባ እንደበዛ አውቃለሁ፡፡ በሌለኝ መረጃ የእኔን ስም እየጠቀሱ ሰዎች ፖስት እንደሚያደርጉ ከሰዎች ብሰማም የእኔ ፌስ ቡክ ይህን አልገለፀልኝም፡፡ ለማኛውም መንግሥት በእምነት ላይ ዘመቻ ሲጀምር በኦርቶዶክስ ላይ በማኅበረ ቅዱሳን መስመር እንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒሰትር አቶ መለስ ይህን አሰመልክተው ለሰጡት አሰተያየት የሰጠሁትን ምላሽ በድጋሚ ላጋራችሁ፡፡ ይህ ነው የእኔ አቋም፡፡ ይህ ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ከገጠመ እሰየው ነው፡፡ ለነሱ የተሰጠው ስም ለእኔም ይገባኛል፡፡ የሰጠሁት ምላሽ እንደወረደ ይህን ይመስል ነበር፡፡


ብዙ ጉዳዮች እንደተርጓሚው እንደሚሆን መገመት ይቻላል ነገር ግን አንድ እምነት አንድ ሀገር ማለት ግን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እንተረጎሙት ሳይሆን፤ አንድ ሰው ሊኖረው የሚገባው አንድ ምነት ብቻ ነው (ሰኞ፤ ዕሮብና አርብ ሙስሊም ማክሰኞ፤ ሀሙስና ቅዳ ክርስቲያን፤ ወዘተ መሆን አይቻልም) ይህ ደግሞ አምላካዊ ቃል ነው(እኔ ቀናተኛ አምላክ ነኝ ሲል) ይህ አምላካዊ ቃል ደግም የሚሰራው ለሚያምኑበት ነው፡፡ ቃልቻ ቤት እየሄዳችሁ ቤተ ክርስቲያን አትምጡ ማለት ነው፡፡ ሊኖረን የሚገባው አንድ እምነት ነው፡፡ በእርግጠኝነት ሙስሊም ሆኖም ክርስቲያን መሆን አይቻልም ለዚህ ይህ ለአንድ እምነት የመገዛት ፍልስፍና የሁ የእምነት ዘርፎች መለያ ነው፡፡ ጥንቆላ ብቻ ነው ይህንን የሚፈቅደው ይህ ደግም በሁሉም እምነቶች የተወገዘ የመጥፎ መንፈስ ነው፡፡ ለዚህ እኔ ያለኝ አንድ እምነት ብቻ ነው፡፡ መፍክሬም ነው፡፡

ከአንድ እምነት ጋር ተያይዛ የመጣችው የአንድ ሀገር ጉዳይ ነው፡፡ ይህ በእርግጥ አከራካሪ ነው፡፡ አንድ አንድ ሀገሮች ጥምር ዜግነትን የሚፈቅዱ አሉ ይህም ሆኖ እኔ በግሌ ኢትዮጵያ ከምትባል ሀገር በሰተቀር ሌላ ሀገር የለኝምእንዲኖረኝም አልፈልግም ይህን አቋሜን ገልፅ ግን እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ስል ሌሎች ኢትዮጵያዊ አይደላችሁም አለ ተብሎ ልከሰስ አይገባም፡፡ አንድ የእስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊ ሊሆን እንደሚችል ብዥታ ኖሮብኝ አያውቅም ወይም የሌላ ክርስትና እምነት ተከታዮች ኢትዮጵያዊ ንደሆኑ አልጠራጠርም፡፡ አማኒያንም ቢሆኑ፡፡
አንድ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አለችኝ ብዬ ነው ለዚህች ሀገር እድገት (ሁሉ አቀፍ እድገት ማለቴ ነው) የሚከፈል መሰዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆኑኩት፡፡ ሌላ አማራጭ የለኝምአማራጭ ያለው ግን ካልተመቸው ወደዛኛ ሊሄድ ይችላል፡፡ ሁለት ጉርጓድ ያላት አይጥ እንደሚባለው፡፡ እኔ ግን ሀገሬ አንድ እና አንድ ነች፡፡ ኢትዮጵያ፡፡ ይህ ማለት ግን በምንም መመዘኛ ይህች ሀገር የኔ ብቻ ነች ማለት አይቻልም፡፡ አይሆንምም፡፡ እኔ የአንድ እምነት እና አንድ ሀገር ባለቤት ነኝ፡፡

ምንጭ፦ የፌስቡክ ገጻቸው።

 

Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መጋቢት 28 የሚደረገዉን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ፣ የአንድነት አባላቶችንና ደጋፊዎች በአራት የከተማዋ አቅጣጫዎች በመሰማራት በራሪ ወረቀቶችን ለሕዝብ ሲያደርሱ እንደነበረ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። በአዲስ አበባ መንገዶች ሲሰራጩ ከነበሩ በራሪ ወረቀቶች መካከል ፡

መጋቢት 20/ 2006 ዓ.ም የወላይታ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሶዶ ውስጥ ስብሰባ ለማድረግ ዝግጅት እያደረጉ በነበረበት ወቅት ፖሊስ ምንም አይነት ምክንያት ሳይሰጥ ሰብስቦ እንዳሰራቸው ከአካባቢው የፓርቲው ተወካዮች ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት አመራሮቹ ድል በትግል በተባለው የፖሊስ ጣቢያ ታስረው ይገኛሉ፡፡ በአሁኑ ወቅትም እስር ላይ ከሚገኙት መካከልም፡- 1. ወጨፎ ሳዳሞ የወላይታ ዞን ምክትል ሰብሳቢ 2. ታደመ ፍቃዱ […]

«በሀዋሳ ከተማ ታቦር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚማሩ የሲዳማ ተወላጆች የሚኒ ሚዲያ ፕሮግራም በሲዳመኛ ቋንቋ ይተላለፍ፣ ታቦር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚለውም ታፔላ በሲዳመኛ ቋንቋ ይጻፍ በሚል መነሻና ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ረብሻ ተፈጥሮ፣ የፌደራል ፖሊሶች ወደ ግቢው ሲጠጉ ተማሪዎቹ ድንጋይ በመወርወር በርካታ ፖሊሶች ቆስለዋል፡፡ ፖሊሶቹ በወሰዱት ርምጃ ብዙዎች ለጉዳት ተዳርገዋል» ሲል ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ከአዲስ አበባ […]

ጉባኤዉ ገና ሳይጀመር በፊት የአዉሮጳ ሕብረት የአፍሪቃ ሕብረት አባል ያልሆኑትን የአፍሪቃ መሪዎች ጋብዞ አባል ከሆኑት አንዳንዶቹን አለመጋበዙን የተቃወሙ የአፍሪቃ መሪዎች በጉባኤዉ አልተሳተፉም

ኢንተርኔት ፤ በአሁኑ ዘመን ችላ የማይባል የዕለታዊ ህይወት አንድ አካል ነው ከተባለ፣ አባባሉ ሢሦውን የዓለም ሕዝብ ብቻ ነው የሚመለከተው። አብዛኛው የዓለም ሕዝብ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባቀረበው መረጃ መሠረት የኢንተርኔት ተጠቃሚ

የሰሃራን ምድረ በዳ አቋርጠው በጀልባ አውሮፓ ለመግባት የሚጥሩ አያሌ ወጣቶችና ጎልማሶች በየጊዜው ስለሚያጋጥሟቸው አያሌ ሕልውና ተፈታታኝ ተግዳሮቶች ያልተነገረበት ጊዜ የለም። ቀደም ባሉት ጊዜያት ከሰሜን ምዕራብ አፍሪቃ በጀልባዎች ወደ ካናሪ ደሴቶች

ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ቃል አሸባሪዎች እንዳልሆኑ፤ እስር ቤት ዉስጥ እንደተደበደቡ፤ እንደተሰቃዩና ያልተናገሩትንና ያላሉትን እንዳሉ ተደርጎ እንዲፈርሙ መርማሪዎች እንዳስፈራሯቸው ገልፀዋል

‪#‎udj‬@addisabeba የአዲስ አበባ የሰላማዊ ሰልፍና የፖለቲካ ስብሰባዎች ማሳወቂያ ክፍል ኦፊሰር የሆኑት አቶ ማርቆስ ብዙነህ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ላቀረበላቸው የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ደብዳቤ ህገ ወጥ ምላሽ በመስጠታቸው ፓርቲው ደብዳቤውን የተቃወመበትን የህግ አግባብ በመጥቀስ ደብዳቤ ልኮላቸው ነበር፡፡ አቶ ማርቆስ በጽ/ቤታቸው በአካል የተላከላቸውን ደብዳቤ ምስክሮች ባሉበት ‹‹አልቀበልም ብትፈልጉ ክሰሱኝ››በማለት በህጋዊ መንገድ የቀረበላቸውን ደብዳቤ አልቀበልም በማለት መልሰዋል፡፡አንድነት ፓርቲ […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ስራ አስፈጻሚ በዛሬው ዕለት በፓርቲው ዋና ጽ/ቤት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ‹‹በህገ ወጥ መንገድ የሚቀለበስ ሰላማዊ የትግል ስልት ባለመኖሩ የአዲስ አበባ ህዝብ ለቀረበለት የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ምላሹን እንዲሰጥ በአክብሮት እንጠይቃለን››ብሏል፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ህገ ወጥ ደብዳቤ በመጻፍ ሰልፉን ማከናወን አትችሉም ማለቱ ከህግ በላይ ነኝ የሚል መንፈስ እንዳለው እንደሚያሳይ የገለጸው […]

የኢትዮጵያ ሬዲየና ቴሌቪዥን ድርጅት ከኅዳር 16 እስከ 18 ቀን 2004 ዓ.ም. በተከታታይ ሦስት ክፍሎች ‹‹አኬልዳማ›› በሚል ባቀረበው ዘጋቢ ፕሮግራም፣ክብርና ዝናን የሚያጠፋ በድምፅ፣ በምስልና በጽሑፍ በተቀነባበረ መንገድ ስሙን እንዳጠፋው በመግለጽ፣ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በመሠረተበት የፍትሐ ብሔር ክስ ተረታ፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ዘጠነኛ የፍትሐ ብሔር ችሎት መጋቢት 23 ቀን 2006 ዓ.ም. […]

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

ማሕበረወያኔ

በኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሚመራው መንግስት ከናቅፋ እስከ ጉና ተራራ ያሉ ምሽጎቻቸውን ከሰማይ በጦር አይሮፕላን፣ ከምድር እሳት በሚያዘንቡ ቢ.ኤሞችና መድፎች ሳያቋርጥ ቢደበድብም፤ በሀገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢ ከቀን ወደ ቀን ግዛታቸውን እያሰፉ የተጠናከሩት ‹‹ወንበዴዎች›› ራስ ምታት ሆነውበታል። የኤርትራ ‹‹ነጻ አውጪ›› ቤዝ-አምባው በተወሰነ መልኩም ቢሆን ለጥቃት የመጋለጥ እድሉ አናሳ በሆነው የሳህል በረሃ በመሆኑ አብዛኛው የአመራር አባል መሸሸጊያው አድርጎታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንድነት በቅርቡ ይፋ ባደረገው የሚሊዮን ድምጽ ንቅናቄ አሥራ አራት የተመረጡ ቢሆንም፣ ከአሥራ አራቱ ከተሞች ዉጭ ያሉ ሌሎች ከተሞችና ወረዳዎች ም «ለምን እኛ ጋር አልተደረገም ?» የሚሉ ጥያቄዎች እያነሱ እንደሆነ ይነገራል። ከነዚህ ቦታዎች አንዱ ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ የምትገኛው የደራሼ ልዩ ወረዳ፣ የምትገኘው የጊዶሌ ከተማ ናት። በወረዳው ያሉ ነዋሪዎች ፣ «የትግሉ መሪ እኛ ነን ። እባካችሁ በአደባባይ […]

እንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/ የፊታችን እሁድ መጋቢት28 ቀን 2006 ዓ.ም፣ በታላቋ የደሴ ከተማ፣ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርግ ለማረጋገጥ ችለናል። አስፈላጊው ባለስልጣናትን የማሳወቅ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ አንድነት በደሴ እና በአካባቢዋ ያሉ ነዋሪዎች በሙሉ፣ በነቂስ እንዲወጡና ሰላማዊ ሰልፉ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል። በከተማዋም ቅስቀሳ፣ በጥቂት ቀናቶች ዉስጥ ይጀመራል ተብሎ ይገመታል። ከስድስት ወራት በፊት፣ የሚሊዮኖች ድምጽ […]

«አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት፣ ዛሬ ባካሄደው ልዩ አስቸኳይ ስብሰባ መጋቢት 28 ቀን 2006 ዓ.ም ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል መሪ ቃል የተጠራው ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ማወቅ ለሚገባው አካል ሁሉ የማሳወቅ ስራው የተጠናቀቀ በመሆኑ፣ የአደባባይ ቅስቀሳ ስራው ከነገ ማለትም መጋቢት 24 ቀን 2006 ዓ.ም፣ ጀምሮ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል እና ሰልፉ በተያዘለት ቀን እንዲደረግ ምክር […]

መጋቢት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ጄኔራል አቶ ጌታቸው አረዳ እንደተናገሩት ” የኤርትራ መንግስት ሃሳቡን ቀይሮ ወደ ሰላም ቢመጣ የኢትዮጵያ መንግስት ችግር የለበትም። የኤርትራ ተቃዋሚዎች ከጉያችን ስላሉ ምን እንሆናለን የሚል ስጋት የለብንም” በማለት ተናግረዋል።

የታጠቁ የኤርትራ ሃይሎች እርምጃ የማይወስዱት በድንበር አካባቢ የኤርትራ ሰራዊት በብዛት ስላለ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ዳይሬክተሩ፣ የኤርትራ መንግስት ከእኛ ጋር ለመስማማት ከፈለገ ምንም ቂምና ቁርሾ የምንይዝበት ነገር አይኖርም ሲሉ አክለዋል።

ኢትዮጵያ 20 ሺ ኤርትራውያን ስደተኞችን ታስተምራለች የተባለውም የተጋነነና ቁጥሩ ከ1800 እንደማይበልጥ የተናገሩት አቶ ጌታቸው፣ እነዚህ ተማሪዎች የጸጥታ ስጋት እንደማይሆኑና አስፈላጊው ምርመራ ተካሂዶባቸው ትምህርት እንደጀመሩ ገልጸዋል።

ከኤርትራ ስደተኞች ይልቅ የጸጥታ ስጋት የሚፈጥረው የኢትዮጵያ ተስፋ የቆረጠው ወጣት ነው ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ይህን ወጣት መከታተል የጸጥታ ችግሮችን እንደሚቀርፍ ገልጸዋል።

በንግግራቸው መሃል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ባይከብርም የመክፈር ፍላጎት እንዲኖረው በማድረጋችን ጸጥአየትኩረት አቅጣጫውን ለማስቀየር ችለናል ብለዋል።

የጅቡቲ ወደብን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ደግሞ፣ ለጅቡቲ ወደብ የምንከፍለውን ኪራይ የጅቡቲ መሪዎች ቤተሰቦች የሚቀራመቱት በመሆኑ አገሪቱ ወደብ ትከለክለናለች ብለን አንሰጋም ሲሉ መልሰዋል።

በመብራት መቆራረጥ የሚሰቃየው የኢትዮጵያ ህዝብ “እፎይ” የሚልበትን ቀን ሁሉም ይናፍቃል። የአባይ ወንዝ ከተገደበ በኋላ የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ከኢትዮጵያ አልፎ ለሱዳን እና ለግብጽ እንደሚበቃም ይነገራል። ከዚህ ግድብ በተጨማሪ የግልገል ጊቤ 2 እና 3 ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የሚኖራት የመብራት ሃይል በአስር እጥፍ እንደሚጨምር የዘርፉ ሙያተኞች ይመሰክራሉ። በዚህ አጋጣሚም በመብራት መቆራረጥ እና እጦት የሚሰቃየውም ህዝብ የሚካስበት አጋጣሚ ይፈጠራል። […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ኢቲቪ ተመጣጣኝ የማስተባበያ አየር ሰዓት ለአንድነት ፓርቲ እንዲሰጥ ታዟል የዘገየ ፍትህ እንደተሰጠ ባይቀጠርም በአንድነት ፓርቲ እና በኢትጵያ ቴሌቪዥን መካከል “አኬልዳማ ዘጋቢ ፊልምን አስመልክቶ ለነበረው 3 አመታትን ለፈጀ ክርክር ለአንድነት ፓርቲ ፈርዶ መቋጫ ሰጥቶታል በመሆኑም ኢ.ቲ.ቪ የአንድነት ፓርቲን ስም በማጥፋቱ ተመጣጣኝ የማስተባቤ አየር ሰዓት ለአንድነት እንዲሰጥ ፍርድቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ችሎቱን የተከታተለው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ […]

ችሎቱ በተከሳሽ በእነ አቶ አቡበከር አህመድ መዝገብ በአሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች ቃልም ማድመጥ ጀምሯል ። ዛሬ የአንዱን ተከሳሽ ቃል ያደመጠው ችሎቱ የተቀሩትን 18 ተከሳሾች የተከሳሽነት ቃል ለማዳመጥ ለነገ ቀጠሮ ሰጥቷል ።

በጎርጎሮሳውያኑ 2013 ጀርመን ተገን እንድትሰጣቸው የጠየቁ ስደተኞች ቁጥር በኢንዱስትሪ በበለፀጉ ሌሎች ሃገራት ካመለከቱት ቁጥር ጋር ሲነፃጸር ከፍተኛ ነው ። ሆኖም አብዛኛዎቹ ጀርመን እንድትቀበላቸው የጠየቁ አመልካቾች የመኖሪያ ፈቃድ የማግኘት እድላቸው አነስተኛ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ ።

በኬንያ መዲና፣ ናይሮቢ በተጣሉ ሦስት የቦምብ ጥቃቶች ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን እና 25 መቁሰላቸውን የኬንያ ሀገር አስተዳደር ባለሥልጣናት አስታወቁ። ትናንት ማታ የተጣሉት ጥቃቶች ዒላማ ያደረጉት በብዛት

አቶ አስራት ዛሬ በጠበቃቸው በኩል ለልዩ ችሎቱ ባቀረቡት ይግባኝ በአንድ የግል መፅሄት ላይ ፍርድ ቤቱን በመድፈርና በመተቸት ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የተጣለባቸው የ2 ዓመት ገደብ እንዲነሳላቸው ጠይቀው ነበር ።

የአፍሪቃ መሪዎች ስምምነቱን ላለመቀበል የሚያቅማሙበት ብዙ ምክንያት አላቸዉ።ቀድሞ የሚጠቀሰዉ ግን ማርቲን እንደሚሉት አዉሮፖች ለአፍሪቃ ምርቶች ቀረጥ ሳይጠይቁ ገበያቸዉን ክፍት ካደረጉ፤ አፍሪቃዎችም በምላሹ ለአዉሮጳ ሸቀጦች ቀረጥ ሳያስከፍሉ ገበያቸዉን ክፍት እንዲያደርጉ መጠየቃቸዉ ነዉ።

አዋጁን-።«ለማስከበር እና ቦኩ ሐራምን ለማጥፋት» ተብሎ የዘመተዉ ጦር ሕዝቡን መዉጪያ መግቢያ አሳጣዉ።የጠረጠረዉን በመደዳ-ያስር፤ያሰረዉን ይገርፍ፤ ያሰቃይ፤ እስራት-ስቃዩን ለማምለጥ የሞከረዉን እያሳደደ-ይገድለዉ ያዘ።አምንስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለዉ ይሕ የሁለቱ ሐይላት እርምጃ ከጦር ወንጀል የሚቆጠር ነዉ።

ሰውዬው ዛፍ ሥር ቁጭ ብሎ ያዳምጣል፡፡ ወፏን፡፡ የሚመስለው ግን የተመሰጠ በገና ደርዳሪን፣ የተሸለመ መሰንቆ መቺን፣ ከብቶቹ ለምለም ሣር ያገኙለት ባለ ዋሽት እረኛን እንደሚያዳምጥ ነው፡፡ ዐሥር ጊዜ አንገቱን ይነቀንቃል፡፡ የወፏ ዝማሬ ገብቶታል መሰል፡፡ በግጥሙ ቤት፣ በስንኙ አወቃቀር፣ በሐረጉም ቅኔ እንደረካ ሰው ነው ሁኔታው፡፡ ሰምና ወርቁን እንዳገኘ ቅኔ ሰሚ አንገቱን ግራ ቀኝ ይወዘውዛል፡፡ ደግሞ አንዳንድ ጊዜ ወፏ ራሷ ደንግጣ ልትበርር እስክትደርስ ድረስ ለወፏ ዝማሬ የፊልም ቤት ጭብጨባ ያጨበጭባል፡፡

ይኼ ሁሉ ሲሆን አሻግሮ ሌላ ሰው ያየዋል፡፡ ያውም የሰውየውን ጤንነት እየተጠራጠረ፡፡ መጀመሪያ የሆነ ሌላ ነገር እያዳመጠ መስሎት ነበር፡፡ ጠጋ ሲል ምንም ሌላ ነገር አጣ፡፡ የሚያነብም መስሎት ነበር፡፡እጁ ግን ባዶ ነው፡፡ በአካባቢውም አንገቱን አዟዙሮ የሚያወጋው አንዳች ነገር ካለ ብሎ ፈለገ፡፡ ሰውዬው ብቻውን ነው፡፡ የሚገርመው ግን ወፍ አዳማጩ ሰው መንገደኛውን አላየውም፡፡ እርሱ ተመስጦ ላይ ነው፡፡ አንዳች ነገር ልቡን ነክቶት እንገቱን ከላይ ወደ ታች እየነቀነቀ ነው፡፡

መንገደኛው ሰው ጠጋ አለው፡፡ ወፍ አዳማጩ ሰው ቀና አለ፡፡ በእጁ እንዲቀመጥ ጋበዘው፡፡ መንገደኛው እየተገረመ ተቀመጠ፡፡

‹‹አንዳች ነገር መጠየቅ እችላለሁ›› አለ መንገደኛው ሰው፡፡

‹‹ድምጽህን ቀንሰህ እንጂ አዎ›› አለው የሹክሹክታ ያህል››

‹‹እ-ሺ – ምንድን ነው የምታዳምጠው›› አለው በጆሮው የመናገር ያህል ቀስ ብሎ፡፡

‹‹ወፏን››

መንገደኛው በኤሌክትሪክ ወንበር ላይ ያስቀመጡት ያህል ተስፈንጥሮ ተነሣ፡፡ ከሆነ አንድ ጠንቋይ ጋር የተቀመጠ መሰለው፡፡ ወፍ ከሚሰማ ጠንቋይ፡፡ ደግሞስ ወፏ ምን እያለች እንደሆነ ማን ያውቃል፡፡ የምትናገረው ስለ እርሱ ቢሆንስ፡፡ ወፍ አዳማጩ ሰው ግን ግራ እጁን ይዞ ጎተተና እንደገና አስቀመጠው፡፡

‹‹ለምን ደነገጥክ?›› አለው ቀስ ብሎ፡፡

‹‹አይ ታስፈራለህ፡፡ ልሄድ ነው በቃ›› አለ እጁን ለማስለቀቅ እየሞከረ

‹‹ይልቅ ሞኝ አትሁን፤ ተቀመጥና ወፏን አዳምጥ፡፡ ስንት ነገር ታገኛለህ መሰለህ›› አለው፡፡

መንገደኛው ድንጋጤውና ፍርሃቱ ጨመረበት፡፡ ‹‹አልችልም፤ እኔ ወፍ ማዳመጥ አልችልም›› አለው መንገደኛው፡፡

ወፍ አዳማጩ ሰው በቀሰስታ ‹‹እኔ አሳይሃለሁ መንገዱን›› አለው፡፡ መንገደኛው አሁን ጭራሽ ባሰበት፡፡ እርሱንም ጠንቋይ ሊያደርገው ያሰበ መሰለው፡፡ ዘወር ዘወርወር ብሎ አካባቢውን ማተረ፡፡ በሩቁ በሚታየው የማቋረጫ መንገድ በኩል እንደርሱ ያሉ መንገደኞች ሲጓዙ ይታዩታል፡፡ እርሱም እንዳች ማረፊያ ጥላ ፍለጋ ነበር ወደዚህ አሳብሮ የመጣው፡፡ የገጠመው ግን ወፍ የሚያዳምጥ ሰው ነው፡፡ በርግጥ ይህ ዛፍ በመንገድ ለሚደክሙ መንገደኞች አሳብረው የሚያርፉበት ነበር፡፡ እርሱም ብዙ ጊዜ እዚያ ዐርፎ ያውቃል፡፡ እዚያ ሲያርፍም የወፎችን ዝማሬ በአልፎ ሂያጅ ልቡ ሰምቶ ያውቃል፡፡ በአካባቢው ትልቁ ዛፍ ያ ስለሆነ ወፎቹ ይመርጡታል፡፡ ያ ዝማሬያቸው ግን የዚህን ሰውዬ ያህል መስጦትም፣ አስደስቶትም አያውቅም፡፡

‹‹አሁን እንዴው የምርህን ወፍ እያዳመጥክ ነው›› አለው መንገደኛው፡፡

‹‹አንተ ግን ምንም አይሰማህም›› ብሎ መለሰለት አዳማጩ፡፡

‹‹በቃ ያው የወፍ ዜማ፤ በቃ፡፡ የወፍ ዜማ ብርቅ ነው እንዴ››

‹‹ወፏ የምትለውንስ ትሰማለህ››

‹‹ልጅ ሆነን የወፍ ቋንቋ እያልን እንጫወት ነበር፡፡ ያ ግን የወፍ ቋንቋ አይመስለኝም፡፡ ሰውም የወፍ ቋንቋ የሚያውቅ አይመስለኝም››

‹‹የወፍን ቋንቋኮ ማንም ሰው መስማት ይችላል››

‹‹እኔ ለምሳሌ አልችልም›› ጆሮውን በእጆቹ ዳሰሰ፡፡

‹‹ትችላለህ››

‹‹አንተ እኔን ታውቀኛለህ›› በጥንቆላው እንዳያውቀው በመፍራቱ ‹አላውቅህም› እንዲለው ፈለገ፡፡

‹‹ሰው አይደለህም እንዴ››

‹‹ብሆንስ››

‹‹ከሆንክማ ትችላለህ ማለት ነው፡፡ ሰው ሁለት ዓይነት ጆሮ አለው፡፡ የሥጋ ጆሮና የልቡና ጆሮ ወይም እዝነ ሥጋ እና እዝነ ልቡና፡፡ በሥጋ ጆሮው ማዳመጥ የሚችለው የሰው ቋንቋ፣ መስማት የሚችለውም አልፎ ሂያጅ ድምጽ ነው፡፡ በልቡና ጆሮው ግን ወፍንም፣ እንስሳንም፣ ወንዝንም፣ መብረቅንም፣ ተራራንም፣ ዛፍንም መስማት ይችላል›› አለው፡፡ ከበደ ሚካኤል ይህንን ችሎታቸውን ተጠቅመው ነው ደመናና ጽጌረዳ ሲያወሩ የሰሙትን የነገሩን፡፡ ‹ጽጌረዳና ደመና› የሚለውን ግጥማቸውን ታውቀዋለህ?

‹‹እሺ አንተ ከወፏ ምን ሰማህ?›› አለው መንገደኛው፡፡

‹‹ምን የመሰለ ቅኔ፣ ምን የመሰለ ዕውቀት፣ ምን የመሰለ የሕይወት ትርጓሜ››

‹‹እስኪ አንዱን ንገረኝ››

‹‹ወፏ ምን አለች መሰለህ፡፡ ትዘምር የነበረው ስለ ዛፉ ነው፡፡ ዛፍ ሆይ አትመካ፣ እኔን አስጠለልኳት፣ አሳረፍኳት ብለህ አትመካ፡፡ በቅርንጫፍህ አትመካ፡፡ ለእኔ ዋናው ያንተ ቅርንጫፍ አይደለም፡፡ለእኔ ዋናው የራሴ ክንፍ ነው፡፡ ቅርንጫፍህ ሊቀር ይችላል፡፡ አንተም አላስጠልልም ልትል ትችላለህ፡፡ ያ ያንተ መብት ነው፡፡ እኔ ግን የምመካውም የምተማመነውም በገዛ ክንፎቼ ነው፡፡ ክንፎቼ ካሉልኝ የትም እሄዳለሁ፡፡ ሌላ ዛፍ ላይ ዐርፋለሁ፡፡ ሌላ ቤት ላይ እወጣለሁ፡፡ በተራሮች ላይ እቆማለሁ፡፡ በመስኩ ላይ እራመዳለሁ፡፡ ስለዚህ ልሰበር ነው፤ ልወድቅ ነው፤ ልጥልሽ ነው፤ ልወዛወዝ ነው እያልክ አታስፈራራኝ፡፡ ወፍ የተባልኩት ከእኔ ጋር ባሉት ክንፎቼ እንጂ አንተ ጋር ባሉት ቅርንጫፎችህ አይደለም፡፡ ወፍ የሆንኩት እኔ ጋር ባሉት ላባዎቼ እንጂ አንተ ጋር ባሉት ቅጠሎች አይደለም፡፡ ወፍ የተባልኩት በቆምኩበት እግሬ እንጂ በቆምኩበት ግንድ አይደለም፡፡ እኔ ባለኝ እንጂ በምትሰጠኝ አልተማመንም፤ እኔ በያዝኩት እንጂ በተለገስኩት አልመካም፡፡ – ይህንን ነበር የምትዘምረው››

መንገደኛው ተገረመ፡፡ የወፍ አድማጩን ችሎታም አደነቀ፡፡ አብልጦ ደግሞ የወፏን ዝማሬ አደነቀ፡፡ ወፍኛ ቢችል ኖሮ መወድስ ያደርሳት ነበር፡፡

‹‹ቆይ አንተ ይህንን የወፍ ቋንቋ ከየት ተማርከው›› መንገደኛው ጠየቀ፡፡ ቅድም እንዳልፈራ ሁሉ አሁን ለማወቅ ጓጓ፡፡ የማያውቁት ነገር ምንጊዜም ያስፈራል፡፡ መቃብር ለመቃብር ቆፋና ለቀባሪ እኩል አያስፈራም፡፡

‹‹ይህ ነገር የምትማረው አይደለም፡፡ ሰው በመሆንህ የምታገኘው ነው፡፡ ግን ማሳደግ ይፈልጋል፡፡ እዝነ ልቡናህን መጠቀም ይፈልጋል፡፡ ለሕይወት ትርጉም መስጠትን ይፈልጋል፡፡ ዝም ብሎ የተፈጠረ፣ ዝም ብሎም የሚኖር፣ ዝም ብሎ ነገር የለምና፤ ዝም ብለህ የምታልፈው ዝም ብሎ ነገር ሊኖር አይገባም፡፡ ኑሮ ከንቱ አይደለችም፤ ሕይወት ቂላቂል አይደለችም፡፤ ሕይወት ቅኔ ናት፡፡ እየፈታህ የምትማርባትም የምትደመምባትም፡፡ ፍጡራን ሁሉ ልዩ ልዩ ዓይነት ቅኔዎች ናቸው፡፡ ማዳመጥ፣ ማየት፣ መንካት፣ መመርመር፣ መተንተን የሚፈልጉ ቅኔዎች፡፡ አየህ በሥጋ ጆሯችን ብዙ ቸበርቻቻዎች ስንሰማ ስለምንኖር የሕይወትን ዝማሬ የመስማት ዕድላችን ጠብቧል፡፡ አንት ግን እይ፣ ስማ፤ አካባቢውን፣ የዐየሩን ሁኔታ፣ ድምጹን፣ የፍጥረትን እንቅስቃሴ፣ የፍጥረትን የርስበርስ ተግባቦት አድንቅ፤ አድንቅና ፍታው፡፡ ድምጽ ዝማሬ፣ ትርዒትና መልእክት የሌለው ፍጡር የለም፡፡ ዝማሬያቸው ግን የሚሰማው፣ ትርዒታቸው ግን የሚታየው፣ መልእክታቸው ግን የሚረዳው ለሰው ነው፡፡ሰው ነው የሚፈታላቸው፡፡ ፍቺው ግን እንደየዕውቀታችን፣ እንደየኑሯችን፣ እንደየ ዐቅማችን፣ እንደየመረዳታችን፣ እንደየ ባሕላችን ሊለያይ ይችላል፤ የወፏን ዝማሬ እንተ ብትሰማው ሌላ ይሆናል የምትረዳው፡፡ ወፏ እንደዚያ አላለችም፡፡ እኔ ነኝ እንደዚያ የተረዳኋት፡፡ መድኃኒት እንደየበሽታው ነው፡፡

‹‹ያሬድ ያያትን፣ ሰባት ጊዜ እየወደቀች የተነሣችውን ትል አንተ ብታያት ኖሮ ሌላ ነገር ልትረዳ ትችል ይሆናል፡፡ ያሬድ ግን ወድቆ መነሣትን፣ ታግሎ ማሸነፍን፣ ተስፋ አለመቁረጥን፣ አለመታከትን ከእርሷ ተማረ፡፡እርሷ ተጓዘች፡፡ እርሱም ጉዞዋን ተረጎመላት፡፡ ስለ ጳልቃን ጣልቃን፣ ስለ ከራድዮን፣ ስለ ዝሆን (ውርዝው ነጌና ዐቢይ ነጌ)፣ ስለ አንበሳ፣ ስለ ቀበሮ፣ ስለ ቁራ፣ ስለ ርግብ፣ ስለ ጉንዳን የምንሰማቸው ታሪኮች ሁሉ የእነርሱን አነዋወር ተመልክቶና አዳምጦ ለሕይወት የሚበጅ ትርጉም ከመስጠት የመጣ ነው፡፡

‹‹እይ፣ ዝም ብለህ ግን አትይ፤ ስማ፣ ዝም ብለህ ግን አትስማ፡፡ ዓለም መጽሐፍ ናት፡፡ ሚሊዮን ገጾች ያሏት፡፡ ገጹ እያንዳንዱ ገጠመኝህ ነው፡፡ ብልሆች እያንዳንዱን ገጽ ያነቡታል፡፡ ይማሩበታልም፡፡ ሞኞች ግን ገጹን እያጠፉ ብቻ ያልፉታል›› ይሄው ነው ወዳጄ፡፡

አሁን መንገደኛው ራሱ የወፏን ዝማሬ መስማት ጀመረ፡፡ አንገቱንም መነቅነቅ ቀጠለ፡፡ እርሱ የሰማውን ደግሞ ሌላ ደራሲ ይነግረን ይሆናል፡፡

ፍራንክፈርት፣ ጀርመን