የአፍሪቃ እና የአዉሮጳ መሪዎች ጉባኤ

የአፍሪቃ መሪዎች ስምምነቱን ላለመቀበል የሚያቅማሙበት ብዙ ምክንያት አላቸዉ።ቀድሞ የሚጠቀሰዉ ግን ማርቲን እንደሚሉት አዉሮፖች ለአፍሪቃ ምርቶች ቀረጥ ሳይጠይቁ ገበያቸዉን ክፍት ካደረጉ፤ አፍሪቃዎችም በምላሹ ለአዉሮጳ ሸቀጦች ቀረጥ ሳያስከፍሉ ገበያቸዉን ክፍት እንዲያደርጉ መጠየቃቸዉ ነዉ።