ቁጥጥር ከሚደረግባቸው ሕገ ወጥ ተግባራት መካከል÷ ያልተፈቀደላቸው ሰባክያን ስምሪትና የኅትመት ውጤቶቻቸው፣ የአስመሳይ ባሕታውያንና መነኰሳት ነውረኛ ድርጊቶች፣ ሕገ ወጥ ልመና፣ የአጥቢያ አስተዳደር ሙስናና የወጣት ሱሰኝነት ይገኙበታል፡፡ ማዕተብ ያለው ኦርቶዶክሳዊ ምእመን በተለይም ወጣቱ ከሱስ ነጻ መኾን አለበት፤ መስቀሉን አንጠልጥሎ በየባንኮኒውና በየዳንኪራው ከመታየት መጠበቅ አለበት፤ ዶግማውን፣ ቀኖናውንና ትውፊቱን ያወቀና የጠነቀቀ፣ በኢኮኖሚያዊና ፋይናንሳዊ አቅሙም ጠንካራና እርስ በርሱ መደጋገፍ ይገባዋል፡፡ …

ታላቁ የዘመናችን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አርበኛ የሆኑት ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ በተለያዩ የቤተክርስቲያናችን አንገብጋቢና አሳሳቢ ጉዳዩች ላይ ጥልቀት ያላቸው፣ በጥንቃቄ የተመረመሩና በመረጃ የተደገፉ የተለያዩ ሐይማኖታዊና ሀገራዊ ጽሁፎችን ለአንባቢያን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። በዚህም መሠረት በቅርቡ ከስልጣነ ክህነታቸው የተገፈፉትና የተወገዙት አቶ ታደሰ ሲሳይን አስመልክቶ …

አባ ፋኑኤል አዲስ ተክል ናቸው Read more »


(ደጀ ሰላም፣ መጋቢት 22/2006 ዓ.ም፤ ማርች 31/2014. PDF)፦ የአስቆሮቱ ይሁዳ ጌታችንን አሳልፎ ሰጠው። ምህሩንና ጌታውን ክዶ፣ ስሞ ለግርፋት እና ለመስቀል ሞት ተስማማ። ይህንን የጌታን ሕማማት፣ ስቅላት፣ ሞትና ትንሣኤ በምናስብበት በአሁኑ ወቅት ማኅበረ ቅዱሳንን ለሕማም፣ ለስቅላት እና ለሞት አሳልፎ ለመስጠት የሚደረገው ትርምስ ተጀምሯል። ይሁዳ ለ30 ዶላር እነዚህ የዘመናችን ሰቃልያን ደግሞ “ማኅበሩ ያፈራውን ሀብት በሙሉ ለመዝረፍ ጊዜው አሁን ነው” ብለዋል። በዚህም በዚያም ክህደት እና ስቅለት።

መጋቢት 13/2006 ዓ.ም “በዓይነቱ ለየት ያለ” ስብሰባ በቤተ ክህነቱ ግቢ ተካሒዷል። ለየት ያለ የተባለው አጀንዳውና ቁመነገሩ ሳይሆን ቤተ ክህነቱ ባልለመደው ሁኔታ፣ ከቤተ ክህንቱ ይትባህል ውጪ በዐቢይ ጾም ወቅት ዩየተደረገ የ“ስቅሎ ስቅሎ ስብሰባ” (የስቀለው ስቀለው ስብሰባ) መሆኑ ነው። ፋክት መጽሔት “ለመጽሔቱ ዝግጅት ክፍል የደረሰው በድምፅ የተቀረፀ የውይይቱ ሙሉ ክፍልን ጠቅሶ እንደገለጠው ተሰብሳቢዎቹ ማኅበሩን በተመለከተ ያወጡት የአቋም መግለጫ÷

  • የማኅበሩና የዋነኛ መሥራቾችና አባላት የባንክ አካውንት፣ ቀላልና ከባድ ተሸከርካሪዎች ጨምሮ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶች፣ /ቤቶች፣ የንግድ ተቋማት፣ የአክስዮን ተቋማት፣ የንዋያተ ቅድሳት ማምረቻዎችና ማከፋፈያዎች፣ ከቀረጥ ነጻ የገቡና በመግባት ላይ ያሉ ዕቃዎች በሚመለከታቸው የመንግሥት መሥ/ቤቶች እንዲታገዱ በቅ/ሲኖዶስ አማካይነት ደብዳቤ እንዲጻፍ፤
  •  ከምእመናን በቀጥታም ኾነ በተዘዋዋሪ የሚቀበለው ዓሥራት እየፈረጠመበት ስለኾነ እንዳይቀበል ይከልከል፤
  • የግቢ ጉባኤያት (የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) እርሱ በሚቀርፀው ትምህርት እንዳይወሰዱብን በደንብ መሥራት፤
  • ተጠሪነቱ ከዋና ሥራ አስኪያጅነቱ ሥር ወጥቶ በሰንበት /ቤቶች /መምሪያ ውስጥ አንድ ንኡስ ክፍል ይኹን የሚሉና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

የተሰብሳቢዎቹ ማንነት እና ምግባራቸውን ለጊዜው ብንተተውና ጥያቄያቸውን ብቻ ተመርኩዘን ብንወያይ እንኳን ብዙ ሐጸጽ እና ኢ-ኦርቶዶክሳዊ ተግባራትን ማግኘት እንችላለን።
በዚህ በዐቢይ ጾም የሱባዔ ወቅት እንዲህ ያለውን የአድማ ስብሰባ ለማካሔድ ሲጠይቁ ፈቃድ የሰጠው አካል አንድም ቤተ ክህነቱንና ቤተ ክርስቲያኑቱን አያውቅም ወይም አያምንባትም፤ አንድም ከአቅሙ በላይ የሆነ ተጽዕኖ ተደርጎበታል። ሌላው ሁሉ ቢቀር አዲሱ ፓትርያርክ በዚህ የአመጽ ተግባር ላይ እጃቸውን አስገብተው መገኘታቸው ለዘመነ ፕትርክናቸው ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ያስቀምጥባቸዋል። ምን ይሉኝ ማለት የማያውቁት ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ እንኳን (አፈር ይቅለላቸውና) እንዲህ ያለ ስሕተት ሲሳሳቱ ታይተው አይታወቁም።
የማኅበሩ ንብረት ለመሆኑ የማን ነው?
ይህንን በሥርዓት አስረግጦ መመለስ ያስፈልጋል። ደጀ ሰላም እስከምትረዳው ድረስ ማኅበሩ ሕጋዊ ሰውነት ያገኘው ከቤተ ክርስቲያኒቱ ነው። ቤተ ክርስቲያን ይሁነኝ ብላ ያቆመችው፣ ነፍስ የዘራችበት ማኅበር ነው። በአገሪቱ ሕግ መሠረት ማንኛውም ተቋም ሕጋዊነት ሳይኖረው መንቀሳቀስ አይችልም። ማኅረሩ ቅዱሳን በኤን.ጂ.ኦ ሕግ በመንግሥት መዝገብ ፈቃድ ያወጣ ሳይሆን ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው ፈቃድ፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ዕውቅና የሚንቀሳቀስ ነው።
በምሳሌ እናስረዳ። አራዳ ጊዮርጊስ ያስገነባው ሕንጻ፣ የልደታ ቤተ ክርስቲያን ግንቦች፣ የምስካየ ኅዙናን  ገዳም ት/ቤት የማን ንብረት ናቸው ተብሎ ይጠየቃል? አቡነ ጳውሎስ ያሠሩት መንበረ ፕትርክናው የማን ነው ተብሎ ይጠየቃል? አንዱ ገዳም እርሻ ቢኖረው የማን እርሻ ነው ይባላል? እንዲህ የሚል ሰው ቢመጣም መልሱ ቀላል ነው። “ይህ ንብረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ነው” የሚል ነው።
የምስካየ ኅዙናን ገዳም ት/ቤት የቤተ ክርስቲያኒቱ ቢሆንም የማስተዳደር ኃላፊነቱ የገዳሙ ነው። የአራዳ ጊዮርጊስ ንብረት፣ የመርካቶው ራጉኤል ሕንጻዎችም ወዘተ ወዘተ የቤተ ክርስቲያን ናቸው የሚያስተዳድሯቸው ግን አጥቢያዎቹ ናቸው።
ታዲያ የማኅበረ ቅዱሳን ንብረት የተለየ እንደሆነ ተደርጎ የሚቀርበው ለምንድነ ነው? የቤተ ክርስቲያን ንብረት መሆኑ እየታወቀ፣ ነገረ አስተዳደሩ በማኅበሩ ጠቅላላ አባላት ምርጫ በሚሰየሙ የሥራ አመራር እና የሥራ አስፈጻሚ አካላት መሆኑ እሙን ሆኖ ሳለ የሌላ አካል ሀብት እንደሆነ አድርጎ ማቅረቡ ለምን አስፈለገ?
መልሱ ግልጽ ነው። ንብረቱን ለመዝረፍ፣ ሀብቱን ለመመዝበር ያቆበቆበ፣ የቋመጠ፣ የአጥቢያዎችን ንብረት በመዝረፍ ሚሊዬነር የሆነ የብላው እንብላው ቡድን ፍላጎት ነው።
አዎ፣ ማኅበሩ ከአባላቱ ላብ ባገኘው የፈቃድ ድጋፍ እና አገልግሎቱ በገባቸው ኦርቶዶክሳውያን ርዳታ ሕንጻውን ጨርሷል። አሁን ሲያዩት ያጓጓል። ለእነ ሆድ አምላኩ ዝርፊያ የማይመች ይህንን የመሰለ ነገር አይቶ ማለፍ አይቻላቸውም። ስለዚህም አይሁድ ጌታን በሰላላ ዲናር ክህደት ለመስቀል ሞት እንዳበቁት፤ በግዑ ለእግዚአብሔር (የእግዚአብሔር በግ) ክርስቶስን አርደው ሳይበሉት እንደቀሩት፣ እነዚህ የዘመናችን ተረፈ አይሁድም ማኅበረ ቅዱሳንን ለመስቀል ቋምጠዋል። ላይበሉት፣ ላይጠቀሙበት።
ማኅበሩ አጠቃላይ የገቢና የወጪ ሥርዓቱን የሚያካሒደው ዘመኑ በፈቀደው ጥበብ ሁሉ እንጂ ጊዜ ባለፈበት እና ለዝርፊያ እና ለሙስና በተጋለጠ ያረጀ ያፈጀ የሒሳብ አሠራር አይደለም። እነዚህ ሰቃልያንና ዘራፍያን ይህንን ያውቃሉ። ገንዘቡ እኛ በምንፈልገው መልክ ይሰብሰብ ማለታቸው ለዚያ ነው።
አሁን ስለተጀመረው የቤተ ክህነቱ የመዋቅርና አስተዳደራዊ ለውጥ እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ስለተስፋፋው ዝርፊያ በቅድስት ማርያም ዩኒቨርስቲ የአካውንቲንግ መምህር እና በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ” የሆኑት አቶ ምሐባው ዓለሙ ለአዲስ ጉዳይ መጽሔት ያሉትን ለማስረጃ እንጥቀስ።
“ስለ ፋይናንስ ሥርዓቱ ሲነሣ ብዙ ሰዎች ቤተ ክርስቲያኒቱ የምትጠቀምበት ዘመናዊ አሠራር (double entry) ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን አኹን እየተጠቀመችበት ያለው የፋይናንስ ሥርዓት ዓለም በ፲፯ኛው // የተወውንና የነጠላ ሒሳብ አሠራር (single entry) የሚባለውንና በሞዴል የሚሠራ የሒሳብ አሠራር ነው፡፡ በዓለም ላይ እንዲኽ ዓይነት የሒሳብ አሠራር የሚከተል ምንም ተቋም የለም፡፡ በመኾኑም ይኼን ተረድቶ የፋይናንስ ሥርዓቱን ማዘመን ይገባል፡፡ ይኼ የሒሳብ አሠራር በፍጹም ምቹ አይደለም፡፡ የሒሳብ አሠራሩ በራሱ ነጠላ ነው፡፡ ወጪን ወጪ ይላል እንጂ ምክንያቱን አይናገርም፡፡ ስለዚኽ ወጪን ከነምክንያቱ ገቢን ከነምንጩ የሚጠቅሰው የሁለትዮሽ (ደብል) አሠራር ሥርዓት የላትም፡፡ ይኼ አሠራር ደግሞ በአፋጣኝ መለወጥ አለበት፡፡”
ግለሰቡ “የቤተ ክርስቲያን ፈተናዎች”የሚልና ስለ ዝርፊያው ጥልቅ ምንነት አይን ገላጭ የሆነ ማስረጃ ያቀረቡ ናቸው። ዝርፊያው ምን ያህል የጎላ መሆኑን ሲያብራሩ ያሉትን እናክል፦
አዲስ ጉዳይ፡- በአኃዛዊ ስሌት የገንዘብ ዘረፋው ምን ያህል ይደርሳል?
 አቶ ምሐባው፦ እኔ በየዓመቱ ቤተ ክርስቲያን በመቶ ሚልዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ትመዘበራለች ብዬ በመጽሐፌ ላይ ገልጩ ነበር፡፡ ይኹን እንጂ አሁን ከቀድሞ በተሻለ ጉዳዩን ስመለከተው ቤተ ክርስቲያን በምዝበራ የምታጣው ሀብት ከመቶ ሚልዮኖች የሚልቅ መሆኑን ለመረዳት ችያለሁ፡፡ (አዲስ ጉዳይ፤ ቅጽ 8 ቁጥር 206፤ መጋቢት 2006 ዓ.ም.)
በዚህ ምዝበራ ላይ የተሰማሩት እነማን ናቸው? ፖለቲካዊ አቋማቸው ምንድነው? ይህ ሁሉ ሚሊዮን እና ሚሊዮን የምእመናን ላብና ደም፣ የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሚዘረፈው በነማን ነው? ብለን ትንሽ ገፋ አድርገን ስንጠይቅ ከፍ ብለን የጠቀስነውን የአመጽ ስብሰባ ወደሚያደራጁት አካላት እንመጣለን።
ታዲያ ይሄ የዘረፋ ቡድን፣ በመንግሥት ጥበቃ እንዴት ሊያገኝ ቻለ? የፓርቲያቸው አባላት የሆኑ ሰዎች በቤተ ክርስቲያን ዝርፊያ ላይ ሲሰማሩ አበጃችሁ እየተባሉ ከአባላት ድጎማ በመሰብሰብ በሚያገኘው ሳንቲም ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚረዳ ስብስብን ለማጥቃት ዘመቻ ሲጀመር መንግሥታዊ ጥበቃ አለማድረግ በዘመቻው ከመተባበር ተለይቶ አይታይም።
ከሁሉ ከሁሉ አዲሱ ፓትርያርክ እና አዲሱ አስተዳደራቸው እየተከተለ ያለው አካሔድ ግን ያልተጠበቀ ባይሆንም ለታሪካቸው የማይበጅ እና አሳፋሪ የሚባል ነው። በየሳምንቱ አዳዲስ ደብዳቤ ለማኅበረ ቅዱሳን ለማብረር የማይደክሙ ሰዎች ምእመናንን የሚጠቅም ሥራ ለመሥራት እጃቸውና እግራቸው ሲተሳሰር ማየት ያሳፍራል። “በነገሩ የለሁበትም” እያሉ የሚምሉ የሚገዘቱት አቡነ ማቴዎስም (ሥራ አስኪያጅ) ሆኑ ፓትርያርኩ አቡነ ማቲያስ ከታሪክ ተወቃሽነት ሊያመልጡ አይችሉም።
ቢያንስ ቢያንስ “ኧረ ዐቢይ ጾም ነው፤ ሰው ምን ይለናል” ማለት ማንን ገደለ? ወይስ የቆሎ ተማሪው “ቀራንዮም ቀራንዮ፤ ካህናቱም ካህናቱ” እንዳለው ሆነ? ታሪክ፦ተማሪው ፍርፋሪ ፍለጋ  በእንተ ስማ ለማርያም እያለ ወደ ቀራንዮ ቤት ክርስቲያን ሄደ አሉ።፡ከዚያ ካህናቱ ሳይራሩለት ይቀራሉ። እያዋዛ መናገር የሚችለው ተማሪም “ቀራንዮም ቀራንዮ፤ ካህናቱም ካህናቱ” አለ ይባላል። አሁንም በዚህ የጌታ ጾም እንደቀደሙት ካህናተ አይሁድ “ስቅሎ ስቅሎ” ማለት በስምም በግብርም አያመሳስላችሁም? ቤተ ክርስቲያንን ብሎ የተሰበሰበው ይህ ትውልድ ግን በዳዊት ቃል፦
“”ፍታሕ ሊተ እግዚኦ አምላኪየ በከመ ጽድቅከ፤
ወኢይትፈስሑ ላዕሌየ።
አቤቱ አምላኬ እንደ ጽድቅህ ፍረድልኝ፤
በላዬም ደስ አይበላቸው” (መዝ 35፡24) እንደሚል ባይዘነጉት ግሩም ነው።
ቀጥሎም፦
“ሐሰስክዎ ለእግዚአብሔር ወተሰጥወኒ፤
ወእምኵሉ ምንዳቤየ አድኀነኒ፤
እግዚአብሔርን ፈለግኹት መለሰልኝም፤
ከመከራዬም ሁሉ አዳነኝ።” (መዝ. 33፡ 4) ማለቱ አይቀርም። እግዚአብሔርን ያለ ትውልድ ነዋ።
ጆሮ ያለው ይስማ።
ቸር ወሬ ያሰማን፤
አሜን
Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

የመንግስት ባለስልጣናት የሙስና መንገዳቸውን ለማሳካት ሲሉ በመንግሥት ፖሊሲ፣ አሠራርና መመርያ ላይ ጫና እየፈጠሩ እንደሚመቻቸው ተደርጎ እንዲወጣ በማድረግ ላይ ናቸው ሲል ሙስና ኮሚሽን አማሯል።

ኢትየጵያ ውስጥ አሁን ያለው የሙስና መጠን ትናንትና ከነበረው እጥፍና ከእጥፍ በላይ አሻቅቧል፡፡ አሁን አገሪቷ ውስጥ ያለው የኑሮ ውድነት ወደላይ እንዲያሻቅብ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱም የሙስና ጣርያ መንካት ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ላይ አሳሳቢ መሆኑን መግለጽ ቀርቶ የእገሌን አገር ደረጃ አያክልም የሚለውን አባባል የኢትዮጵያ ሕዝብን እንደመናቅ ይቆጠራል፡፡በአሁኑ ወቅት ሙስና በኢትዮጵያ ውስጥ ተንሰራፍቷል፡፡ ባለጉዳይም ጉቦ ካልሰጠ ጉዳዩን እንደማያስጨርስ፤ ጉዳይ ፈጻሚም ገንዘብ ካላገኘ ጉዳይን ማስጨረስ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን በገሃድ በሚታይበት ደረጃ ላይ ነን፡፡ በቀበሌ፣ በወረዳ፣ በክፍለ ከተማ፣ በአዲስ አበባ መስተዳድር፣ በፖሊስ፣ በፍርድ ቤት፣ በአገር ውስጥ ገቢ፣ በጉምሩክ፣ በመንገድ ትራንስፖርት፣ በሆስፒታሎች፣ በኢሚግሬሽን፣ ወዘተ ጉዳይን ለማስጨረስ ጉቦ መስጠት የተለመደ ሆኗል፡፡

ጉቦ መስጠትም ሆነ መቀበል እንደ ብቃትና እንደ ሥልጡንነት እየታየ ነው፡፡ ጉቦ የማይቀበል የማይረባና የማይጠቅም ተብሎ የሚሰየምበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን እያንዳንዱ ሰው በሚገባ ያውቀዋል፡፡ እንደዚህ በመሰለ አስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ባለንበት ወቅት ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ አሳሳቢ ደረጃ ላይ አይደለም ሲባል ምን ማለት ነው? መረጃው የተገኘውስ ከየት ነው? ከተበዳይ ወይስ ከበዳይ?

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄዱ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ግዢዎች አነስተኛም ይሁኑ ትላልቅ የፕሮጀክት ጨረታዎች ያለኮሚሽን ክፍያ የተፈጸሙ ናቸው የሚል ጥናት ፍፁም ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፡፡ ምንልክሳልሳዊበአሁኑ ወቅት በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ የሚካሄዱ ግዢዎችና ጨረታዎች ሕጋዊነትን ለማስያዝ ብቻ የሚካሄዱ ካልሆነ በስተቀር፣ አስቀድሞ ከታቀደውና ከታለመው ሰው ወይም ድርጅት ውጭ ማንም እንዲገባ በማይፈቀድበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን የዋህ ሰው ሳይቀር በሚገባ የሚረዳበት ደረጃ ላይ እኮ ነን ያለነው፡፡ ግዢዎች ሲፈጸሙ ወይም ጨረታ በሚወጣበት ጊዜ የሚደረገውን ለአብነት እንይ፡፡

እጅግ የሚያስፈራው ደግሞ ሙስና ከመስፋፋቱም በላይ ሙስናን የሚዋጋና እውነታው ገሃድ እንዲሆን ጥረት የሚያደርግ ወገን ያለአግባብ እየተበደለ ነው፡፡ ሙሰኞች በያዙት የሕዝብና የመንግሥት ሥልጣን ሀቅን ለመቅበር የሚችሉትን ያህል ማድረግ የሚችሉበት ደረጃ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ አገሪቷን እጅና እግሯን አስሮ ለጅብ እንደመስጠት ይቆጠራል፡፡

የጨረታ ዶክመንት ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ሰው ከሳምንታት ወይም ወራት በፊት አስቀድሞ እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡ የጨረታ ዶክመንቱ (ቴክኒካል ስፔስፊኬሽኑ) በአጫራቹ ድርጅት አማካይነት በተመረጡና በታመኑ ሰዎች እንዲሠራ ይደረጋል፡፡ ይህ በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ግዥ በሚፈጽሙ ተቋማት ውስጥ በግልጽ እንደሚደረግ ግልጽ ነው፡፡ ፀሐይ የሞቀውም ነው፡፡ ለጨረታ ወይም ለግዥው የተዘጋጀው ወይም የተመደበው ገንዘብ ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ግለሰብ አስቀድሞ እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡ ለጨረታ የተዘጋጀው ወይም የተመደበው ገንዘብ አስቀድሞ ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ግለሰብ ከተሰጠ በኋላ፣ በሚያቀርበው ዋጋ ላይ ምንም ዓይነት ልዩነት ሳይኖረው ተፈላጊው ድርጅት ወይም ግለሰብ እንዲያቀርብ ተደርጎ ተመራጭ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ ምንልክሳልሳዊበአንዳንድ ግዥዎች አሸናፊ እንዲሆን የሚፈለግ የተጫራች ድርጅት ስፔስፊኬሽን እንዳለ የጨረታ ዶክመንት ሆኖ እንደሚቀርብ በግልጽ በሚታወቅበት ደረጃ ላይ ነን፡፡

በአሁኑ ወቅት እየተካሄዱ ያሉ ግዥዎችና ጨረታዎች ከፍተኛ ሙስና እየተፈጸመባቸው የሚካሄዱ መሆኑ ቢታይም፣ ሕጋዊነትን ተከትለው እንደተፈጸሙ ስለሚቀመጡ (በወረቀት፣ በአካሄድና በአሠራር) እጅግ የረቀቁና ሥር እየሰደዱ የመጡ ሙስናዎችን ለማየት ግን አዳጋች አይደለም፡፡ ምንልክሳልሳዊአንድ ድርጅት ከሁለት በላይ የተለያዩ ስም የያዙ የድርጅት ስሞችን ይዞ በመቅረብ አንዱ አሸናፊ ሌሎች አጃቢዎች ሁነው እንደሚቀርቡ በግልጽ ይታወቃል፡፡ የጨረታ ጊዜዎችን እጅግ በማሳጠር አሸናፊ እንዲሆን ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ግለሰብ ግን አስቀድሞ መረጃውን በመንገርና ተዘጋጅቶ እንዲቆይ በሚደረግ፣ የሌሎች ተጫራቾችን ጊዜ በማሳጠርና የዝግጅት ጊዜ እንዲያጡ በማድረግ የሚፈጸሙ ግዥዎችና ጨረታዎች ናቸው እየተካሄዱ ያሉት፡፡ምንልክሳልሳዊ

አንዳንድ ቦታ ጨረታ በሚዘጋጅበት ወይም በሚካሄድበት ጊዜ ተጫራቾቹ በአጫራቹ ድርጅት ግለሰቦች ስም የሚጠሩበት አጋጣሚ እንዳለም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ ማን አሸነፈ ሲባል የአጫራቹ ግለሰብ ስም እየተጠራ እገሌ አሸነፈ ተብሎ በሚነገርበት ደረጃ ላይ እንዳለን ለማንም ባልተሰወረበት ሁኔታ ላይ ነን፡፡ እጅግ በጣም የሚገርመው ደግሞ ከጨረታ በኋላ አሸናፊው ድርጅት በፕሮጀክቶች ክትትልና በዕቃ ርክክብ ከሚፈለገው ደረጃና ብቃት በታች አፈጻጸም ያሳያል፡፡ ከሚፈለገው ዕቃ ውጭ አቅርቦቶች ሲካሄዱ ዝም እየተባለ የሚፈጸሙ የፕሮጀክቶች ግዥዎች ከበስተጀርባቸው ትልቅ ሙስና እንደሚካሄድባቸው ብዙዎች ያውቁታል፡፡ ምንልክሳልሳዊ

ለዚህ ትልቅ ማሳያ ሊሆኑ የሚችሉ በመንገድ ግንባታ፣ በትላልቅ ግድቦች ግንባታ፣ በውኃ ሥራዎች፣ በቴሌኮም ፕሮጀክቶች፣ በቤቶች ግንባታና ማጠናቀቂያ ላይ ችግሮች ጎልተው እንደሚታዩ በእጅጉ ይታወቃል፡፡ እንደ ምሳሌ ለማቅረብ ከኤርፖርት እስከ መስቀል አደባባይ እየተሠራ ያለው መንገድ ቀደም ብሎ ለሌላ ድርጅት ተሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ኋላ ግን ተቀይሮ ለሲአርቢሲ ተሰጥቷል፡፡ የመጀመርያው ተጫራችና አሸናፊ ድርጅት አቅም ሲመዘን እንኳን በዚህ ትልቅና አስቸጋሪ መንገድ እንዲሳተፍ በገጠር መንገድም ለማሳተፍ የሚያስችል ብቃት እንደሌለው ግልጽ ነበር፡፡ ታዲያ ይህ ድርጅት አሸናፊ እንዲሆን ተመርጦ የነበረው አላስፈላጊ ግንኙነት በመመሥረቱ ነበር፡፡ የዚህ ዓይነት መሰል ገጠመኞች ደግሞ እጅግ በጣም ብዙ ናቸው፡፡ ባንኮች ብድርና የውጭ ምንዛሪ ለመስጠት በግልጽ ኮሚሽን በሚቀበሉበት አገር ላይ ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ አሳሳቢ ደረጃ አይደለም እንዴት ይባላል?

የፀረ ሙስና ኮሚሽን አንዳንድ ሰዎች አሳሳቢ የሚባል የሙስና መረጃ ሲያገኙ፣ በተለይ ከሀብታም ነጋዴዎች ጋር የሚያያዝ ከሆነ ቀድመው ችግሩን ለማወቅና ለመፍታት ከሚጥሩ ይልቅ ለግልግል በሚሯሯጡበት አገር ላይ እያለን፣ ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ ዝቅተኛ ነው እንዴት ይባላል? በአሁኑ ወቅት ከከፍተኛ እስከ ዝቅተኛ የመንግሥት አመራሮች ድረስ በሀብታም ተፅዕኖ ሥር በወደቁበት፣ ጉቦ በመቀበል የአገራቸውን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው በሚሰጡበት፣ ሀቅን በገንዘብ በሚለውጡበት፣ በጠራራ ፀሐይ ብሉ ሌብልና ቪኤስኦፒ በካርቶን በሚጫንበት፣ የሰው ሕይወት በገንዘብ አደጋ ላይ በሚወድቅበት፣ ዓይን ያወጡ ሙሰኞች በሰፊው ሕዝብ ፊት ደረታቸውን ነፍተው ጉራቸውን በሚነፉበትና ኃይላቸውን የሚያሳዩበት ወቅት መሆናችን እየታወቀ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ አይደለም እንዴት ይባላል?

ትናንትና ለሀቅ፣ ለዲሞክራሲና ለአገራቸው ብልጽግና ሲሉ የወጣትነት ዕድሜያቸውን በረሃ የወጡ ወንድሞቻቸውን፣ እህቶቻቸውንና ጓደኞቻቸውን ቀብረው እዚህ ደረጃ ላይ የደረሱ ጀግኖች በሙስና ተነክረው ሀብታም ሥር በተንበረከኩበት ወቅት፣ የተለያዩ ድርጅቶች ቅጥረኛ በሆኑበት ወቅት፣ አሠራርና መመርያዎችን ጥሰው በኔትወርክ በተሳሰሩበት ወቅት፣ እርስ በራሳቸው እሳትና ጭድ ሁነው በማይተማመኑበት ወቅት፣ ለሕዝብ ህልውና ዋስትና በታጣበት ወቅት፣ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያሳስብ አይገባም ተብሎ እንዴት ይነገራል?

ከምንም ጊዜ በላይ እጅግ አሳሳቢ፣ ከአሳሳቢነቱ በላይም ጊዜ የማይሰጠውና ወረርሽኝ በሆነበት ደረጃ ላይ ነው ያለነው፡፡ አንዳንድ ቦታ ላይም ሙሰኞች የሙስና መንገዳቸውን ለማሳካት ሲሉ በመንግሥት ፖሊሲ፣ አሠራርና መመርያ ላይ ጫና እየፈጠሩ እንደሚመቻቸው ተደርጎ እንዲወጣ በማድረግ ላይ እንደሆኑ ወሬዎች በሚናፈሱበት ደረጃ ላይ ነው ያለነው፡፡ አንዳንዱ ቅንጣት ጥፋት የሌለው ይመስል ከራባቱን አስሮ ‹‹ሙስናን እንዋጋ›› የሚለው ከበስተጀርባው ትልቅ ጥፋት ተሸክሞ ነው፡፡

እጅግ የሚያስፈራው ደግሞ ሙስና ከመስፋፋቱም በላይ ሙስናን የሚዋጋና እውነታው ገሃድ እንዲሆን ጥረት የሚያደርግ ወገን ያለአግባብ እየተበደለ ነው፡፡ ሙሰኞች በያዙት የሕዝብና የመንግሥት ሥልጣን ሀቅን ለመቅበር የሚችሉትን ያህል ማድረግ የሚችሉበት ደረጃ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ አገሪቷን እጅና እግሯን አስሮ ለጅብ እንደመስጠት ይቆጠራል፡፡ምንልክሳልሳዊ

Image

ቅሬታቸውን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች ገልጸዋል:

(አዲስ አድማስ መጋቢት 20 2006 ዓ.ም)

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ በኾኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን እምነትና ሥርዐት እንዲማሩ፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን በማቀናጀት ሞያዊ ድጋፍ እንዲያበረክቱ በማስተባበር ላይ የሚገኘውን ማኅበረ ቅዱሳንን በአሸባሪነት በመፈረጅ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካይነት ጠቅላላ ሀብቱና ንብረቱ የሚታገድበት ውሳኔ እንዲተላለፍ በመንግሥትም በኩል እርምትና ርምጃ እንዲወሰድበት የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የአድባራት አስተዳዳሪዎች መግለጫ አውጥተውበታል በተባለው ስብሰባ ጉዳይ ኹለት የቅ/ሲኖዶስ አባላት ለከፍተኛ የመንግሥት ሓላፊዎች ቅሬታቸውን ማሰማታቸው ተገለጸ፡፡

የቅ/ሲኖዶሱን ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሉቃስንና በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስና የጅማ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን በስም የጠቀሱት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ምንጮች፣ ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅሬታቸውን ያቀረቡት ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች እንደኾነ ቢገልጹም የሓላፊዎቹን ስም ከማሳወቅ ተቆጥበዋል።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በፀረ ሙስናና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከመንግሥት ጋራ የተጠናከረ ሥራ ለመሥራት በቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መወሰኗን ሊቃነ ጳጳሳቱ አስታውሰው፣ በዚህም መሠረት ለሙስናና ብክነት የተጋለጡ አሠራሮችን ለማረምና ለማስተካከል ጥረት እያደረገች ቢኾንም ባለሥልጣናቱ ከማን ጋር መሥራት እንዳለባቸው በትክክል አለመለየታቸውንና ግንኙነቱም ሙሰኞችን በአይዟችኹ ባይነት የሚያበረታታ እንደኾነ መናገራቸው ተጠቅሷል፡፡

ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅሬታቸውን በዚህ መልኩ ለባለሥልጣናቱ ለማቅረብ ያስገደዳቸው የአድባራት አስተዳዳሪዎቹ፣ ‹‹ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችን ለአድማ ያነሣሣል፤ በሀገርና በቤተ ክርስቲያን ላይ ሁከትና ሽብር እንዲፈጠርና ሰላም እንዲደፈርስ ያደርጋል›› ባሉት በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚወሰደው አስተዳደራዊ ርምጃ በፀረ ሽብር ሕጉ መሠረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጠየቁበት መግለጫቸው ነው፡፡

የመንግሥት የተለመደ እገዛ እንዳላቸው በአጽንዖት የጠቀሱት አስተዳዳሪዎቹ በዚሁ መግለጫቸው፣ መንግሥት በፀረ ሽብር ሕጉ ታሳቢነት ገለልተኛ ኦዲተር መድቦ በማኅበሩ ላይ የሀብትና ንብረት ቁጥጥር የማካሔድ ድጋፉ እንዳይለያቸው ያስተላለፉት ጥሪ በሌላቸው ሕጋዊነትና ውክልና የቀረበ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በራስዋ መንገድ ማከናወን በሚገባት ተግባር ላይ አላስፈላጊ ጣልቃ ገብነትን የሚጋብዝና ለውጭ ተጽዕኖ አሳልፎ የሚሰጥ እንደኾነ ተመልክቷል፡፡

በመንበረ ፓትርያርኩ ከተገኙት የመንግሥት ሓላፊዎች ጋራ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እንደተካሔደ በተገለጸው የኹለትዮሽ ውይይት፣ ማኅበረ ቅዱሳንን በመቃወም ሰበብ የወጣው የአስተዳዳሪዎቹ መግለጫ ዋነኛ ዓላማ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ ወስና የምታካሒደውን የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ሒደት መጋፋት ነው ተብሏል፡፡ መላውን የሀገረ ስብከቱን አድባራት አገልጋዮች ለመወከል የማይበቁ ጥቂት ግለሰቦችን በመያዝ ይደረጋል የተባለው ይኸው እንቅስቃሴም ‹‹የት እንደሚያደርስ እናየዋለን›› የሚሉ ንግግሮች ጭምር ከሊቃነ ጳጳሳቱ የተሰሙበት እንደነበር ምንጮቹ አስታውቀዋል፤ ጉዳዩም በመጪው ግንቦት በሚካሔደው የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓቢይ መነጋገርያ መኾኑ እንደማይቀር ተጠቁሟል፡፡

ከሀገረ ስብከቱ አድባራት የተውጣጡ ናቸው የተባሉ አስተዳዳሪዎች ያደረጉት ስብሰባ፣ አስተባባሪዎቹ ከፓትርያርኩ ተሰጥቶናል ከሚሉት ፈቃድ በቀር በሀገረ ስብከቱ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስና በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ዘንድ በይፋ የታወቀና የተፈቀደ እንዳልነበረ ምንጮቹ ለአዲስ አድማስ ገልጸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳንን በሁከትና ሽብር ለሚከሱ በቂ ሕጋዊነትና ውክልና የላቸውም ለተባሉ አካላት ፓትርያርኩ የሰጡትን የስብሰባ ፈቃድ፣ በቅርቡ ማኀበሩ አገር አቀፍ የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤ እንዳያካሒድ ከተጣለበት እገዳ ጋር ያነፃፀሩ ታዛቢዎች፣ ሁኔታው የፓትርያርኩን ርምጃዎች መርሕ አልባነት የሚያጋልጥ ነው ይላሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር መተዳደርያ ደንብ ያለውና ግልጽ ተልእኮ ይዞ የሚንቀሳቀሰው ማኅበር፣ህልውናና አገልግሎት በግልጽ አስተዳደራዊ ጫና ውስጥ መግባቱን እንደሚያመለክት ታዛቢዎቹ ያምናሉ፡፡

ከመዋቅር፣ ከሀብትና ንብረት ቁጥጥር ጋራ በተያያዘ በማኅበሩ ላይ የሚቀርቡት ውንጀላዎች፣ በፀረ አክራሪነት ስም የሚናፈስበትን ፕሮፓጋንዳ በማጠናከር ፖሊቲካዊ ርምጃ እንዲወሰድበት ፍላጎት ያላቸውን አካላት ምኞት በጉልሕ እንደሚያሳይ አስረድተዋል፡፡ ማኅበሩ ሃይማኖቱን የሚጠብቅ፣ ቤተ ክርስቲያኑን የሚከባከብና ሀገሩን የሚወድ ብቁ ዜጋ ለማፍራት ያለውን ዓላማ የሚረዱ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ምእመናንና የመንግሥት አካላትም የተቃዋሚዎቹን አቋምና መግለጫ በጥንቃቄ እንዲመለከቱትም አሳስበዋል፡፡

በሌላ በኩል፣ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖናና ትውፊት ውጭ ነው በተባለ የሌላ እምነት አስተምህሮ የተነሳ በኮሌጁ ደቀ መዛሙርት መካከልና በደቀ መዛሙርቱ ምክር ቤት አባላት ውስጥ ያለው ግንኙነት ውጥረት ውስጥ እንደገባ እየተገለጸ ነው፡፡

ከኮሌጁ ውጭ ከሚገኙና በቅ/ሲኖዶስ ከተወገዙ ግለሰቦችና ቡድኖች ጋር የዓላማና የጥቅም ግንኙነት መሥርተዋል በተባሉ ጥቂት ደቀ መዛሙርት አማካይነት በኮሌጁ ውስጥ ከመንጸባረቅ አልፎ እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ ነው የተባለው ይኸው አስተምህሮ፣ አስተዳደራዊ መፍትሔ እንዲበጅለት የደቀ መዛሙርቱ ምክር ቤት ጥር 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ለኮሌጁ አስተዳደር ያቀረበው ጥያቄ እስከ አሁን ምላሽ አለማግኘቱ ውጥረቱን የበለጠ እንዳባባሰው ለአዲስ አድማስ የደረሰው መረጃ አመልክቷል፡፡

የአስተምህሮው ውዝግብ አፋጣኝ መፍትሔ አለማግኘቱ ከደቀ መዛሙርቱ አልፎ የምክር ቤት አባላትን ለሁለት እንደከፈለ ተገልጧል፡፡ ኮሌጁንና ደቀ መዛሙርቱን በቅንነትና በትጋት ለማገልገል በደቀ መዛሙርቱ ጠቅላላ ጉባኤ የተመረጠውና ከፍተኛ ሓላፊነት የተጣለበት የደቀ መዛሙርቱ ምክር ቤት፣ ‹‹ከልማቱ ጥፋቱ አመዝኗል›› ያሉት ጸሐፊውና አንድ የአመራር አባሉም ራሳቸውን ማግለላቸው ታውቋል፡፡

‹‹ከቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖናና ትውፊት ውጭ የኾነ የኑፋቄ ትምህርት ሲዘራ ድምፀ ተዓቅቦ ከማድረግ ባሻገር ችግር አለባቸው ከሚባሉት ደቀ መዛሙርት ጎን ተሰልፈው ኮሌጁንም ኾነ ሓላፊነት የሰጠንን ደቀ መዝሙር በቅንነት እንዳናገለግል የአንዳንድ መማክርት አባላት ተግባር አውኮናል›› ያሉት ሁለቱ አባላት፤ በዚህ ሳምንት ለኮሌጁ ዋና ዲን ጽ/ቤት በጻፉት ደብዳቤ፣ ምክር ቤቱ የችግሩ ተባባሪ በመኾኑ ከሓላፊነቱ ታግዶ ጉዳዩ እንዲጣራና እምነታቸውና ሥነ ምግባራቸው በተመሰከረላቸው ደቀ መዛሙርት እንዲተካ ጠይቀዋል፡፡

‹‹የቤተ ክርስቲያንን እንጀራ እየበሉ፣ በጀቷን አውጥታ እያስተማረቻቸው የሌላ እምነት የሚያራምዱ›› ያሏቸውን ወገኖች አጥብቀው እንደሚቃወሙ የገለጹ የደቀ መዛሙርት ተወካዮች በበኩላቸው፣ ኮሌጁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖናና ትውፊት ለመጠበቅና ለማስፋፋት የቆመ በመኾኑ አስተዳደሩ፣ በቃል፣ በድምፅና በጽሑፍ የሚቀርቡለትን ማስረጃዎች መርምሮ አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የአሜሪካን ባለስልጣናት ኢህአዴግን በተመለከተ የሚጠቀሙት ቃልና የድምጻቸው ቃና ተቀይሯል::

ጎልጉል ፦ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም ብቸኛ ተዋናይና ፊት አውራሪ አድርጎ ራሱን የሾመው ኢህአዴግ ለቀጠናው ስጋት እንደሚሆን ተጠቆመ። አልሸባብንና አልቃይዳን ከምንጩ እናጠፋለን በሚል ስትራቴጂ መለስ ከቆፈሩት ጉድጓድ ውስጥ ሰምጣ የነበረችው አሜሪካ ከጉድጓዱ ለመውጣት ወስናለች። ኢትዮጵያዊያን የሚያምኑትና የሚቀበሉትን መሪ በድፍረት አደባባይ የማውጣት ሃላፊነቱ “አገር ወዳድ” በሚሉ ዜጎችና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጫንቃ ላይ ነው።

ህወሃት ያቋቋማቸው ጥቃቅን መንግስታት ከህዝብ ይልቅ ለህወሃት የወደፊት እቅድ ታማኝ በመሆን መጓዛቸው ከቀን ወደቅን የፈጠረው ስሜት ኢህአዴግን እየበላው እንደሆነ የጠቆሙ የዜናው ምንጮች፣ ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪቃ የሰላም አባት ሊሆን ቀርቶ የራሱንም ችግር መፍታት ወደማይችልበት የቁርሾ ማሳ ውስጥ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

ህወሃት “በነጻ አውጪነት” ያሰላውና፣ ይህንኑ ዓላማውን በፈለገበት ቀን ተግባራዊ ለማድረግ ያመቸው ዘንድ በየክልሉ ለጣጥፎ ያቋቋማቸውን ፓርቲዎች ሲመሩ የነበሩት አቶ መለስ በድንገት ካለፉ በኋላ ኢህአዴግ ውስጣዊ ሰላሙ መናጋቱ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ነው። ኢህአዴግ በበኩሉ “የጓድ መለስን ውርስና ራዕይ ያለማዛነፍ እናስቀጥላለን” እያለ አገሪቱን በደቦ እንድተመራ ማድረጉ የሚታወስ ነው።

አቶ መለስ በጓዶቻቸው ቋንቋ “ተሰው” ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ምክትል ጠ/ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን ለመተካት ተቸግሮ ነበር። ደህንነቱን፣ መከላከያውን፣ ፖሊስና ዋንኛ የአገሪቱን ተቋማት ጠቅልሎ የያዘው ህወሃት በቀጥታ አሜሪካ ባደረገችው ጫና ሳይወድ በግዱ አቶ ሃይለማርያምን በጠ/ሚኒስትርነት ለመሰየም ተገደደ። የስልጣን ክፍተቱን በተመለከተ አቻ ድርጅቶችና ህወሃት ውስጥ አለመግባባት ተፈጥሮ ስለነበር “ምደባ” በሚል ኢትዮጵያ በደቦ የሚመሯት አራት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተሰየሙላት።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የአሜሪካ ዲፕሎማት እንዳሉት አሜሪካ ስጋት የገባት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነበር። መለስ እንዳለፉ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ በመላክ ሁኔታውን በመገምገም ስራ የጀመረችው አሜሪካ አሁን አሁን በህወሃት ስትራቴጂ የተሰራው ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ዋንኛ የችግር ምንጭ ስለመሆኑ ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል። በዚህም የተነሳ የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየመከሩበትና የመፍትሔ ስትራቴጂ እየነደፉ ነው።

“We cannot afford to lose Ethiopia” አሜሪካ ኢትዮጵያን ልታጣት አይገባም በማለት ለጎልጉል የዋሽንግቶን ዘጋቢ የተናገሩት የዲፕሎማት ምንጭ “የአሜሪካን ባለስልጣናት ኢህአዴግን በተመለከተ የሚጠቀሙት ቃልና የድምጻቸው ቃና ተቀይሯል” ሲሉ የጉዳዩን ክብደት አመላክተዋል።

በዋሽንግቶን የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የምክር ቤት አባላት እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው ኢህአዴግን አስመልክቶ ተደጋጋሚ ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል። አዲስ አበባም ተወካይ በመላክ ከሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጋር በግል እየተነጋገሩ ነው። በያዝነው ሳምንትም ለተመሳሳይ ስራ አዲስ አበባ የተጓዙ አሉ። እንደ ዲፕሎማቱ ገለጻ የህወሃት ሰዎች ውስጣዊ ችግር እንዳለ አይቀበሉም። በግል ያነጋገሯቸው የሌሎች ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ግን ኢህአዴግ ውስጡ አለመረጋጋትና ስጋት የተሞላው ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

በኢትዮጵያ አንድ ችግር ቢፈጠር ለማረጋጋት አስቸጋሪ እንደሚሆን፣ ህዝቡ በተለይ በህወሃቶች ላይ የሚያሳየው ጥላቻ እየተካረረ መምጣቱ፣ በአገሪቱ የሚፈጸመው ያልተመጣጠነ የሃብት ስርጭት፣ አፈናውና ሌሎች የህወሃት/ኢህአዴግ ተግባራት ተዳምረው ህዝቡን ክፉኛ ማስቀየሙ ያልታሰበ ችግር ሊቀሰቅስ እንደሚችል አሜሪካ መገንዘቧን ያወሱት ዲፕሎማት፣ “ህወሀቶች የቀጠናው የሰላም ምንጮች ስለመሆናቸው ለራሳቸው ምስክርነት ለመስጠት ቢሞክሩም በተግባር የሚታየው ግልባጩ ነው” ብለዋል።

ኢትዮጵያ ላይ የተተከለው የጎሳ አገዛዝ እንደሆነ ያመለከቱት እኚሁ ዲፕሎማት “በጎሳ አስተሳሰብ የተዋቀረው ኢህአዴግ ችግሩ ከገነፈለ ሊቆጣጠረው የሚችል ባለስልጣንና መሪ የለውም። አስተዳዳራዊ ማዕከላዊነት አይታይበትም። በግል የሚወስን ባለስልጣንና ርምጃ የሚወስድ አካል የለውም” ሲሉ የስጋቱን ግዝፈት ያሳያሉ። በዚህ ሂደት ውስጥ ችግሩ ቢከሰት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰቡ አዳጋች እንደማይሆን ይጠቁማሉ። አያይዘውም “አሜሪካ ቸል ብላ ስትመለከተው የነበረውን ጉዳይ አጽንኦት ብትሰጠው አይገርምም” ብለዋል። አሜሪካ ይህንን የምታደርገው ለራሷ ስትል እንደሆነ ያልሸሸጉት ዲፕሎማት አንድ ጥያቄም ጠይቀዋል። “እናንተስ ለራሳችሁ ስትሉ ምን እየሰራችሁ ነው?” ከረጅም ፈገግታ ጋር።

አልቃይዳን ከምንጩ ማድረቅ በሚለው የመለስ ስትራቴጂ ለኢህአዴግ ግብር ስታስገባ የነበረችው አሜሪካ ግብሯን ስትገብር የኖረችው በፔንታጎን ወታደራዊ ውሳኔ መሰረት ነበር። ኢህአዴግም ግብሩ እንዳይቆምበት በአዲስ አበባ ታክሲ ላይና ህዝብ በሚያዘወትርባቸው ቦታዎች ፈንጂ በማፈንዳት ሲጫወተው የነበረውን ድራማ ዊኪሊክስ (ሹልክ ዓምድ) አምባሳደር ያማማቶን ጠቅሶ ማጋለጡ አይዘነጋም። በዚሁ መነሻ ይመስላል ኢህአዴግ የቀድሞውን ጨዋታ የመጫወት እድሉ እንዳከተመ እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ባደባባይ የመለስን ስብዕና በመዝለፍ ባልተለመደ መልኩ ተናግረው ነበር።

ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ዲፕሎማት “እናንተስ” በሚል ለሰነዘሩት ጥያቄ ማብራሪያ ተጠይቀው “እኔ ኢትዮጵያዊ ብሆን አገሬን አስቀድማለሁ” የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል። አሜሪካ አማራጭ ማጣቷንም እንደ አንድ ችግር አንስተዋል።

በዲፕሎማቱ አስተያየት ላይ ገለልተኛ ወገኖችን አነጋግረናል። ያሰባሰባንቸው አስተያየቶች “አሜሪካ እዚህ ደረጃ ከደረሰች፣ ኢህአዴግም በዚህ ደረጃ ከተመደበ ተቃዋሚዎች የግል ጉዳያቸውንና ፕሮግራማቸውን ለህዝብ ውሳኔ በመተው ለመጪው ትውልድና ለአገር ሲሉ ከመቧደን በሽታ ሊፈወሱ ይገባል” የሚል ይገኝበታል።

የተቃዋሚ ፓርቲዎች ተቀናጅቶ መበተን፣ ተደራጅቶ መፍረክረክ፣ ተደላድለው መስለል በተለያዩ ወቅቶች ህዝብ ተስፋ እንዲቆርጥ አድርገዋል። የሚፎካከሩትን ፓርቲ ትተው እርስ በርሳቸው ለተራ ጉዳይ ሲሻኮቱ ዓመታት አሳልፈዋል። በዚህም የተነሳ “አማራጭ የለም” በሚል ኢህአዴግን ማንገስ ግድ እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች “የተቃዋሚ ፓርቲዎች ይህንን አስተሳሰብ ሰብረው አገር መምራት እንደሚችሉ የሚያረጋግጥ ህብረት መፍጠር ይገባቸዋል። ይህም ካልሆነ የርስ በርስ ውዝግባቸውን ማቆምና የራሳቸውን የቤት ስራ መስራት ላይ ማተኮር ግዳጃቸው ይሆናል” ብለዋል።

ምሁራን ከተደበቁበት ሊወጡ እንደሚገቡም ያሳሰቡ አሉ። አገር የመምራት፣ በህዝብ የመታመን፣ የህዝብን ይሁንታ ማግኘት እንችላለን የሚሉ ከፊት ለፊት፣ አሁን ከፊት ያለውን ችግር በመጥረግ የወደፊቷን ኢትዮጵያ በመገንባትና መጪውን ትውልድ በማዳኑ ስራ አጋዥ ሃይል ለመሆን መወሰን እንደሚገባቸው በመግለጽ ጥሪ አቅርበዋል። ከሁሉም በላይ ግን “አሁን ካለው ህዝብን ካገለለ ዘመናዊ የመሳፍንት ስርዓት ኢትዮጵያንና ህዝቧን ማሻገር የሚችል ሞገሰ ሙሉ፣ ቅን፣ ከጥላቻ የጸዳ፣ ከሥልጣን ይልቅ የወደፊቷን ኢትዮጵያ አሻግሮ መመልከት የሚችል መሪ ወደ ፊት ወጥቶ በግልጽ ለህዝብ የሚተዋወቅበትን መንገድ የማህበራዊ ሚዲያዎች፣ ድረገጾች፣ ሬዲዮኖች አገር ወዳድ የመገናኛ አውታሮች አጀንዳ አድርገው ሊወያዩበት ይገባል” የሚለው አስተያየት ሚዛኑን የደፋ ሆኗል።

“…የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄውን አልተቀበኩትም::” የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

ምላሹን አልቀበልም በማለቱም በፖስታ ቤት ተልኮለታል ህገ መንግስቱ እውቅና የቸረው ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ሳይሸራረፍ መተግበሩን እንዲከታተል በአዋጅ የተቋቋመው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መጋቢት 28/2006 ዓ.ም መነሻውን ፓርቲው ከሚገኝበት ቀበና በማድረግ በአራት ኪሎ አደባባይ በመዞር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ፊት ለፊት የሚጠናቀቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ በመግለጽ ለኦፊሰሩ ደብዳቤ አስገብቶ የነበረ ቢሆንም መስተዳድሩ በአዋጅ የተሰጠውን ጊዜ ገደብ አሳልፎ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ኦፊሰሩ በደብዳቤያቸው ‹‹በርካታ ትምህርት ቤቶች ዩኒቨርስቲና ፣የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ የተጠየቀውን የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን፡፡››ብሏል፡፡ የአገሪቱ ፓርላማ ‹‹ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ስነ ስርዓት ባወጣው አዋጅ ‹‹የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ግዜም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም››(አዋጅ ቁጥር 3/1983 )በማለት ያወጀውን በአዋጁ ስር የተቋቋመው ጽ/ቤት በማን አለብኝነት በመሻር የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄውን አልተቀበኩትም ብሏል፡፡

አንድነት አዋጁን የጣሰውን ደብዳቤ እንደማይቀበል በመግለጽ ለኦፊሰሩ ደብዳቤ በመጻፍ በአካል ቢሯቸው በመገኘት ለመስጠት ቢሞክርም በአስገራሚ ሁኔታ ኦፊሰሩ ደብዳቤውን አልቀበልም ብለዋል፡፡
የኦፊሰሩ ድርጊት ህገ ወጥ መሆኑን የተገነዘበው ፓርቲያችን ደብዳቤውን ቢሯቸው ጠረጴዛ ላይ ትቶ ከመውጣቱም በላይ በሪኮማንዴ እንዲደርሳቸው አድርጓል፡፡ ኦፊሰሩ እየሰሩ የሚገኙት ነገር ህገ ወጥ መሆኑን እንዲገነዘቡም ለፌደራል ፖሊስ፣ለአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ በግልባጭ ደብዳቤው እንዲደርሳቸው መደረጉን የአንድነት የአዲስ አበባ ዋና ጸሐፊ አቶ ነብዩ ባዘዘው ተናግረዋል፡፡ በህገ ወጥ ደብዳቤ የሚሰረዝ ሰላማዊ የህዝብ ጥያቄ ባለመኖሩም ሰላማዊ ሰልፉ በተያዘለት ቀነ ገደብ እንደሚደረግ አቶ ነብዩ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ Finotenetsanet
Image

Image

ሺህ ዘመናት በኢትዮጵያዊነቱ የኖረውን የትግራይ ህዝብን፤ከተፈጠረ 40 አመት ያልሞላው ህወሐት እኔ ከሌለሁ ትጠፋላችሁ ይላል፡፡ የትግራይ ተወላጅ ሺህ ዘመናትን የኖረው በኢትዮጵያዊነቱ እንጂ በህወሐት አባልነቱ አይደለም፡፡ ዘረኝነት ባታራምዱ የተሻለ ነው የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላቶች የትግራይ ተወላጆች ሳይሆኑ / ሕወሓት/ ነው፡፤ ዋናው ትግላችንም ሕወሓትን ማስወገድ ነው። እናንተ የትግራይ ህዝብ ላይ አተኩራችሁ አቃቂር ስታወጡ ሕወሓት እናንተን እንደማስረጃ እየተቀሰ በትግራይ ውስጥ ጥላቻን እየዘራ ነው። ስለዚህ ዘር እየጠሩ ዘመቻ አያዛልቅም ለህዝቦች አንድነት እና ፍቅር ተባብረን ብንነሳ መልካም ነው።

በቅኝ አገዛዝ ታሪክ ብቻ ሳይሆን በአምባገነን ስር አት ውስጥም ባንዳዎች ይፈለፈላሉ ። ይህ የታወቀ ነገር ንው። ውዴታዊ ባንዳነት እንዳለ ሁሉ ግዴታዊ ባንዳነት ከዛ መላመድም እንዳለ ታሪክ ስናገላብጥ አንብበናል። ቢሆንም መልካም የህዝቦችን ታሪክ እየያዝን ለክፉው ታሪክ መቃብር እየማስን እየቀበርን በትግል ወደፊት በመገስገስ በኢትዮጵያ ላይ የተጫነውን የሕወሓት አምባገነናዊ ጁንታ መንግለን መጣል አለብን ።

እደግመዋለሁ !!! ሺህ ዘመናት በኢትዮጵያዊነቱ የኖረውን የትግራይ ህዝብን፤ከተፈጠረ 40 አመት ያልሞላው ህወሐት እኔ ከሌለሁ ትጠፋላችሁ ይላል፡፡ የትግራይ ተወላጅ ሺህ ዘመናትን የኖረው በኢትዮጵያዊነቱ እንጂ በህወሐት አባልነቱ አይደለም፡፡ ድርጅት ይወልዳል ያድጋል ይሞታል፣ህዝብ ግን ለዘላልም ይኖራል፡፡ ፍቅር ያሸንፋል!!!ምንሊክ ሳልሳዊ

ያኔ-ከ21ዱ የወታደራዊ ሁንታዉ አባላት ሁሉ ወጣት ነበሩ።ያን ሚስጥር-በመናገራቸዉ የካይሮ ሠልፈኞችን በቁጣ፤ የመብት በተለይም የሴቶች መብት ተሟጋቾችን በዉግዘት ከማንጫጫቱ ባለፍ፤ ድምፀ ለሥላሳዉ ወጣት ጄኔራል የሚፈልጉትን ለማደረግ-የፖለቲካዉን ትኩሳት የለኩበት መግለጫ መሆኑን ያሰበ-ያስተዋል አልነበረም።

‪በደሴ ከተማ የሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተባበር ወደ ስፍራው የተጓዙት የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ አቶ አዕምሮ አወቀ ድብደባና ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡ ዓርብ መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡15 ላይ በደሴ ከተማ በተለምዶ ቶታል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕራት በልተው ሲወጡ ታርጋ የሌለውና መስታወቱ ጥቁር በሆነ ኮብራ መኪና አጠገባቸው መጥቶ ሲቆም ከውጪ ሁለት ሰዎች […]

በርካታ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የርቀት ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በ2005 ዓም ትምህርታቸውን ቢጨርሱም፣ ጊዚያዊ ዲግሪያቸውን ፣ ማለትም የዲግሪያቸውን ቅጂ ባለማግኘታቸው በስራ ፍለጋ ጥረታቸው ላይ እክል እንደደቀነባቸው በምሬት ገልጸዋል።

የጀርመን የልማት ትብብር ሚንስትር ጌርድ ሚውለር ሰሞኑን ደቡብ ሱዳንን እና ማሊን ጎብኝተውዋል። ሚንስትሩ ወደ ሁለቱ ሀገራት የተጓዙት በቦታው በመገኘት በዚያ ስላለው የመሠረተ ልማት ግንባታ፣

የአንድነት ፓርቲ መጋቢት 28 ቀን ሰልፍ እንደሚያደርግ፣ ለአዲስ አበባ አስተዳደር መጋቢት 15 ቀን ያሳዉቃል። «የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ አሰራር ሥነ-ሥርዓት በርካታ ትምህርት ቤቶች ዩኒቨርሲና የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ የተጠየቀዉን የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን» ሲል አስተዳደሩ ከ48 ሰዓታት በኋላ መጋቢት 17 ቀን ምላሽ ይሰጣል። […]

ትናንት እሁድ መጋቢት 21, 2006 ዓም ዓረና ከእንደርታ ህዝብ ጋር ለመወያየት በኲሓ ከተማ ሐየሎም አዳራሽ ቀጠሮ መያዙ ይታወሳል። ለስብሰባው በስፒከር ለመቀስቀስ ሞክረን እንደተከለከልን፣ የአመራር አባሎቻችንም መታሰራቸው እንደዉጤቱም የቅስቀሳ ሂደቱ መተጓጎሉ ጠቅሼ ነበር። ሁኖም ግን የዓረና አማራጭ ሐሳብ የያዘ በራሪ ወረቀት ለኗሪዎች በማደል የተወሰነ ቅስቀሳ አድርገናል። ከሌሎች አከባቢዎች ለየት ባለ መልኩ በእንደርታ ወረዳ በስፒከር እንዳንቀሰቅስ የተፈለገበት […]

ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅሬታቸውን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች ገልጸዋል የቤተ ክርስቲያንን እንጀራ እየበሉና በጀቷን አውጥታ እያስተማረቻቸው የሌላ እምነት በሚያራምዱ የስም ደቀ መዛሙርት ላይ ርምጃ እንዲወሰድ ተጠየቀ (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፵፩፤ መጋቢት ፳ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የኾኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን እምነትና ሥርዐት እንዲማሩ፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን በማቀናጀት ሞያዊ ድጋፍ …

በሀገራችን የኑሮ ውድነት ከእለት እለት እየከፋ የድሃውን ህዝብ ጉስቁልና እያበዛ እንደሆነ ነጋሪ የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ በቤተ መንግሰትና አካባቢ የሚኖሩት ይህ ጉዳይ አይመለከታቸውም፡፡ ለዚህ የኑሮ ውድነት አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት የዋጋ ንረት መሆኑን ብዙዎች ይረዳሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ዛሬ ለፅሁፌ ዋና ማጠንጠኛም የማደርገው የዋጋ ንረት ምንስዔው ምን እንደሆነ በተለይ የመንግሰት ሚና ከዚህ አንፃር ምን እንደሆነ ማስረዳት ነው፡፡ […]

በዛሬው እለት በቦስተን በተደረገው “የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የውደሳ እና የምስጋና ቀን” በርካታ ኢትዮጵያውያኖች በተገኙበት በደማቅ እና እጅግ በተሳካ ሁኔታ ተክናውኗል። በዚሁ ዝግጀት ላይ የሕሊና እስረኛ አንዱአለም አራጌ የሕይወት ታሪክ እና በኢትዮጵያ ውስጥ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር በሚደረገው የሰላማዊ ትግል ያደረገውን አስተዋጻኦ በተመለከተ የተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም የቀርበ ሲሆን፤ በወጣት ማሙሽ እና በወ/ሮ ደብረወርቅ የተዘጋጁ ጽሁፍ እና […]

በወያኔ የከተማ ልማት፣ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የተዘጋጀ “በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ዲያፖራዎች የፕሮፋይል ሰነድ” የሚል 170 ገጾች ያለው ዝርዝር መረጃ እጃችን ገብቷል። በዚህ ሰነድ ውስጥ ስማቸው ከተዘረዘረው መካከል ለወያኔ በስለላና መረጃ በማቀበል ተግባር ላይ የተሰማሩ እንዳሉ አይጠረጠርም። ሰነዱን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። በዲያስፖራ …

በዲያስፖራ የሚኖሩ የወያኔ አገልጋዮች ስም ዝርዝር Read more »

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መብራት ውሃ የስልክና የኢንተርኔት ኔትወርክ አገልግሎቶች መብቶች የህዝብ ናቸው!!!!! አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው …ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው::እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው የሚላተሙ የጆተኒ ተቃዋሚ […]

የደቡብ ሱዳን ጦርነት አዲሲቱን ሐገር እያነደደ ደሐ ሕዝቧን እየፈጀ-በገፍ እያሰደደ ነዉ።ተፋላሚ ሐይላት በምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን ( ኢጋድ ) ሸምጋይነት የተኩስ አቁም ሥምምነት ቢፈራረሙም ሥምምነቱ ገቢራዊ አልሆነም።

የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችን ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው አይችልም።የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 ዜጎች ነፍጥ ሳይዙ የመሰባሰብ፣ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች የማድረግ፣ ፔትሽኖችን የማሰባሰብ ሙሉ መብት […]

(ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፴፱፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.) ተመስገን ደሳለኝ በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሺፈራው ተክለ ማርያም አዝማችነት በማኅበሩ ላይ የደቦ ዘመቻ ከተከፈተ ሰነባብቷል፡፡ በጥናት ስም በተከታታይ የሚወጡና በየመድረኩ የሚቀርቡ ወረቀቶች ማኅበሩን የኦርቶዶክስ አክራሪ ከማለት አሻግረው ‹‹የግንቦት ሰባት መንፈሳዊ ክንፍ/የግንቦት ሰባት ከበሮ መቺ/›› ሲሉ ይወነጅሉታል፡፡ የማኅበሩ አመራሮች እንዲኽ ዓይነቱን ውንጀላ በተመለከተ በተለያየ ጊዜ ከአቶ …

ኢህአዴግ የእምነት ተቋማትን በጥብቅ የሚቆጣጠርበት ህግ ሊያጸድቅ ነው።
ህጉ ጣጣ እንዳያመጣ የሰጉ ኢህአዴግን እየመከሩ ነው። ጎልጉል

ኢትዮጵያን ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ እየገዛ ያለው ኢህአዴግ የሃይማኖት ተቋማትንና ምዕመናኑን በጥብቅ የሚቆጣጠርበትን ህግ ለማጽደቅ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። የህጉ ረቂቅ የደረሳቸው ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ኢህአዴግን አበክረው እየመከሩና በሚያመጣው አጠቃላይ መዘዝ ዙሪያ እያስጠነቀቁ ነው።

ጎልጉል ከዲፕሎማት ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ኢህአዴግ በእምነት ተቋማት ላይ ቁጥጥሩን የሚያጠብቅበትንና ከሃይማኖት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውጭ መሰብሰብን፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግንና የተቃውሞ ድምጽ ማሰማትን የሚከለክል ህግ አዘጋጅቷል።

የዜናው ምንጮች ዝርዝር ህጉን ለጊዜው ይፋ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የሚደነገገውን አዲስ ህግ ጥሰዋል በሚል የሚከሰሱ ምዕመኖች እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ የሚያዝ አንቀጽ አለበት። አዲሱ ህግ ከሽብርተኞች ህግ ጋር የሚጣቀስ እንደሆነም የጠቆሙት ክፍሎች ኢህአዴግ “ከእምነት ነጻነት” ጥያቄ ጋር በተያያዘና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ውስጥ ውስጡን እየነደደ ያለው ችግር ስላስጨነቀው ይህንን ህግ ለማውጣት መገደዱን አስረድተዋል። በሌላ በኩልም እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የሙስሊሞች ጥያቄ ከዚያም ጋር ተከትሎ የተከሰተው ደም መፋሰስ ወደፊት ሊያመጣ በሚችለው ጉዳይ ላይ ኢህአዴግን በብርቱ አሳስቦታል፡፡

ኢህአዴግ ከቀን ወደ ቀን ቀውስ እየተደራረበት እንደሆነ የተረዳችው አሜሪካ በከፍተኛ ባለስልጣኖቿ አማካይነት ኢህአዴግን እየመከረች እንደሆነ ከዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከፖለቲካው ቀውስና በቀጠናው ካለው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አሜሪካ በተደጋጋሚ የህወሃትን ሰዎች በተናጠል እያነጋገረች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። ዲፕሎማቶቹ እንደሚሉት አሜሪካ መለስ “ከተሰዉ” በኋላ አገሪቱን ማን እየመራት እንደሆነ በቅጡ ለመረዳት በሚያስቸግር ሁኔታ የስልጣን መዛነፍና ደረጃን የጠበቀ የስልጣን ተዋረድ አለመኖሩም አሳስቧታል። ኢህአዴግ ለህልውናዬ ያሰጋኛል በሚል መንግሥታዊ ባልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች /መያዶች/ ላይ ያወጣውን አፋኝ ህግም ጠቅሰዋል። ዲፕሎማቶቹ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ወቅቱ አሁን እንዳልሆነ አመልክተዋል። ጎልጉል

የበደለ፣ የአገር ሀብት ያባከነ፣ ሕገ የረገጠ ግለሰብ ማጥፋቱ እየታወቀ ይቀጣል ወይስ አይቀጣም ለሚለው ጥያቄ ወሳኙ ማስረጃ መሆኑ እየቀረ ነው፡፡ የፖለቲካ ገጠመኝ ሆኗል፡፡ ይታሰራል የተባለው ሊሾም፣ ተጠያቂ ይሆናል የተባለው ጠያቂ የሚሆንበት ሁኔታ አለ፡፡

መልካም አስተዳደር በሕግና በመርህ ደረጃ መከበር አለበት ተብሎ የታወጀ፣ የተነገረ፣ የተለፈፈለት ነው፡፡ በተግባር ደግሞ አቤት ብዬ ሰሚ አገኛለሁ፣ ቅሬታ አቅርቤ ይፈታልኛል የሚል ዜጋ የለም!!!! በዚህ ዙሪያም ጉቦና ጥቅማ ጥቅም የበላይነት እየያዙ ነው፡፡ የአቅም ማነስ ችግር ትልቅ እንቅፋት ነው፡፡ ስብሰባዎችና ሥልጠናዎች የችግር መፍቻ መድረኮች መሆናቸው ቀርቶ መደበቂያ እየሆኑ ነው፡፡ ‹‹በስብሰባና በሥልጠና ምክንያት ኃላፊ የለም›› የሚል ማስታወቂያ መለጠፍ ነው የቀረው፡፡ ኃላፊ ቢሮው ገብቶ አቤቱታ አንብቦ ችግር መፍታት መርህና ግዴታው መሆኑ ቀርቶ የፖለቲካ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡

የሕግ የበላይነት እንዲኖር፣ ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ የፕሬስ ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን እንዲሆን የሚያደርጉ ሕገ መንግሥትና ሕጎች አሉን ????????? ከድህነት የሚያላቅቅ፣ መካከለኛ ገቢ ወዳላት አገር የሚያሸጋግር፣ የቤት፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የትራንስፖርት፣ ወዘተ ችግሮችን የሚፈታ ዕቅድም አለን ???????????

እነዚህ አሉ ማለት ግን ዲሞክራሲ ተረጋገጠ፣ ልማት እውን ሆነ ማለት አይደለም፡፡ በመርህ ደረጃ ተግባር ላይ ካዋልናቸው ይጠቅማሉ፡፡ ካላከበርናቸው፣ ከረገጥናቸውና ከጣልናቸው ደግሞ ገጠመኝ ይሆናሉ፡፡ ፍትሕ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡ምንሊክሳልሳዊ የፍትሕ መጓደል በሚያሳስብ ሁኔታ እየታየ ነው፡፡ በፍትሕ አካላት ውስጥ በአቅምና በአመለካከት ድክመት አለ፡፡ የሥነ ምግባር ጉድለት በትልቁ እየታየ ነው፡፡ በጠበቆች፣ በዳኞችና በዓቃቢያነ ሕግ በኩል አሳሳቢ የሥነ ምግባርና የአቅም ችግር እየተስተዋለ ነው፡፡

በአጠቃላይ የፍትሕ አካላት መጠናከር እያሳዩ ከመጓዝ ይልቅ እየተልፈሰፈሱና እየተንገዳገዱ ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ፍትሕ ማግኘት መርህ መሆኑ ቀርቶ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡ ጉቦ የአንቀጾች ሁሉ የበላይ አንቀጽ እየሆነ መጥቷል፡፡ሰላማችን፣ ሉዓላዊነታችን፣ አንድነታችንና ህልውናችን በመርህ ደረጃ ዋስትና ያላቸው መሆናቸው ቀርቶ የፖለቲካ ገጠመኝ ሆነዋል፡፡ የአገር እና የህዝብ ህልውና ገጠመኝ በመሆኑ ወያነ ደግሞ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በጋራ የዛፍ ላይ እንቅልፉን የሚለጥጠውን ወያነን በማውረድ ህዝባዊ የበላይነትን መቀናጀት የዜግነት ግደታችንን መወጣት አለብን::ምንሊክሳልሳዊ

መብራት ውሃ የስልክና የኢንተርኔት ኔትወርክ አገልግሎቶች መብቶች የህዝብ ናቸው!!!!!
ምንሊክ ሳልሳዊ

Image

አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው …ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው::እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው የሚላተሙ የጆተኒ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በላም አለኝ ተስፋ ህዝባችንን አረንቋ ውስጥ እየጨመሩት ነው::

ለጋች አገራት የሚያወጧቸው ሃሰተኛ ጸረ አፍሪካ ሪፖርቶች በተለይ የምስራቅ አፍሪካን ተገን አድርጎ የተመቻቸው የብሄራዊ ጥቅማቸው ፎርሙላ ስኬት የአምባገነኖችን እድሜ በማስረዘም ህዝብ እንዲጭበረበር የህዝብ ጥያቄዎች እንዲደናቀፉ ለገዢዎቻችን የልብ ልብ ሰቷቸዋል:: ለብሄራዊ ጥቅም አስጊ ይሆናሉ የተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን እስከማጨማደድ እየዘለቀ በኢጅ አዙህ ህዝባዊ ጥያቄዎች እንዲታፈኑ እየተደረገ አምባገነናዊ አገዛዝን አፍልተውብናል እንሱ ለጋሽ አገራት::

መሰረታዊ ፍላጎቶች እና የአገልግሎት ፍጆታችን በበቂ ሁኔታ ባልተሟላበት አገር መንግስት ፕሮጀክት ለመጨረስ የገንዘብ እጥረት ገጠመኝ በሚልበት አገር ብሄራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሬ የለኝም በሚልበት እና የመንግስት ካዝና ባዶ ሆኖ በዕቃ ግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ ከቱጃሮች መንግስት በሚበደርባት አገር ጥቂት ፖለቲካው የወለዳቸው ሃብታሞች እጅግ ብዙ የኢኮኖሚ ድቀት ያፈራቸው ደሃዎች በፈሉበት አገር ምን አይነት የኢኮኖሚ እድገት እንደተመዘገበ አነጋጋሪ ነው:; እስከመቼ የአምባገነኖችን ደጋፊዎች ዉሸት ተሸክመን እንዘልቃለን::

መብራት ውሃ ስልክ ሀገሪቷ ተሰርቶ እና ተበድራ ሳይሆን በተፈጥሮ የታደለችው ጸጋዋ እንደሆነም ያለን ሃብት ይመሰክራል ህዝቡ ያለውን ቴክኖሎጂ ከተፈጥሮ ሃብቱ ጋር አደባልቆ እንዳይጠቀም እኛ እናውቅላቹዋለን የሚሉ የወያኔ አውሬዎች ቀፍድደው ይዘውታል::
በቀላል ሊፈታ የሚችል ችግርን በፖለቲካዋ ሳንካ መተብተብ ምንም የሚጠቅም ስላልሆነ ህዝቡ አስፈላጊውን የአገልግሎቶች አቅርቦት እንዲያገኝ መደረግ አለበት ብለን ካሁን በፊት ብንጮህም ከቀድሞ በባሰ መልኩ ብሶበት ይገኛል::

በአለማችን በረሃ በተባሉት አገሮች የውሃ አቅርቦት በሰፊው ለህዝባቸው እየሰጡ ሲሆን የተጣሩ ውሃዎች ሳይቀር በርካሽ ዋጋ እየተሸጡ ነው::በኢትዮጵያችን ግን በተፈጥሮ የታደልነውን ውሃ በፖለቲካ ሹማምንት ልፍስፍስነት ልንጠቀምበት አልቻልንም ትልልቅ እና ገባር እንዲሁም ትንንሽ ወንዞች እና የተፈጥሮ ውሃ ምንጮች በሞሉባት ሃገራችን ህዝብ ውሃ ተጠማሁ ሲል መመልከት አስደንጋጭ ነው::ሃገሪቱ በውሃ ችግር ተውጣልች::የውሃ እጥረት ኖሮን ሳይሆን በአግባቡ አለመጠቀም እና ችግሩን የመፍታት ባህል ስላሌለን ነው::ለጎረቤት አገሮች ውሃ እንሰጣለን እየተባለ ባለበት የፕሮፓጋንዳ ጡዘት ውስጥ እኛ በጥማት ማለቃችን አሳፋሪ ነው::

ወድ መብራት ስንመጣ ደሞ መንግስት ያለ እንኳን ተደርጎ ማሰብ ይከብዳል:: የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ መብራት ጠፍቶ ሲመጣ መብራት መጣ ብሎ መጮህ ነው ተብሎ በሰው ሃገር ጋዜጦች እስኪቀለድብን ድረስ ወያኔ በህዝብ ጭንቅላት ጢባጢቦ እየተጫወተች ነው::ይህ እንደገጠመኝ እና እድል የሚታየው የመብራት እቃቃ ጨዋታ በአግባቡ መፍታት እየተቻለ ችግሩንም ማድረቅ እየተቻለ ለምን መዘናጋት እንደሚፈጠር ማስረዳት የሚችል ባለስልጣን አልተገኘም::በኤሌክትሪክ መጥፋትና ሥርዓት አልበኝነት ምክንያት በርካታ ኢንዱስትሪዎች ሥራቸውን እያቆሙ ናቸው፡፡ በርካታ ማሽኖች ከጥቅም ውጭ እየሆኑ ናቸው፡፡ በመኖሪያ ቤቶች ቴሌቪዥኖች፣ ፍሪጆችና ሌሎች የኤሌክትሪክ ዕቃዎች እየፈነዱና እየተቃጠሉ ነው፡፡ በመብራት መጥፋት ምክንያትም የየዕለቱ ኑሮ ይዘቱም ገጽታውም እየተበላሸ ነው፡፡ ከመኖሪያ ቤቶች አልፎ ካፌዎችም በመብራት መጥፋት ምክንያት ‹‹ተረኛ መድኃኒት ቤት›› እየመሰሉ ነው፡፡ ሻይ ታዞ ‹‹ይቅርታ መብራት የለም›› የሚል መልስ መስማት የተለመደ እየሆነ ነው፡፡ እውነት ኢትዮጵያ ለዜጎቿ፣ ለኢንዱስትሪዎቿም ሆነ ለሁሉም ዓይነት እንቅስቃሴዎቿ የሚሆን በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የላትም? አይኖራትም? አላትም ይኖራታልም፡፡ በቂ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች የንፋስ የኃይል ማመንጫዎች የፀሐይ የኃይል ማመንጫ አቅም የጂኦ ተርማል የኃይል ማመንጫ አቅምም አለ፡፡ እንኳን ለራስዋ ለሌሎች አገሮችም የሚሆን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ዕምቅ ሀብት አላት፡፡ ኦኖም ግን በአግባቡ የሚያዳርስ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች አጣብቂኝ ውስጥ ስለከተቷት ህዝቧ አስፈላጊውን የአገልግሎት መብቶች እና አቅርቦቶች ሊያገኝ አልቻለም::በሃይል ግንባታ ሰበብ በህዝብ ላይ መንግስታዊ አሻጥር እየተፈፀመ ነው::ምንሊክ ሳልሳዊ

ወደ ስልክ እና ኢንተርኔት ኔትወርክ ስንመጣ በጸሎች የሚገኝ ያውም ተለቅሶ መፍትሄም የጠፋለት ጉዳይ ከሆነ ቆይቷል:: በአለማችን በስፋት ይህን የኔትዎርክ ችግር ተቀርፎ ባለበት ሰአት የወያኔ ባለስልጣናት ግን በአደናባሪዎቻቸው በኩል በፋይበር ቅንጠሳ እና በህንጻ መብዛት ቢያሳስቡም ከነሱ ቀድሞ ንቃተ ህሊናው ያደገውን ህዝብ ግን ሊሸውዱት አልቻሉም:: ያው እንደለመዱት በጠበንጃ እና ሽብር በመንዛት ዝም አሰኝተውታል:: የወያኔ መንግስት የህዝብን የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች መፍታት እየቻለ እንዳይፈቱ በማድረግ በሚፈጸም አሻጥር እራሱ አጣብቂኝ ውስጥ እንደገባ ሊገነዘበው አልደፈረም:: የመልካም አስተዳደር ብልሃት የሞላበት አመራር ህግ አክባሪ እና አስከባሪ ባለስልጣንትን ለማግኘት ሁላችንም በትግሉ ላይ እንረባረብ።ምንሊክ ሳልሳዊ

March 29, 2014 የጎሠኛነት አጭር ትርጉም ዓለምን በራሱ ጠባብ ኢምንትነት የሚለካ ሰው ነው፤ ለኪው መለኪያው ነው፤ መለኪያውም ለኪው ነው፤ ጎሠኛነት የዘረኛነት የባሕርይ ልጅ ነው፤ ዘረኛነትም ሆነ ጎሠኛነት መሠረታቸው ድንቁርና ነው፤ የድንቁርናው ዓይነተኛ መገለጫ ‹‹ንጹሕ›› የሚለው ቃል ነው፤ ለዚህ ዋና ምስክር አድርጌ የማቀርበው አዶልፍ ሂትለርን ነው፤ ስለ‹‹አርያን ዘር›› ማንነትና ‹‹ንጹሕነት›› የሂትለር Mien Kampf የሚለውን መጽሐፍ ነው፤ […]

ጽሁፉን በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። በጥላሁን ገሰሰ ስም እየነገደ ያለው ሰው በዲሲና አካባቢዋ በወያኔ ስውር ተልዕኮ ተሰጥቶት እያወናበደ ስለሚገኘው መስፍን በዙ ስለተባለው ግለሰብ ከዓመት ገደማ በፊት በተለያዩ ድረገጾች  “በጥላሁን ገሰሰ ስም እየነገደ ያለው ሰው ምነው ተው ባይ አጣ?” በሚል ርዕስ የተለቀቀው …

በጥላሁን ገሰሰ ስም እየነገደ ያለው ሰው ምነው ተው ባይ አጣ? Read more »

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በፕሬዚደንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት የሚመራው የመንግሥቱ ጦር እና የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት ሪየክ ማቸርን በሚደግፉት ታጣቂ ኃይላት መካከል በሚካሄደው ውጊያ ሰበብ ሀገሪቱ ለምትገኝበት ውዝግብ መፍትሔ ለማፈላለግ የተጀመረው ጥረት ችግር እንደገጠመው ይገኛል።

አምስት የአንድነት ፓርቲ አባላት ታስረዋል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መጋቢት 20 ቀን 2006 ዓ.ም. March 29, 2014)፦ ዛሬ ገዥው ፓርቲ በጎንደር ከተማ አደባባይ እየሱስ በጠራው ስብሰባ ለእያንዳንዳቸው ተሰብሳቢዎች 8ሺህ ብር ብድር በመስጠት መጭውን ምርጫ ግን ኢህአዲግን እንዲመርጡ በመቀስቀስ ላይ ባለበት ወቅት ምርጫን በገንዘብ መግዛት አይቻልም ብለው ጥያቄ ያቀረቡ አምስት የአንድነት ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን አቶ ሃብታሙ አያሌው ዛሬ ይፋ አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሁሉንም ተቃዋሚ እንደአንድ መመልከትም ሆነ በአንድ አዕምሮ እንዲያስብ መጠበቅ የገዢው፣ የተገዢዎች፣ የተቃዋሚዎች ሁሉ የጋራ ችግር ነው። ሚሊዮን ችግሮች እና ሚሊዮን ተቃዋሚዎች ባሉበት አገር ውስጥ ተቃዋሚዎች ሁሉ አንድ ዓይነት ሊሆኑ አይችሉም። ይሁን እንጂ ሁሉም ተቃዋሚዎች ልዩነታቸውን በቅጡ ያውቃሉ ብሎ ለማለትም ያስቸግራል፤ ምክንያቱም “በስመ ተቃዋሚ ሲሳሳሙ” ማየት የተለመደ ነው። ተቃዋሚዎችን በተቃውሞ አካሔዳቸው መግባባት ላይ መድረስ እንዲያቅታቸው ከሚያደርጋቸው ችግር አንዱ ኢሕአዴግን የሚበይኑበት (define የሚያደርጉበት) መንገድ መለያየቱ ወይም ግልጽነት ማጣቱ መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው።

ብያኔ ለምን ያስፈልጋል?

40 ዓመት ወደኋላ መለስ ብለን የአብዮቱን ልጆች ለመከፋፈል እና ለእርስበርስ እልቂት የዳረጋቸው ዋነኛውን፣ የሚታገሉትን አካል (ደርግን) የበየኑበት መንገድ ነው። የኢሕአፓ እና የመኢሶን ዋነኛ ልዩነት፣ የኢሕአፓና አንጃ እያለ የሚጠራቸው አባላቱ መካከል የተከሰተው የሐሳብ መሰነጣጠቅ፣ ብሎም እርስበርስ መጨራረስ ደርግን የሚበይኑበት መንገድ መለያየትን ተከትሎ የተወለደው ደርግን ለማስወገድ የመረጡት መንገድ ነው። ሁለቱ (የተቀናቃኝ ወገን ብያኔ እና የመቀናቀኛ መንገድ ምርጫ) ተሰናስለው የሚኖሩ ጉዳዮች ናቸው። በጥንቃቄ ሳይጤን የሚገበቡበት ገደል አይደለም።

ኢሕአዴግ፣ በዚህ ረገድ ራሱን ግልጽ የማድረግ ችግር የለበትም። ተቀናቃኞቹን አንዱን አሸባሪ፣ አንዱን የአሸባሪ ደጋፊ፣ ሌላውን ለዘብተኛ እያለ የሚኮረኩምበትን መንገድ አስቀምጧል። ኢሕአዴግ መሣሪያ ታጣቂ እንደመሆኑ ተቀናቃኞቹን ባይበይናቸውም ቅሉ ማሽመድመጃ መንገድ አይቸግረውም። ለተቃዋሚዎች ግን ‘ኢሕአዴግ ምንድን ነው?’ የሚለውን ጥያቄ መመለስ የሕልውና ጉዳይ ብቻም ሳይሆን ወዴት እና እንዴት እየሄደ እንደሆነ የሚያውቁበት ወሳኝ ጥያቄ ነው።

የበኩር ጥያቄ፤ ኢሕአዴግ ምን ያስባል?

ኢሕአዴግ እንደማንኛውም ገዢ ፓርቲ በፖለቲካዊ ብልጫ ሥልጣን ላይ የቆየ ፓርቲ ነው? በኃይል ሥልጣን ተቆጣጥሮ የሚኖር ፓርቲ ነው? እያጭበረበረ የሚኖር ፓርቲ ነው? በኃይል ሥልጣን ተቆጣጥሮ ሕጋዊ ዕውቅና አግኝቶ በሕጋዊ መንገድ ሥልጣን ላይ የቆየ ፓርቲ ነው? ሕዝባዊ ይሁንታ ባገኘ መንገድ ሥልጣን ላይ ከወጣ በኋላ ኃይሉን መከታ በማድረግ ሥልጣኑን ያለመጋራት የተቆጣጠረ ፓርቲ ነው? በኃይል ሥልጣን ተቆጣጥሮ በኃይል ሥልጣኑን እያስጠበቀ ያለ ፓርቲ ነው? ወይስ ምንድን ነው?…ብዙ ዓይነት ትርጉሞች (ሁሉም እውነት ያላቸውን) ማስቀመጥ ይቻላል። የራስንና አንድ ወጥ ትርጉም ማስቀመጥ የሚበጀው የሚከተሉትን የትግል ስልት ለማወቅ እና የሚጠብቁትንም (what to expect) ለማወቅ ነው።

በአማራጭ ፓርቲዎች መካከል እና ለዴሞክራሲያዊነት  በሚደረጉ ነጻ (የአራማጆች እና የሲቪል ማኅበረሰብ) ትግሎች ምን ዓይነት መሆን አለባቸው የሚለውን መወሰን የሚቻለው የሚታገሉለትን ነገር በማወቅ (ለምሳሌ ለዴሞክራሲ በዴሞክራሲያዊ መንገድ) ከሚለው በተጨማሪ ተቀናቃኝ አካላትን በሚገባ በማወቅና በመበየንም ጭምር ነው። የኢሕአዴግን ማንነትም በቅጡ መበየን የሚያስፈልገው አላስፈላጊ ጊዜ፣ ገንዘብና ጥረት ላለማባከን እና የጠበቁትን ውጤት ለማግኘት ነው።

‘ኢሕአዴግ ሥልጣኑን በኃይል ተቆጣጥሮ በኃይል እያስጠበቀ ያለ ድርጅት ነው’ ብለን ካልን ሠላማዊ ትግል የሚባለው ሁሉ ትርጉም ላይኖረው ይችላል። ግን ይህንን ለማለት የሚያስችል በቂ መረጃ አለ ወይ? ኢሕአዴግ ብረት ታጣቂውን ደርግ ለመገርሰስ ከኃይል ውጪ አማራጭ ነበረው? የሥልጣን ባለቤት ከሆነ በኋላ ሥልጣኑን ያላስረከበው በፓርቲው እምቢተኝነት [ብቻ] ነው ወይስ የተቀናቃኞቹም እጅ (ድክመት) አለበት? ኢሕአዴግን ከኃይል መለስ ባለ ነገር ከሥልጣን ለማውረድ የሚያስችሉት በሮች ሁሉ ተዘግተዋል? ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አባላት ያሉትን ፓርቲ ‘ጠላት’ ብሎ ለመፈረጅ የሚያስችል ሁኔታ አለ? ይህ መሰሉ ድምዳሜ እና ፍረጃ በታሪክ ከተሠሩ ስህተቶች አንፃር ምን ያክል የተማረ/የታረመ ነው?

‘ኢሕአዴግ በኃይል ያገኘውን ሥልጣን በሕዝባዊ ይሁንታ (እንበል ምርጫ) ቀጥሎበታል’ ካልን ደግሞ ለስርዓት ለውጥ የሚደረጉ ትግሎች ፍፁም ሠላማዊና ግልጽ መሆን ይኖርባቸዋል ማለት ነው። ይህም እልፍ ጥያቄዎችን ይወልዳል። ኢትዮጵያ ውስጥ በምርጫ እውን የሥልጣን ርክክብ ማድረግ ይቻላል? ከምርጫ ውጪ የሥልጣን ሽግግር የሚመጣባቸው ሌሎች መንገዶች አሉ? ኢሕአዴግ ሕዝባዊ ይሁንታ ካለው ትግሉ (ለውጡ) ለምንድን ነው? በሠላማዊ መንገድ የሚመጣው ለውጥ ምን ዓይነት ነው?… ወዘተ።

እነዚህን ሁለት ጥያቄዎች እንደምሳሌነት ብንወስድም፣ ሌሎችም ጥያቄዎች በተለያዩ ብያኔዎች ላይ ተመሥርቶ ማውጣት ይቻላል። በምሳሌው ውስጥ የተካተቱትን ሁለት ብያኔዎች ተንተርሶም፥ ሁለቱን ብያኔዎች የሚሰጡ አካላት አብረው ሊሠሩባቸው የሚችሏቸው እና የማይችሏቸውን ጉዳዮች አብጠርጥሮ ማውጣትም ያስፈልጋል እንጂ በብያኔ ተለያይተናልና አብረን የምንሠራበት መንገድ የለም ማለት ላይሆን ይችላል። ይህን ባለማወቅ የሚደረግ ትግል ግን መነሻውንም፣ መድረሻውንም የማያውቅ ተራ ጥላቻ የሚመራው ጉዞ ነው።

መበየን ቀላልም፣ ከባድም፤ ትንሽም፣ ብዙም ነው

ኢሕአዴግን የተለያዩ አካላት የተለያየ ብያኔ ይሰጡታል። ኢሕአዴግ ኢትዮጵያዊ (ብሔራዊ) ስሜት የለውም ከሚሉት ጀምሮ ለኢትዮጵያ የመጨረሻው የመድኅን ስጦታ ነው እስከሚሉት ጽንፎች ድረስ የሚደርስ ብያኔዎች አሉት።

እኔ በግሌ ኢሕአዴግ በተለያዩ ሒደቶች ውስጥ የተለያየ ምልከታዎችን በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ እያጎለበተ የመጣ ቡድን ነው ብዬ አምናለሁ። ፕሮፌሰር ክላፋም እንዳሉት፥ ‘ሕወሓት በብሔር ዓይን ኢትዮጵያን እየተመለከተ መጥቶ ገዢ ሆነ፤ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ደግሞ ኢትዮጵያን ወክሎ (በኢትዮጵያዊ ዓይን) ኤርትራን ጦርነት ገጠመ፤ ይህም ሁለተኛ ዕይታ ሰጠው’። ምናልባት እዚህ’ጋ መጨመር ቢያስፈልግ ሕወሓት (የጠቅላላው ኢሕአዴግ ዕጣ ፈንታ ወሳኝ እንደመሆኑ) ከምርጫ 97 በኋላ ኢትዮጵያዊ (ኅብረብሔራዊ) ስሜት ማዳበር ባይችል እንኳን ያለሱ ብዙ እርምጃ መጓዝ እንደማይችል ተረድቷል። ስለዚህ ኢሕአዴግ በሦስት ደረጃዎች ውስጥ አልፎ እዚህ ደርሷል ባይ ነኝ፤ ሁሉንም ነገር በዘውግ-ብሔር ዓይን የሚመለከትበትና የሚተረጉምበት ደረጃ (አንድ)፣ ኢትዮጵያዊ ኅብረብሔርተኝነትን ለአጀንዳ ማስፈፀሚያነት (ለምሳሌ ለጦር መቀስቀሻነት) የሚያውልበት ደረጃ (ሁለት)፣ እና ያለኢትዮጵያዊ ኅብረብሔራዊ ስሜት እና መሰል እርምጃዎች (ምሳሌ የባንዲራ ቀን) መራመድ እንደማይችል የተረዳበት ደረጃ (ሦስት) ናቸው። ይሁን እንጂ የዘውግብሔርተኝነትን እና ሕብረብሔርተኝነትን ሚዛን የሚያስጠብቅበት ግልጽ አካሔድ የለውም፤ ይልቁንም እንደ ሕዝባዊው ስሜት አነፋፈስ ተስማምቶ ለመንፈስ ብቻ እየተፍጨረጨረ ነው።

ኢሕአዴግን ከላይ ልበይነው የሞከርኩት በኢተዮጵያዊነት ስሜቱ ነው። በተመሳሳይ መንገድ ሥልጣን ላይ ያለውን አመለካከትም በአካሔዱ ለመተርጎም ብሞክርም በርግጠኝነት ልበይነው አልቻልኩም። ኢሕአዴግ ከስኒ ማዕበል በላይ አቅም የሌላቸውን ተቃዋሚዎች ይቀበላል። ከዚያ በላይ ያሉትን ግን በቀና ልቦና እንደሚቀበል አላሳየም፤ ሆኖም በሙሉ አቅም ተፈትኗል ማለትም አይቻልም። የደኅንነት፣ የኮሙኒኬሽን እና የመከላከያውን ቁልፍ ሚናዎች በሕወሓት ቁጥጥር ስር እንዲውሉ እንዲሁም ኢኮኖሚው በመንግሥት ከፍተኛ ቁጥጥር ስር ማድረጉም ሥልጣኑን በሠላማዊ መንገድ ለመልቀቅ ያለውን ዝግጁነት አጠራጣሪ ያደርገዋል። ይሁን እንጂ እስከመጨረሻው ድረስ ተገፍቶ ያልተሞከረ በመሆኑ ለሠላማዊ ትግል በር ተዘግቷል ሊባል በማይቻል መወላወል ውስጥ አስቁሞናል።

ብያኔ ቸኩለው የሚገቡበት ጉዳይ አይደለም። ርዕሱን ከብዙ ገጾች ማየት ያስፈልጋል። ነገር ግን ያለብያኔ ቋሚ አቅጣጫ መያዝ አይቻልም፤ ባይሆን ብያኔንም አቅጣጫንም በየጊዜው መከለስ ያዋጣል።

እውነቱን ለመናገር በኢትዮጵያ ፖለቲካ ምክንያት እንደሰሞኑን በግኜ የማውቅ ኣይመስለኝም። ኣቤት ክህደታችን! እንዴት ተክነንበታልሳ ወገኖች! ረጋ ብላችሁ በጥሞና ኣንድታነቡኝ ብርታቱን ይስጣችሁ፥ 1• በዛሬይቱ ኢትዮጵያችን ነባራዊ ሁኔታ ብሄር ማለት ምን ማለት እንደሆነ በትክክል የሚነግራችሁ ሰው ኣታገኙም። የብሄር ፖለቲካ ኣቀንቃኞቹ ራሳቸው የሚግባቡበት ወጥ የሆነ የብሄር ትርጉም እንኳን የላቸውም። ብሄር ለኣንዳንዱ በቋንቋ ነው የሚገለፀው፤ ለሌላው በዘርና ትውልድ ሃረግ ነው […]

ሥርዐቱ በተለይም መንግሥታዊ ሥልጣናቸውን ለሃይማኖታዊ ተልእኮ የሚጠቀሙ ሓላፊዎችና አማሳኝ የደኅንነት ግለሰቦች አሁን በተያዘው መንገድ ቀጥለው ማኅበረ ቅዱሳንን አላግባብ ወደ መገዳደር ብሎም ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አማሳኝ ግለሰብ ሓላፊዎች ጋራ ተባብረው ወደ ማፍረስ የሚሸጋገሩ ከኾነ ያለምንም ጥርጥር የተቃውሞው ጎራ ይጠናከራል፡፡ ይህም አገሪቱን በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ የአውራ ፓርቲ ሥርዐት ለአርባና ኃምሳ ዓመታት እመራለው ለሚለው ገዥው ፓርቲ ግብዓተ መሬት አፋጣኝ …


(ደጀ ሰላም፣ መጋቢት 20/2006 ዓ.ም፤ ማርች 29/2014/ PDF)፦ ሥርዓተ ቅዳሴውን ለመምራት  ተሰይመው ለተመለከታቸው ከረጅሙ ነጭ ጽህማቸው  ጋር ውብ  የሆነውን  መረዋ  ድምጽ ሲሰማ ምድራዊ  ሳይሆን  ከሰማይ የተገለጠ መልአክ ይመስሉ ነበር፡፡ ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተለየ ፍቅር ስለነበራቸው በተጋበዙበት መድረክ ሁሉ አክብረው በሰዓቱ ይገኛሉ፡፡ ለማስተማር ከተነሱም በትርጋሜ  የተዋዛ  ምስር አዘል ትምህርታቸውን ለምእመናን ቀምመው ያቀርባሉ፡፡ ለሃይማኖት ያላቸውን ቀናዊነት ለመረዳት በትምህርታቸው መግቢያ  የሚናገሩትን  መልእክት መስማት ብቻ በቂ ነው፡፡ ይህ የመግቢያ መልእክታቸው ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ልተበረዘች ያልተከለሰች  መሆን የሚስረዱበት በተለያዩ ዘመናት የተነሱባትን መናፍቃን በመጥቀስ እነዚህ ሁሉ ያልበረዛት ያልከለሳት መሆናን የሚገልጹበት ነው፡፡ እናም በጥዑም አንደበታቸው ስለቤተ ክርስቲያን ሲናገሩ ለሰማቸው  የሊቃውንቱ ዘመን የእነ እትናቴዎስ ዘመን የሃይማኖት ቅናት በውስጣቸው እንዳለ ይረዳል፡፡ ብፁዕ አቡነ ቶማስ፡፡

በደብረ ሊባኖስ ገዳም መጻሕፍተ ሊቃውንትን ረዘም ላለ ጊዜ  በማስተማር  ቆይተው ነው  ወደ አዲስ አበባ የተዛወሩት፡፡ በገዳሙ ውስጥ ሲኖሩ የነበራቸውን መንፈሳዊ ሕይወት እና አንድምታውን የማስተማር ብቃት በወቅቱ የነበሩ አባቶች የሚመሰክሩት በታላቅ አድናቆት ነው፡፡ ሊቅነትን  ከመንፈሳዊነት   ጋር ይዘው በመገኘታቸውም ቤተ ክርስቲያን ለበለጠው አላፊነት አጭታ ለጵጵስና ማዕረግ በቅተዋል፡፡ መናፍቃንን  በተመለከተ ግልጽ የሆነ ቀጥ  ያለ አቃም ነበራቸው፡፡ፀረ  ማርያም  የሆነን  የተሐድሶ ጭፍራ መታገሥ አይችሉም፡፡ በቅዱስ ውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የነበረውን የተሐድሶ እንቅስቃሴ ሥሩን ነቅለው የጣሉበት የዲንነት ዘመናቸው ለዚህ ምስክር ነው፡፡ እንደእነ ቅዱስ ቄርሎስ የመናፍቃን መቀጥቀጫ መዶሻ ነበሩ፡፡ ላ ይህ ቀናነታቸው እና  አድርባይ ሊሆኑ ያለመቻላቸው ጉዳይ  በቤተ ክህነቱ ውስጥ በተሰገሰጉ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ስላልተወደደላቸው እንዲጠሉና እንዲገለሉ አድርቸዋል፡፡ ፓትርያክ አቡነ ጳውሎስ  ምርጥ ምርጡን ለወዳጆቼ በሚሉበት እንዳሻቸው ሃገረ ስብከት በሚያድሉበትም ዘመን አቃማቸውን ብዙም ስሎማይወዱላቸው ጠረፋማ ሥፍራዎች  ላይ እንዲመደቡ ሆነዋል፡፡ለነገሩ ብፁዕ አቡነ ቶማስ ስለሚመደቡበት ሃገረ ስብከት ብዙም የሚጨነቁ  ስላልሆኑ ወደተላኩበት ሁሉ በደስታ  ይሄዳሉ፡፡ ፍሬም ያፈራሉ፡ቤተ ክርስቲያን የሰው ያለህ በምትልበት በዚህ ወቅት እንዲህ ያለ አባት ማጣት ትልቅ ሀዘን ነው፡፡ ብፁዕነታቸው ወደ አገለገሉት አምልክ በክብር ቢሄዱም እኛ ግን በትልቁ ተጎድተናል፡፡
ወቅቱ በአጠገባችን ያሉ ጥቂት መንፈሳዊ አባቶችን በስስት የምንመለከትብት ነው፡፡አይቴ ሀለ ቀደምት ጳጳሳት የቀደሙ አባቶች ደጋጎቹ ሊቃነ ጳጳሳት ወዴት አሉ?” እያልን ዘመን ገድባቸው የተለዩንን በሀዘንና በቁጭት የምናስታውስበት ነው፡፡ በግል ቂምና በቀል ተ ክርስቲያንን ለመናፍቃን አሳልፈው የማይሰጡ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን የሚገባቸውን መከራ ሁሉ በጥብዓት የሚቀበሉ፣ ከአላውያን ነገሥታት እምነት የለሽ መንግሥታት ጋር የማይዛመዱ፣ በፍልስፍናና በምድራዊ ተድላ ተይዘው  በእምነት ጉዳይ  ቸልተኛ ያሆኑ፣ መስሎ ለማደር ሲሉ ከቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ጋር የማይተባበሩበሚያልፍ ጊዜ የማያልፍ የታሪክ ጠባሳ ለትውልዱ ላለመተው የሚጠነቀቁእኔ ካልተነካ ሕዝቡም ሆነ አገልጋዩ ያሻውን መከራ ቢቀበል ምን አግብቶኝ ሲሉ የማይገኙ አባቶችን ተጠምተናል፡፡
እንደ ሙሴ ሕዝብህ ከሚጠፋ እኔን ከይወት መጽሐፍ ደምስስ የሚሉ፣ እንደ ነ  ኤልያስ  ስለ እግዚብሔር ክብር የሚቀኑ፣ እንደ ነዩ ዳዊት የተቀመጡበት ዙፋን የሚኖሩት የተድላ ኑሮ የተነሱበትን የማያዘናጋቸውበመንፈስ ቅዱስ ፀጋ ላፊያትና መጻዕያትን የሚረዱ፣ ሳይነገራቸው የመናፍቃንና የአላውያን ነገሥታት የጥፋት አካሄድ የሚገባቸው፡፡ እንደ ነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔር በክብሩ ዙፋን ተቀምጦ የሚታያቸው፣ ከምድራዊ ነገሥታት ከመዘመድ ይልቅ አደራውን ለሰጣቸው ለሰማዩ  ንጉሥ  መታዘዝ እንደሚበልጥ የሚረዱ፡፡ እንደ ሐዋርያት እስከ ሞት የሚታመኑ፡፡ እንደ ሊቃውንት መናፍቃንን የሚገስጹ አልመለስ ያሉትንም የሚያወግዙ አባቶችን ተጠምተናል፡፡
የቤተ ክርስቲያን አምክ ነገን እንደ አትናቴዎስ ያለ አትናቴዎስ፣ አባ ጊርጊስ ዘጋስጫን የሚተካ ሌላ አባ ጊርጊስ  እንዲተካ አጥብቀን  እንለምነው፡፡ ለእርሱ ምን ይሳነዋል? ይህ ሁሉ ወጀብ አልፎ ደግ ዘመን ያመጣልን ይሆናል፡፡ ለሁሉም በሕይወት ያሉትን  ለተዋሕዶ ጠበቃና አርበኛ የሆኑ አባቶች ድሜ ያርዝምልን፡፡ ያረፉትን አባቶች በረከትም በያለንበት ያድለን፡፡ አሜን፡፡                                                                                                                        ቸር ወሬ ያሰማን፤ አሜን።  ቸር ወሬ ያሰማን።
Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

በቅ/ሲኖዶሱ በይፋ ከተወገዙና በኑፋቄ አራማጅነት ከሚጠረጠሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ጋራ ግንኙነት ያላቸውና በኅቡእ በሚንቀሳቀሱ ጥቂት ተማሪዎች የሚራመድ ነው ‹‹ችግሩን በዝምታ ለመመልከት ኅሊናችም ሃይማኖታችንም አይፈቅድልንም›› /ብዙኃኑ ደቀ መዛሙርትና የደቀ መዛሙርት ምክር ቤት አባላት ለእምነትና ሥርዓት የሚቆረቆሩ መምህራንና ተማሪዎች ‹ማኅበረ ቅዱሳንና ፖሊቲከኞች ናችኹ› በሚል እንዲሸማቀቁ ይደረጋሉ (ዕንቊ፤ ቅጽ ፮ ቁጥር ፻፲፬፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን …

Image

የጋምቤላ ክልልን ሲመሩ ቆይተው ባለመስማማት የኮበለሉት የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፍነው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ዜናው በገለልተኛ ወገን ባይገለጽም ኖርዌይ በስደት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ በኢህአዴግ በጥብቅ የሚፈለጉ ሰው ነበሩ።

በመለስ ዜናዊ ውሳኔ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ በጅምላ የተከናወነውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ተቃውሞ በማሰማት የኮበለሉት አቶ ኦኬሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ከማምራታቸው በፊት ኬንያ እንደነበሩ፣ ከኬንያ ወደ ደቡብ ሱዳን ለምን እንደተጓዙ የዜናው ምንጮች በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል። ስማቸው እንዲደበቅላቸው የጠየቁ የጋምቤላ አስተዳደር ባልደረባ ለጎልጉል የአካባቢው ዘጋቢ እንደተናገሩት አቶ ኦኬሎ ደቡብ ሱዳን ሆቴል በተቀመጡበት መታፈናቸውን አረጋግጠዋል።

“ወያኔ እጅ ገብቷል” ሲሉ ያከሉት እኚሁ ሰው “አቶ ኦኬሎ ብረት በማንሳት ወያኔን ለመታገል ከተነሱ ጋር ተቀላቅለዋል በሚል ስማቸው መመዝገቡንና ወደ ደቡብ ሱዳን ማቅናታቸው በመታወቁ ህወሃቶች እጅ ሊወድቁ ችለዋል” ብለዋል። ምንጩ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ ኦኬሎ አክዋይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑበትን ምክንያት በርግጠኛነት ሃላፊነት ወስዶ የገለጸ ወገን አልተደመጠም። ኢህአዴግም ቢሆን የቀድሞውን ሹመኛ ስለመያዙ ይፋ ያደረገው ነገር የለም። ከደቡብ ሱዳን ቀውስ ጋር በተያያዘ የኑዌር ተወላጅ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጦር ጋር በመሰለፍ የሳልቫ ኪርን ሃይል ሲወጉ ከተገደሉ ወታደሮች መካከል የኢህአዴግን ሰራዊት መለያ የለበሱ ኑዌሮች መገኘታቸው ውዝግብ አስነስቶ እንደነበር ያመለከቱት ምንጭ “ደቡብ ሱዳን እየወጋት ካለው ኢህአዴግ ጋር አብራ የቀድሞውን የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳደር ከምድሯ ላይ እንዲታፈኑ መፍቀዷ ቅሬታ ያስነሳል” ብለዋል።

ከቤተሰባቸው ተነጥለው በስደት ከሚኖሩበት ኖርዌይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያመሩት የቀድሞው የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ደቡብ ሱዳን በህወሃት ሙሉ ቁጥጥርና ፈቃድ የምትንቀሳቀስ አገር መሆኗን እያወቁ ወደዛ ማቅናታቸውን ባሥልጣኑ “ታላቅ ጥፋት” ብለውታል። ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በቅርቡ አቶ ኦሞት ኦባንግ መኮብለላቸውና በብዙዎች ዘንድ አውሮጳ እንዳሉ ቢነገርም በትክክል ያሉበት አገር በይፋ አለመታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
goolgule.com/

የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችን ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው አይችልም። የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 ዜጎች ነፍጥ ሳይዙ የመሰባሰብ፣ ሕዝባዊ ሰላምዊ ሰልፎች የማድረግ፣ ፔትሽኖችን የማሰባሰብ ሙሉ […]