ኢትዮጵያ የበርካታ ባህልና የታሪክ ቅርሶች መገኛ ብትሆንም በአንፃሩ በተለያዩ መንገዶች ቅርሶቿ ከሀገር የሚወጡባቸዉ አጋጣሚዎች ብዙ ናቸዉ። እርግጥ ነዉ አንዳንድ ከሀገር የሚወጡ ቅርሶችን የማስመለስ እንቅስቃሴ አልፎ አልፎ ቢታይም አሁንም በርካታ የኢትዮጵያ ቅርሶች በተለያዩ ሃገራት ቤተ መዘክሮችና ግለሰቦች እጅ ላይ መገኘታቸዉ አልቀረም።

የተመድ የልማት መረሃ ግብር በምህፃሩ UNDP የ2014 ዓመታዊ ዘገባ ሥራና ማኅበራዊ ዋስትና፤ ለአፍሪቃ እድገት ያመጣል ይላል። ይህች አህጉር ግን አሁንም ቢሆን አደጋ የተደቀነባት ናት። ድርጅቱ በመጀመርያ ገጹ ይፋ ያደረገዉ ዘገባ ተስፋ ይሚሰጥ ነዉ።

በደቡባዊ ጣሊያን በሲሲሊ ግዛት የካታኒያ ከተማ ፖሊስ ከሊቢያ ወደጣሊያን ያቀኑ የነበሩ ስደኞችን የጫነች ጀልባ ዉስጥ ስደተኞችን ገድለዉ ባህር ዉስጥ በመወርወር የተጠረጠሩ አምስት ሰዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታዉቋል።

ናይጀሪያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሰዉ እስላማዊ ታጣቂ ቡድን ቦኮሃራም በሰሜን ምሥራቅ የሃገሪቱ ክፍል ከሚገኘዉ ቦርኖ ግዛት ከ200 የሚበልጡ ታዳጊ ሴት ተማሪዎችን አግቶ ከወሰደ 100 ቀን ሞላዉ። ከጎርጎሪዮሳዊዉ 2009ዓ,ም ጀምሮ ከ10,000 ሕዝብ በላይ ከፈጀዉ ከዚህ ቡድን እስካሁን ልጆቹን ማስለቀቅ ባለመቻሉ የናይጀሪያ የጦር ኃይል ይተቻል።

በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ በሱዳን ድንበር አቅራቢያ በአባይ ወንዝ ላይ የሚገነባዉ የኃይል ማመንጫ ግዙፍ ግድብ የአባይ ተፋሰስ ሃገራትን ብቻ ሳይሆን የበርካቶችን ቀልብ የሳበ ፕሮጀክት ነዉ። ግድቡ ሲጠናቀቅ 6,000 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል።

ሁለት ሣምንታትን ያስቆጠረው የእስራኤል ፍልስጥኤም ግጭት አሁንም ድረስ አልተቋረጠም። በፍልስጥኤም በኩል ከ600 በላይ፣ ከእስራኤል ወገን ደግሞ ወደ 30 የሚጠጉ አይሁዶች መገደላቸው ተዘግቧል። የአረብ ሊግ እና የአውሮፓ ኅብረትን ጨምሮ የተመድ ብሎም ዩናይትድ ስቴትስ ግጭቱን ለማስቆም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸው ተጠቅሷል።

የአውሮፓ ህብረት ፍርድ ቤት ባለፈው ሰሞን በጀርመን የቪዛ አሰጣጥ ህግ በተለይም ቱርኮችን በሚመለከተው ደንብ ላይ ያሳለፈው ብይን ቱርካውያንን አስደስቷል ። በአንፃሩ አንዳንድ የጀርመን ፖለቲከኞችን ቅር አሰንኝቷል ።

ደቡብ ሱዳን ከፍተኛ የረሃብ አደጋ ያሰጋታል ሲል የተመድ የሰብዓዊ እርዳታዎች አስተባባሪ ቢሮ አስጠነቀቀ። ድርጅቱ እንዳለው የደቡብ ሱዳን ሰብዓዊ ቀውስ እየተባባባሰ በመሄዱ ደቡብ ሱዳን ውስጥ በጣም በቅርቡ ከፍተኛ የረሃብ አደጋ ሊከሰት ይችላል።

በደቡብ ሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱ ተፈናቃዮች ቁጥር ከ200,000 በላይ መድረሱ ተነግሯል። ስደተኞቹ በተለይ ወደ ጋምቤላ የፈለሱ ሲሆን፤ የሚገኙበት ሁናቴ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በተመድ የሠብዓዊ ርዳታ አስተባባሪ በእንግሊዘኛ ምኅፃሩ ኦቻ ዋና ዳይሬክተር ጆን ጊንግ አስታውቀዋል።

በጎርጎሪዮሳዊዉ 2012ዓ,ም በ50 ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸዉ ሃገራት የተካሄደ ምርምር 12 በመቶ የሚሆኑት በወሲብ ንግድ የተሠማሩ ሰዎች በHIV ቫይረስ መያዛቸዉን ያመለክታል። በዚህ ተግባር ከተሠማሩት 50 በመቶዉ የሚሆኑት በቫይረሱ የተያዙባቸዉ አካባቢዎች ደግሞ ከሰሃራ በስተደቡብ የገኙት ሃገራት ናቸዉ።

የአውሮጳ ታላላቅ የእግር ኳስ ቡድኖች ጨዋታ በአዲስ መልክ ከመጀመሩ አስቀድሞ ቡድኖቹ በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች እየተዘዋወሩ የአቋም መለኪያ ግጥሚያዎችን በማከናወን ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን አዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ ከጋቦን አቻው ጋር እኩል ለእኩል ወጥቷል። ሌሎች ዜናዎችንም አካተናል

የእሥራኤል ጦር ትንሽቱን ሠርጥ ለቅቆ ቢወጣም ዙሪያ ገባዋን እንደከበባት ነዉ።ጋዛ ነዋሪዎችዋ እንደሚሉት ጣራ-የሌላት ትልቅ «እስር ቤት» ናት።በጀርመን የፍልስጤም አምባሳደር ኾሉድ ዳይቤስ ደግሞ የሕዝብ ጉረኖ-ይሏታል።

የብሔራዊው ሶሻሊስት ጦር መኮንኖች እአአ ሀምሌ 20፣ 1944 ዓም አዶልፍ ሂትለርን ለመግደል ያደረጉት ሙከራ ሰባኛ ዓመት ትናንት በበርሊን ፕሬዚደንት ዮአኺም ጋውክ እና የመከላከያ ሚንስትር ኡርዙላ ፎን ዴር ላየን ፣ እንዲሁም ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ታስቦ ዋለ።

ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ የአፍሪቃ ልማት ባንክ አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ አካሂዷል። በዚህ ጉባኤም ባንኩ የአፍሪቃ ሃገራት በምጣኔ ሃብት ረገድ የምርት ሰንሰለትን ማሳደግ እንደሚኖራባቸዉ ገምግሟል።

ሐምሌ 11፤ አርብ አዲስ አበባ አንዋር መስጊድ በተቀሰቀሰ ከፍተኛ ግጭት በርካታ ሰዎች መጎዳታቸዉ ተሰምቶአል። ተሰምቶአል። የአይን እማኞች ፖሊሶች እና የጸጥታ ኃይላት ናቸዉ ያሏቸዉ፤ በታላቁ አንዋር መስጊድ ለጁምዓ ሶላት የተሰበሰበዉን ምዕመን በያዙት ዱላ መደብደባቸዉንና ወንድ ሴት ሳይለዩ እያጋዙ መዉሰዳቸዉን ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ዉስጥ ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓት ጥርጊያ የሚከፍተዉ በነፃ የመደራጀት መብት በሕገ መንግስት ተደንግጎ እንቅስቃሴ ከተጀመረ ከሁለት አስርት ዓመታት ያላነሰ ጊዜ አስቆጥሯል። በዚህ ጊዜም በሥልጣን ላይ ያለዉን ማለትም ገዢዉን ፓርቲ ለመፎካከር በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች እየተቋቋሙ ፈርሰዋል።

የእስራኤል ጦር በጋዛ ሰርጥ ሟቾችን እና ቁስለኞችን ለማንሳት ለ2 ሰዓታት የተኩስ አቁም ተስማምቷል ተብሎ ነበር። ይሁንና የሀማስ ቡድን ቃሉን እንዳልጠበቀ ነው የሚነገረው። ሁለቱ ቡድኖች ባደረጉት የተኩስ አቁም ስምምነት የተነሳ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ወደ ስፍራው ሰርጎ ገብቶ ነበር።

የማሊ መንግሥት እና የቱዋሬግ ዓማፅያን በአልጀሪያ የሰላም ድርድር ጀምረዋል። ማሊ ውስጥ እኢአ በ 2012 ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከተካሄደ በኋላ እና በሀገሪቱ ሰሜናዊ ከፊል የሚንቀሳቀሱት ለዘብተኛ እና አክራሪ የቱዋሬግ ዓማፅያንም በመንግሥቱ አንፃር ትግላቸውን ካጠናከሩ በኋላ ማሊ መረጋጋት አልቻለችም።

ምሥራቅ ዩክሬይን ተመቶ የወደቀው የማሌዢያዉ የመንገደኞች ማመላለሻ አይሮፕላንን ተከትሎ፤ የዮክሬይን መንግሥት መፍቀሬ ሩሲያንን ወነጀለ። እንደ ዮክሬይን መንግስት፤ መፍቀሬ ሩስያ ተገንጣዮቹ ከአይሮፕላኑ የተገኙ የምስክር ማስረጃዎችን እያሸሹ እና እያጠፉ ይገኛሉ።

ካርቱም-ሱዳን ይደረግ የነበረዉ የሠወስትዮሾ ድርድር የተቋረጠዉ ኢትዮጵያና ግብፅ ባለመግባባታቸዉ ነበር።አሁን ግን የሁለቱ ሐገራት መሪዎች ባለፈዉ ወር ማላቦ-ኢኳቶሪያል ጊኒ ባደረጉት ዉይይት ድርድሩ እንዲቀጥል ተስማምተዋል

ትናንት ከሰዓት በኋላ በዩክሬን አየር ክልል ላይ ሲበር የወደቀው የማሌዥያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን በሚሳይል ሳይመታ አልቀረም መባሉ ማነጋገሩን ቀጥሏል ። የዩክሬን ባለሥልጣናት አደጋው እንደደረሰ በሰጡት መግለጫ አውሮፕላኑ አካባቢውን በተቆጣጠሩት በዩክሬን አማፅያን ከምድር ወደ ሰማይ በተተኮሰ ሚሳይል ነው የተመታው ሲሉ አስታውቀዋል ።

የሊቢያ ተቀናቃኝ ሚሊሽያዎች በሃገሪቱ የበላይነት ለመያዝ የሚያካሂዱት ትግል እንደቀጠለ ነው ። በተለይ በሊቢያው የትሪፖሊ አየር ማረፊያ የሚካሄደው ውጊያ ዛሬም አላበቃም። ከእሁድ አንስቶ የተዘጋው አውሮፕላን ማረፊያው ሥራ እስኪጀምር ድረስ ወራት ሊወስድ እንደሚችል ይገመታል በመገናና ብዙሃን ዘገባ መሰረት በውጊያው ሰዎች ተገድለዋል ፣ቆስለዋልም ።

የአውሮፓው ሕብረት አባል ሃገራት ፣ በብራሰልስ ያካሄዱት ጉባዔ እስከዛሬ ጧት ድረስ ቢጓተትም የ 28 ቱን ሃገራት ኮሚሽን ፤ በሚመጡት 5 ዓመታት እነማን እንደሚመሩት በመወሰን ረገድ ስምምነት ላይ ሳይደርስ መቅረቱ ተነገረ ። ጎርጎሪዮሳዊው 2014

ሠራተኞቹ እንደሚሉት የአንድ ወር ደመወዝ አልተከፈላቸውም። የዞኑ ሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በበኩሉ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ በአዋጅ የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅሞች አሠሪው በ7 ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያሟላ ስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቋል።

በጀርመን ሃገር የምንኖር አብዛኞች የዉጭ ሃገር ዜጎች በሃገሪቱ የፈለግነዉን ነገር ስለምናደርግ፤ አብዛኞች የዉጭ ተወላጆች ብንሆንም በዜግነት ጀርመናዊ በመሆናችን ከህዝቡ ጋር ፤ የቡድኑን ማልያ ለብሰን ባንዲራዉን አንግበን ጨዋታዉን በሚገባ በሃሳብ ተካፍለናል፤ አብረን ከቡድኑ ጋር ታመናል። ጀርመን ዋንጫዉን በመዉሰዱ በጣም ደስተኛ ሆነናል ይሉን፤

የጋዛ ግጭት ውዝግቡ ካለፈው አንድ ሳምንት ወዲህ ተጠናክሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል፣ ፍልሥጤማውያን ከጋዛ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን መተኮሳቸውን፣ የእስራኤል ጦርም ጋዛን ማጥቃታቸውን ቀጥለዋል። በዚሁ መሀል እስራኤል እና

ብራዚል ውስጥ በተካሄደው የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ላይ በፍጻሜ ግጥሚያ ጀርመን አርጀንቲናን አንድ ለባዶ አሸንፋ ለአራተኛ ጊዜ የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ባለቤት ከሆነች ይኸው ሁለት ቀናት አልፈዋል።

በፍጥረተ ዓለም ፣ በተለይ በዝች እኛ ከምንኖርባት ምድር (ፕላኔት) ውጭ በሌሎች ዓለማት እጅግ የrr,ቀቀ የራሳቸው ሥልጣኔ ያላቸው ፍጡራን ይኖሩ ይሆን? የሚታሰቡት ፍጡራን ቀለማቸው፣ አረንጓዴ፤ ይሁን ፤ ግዙፍ ይሁኑ ንዑስ፤ የሰው ቅርጽ ይኑራቸው የሌላ

ትናንት የጀርመኑ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር፤ ዛሬ ደግሞ የኢጣሊያዋ አቻቸዉ ፌደሪካ ሞግሔሪኒ እየሩሳሌም-እየደረሱ ተመልሰዋል።የፍልጤም ፕሬዝዳንት ማሕሙድ አባስ የግብፅና የቱርክ መሪዎችን ድጋፍ ለመጠየቅ ሁለቱን ሐገራት ይጎበኛሉ።ግድያዉ ቀጥሏል።

ኢትዮጵያ ውስጥ በአሸባሪነት ተጠርጥረዋል ተብለው የተያዙት 6 የኢንተርኔት ጸሐፍትና 3 ጋዜጠኞች ላይ ፖሊስ ሲያካሂድ የቆየው ምርመራ ተጠናቋል ቢባልም ምንም ዓይነት ውሳኔ እንዳልተሰጣቸው ጠበቃቸው አስታወቁ። ክሳቸው ዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት ካልገባም ነገ ክስ ለመመሥረት ማሰባቸውን ጠበቃቸው አቶ አምሃ መኮንን ዛሬ ለዶቼቬለ ተናግረዋል።

የቡድኑ አባላት በግልፅ መኪና ተሳፍረዉ ከበርሊን አዉሮፕላን ማረፊያ ዋናዉ ድግሥ-ሥፍራ ብራንደርቡርገር ቶር እስኪደርሱ ድረሥም በብዙ ሺሕ የሚቆጠር ሕዝብ በመንገዶች ግራና ቀኝ በመሆን የጀግና አቀባበል አድርጎላቸዋል

ዩናይትድ ስቴትስ ሁለት የጀርመን መንግሥት ሠራተኞችን ለስለላ መመልመሏ ከተደረሰበት በኋላ በበርሊን የአሜሪካን ማዕከላዊ የስለላ ድርጅት CIA ተጠሪ ሃገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ጀርመን መጠየቋ በሁለቱ ሃገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይ ጥላ አጥልቷል። የጀርመን መንግሥት ፖለቲከኞች ጀርመንም ለአፀፋ ስለላ እድትዘጋጅ እየጠየቁ ነው።

በኤቦላ ቫይረስ ወይም ተህዋሲ ከሚያዙ ሰዎች 90 በመቶዉ እንደማይተርፉ ነዉ መረጃዎች የሚያመለክቱት። ተህዋሲዉን የሚከላከልም ሆነ የሚያድን ክትባትም ሆነ መድሃኒት እስካሁን አልተገኘም። ኤቦላ ከዚህ ቀደም በዴሞክራቲክ ሪፑብሊክ ኮንጎ፣ ሱዳን፣ ጋቦን፣ አይቮሪኮስትና ዩጋንዳ በተደጋጋሚ ተከስቷል።

የጋዛ ግጭት ውዝግቡ ካለፈው አንድ ሳምንት ወዲህ ተጠናክሮ በመካሄድ ላይ ይገኛል፣ ፍልሥጤማውያን ከጋዛ ወደ እስራኤል ሮኬቶችን መተኮሳቸውን፣ የእስራኤል ጦርም ጋዛን ማጥቃታቸውን ቀጥለዋል። በዚሁ መሀል እስራኤል እና

የብራዚል፣ ሩስያ፣ ሕንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪቃ ርዕሳነ ብሔር እና መራሕያነ መንግሥታት ከሁለት ቀናት በፊት የተጠናቀቀውን የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ባስተናገደችው ብራዚል ዛሬ የሁለት ቀናት ጉባዔ ይጀምራሉ።