በቤንች ማጂ ዞን የማሌዥያ ኩባንያ ሠራተኞች አቤቱታ

ሠራተኞቹ እንደሚሉት የአንድ ወር ደመወዝ አልተከፈላቸውም። የዞኑ ሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በበኩሉ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ በአዋጅ የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅሞች አሠሪው በ7 ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያሟላ ስምምነት ላይ መደረሱን አስታውቋል።