ደራሲ መሥፍን ተቀበረ
መስፍን ሐብተማርያም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ የወግ ፀሐፊ ነበር።በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ወጎችን የፃፈና ያሳተመ፤ ተርጓሚ፤ የሥነ-ፅሁፍ ሐያሲ እና አዲስ አበባና አሥመራ ዩኒቭርስቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ያስተማረ የሥነ-ፅሁፍ ሰዉ ነበር።
መስፍን ሐብተማርያም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ የወግ ፀሐፊ ነበር።በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ወጎችን የፃፈና ያሳተመ፤ ተርጓሚ፤ የሥነ-ፅሁፍ ሐያሲ እና አዲስ አበባና አሥመራ ዩኒቭርስቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ያስተማረ የሥነ-ፅሁፍ ሰዉ ነበር።
ጀርመን በመከላከያና በስለላ ተቋሞቿ የሚሠሩ ሁለት ዜጎቿ ለዩናይትድ ስቴትስ መረጃ እንደሚያቀብሉ ከደረሰችበት ወዲህ ከአሜሪካ ጋ የነበራት ጠንካራ ግንኙነት ጥያቄ ላይ የወደቀ እንደመሰለ ነዉ።
በእሥራኤልና በጋዛው የፍልስጤማውያን ኃይል ፣ ሐማስ መካከል፣ በአየር ኃይል ድብደባና በሮኬት አጸፋዊ መልስ በተለይ በጋዛ የብዙ ሲቭሎች ሕይወት የተቀጠፈበት ፍልሚያ ከተጀመረ ሰባት ቀን ሆኖታል። ተኩስ ይቆም ዘንድ
ብራዚል ውስጥ በተካሄደው የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ፣ ትናንት ማታ በፍጽሜ ግጥሚያ ጀርመን አርጀንቲናን 1-0 አሸንፋ ለ 4ኛ ጊዜ የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ባለቤት ለመሆን በቅታለች።
እግር ኳስ አፍቃሪው የጀርመን ሕዝብ ከልሂቅ
እንደ ጦርነት፤ ግጭት፤ሽብሩ ሁሉ ድርድር፤ ዉይይት፤የድርድር ዕቅድ ቃል ተስፋዉ በርግጥ ያን ምድር አልተለየዉም።የቤራንዲዶት ዕቅድ፤የሮጀር ዕቅድ፤የአሎን ዕቅድ፤የካምፕ ዴቪድ ዉል፤የፈሕድ ዕቅድ፤ የማድሪድ ጉባኤ፤የኦስሎ ስምምነት፤ እየተባለ በሥልሳ-ሰባት ዓመት ዉስጥ ሰላሳ-አንድ የሠላም ዕቅዶች፤ ሥምምነቶች ወይም የመፍትሔ ሐሳቦች ተሠንዝረዋል።
20ኛዉ የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ዉድድር በጀርመን ድል ትናንት ተጠናቀቀ። ጀርመን ከምድቧ ማለትም ከምድብ G በአንደኝነት ነበር ወደቀጣዮቹ የግጥሚያ ዉድድሮች የተሻገረችዉ።
የጀርመን ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከእርጀቲና ቡድን ጋር ባደረገው የዋንጫ ግጥሚያ አርጀንቲናን አንድ ለባዶ በመርታት የዋንጫ ባለቤት ሆነ። እስከ በመደበኛው የጨዋታ ጊዜ ፍፃሜ ሁለቱ ቡድኖች ባዶ ለባዶ ስለነበሩ ጨዋታው መራዘም ግድ ነበረበት። ከዚያም በ113 ኛ ደቂቃ ማርዮ ገትስ ባስቆጠራት ግብ ነበር ጀርመናውያን ድል ሊቀዳጁ የቻሉት።
የአቶ አንዳርጋቸዉ መያዝ በተሰማ-በ16ኛዉ ቀን ባለፈዉ ማክስኞ የኢትዮጵያ መንግሥት በሚቆጣጠረዉ ቴሊቪዥን ጣቢያ ባሠራጨዉ መግለጫ ግን «የአሸባሪ ድርጅት አመራርና በጥብቅ የሚፈለጉ » ያላቸዉ አቶ አንዳርጋቸዉ እና ሌሎች ሰዎች መታሰራቸዉን አረጋግጧል::
በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ የብረቱ ትግል ከተጀመረ ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ በኋላም በብዙው የሀገሪቱ አካባቢ በቀድሞ ሙሥሊሞች የሴሌካ ዓማፅያን እና በአንፃራቸው በሚንቀሳቀሱት የፀረ ባላካ ሚሊሺያዎች መካከል ግጭቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ሀገሪቱም ከግጭት አዙሪት መውጣት ተስኗታል። መንግሥትም ቀውሱን የማስቆም አቅም ተጓድሎት ይገኛል።
የአውሮጳው ሕብረት በደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ላይ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት ፣ እየጣሱ ነው ባላቸው 2 የጦር አዛዦች ላይ የጉዞ እገዳ ጣለ።
በጀርመን መዲና በበርሊን በሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ፣ የፀጥታ ክፍል የበላይ አዛዡ ፣ ራሱን በቻለው ጽ/ቤታቸው ተግባራቸውን ሲያከናውኑ መቆየታቸው እሙን ነው።
በዉጭ የሚኖሩ የአፋር ተወላጆች መገናኛ መረብ የተሰኘዉ ስብስብ በሶማሌ ተወላጆችና በአፋሮች መካከል በመሬት ይገባኛል ምክንያት የሚነሳዉን ግጭት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ትኩረት አልሰጠዉም ሲል ወቀሰ።
ከ15 ቀናት በፊት በማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ በተደረገዉ የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ የሰብዓዊና የሕዝብ መብት ጉዳይ ላይ በተወያዩበት ርእስ ለማብራሪያ ያህል በአፍሪቃ ሕብረት የሕግ መምሪያ ኃላፊዉ ፕሮፌሰር ቪንሰንት ሜኺዮሌ መግለጫ ሰጥተዋል።
ለመሆኑ ወጣቱ ፆሙን እንዴት ይጾማል? ያፈጥራልስ? የረመዳን ጾም ከገባ ሁለት ሳምንት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ነው የቀሩት። በዚህ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በፆም ፀሎት የሚታሰበው የቅዱስ ወር ለማን ም ሙስሊም ቢሆን ግዴታ ነው።
የሶማልያ ጠ/ሚንስትር አብዲዋሊ ሼክ አህመድ ሙሐመድ፣የብሔራዊ ደኅንነት ድርጅት ሹም የነበሩትን በሺር ጉቤንና የፖሊሱን ኃይል አዛዥ አብዲከሪም ዳሒርን በመሻር በምትካቸው፤ በብሪታንያ የሶማልያ አምባሰደር የነበሩት
በብራዚል በመካሄድ ላይ ባለውና ፣ የፊታችን እሁድ በሚያከትመው የዘንድሮው የዓለም የአግር ኳስ ዋንጫ ውድድር፣ ትናንት ማታ በተካሄደው ሁለተኛው የግማሽ ፍጻሜ ውድድር አርጀንቲናና ኔደርላንድ በ9o ው ደቂቃ ጨዋታና 30 ደቂቃም ተጨምሮ ባለመሸና
ተማርን የሚሉ ሰዎች አማርኛን ቋንቋ ዉስጥ አንዳንድ የእንግሊዘኛ ቋንቋን እየሰነቀሩ ቋንቋዉ እንዲመነምን እየዳረጉ ናቸዉ ይላሉ ምሁራን። በሌላ በኩል ሃሳብን ለመግለፅ አማርኛ ቋንቋ አስቸጋሪ ነዉ የሚሉም አልጠፉም!የባዕድ ቃላትን የመዋስ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ፤ እንግሊዘኛ ቃላትን ጣል እያደረጉ የመናገር አባዜ የተለመደ ይመስላል
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ መንግሥት ለፖለቲካ ፓርቲዎች በሚሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ላይ አድሎአዊ አሰራር ይታይበታል፣ ሕጋዊም አይደለም ሲል ቅሬታውን አሰማ።
የእስራኤል የጦር አዉሮፕላኖች በፍልስጤም ግዛት ጋዛ ላይ ዛሬ ደጋግመዉ ባደረሱት ድብደባ የተጎዱ ሲቪሎች ቁጥር መጨመሩን ዘገባዎች ያመለክታሉ። የተመድ የፀጥታዉ ምክር ቤት እስራኤል ከሃማስ ጋ የገጠመችዉን ፍጥጫ ለመመልከት አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋል።
እ ጎ አ ካለፈው ጥር ወር መግቢያ ወዲህ፣ በዩናይትድ ስቴትስ ፣ ኒው ዮርክ፤ ቢል ደ ብላሲዮ የተባሉት የዴሞክራቱ ፓርቲ አባል የከተማይቱን የከንቲባነት ሥልጣን ከመረከባቸው በፊት፤ ከዚያ በፊት ፣ 3 ጊዜ ተመርጠው እ ጎ አ ከ ጥር 1፤ 2002
የመን ለኢትዮጵያ መንግሥት አሳልፋ የሰጠቻቸው የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ፓርቲ ዋና ፀሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በኢትዮጵያ እሥር ቤት ውስጥ ይበደላሉ ብሎ እንደሚፈራ ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታወቀ ።
ደቡብ ሱዳን ሶስተኛ ዓመት የነፃነት በዓሏን ዛሬ አከበረች ።ርዕሠ-ከተማ ጁባ ዉስጥ በከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ በተከበረው በዚሁ የነፃነት በዓል ላይ የደቡብ ሱዳን መሪ ሳልቫ ኪር ፣ተቀናቃናቸው የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር የሰላም ንግግሩን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል ።
የግብፅ መንግሥት በነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጭማሬ አደረገ። የሀገሪቱ የዜና አገልግሎት አል- አህራም እንደዘገበው ግብፃዉያን ከዛሬ ጀምሮ በየነዳጅ ማድያው ከ40 እስከ 80 በመቶ ጭማሪ ገንዘብ በማዉጣት ነዳጅ ይሸምታሉ።
በአጓጊነቱ የቀጠለዉ ብራዚል ላይ እየተካሄደ ያለዉ የዓለም የእግር ኳስ ግጥምያ ዛሬ በአስተናጋጅ ሀገር ብራዚል እና በጀርመን መካከል ጀምሮአል። ግጥምያዉ በጀርመን በጉጉት እየተጠበቀ ነዉ
በአጓጊነቱ የቀጠለዉ ብራዚል ላይ እየተካሄደ ያለዉ የዓለም የእግር ኳስ ግጥምያ ዛሬ በአስተናጋጅ ሀገር ብራዚል እና በጀርመን መካከል ጀምሮአል። ግጥምያዉ በጀርመን በጉጉት እየተጠበቀ ነዉ
ከግማሽ የሚበልጠዉ የየመን ሕዝብ ሠብአዊ ርዳታ እንደሚያሥፈልገዉ የተባበሩት መንግሥታት የሠብአዊ ርዳታ ማስተባባሪያ ቢሮ (OCHA በምሕፃሩ) እስታወቀ።OCHA እንደሚለዉ ለችግር ለተጋለጠዉ የመናዊ እስቸኳይ ርዳታ ካልደረሰ ለመገመት የሚከብድ ሠብአዊ ድቀት መከሰቱ አይቀርም።
ከግማሽ የሚበልጠዉ የየመን ሕዝብ ሠብአዊ ርዳታ እንደሚያሥፈልገዉ የተባበሩት መንግሥታት የሠብአዊ ርዳታ ማስተባባሪያ ቢሮ (OCHA በምሕፃሩ) እስታወቀ።OCHA እንደሚለዉ ለችግር ለተጋለጠዉ የመናዊ እስቸኳይ ርዳታ ካልደረሰ ለመገመት የሚከብድ ሠብአዊ ድቀት መከሰቱ አይቀርም።
በአፍሪቃ ኅብረት ትጥቅ ለማስፈታት አዲስ አበባ አፍሪቃ ኅብረት የተካሄደዉ ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
በአፍሪቃ ኅብረት ትጥቅ ለማስፈታት አዲስ አበባ አፍሪቃ ኅብረት የተካሄደዉ ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
የብሪታኒያ መንግሥት ዜጋው አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከየመን ለኢትዮጵያ ተላልፈው መሰጠታቸው በእጅጉ እንዳሳሰበው ለኢትዮጵያ መንግሥት ማንሳቱን አስታወቋል። የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የመን ላይ መያዝና ወደ ኢትዮጵያ መወሰድን በመቃወም ዛሬ በተለያዩ ሐገራት ሠልፍ ተደርጓል።
አንድ የጀርመን የስለላ መሥሪያ ቤት ባልደረባ ለአሜሪካጠቃሚ መረጃ በመስጠት ንም በመሰለል መጠርጠሩ የጀርመንን መንግሥትና ህዝብ አስቆጥቷል ። የጀርመን መንግሥት የስለላው እውነትነት ከተረጋገጠ ሃገሪቱ በአሜሪካን ላይ ያላትን እምነት አደጋ ላይ እንደሚጥል አስጠንቅቋል ።
በጎርጎሪዮሳዊዉ 2000 ዓ,ም የታቀደዉ የአምዓቱ የልማት ግብ በዋነኝነት በ15ዓመታት ዉስጥ በመላዉ ዓለም ያለዉን ድህነትና ረሃብ በግማሽ ለመቀነስ ያለመ ነዉ። የተመድ እንደሚለዉ የተጀመረዉ ጥረት ባለበት ሁኔታ ከቀጠለ አብዛኞቹ የታለሙት እቅዶች እስከ መጪዉጎርጎሪዮሳዊ ዓመት ማብቂያ ድረስ ሊደረስባቸዉ ይችላል።
ጀርመን አንድ ዜጋዋ በሀገሪቱ የስለላ ተቋም ተቀጥሮ ለዩናይትድ ስቴትስ እንደሚሰልል ከደረሰችበት ወዲህ ጉዳዩ የሀገሪቱን ከፍተኛ የፖለቲካ ኃይሎች እያነጋገረ ነዉ። በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለመሰላለልን ስምምነት ለመፈረም ዝግጁ አለመሆኗን ዋሽንግተን ባለፈዉ ሳምንት መገባደጃ ላይ አመልክታለች።
የኬንያ የፖለቲካ ተቃዋሚዎች መንግሥትን በመንቀፍ ህዝብ ለተቃዉሞ እንዲወጣ ጥሪ ያቀርባሉ። በሀገሪቱ የሚታየዉ የፖለቲካ ልዩነትና መቃቃር፤ የጎሳ ግጭት ቀዉስ አጥልቶበታል። በኬንያ በሚገኙት የተለያዩ ጎሳዎች መካከል የሚታየዉ ቀዉስ እየሰፋ መጥቶአል።
የአዉሮጳ ኅብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የመን-ርዕሠ ከተማ ሰነዓ አዉሮፕላን ማረፊያ ተይዘዉ ወደ ኢትዮጵያ ተግዘዋል የተባሉትን የግንቦት ሰባት ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ፅጌን ለማስፈታት እንዲጥሩ GESELLSCHAFT FÜR BEDROHTE VÖLKER የተሰኘዉ የጀርመን የመብት ተሟጋች ድርጅት ጠየቀ።
የዘመነ-ዘመናቱ ፀሎት፤ ድርድር፤ የዲፕሎማሲ ጥረት ብዙዎች ብዙ ጊዜ እንዳሉት«ከልብ እና ፍትሐዊ» ሥላልሆነ—ሠላም የለም።ከልብ የሚደረገዉ ፖለቲካዊ መደባባት፤ ወታደራዊ መገዳደል፤እና መበቃቀል ግን ጥንትም-ድሮም ዘንድሮም አለ።
የአንድን ሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን መሠረተ ልማት ዘርግቶ በአቅድ መንቀሳቀስ የሚፈለግና የተለመደም ጉዳይ ቢሆንም፣ የሚሠምረውም ሆነ ውጤታማ ሆኖ መገኘት የሚቻለው ፣ ሥራ በየረድፉ በሙያ በሰለጠ የሰው ጉልበት በተቀላጠፈ ሁኔታ ሲከናወን ነው።
በግብፅ የሙሥሊም ወንድማማችነት ማህበር የቀድሞው ፕሬዚደንት መሀመድ ሙርሲ ከሥልጣን የተወገዱበትን አንደኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ግዙፍ ተቃውሞ ተካሄደ። የሴቶች ዓለም አቀፍ የምክር ቤት መድረክ አባላት ሴቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚያጋጥማቸው የፀጥታ ችግር አንፃር ጠንካራ ርምጃ እንዲወሰድ ጥሪ አስተላለፈ።
የግብፅ መንግሥት በነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጭማሬ አደረገ። የሀገሪቱ የዜና አገልግሎት አል- አህራም እንደዘገበው ግብፃዉያን ከዛሬ ጀምሮ በየነዳጅ ማድያው ከ40 እስከ በ80 መቶ ጭማሪ ገንዘብ በማዉጣት ነዳጅ ይሸምታሉ።
በተንቀሳቃሽ ስልክ እና በኢንተርኔት አማካይነት በቀላሉ የሚገኙ መረጃ እና አገልግሎቶችን ተጠቅሞ እውቀትን እንዴት ማዳበር ይቻላል የሚሉ ጥያቄዎች ከሰኞ እስከ እሮብ በቆየው እና ዶይቸ ቬለ ባዘጋጀው ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን መድረክ የተነሱ ጥያቄዎች ናቸው።
ፓርቲው በቅርቡ በሰጠው መግለጫ በአባላቱና በአመራር አካላት እንዲሁም በደጋፊዎቹ ላይ የመብት ጥሰት መፈፀሙንና ኢ ህገ መንግሥታዊ እርምጃዎች መወሰዳቸውንም አስታውቋል ።
የእስራኤል ፖሊስ ኢየሩሳሉም ዉስጥ ከፍልስጤም የተቃዉሞ ሰልፈኞች ጋ መጋጨቱ ተሰማ። ፍልስጤማዉያኑ በፅንፈኛ እስራኤላዉያን ሳይገደል እንዳልቀረ በሚገመተዉ ፍልስጤማዊ ታዳጊ ወጣት ቀብር የተሰባሰቡ እንደሆኑ አሶሲየትድ ፕረስ ከስፍራዉ ዘግቧል።
የጀርመን መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል በያዝነዉ ሳምንት መጨረሻ ቻይናን ይጎበኛሉ። ሜርክል የጀርመን ከፍተኛ የንግድና ባንክ ባለስልጣናትን አስከትለዉ ለአራት ቀናት በቻይና በሚያደርጉት ጉብኝት ከፕሬዝደንት ሺ ቺ ፒንግና ከጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪጂንግ ጋ ይነጋገራሉ።