የአንዋር መስጊድ ተቃዉሞ

ሐምሌ 11፤ አርብ አዲስ አበባ አንዋር መስጊድ በተቀሰቀሰ ከፍተኛ ግጭት በርካታ ሰዎች መጎዳታቸዉ ተሰምቶአል። ተሰምቶአል። የአይን እማኞች ፖሊሶች እና የጸጥታ ኃይላት ናቸዉ ያሏቸዉ፤ በታላቁ አንዋር መስጊድ ለጁምዓ ሶላት የተሰበሰበዉን ምዕመን በያዙት ዱላ መደብደባቸዉንና ወንድ ሴት ሳይለዩ እያጋዙ መዉሰዳቸዉን ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።