የአሜሪካንና የጀርመን የስለላ ቅሌትና ተፅእኖው

ዩናይትድ ስቴትስ ሁለት የጀርመን መንግሥት ሠራተኞችን ለስለላ መመልመሏ ከተደረሰበት በኋላ በበርሊን የአሜሪካን ማዕከላዊ የስለላ ድርጅት CIA ተጠሪ ሃገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ጀርመን መጠየቋ በሁለቱ ሃገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይ ጥላ አጥልቷል። የጀርመን መንግሥት ፖለቲከኞች ጀርመንም ለአፀፋ ስለላ እድትዘጋጅ እየጠየቁ ነው።