የተመድ ባለስልጣናት የስደተኞች ጉብኝት በጋምቤላ

በደቡብ ሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱ ተፈናቃዮች ቁጥር ከ200,000 በላይ መድረሱ ተነግሯል። ስደተኞቹ በተለይ ወደ ጋምቤላ የፈለሱ ሲሆን፤ የሚገኙበት ሁናቴ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በተመድ የሠብዓዊ ርዳታ አስተባባሪ በእንግሊዘኛ ምኅፃሩ ኦቻ ዋና ዳይሬክተር ጆን ጊንግ አስታውቀዋል።